query_id
stringlengths 32
32
| passage_id
stringlengths 32
32
| query
stringlengths 2
182
| passage
stringlengths 137
1.88k
| label
int64 0
1
|
---|---|---|---|---|
84a972eaf2507be7e795f02ff5b8b793
|
5021d902da812b2ae3f1ddd89bfab1d8
|
የኢትስዊች ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከኃላፊነታቸው ለቀቁ
|
ላለፉት በርካታ ዓመታት የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣንን ሲመሩ ቆይተው ከኃላፊነታቸው የተነሱ አመራሮች ስላከናወኗቸው ተግባራትና ለምን ከኃላፊነታቸው ሊነሱ እንደቻሉ፣ መንግሥት ማጣራት እንደሚጀምር ተጠቆመ፡፡የሪፖርተር ምንጮች እንደገለጹት መንግሥት ባለሥልጣኑን በሚመለከት ማጣራት እንደሚጀምር የገለጸው፣ ኢሕአዴግ በጥልቀት ለመታደስ ማድረግ ስለሚገባው ጉዳዮች አስመልክቶ በጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ሰብሳቢነት ለሦስት ቀናት በሚኒስትሮች ምክር ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ፣ ከፌዴራል ተቋማት ለተገኙ ተወካዮች ማብራሪያ በተሰጠበት ወቅት ነው፡፡በተለያዩ የመንግሥት ተቋማት ኃላፊ ሆነው የሚሾሙ ባለሥልጣናት ከኃላፊናቸው ሲነሱም ሆነ በከፍተኛ ሹመት ወደ ሌላ ሲዘዋወሩ ለሕዝብ ለምን በግልጽ እንደማይነገር ከተሰብሳቢዎቹ ጥያቄ ከተነሳ በኋላ፣ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን አመራሮች ከኃላፊነታቸው ስለመነሳታቸው እንጂ፣ በምን ምክንያትና ስለቀጣዩ ዕርምጃ አለመገለጹ እንደማሳያ መነሳቱን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ተሰብሳቢዎቹ ላነሱት ጥያቄ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም በሰጡት አስተያየት፣ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን አመራሮች ከኃላፊነታቸው ሲነሱ የምሥጋናና የውዳሴ ደብዳቤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰጣቸው ቢሆንም፣ መንግሥት ግን የማጣራት ሥራ እንደሚጀምር መናገራቸውን ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን በደንብ ቁጥር 7/1990 መሠረት የተቋቋመ ተቋም ሲሆን፣ በወቅቱ የመንገድ ሽፋን 5.52 በመቶ ነበር፡፡ በ2007 በጀት ዓመት 19.8 በመቶ መድረስ ችሏል፡፡ ባለሥልጣኑን በዋና ሥራ አስኪያጅነት ኢንጂነር ፍቃዱ ኃይሌ ለ14 ዓመታት መርተውታል፡፡ኢንጂነር ፍቃዱ ግልጽ ባልሆነ ምክንያት በነሐሴ ወር 2008 ዓ.ም. ከምክትል ሥራ አስኪያጁ አቶ ግደይ ህሽ ጋር ከኃላፊነታቸው መነሳታቸው ይታወሳል፡፡
| 0 |
9234db6d3f3f4e492851bedef95275ea
|
91c648662776c74138e8f78ac99844e6
|
ኻርቱም አይሮፕላን ጣቢያ ላይ ተይዛ የምትገኘው መርየም የሕያ እንድትለቀቅ ተጠየቀ
|
የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ እና ኢትዮጵያ ውስጥ ይፋ መንግሥታዊ ጉብኝት እያደረጉ ያሉት የግብፅ ፕሬዚዳንት አብዱልፋታህ ኤል-ሲሲ የሃገሮቻቸውን ግንኙነት፣ አካባቢያዊና አህጉራዊ የፀጥታ ጉዳዮችን በተመለከተ ጠቅለል ያሉ ጉዳዮችን እንዲሁም የኅዳሴ ግድብ ግንባታን አስመልክቶ መወያየታቸውን ለጋዜጠኞች አስታውቀዋል፡፡መሪዎቹ በአዲስ አበባው ብሔራዊ ቤተመንግሥት ዛሬ /ማክሰኞ፤ መጋቢት 15/2007ዓ.ም/ በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የያዙት አቅጣጫ ትክክለኛ ነው ብለው እንደሚያምኑና ትናንት ኻርቱም ላይ የተፈራረሙት ሠነድም ከፍተኛ ግምት የሚሰጠው መሆኑን ተናግረዋል፡፡“…የታላቁን ኅዳሴ ግድብ በተመለከተ ወንድም ከሆነው ከሱዳን ሕዝብ ጭምር ትናንት ኻርቱም ላይ የተፈራረምነው የመርኅ ስምምነት በሦስቱ ሃገሮች መካከል ስለሚኖር የጠነከረ ግንኙነት በትክክለኛ አቅጣጫ የተደረገ እርምጃን እንደሚያመለክት እናምናለን…” ብለዋል የግብፁ ፕሬዚዳንት፡፡የኢትዮጵያው ኃይለማርያም ደሣለኝም “…ያሣካው ዋናው እርምጃ በሁለታችንም በኩል የታየው ፖለቲካዊ ፍቃደኝነትና ቁርጠኝነት ነው፤ ይህ ደግሞ ለሁለቱም ሕዝቦቻችን ጥቅም ስንል እና በሁለቱ ሕዝቦች መካከል ያለውን ታሪካዊ ትሥሥር ለማጠናከር ያደረግነው ነው…” ብለዋል፡፡በሌላ በኩል ደግሞ ግብፅ ወደ እንዲህ ዓይነቱ የትብብር መንፈስ ፊቷን ያዞረችው ከዚህ ቀደም ለዘመናት ስትከተለው የቆየችው መንገድ ከእንግዲህ እንደማያስኬድ መሪዎቿ በመገንዘባቸው ነው ሲሉ አንድ ኢትዮጵያዊ የአፍሪካ ቀንድ ጉዳዮች ተመራማሪ ለቪኦኤ በሰጡት ትንተና አመልክተዋል፡፡ለዝርዝሩ የተያያዙትን የድምፅ ፋይሎች ያዳምጡ፡፡
| 0 |
f7b4381e9a373a56d683ab8ef2bfd620
|
f7b4381e9a373a56d683ab8ef2bfd620
|
አሜሪካ በወታደራዊ ሃይል ከአለማችን አገራት 1ኛ መሆኗ ተነገረ
|
የ2019 የአለማችን አገራት ወታደራዊ ሃይል አቅም ሪፖርት ከሰሞኑ ይፋ የተደረገ ሲሆን 2 ሚሊዮን ያህል የሰው ሃይልና እጅግ ከፍተኛ የጦር መሳሪያ አቅም ያላት አሜሪካ፣ ከአለማችን አገራት በ1ኛ ደረጃ ላይ መቀመጧ ተነግሯል፡፡137 የአለማችን አገራት የተካተቱበትንና የሰው ሃይል፣ የጦር መሳሪያ አቅም፣ የኢንዱስትሪ ብቃትና የፋይናንስ አቅምን ጨምሮ የተለያዩ 55 ያህል መስፈርቶችን በመጠቀም በተደረገ ግምገማ፣ ባለፈው ሳምንት ይፋ የተደረገውን የ2019 አለማቀፍ ወታደራዊ አቅም ሪፖርት ጠቅሶ ያሁ ኒውስ እንደዘገበው፤ 716 ቢሊዮን ዶላር የመከላከያ በጀት፣ 13 ሺህ 398 አውሮፕላኖች፣ 2 ሺህ 362 ተዋጊ ጀቶች፣ 6 ሺህ 287 ታንኮችና ሌሎች በርካታ የጦር መሳሪያዎች ያሏት አሜሪካ በአንደኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች:: በአመቱ የአገራት ወታደራዊ አቅም ደረጃ፣ ሩስያና ቻይና በሁለተኛና በሶስተኛነት ሲከተሉ፤ ህንድ፣ ፈረንሳይ፣ ጃፓን፣ ደቡብ ኮርያ፣ እንግሊዝ፣ ቱርክና ጀርመን እንደ ቅደም ተከተላቸው፣ ከአራተኛ እስከ አስረኛ ያለውን ደረጃ የያዙ የአለማችን አገራት መሆናቸውንም ዘገባው አመልክቷል፡፡
| 1 |
40b958b74cdb7cc2a6cea7882dc93fbc
|
b27756d9d0a929ca71b6cf68bf472ac8
|
በህዝበ ውሳኔው ላይ 5.6 ሚሊዮን መራጮች ተሳትፈዋል
|
የጋና ፕሬዝዳንት ናና አኩፎ አዶ በድጋሚ ምርጫ በማሸነፋቸው ተጨማሪ የአራት ዓመት የስልጣን ጊዜ እንዳገኙ የሀገሪቱ የምርጫ ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡የ 76 ዓመቱ አኩፎ አዶ 51 ነጥብ 6 በመቶ ድምጽ በማግኘት ማሸነፋቸውን የሀገሪቱ የምርጫ ኮሚሽን ሃላፊ ጄን ሜንሳ ገልጸዋል።ተቀናቃኛቸው ናሽናል ዴሞክራቲክ ኮንግረስ መሪ ጆን ማሃማ 47 ነጥብ 4 በመቶ ድምጽ ማግኘታቸውንም የኮሚሽኑ ሃላፊ አስታውቀዋል።በ 38 ሺህ የምርጫ ጣቢያዎች 17 ሚሊየን መራጮች መሳተፋቸው የተገለጸ ሲሆን ፣ መራጮች ለብሔራዊ ፓርላማ 275 የሕግ አርቃቂዎች መምረጣቸውም ሲጂቲኤን አስነብቧል፡፡አፍሪካ ህብረት፣ ኢኮዋስ እና የምዕራብ አፍሪካ የተባበሩት መንግስታት ጽህፈት ቤት በጋራ በሰጡት መግለጫ የጋና ህዝብ ምርጫውን በሰላማዊ መንገድ በማከናወኑ አመስግነዋል።
| 0 |
28c19fbae2cb5e9a84ca833119363d9d
|
493018c948e823e1ca84a0140ca2b42c
|
የኢትዮጵያ ዋንጫ ዘንድሮ አይደረግም
|
በአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌደሬሽን ስር የሚደረጉ 5 የመዲናይቱ ውድድሮች በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ቀሪዎቹ መርሃ ግብሮች ዘንድሮ እንደማያከናውኑ ተገልጿል።ይህ ፌደሬሽን የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ (ሲቲ ካፕ) በዓመቱ መጀመሪያ ከማድረጉ ጎን ለጎን ዓመታዊ ውድድሮችን በየጊዜው እያከናወነ ይገኛል። በዚህም ፌደሬሽኑ በከፍተኛ የወንዶች እና ሴቶች ዲቪዚዮን፣ በአንደኛ ዲቪዚዮን፣ ከ17 ዓመት በታች ኤም አራ አይ ያለው እንዲሁም የሌለው፣ ከ15 ዓመት በታች እና ከ13 ዓመት በታች እየተደረጉ የነበሩ ውድድሮቹን በወረርሽኙ እና በሃገሪቱ በታወጀው አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አማካኝነት ማገዱ ይታወቃል።ይህንን ተከትሎ ትላንት ስለ ውድድሩ ቀጣይ እጣ ፈንታ ውይይት ያደረጉት የፌደሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ አባላት ውድድሩ በዚህ ዓመት እንደማይመለስ ተነጋግረው ውሳኔ አሳልፈዋል። ሶከር ኢትዮጵያ ከስራ አስፈፃሚዎቹ ባገኘው መረጃ ውድድሮቹ ዘንድሮ ባይደረጉም ቀጣይ ዓመት ላይ በሚኖረው የወረርሽኙ ሁኔታ መነሻነት ቀጣይ ውሳኔዎች እንደሚሰጡ ተገልጿል። በዚህም የውድድሮቹ አሸናፊዎች በቀጣይ ከወረርሽኙ ጋር በሚመጡ የሃገር ሁኔታዎች ታሳቢነት ስራ አስፈፃሚዎች ውሳኔዎችን እንደሚያስተላልፉ ተነግሯል።
| 0 |
6c825986f4c2ab4b7ac9599acc82de75
|
a782583b3bce2c65afc4e83add814160
|
በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የትላንት ጨዋታዎች ደደቢት በድል ጉዞው ሲቀጥል ባንክ ደረጃውን አሻሽሏል
|
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ማጠቃለያ ውድድር በሀዋሳ መካሄዱን ቀጥሎ የምድብ ጨዋታዎች ፍፃሜያቸውን አግኝተዋል፡፡08:00 ላይ ደደቢት ቅዱስ ጊዮርጊስን ገጥሞ 3-1 በማሸነፍ በ100% የማሸነፍ ሪኮርድ ወደ ግማሽ ፍፃመሜው ተቀላቅሏል፡፡የደደቢትን የድል ግቦች ልማደኛዋ ሎዛ አበራ (2) እና ነህምያ ሲያስቆጥሩ የፈረሰኞቹን ብቸኛ ግብ ቱቱ በላይ ከመረብ አሳርፋለች፡፡ውጤቱን ተከትሎ ደደቢት በሙሉ 12 ነጥብ ወደ ግማሽ ፍፃሜ ሲያልፍ በማሸነፍ ላይ ብቻ የተመሰረተ እድል ይዞ የገባው ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ ግማሽ ፍጻሜ ሳያልፍ ቀርቷል፡፡ መከላከያ ደደቢትን ተከትሎ ያለፈ ቡድን ሆኗል፡፡10:00 ላይ መውደቃቸውን ያረጋገጡት ሲዳማ ቡና እና አርባምንጭ ከተማ ባደረጉት ጨዋታ ሲዳማ 4-1 አሸንፏል፡፡ ሰአዳ ኡስማን ሶስት ግቦች አስቆጥራ ሐት-ትሪክ ስትሰራ አስራት አለሙ ቀሪዋን ግብ አስቆጥራለች፡፡ የአርባምንጭን ብቸኛ ግብ መሰረት ማቲዮስ አስቆጥራለች፡፡የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታዎች በመጪው ሀሙስ በአዲሱ የሀዋሳ ኢንተርናሽናል ስታድየም ሲካሄዱ 08:00 ላይ ደደቢት ከ ዳሽን ቢራ ፤ 10:00 ላይ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ መከላከያ ይፋለማሉ፡፡የከፍተኛ ግብ አግቢነቱን ሎዛ አበራ በ8 ግቦች ስትመራ ሽታዬ ሲሳይ በ5 ትከተላለች፡፡
| 0 |
d825242f30ad1ad6820f882a8ea569db
|
d825242f30ad1ad6820f882a8ea569db
|
የኡክራይን ፕሬዚዳንት በወታደሮች ሞት ምክንያት ቩላዲሚር ፑቲንን አናገሩ
|
"ወድያውኑ ነው ስልክ የደወልኩላቸው፤ ይህ ወደ ሰላም ሊያቀርበን አይችልም አልኳቸው" ሲሉ ዘለንስኪ ዛሬ ኪቭ በተደረገ ጋዜጣዊ ጉባዔ ተናግረዋል። በሞስኮ የሚደገፉት ተገንጣዮች "ህዝባችንን መግደል እንዲያቆሙ" እንዲነግሯቸው ለፑቲን ጥሪ አድርጊያለሁ ሲሉም አክለዋል።ፑቲን የገቡላቸው ቃል እንዳለና ቆይቶ የሚገልጽ መሆኑን የኡክራይኑ ፕሬዚዳንት ገልፀዋል። ሞስኮ ስለተባለው የስልክ ጥሪ የተናገረቸው ነገር የለም።የኡክራይን የመከላከያ ሚኒስቴር ባወጣው መግልጫ መሰረት ተገንጣዮቹ ትላንት በዶኔትስክ ክልል በሚገኘው ወታደራዊ ሰፈር ላይ ተኩስ ከፍተዋል። ፈንጂ ተኳሾችን፣ መትረየሶችንና ጠመንጃዎችን ተጠቅመው እንደተኮሱ የመከላከያው ሚኒስቴር ገልጿል።
| 1 |
2030abd765dfa01a64def90641493ed4
|
4c16fbdcf8d400d16b07dff86c4dffd3
|
የህዳሴ ግድብ በሱዳን ሲፈጠር የነበረን ጎርፍ በማስቀረት ተጨማሪ የእርሻ ቦታ እንደሚያስገኝላቸው የሱዳን አርሶ አደሮች ተናገሩ
|
ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 13/2013 (አብመድ) በአማራ ክልል ግብርና ቢሮ የአትክልትና ፍራፍሬ ዳይሬክቶሬት የአትክልት ባለሙያ ተፈራ ሰይፉ እንደተናገሩት በ2013 ዓ.ም የመስኖ እርሻ 248 ሺህ ሄክታር ማሳ በዘር ይሸፈናል፡፡ በመስኖ እርሻ ልማት 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን አርሶ አደሮች በመሳተፍ 37 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማገኘት እቅድ እንደተያዘም ነው የተናገሩት፡፡ አርሶ አደሮች ገበያ ተኮር ሰብሎች ላይ ትኩረት በማድርግ የመስኖ ስራቸውን እንዲያከናውኑ አቅጣጫ ተይዟል ያሉት አቶ ተፈራ 80 በመቶ የሚሆን ማሳ በአተክልትና ፍራፍሬ እንደሚሸፈን አስረድተዋል፡፡በቆላማ አካባቢዎች ላይም የቆላ ስንዴ ለመዝበቅድመ ዝግጅቱ ለመስኖ ልማት የሚውሉ በመንገድ ሥራና በጎርፍ ጉዳት የደረሰባቸውን ቦዮች መጠገንና የመጥረግ ሥራም እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ የክረምቱ ጎርፍ ከፍተኛ ስለ ነበር በርካታ ቦዮች በደለል መሙላታቸውን አቶ ተፈራ ተናግረዋል፡፡ በአርሶ አደሮች የሚጠገኑና ከአርሶ አደሮች አቅም በላይ የሆኑ የመስኖ ቦዮችም መለየታቸውን ጠቁመዋል፡፡
| 0 |
f80c75ee48ba75c7fb1a7a5ff164d471
|
f80c75ee48ba75c7fb1a7a5ff164d471
|
10ኛው የኢትዮጵያ የሰንደቅ አላማ ቀን በጅቡቲና አልጀሪያ ተከበረ
|
10ኛው የኢትዮጵያ ብሔራዊ የሰንደቅ አላማ ቀን በጂቡቲና በአልጀሪያ የኢፌዴሪ ኤምባሲዎች “ራዕይ ሰንቀናል ለላቀ ድል ተነስተናል” በድምቀት ተከበረ።በጅቡቲ የኢፌዴሪ ኤምባሲ ጊዜያዊ ጉዳይ አስፈጻሚ አቶ ስንታየሁ ሁንዴ ሲናገሩ ሰንደቅ አላማ የአንድ አገር የሉዓላዊነትና የነጻነቱ አርማ በመሆኑ ሁሉም ዜጋ ተገቢውን ክብር ሊሰጠው ይገባል ብለዋል።የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች፣ ተዋደውና ተከባብረው የመኖራቸውና የአንድነታቸው አርማ መሆኑንም ጠቁመዋል።በወቅቱ በኦሮሚያና በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ድንበር አካባቢ ተከስቶ የነበረውን ግጭት በዘላቂነት ለመፍታት የፌደራል መንግስት ከሁለቱ ክልሎች ሃላፊዎች ጋር በመሆን እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።በተያያዘ በአልጀሪያ የኢፌዴሪ ኤምባሲ 10ኛው ብሔራዊ የሰንደቅ አላማ ቀን ተከብሯል።የኤምባሲው ተወካይ አቶ አበበ ታደሰ እንዳሉት ሰንደቅ አላማ ኢትዮጵያውያን በድህነትና ኋላ ቀርነት የከፈቱትን ዘመቻ በአንድ የሚያስተሳስር አርማ ነው ብለዋል።በአልጀርስ የኢትዮጵያ ኮሚዩኒቲ ተወካይ አቶ ሃሺም ሳልም በበኩላቸው ለሰንደቅ አላማችን ከፍ ያለ ክብር ሁሉም ዜጋ በልማት ላይ የበኩሉን ሚና በመወጣት የበኩሉን ሚና መጫወት አለበት ብለዋል።በስነ ስርዓቱ የየኤምባሲዎቹ ሠራተኞች፣ የኢትዮጵያ ኮሚዩኒቲ አባላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
| 1 |
eae995564f6b34d7ed03a8f3b074ed55
|
eae995564f6b34d7ed03a8f3b074ed55
|
የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ከዛሬ ጀምሮ ይከፈት ይሆን?
|
የኢትዮጵያ ወንዶች እና ሴቶች ተጫዋቾች የውድድር ዘመን አጋማሽ (የጥር የዝውውር መስኮት) አስቀድሞ በተገለፀው መሠረት ዛሬ ስለመከፈቱ አጠራጥሯል።ከዚህ ቀደም በተለምዶ የፕሪምየር ሊጉ የመጀመርያ የውድድር ዘመን (አንደኛ ዙር) አጋማሽ ሲጠናቀቅ የሚከፈተው የዝውውር መስኮት ከዘንድሮው ጀምሮ አሰራሩን በመቀየር የዓመቱ አጋማሽ የዝውውር መስኮት (ዛሬ) ጥር 1 ጀምሮ እስከ ጥር 30 ቀን 2012 (ከጃንዋሪ 10 እስከ ፌብሩዋሪ 8) ድረስ ክፍት ይሆናል። ይህንንም የኢትዮጵባ እግርኳስ ፌዴሬሽን ክረምት ላይ ይፋ ማድረጉ አይዘነጋም።ሆኖም ከፌዴሬሽኑ አካባቢ ባገኘነው መረጃ መሠረት ሊጉ ገና ጅማሬው ላይ በመሆኑ አስቀድሞ የወጣውን የዝውውር ቀናት በመቀየር የአንደኛው ዙር ማጠናቀቂያ ላይ ለማድረግ ስለመታቀዱ ሰምተናል። የውጪ ተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ግን በቅድሚያ ፊፋ ላይ በተመዘገበው (ከጥር 1-30 / ከጃንዋሪ 10 – ፌብሩዋሪ 8) መሠረት ከዛሬ ጀምሮ እንደሚከናወን ይጠበቃል።የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ዘንድሮ በታሪኩ እጅግ ዘግይቶ ኅዳር 21 መጀመሩ የሚታወስ ሲሆን እስካሁን የ7 ሳምንት ጨዋታዎች ብቻ ከመካሄዳቸው አንፃር ገና ጅማሮው ላይ ይገኛል ማለት ይቻላል። በዚህም ምናልባትም አስቀድሞ በተገለፀው ቀን ዛሬ የዝውውር መስኮቱ የሚከፈት ከሆነ አብዛኛዎቹ ክለቦች ከጊዜው በፍጥነት መድረስ እና ከበጀት እጥረት አንፃር ተጫዋቾችን ለማዘዋወር ገበያ የመውጣታቸው ሁኔታ አጠራጣሪ ነው።
| 1 |
eeb7b734a6d4a595117df17a75474350
|
495deb544d2ce76b1e9f1e514c22800e
|
የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 2ኛ ዙር የሚጀመርበት ቀን ታውቋል
|
ሊጉ በሳምንቱ መጨረሻ ህዳር 17 እና 18 እንዲጀመር ክለቦች በእጣ ማውጣቱ ስነስርአት ወቅት ተስማምተው የነበረ ቢሆንም የዳኞች እና ታዛቢዎችን ክፍያ ከፍለው ባለማጠናቀቃቸው ውድድሩ የሚጀመርበት ቀን በ1 ሳምንት ተራዝሞ ህዳር 24 እና 25 በሚደረጉ ጨዋታዎች እንዲጀምር ተወስኗል፡፡ብሄራዊ ሊጉ አምናም በተመሳሳይ የሚጀመርበት ቀን በዳኞች እና ታዛቢዎች ክፍያ በወቅቱ አለመጠናቀቅ ምክንያት በጥር ወር መጀመሩ የሚታወስ ነው፡፡የ2009 የውድድር ዘመን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሊግ በ5 ምድቦች እና 55 ክለቦች መካከል የሚካሄድ ሲሆን የየምድባቸው አሸናፊዎች እና በጥሩ 2ኛነት ያጠናቀቀ አንድ ክለብ በቀጥታ ወደ 2010 ከፍተኛ ሊግ የሚያድጉ ይሆናል፡፡
| 0 |
351ba1a720f05959b18e6ccee716f8f1
|
ff815e9e63ed4db5335c285eada5f299
|
ኬንያ ግዙፉን የድሆች ሰፈር አፈራርሳለች ሲል አምነስቲ ኢንተርናሽናል አወገዘ
|
“ነውጠኛው እስላማዊ ቡድን” ቦኮ ሀራም ካለፈው ሚያዝያ ጀምሮ ናይጄሪያና ካሜሩን ውስጥ ባካሄደው ጥቃት፣ ወደ 4መቶ ሲቪሎች በአጥፍቶ ጠፊ ቡድኖች መገደላቸውን፣ አምነስቲ ኢንተርናሽናል አስታወቀ።ይህ በዚህ ዓመት ብቻ የተካሄደ ጥቃት ሲሆን፣ ባለፉት አምስት ወራት ከነበረው ከእጥፍ በላይ እንደሆነም ታውቋል።ዓለማቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ቡድን አምነስቲ ዛሬ ማክሰኞ ይፋ ባደረገው በዚህ ሪፖርቱ እንዳመለከተው፣ በነሐሴ ወር የተገደሉትን መቶ ሲቪሎችን ጨምሮ ካለፈው ሚያዝያ ወር ወዲህ 2መቶ ሃያ ሦስት ሲቪሎች የተገደሉት በቦኮ ሀራም እጅ ነው።ከፍተኛ የደም መፋሰስ የተፈፀመበት ጥቃት የተካሄደው፣ እአአ ባለፈው ሐምሌ 25 ቀን 40 ሰዎች ቦርኖ ውስጥ በሚገኝ የነዳጅ ማውጫ ላይ ፍንዳታ በተደረገበት ጊዜ መሆኑም ታውቋል።በጎረቤት ካሜሩን ደግሞ ካለፈው ሚያዝያ ወር ወዲህ ቢያንስ 1መቶ ሃምሳ ስምንት ሲቪሎች በ30 የተለያዩ አጥፍቶ ጠፊዎች የተገደሉ ሲሆን፣ ሌሎች 16 ሲቪሎችም ዋዛ ውስጥ በተመሳሳይ ጥቃት ሕይወታችው አልፏል።በእነዚህ የምዕራብ አፍሪካ አገሮች የሚፈፀመው ግድያ ከፍተኛውን አኃዝ ያስመዘገበ መሆኑን ያመለከተው አምነስቲ፣ ብዙውን ጊዜ አጥፍቶ ጠፊዎቹ በቦኮ ሀራም የሚመለመሉ ሴቶችና ህፃናት ናቸው ብሏል።የቦኮ ሀራምን ጥቃት ሽሽት፣ ወደ 2.3 ሚሊዮን ሕዝብ ከናይጄሪያ፣ ከካሜሩን፣ ከቻድና ከኒዠር የተሰደዱ ሲሆን፣ ከነዚሁ ውስጥ ወደ 7 ሚሊዮን ያህሉ፣ ለከፋ ረሀብና የመግብ እጥረት የተጋለጡ ናቸው ብሏል።
| 0 |
167651e812f87f88aea9b58145243cd4
|
a2d70633d63368f0c5f9ba536cc4ea31
|
ዶናልድ ትራምፕ፡ "አሜሪካ የዓለም ጤና ድርጅትን ጥላ የምትወጣበት በቂ ምክንያት የላትም" ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም
|
የዓለም ጤና ድርጅት ኃላፊው ዶ/ር ቴድሮስ አድኃኖም በቅርቡ ከእሳቸው ጋር ንክኪ የነበረው ግለሰብ በኮሮናቫይረስ መያዙ መረጋገጡን ተከትሎ ራሳቸውን አግልለው እንደሚገኙ አስታውቀዋል።ዶክተር ቴድሮስ እስካሁን ድረስ ምንም አይነት የበሽታው ምልክት እንደማይታይባቸው ገልጸዋል።''በኮቪድ-19 መያዙ ከተረጋገጠ ግለሰብ ጋር ንክኪ እንዳለኝ ታውቋል። በጥሩ ጤንነት ላይ ነው የምገኘው፤ ምንም የቫይረሱን ምልክቶችም እያሳየሁ አይደለም። ነገር ግን በዓለም ጤና ድርጅት መመሪያዎች መሰረት ለሚቀጥሉት ቀናት ራሴን አግልዬ እቆያለሁ። ሥራዬንም ከቤቴ እሰራለሁ'' ሲሉ በትዊተር ገጻቸው በኩል አስታውቀዋል።''እኔ እና የዓለም ጤና ድርጅት ባልደረቦቼ የሰዎችን ሕይወት ለማዳንና ተጋላጭ የሆኑትን ከቫይረሱ ለመከላከል አብረውን ከሚሰሩ ድርጅቶች ጋር ያለንን የትብብር ሥራ እናስቀጥላለን'' ሲሉም አክለዋል።''ሁሉንም የጤና መመሪያዎች መከተል የሕይወትና የሞት ጉዳይ ነው'' ብለዋል የ55 ዓመቱ የቀድሞ የኢትዯጵያ የጤና ሚኒስትር። . . . ''የኮቪድ-19 ስርጨት ሰንሰለትን መስበር የምንችለው በዚህ መንገድ ነው። ይህንን ካደረግንም ቫይረሱን እናሸንፈዋልን፤ የጤና ስርአታችንንም እንከላከለዋለን'' ብለዋል።ዶክተር ቴድሮስ የዓለም ጤና ድርጅትን መምራት የቻሉ ብቸኛው አፍሪካዊ ናቸው።የዓለም ጤና ድርጅት ኃላፊ ሆነው ሲሾሙ በየዓመቱ ሚሊዮኖችን እየገደሉ ያሉ እንደ ወባ፣ ኩፍኝና ኤድስን እገታለሁ ሲሉ ነበር በወቅቱ ቃል የገቡት። ምንም እንኳ መሥሪያ ቤታቸው እነዚህን በሽታዎች ለመግታት ቢታገልም፤ በሥልጣናቸው መባቻ ከባድ ፈተና ሆኖባቸው የነበረው ኮንጎ ውስጥ የተቀሰቀሰው ኢቦላ ነበር። አሁን ደግሞ ኮሮናቫይረስ።
| 0 |
9a34328eafd52c1e530a69e992dc99a6
|
7fe93da58c69465d27df61fec1fd61d8
|
የህወሐት ማዕከላዊ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ ተጀመረ
|
የብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ብአዴን/ ማዕከላዊ ኮሚቴ ባደረገው መደበኛ ስብሰባ ባለፉት 6 ወራት በጥልቀት የመታደስ ንቅናቄ እና መደበኛ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት አፈፃፀምን ከገመገመ በሗላ በኪራይ ሰብሳቢነት በተጠረጠሩ አመራሮቹ ላይ እርምጃ መዉሰዱን አመለከተ፡፡የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለምነው መኮነን ከጉባኤዉ መጠናቀቅ በሗላ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ከጥልቅ ተሀድሶው በፊት በአንዳንድ አመራሮች ዘንድ የኪራይ ሰብሳቢነት አስተሳሰብና ተግባር ጐልቶ ይታይ ነበር ብለዋል፡፡በዚህም የተጠረጠሩ 462 ከፍተኛ እና መካከለኛ እንዲሁም 362 የታችኛው አመራሮች ጉዳያቸው በመጣራት ላይ ያለ ሲሆን ከተጠሩት ጉዳዮች ውስጥ በ1ኛው ላይ ከማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነቱ እንዲታገድ በሁለተኛው ላይ ከባድ ማስጠንቀቂያ እንዲሰጠው ማዕከላዊ ኮሚቴው ወስኗል፡፡ ከክልል ኃላፊዎች መካከል 16ቱ ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ፣ 11ዱ ደግሞ ከደረጃቸው ዝቅ እንዲሉ መደረጋቸዉን ጠቁመዋል፡፡ብአዴን ባሳለፋቸው ሂደቶች ብዙ ውጤቶችን ያስመዘገበ ቢሆንም ሂደቱ ደረጃ በደረጃ ህዝቡን ከመምራት ብቃት አኳያ የአስተሳሰብ ድክመትና የአፈፃፀም ጉድለት አጋጥሞታል፡፡ በመሆኑም የተሀድሶው ንቅናቄ የአስተሳሰብ ችግሮችን በመፍታት ለሰላም፣ለልማትና ለመልካም አስተዳደር የተመቸ የአመራር አንድነትና መዋቅራዊ ለውጥ ሊያመጣ የሚያስችል እና የህዝቡን መሰረታዊ ጥያቄዎችን በአጭርና በመካከለኛ ጊዜ ለመፍታት ያለመ ንቅናቄ እንደነበር አስታዉሰዋል፡፡ በዚህም ማዕከላዊ ኮሚቴው የአስተሳሰብ ግልጽነትና የሃሳብ አንድነት በድርጅቱ አመራሮች ዘንድ መምጣቱን እንደገመገመና ይህ በመሆኑም ድርጅቱ ህልውናው ተጠናክሮ ህዝብን መምራት በሚያስችል ቁመና ላይ እንዲገኝ የጥልቅ ተሀድሶው ንቅናቄ ትልቅ አቅም ፈጥሮለታል ብለዋል፡፡በቀጣይ ብአዴን ህዝብ የመምራት ብቃቱ እንዲረጋገጥ ህዝብን የሚጠቅሙ አስተሳሰቦችን መያዝ፣የህዝቡን ጥያቄዎች ለመመለስ መረባረብ ፣ የግብርና ምርት እንዲያድግ ህዝብን ማነቃነቅ ፣ በከተሞች የአምራች ኢንዱስትሪ መስኮችን ማስፋት ፣ ህዝባዊ አገልግሎትና ዲሞክራሲያዊ ግንኙነትን ለማጠናከር ድርጅቱ በቀጣይ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራም አመልክተዋል፡፡
አቶ አለምነው መኮነን በመግለጫቸው አያይዘውም በአዲስ አበባ በተለምዶ ቆሸ በሚባለው አካባቢ በመሬት መንሸራተት ምክንያት በተጐዱ ወገኖች ድርጅታቸዉ የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀው ለቤተሰቦቻቸውና ለዘመዶቻቸው መፅናናትን¨ተመኝተዋል፡፡
| 0 |
6946a8f10dc298fefc80ddace88b6798
|
6946a8f10dc298fefc80ddace88b6798
|
ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ የ40/60 ሱቅ ለመግዛት ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ አቀረበ
|
ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ የአዲስ አበባ ከተማ የቁጠባ ቤቶች ኢንተርፕራይዝ የንግድ ቤቶችን ለመሸጥ ባወጣው ጨረታ፣ 156 ካሬ ሜትር የ40/60 ሱቅ ለመግዛት 26.6 ሚሊዮን ብር የመጫረቻ ዋጋ አቀረበ፡፡ ባንኩ የሰጠው ዋጋ ለሁሉም ሱቆች ከተሰጡት ዋጋዎች በከፍተኛነት ተመዝግቧል፡፡ መጋቢት 18 ቀን 2010 ዓ.ም. በተከፈተው ጨረታ ኢንተርፕራይዙ 320 ሱቆችን ለጨረታ አቅርቦ ነበር፡፡ የተጠቀሱትን ሱቆች ለመግዛትም 4,100 የጨረታ ሰነዶች ተሸጠዋል፡፡፡ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ ለመግዛት በተጫረተው ጨረታ ለካሬ ሜትር 171 ሺሕ ብር ከ50 ሳንቲም የሰጠ ሲሆን፣ አብሮ ተፎካካሪ ከነበረው ሁለተኛ ተጫራች በ50 ሳንቲም በካሬ የተሻለ ዋጋ አቅቧል፡፡ሦስት መቶ ሃያ ሱቆች በቅርቡ ተጠናቀው ለገዥዎች እየተላለፉ የሚገኙት የሠንጋ ተራና የክራውን የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ሳይት የሚገኙ ሲሆን፣ በጨረታው አብዛኛው ከፍተኛ የመጫረቻ ዋጋ ያቀረቡትም ባንኮች መሆናቸው ታውቋል፡፡ ‹‹እኛም ሆነ ሌሎች ተጫራቾች የሰጠነው ዋጋ ከፍተኛ ቢሆንም፣ በአካባቢው የራሳችንን ሕንፃ ለመገንባት በቂ ቦታ የለም፤›› ያሉት የኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ፣ ‹‹በተጨማሪ በአካባቢው እንከራይ ብንል የምናወጣው ወጪም ከፍተኛ ነው፤›› ብለዋል፡፡ ባንኩ በሚቀጥለው ዓመት የራሱን ሕንፃ ለመገንባት እንቅስቃሴ የጀመረ ሲሆን፣ ‹‹አስፈላጊ ከሆነ ሕንፃውን ገንብተን እንደጨረስን ሱቁን እንሽጠው ብንል አሁን በጨረታው ካቀረብነው በላይ ዋጋ ማግኘት እንችላለን፤›› ሲሉ አቶ አቤ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡በጨረታው ለሽያጭ የቀረቡት ሱቆች እያንዳንዳቸው ከ70 ካሬ ሜትር እስከ 395 ካሬ ሜትር ስፋት ያላቸው ናቸው፡፡ ከፍተኛ የመጫረቻ ዋጋ ያገኘው 155.97 ካሬ ሜትር ስፋት ያለው ሱቅ በካሬ ሜትር መነሻ ዋጋው 19,346 ብር ነበር፡፡ ይህ የመነሻ ዋጋ በአጠቃላይ ሱቁን ለመገንባት የወጣውን ወጪ ያህል ነው ሲሉ የጨረታ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ አብርሃም ተስፋዬ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ ‹‹አስፈላጊውን ማጣራት አድርገን የጨረታውን ውጤት በቅርቡ ይፋ እናደርጋለን፤›› ብለዋል፡፡
| 1 |
6201a6afc2a603c163439e1d85659540
|
7c8e45bbe87221957945d432249b7539
|
ባየር ሙኒክ በኢትዮጵያ ሥልጠና ይሰጣል
|
አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 23/ 2006 (ዋኢማ) – የአክራሪነትና ፅንፈኝነት ዝንባሌዎችን ለመከላከል በተደረገ ጥራት በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ለ42ሺ995 የህብረተሰብ አባለት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና መስጠቱን የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር አስታወቀ። በሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አበበ ወርቁ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለጹት ሥልጠናው በዋናነት ያተኮረው በብዝሃነት አያያዝ፣አክራሪነትና የጽንፈኝነት ዝንባሌዎች እና መፍቴያቸው ላይ ነው።ሥልጠናው የተሰጠው በመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ለሚገኙ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች እንዲሁም ተማሪዎች መሆኑን ኃላፊው አስረድተዋል። እንደ አቶ አበበ ገለጻ 20ሺ9 መምህራንና የአስተዳደር ሰራተኞች እንዲሁም 22ሺ986 ተማሪዎች ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ከፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር በተውጣጡ ባለሙያዎች የተሰጠውን ሥልጠና ተካፍለዋል። ኃላፊ አያይዘው እንደገለጹት ለስድስተኛ ጊዜ በአገር አቀፍ ደረጃ የተከበረውን የሰንደቅ ዓላም ቀን አስመልክቶ በሰንደቅ አላማ አከባበር እንዲሁም በብሔር ብሔረሰቦች አብሮ የመኖርና የጋራ ልማት ላይ ሥልጠና ተሰጥቷል።
| 0 |
2ece9eef111f7001e1146de5f1ea0ed8
|
7b93eb7c63440ad63d3cfcdc8836cb0f
|
ኦብነግ ከ1ሺህ 700 በላይ ወታደሮቹን ለመንግስት አስረከበ
|
የፍቼ ከተማ አስተዳደር ህገ ወጥ ንግድ በማንቀሳቀስ ማግኘት የነበረብኝን ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ አሳጥተውኛል ባላቸው የንግድ ድርጅቶች ላይ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቋል።ከአስተዳደሩ ንግድ እና ገበያ ልማት ጽህፈት ቤት የተገኘ መረጃ እንደሚያመለክተው በከተማዋ ቀረጥ እና ግብር ሳይከፍሉ በህገወጥ መንገድ የሚነግዱ ከ1ሺህ 6ዐዐ በላይ ግለሰቦች እንደሚገኙ በጥናት ተረጋግጧል፡፡ህገወጥ ነጋዴዎቹ በህጋዊ ነጋዴዎች ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ከማሳደራቸውም ሌላ ባለፈው በጀት ዓመት መንግሥት ከግብር ማግኘት የነበረበትን ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ እንዲያጣ አድርገዋል ብሏል ጽህፈት ቤቱ፡፡ ህገወጥ ነጋዴዎቹ በከተማዋ ከግብር እና ቀረጥ ለመሸሽ አመቺ ጊዜ እየጠበቁ በመፈራረቅ እንደሚንቀሳቀሱ ያመለከተው ጽህፈት ቤቱ በአብዛኞቹ ህገወጥ ነጋዴዎች በአዲስ እና ልባሽ ጨርቆች፣ በቤት ውስጥ የመገልገያ ቁሳቁሶች ፣በወተት ማሰባሰብ እና ማከፋፈል ፣በሴራሚክ ችርቻሮ እና በአሸዋና ጠጠር ንግድ ስራ የተሰማሩ መሆናቸውን ይጠቁማል።
| 0 |
379b88d9d6f278e8e58cae9fe3cace44
|
379b88d9d6f278e8e58cae9fe3cace44
|
ኬንያ በአካሄደችው ምርጫ “የመለኪያውን ፈተና አልፋለች”- ዓለምቀፍ ታዛቢዎች
|
ዓለምቀፍ ታዛቢዎች ኬንያ በብሔራዊ ደረጃ በአካሄደችው ምርጫ “የመለኪያውን ፈተና አልፋለች” ብለዋል።በሌላ በኩል ደግሞ በዛሬው ዕለት ይፋ ይደረጋል ተብሎ የሚጠበቀው የምርጫ ውጤት ሊዘገይ እንደሚችል በኬንያ የሚገኙ ዘጋቢዎቻችን ጠቁመዋል።ያለምአቀፍ ታዛቢዎቹን አስተያየት በተመለከተ -ላሪ ሩቬዣ ለአሜሪካ ድምፅ ከናይሮቢ ዘገባ ልኳል።
| 1 |
5cb3e177bdf1a087d4ffa41105e32b77
|
5cb3e177bdf1a087d4ffa41105e32b77
|
ስንቄ
|
"ስንቄ" ሴቶች ነፃነታቸውና መብታቸውን የሚያስከብሩበትና ማኅበራዊ ኃላፊነት የሚሸከሙበት ባህላዊ ሥርዓት ነው ብሏል የኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ፡፡"ስንቄ" በጋዳ ስርዓት ሴቷን ከአባጋዳ ጋር አቻ የሚያደርጋት የ"Hadha"ስንቄ" ምልክት ነው ተብሏል፡፡የሱዳን ሴቶች የባህልና የሰላም ሉዑካን ቡድን የ "ስንቄ" ባህል በአሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሶ ዞን ኮፌሌ ከተማ ድረስ መጥተው ጎብኝተዋል፡፡የልዑኩ መሪ ፕሮፌሰር ሜኪ ሀሻብሊ ኢትዮጵያ ግጭቶችን በባህላዊ መንገድ በመፍታት ረገድ ጥሩ ተሞክሮ አላት ብለዋል፡፡
| 1 |
704707e5fbb5d49beb584acf840c9349
|
93c12a1b8841f4f2e8940edef41df82a
|
ሴራሊዮን በፊፋ እገዳ ተጣለባት
|
አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 17 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ)ቲክቶክ የዶናልድ ትራምፕ እገዳ ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ፡፡የቻይናው ተንቀሳቃሽ ምስል አጋሪ ቲክቶክ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኩባንያው በአሜሪካ እንዳይሰራ የጣሉትን እገዳ ለመቃወም ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ማስታወቁ ተነግሯል፡፡የትራምፕ እገዳ ከቲክቶክ ባለቤት ባይስ ዳንስ ጋር የሚደረግ ግብይትን ከመስከረም ወር አጋማሽ ጀምሮ ይከለክላል፡፡በዋሽንግተን የሚገኙ ባለስልጣናትም ኩባንያው በአሜሪካ ተጠቃሚዎች በኩል መረጃዎችን ለቻይና መንግስት ሊያስተላልፍ ይችላል የሚል ስጋት አላቸው ፡፡በዚህም የኩባንያው ቃል አቀባይ የህግ የበላይነት ወደ ጎን አይባልም ለዚህም የፕሬዝዳንቱን ትዕዛዝ ለመቃወም ወደ ፍርድ ቤት እናመራለን ብለዋል፡፡የቲክቶክ ህጋዊ እርምጃም በዚህ ሳምንት እንደሚጀምር ይጠብቃል ነው የተባለው፡፡አጭር ተንቀሳቃሽ ምስል ማጋሪያ ቲክቶክ በአሜሪካ 80 ሚሊየን ተጠቃሚዎች አሉት ፡፡ምንጭ፡-ቢቢሲ
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
| 0 |
4b5266cdce2f228d19e48129200e5631
|
48c971967f2e08d505f3a1287e2f301e
|
አቶ ጌታቸው አምባዬ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የሕግ አማካሪ ሆነው ተሾሙ
|
– የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ለሁለት የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ሹመት ሰጡ፡፡ በዚሁ መሰረትም፡-1. አቶ በረከተ ስምኦን የጠቅላይ ሚንስትሩ የፖሊሲ ጥናት እና ምርምር አማካሪ ሚንስትር፣2. አቶ ኩማ ደመቅሳ የጠቅላይ ሚንስትሩ የፖሊሲ ጥናት እና ምርምር አማካሪ ሚንስትር፣ሆነው መሾማቸውን የጠቅላይ ሚንስትር ጽ/ቤት ለኢ.ሬ.ቴ.ድ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡አቶ በረከት ስምኦን የመንግስት ኮመኒኬሽን ጉዳዮች ፅሕፈት ቤት ሃላፊ ሚኒስትር የነበሩ ሲሆን አቶ ኩማ ደመቅሳ ደግሞ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ የነበሩ መሆናቸው ይታወሳል፡፡
| 0 |
3c24c9b2bd6d5e274a35027f21b234f2
|
96571e45778acd5a2d497e753c7a414b
|
ህገወጡን የትህነግ ቡድን ለመመከት የትጥቅ እና የሥነ ልቦና ዝግጅት በማድረግ ወደ መከላከል ተግባር መግባታቸውን የሚሊሻ አባላት ተናገሩ፡፡
|
በሳምንቱ ተጠባቂ የነበረው የመቐለ እና ኢትዮጵያ ቡና በአቻ ውጤት ከተጠናቀቀ በኋላ የሁለቱም. ቡድን አሰልጣኞች የሚከተለውን አስተያየት ሰጥተዋል።“በተጫዋቾቻችን ላይ የሥነ-ልቦና ጫና እየታየ ነው” ገብረመድህን ኃይሌስለ ጨዋታውጨዋታው ሁለት መልክ ነበረው። የመጀመርያው አጋማሽ ቡድናችን ትኩረቱን ያጣበት ጊዜ ሲሆን ሁለተኛው አጋማሽ ግን በሙሉ አቅማችን ለማጥቃት የሞከርንበት ነበር። ያገኘናቸው ዕድሎች መጠቀም አልቻልንም።በተጫዋቾቻችን ላይ የሥነ-ልቦና ጫና እየታየ ነው። የውድድሩ አሸናፊ ስለሆንን ተከታታይ ጨዋታዎች ማሸነፍ ይጠበቅብናል። እሱ ሳይሆን ሲቀር ደሞ ጫናዎች እንዳሉ የታወቀ ነው። እንደ ቡድን የመጫወት አቅማችን ጥሩ አይደለም። የተናጠል ጨዋታ እየበዛ ነው፤ በቀጣይ ይህንን አስተካክለን እንመጣለን።“በሚቀጥለውም ይህን መንፈስ ይዘን ነው ለማሸነፍ የምንጫወተው” ካሣዬ አራጌጨዋታው ጥሩ ነበር። መቐለዎች በሚጣሉ ኳሶች ጫና በመፍጠር በዛ መንገድ ነው የጎል ዕድል የፈለጉት። እኛም የሚመጡትን ኳሶች ተቆጣጥረን የመጫወት ሂደት ነበር። እንደዚ አይነት ነበረው አብዛኛው የጨዋታው መልክ። እኛ ሁሌ ለማሸነፍ ነው የምንጫወተው፤ ከዛ በኋላ ግን ሜዳ ውስጥ ያለውን ነገር ይወስነዋል። የቡድኑ መንስፈስ በሜዳችም ይሁን ከሜዳችም ውጭ ለማሸነፍ ነው። በሚቀጥመውም ይህን መንፈስ ይዘን ነው ለማሸነፍ ምንጫወተው።ስለ አጨዋወቱ እና ስለሚፈጠሩት ስህተቶችዛሬ ብዙ ስህተቶች አልተፈጠሩም። ያልተፈጠሩት ለምንድነው ተጫዋቾቻችን ሃላፊነት ወስዶ ለመጫወት አልደፈሩም። ግብ ጠባቂያችንም ኳሶች በረጅሙ ይልክ ነበር፤ መጫወት ነበረብን። ስህተቶችን እያረምን ነው የምንሄደው። ግን ያንን በትክክል እያደረጉት አልነበረም። ሃላፊነት ለመውሰድ እየፈሩ ነበር ያንን ችግር ይታይ ነበር። እንደዛ ስንጫወት የሚፈጠሩ ስህተቶች ሊኖሩ ይችላሉ። ግን እንቅስቃሴው ይዘን መቀጠል ነበረብን፤ ዛሬ ግን ያ በብዛት አልነበረም።
| 0 |
897d279e685197e05ee1b3ca7827e774
|
897d279e685197e05ee1b3ca7827e774
|
የቱርክ ኩባንያ በትግራይ ክልል በ750 ሚሊዮን ዩሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ ለመገንባት የኢንቨስትመንት ፈቃድ ማውጣት ጀመረ
|
በቱርክ ፕሬዚዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶዋን ቀጥተኛ መመርያ ተርኪሽ ሆልዲንግ ኤኤስ፣ በትግራይ ክልል በ750 ሚሊዮን ዩሮ አዲስ የኢንዱስትሪ ፓርክ ለመገንባት የኢንቨስትመንት ፈቃድ በማውጣት ላይ መሆኑ ታወቀ፡፡ተርኪሽ ኢንዱስትሪያል ሆልዲንግ የኮንስትራክሽን፣ የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ዕቃዎችን የሚያመርት ኢንዱስትሪ ፓርክ ለመገንባት ያቀደው በትግራይ ክልል ደቡባዊ ዞን አዲጉደም ከተማ ነው፡፡ የኩባንያው ባለሥልጣናት ከአዲጉደም ከተማና አቅራቢያ ነዋሪዎች ጋር፣ በኢንዱስትሪ ፓርኩ ግንባታና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ምክክር ማድረጋቸው ታውቋል፡፡ተርኪሽ ኢንዱስትሪያል ሆልዲንግ ግንባታውን ለማካሄድ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን ማካሄዱን በመቀጠል፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የኢንቨስትመንት ፈቃድ በማውጣት ሒደት ላይ እንደሚገኝ ለመረዳት ተችሏል፡፡የትግራይ ክልል ከተማ ልማት፣ ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀብቶም ፋንታሁን ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ተርኪሽ ኢንዱስትሪያል ሆልዲንግ የኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ ለማካሄድ 500 ሔክታር መሬት እንደሚፈልግ አሳውቋል፡፡‹‹ኩባንያው የኢንቨስትመንት ፈቃድና የሚያስፈልጉ ዝግጅቶችን ሲያጠናቅቅ፣ ለግንባታ የሚያስፈልገውን ቦታ ያገኛል፤›› ሲሉ አቶ ሀብቶም ተናግረዋል፡፡ተርኪሽ ኢንዱስትሪያል ሆልዲንግ በቱርክ ከሚገኙ ግዙፍ ኩባንያዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ በተለይ በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ፣ በብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ የኢንዱስትሪ ምርቶች ይታወቃል፡፡ኩባንያው ኢትዮጵያ ውስጥ በእነዚህ ዘርፎች በስፋት ለመግባት ፍላጎት እንዳለው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ሲያስረዳ፣ አቶ ሀብቶምም ይኼንኑ አረጋግጠዋል፡፡‹‹የደቡባዊ ትግራይ አካባቢ ከፍተኛ የማዕድን ሀብት አለው፣ ለመቀሌ ከተማም ቅርብ በመሆኑ በኩባንያው ተመራጭ ሆኗል፤›› ሲሉ አቶ ሀብቶም ገልጸዋል፡፡የቱርክ ፕሬዚዳንት ትግራይ ለሚገኘው ጥንታዊው ነጋሽ መስጊድ ልዩ ፍላጎት እንዳላቸው ይነገራል፡፡ የኩባንያው ኃላፊዎች አዲስ አበባ በመጡበት ወቅት ከቀድሞው ፕሬዚዳንት ሙላቱ ተሾመ (ዶ/ር) ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ በጥንታዊው ነጋሽ መስጊድ ጉዳይና በትግራይ የኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ ከፕሬዚዳንት ኤርዶዋን መመርያ እንደተሰጣቸው መወያየታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ ያመለክታል፡፡
| 1 |
f40bef9960f33fc23acc1afc3176b474
|
cffc9478f096d49e4da1aebd5e7a8956
|
መንግስት ከ300 በላይ እስረኞች በይቅርታ እንዲፈቱ ወሰነ
|
በኢትዮጵያ ለ650 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታና ምህረት ተደርጎ በመፈታት ላይ መሆናቸው ተገለጠ፡፡የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ የይቅርታ ቦርድ በሐምሌ 28/2010 ዓ.ም ባሳለፈው የውሳኔ ሀሳብ መሰረት ካለፈው ማክሰኞ ጀምሮ ታራሚዎቹ እንዲፈቱ እየተደረገ መሆኑ ታውቋል።በሀገር ውስጥ ዘገባዎች መሰረት ይቅርታ የተደረገላቸው ታራሚዎች ድሬደዋ፣ ከቃሊቲ፣ ዝዋይ እና ቂሊንጦ ማራሚያ ቤት የሚገኙ ናቸው።ታራሚዎቹ በይቅርታ አዋጁ መስፈርት መሰረት በልዩ ሁኔታ ማለትም በዕድሜ መግፋት፣ በከባድ ጤና ችግርና የተፈረደባቸውን ፍርድ አንድ ሦስተኛ የጨረሱ እንዲሁም የገንዘብ ቅጣታቸውን የከፈሉ እንደሚገኙባቸው ዘገባው አመልክቷል።
| 0 |
85c3d1ea2cc0daab07ac4bd5fca7dbee
|
00e5b4aacbf75faec2af7ddd0ae631d9
|
ምዓም አናብስት ድጋፍ አደረጉ
|
በካፍ ቻምፒየንስ ሊግ የመጀመርያ ጨዋታቸውን ለማድረግ ወደ ኢኳቶርያል ጊኒ ማላቦ ያመሩት የተጠናቀቀው የውድድር ዓመት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አሸናፊ መቐለ 70 እንደርታዎች በካኖ ስፖርት የ 2-1 ሽንፈት አስተናግደዋል።ከአዲስ ፈራሚዎች መካከል ታፈሰ ሰርካን ብቻ በመጀመርያ አሰላለፍ በማካተት እና ኢኳቶርያል ጊኒያዊው ግብ ጠባቂ ፊሊፕ ኦቮኖን በአምበልነት በመጠቀም በተለመደው አሰላለፋቸው ወደ ሜዳ የገቡት ምዓም አናብስት በመጀመርያው የአፍሪካ ውድድራቸው እስከ 81ኛው ደቂቃ ድረስ 2-0 ሲመሩ የነበረ ሲሆን በተጠቀሰው ደቂቃ አማኑኤል ገብረሚካኤል ግብ በማስቆጠር ቡድኑን ከባዶ መሸነፍ ከማዳኑም ባለፈ ከሜዳው ውጭ ጥሩ ውጤት ይዞ እንዲወጣ አስችሏል።ለመቐለ በታሪክ የመጀመርያ በሆነው የአፍሪካ መድረክ ጨዋታ በተከታታይ ዓመታት የቡድኑ ቁልፍ ተጫዋች የሆነው አማኑኤል ገብረሚካኤል ታሪካዊዋን የመጀመርያ ጎል ማስቆጠር ችሏል።መቐለ 70 እንደርታዎች ባለፈው ሳምንት የትግራይ ስታዲየም የካፍ ፍቃድ ማግኘቱን ተከትሎ ከአስራ አምስት ቀናት በኋላ የመልስ ጨዋታቸውን በመቐለ ያደርጋሉ።
| 0 |
309da6834e53bf5331bd2fbbe5fe5e46
|
5621f8aee34e779d36f007577459a0c2
|
ሁለት የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሰራተኞች ጉቦ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ ተያዙ
|
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከጥቅምት 23 እስከ 30 /2012 ሦስት የተለያዩ ቀናት ውስጥ 7 የተለያዩ አይነት የጦር መሳሪያዎች እና 197 መሰል ጥይቶች ከነተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል። ኮሚሽኑ እንዳስታወቀው ጥቅምት23፣ 28 እና 30/2012 ከተለያዩ ሸቀጦች እና ጭነቶች ጋር በማድረግ ሕጋዊ ጭነት በማስመሰል ወደ ክልሎች ለማጓጓዝ ሲሞከር እጅ ከፍንጅ መያዙን ገልጿል። ሕገ ወጥ የጦር መሳሪያዎች በሕብረተሰቡ ጥቆማ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የገለፀው ኮሚሽኑ አሁንም ሕብረተሰቡ አጠራጣሪ ነገሮችን ሲያይ ለፖሊስ ጥቆማ እንዲያደርግ አሳስቧል።
| 0 |
b7a2b1a598a415849cc734bd4231b6d1
|
28ee324e2ae39a6f04ddff4c63e3c8d3
|
በሙስሊሙ ማህብረሰብ የሚስተዋሉ መከፋፈሎችን ለማጥበብ የሚያስችል ውይይት ይደረጋል
|
ዛሬ ቅዳሜ ሕዳር 22/2011 ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ስር የሚገኘው የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ የስነ ጥበባት ማዕከል 41ኛውን የጥበብ ውሎ ውይይት ያደርጋል።
የዛሬው ዝግጅት ማዕከሉ በስማቸው በተሰየመላቸው ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ ሕይወትና ስራዎች ላይ ያጠነጥናል። ከ1871 እስከ 1931 በሚሸፍነው የብላቴን ጌታ ኅሩይ ህይወትና ስራዎች ላይ በተለይም ባለታሪኩ በ1916 እና በ1925 በጻፏቸው ‹‹አዲስ ዓለም›› እና ‹‹ወዳጄ ልቤ›› በተሰኙ መጻሕፍት ላይ ውይይት ይደረጋል።
የስነ ጽሑፍና ፎክሎር ባለሙያ እንዲሁም የስነ ጥበብ ማዕከሉ ዳይሬክተር እንዳለጌታ ከበደ የውይይት መነሻ ሀሳብ ያቀርባሉ። በዕለቱ ከብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ የሕይወት ታሪክ በተጨማሪ አጭር ዘጋቢ ፊልም፣ ግጥሞች፣ ትረካዎችና ዲስኩሮች ይቀርባሉ ተብሏል። የብላቴን ጌታ ኅሩይ የልጅ ልጆችና ሌሎች እንግዶች በዛሬው የጥበብ ውሎ ይታደማሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የ20ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ ምሑር የሚሰኙት ኅሩይ ወልደሥላሴ በቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ዘመን የመጀመሪያው የውጭ ጉዳይ ሚንስትርና ደራሲ ነበሩ።
ከአስራ አምስት ቀን በኃላ የሚኖረው ዝግጅት በኃይሌ ገሪማ ‹‹ጤዛ›› ፊልም ላይ ውይይት እንደሚደረግ ከወዲሁ ታውቋል ማዕከሉ በየሁለት ሳምንቱ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ውይይት የሚያደርግ ሲሆን ፍላጎቱ ላላቸው ሁሉ ክፍት መሆኑን ከዚህ ቀደም መዘገባችን ይታወሳል።ቅጽ 1 ቁጥር 3 ኅዳር 22 ቀን 2011
| 0 |
a72a53359e581c769dc92b26f90e7b26
|
a72a53359e581c769dc92b26f90e7b26
|
ብርሀኑ ግዛው የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ በመሆን ተሾሙ
|
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የንግድ ባንክ የሴቶች ቡድን አሰልጣኝ የሆኑት ብርሀኑ ግዛውን የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ በማድረግ ሾሟል፡፡በቀጣዩ ወር ኅዳር መጀመሪያ ላይ በታንዛኒያ አስተናጋጅነት የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ ውድድር የሚደረግ ሲሆን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎችም ይከተላሉ። በቅርቡ ከአሰልጣኝ ሰላም ዘርዓይ ጋር የተለያየው ፌዴሬሽኑም ለውድድሮቹ ዝግጅት እንዲረዳው ብርሀኑ ግዛውን በዋና አሰልጣኝነት መሾሙን አሰልጣኙ ለሶከር ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡ ከዚህ ቀደም በየካ እና ሴንትራል ዩኒቨርሲቲ ክለቦች እንዲሁም ከ2004 ጀምሮ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ክለብን በማሰልጠን ላይ የሚገኙት አሰልጣኙ ከዚህ ቀደም በሊሱዎቹ የአሰልጣኝ ሥዩም ከበደ እና አብርሀም ተክለሀይማኖት ረዳትነት እንዲሁም በ2008 በዋና አሰልጣኝነት ሰርተዋል፡፡አሰልጣኙ ነገ ረዳቶቻቸውን እና የተመረጡ ተጫዋቾችን ይፋ የሚያደርጉ ሲሆን ዝግጅታቸውን ደግሞ በዚህ ሳምንት ሀዋሳ ወይም አዲስ አበባ ላይ ሊጀምሩ እንደሚችሉ ሰምተናል፡፡ኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በታንዛኒያ በሚካሄደው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ላይ በምድብ ለ ከዩጋንዳ፣ ኬንያ እና ጅቡቲ ጋር መደልደሉ ይታወሳል።
| 1 |
3ce5427eb30d8f8ae8bbef15136e9ad5
|
7624430b3a0c47c37142a41b88fd620c
|
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጠቅላላ ሀብቱ ግማሽ ትሪሊዮን መድረሱ ተገለጸ
|
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለዓባይ ባንክ ምክትል ፕሬዚዳንትነት የታጩትን የአቶ በለጠ ዳኘውን ሹመት ማፅደቁ ተገለጸ፡፡ከባንኩ የተገኘው መረጃ እንደሚያስረዳው፣ የአቶ በለጠ ሹመት የፀደቀው የዓባይ የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ጥያቄው ባቀረበ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ነው፡፡ ሹመቱ የፀደቀላቸው አዲሱ የዓባይ ባንክ ምክትል ፕሬዚዳንት ወደ ባንኩ ከመምጣታቸው ቀደም ብሎ፣ የቡና ኢንተርናሽናል ባንክ የቅርንጫፍ ማስተባበሪያ መምርያ ዳይሬክተር በመሆን ለስድስት ዓመታት ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡በባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ 25 ዓመታት ማገልገላቸው የተገለጸው አቶ በለጠ፣ ኢንዱትሪውን የተቀላቀሉት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በመቀጠር ነው፡፡ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሥር ዓመት የሠሩ ሲሆን፣ በኃላፊነት ደረጃም የባንኩ የቅርንጫፍ መመርያ ሥራ አስኪያጅ ሆነው ያገለግሉ እንደነበር የተገኘው መረጃ ያስረዳል፡፡ በአቢሲኒያ ባንክ ውስጥም በተመሳሳይ የኃላፊነት መደብ የቅርንጫፎች መምርያ ኃላፊና የቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ በመሆን ሲያገለግሉ እንደነበር ታውቋል፡፡አቶ በለጠ በኢኮኖሚክስ የመጀመርያ ዲግሪ፣ በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን ሁለተኛ ዲግሪ አላቸው፡፡በምክትል ፕሬዚዳንትነት የተሾሙበት ዓባይ ባንክ ከ3,300 በላይ ባለአክሲዮኖች ሲኖሩት፣ ከ90 በላይ ቅርንጫፎች አሉት፡፡
| 0 |
5f7408cb5b818f324df155edaca8ab07
|
5f7408cb5b818f324df155edaca8ab07
|
አበባው ቡታቆ ከአል ሂላል ጋር ተለያየ
|
የሱዳኑ ታላቅ ክለብ አል ሂላል ኢትዮጵያዊው የመስመር ተከላካይ አበባው ቡታቃን መልቀቃቸውን ዛሬ ይፋ አድርገዋል፡፡አበባው በክረምት የዝውውር መሰስኮት ቅዱስ ጊዮርጊስን ለቆ ወደ ሱዳን ካመራ ወዲህ በክለቡ ቋሚ ተሰላፊነትን ማግኘት ያልቻለ ሲሆን ክለቡን ለመልመድ እንደተቸገረም ተነግሯል፡፡ክለቡ ከደቂዎች በፊት እንዳስታወቀው ማሊያዊው ሱሌይማን ኮናቴ እና አበባው ቡታቆ ለክለቡ በቂ ግልጋሎት መስጠት ባለመቻላቸው ለመልቀቅ እንደወሰኑ ከመግለፁ ውጪ የተብራራ መግለጫ አላወጣም፡፡
| 1 |
fd974bc2f576f13c4adcec9a1b295122
|
fd974bc2f576f13c4adcec9a1b295122
|
በደቡብ ኦሮሚያ ጉጂና ሶማሌ ክልል የኮሌራ ወረርሽኝ ተከስቷል
|
24 ሰዎች በወረርሽኙ መሞታቸው ተገልጿል ከታህሳስ መጨረሻ ጀምሮ በደቡብ በሶማሌና በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን የኮሌራ በሽታ ወረርሽኝ መከሰቱን ዩኒሴፍ ያስታወቀ ሲሆን እስካሁን በበሽታው 24 ሰዎች መሞታቸው ተገልጿል፡፡በሪፖርቱ በተጠቀሱት የደቡብ፣ ሶማሌ ክልል ሸበሌ ዞንና በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን ባለፉት ሳምንታት ውስጥ 1045 ያህል የኮሌራ ህመምተኞች መመዝገባቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከፍተኛ የወረርሽኝ መጠን በተመዘገበው በደቡብ ክልል ማለትም በደቡብ ኦሞና ጎፋ ዞን ሲሆን 970 ሰዎች በበሽታው መያዛቸውንና በእነዚህ አካባቢዎች 18 ያህል ሕይወታቸው ማለፉ ተመልክቷል፡፡ በአካባቢዎቹ የተከሰተውን ድንገተኛ የኮሌራ ወረርሽኝ ለመቆጣጠር የአካባቢው አስተዳደሮችና የጤና አካላት፣ ጊዜያዊ የአደጋ መከላከል ኮሚቴ አዋቅረው እየተንቀሳቀሱ መሆኑንና በዚህ እርብርብ ላይም የአለም ጤና ድርጅትና የአለም ህጻናት አድንን ጨምሮ የተለያዩ አለማቀፍ ተቋማት እየተሳተፉ መሆኑ ተጠቁሟል - በሪፖርቱ፡፡ የኮሌራ ወረርሽኝ በአካባቢዎቹ መከሰቱን ተከትሎ፣ ወደ ሌሎች አካባቢዎች አድማሱን እንዳያሰፋ ከወዲሁ ለመከላከል የየክልሎቹ ጤና ቢሮዎችና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የቅድመ መከላከል ተግባር እያከናወኑ ነው ተብሏል፡፡ ባለፈው የፈረንጆች አመት (2019) ከቤንሻንጉል ጉሙዝና ከጋምቤላ ክልል ውጪ ባሉት ሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች ከ2074 በላይ የኮሌራ በሽታ ተጠቂዎች መመዝገባቸውንም ሪፖርቱ አስታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ ኮሌራ ፈተና እየሆነ የመጣው በማህበረሰብ አቀፍ የንጽሕናና ጤና አጠባበቅ ላይ በጥንካሬ ባለመሰራቱ መሆኑንም ሪፖርቱ አትቷል፡፡
| 1 |
4cbf3d080c13e8b6895dde3a136d95ef
|
4cbf3d080c13e8b6895dde3a136d95ef
|
በኢትዮጵያ በአንድ ቀን ብቻ 17 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው
|
አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 28 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት 24 ሰዓታት ለ1 ሺህ 382 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 17 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ።ሚኒስትሯ በፌስ ቡክ ገጻቸው እንዳስታወቁት ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ሁሉም ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ፥ አሁን ላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 162 ደርሷል።ቫይረሱ ከተገኘባቸው ውስጥ ሰባቱ ከጂቡቲ የተመለሱና በአፋር አስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውስጥ የነበሩ ሲሆኑ፥ ስድስቱ ደግሞ ከሶማሊያ የተመለሱና በሶማሌ ክልል አስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውስጥ የነበሩ ናቸው ተብሏል።አራቱ ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ ሲሆኑ፥ ሁሉም የውጭ ሃገር የጉዞ ታሪክ የሌላቸው ናቸው።ከእነዚህ ውስጥ የ27 አመቱ ወጣት የስራው ባህሪ ተጋላጭነት ያለው ሲሆን፥ የ28 አመቷ ወጣት እና የ53 አመቷ ሴት ደግሞ ቫይረሱ ከተገኘበት ሰው ጋር ግንኙነት ያላቸው ናቸው።የአፋር ክልል ነዋሪ የሆነውና አዲስ አበባ ከተማ የተገኘው የ39 አመቱ ኢትዮጵያዊ በቫይረሱ ከተያዘ ሰው ጋር ያለው ንክኪ እየተጣራ መሆኑ ተገልጿል።አሁን ላይ በኢትዮጵያ በለይቶ ህክምና ውስጥ ያሉ 63 ሲሆኑ፥ 93 ሰዎች ደግሞ ከቫይረሱ አገግመዋል ተብሏል።የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
| 1 |
98e1dccfb979f166053dcf36da1c9861
|
98e1dccfb979f166053dcf36da1c9861
|
አዳነ ግርማ ወደ አዲስ አዳጊው ቡድን ለማምራት ተስማምቷል
|
አዲስ አዳጊው ወልቂጤ ከተማ አዳነ ግርማን ወደ ቡድኑ ለመቀላቀል ስምምነት ላይ ሲደርስ ከተጫዋችነት በተጨማሪ ሌላ ሚና ሊሰጠው እንደሆነም ተገልጿል።የእግር ኳስ ህይወቱን በሀዋሳ ከተማ የጀመረው አንጋፋው ሁለገብ ተጫዋች በቅዱስ ጊዮርጊስ ቆይታው የብቃቱ ጫፍ ላይ የደረሰ ሲሆን ለብሔራዊ ቡድንም ወሳኝ ግልጋሎት አበርክቷል። ተጫዋቹ ከአስር ዓመት የጊዮርጊስ ቆይታው በኋላ አምና ወደ ሀዋሳ ተመልሶ መጫወት የቻለ ሲሆን አሁን ደግሞ በርካታ ተጫዋቾችን ወዳስፈረመው ወልቂጤ አምርቷል።አዳነ በአዲሱ ቡድኑ ከተጫዋችነት በተጨማሪ ሌላ ሚና ሊሰጠው እንደሚችል ታማኝ ምንጮች ለሶከር ኢትዮጵያ ገልፀዋል። ለአሰልጣኝ ደግአረገ ምክትል ለመቅጠር ተቃርቦ ከተመስገን ዳና ጋር ሳይስማማ የቀረው ክለቡ አዳነን የምክትል አሰልጣኝነት ሚና ሊሰጠው እንደሆነ ታውቋል።
| 1 |
ab623749cdeef1bc7013cfd6b83d1b3c
|
36b509a4b040231b012636c22cf5116a
|
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በንፁሃን ዜጐች ላይ በደረሰው ጥቃት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገለጸ
|
የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጣና በለስ የስኳር ፕሮጀክት ይሰሩ በነበሩ የትግራይ ተወላጆች ላይ የደረሰውን ጥቃት አውግዟል፡፡የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስትም በድርጊቱ የተሰማውን ሀዘን በመግለፅ፣ ጉዳዩን አጣርቶ አጥፊዎችን ለህግ ለማቅረብ ወደ ስፍራው የአመራርና ባለሙያዎች ቡድን መላኩን አስታውቋል።በፕሮጀክቱ ይሰሩ በነበሩ የትግራይ ተወላጆች ላይ በደረሰው ጥቃት ሶስት ንጹሐን ዜጎች ለህልፈት መዳረጋቸውን የትግራይ ክልል ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ትናንት ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ገልጿል፡፡በአማራ ክልል ጣና በለስ የስኳር ፕሮጀክት ላይ ይሠሩ በነበሩ የትግራይ ተወላጆች ላይ የደረሰው ጥቃት ህገ መንግስታዊ መብትና የሰዎች ነጻነትን የሚገፋ መሆኑን በመግለጽ አውግዘዋል፡፡“የሓሳብ ልዩነት ካለ ሰላማዊ በሆነ መንገድ መግለጽ እየተቻለ ዘርን በመለየት የሚደረገው ጥቃት በማንኛውንም መለኪያ ተቀባይነት ሊኖረው አይገባም “ብለዋል፡፡የክልሉ መንግስት በዜጎች ላይ የደረሰው ጥቃት መሪር ሀዘን እንደተሰማውና ለሟች ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝተዋል፡፡በዜጎች ላይ ጥቃት ያደረሱ ግለሰቦች ወደ ህግ እንዲቀርቡ የፌደራልና የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ወደ ህግ በማቅረብ አስተማሪ እርምጃ እንዲወስዱ ጠይቀዋል፡፡የትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ወደ አካባቢው ቡድን በመላክ ዝርዝር መረጃ ለማቅረብ ጥረት እንደሚያድርግ ጠቅሷል፡፡በሌላ በኩል የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን እንደገለጹት በአማራ ክልል በለስ ስኳር ፕሮጀክት በዜጎች ላይ በደረሰው ጉዳት የክልሉ መንግስት የተሰማውን ሀዘን ይገልጻል ፤ ጉዳዩን አጣርቶ አጥፊዎችን ለህግ ለማቅረብም ወደ ስፍራው የአመራርና ባለሙያዎች ቡድን ልኳል።በክልሉ ውስጥ የዜጎችን ማንነት መነሻ አድርጎ የሚደርስ ጉዳትም ሆነ ማንኛውም ጥቃት የክልሉ መንግስት አምርሮ እንደሚያወግዝና እንደሚታገለው የቢሮው ኃላፊ አቶ ንጉሱ አስታውቀዋል።
| 0 |
c3c65849de50330a0ee6cc7324c28992
|
8e839abd70d9c21e0da339769c48092c
|
የተመድ ዋና ጸሐፊ በኢራቅ ውጊያ ለሲብሎች ከለላ ይደረግ አሉ
|
የሀገሪቱ መከላከያ መስሪያ ቤት ፔንታጎን የአሜሪካ ወታደሮች ኢራቅን ለቀው ይወጣሉ መባሉን አስተባብሏል፡፡
እንደ ሮይተርስ ዘገባ ከሆነ የፔንታጎን ዋና ጸሃፊው ማርክ ኢስፐር ሃገራቸው ወታደሮቿን ከኢራቅ የማስወጣት ዕቀድ እንደሌላት ተናግረዋል፡፡
ሆኖም ግን ከሰሞኑ የውጭ ሃገራት ወታደሮች ኢራቅን ለቀው እንዲወጡ የሀገሪቱ ባለስልጣናት ወስነዋል በሚል እነ ሮይተርስ ጭምር ዘግበው እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡
የረጅም ጊዜ ተቃናቃኞቹ ቴህራንና ዋሽንግተን በፕሬዘዳንት ትራምፕ ትእዛዝ የኢራኑ መታደራዊ አዛዥ ካሴም ሱሌማኒ ኢራቅ ውስጥ ከተገደሉ በኋላ የቃላት ጦርነት ውስጥ ገብተዋል፡፡
ጄነራል ካሴም ሱሌማኒ በኢራቅ ዉስጥ ከመንፈሳዊ መሪው አያቶላህ አሊ ካሚኒ ቀጥሎ ተጽእኖ ፈጣሪ መሆናቸው ተነግሯል፡፡
የኢራን ጄነራል በአሜሪካ ወታደራዊ ዘመቻ በኢራቅ ምድር ከተገደሉ በኋላ ነበር ኢራቅ በሀገሪቱ የሚገኙ የውጭ ወታደሮች እንዲወጡ በሀገሪቱ ፓርላማ በኩል የወሰነችው፡፡
ቴህራን የበቀል እርምጃ የምትወስድ ከሆነ፣ አሜሪካ በኢራን ላይ ተጨማሪ ማእቀብ እንደምትጥልና የኢራንን ቅርሶችን ኢላማ ያደረገ ጥቃት እንደምትሰነዝርም አስታውቀም ነበር፡፡
| 0 |
84e560fe384ff4d49b7a699b03800229
|
8b01e055d98986b6f89f7c0df5501bcf
|
ዋትስአፕ የኢንተርኔት ቀበኞችን መቆጣጠሪያ ዘዴውን አጠበቀ
|
በየዓመቱ የሚካሔደው እና ዘንድሮ ለስድስተኛ ጊዜ የሚደረገው ዓመታዊው የኢንተርኔት ነፃነት በአፍሪካ ፎረም በኢኖቬሽና ቴክኖሎጂ ሚንስቴር ተባባሪ አዘጋጅነት በአዲስ አበባ ይካሔዳል። ከኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ፎረሙ በቀጣዩ ዓመት 2012 መስከረም ላይ እንደሚካሔድ የታወቀ ሲሆን በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል 3 መቶ ተሳታፊዎችን ከመላው አፍሪካ እንደሚያሳትፍም ይጠበቃል።ከኢንተርኔት ነፃነት በአፍሪካ ጋር በተያያዘ ከሚደረጉ ውስን መወያያ አጋጣሚዎች አንዱ የሆነውን ይህን ፎረም ከሌሎች ባለ ድርሻ አካላት ጋር በጋራ በማዘጋጀቱ ትልቅ ኩራት እንደሚሰማው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚንስቴር ገልጿል። ፎረሙ በኢትዮጵያ የቴሌኮም ምኅዳሩ ላይም ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት ተጠቁሟል።
| 0 |
e0d41f4c085907a39e55feb5732b99b2
|
ad6fea9588619dda3584e2677caf0a72
|
ጠ/ሚ ዐቢይ የፈጠራ ሐሳቦች ላደረሱ ወገኖች ምስጋና አቀረቡ
|
አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በለንደን በተካሄደው የወንዶች ማራቶን አሸናፊ ለሆኑ አትሌቶች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትዊተር ገፃቸው ላይ በለንደን ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አስደናቂት ውጤት አስመዝግበዋል ሲሉ አስፍረዋል።አትሌት ሹራ ቅጣታ የ2020 የለንደን ማራቶንን በማሸነፉ እንኳን ደስ መልዕክት አስተላልፈዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በሄዳችሁበት ሁሉ የሀገራችንን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጋችሁ የምታውለበልቡ ጀግኖች ሯጮቻችን ሁሉ አድናቆቴ ይድረሳችሁ ፤ ሀገራችን ትኮራባችኋለች ብለዋል ባስተላለፉት መልዕክት።ሲጠበቅ የነበረውን የለንደን ማራቶን ኢትዮጵያዊው ሹራ ቅጣታ ቶላ ሲያሸንፍ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ ሲሳይ ለማ ሶስተኛ ደረጃን ማጠናቀቁ የሚታወስ ነው።ሹራ ቅጣታ ቶላ 2 ሰዓት ከ5 ደቂቃ ከ41 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ነው ውድድሩን ያሸነፈው።ኢትዮጵያውያን ሞስነት ገረመው ፣ ሙሌ ዋሲሁን እና ታምራት ቶላ ከ4 እስከ 6ኛ ያለውን ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል።
| 0 |
34591da46c94794f3bfb28ce5bd10854
|
461a4757db1980f13ca1f82d97f4b1c1
|
ኢትዮጵያ ከዓለም የንግድ ድርጅት አባልነት ብዙ እንደምታተርፍ ተገለጸ
|
የኢፌደሪ ፕሬዚዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት በማድረግ ላይ የሚገኙትን የፖላንድ ፕሬዚዳንት አንድሬ ዱዳን በብሄራዊ ቤተ መንግስት ተቀብለው አወያይተዋል ፡፡በቀጣይም በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ማህበራዊ ጉዳዮች የሁለቱን ሀገራት ትስስር ለማጎልበት የበኩላቸውን ለመጫወት መሪዎቹ ከመግባባት ደርሰዋል።ፕሬዚዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ከውይይቱ በኋላ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በአሁኑ ወቅት በሁለቱ ሃገራት መካከል ያለው የንግድ ግንኙነት36 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር መድረሱን ጠቁመው ይህ ከዚህ የበለጠ ሊያድግ እንደሚገባው አመልክተዋል ።ፕሬዚዳንት አንድሬ ዱዳ በበኩላቸው ጉብኝቱ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የዲፕሎማሲና ፖለቲካዊ ማእከል መሆኗ የፖላንድ መንግስትና ህዝብ እንደሚያምን ነው የገለጹት ።የሁለቱም ወዳጅ ሀገራት ግንኙነት ረዥም አመት ያስቆጠረ ቢሆንም የዚያ ያህል ግን እድገቱ ጠንካራ ባለመሆኑ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙት እንዲያድግ ፍላጎት እንዳላቸው አስታውቀዋል ፡፡ስለሆነም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ንግድ ልውውጥም በመቶ ሚሊየን ወደ ሚቆጠሩ የአሜሪካ ዶላሮች ከፍ ለማድረግ እንደሚሰሩም ጠቁመዋል።ፕሬዚዳንት አንድሬ ዱዳ ፖላንድ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2018/19 በመንግስታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ለምታደርገው የተለዋጭ አባልነት ምርጫ ኢትዮጵያ ድጋፍ እንድታደርግላቸው ጠይቀዋል።ፕሬዚዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ጥያቄውን እንደምታጤነውና ወደፊት እንደምታሳውቅ ገልጸዋል ።
| 0 |
128b43bcc2fc309e51114289096d034f
|
128b43bcc2fc309e51114289096d034f
|
ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የምጣኔ ኃብት ማሻሻያ ለማድረግ ቃል ገቡ
|
ፈረንሣይን ሲንጣት ከከረመው ፀረ-መንግሥት ተቃውሞ በኋላ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ዛሬ ለመጀመሪያ ጊዜ ወጥተው ባደረጉት ንግግር በርካታ የምጣኔ ኃብት ማሻሻያ ቃሎች ገብተዋል። ይሁን እንጂ ሥልጣናቸውን እንደማይለቅቁ ተናግረዋል።“በርግጥ ሰዎችን በንግግሮቼ አስቀይሜ ሊሆን ይችላል፤ ለዚህ የራሴን ኃላፊነት እወስዳለሁ” ብለዋል ማክሮን በዛሬው ንግግራቸው።የግብር ጭማሪ ሃሣባቸውም “ፍትሃዊ አይደለም” ሲሉ አምነዋል። ይሁን እንጂ የሰሞኑ ቁጣ የገነፈለው ላለፉት አርባ ዓመታት በተለይ በገጠሪቱ ፈረንሣይ ሲንተከተክ ከቆየ በኋላ ነው ብለዋል።
| 1 |
5e63a9b07d803385874b4c9b97b10f5a
|
4fb6fdda94d47e63f73fdcfd149f2657
|
በስሪንጅ እጥረት የተቋረጠው የክትባትአገልግሎት መስተካከሉ ተገለጸ
|
ሩሲያ በናይጄሪያ ሁለት ግዙፍ ማብላያዎችን ለመገንባት የሁለትዮሽ ስምምነት ማድረጋቸው ተገለጸ ፡፡የአፍሪካ ኢኮኖሚ ትልቁ የናይጄሪያ ኢኮኖሚ እያጋጠመው ያለውን የሀይል እጥረት ይቀርፋሉ የተባሉት ፕሮጀክቶች በሀገሪቱ ደቡባዊና ማዕከላዊ ስፍራዎች ላይ እንደሚገነቡ የናይጄሪያ አቶሚክ ሀይል ኮሚሽን ለቢቢሲ ገልጿል፡፡ትክክለኛው የፕሮጀክቶቹ ወጭ ባይታወቅም እስከ 20 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር እንደሚገመት የሀገሪቱ ብዙኋን መገኛዎች ዘግበዋል፡፡ ግንባታውን የሚያካሂደው የሩስያ ድርጅት ከ ደቡብ አፍሪካና ጋና ጋርም ድርድር ስለመጀመሩ ታውቋል፡፡ከናይጄሪያ ጋር የተደረገው ስምምነት ድርድሩ የተጀመረው እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር 2009 ላይ ነው ፡፡ይህ ረጅም ግዜ የፈጀው የሁለቱ ሀገራት ድርድር ከዳር የደረሰው ሁለቱ ሀገራት በኒውክለር ፕሮግራም አብረው ለመስራት መስማማታቸውን ተከትሎ ነው፡፡ማብላያዎቹ በቀጣይ ሁለት አመታት ግንባታቸው ይካሄዳል ሲል የዘገበው ቢቢሲ ነው፡፡
| 0 |
f2759684678c4150a73d4e756ca20da4
|
6f71dd583fc23c74859fee524df5595c
|
ጣሊያን በፈንሳይ የውስጥ ጉዳይ የምታደርገውን ጣልቃ ገብነት እንድታቆም ፈረንሳይ አስጠነቀቀች
|
አዲስ አበባ ፣ሰኔ 16 ፣2012 (ኤፍ.ቢሲ) የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋችው ከጣሊያን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሉይጊ ዲማዮ ጋር ዛሬ በስልክ ተወያይተዋል።ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው የሁለቱን አገሮች ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው እና ኮቪድ 19ን በጋራ መግታት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ በትብብር ለመስራት ከመስማማታቸውም ባለፈ ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ መረጃ መለዋወጣቸው ተገልጿል።አቶ ገዱ በዚሁ ወቅት ጣሊያን የኢትዮጵያን ሪፎርም በመደገፍ እያደረገች ላለችው የልማት እርዳታ አመስግነው÷ በቀጣይም ኢትዮጵያ ከጣሊየን ጋር ያላትን ሀሉን አቀፍ ግንኙነትም ይበልጥ ለማጠናከር ትስራለች ብለዋል።በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ምክንያት በዓለም ላይ በጠፋው የሰው ህይወት የተሰማቸውን ሃዘን የገለጹት ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ለመግታት እያደረገች ያለውን እንቅስቃሴ በተመከለተም ገለጻ አድርገዋል።ኢትዮጵያ ወረርሽኙን ለመከላከል ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እና ከጣሊያን መንግስት ጋር በትብብር መስራቷን እንደምትቀጥልም ገልጸዋል።አያይዘውም የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የደረሰበትን ደረጃ እና ኢትዮጵያ፣ ግብጽና ሱዳን እያደረጉት ያለውን ውይይት በተመለከተም አቶ ገዱ ለጣሊያኑ አቻቸው ማብራሪያ ሰጥተዋል።የጣሊያን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክሉይጊ ዲማዮ በበኩላቸው÷ ጣሊያን ከኢትዮጵያ ጋር ላላት ግንኙነት ልዩ ትኩረት እንደምትሰጥና ግንኙነቱን ይበልጥ ለማጠናከር እንደምትሰራ ገልጸዋል።ዓለም አቀፍ ስጋት የሆነውን የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ለመግታት ጣሊያን ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር እንደምትሰራና የምታደርገውን የልማት ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥልም ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል።የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንበታ የሶስቱንም አገሮች ጥቅም ባማከለ መልኩ በውይይት እንዲፈታ ጣሊያን ታበረታታለችም ማለታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል ቀባይ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል ። #FBCየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
| 0 |
07e6c957050738f40f42885d7ffcb15f
|
38108ac0258e27bd008079efc19d01d7
|
የግሉ ዘርፍ ፈጠራ በታከለበት መንገድ ምርቶችን በማዳበር በቡና ኢንዱስትሪው ቢሰማራ የላቀ ውጤት ያስገኛል- ጠ/ሚ ዐቢይ
|
አዲስ አበባ፣ መስከረም 1፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በቪዲዮ በተካሄደው የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ጉባኤ ላይ ተሳተፉ።ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጉባኤው ላይ የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን እና ፈጠራ የታከለበት እንዲሆን ለማስቻል ብዙ ሥራ እንደሚጠይቅ በዚህ ጉባኤ ላይ አንስተዋል።እስካሁንም ቢሆን በነበሩ ጠንካራ ጎኖች ላይ በመመርኮዝ በአስደናቂ ሁኔታ በዘርፉ ገስግሰናል ነው ያሉት።በቴክኖሎጂ እና በፈጠራ አማካኝነት፣ የመንግሥት መዋዕለ ንዋይ ከተጠናከረ የግል ዘርፍ ተሳትፎ ጋር ተዳምሮ የግብርናውን ዘርፍ ግሥጋሴን እንደሚያፋጥን ገልፀዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ ከቪዲዮ ኮንፍረንሱ በኋላ በፌስቡክ ገፃቸው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት በሩዋንዳ ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ አስተባባሪነት በተካሄደው የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ጉባኤ ላይ ጠቃሚ እሳቤዎችን ለማጋራት በመቻላቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል።
| 0 |
c1fa1e8b4e1941dacc9e0e7d2691a57e
|
c1fa1e8b4e1941dacc9e0e7d2691a57e
|
የጤና ዘርፍ ባለሙያዎችና አመራሮች በትግራይ ክልል የሚገኙ የጤና አገልግሎት መስጪያ ተቋማትን ጎበኙ
|
በመቐለ ከተማ በሚካሄደው 20ኛው የጤና ዘርፍ ዓመታዊ ጉባኤ የሚሳተፉ የጤና ዘርፍ ባለሙያዎች፣ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት በትግራይ ክልል የሚገኙ የተለያዩ የጤና አገልግሎት መስጫ ተቋማትን ጎበኙ ። የጤና ዘርፉ ባለሞያዎች፣ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት በትግራይ ክልል ህብረተሰቡን የተሻለ ተጠቃሚ ለማድረግ የተሠሩትን የተለያዩ የጤና አገልግሎት መስጫ ተቋማትን ጎብኝተዋል፡፡በመስክ ምልከታ ወቅትም በክልሉ በጤና ዘርፍ የሚገኘውን ተሞክሮ በመውሰድ በቀጣይ ለሚዘጋጁ እቅዶችና ለችግሮች አፈታት በግብአትነት ለመጠቀም የሚረዳ መሆኑን በጉብኝቱ ወቅት ተነሰቷል፡፡በትግራይ ክልል በጤና አገልግሎት መስጪያ ተቋማት ላይ በተደረገው የመስክ ጉብኝትም የፊደራል ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሚኒስትሮች የክልል የጤና ቢሮ ኃላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላትም ተሳትፈዋል፡፡ለ20ኛ ጊዜ በሚካሄደው ሀገር አቀፍ የጤና ዘርፍ ጉባኤ ክልሎች ባለፈው በጀት አመት ያከናወኗቸው ተግባራትን ሪፖርት በማቅረብ ውይይት የሚያካሂዱበት መድረክ ይሆናልም ተብሎ ይጠበቃል፡፡“ሁሉን አቀፍ የጤና ሽፋን ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ጠንካራ የጤና ስርአት መገንባት ” በሚል መሪ ቃል የሚከናወነው 20ኛው ሀገር አቀፍ የጤና ዘርፍ ጉባኤ በመቐለ ከተማ ከህዳር 14 እስከ 16 ድረስ ለሦስት ቀናት ይከናወናል ፡፡20ኛው የጤና ዘርፍ ዓመታዊ ጉባኤ በዛሬው ዕለት በመቐለ ከተማ የተጀመረ ሲሆን ከፌደራል የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ፣ የክልሎች የጤና ቢሮ ኃላፊዎች ፣ ባለድርሻ አካላትና የጤና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛል ።
| 1 |
2cacbf3cfdc751527f704ccc601601e2
|
2cacbf3cfdc751527f704ccc601601e2
|
ካፍ በዚህ ሳምንት የኢትዮጵያ ስታዲየሞች የጥራት ደረጃ ይመዝናል
|
ካፍ ለትግራይ እና ለባህር ዳር ስታዲየሞች የሰጠው ቀነ ገደብ በዛሬው ዕለት ሲጠናቀቅ በድጋሚ ፈቃድ ለማግኘት በቀጣይ ቀናት ይመዘናሉ።ከወራት በፊት ካፍ ለሁለቱም የኢትዮጵያ ስታዲየሞች አህጉራዊ ጨዋታዎች እንዲያስተናግዱ በሁለት ወራት በቀነ ገደብ ፍቃድ መስጠቱ ይታወሳል፤ በስታዲየሞቹ ሊሟሉ የሚገባቸው ነገሮች በመጥቀስ የሁለት ወራት የተሰጠው ቀነ ገደብም ዛሬ ተጠናቋል። ይህን ተከትሎ የካፍ አባላት በዚህ ሳምንት ስታዲሞሞቹ ያሉበት ወቅታዊ ሁኔታን የሚመዝኑ ሲሆን የባህር ዳር ሐሙስ፣ የትግራይ ስታድየም ደግሞ ከዓርብ በኃላ ባሉት ቀናት በካፍ ሃላፊዎች እንደሚጎበኙ ይጠበቃል።የካፍ ፍቃድ ካገኘ በኃላ ሁለት ጨዋታዎች ያስተናገደው የትግራይ ስቴድየም በዚህ ሰዓት የሳር ማስተካከል፣ የአጥር፣ የመግቢያ በር እና ሌሎች እድሳቶች እየተደረጉበት ሲገኝ የባህር ዳር ስቴድየም ደግሞ ከባለፈው ይዞታው በተሻለ የድህንነት ካሜራን ጨምሮ በርካታ መሻሻሎች አድርጎ የካፍ ምዘናን እየተጠባበቀ ይገኛል።
| 1 |
2da866d7253965bd13419296f28c0452
|
bafe68168a345892605686abb38ea182
|
የቀድሞው የሰማያዊ ፓርቲ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጥፋተኛ ተባለ
|
ከፍተኛ የአመራር አባሉ አቶ አብረሃ ደስታ ባለፈው ሣምንት መቀሌ ውስጥ ተይዘው በፖሊስ ከተወሰዱ በኋላ የተወሰዱበትን ማወቅ አለመቻሉን አረና ትግራይ ፓርቲ ባለፈው ሣምንት አስታውቆ ነበር፡፡አባሉ የተያዙበትን እሥር ቤት ሰሞኑን ማረጋገጡን የገለጠው አረና ጠበቃ የማማከር ሕገመንግሥታዊ መብታቸው ግን ተነፍጓል ሲል ፖሊስን ከስሷል፡፡በሌላ በኩል ደግሞ ባለፈው ሣምንት በተመሣሣይ ሁኔታ የተሠሩ የተለያዩ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች መሪዎች የአንድነቱ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሃብታሙ አያሌው፤ የድርጅት ጉዳይ ምክትል ኃላፊው አቶ ዳንኤል ሺበሺና የሰማያዊ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ አቶ የሺዋስ አሰፋ እስከአሁን ፍርድ ቤት ያለመቅረባቸውን ድርጅቶቹ አስታውቀዋል፡፡ተከሣሾች በ48 ሰዓታት ውስጥ ፍርድ ቤት የመቅረብ ሕገመንግሥታዊ መብታቸው ያለመከበሩን መሠረት ያደረገው የተከሣሾች ጠበቃ በበኩሉ በመሠረተው አካልን ነፃ የማድረግ አቤቱታ ወይም ሃቢየስ ኮርፐስ የሕግ ሂደት የያዛቸው ክፍል ቀርቦ መልስ እንዲሰጥ ለነገ፣ ማክሰኞ ሐምሌ 8/2006 ዓ.ም አዝዟል፡፡ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
| 0 |
4e9ab045918276fd8321f98f70e00ecb
|
4e9ab045918276fd8321f98f70e00ecb
|
የለውጥ አመራር ሰጭነት ስልጠና በባሕር ዳር እየተሰጠ ነው፡፡
|
የለውጥ አመራር ሰጭነት ስልጠና በባሕር ዳር እየተሰጠ ነው፡፡ለክልሉ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ራሳቸውን አውቀው ለሌሎች መንገድ እንዲያሳዩ የሚያስችል ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ለአማራ ክልል ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ከዛሬ ጀምሮ ለሦስት ቀናት የሚቆይ የአሻጋሪ አመራር ሰጭነት (ትራንስፎርሜሽናል ሊደርሽፕ) ስልጠና በባሕር ዳር ከተማ እየተሰጠ ነው፡፡የስልጠናው ዓላማ የክልሉ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች አቅማቸውን ፈትሸው ስለተቋማዊ ዕድገት እና ተግባቦት ክህሎት ግንዛቤ መፍጠር ነው፡፡ ልማትን፣ ሠላምን እና አብሮነትን በማስጠበቅ የኢትዮጵያን መፃዒ ዕድል የተሻለ ለማድረግ በሚመሩት ሕዝብና ሠራተኞች መካከል መነቃቃት እንዲፈጥሩ ያስችላቸዋል ተብሏል፡፡በሀገሪቱ ከዘመናት በፊት የነበረው አንድነት እና መተሳሰብ እየቀነሰ መምጣቱን ተከትሎ በስልጠና የመሪዎችን የአዕምሮ ውቅር ማስተካከል ተገቢ መሆኑን የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር በዛብህ ገብረየስ ተናግረዋል፡፡በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን አስተባባሪነት የሚሰጠውን ስልጠና ‹ጴጥሮስ ኔትወርክ› የሚባል በየአሜሪካን ድርጅት እና ‘ፎርድ ቴይለር ግሩፕ’ አማካኝነት የሚሰጥ ነው፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ በስፋት እየተቀነቀነ ያለውን አሻጋሪ አመራር ሰጭነት (ትራንስፎርሜሽናል ሊደርሽፕ) ጸሐፊ እና መሥራች ፎርድ ቴይለር ስልጠናውን ይሰጣሉ፡፡
| 1 |
7da371c3899e35e3703e28fd25f8fbbc
|
71559df0de11a09e3f2205402d759685
|
በሀዋሳ ከተማ በ1ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር የዘይት መጭመቂያ ፋብሪካ ሊገነባ ነው
|
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ በቦሌ ክፍለ ከተማ በ2.06 ቢሊዮን ብር ሆስፒታል ሊያስገነባ ነው፡፡ ጨረታውን ካሸነፈው አፍሮ ጽዮን ኮንስትራክሽን ኩባንያ ጋር የግንባታ ውል ተፈራርሟል፡፡ወራት ባስቆጠረው የጨረታ ውድድር ዝቅተኛውን ዋጋ በማቅረብ ስምምነቱን የተፈራረመው አፍሮ ጽዮን፣ ሆስፒታሉን ገንብቶ ለመጨረስ ሦስት ዓመት ይፈጅበታል ተብሏል፡፡ስምንት ፎቅ ይኖረዋል የተባለው ሆስፒታል ተገንብቶ ሲያልቅ 740 የመኝታ ክፍሎች ይኖሩታል ተብሏል፡፡ በተጨማሪም ሆስፒታሉ የሔሊኮፕተር ማሳረፊያና 1,000 ተሽከርካሪዎችን የሚያስተናግድ ቦታ እንደሚኖረው ተገልጿል፡፡እንዲሁም ሆስፒታሉ የአስታማሚዎች ማረፊያና ሌሎች አገልግሎት መስጫ ተቋማት እንደሚኖሩት ታውቋል፡፡በ31 ሺሕ ካሬ ሜትር ላይ የሚያርፈውን ሆስፒታል ለመገንባት ከቻይና ኩባንያዎች ጋር ተወዳድሮ ያሸነፈው አፍሮ ጽዮን ኮንስትራክሽን ኩባንያ፣ ከተፎካካሪዎቹ የተሻለ ዋጋ በማቅረብ ጨረታ ማሸነፉ ይታወሳል፡፡ከ20 ዓመት በፊት በአቶ ሲሳይ ደስታ (ኢንጂነር) የተመሠረተው ይኼ ኩባንያ፣ አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት ታዋቂ የኮንስትራክሽን ኩባንያዎች አንዱ ነው፡፡ኩባንያው ሲመሠረት 50 ሺሕ ብር የመነሻ ካፒታል የነበረው ሲሆን፣ በአሁኑ ጊዜ ግን በዓመት ቢሊዮን ብሮችን ያንቀሳቅሳል፡፡በቦሌ ክፍለ ከተማ የሚገነባው ሆስፒታል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለመገንባት ካሰባቸው ሦስት አጠቃላይ ሆስፒታሎች አንዱ ሲሆን፣ በንፋስ ስልክና በኮልፌ ክፍላተ ከተሞች ይገነባሉ የተባሉት ሁለት ሆስፒታሎች በጨረታ ሒደት ላይ ይገኛሉ፡፡ሦስቱም ሆስፒታሎች ተገንብተው ሲያልቁ በዓመት አንድ ሚሊዮን ታካሚዎችን ያስተናግዳሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
| 0 |
5c898797ac9dd88a7cd533bcee4a3939
|
5c898797ac9dd88a7cd533bcee4a3939
|
ኢትዮጵያ ዕድገት የምታመጣው የኃይል ማመንጫና የመስኖ ግድቦቿን ቁጥር ስታሳድግ መሆኑን ምሁራን አሳሰቡ።
|
ባሕር ዳር፡ ግንቦት 30/2012 ዓ.ም (አብመድ) በዓባይ ወንዝ አጠቃቀም እና በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ላይ ያተኮረ ውይይት በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ትናንት ተካሂዷል።በውይይቱ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሲቪልና ምሕንድስና ፋኩሊቲ ረዳት ፕሮፌሰር ዳኛቸው አክሎግ (ዶክተር) የኢትዮጵያን የውኃ መጠን፣ የሀብት አጠቃቀም እና ዓለም ዓቀፍ ተሞክሮዎችን መሠረት ያደረገ የውይይት መነሻ ሐሳብ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ ባላት ፀጋ ልትለማ የምትችለው የግድቦቿን ቁጥር ስታሳድግ እና ውኃዋል ለልማት ስታውል መሆኑ ባቀረቡት የውይይት መነሻ ሐሳብ አመላክተዋል።ዶክተር ዳኛቸው እንዳሉት ኢትዮጵያ ካላት መልክአ ምድር፣ ተፈጥሯዊ አቀማመጥ እና ችሮታ አንጻር ከውኃ እና አፈር ውጭ ብዙ የተፈጥሮ ሀብት የላትም። ምንም እንኳን ኢትዮጵያ የውኃ ማማ እየተባለች ብትጠራም የውኃ ሀብት አጠቃቀሟ ካላት የሕዝብ ብዛት ጋር ሲነጻጸር እጥረት እንዳለበት አስገንዝበዋል። ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መለኪያ መስፈርት መሠረት የውኃ እጥረት ያለባቸው በሚባልበት ደረጃ ላይ እንደምትገኝም አመላክተዋል።የሀገሪቱ ውኃ በብዛት የሚመነጨው በምዕራባዊ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ነው። ኢትዮጵያ ካላት አጠቃላይ ውኃ መካከል ደግሞ ወደ ዓባይ የሚፈስሱት ወንዞች 70 በመቶውን ይሸፍናሉ። እነዚህ ወንዞች ሀገር አቋርጠው የሚስሱ ናቸው፤ የኢትዮጵያ የመጠቀም ሁኔታ ግን በጣም አናሳ ሆኖ መቆየቱን ጠቁመዋል፡፡በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በዝናብ ተኮር ግብርና ላይ የተመሠረተ ነው። አብዛኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች በተለይም ምሥራቅ እና ሰሜን ምሥራቅ ኢትዮጵያ አካባቢዎች በቂ ዝናብ የማያገኙ ናቸው። በዚህ የተነሳም ሕዝብ ለተደጋጋሚ ድርቅ እና ረሀብ እንደተጋለጡ በማብራሪያቸው አሳይተዋል።
| 1 |
f9018f0ba2ad90eb57e9fec39ab29cc1
|
66599c5eca72e95cb23febb2ef28f9e3
|
ብሄራዊ የስፓርት ፌዴሬሺኖች እዉቀት ባላቸዉ ሰዎች መመራት አለባቸው
|
ፍኖተ ካርታው እስከዛሬ ባለመኖሩ የአገሪቱ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፉ ላለፉት 50 ዓመታት ሳያድግ ቀርቷል ተብሏል፡፡የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርና የመንግስት የልማት ድርጅቶች ሚኒስቴር በጋራ ባዘጋጁት የቴክኖሎጂ ፍኖተ ካርታ ውይይት የኢትዮጵያን ቴክኖሎጂ በተደራጀ መልኩ ለማሳደግ ዘርፉ በፍኖተ ካርታ መመራት እንዳለበት ተገልጿል፡፡በተበጣጠሰ መንገድ ሲመራ የነበረው የቴክኖሎጂው ዘርፍ ኢትዮጵያ ከቴክኖሎጂው እንዳትጠቀም ከማድጉም ባሻገር ማግኘት የነበረባትን የውጭ ምንዛሬ አሳጥቷታል ተብሏል በውይይቱ ፡፡በፍኖተ ካርታው 20 ተቋማትን ያቀፈ ሲሆን 12ቱ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ናቸው፡፡
| 0 |
b54fbe0bd1a1667fb2f76fc35210c633
|
a9b120334a036561b8fc455ce5f0c99b
|
“የሳላዲን ውሳኔ ተጫዋቹን እንድናከብረው የሚያደርግ እንጂ የሚያስወቅሰው አይደለም” አሰልጣኝ ዮሃንስ ሳህሌ
|
አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ከወልዋሎ ዓ/ዩ ጋር እንደሚቀጥሉ ተረጋግጧል።
ከትናንት በስቲያ ወልዋሎዎች ከዋና አሰልጣኛቸው ዮሃንስ ሳህሌ ጋር ለመቀጠል መስማማታቸው መግለፃችን ይታወሳል። ትናንት ደግሞ ክለቡ ከአሰልጣኙ ጋር በይፋ በመፈራረሙ አሰልጣኙ እስከ ቀጣዩ የውድድር ዓመት መጨረሻ ድረስ ከቡድኑ ጋር እንደሚቆዩ ተረጋግጧል። በጥር ወር ቡድኑን ተረክበው የስድስት ወራት ቆይታ ያደረጉት አሰልጣኙ ከወዲሁ ለቀጣይ ዓመት ስራዎችን መጀመራቸው ሲታወቅ ከዛሬ ጀምሮ ተጫዋቾች ለማስፈረም እንቅስቃሴዎች እንደሚጀምሩ ይጠበቃል።ባለፉት ዓመታት በፕሪምየር ሊጉ ደደቢት ፣ መቐለ 70 እንደርታ እና ድሬዳዋ ከተማን ማሰልጠን የቻሉት አሰልጣኝ ዮሐንስ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ከወልዋሎ ጋር በነበታቸው ቆይታ ለአዲስ አዳጊዎቹ ሠመረ ሃፍታይ ፣ ስምዖን ማሩ እና ሽሻይ መዝገቦ የመጫወት ዕድል በመስጠታቸው ከደጋፊው ተቀባይነት ማግኘታቸው ይታወሳል።
| 0 |
724434621b54b5f5e7c776ad62121705
|
0b0ba727b4ce130776bb0a2265cb6b41
|
ሳምሰንግ ከፔሌ የ30 ሚ ዶላር ክስ ቀረበበት
|
የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ በመንግሥትና በሕዝብ ላይ ከ768.7 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት አድርሰዋል በማለት በቀድሞ የኢትዮ ቴሌኮም የቀድሞ ኤንጂፒኦ ዳይሬክተር ላይ አቅርቦ የነበረውን ክስ አሻሽሎ አቀረበ፡፡ ዓቃቤ ሕግ ክሱን ያሻሻለው ክስ የተመሠረተባቸው አቶ ኢሳያስ ዳኘው ቀደም ብሎ በቀረበባቸው ክስ ላይ ያቀረቡትን የቅድመ ክስ መቃወሚያ፣ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 15ኛ ወንጀል ችሎት በመቀበሉና ክሱ እንዲሻሻል ትዕዛዝ በመስጠቱ ነው፡፡ዓቃቤ ሕግ በመጀመርያ ክሱ ላይ አቶ ኢሳያስ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 33 እና 411 በመተላለፍ፣ በልዩ ወንጀል ተካፋይ በመሆንና የመንግሥትን ሥራ በማያመች መንገድ መርተዋል በማለት ሁለተኛ ክስ አድርጎ አቅርቦባቸው ነበር፡፡ ነገር ግን ፍርድ ቤቱ እንዲያሻሽል በሰጠው ትዕዛዝ ‹‹ከግብረ አበሮቻቸው ጋር በመሆን›› የሚለውንም በመተውና አንቀጹንም ወደ ወንጀል ሕግ አንቀጽ 32 እና 407 በመቀየር፣ ሥልጣንን ያላግባብ መገልገል ወንጀል በማለት አሻሽሎ አቅርቧል፡፡ በመሆኑም አቶ ኢሳያስ ሥልጣናቸውን ያላግባብ በመጠቀም፣ ራሳቸውን ለመጥቀምና ዜድቲኢ የተባለውን የቻይና ቴሌኮም ኩባንያ ለመጥቀም ግዥ እንዲፈጽም ማድረጋቸውን አካቶ ቀርቧል፡፡ ለዩኒቨርሲቲዎች የኔትወርክ ግንባታ አገልግሎት ያለ ጨረታና ከተቋሙ የግዥ መመርያ ውጪ የ44,510,971 ዶላር ወይም 768,704,469 ብር ግዥ እንዲፈጸም በማድረግ፣ በተቋሙ ላይ ጉዳት አድርሰዋል በማለት ክስ ዓቃቤ ሕግ ማቅረቡን መዘገባችን ይታወሳል፡፡የተሻሻለውን ክስ የተቀበለው ፍርድ ቤቱ ለተከሳሹ እንዲደርሳቸው ካደረገ በኋላ፣ በተሻሻለው ክስ ላይ አስተያየት ካላቸው ለመጠባበቅ ለሐሙስ መጋቢት 12 ቀን 2011 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
| 0 |
54491934543b9947b065c8bce54ce18d
|
2484ae7f4295769c0b46118b8f65c001
|
አሜሪካ ማክስን አወረደች
|
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ ሀገራቸው ከውጭ በሚገቡት የብረት ምርቶች 25 ከመቶ በአሉሚኒየም ምርቶች ደግሞ 10 ከመቶ ቀረጥ ለመጣል በወሰደችው ውሳኔ እንደምትጸና ትላንት ተናግረዋል። የፖለቲካና የዲፕሎማሲ አጋሮች እንዲሁም የዩናይትድ ስቴትስ ኩባንያዎች አሜሪካ የንግድ ጦርነት ሊያስከትል የሚችል ፖሊሲን እንዳትከተል ጫና እያደረጉ ናቸው።ፕሬዚዳንት ትረምፕ ትላንት ከእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኒታንያሁ ጋር ተገናኝተው ከመነጋገራቸው በፊት አዲስ ፍትሃዊ የሆነ የሰሜን አሜሪካ የአጻ ንግድ ስምምነት ከተደረገ ሜክሲኮና ካናዳ ቀረጥ ከመጣሉ እቅድ ነጻ ሊሆኑ ይችላሉ ብለዋል።“ዋግ ቢስ የነበረውን የሰሜን አሜሪካ ነጻ የንግድ ስምምነትን ለማሻሻል እየተደራደርን ነው። ስምምነት ላይ ካልደረስን ግን አቆመዋለሁ” ሲሉ ፕሬዚዳንት ትረምፕ ዝተዋል።ዩናይትድ ስቴትስ ሜክሲኮና ካናዳ የሰሜን አሜሪካ ነጻ የንግድ ስምምነትን ለማሻሳል እየሰሩ ናቸው።
| 0 |
2616bb512995f008ea20a46361dfcf9c
|
d45d5ffb0026c5e6ab4292c958efd211
|
በዋሺንግተን ዲሲ ስለተደረጉ ሰልፎች
|
ሰልፉ በተለያዩ የዓለም ከተሞች ከሚደረጉት ተመሳሳይ ሰልፎች ጋር የተቀናጀ መሆኑን የተገለጸ ሲሆን፣ ኢትዮጵያውንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተሳተፉበት ሰልፍ በዋሽንግተን ዲሲ ካፒቶል ፊት ለፊትና ከዚያም ፍሪደም ፕላዛ ወይም የነጻነት አደባባይ እየተባለ በሚጠራው ቦታ ላይ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ ሰልፈኞቹ ከመስከረም 30 በኋላ የኢትዮጵያ መንግሥት የሥልጣን ዘመኑ ስለሚያበቃ ተቀባይነት የለውም በሚል ኢትዮጵያን የሚበትንና አለመረጋጋትና ቀውስን የሚጋብዝ ጥሪ አስተጋብተዋል ያሏቸውን ወገኖች በመቃወም አደባባይ መውጣታቸውን ገልጸዋል፡፡
| 0 |
1ea5abe2726d602873e9444ea9142e8d
|
2376a62786c5dae057f1ccb98c816133
|
የእስር ጊዜያቸውን ጨርሰው ሲወጡ ሌላ ክስ የተመሠረተባቸው የሰማያዊ ፓርቲ አባላት በዋስ ተለቀቁ
|
በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ክስ የተመሠረተባቸው የቀድሞ የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ (አንድነት)፣ የአረናና ሰማያዊ ፓርቲዎች አመራሮች ላይ፣ ዓቃቤ ሕግ ምስክሮቹን ከሰኔ 1 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ ማሰማት ጀመረ፡፡ክሱን የመሠረተው የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ምስክሮቹን አቅርቦ ከማሰማቱ በፊት፣ በፀረ ሽብርተኝነት አዋጁ አንቀጽ 32 መሠረት ምስክርነቱ በዝግ እንዲታይ ለፍርድ ቤቱ አመልክቷል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ‹‹በምስክሮቼ ላይ ማስፈራሪያና ዛቻ ደርሶባቸዋል›› የሚል ነበር፡፡ተከሳሾቹ ግን የተጠቀሰባቸው ሕግ እስከ ሞት ድረስ ሊያስቀጣ የሚችል መሆኑን በመጠቆምና ምስክርነቱን ሕዝብ መስማት እንዳለበት በመግለጽ፣ ምስክርነቱ በግልጽ ችሎት እንዲታይ ፍርድ ቤቱን በመጠየቅ የዓቃቤ ሕግን ማመልከቻ ተቃውመዋል፡፡ሁሉንም እስረኞች በመወከል ለፍርድ ቤቱ ያመለከቱት የቀድሞው የአንድነት ፓርቲ አመራር አቶ ሀብታሙ አያሌው ሲሆኑ፣ ያሉት ማረሚያ ቤት ውስጥ መሆኑንና የምስክሮቹ ዝርዝር ሊደርሳቸው የሚገባ ቢሆንም መከልከላቸውን አስረድተዋል፡፡በመሆኑም በምስክሮቹ ላይ ማንም ዛቻና ማስፈራሪያ ሊያደርስ የሚችልበት መንገድ እንደሌለ ጠቁመው፣ የዓቃቤ ሕግ ጥያቄ ውድቅ እንዲደረግላቸው አመልክተዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ ምስክርነቱን በዝግ ችሎት የሚያየው ከሆነ፣ ሁሉም ተከሳሾች የግፍ ፍርደኛ ሆነው ወደ እስር ቤት እንደሚመለሱና በቀጣይም ምንም ዓይነት ክርክር እንደማያደርጉ ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል፡፡ፍርድ ቤቱ የሁለቱንም ወገኖች ክርክር በማዳመጥ ውይይት ካደረገ በኋላ፣ የዓቃቤ ሕግን ማመልከቻ ውድቅ በማድረግ፣ ምስክርነቱ በግልጽ ችሎት እንዲታይ ብይን ሰጥቷል፡፡ ነገር ግን የዓቃቤ ሕግ ምስክሮች የሚናገሩትንም ሆነ ስማቸውን ጠቅሰው የኅትመትም ሆነ የኤሌክትሮኒክስ መገናኛ ብዙኃን መዘገብ እንደማይችሉ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡በዕለቱ በአሥረኛ ተከሳሽ አቶ ተስፋዬ ተፈሪ ላይ አንድ የዓቃቤ ሕግ ምስክር ተሰምተዋል፡፡ተከሳሾቹ አቶ ዘለዓለም ወርቅአገኘሁ ጋሻው፣ የአንድነት አመራር የነበሩት አቶ ሀብታሙ አያሌውና አቶ ዳንኤል ሺበሺ፣ የሰማያዊ ፓርቲ አመራር አቶ የሺዋስ አሰፋ፣ የአረና ፓርቲ አመራር አቶ አብርሃ ደስታ፣ እንዲሁም አቶ ዮናታን ወልዴ፣ አቶ አብርሃም ሰለሞን፣ አቶ ሰለሞን ግርማ፣ አቶ ባህሩ ደጉና አቶ ተስፋዬ ተፈሪ መሆናቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡
| 0 |
183acfe831898687bd9f72ace271ad4c
|
183acfe831898687bd9f72ace271ad4c
|
የአሜሪካ ሹልዝ ኢንቨስትመንት ከፋሚሊ ወተት የ45 በመቶ ድርሻ ገዛ
|
ላለፉት ሦስት ዓመታት በኢትዮጵያ በልዩ ልዩ መስኮች ኢንቨስት ሲያደርግ የቆየው የአሜሪካው ሹልዝ ግሎባል ኢንቨስትመንትስ፣ በግብርና ዘርፍ ሊያካሂደው ካቀደው ኢንቨስትመንት አንዱ የሆነውን የወተትና የወተት ተዋጽኦ ምርት ማቀነባበሪያ ፋብሪካን ከፋሚሊ ወተት የ45 በመቶ ድርሻ በመግዛት ዕውን ማድረጉን ገለጸ፡፡ ሹልዝ ኢንቨስትመት ሐሙስ ጥር 12 ቀን 2008 ዓ.ም. በጽሕፈት ቤቱ በተዘጋጀ የውል ስምምነት እንዳረጋገጠው ይህ ትልቅ ኢንቨስትመንት ነው፡፡የሹልዝ ግሎባል ኢንቨስትመንትስ የኢትዮጵያ ተጠሪ ሚስተር ክሬግ ሜትሮ በፊርማ ሥነ ሥርዓቱ ላይ እንደገለጹት፣ ግዙፉ የአሜሪካን ኩባንያ በዓለም ዙሪያ ከሚያካሂደው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት አንዱ እንደሆነ በሚቆጠረው በዚህ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንቱ ወደ ላቀ ደረጃ ተሸጋግሯል፡፡ አጠቃላይ የድርሻ ሽያጩ ምን ያህል እንደሆነ ባልተገለጸው በዚህ ስምምነት ፋሚሊ ወተት ከዚህ በፊት በሚያመርተው የወተትና የወተት ተዋጽኦ ምርት ላይ ሦስት እጅ እጥፍ ምርት እንደሚጨምር፣ አጠቃላዩን የግብርናውንና የአመራረቱን ሒደትም በዘመናዊ ዘዴና የሠለጠነ የሰው ኃይል እንደሚያሻሽለው ሚስተር ክሬግ አስታውቀዋል፡፡ላለፉት 15 ዓመታት በወተት ገበያ ውስጥ የቆየው ፋሚሊ ወተት አገሪቱ ውስጥ ባለው ከፍተኛ የወተት ፍላጎት ሳቢያ ከውጭ አገር የሚገቡ የወተት ምርቶች ለመተካት አቅዶ እየሠራ ቢገኝም፣ አቅሙን አጎልብቶ ወደ ላቀ ደረጃ ለመሸጋገርና ገበያውን ለመምራት በማቀድ ከአሜሪካኑ ኩባንያ ጋር የሁለትዮሽ የባለቤትነት ድርሻ ይዞ ለመሥራት መወሰኑን፣ የፋሚሊ ወተት ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ዳዊት መቻል ገልጸዋል፡፡በስምምነቱ መግለጫ ወቅት የተገኙት የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር መብራቱ መለስ በአገሪቱ ያለውን ሰፊ የቀንድ ሀብትና ተያያዥ ሀብቶችን በአግባቡ ለመጠቀም፣ ከአገር በቀል ኢንቨስትመንት ጎን ለጎን ዓለም አቀፍ ኢንቨስትመንት ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው በመግለጽ የስምምነቱን ፋይዳ አስረድተዋል፡፡
| 1 |
0b416588a09ce5f6dddf63445592d76e
|
7732442ddde3b5789242e99145e5b0c4
|
ደርባ ሚድሮክ ሁለተኛውን ፋብሪካ ለመገንባት ድርድር እያካሄደ ነው
|
በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ወታደራዊና የአደጋ ጊዜ የደህንነት ተሽከርካሪዎቸን የሚያመርተው ስትሬት ግሩፕ ኩባንያ በኢትዮጵያ የተሸከርካሪ መገጣጠሚያ ለመገንባት ፍላጎት እንዳለው ገለጸ፡፡በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ በወታደራዊ እና ለደህንነት አገልግሎት የሚውሉ እንዲሁም ሌሎች ሲቪል ተሽከርካሪዎችን የሚያመርተውን ስትሬት ግሩፕ ኩባንያን በጎበኙበት ወቅት ነው የኩባንያው ዋና አስተዳዳሪ ሩሴል አርኖት የተናገሩት፡፡እንደ ኩባንያው አስተዳዳሪ ገለፃ ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ያላት ተቀባይነት እና የድርጅታቸውን ምርት ወደ ሌሎች የአፍሪካ አገራት ለመላክ ስትራቴጂያዊ ቦታ መሆኗን ገልፀዋል። ለዚህም ነው ድርጅታቸው በኢትዮጵያ የመገጣጠሚያ ፋብሪካ ለመገንባት ከፍተኛ ፍላጎት ያደረበት ሲሉ ተናግረዋል፡፡የአምባሳደሩ ጉብኝትም ለኩባንያው በኢትዮጵያ ያለውን የኢንቨስትመንት አማራጮችን ማስተዋወቅ እና ወደ ኢትዮጵያም በመምጣት መዋዕለ ንዋዩን እንዲያፈስ ለማግባባት ያለመ መሆኑ ተጠቅሷል።በጥቂት ቀናት ውስጥም ኩባንያው ወደ ኢትዮጵያ አንድ ልዑክ በመላክ ያለውን የኢንቨስትመንት አማራጮችን እንደሚያጠና ነው በውይይቱ የተገለፀው።አምባሳደሩ ከጉብኝታቸው በኋላ እንዳሉትም ኩባንያው ወደ ኢትዮጵያ አጥኚ ቡድን በመላክ የሚያገኘውን ውጤት መሰረት አድርጎ በሀገሪቱ መዋዕለ ንዋዩን እንደሚያፈስ እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል።
| 0 |
0a196f36d460ab99a9f95d7b3c671271
|
8a6f32969b8e544d12c411aa0d992013
|
ከፕሬዝዳንታዊ ሥልጣን እሰከማስነሳት የሚደርስ ሕገ መንግስታዊ ሂደት Impeachment ምንነትና አንድምታ!
|
አዲስ አበባ ፣ ህዳር 8 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) መንግስት በትግራይ ክልል የጀመረው ሕግ የማስከበር እርምጃ ዓላማው ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን የናደውን የመቐለ ጁንታ ለሕግ ተገዥ የማድረግና ሕገ መንግስታዊ ስርዓትን ማስጠበቅ መሆኑን በአልጀሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ገለጹ።አምባሳደር ነብያት ከአልጄሪያው ዕለታዊ የዓረብኛ ጋዜጣ አል ፋጅር ጋር ቆይታ አድርገዋል። በቆይታቸውም በኢትዮጵያ የተከናወኑ ዘርፈ ብዙ የሪፎርም ስራዎችና የተገኙ ውጤቶችን፣ እየተካሄደ ያለውን የፖለቲካ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የለውጥ ስራዎችን አንስተዋል።በዚህም ለዴሞክራሲ ማበብ የሕግ የበላይነት መከበር ወሳኝ መሆኑን፣ ማንኛውም ሀገር ህግን የተላለፉ አካላት በሚኖሩ ጊዜ ህግን የማስከበር ስራ እንደሚሰራ ሁሉ የኢትዮጵያ መንግስትም በትግራይ ክልል ህግ የማስከበር ዘመቻ እያካሄደ መሆኑን አስረድተዋል። በሌላ በኩል የኢትዮጵያንና የአልጀሪያን ግንኙነት በፖለቲካ፣ በንግድና ኢንቨስትመንት እንዲሁም በህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለማጠናከር በአልጀሪያ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሚሲዮን እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑንም ጠቅሰዋል። በአልጄሪያ በኩልም ግንኙነቱን በሚያጠናክሩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ተባብሮ ለመሥራት ሙሉ ዝግጁነት እንዳለ አስታውቀዋል። በህዳሴ ግድብ ዙሪያም የኢትዮጵያን አቋም ማስረዳት መቻሉንና ለአልጄሪያ የተለያዩ አካላትም ወቅታዊ መረጃ እንዲደርሳቸው መደረጉን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።አል- ፈጅር ሚድያ በአልጀሪያ፣ በመካከለኛው ምስራቅና ሰሜን አፍሪካ ሠፊ ተከታዮች ያለው ሚዲያ ነው።
| 0 |
9178e7668be779f1c17b07e3c0e27d05
|
4ce35d46ccda0aeb2db8caf9ae7a6c5e
|
ግብጽና ኢትዮጵያ ከድርድር የተለየ አማራጭ እንደሌላቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያም ደሳለኝ ገለጹ
|
የተባበሩት መንግስታት ድርድት ዋና ጸሐፊ ባን ኪ ሙን ከኢትዮጽያዉ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ ጋር ኢትዮጵያ በአካባቢ ጉዳዮች ስለምትጫወተዉ ገንቢ ሚና ተነጋግረዋል። ዋና ጸሀፊዉ ኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳን ተፋላሚ ወገኖችን በመሸምገል እንዲሁም በሶማሊያ ሰላም እንዲሰፍን ለምታደርገዉ ተሳትፎ አመስግነዋል።በምእራብ አፍሪቃ ኢቦላ ከተሰፋፋባቸዉ አገሮች የጊኒ ፕሬዚደንት ወረርሺኙ አገራቸዉ ላይ እያደረሰ ያለዉን የኢኮኖሚ ቀዉስ ጠቅሰዉ ተናግረዋል። የአይሲል ሰፊ ግዛት የያዘባትና ዓለምአቀፍ ሥጋት የሆነባት የኢራቅ ፕሬዚዳንት እና ከመካከለኛው ምሥራቅ ውጥረት ተዋንያን የአንዷ ግዛት የፍልስጥዔም ፕሬዚዳንት እንዲሁም ተሰናባቹ የናሚቢያ ፕሬዚዳንትም የሃገራቸውን የሚሌኒየም የልማት ግቦች የስኬት ታሪክ፣ የአፋሪካን የኢቦላ፣ የፀጥታና የአየር ንብረት ፈተናዎች አንስተዋል፡፡ ዝርዝሩን ከዘገባው ይከታተሉ።
| 0 |
1f3e20ab634fb97699b141c3542d3481
|
321b55cc3515462b646fbfbe97aad51a
|
“በአማራ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለው የዘር ጭፍጨፋ ሁሉም አካል ሊያወግዘው ይገባል” አቶ አብርሃም አለኸኝ
|
ባሕር ዳር፡ መጋቢት 10/2012 ዓ.ም (አብመድ) የባሕር ዳር ከተማ አስተዳድር ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ኃይሌ አበበ በሀገሪቱ የተነደፉ አዳዲስ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮችን መሪዎች እንዲገነዘቧቸውና እንዲተገብሯቸው ለማድረገ ስልጠና መስጠት ማስፈለጉን ገልጸዋል፡፡ ፓርቲው የሚከተላቸውን መርሆዎች፣ የሚተገብራቸውን እና የሚጠበቁ ውጤቶችን በአግባቡ ተገንዝቦ ተግባራዊ የሚያደርግ ጠንካራ እና ዘመኑን የሚመጥን የመሪ አቅም ለመገንባት በማስፈለጉ ስልጠናው መዘጋጀቱን አቶ ኃይሌ ገልጸዋል፡፡የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አብርሃም አለኸኝ እንደገለጹት ደግስልጠናው በሀገራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርገው በተዘጋጁ ሰነዶች ላይ የሚያተኩር ነው፡፡ የቀጣይ አቅጣጫም ይቀመጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ከዚህ በፊት 10 ሺህ የሚሆኑ ከፍተኛ እና መካከለኛ መሪዎች በክልል ደረጃ በስልጠናው መሳተፋቸው ተገልጧል፡፡ በቀጣይም ከ40 ሸህ በላይ በተለያዬ ደረጃ የሚገኙ መሪዎችን ለማሰልጠን መታሰቡን አቶ አብርሃም ገለጸዋል፡፡ የባሕርዳር ከተማ አስተዳድር የቀበሌና መሠረታዊ ድርጅት መሪዎች ስልጠና ከ400 በላይ ሰልጣኞች እየተሳተፉበት ነው፡፡ስልጠናው ከዛሬ ጀምሮ ለ5 ተካታታይ ቀናት እንደሚሰጥ መርሀ ግብሩ ያመላክታል፡፡ዘጋቢ፡- ዳግማዊ ተሠራ
| 0 |
cea047ec671a52c7ab39332975c49398
|
0106b32d69d662e5c10bdc0495e2ad98
|
የትህነግ ዘራፊ ቡድን ሲጠቀምበት የነበረ 32 ኩንታል አደንዛዥ እፅ በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡
|
በጋምቤላ ክልል በህገ ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ ሃያ ስድስት ክላሽ፣ አንድ ብሬንና ሃያ የጥይት ካዝና በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለፀ።የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በኑዌር ብሄረሰብ ዞን ባደረገው ክትትል ሃያ ስድስት ክላሽ፣ አንድ ብሬንና ሃያ የጥይት ካዝና በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል፡፡የጦር መሳሪያውን ሲያንቀሳቅስ የተገኘው ተጠርጣሪም በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነር አቶ ሳይመን ቲያች ተናግረዋል፡፡በአሁኑ ወቅት በጉዳዩ ዙሪያ ፖሊስ ምርመራ እያካሄደ ሲሆን ፥የምርመራ ሂደቱ እንደተጠናቀቀም ውጤቱ ለፍርድ ቤት የሚላክ መሆኑ ነው የተገለፀው።ህገ ወጥ የጦር መሳሪያዎቹና ተጠርጣሪ ግለሰቡ በቁጥጥር ስር የዋሉትም በህብረተሰቡ ጥቆማና ፖሊስ ባደረገው የተጠናከረ የክትትልና የቁጥጥር ስራ መሆኑን ከጋምቤላ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።የፀጥታ አካላት የህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውርን ለመከላከል በሚያደርጉት ጥረት ህብረተሰቡ የተለመደ ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል ኮሚሽነሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡የጋምቤላ ክልል ከደቡብ ሱዳን ጋር ከሚጋራው ሰፊ የድንበር ወሰን ጋር ተያይዞ ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ወደ ክልሉ እየገባ መሆኑም በመግለጫው ተጠቅሷል፡፡ (ምንጭ ፡ ኤፍ.ቢ.ሲ)
| 0 |
9fd555380027c49898f00c33f2bb94ac
|
9fd555380027c49898f00c33f2bb94ac
|
ባለስልጣናት ከአገር ውጭ የሚያደርጉት ጉዞ ላይ ቁጥጥር እንደሚደረግ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ገለጹ
|
የመንግስት ባለስልጣናት ከአገር ውጭ የሚያደርጉት ጉዞና መዳረሻዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚደረግ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ገለጸዋል።ከአገር ውጭ ያላቸው የባንክ አካውንት ላይም ምርመራ እየተደረገ ነው ብለዋል።ጠቅላይ ሚኒትሩ ለአዲሱ ካቢኔ በቀጣይ ጊዜያት እንዴት ውጤታማ ስራ መስራት እንደሚቻል በሰጡት ማብራሪያ ላይ አፅንኦት ከሰጡባቸው ጉዳዮች መካከል ከውጭ ጉዞ ጋር ተያይዞ እየመጣ ያለ ብክነት አንዱ ነው።በአንድ አመት ከ10 ጊዜ በላይ ውጭ አገር የሚመላለስ ሚኒስትር፣ ሚኒስትር ዴኤታ እና ከዛ በታች ያሉ ግለሰቦች መኖራቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል።ብዙም አስፈላጊ ላልሆኑ ጉዳዮች ወደ ውጭ አገር የሚመላለሱና ከሚሄዱበት አገር በተጨማሪ ሌላ አገር ጎራ የሚሉት ባለስልጣናት በርካታ መሆናቸውን በመግለጽም የሚሄዱበት ምክንያትና መዳረሻቸው ላይ ጥብቅ ክትትል ማድረግ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።ከዚህም ሌላ የአገሪቱ ባለስልጣናት ውጭ አገር ያላቸው የባንክ አካውንት ላይ ጥናት እየተደረገ መሆኑንና ሲጠናቀቅም የተገኘው ውጤት ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግ ገልጸዋል።ለዚህም የተለያዩ አገራት ትብብር እያደረጉ መሆኑን ነው የተናገሩት።የውጭ ጉዞ አያስፈልግም የሚል እሳቤም እንዳይያዝ ኃላፊዎቹ ማቻቻልና ብክነትን በሚቀንስ መልኩ አመጣጥኖ መሰማራት እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። (ኢዜአ)
| 1 |
3b21bb76f5ba8f6cb8b290cd6d1aab99
|
3b21bb76f5ba8f6cb8b290cd6d1aab99
|
የእስር ማዘዣ ወጥቶባቸው ያልተያዙ ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ሳይውሉ አይቀሩም ተባለ
|
የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን እስካሁን ድረስ የእስር ማዘዣ ወጥቶባቸው በቁጥጥር ሥር ያልዋሉ ግለሰቦች ቢዘገይም ነፃ እንደማይሆኑ አስታወቀ፡፡ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔነራል እንደሻው ጣሰው ሐሙስ የካቲት 14 ቀን 2011 ዓ.ም. በኮሚሽኑ መሥሪያ ቤት በሰጡት መግለጫ፣ የእስር ትዕዛዝ ለወጣባቸው ግለሰቦች ትዕዛዙን ለማድረስ ሲኬድ ያጋጠሙ ችግሮች እንደነበሩ በመግለጽ፣ በእንደዚህ ዓይነት ወቅት መታኮስ አስፈላጊ ስላልነበር የተለያዩ አማራጮች ላይ ትኩረት መደረጉን ተናግረዋል፡፡‹‹አንዳንድ ጉዳዮች በመደበኛ የፖሊስ ሥራዎች ብቻ የሚፈቱ አይደሉም፡፡ የተለያዩ ቦታዎች ሔደው የተደበቁ ሰዎች አሉ፡፡ የእስር ማዘዣ ከወጣባቸው በኋላም የእስር ማዘዣውን ቦታው ድረስ ሄዶ ለመስጠት ሲሞከር ያጋጠሙ እንቅፋቶች አሉ፡፡ በዚህ ወቅት አትታኮስም፡፡ ሁኔታው አስተዳደራዊ በሆነ መንገድ በጥሞና እንዲታይ ይደረጋል፡፡ ይኼ ለሰላም ሲባል ነው፡፡ ይኼ የሚደረገው አጠቃላይ ነገር እንዳይበላሽና እንዳይደፈርስ ሲባል ነው፡፡ ይኼ ማለት ግን ሄዶ ሄዶ የእስር ማዘዣ የወጣባቸው ሰዎች ነፃ ይወጣሉ ማለት አይደለም፡፡ እንኳን በአገር ውስጥ ያለ ይቅርና በውጭ አገር በወንጀል የተጠረጠረ ካለ ይዘን እናቀርባለን፤›› ሲሉም አብራርተዋል፡፡ይኼንንም ለማስፈጸም ከተለያዩ ክልሎች ጋር አስተዳደራዊ ውይይቶች እንደተደረጉ በማስታወቅ፣ ‹‹ጉዳዮቹ ጊዜ ተሰጥቷቸው የክልል መንግሥታትም የራሳቸውን ሚና እንዲወጡ ይደረጋል፤›› ብለዋል፡፡ይሁንና በወንጀል የሚጠረጠሩ ግለሰቦችን ይዘው የሚያስረክቡ ክልሎች እንዳሉም ያወሱት ኮሚሽነር ጄኔራሉ፣ በተቃራኒው የሚደብቅ፣ የሚሸሽግና አካባቢዬ ላይ ተጠርጣሪው የለም ብሎ የሚያብር ሰው መልካም ተሞክሮ እንዳልሆነ፣ ብሎም የተጀመረውን ለውጥ የሚያናጋና የሚያበላሽ እንዲሁም የወንጀል መከላከል ሥራ ላይም ጥላ የሚያጠላ ጉዳይ ስለሆነ በሚታረምበት መንገድ ይታረማል ሲሉም አሳስበዋል፡፡
| 1 |
603d48470d06eb4bfe9587e0deca88d1
|
40e8554303eaecc368fa5fae20e675e7
|
የከተሞች ማስፋፍያ እና የኢኮኖሚ አድገት መርሀ ግብር ተግባራዊ ሊሆን ነው
|
በኢትዮጵያ ቀጣናዊ ልማትን በማሳደግ የስደተኞችን ጥበቃ ለማጠናከር የሚረዳ መርሀ ግብር ይፋ ሆነ፡፡ለመርሀ ግብሩ የአውሮፓ ህብረት፣ የኔዘርላንድስ መንግስት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበርና የተባበሩት መንግስታት በአጋርነት በመሳተፍ በመደቡት 720 ሚሊዮን ብር የሚከናወን መሆኑ ተመልክቷል፡፡መርሀ ግብሩ ለስደተኞች ተገቢውን ጥበቃ ለማድረግ የሚያግዙ የልማት ሥራዎችን በማከናወን ስደተኞችንና በስደተኞችን ጣቢያ አካባቢ የሚገኙ የህረተሰብ ክፍሎችን ተግዳሮቶች ለመፍታት ያግዛል ተብሏል፡፡በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት ኃላፊ አምደባሳደር ቻንታል ሄቤሬችት እና በኔዘርላንድስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የልማትና ትብብር ምክትል ኃላፊ ሬይና ቡጂስ መርሀ ግብሩ መጀመሩን ትናንት በካፒታል ሆቴል ይፋ አድርገዋል፡፡ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከተለያዩ አገራት የመጡ 800ሺ ያህል ስደተኞችን ተቀብላ እያስተናገደች መሆኑን ህብረቱ አስታውቋል፡፡ኢትዮጵያ ስደተኞችን በመቀበል ተገቢውን ድጋፍ በማድረግ የሚጠበቅባትን ኃላፊነት በአግባቡ እየተወጣች መሆኑን ህብረቱ ጨምሮ ገልጿል፡፡ ስደተኞች ወደ ትውልድ አገራቸውና ወደ ሶስተኛ አገር እንዲሄዱ የምታደርገው ጥረትን ህብረቱ አድንቆ ይህንን ለማገዝም ዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ ከኢትዮጵያ ጎን እየቆመ ነው ብሏል፡፡ኢትዮጵያ ስደተኞች ከስደተኛ ጣቢያ ውጭ የሚንቀሳቀሱበትን ፖሊሲ መተግበሯ ስደተኞች የተለያዩ ማህበራዊ አገልግሎቶችንና የሥራ ዕድል የሚያገኙበትን አሰራር የሚያግዝ እንደሆነ ተመለክቷል፡፡መርሀግብሩ ከኤርትራና ከሶማሊያ መጥተው በአፋር፣ በሶማሌና በትግራይ የስደተኞች ጣቢያና በዋና ዋና ከተሞች ለሚገኙ ስደተኞችና በስደተኞቹ ጣቢያ አካባቢ ለሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚውል ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የዓለም ባንክ 100 ሚሊዮን ዶላር፣የእንግሊዝ የልማት ድርጅት 125 ሚሊዮን ፓውንድ እና ሌሎች አጋር ድርጅቶች በጀት ፈሰስ በማድረግ በተመሳሳይ መርሀ ግብር እንደሚሳተፉ ለማወቅ ተችሏል፡፡(ትርጉም ዳንኤል ንጉሤ)
| 0 |
45248bbea3f9963c43e63470de71e574
|
fadc6f0863a3be45a69ad77d9d86b87f
|
የኮሌራ ወረርሽኝ በሱዳን የሰዎችን ህይወት እየቀጠፈ መሆኑ ተገለጸ
|
የዓለም የጤና ድርጅት በባንግላዴሽየተከሰተውን የኮሌራ መነሳት ለመከላከል 9መቶ ሺህ ብልቃጥ የክትባት መድሃኒት ልኳል።የክትባቱ መድሃኒት የተላከው ቀደም ሲል በየመን ለተከሰተው ግዙፍ የኮሌራ ወረርሺኝን የዓለሙ ድርጅት ፈጣን ምላሽ መስጠት እንደነበረበት መግለፁን ተከትሎ ነው።የዓለሙ የጤና ድርጅት /WHO/ እአአ እስከ 2030 ድረስ ኮሌራን ጨርሶ ለማጥፋት ቃል ገብቷል።
| 0 |
a5b80c6375e179773f30956f14b31ec1
|
0d89031957eb6a636ab1b323d4879e72
|
የአማራ ክልል አመራሮች ህዝባዊ ውይይት
|
አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል የኢንቨስትመንት ዘርፉን በማስፋፋት ዘላቂ የስራ ዕድል መፍጠር በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ ውይይት እየተካሄደ ነው።የአማራ ክልል ኢንቨስትመንት እና ኢንዱስትሪ ኮሚሽን ባዘጋጀው በዚህ መድረክ ላይ ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች እና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።የአማራ ክልል ርዕስ መስተዳድር ልዩ አማካሪ አቶ ጎሹ እንዳላማው፥ በክልሉ የኢንቨስትመንት ዘርፉን በማጠናከር ለዜጎች ዘላቂ የስራ እድል ለመፍጠር ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ለዚህም የማሌዥያ ቢግዌን የስራ እድል ፈጠራ ዘዴን በመውሰድ እና የክልሉን ተጨባጭ ሁኔታ መሰረት በማድረግ የስራ እድል ፈጠራ ጥናት መጠናቱን ጠቅሰዋል።በጥናቱም ለ146 ሺህ ዜጎች የስራ ዕድል የሚፈጥሩ 34 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 51 ፕሮጀክቶች መለየታቸውን አብራርተዋል።ጥናቱ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር የሚመራ መሆኑን ያነሱት አቶ ጎሹ፥ በዚህም በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ከመለየት ባለፈ ክትትል እና ቁጥጥር እንደሚደረግ ጠቁመዋል።በክትትል እና ቁጥጥር ስራው ሃላፊነታቸውን በማይወጡ የተቋማት ሃላፊዎች እና ባለሙያዎች ላይ ከስራ እስከ ማሰናበት የሚደርስ እርምጃ እንደሚወሰድም ጠቅሰዋል።የክልሉ የስራ ዕድል ፈጠራ የጥናት ቡድን አስተባባሪ አቶ ሞገስ ተኬ በበኩላቸው፥ ሰብል ልማት፣ እንስሳት ሃብት፣ የወተት ላም ማርባት እና ግብርና ማቀነባበር ለዕቅዱ የተመረጡ የስራ ዘፎች መሆናቸውን ገልጸዋል።በቀጣይ በማምረቻው ዘርፍ፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም እና በመብራት ሃይል ዘርፎች ላይ እንደሚሰራም አመላክተዋል።በናትናኤል ጥጋቡትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!
https://t.me/fanatelevision
| 0 |
1a6295c02464c6f2f9fb964d49fbeb85
|
8a4d5541733cbaa8da4363c9065216ee
|
በባንግላዴሽ በከፍተኛ ቀዝቃዜ የ50 ሰዎች ህይወት አለፈ
|
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 13፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በህንድ ዴልሂ ከተማ በደረሰ የእሳት አደጋ የዘጠኝ ሰዎች ህይወት ማለፉ ተሰምቷል።በመኖሪያ ሕንፃ ውስጥ በደረሰው የእሳት አደጋ ህይወታቸውን ካጡ ሰዎች በተጨማሪ 10 ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸው የተነገረው።ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ለህክምና ወደ አከባቢው ሆስፒታል መወሰዳቸው ነው ከስፍራው የወጡ መረጃዎች የሚያመለክቱት።ምንጭ፡- ሲ.ጂ.ቲ.ኤን
| 0 |
6c41137313edc7352ed3e4ded6de9360
|
8ca4997d8f26f80ea6251a86c87878db
|
የኢትዮጵያ ከ17 አመት በታች ብሄራዊ ቡድን ከሰአታት በኋላ ወደ ግብፅ ያመራል
|
ጥቅምት 3 ሊካሄድ የታሰበው የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ በታሰበበት ቀን መካሄድ ያልቻለ ሲሆን በመጪው ሰኞ ጥቅምት 15 ቀን 2009 እንዲካሄድ ተወስኗል፡፡ ህዳር 3 እንደሚጀመር አስቀድሞ የተወሰነው ከፍተኛ ሊጉ የሚጀመርበት ቀን ይራዘም አይራዘም የታወቀ ነገር የለም፡፡የኢትዮጵያ ከ17 አመት በታች ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ጥቅምት 8 እጣ እንዲወጣ ታስቦ የነበረ ቢሆንም በ8 ቀናት ወደፊት ተገፍቶ ማክሰኞ ጥቅምት 16 እንዲካሄድ ተወስኗል፡፡ ለመጀመርያ ጊዜ የሚካሄደው የ20 አመት በታች ፕሪሚየር ሊግ ደግሞ ጥቅምት 11 ሊካሄድ የነበረው ወደ ጥቅምት 16 አንዲሸጋሸግ ተደርጓል፡፡ በዚህም ከ17 እና ከ20 አመት በታች ሊጎች በተመሳሳይ ቀን እጣ የሚወጣ ይሆናል፡፡ከትላንት በስቲያ ሊካሄድ የነበረው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሊግ የእጣ ማውታት ስነስርአት ወደ አርብ ጥቅምት 18 ቀን 2009 ተሸጋግሯል፡፡በኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ስር ከሚካሄዱት የሊግ ወድድሮች መካከል የኢትዮጵያ ወንዶች እና ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ እጣ የወጣ ሲሆን የቀሪዎቹ ከላ በተጠቀሱት ቀናት ከተካሄዱ በኋላ ውድድሮቹ የሚጀመሩባቸው ቀናት ለውጥ ደረግባቸው አይደረግባቸው የሚታወቅ ይሆናል፡፡– – ጥቅምት 20 – ህዳር 11 – ህዳር 3 – ህዳር 11 – ህዳር 11 – ህዳር 18
| 0 |
f532c0c14663c25b26f047e0c1b87fc5
|
f532c0c14663c25b26f047e0c1b87fc5
|
የትግራይ ክልል ምክር ቤት የተቃውሞ ውሳኔ
|
የትግራይ ክልል ምክር ቤት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የወጣውን የድንበርና የማንነት ጉዳዮች ኮምሽን አዋጅ ተቃወመ።ምክር ቤቱ በዛሬው ውሎ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቅርቡ የጸደቀውን አዋጅ “ሕገ-መንግስታዊ አይደለም” ሲል ውሳኔ ማሳለፉን ጠቅሶ ዓለም ፍስሃ ከመቀሌ ተከታዩን አድርሶናል።
| 1 |
ee8ece92295e093b31f5e8783436ed28
|
221862ccc36611da09edc94df741ad73
|
ሀዋሳ ከተማ የወሳኙን አጥቂ ውል አራዝሟል
|
ወጣቱ አጥቂ ብሩክ በየነ ወልቂጤ ከተማን ለቆ ሀዋሳ ከተማን በሁለት ዓመት ውል ተቀላቅሏል፡፡በአሰልጣኝ አዲሴ ካሳ አማካኝነት በ2009 ክረምት ወር ላይ በሀዋሳ ቄራ ተብሎ በሚጠራበት ሜዳ በሚደረግ የታዳጊዎች ውድድር ላይ የተገኘው የአጥቂ ስፍራ ተጫዋቹ ብሩክ በየነ በወቅቱ የወልቂጤ ከተማ አሰልጣኝ የነበረው የአሁኑ የሀዋሳ አሰልጣኝ አዲሴ ካሳ ተመልምሎ የ2010 የውድድር አመትን በወልቂጤ አሳልፏል፡፡ ተጫዋቹ በከፍተኛ ሊጉ 6 ጎሎች በማስቆጠር የክለቡ ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ ሆኖ ሲያጠናቅቅ የአንድ ዓመት የወልቂጤ ውሉን አጠናቆ ከአንድ ወር በላይ የሙከራ ጊዜን በሀዋሳ አሳልፎ አሳማኝ እንቅስቃሴን በማሳየቱ በሁለት ዓመት ውል ሀይቆቹን ተቀላቅሏል፡፡በተያያዘ ዜና ከቀናት በፊት ሀዋሳ ከተማን ተቀላቅሎ የነበረው መሐመድ ናስር ሁለት ቀን ከቡድኑ ጋር ልምምድ ከሰራ በኋላ በስምምነት መለያየቱ ታውቋል፡፡
| 0 |
3569379dcbe7d50344c74207f73d1616
|
3ebb035cd18599d4504e14bbd9bd4f27
|
ኢትዮጵያን እየገጠማት ካለው ችግር ለመታደግ ዛሬም እንደ ትላንቱ ከወንድሞቻችን ጋር በጋራ እንሰራለን- የትግራይ ክልላዊ መንግስት
|
ሕወሀት “ታሪካዊ” ላለው 6ኛው የትግራይ ክልላዊ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ዛሬ ነሀሴ 15 ቀን 2012 ዓ.ም. በመላው ትግራይ መጀመሩን በፌስቡክ ገጹ አስታውቋል። የመራጮች ምዝገባ እስከ ነሓሴ 22 ይቀጥላልም ነው የተባለው።
“የትግራይ ህዝብ በራስ ተነሳሽነትና በላቀ ዲሲፕሊን የምርጫ ካርድ ለመውሰድ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች ዛሬ ከማለዳው ጀምሮ መጉረፍ ጀምሯል” ሲል ፓርቲው ገልጿል።
የትግራይ ክልል ምርጫ ኮሚሽን ከዚህ ቀደም በሰጠው መግለጫ ምርጫው ጳጉሜ 4 እንደሚካሔድ ይፋ አድርጓል፡፡ በምርጫው የሚወዳደሩ ፓርቲዎችም በክልሉ መገናኛ ብዙኃን የምርጫ ቅስቀሳ በማድረግ ላይ ናቸው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በቅርቡ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ባደረጉበት ዉይይት ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ የፌደሬሽን ምክር ቤት በህገመንግስት ትርጉም ምርጫው እንዲራዘም መወሰኑን በማስታወስ “በትግራይ ክልል ችግር የሚፈጠረው በምርጫው ሕወሀት ስልጣኑን ለሌላ ፓርቲ አሳልፎ ከሰጠ ነው” ማለታቸው ይታወሳል፡፡ ከዚያ ዉጭ የፌዴራል መንግስት ምርጫው እንደማያሳስበው ተናግረዋል፡፡
የትግራይ ክልል ምርጫ ኮሚሽነር ሙሉወርቅ ኪዳነማርያም ከሳምንት በፊት ከአል ዐይን ጋር በስልክ ባደረጉት ቆይታ ክልሉን በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሚወክሉ አባላት በፌደራል ደረጃ በሚደረገው ምርጫ እንደሚመረጡ ተናግረዋል፡፡
“ይህ ምርጫ የሚመለከተው ትግራይን ብቻ ነው” ያሉት ኮሚሽነሩ “ለክልል ም/ቤት ድጋሚ ምርጫ ማድረግ አይጠበቅም” ብለዋል፡፡
“በፌዴራል የትግራይ ውክልና ሲፈለግ ሌላ ጉዳይ ይሆናል፤ በፌዴራል ደረጃ የሚወከሉ ሰዎች ምርጫ ይደረጋል ማለት ነው” በማለት ኮሚሽነሩ ለአል ዐይን ሀሳባቸውን ሰጥተዋል፡፡
በክልል ደረጃ የተቋቋመው የምርጫ ኮሚሽንም ይሁን በክልሉ የሚደረገው ምርጫ ሕገ መንግሥቱን የሚቃረን እና ሕገወጥ መሆኑን የፌዴራሉ መንግስት በተደጋጋሚ ገልጿል፡፡
የፌዴሬሽን ም/ቤት ክልሉ ምርጫ ከማድረግ እንቅስቃሴው እንዲታቀብ ከማስጠንቀቁ ዉጭ የፌዴራል መንግስት ይህን ለመከላከል ስለሚወስደው እርምጃ በግልጽ ያለው ነገር ግን የለም፡፡
| 0 |
52bd789d3485d84d88f8358184327f7e
|
0b8fca848f902a163f412d00d83c3f78
|
ሀዲያ ሆሳዕና ለሁለተኛ ጊዜ የዲሲፕሊን ቅጣት ተላልፎበታል
|
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ ወላይታ ድቻ (አአ ስታድየም) መከላከያ ከ ሀዲያ ሆሳዕና (አአ ስታድየም) ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ አርባምንጭ ከተማ (አአ ስታድየም) አዳማ ከተማ ከ ድሬዳዋ ከተማ (አዳማ) ደደቢት ከ ዳሽን ቢራ (አአ ስታድየም) ኤሌክትሪክ ከ ሲዳማ ቡና (አአ ስታድየም) ኢትዮጵያ ቡና ከ ሀዋሳ ከተማ (አአ ስታድየም) ወላይታ ድቻ ከ መከላከያ (ቦዲቲ) ሀዲያ ሆሳዕና ከ አዳማ ከተማ (ሆሳዕና) ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ (አአ ስታድየም) ድሬዳዋ ከተማ ከ ኤሌክትሪክ (ድሬዳዋ) ሲዳማ ቡና ከ ኢትዮጵያ ቡና (ይርጋለም) ዳሽን ቢራ ከ አርባምንጭ ከተማ (?) ሀዋሳ ከተማ ከ ደደቢት (ሀዋሳ) አዳማ ከተማ ከ ወላይታ ድቻ (አዳማ) ደደቢት ከ ሲዳማ ቡና (አአ ስታድየም) መከላከያ ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (አአ ስታድየም) አርባምንጭ ከተማ ከ ሀዋሳ ከተማ (አርባምንጭ) ኤሌክትሪክ ከ ሀዲያ ሆሳዕና (አአ ስታድየም) ኢትዮጵያ ቡና ከ ድሬዳዋ ከተማ (አበበ ቢቂላ) ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ዳሽን ቢራ (አአ ስታድየም) ወላይታ ድቻ ከ ኤሌክትሪክ (ቦዲቲ) ድሬዳዋ ከተማ ከ ደደቢት (ድሬዳዋ) ሲዳማ ከተማ ከ አርባምንጭ ከተማ (ይርጋለም) ሀዋሳ ከተማ ከ ዳሽን ቢራ (ሀዋሳ) ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ አዳማ ከተማ (አአ ስታድየም) ሀዲያ ሆሳዕና ከ ኢትዮጵያ ቡና (ሆሳዕና) መከላከያ ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ (አአ ስታድየም) ኤሌክትሪክ ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (አበበ ቢቂላ ስታድየም) ዳሽን ቢራ ከ ሲዳማ ቡና (?) አርባምንጭ ከተማ ከ ድሬዳዋ ከተማ (አርባምንጭ) አዳማ ከተማ ከ መከላከያ (አዳማ) ኢትዮጵያ ቡና ከ ወላይታ ድቻ (አአ ስታድየም) ደደቢት ከ ሀዲያ ሆሳዕና (አአ ስታድየም) ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ሀዋሳ ከተማ (አአ ስታድየም)
| 0 |
2b89129b9576c0109ff51bd8e8970673
|
0f084f9dec0954b82fe664ef97ba20b4
|
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 3 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው
|
በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገ 5,102 የላቦራቶሪ ምርመራ ተጨማሪ 109 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው እንዲሁም ተጨማሪ 1 ሰው በቫረሱ ምክንያት ህይወቱ ማለፉን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ።በዚህም እስካሁን በሀገሪቱ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 3,630 ደርሷል።ዶክተር ሊያ እንደገለፁት ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው 60 ወንድና 49 ሴቶች ሲሆኑ እድሜያቸውም ከ 1 ዓመት እስከ 78 ዓመት የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ናቸው፡፡በዜግነት ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ናቸው፡፡ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች 81 ሰዎች ከአዲስ አበባ ሲሆኑ፣9 ሰዎች ከኦሮሚያ ክልል፣4 ሰዎች ከሶማሌ ክልል፣4 ሰዎች ከደ/ቡ/ቡሕ ክልል፣3 ሰዎች ከአማራ ክልል፣3 ሰዎች ከትግራይ ክልል፣3 ሰዎች ከአፋር ክልል እና 2 ሰዎች ከሐረሪ ክልል መሆናቸው ተገልጿል፡፡በተጨማሪም በቫይረሱ ምክንያት የተጨማሪ 1 ሰው (የ45 ዓመት የአዲስ አበባ ነዋሪ ሴት) ሕይወት ያለፈ ሲሆን በዚህም በአጠቃላይ በሀገራችን በኮሮና ቫይረስ ህይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቁጥር 61 ደርሷል፡፡በሌላ በኩል በትናንትናው እለት ተጨማሪ 118 ሰዎች (115 ከአዲስ አበባ እንዲሁም 3 ሰዎች ከትግራ ክልል) ከበሽታው ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ 738 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል። 33 ሰዎችም በፅኑ ህክምና ክትትል ላይ ይገኛሉ፡፡ቫይረሱ በሀገራችን እንደተገኘ ገተረጋገጠበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን በአጠቃላይ 192087 የላብራቶሪ ምርመራዎች ተካሂደዋል፡፡
| 0 |
7c785724072021da20d2f836dbac0654
|
5ee5584a40b64d79e91c8636cb6942af
|
ዙማ ለ4 ሚስቶቻቸው በገዟቸው 11 መኪናዎች ተከሰሱ
|
ባለፈው ሳምንት በ95 ዓመታቸው ያረፉት የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ኔልሰን ማንዴላ አስክሬን ለሶሰት ቀናት ለህዝብ እይታ በሚቀርብበት በፕሪቶሪያ ዩኒየን ወደ ተባለው ህንፃ ተወሰደ።እስከ አርብ ድረስም የማንዴላ አስክሬን በህንፃው ለህዝብ እይታ ይቀመጣል፤ የማንዴላ አስክሬን ከሆስፒታል ወደ ህንፃው ሲወሰድም የከተማዋ ነዋሪዎች በመንገዶች ዳርና ዳር በመሆን በማዜም አጅበዋል።ዩኒየን ህንፃ የመንግስት መቀመጫ ሲሆን፥ ማንዴላ የመጀመሪያው የአገሪቱ ጥቁር ፕሬዚዳንት ሆነው ሲመረጡ ቃለ መሀላ የፈፀሙበት ነው።ትናንት በጆሃንስበረግ በተካሄደው ታላቅ የማንዴላ መታሰቢያ ስነ-ስርዓት ላይም የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ ህንፃው ማንዴላ አምፊቲያተር ተብሎ መሰየሙን ይፋ አድርገዋል።በስፍራው ከማለዳው 2: 00 እስከ 11:30 ሰዓት ድረስ ሰዎች አስክሬንን መጎብኘት እንደሚችሉ የተመለከተ ሲሆን፤ ቅዳሜም የቀብር ስነ-ስርዓቱ ወደ ሚፈፀምበት ምስራቃዊ ኬፕ ኩኑ መንደር ይወሰዳል። እሁድም የኔልሰን ማንዴላ የቀበር ስነ- ስርዓት የሚፈፀም እንደሚሆን ኤፍ.ቢ.ሲ ዘግቧል፡፡
| 0 |
41c6a095b0b82d3de3becb65a3b8467f
|
bf47b6afcb8143b20d2f80c67b5c662b
|
የኢቦላ ስብሰባ በአዲስ አበባ
|
ደቡብ ሱዳን የኢቦላ ቫይረስ መከላከያ ክትባት ልትሰጥ መሆኑን የዓለም የጤና ድርጅት ገለጸ፡፡ሀገሪቱ ክትባቱን የምትሠጠው በሽታው በኮንጎ አገርሽቶ አሳሳቢ ደረጃ ላይ የደረሰ በመሆኑ ነው ተብሏል፡፡የዓለም ጤና ድርጅት የደቡብ ሱዳን ጎረቤት በሆነችው ኮንጎ የተነሳው የኢቦላ ቫይረስ ወደ ሀገሪቷ እንዳይዛመት እና ሃገሪቷን አደጋ ላይ እንዳይጥላት ስጋት መኖሩን ገልጿል፡፡በመሆኑም ድርጅቱ በቅርብ ቀናት ውስጥ በሃገሪቱ ፀረ-ኢቦላ ክትባት ለመሥጠት መዘጋጀቱን አሶሺየትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡ተቋሙ ባወጣው መግለጫ መሠረት የደቡብ ሱዳን የጤና ሚኒስቴር ከስምንት ቀናት በኋላ በመዲናዋ ጁባ የሚገኙ የጤና ሠራተኞች እና ሌሎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሊሆኑ የሚችሉ አካላት ይከተባሉ ተብሏል፡፡በአጠቃላይ 4ሺህ ሰዎችን ለመከተብ ያቀደችው ደቡብ ሱዳን የዓለም የጤና ድርጅት ለ2ሺ ዜጎቿ የክትባት ቁሳቁስ እንደሚያቀርብላት ገልጿል፡፡በታሪክ ሁለተኛው ገዳይ በሽታ መሆኑ የተገለጸው ይህ በሽታ እስከ አሁን ወደ ኮንጎ ጎረቤት ሃገራት ባይዛመትም ክትባቱ ግን በኡጋንዳም መጀመሩን ዘገባው አስነብቧል፡፡በኮንጎ እስካሁን 446 ሰዎች በኢቦላ እንደተጠቁ እና 235 ሰዎች ደግሞ ህይወታቸው እንዳለፈ የሃገሪቱ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ይፋ አድርጓል፡፡በቫይረሱ ከተጠቃ አንድ ሰው ከዚያም ከሰው ወደ ሰው በንክኪና በተለያዩ መንገዶች እንደሚተላለፍ በጥናት የተረጋገጠው የኢቦላ ቫይረስ ለመጀመሪያ ጊዜ የታወቀው እኤአ በ1976 በሱዳን እና በቀድሞዋ ዛየር በአሁኗ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ መሆኑን ጥናቶች ያሳያሉ፡፡ (ምንጭ፡-አሶሺየትድ ፕረስ)
| 0 |
410332112131df2ba56f43e8d32c9696
|
2fc9b362c2bce8250c2710d223ca5b6e
|
ክልሉ ከሳዉዲ አረቢያ የሚመለሱ ዜጎችን ለማቋቋም የሁሉም ጥረት እንደሚያስፈልግ ገለፀ
|
የሱማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፋ መሀመድ ኡመር ከሱማሌ ክልል የተፈናቀሉ የኦሮሞ ተወላጆችን ጎብኝተዋል፡፡ለኦሮሞና ሱማሌ የህዝብ ለህዝብ መድረክ አዳማ የነበሩት ምክትል ርዕሰ-መስተዳድሩ ከሱማሌ ክልል ተፈናቅለው በአዳማ አካባቢ የሚገኙ ዜጎችን ጎብኝተዋል፡፡አቶ ሙስጠፋ በጉብኝቱ ወቅት ከሱማሌ ክልል ተፈናቅለው በአዳማ ብቻ ሳይሆን በሌሎች አካባቢዎችም የሚገኙትን ወገኖች ለማቋቋም መንግስታቸው ጥረት ያደርጋል ብለዋል፡፡ከዚህም በተጨማሪ ወደቀያቸው ሲመለሱም እንዲቋቋሙ የሚያስችላቸውን ድጋፍ መንግስት እንደሚያደርግም አቶ ሙስጠፋ ተናግረዋል፡፡የኦዲፒማዕከላዊ ኮሚቴ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ በበኩላቸው በአጠቃላይ በአገሪቱ ምንም ዓይነት መፈናቀል እንዳይኖር ጥረት ይደረጋል ብለዋል፡፡የኦሮሚያ ክልል በጉጂ እና በጌዴኦ አካባቢ ተከስቶ በነበረው ግጭት ተፈናቅለው የነበሩ ወገኖችን ወደቀያቸው መመለስ መጀመሩን ገልጸዋል፡፡ከዚህ በተጨማሪ ከኦሮሚያ ክልል የተፈናቀሉ የሱማሌ ተወላጆችንም ወደቀያቸው በመመለስ ለማቋቋም እንሰራለን ብለዋል፡፡(ምንጭ፡-ኢቲቪ)
| 0 |
d1ba6ebd2460b09b1b108a700ea41a9a
|
d1ba6ebd2460b09b1b108a700ea41a9a
|
ፋሲል ከተማን ወደ ፕሪሚየር ሊግ ላሳደጉ አባላት ሽልማት ተበረከተላቸው
|
ባለፈው የውድድር ዘመን የከፍተኛ ሊጉን በቻምፒዮንነት አጠናቆ ወደ ፕሪሚየር ሊግ ላደገው ፋሲል ከተማ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ትላናት 08:00 ላይ በላንድ ማርክ ሆቴል የዕውቅና እና የሽልማት ስነ ስርአት ተደረጎለታል፡፡የሽልማት መጠኑ እንደየስራ ድርሻቸው እና ባበረከቱት አስተዋጽኦ መጠን የተከፋፈለ ሲሆን 130,000 ብር የተበረከተላቸው ዋና አሰልጣኙ ዘማርያም ወልደጊዮርጊስ ከፍተናውን ሽልማት አግኝተዋል፡፡ ለረዳት አሰልጣኙ 90,000 ፣ ለቡድን መሪ 100,000 ፣ ለህክምና ባለሙያ 60,000 ፣ ለተጨዋቾች በተጫወቱት ብዛት ተሰልቶ የመጀመሪያ ደረጃዎች 100,000 ፣ ለሁለተኛ ደረጃ 90,000 ፣ ለሦስተኛ ደረጃ 85,000 ሽልማት ተበርክቶላችዋል፡፡ ይህን ሽልማት አጠቃላይ ወጪ የሸፈነውም የጎንደር ከተማ አስተዳደር እንደሆነ ተገልጧል፡፡በሽልማት ስነ ስርአት ወቅት የፈረሰው ዳሽን ቢራ አምና ይገለገልበት የነበረውን ዘመናዊ የተጨዋቾች መመላለሻ አውቶብስ ለፋሲል ከተማ የለገሰ ሲሆን ወደፊትም ክለቡን በማንኛውም ረገድ ለመደገፍ አስፈላጊውን ነገር እንደሚያደርግ ቃል ገብቷል፡፡ ፋሲል ከተማ በከፍተኛ ሊግ በነበረው ተሳትፎ የገንዘብ እና ቁሳቁስ ድጋፍ ያደርግለት የነበረው የጎንደር ዮንቨርስቲም ቡድኑ በፕሪሚየር ሊግ በሚያደርገው ቆይታው እንደ ወትሮው ሁሉ ድጋፉ እንደማይለየው አስታውቋል ።በተያያዘ ዜና ለ2009 የውድድር ዘመን የሚጫወትበት አዲስ ማሊያ ከውጭ እንዳስመጣ የታወቀ ሲሆን እና በአካባቢው በነበረው አለመረጋጋት ምክንያት የፋሲል ከተማ የሜዳ ጨዋታዎች በተለዋጭ ሜዳዎች ሊደረግ እንደሚችል ቢገመትም ክለቡ ሁሉንም የሜዳው ጨዋታዎች በጎንደር ፋሲለደስ ስታድየም እንደሚያከናውን ለማወቅ ችለናል፡፡የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ቅዳሜ እና እሁድ በሚደረጉ ጨዋታዎች ሲጀመር ፋሲል ከተማ ከ8 አመታት በኋላ የመጀመርያ የሆነውን የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ በመጪው እሁድ 09፡00 ይርጋለም ስታድየም ላይ ከሲዳማ ቡና ጋር ያደርጋል፡፡
| 1 |
7b0855d0116139c8066e1dc836164cf5
|
7b0855d0116139c8066e1dc836164cf5
|
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከሁለት ቀናት በኋላ ዝግጅቱን ይጀምራል
|
ዋልያዎቹ ለአፍሪካ ዋንጫ አምስተኛ የምድብ ጨዋታ ቅድመ ዝግጅት ከወዲሁ ይጀምራሉ፡፡በ2021 አፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ አራት ጨዋታዎችን አድርጎ ስድስት ነጥቦች የሰበሰበው ብሔራዊ ቡድኑ ለቀጣዩ አምስተኛ የምድቡ ማጣሪያ መጋቢት ወር አጋማሽ ላይ ማዳጋስካርን በሜዳው የሚገጥም ሲሆን ለዚህም ጨዋታ ቅድመ ዝግጅት አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ለተጫዋቾች ጥሪ እንዳደረጉ ሰምተናል፡፡ ከሁለት ቀናት በኋላም ጥር 2 በጅማ ከተማ ዝግጅቱን እንደሚጀምር ታውቋል፡፡ አሰልጣኙ በኒጀሩ የማጣሪያ ጨዋታ ከጠሯቸው ተጫዋቾች በተጨማሪ አዳዲስ ዘጠኝ ተጫዋቾች በስብስቡ ማካተታቸውን ሰምተናል፡፡በጥር ወር የሚደረገው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ጅማ ላይ የሚከወን በመሆኑ ተጫዋቾቹ ባሉበት ጅማ ዝግጅት ለማድረግ እንደተመረጠ ሶከር ኢትዮጵያ ያገኘችው መረጃ ይጠቁማል። በጥር ወር መጨረሻ እና የካቲት መጀመርያ ባሉ የሊግ ጨዋታ በማይደረግባቸው ክፍት ቀናት ተጨማሪ ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚችልም ፍንጭ የሚሰጥ ነው፡፡
| 1 |
8982351b5ad4e5b31730ec35d61ab027
|
06856017fcf0103306a9313d6c3bc3c3
|
የሰላም ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ከተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ ድጋፍ ድርጅት ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ
|
አዲስ አበባ፣ መስከረም 22፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሰላም ሚኒስቴር በአዲስ አበባ ከሚገኘው የዓለም ባንክ ጽህፈት ቤት አመራሮች ጋር ውይይት አካሄደ፡፡ውይይቱ ያተኮረው ነባር የጋራ ፕሮግራሞችን በማጠናከር እና ተጨማሪ የትብብር ዘርፎችን በመዳሰስ ላይ ነበር ተብሏል፡፡የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ መንግስት ተግባራዊ ለሚደረጉ የማሻሻያ ፕሮግራሞች ባንኩ እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡በኢትዮጵያ የባንኩ ዳይሬክተር ኦስማን ዲዮን በበኩላቸው ከመንግስት ጋር ይበልጥ ውጤታማ የሆነ አጋርነት ለመመሥረት እንደሚሰሩ ቃል መግባታቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
| 0 |
35372d217d20801bd36750c08ea22d87
|
fe63e5b2cc6f37d3b30c4831c84ee82a
|
የኮቪድ 19 መከላከያ እርምጃዎች ህገ-መንግስታዊነት
|
ክፍል ሁለት ከጊዜያችን ብርቱ ፈተናዎች አንዱ ለሆነው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ መከላከያ የሚውሉ ሁነኛ መላ ፍለጋ የሚደረገው ጥረት በሁሉም አቅጣጫ ቀጥሏል።በዚህ መላውን የሰው ልጆች በገጠመ ፈተና እንደየተሰማሩበት ሞያና እንደየክህሎቶቻቸው የተያዘው ጥረት አጋዥ ለመሆን የበኩላቸውን ለማድረግ ደፋ ቀና የሚሉት ብዙዎች ናቸው።የወረርሽኙን የጥድፊያ መዛመት ለመግታትት ሁነኛ የመከላከያ ብልሃቶችን በመቀየስ አገራዊውን ጥረት ከሚያጎለብቱት፤ ከፍተኛ እጥረት የሚታይባቸውን አስፈላጊ ቁሳቁሶች እጥረት ለመቀነስ የሚያግዙ መላዎችን እስከሚፈነጥቁት ይዘልቃሉ።የኮቪድ 19 ህሙማንን ለመርዳት በግንባር የተሰለፉትየሕክምና ባለሞያዎች ለበሽታው እንዳይጋለጡ ለማድረግ በታለመ ጥረት '3D ፕሪንተር' በመባል የሚታወቀውን ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተጠቅሞ የመከላከያ ቁሳቁሶችን በመስራት ላይ የሚገኝ ወጣት ነው።ፋሩቅ ሙባረክ ይባላል። ስለ ስራውና ለዚህ መልካም ዓላማ ያነሳሱትን ምክኒያቶች ጨምሮ ሊያጫውተን ከአዲስ አበባ በስልኩ መስመር ብቅ ብሏል። የቃለ ምልልሳችንን ተከታታይ ክፍሎች ከዚህ ያድምጡ።ክፍል አንድ
| 0 |
fa6dca5bc688f78842e0c2d01876beea
|
da93e12813018c83c43e888de9bb631b
|
አዲስ አበባ እና ዋሽንግተን ዲሲ የእህታማሞች ከተማ ስምምነትን ተፈራረሙ
|
ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ውስጥ ባለፈው ቅዳሜ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሂዶ ነበር። በዓለም ባንክ ከ30 ዓመት በላይ በከፍተኛ አማካሪነት የሰሩት ዶ/ር አክሎግ ቢራራ “መደመርን መርህ ያደረገ የኢኮኖሚ መዋቅር እንዴት ይገነባል?” - የሚል ጽሑፍ አቅርበዋል።(የጹሑፉ ሐሳብ ምን እንደነበር ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)
| 0 |
5483a34f3028f6452c61421a81f32cd3
|
dc3aced7366a4af70e9bad6304849102
|
ጣሊያናዊው ግብረሰዶም በመፈጸም ወንጀል ተጠርጥረው ታሠሩ
|
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ከተማ ልማት ቢሮ መሐንዲስ፣ በሕገወጥ መንገድ መሬት በመውሰድ የሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ታሰሩ፡፡ተጠርጣሪው አቶ እስክንድር ዳሪ በከተማ ልማት ቢሮ መሐንዲስ ሆነው ሲሠሩ፣ የተለያዩ የይዞታ ማረጋገጫ ሰነዶችንና የምስክር ወረቀቶችን በመውሰድ በባለቤታቻው፣ በቤተሰቦቻቸውና በሌሎች ግለሰቦች ስም ሐሰተኛ ሰነዶችን ማዘጋጀታቸውን፣ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አሥረኛ ወንጀል ችሎት አስረድቷል፡፡ ተጠርጣሪው ያዘጋጁትን ሐሰተኛ የይዞታ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀቶች፣ የሊዝ ውል፣ ሪከርድና ማኅደር በማዘጋጀት 175 ካሬ ሜትር ቦታ መውሰዳቸውንም አክሏል፡፡ ቦታውን የወሰዱት በቀድሞ ወረዳ 28 ቀበሌ 04 ወይም በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት መሆኑንም ጠቁሟል፡፡ አቶ እስክንድር ካልተያዙ ግብረ አበሮቻቸው ጋር በጥቅም በመተሳሰር የመንግሥትና የሕዝብ ሀብት መውሰዳቸውን መርማሪው ገልጸው፣ ተጠርጣሪው ከባድና ውስብስብ የሙስና ወንጀል በመፈጸማቸው፣ እንዲሁም በመንግሥት ላይ ያደረሱት ጉዳት ከፍተኛ በመሆኑ ተገቢውን የሰውና የሰነድ ማስረጃ ለማሰባሰብ በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 59(2) መሠረት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ጠይቀው ተፈቅዶላቸዋል፡፡
| 0 |
567f0fa7e3bb222e29bd5aa8540744f3
|
13a5cdaed18cad4e2d9544f41a493985
|
ኮሚሽኑ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ለሚያደርገው ጥረት የሃረሪ ክልል እገዛ እንደሚያደርግ አስታወቀ
|
የአማራ ብሄራዊ ክልል የሰላም ኮንፈረንስ በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡በክልሉ ዘላቂ ሰላም ለማምጣት ባለመው መድረክም ከሁሉም የክልሉ አካባቢዎች የተወጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተሳተፉ ነው፡፡በዚህ ውይይት ስለሰላም ፋይዳ ጥናታዊ ጽሁፍ የሚቀርብ ሲሆን ሴቶችና ሰላምን አስመልክቶም ውይይት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡በኮንፈረንሱ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ብናልፍ አንዱዓለም ሰላም የሁሉም መሰረት እንደሆነ ጠቁመው ሰላም እንደፈለጉት የማይገኝና ከፍተኛ ዋጋ ያለው ነገር ነው ብለዋል፡፡የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ክብርት ወይዘሮ ወርቅ ሰሙ ማሞ እንዳሉትም ባለፉት ዓመታት በክልላችንም ሆነ በሀገራችን አለመረጋጋት ተከስቶ የልማት ስራዎቻችን ላይ ተጽዕኖ ሲያሳድር ቆይቷል፡፡ዘላቂ ሰላምን በመፍጠር የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ከዳር ለማድረስ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የበኩሉን አስተዋጽኦ ሊያበረክት ይገበዋል ብለዋል፡፡ይህ አይነቱ መድረክ በሌሎች የክልሉ ከተሞችም የሚካሄድ ይሆናል፡፡/የአማራ ብዙሃን መገናኛ ኤጀንሲ/
| 0 |
3174eaa75194543ff2275d8edb494256
|
fc44b63940c874e7bdd8f5c2baccdcae
|
አሜሪካዊያን ሴናተሮች በአፍሪካ
|
የኮስታሪካ ባለሥልጣናት፣ ትናንት ዕሑድ በተራራማውና በጫካ በተከበበው የምዕራባዊ ሳን ሆዜ ከተማ አካባቢ ተከስክሶ ለአሥር የዩናይትድ ስቴትስ ዜጎችና ለሁለት የኮስታሪካ ዜግነት ላላቸው ፓይለቶች ሕይወት መጥፋት ምክንያት የሆነውን የአይሮፕላን አደጋ መነሻ እያጣሩ መሆናቸው ተገለፀ።ባለሥልጣናቱ እንደገለፁት፣ በረራ ላይ እንደነበር በእሳት ከተያያዘው አይሮፕላን በሕይወት የተረፈ የለም።ከሞቱት መካከል አምስቱ አሜሪካዊያን እረፍት ላይ እንደነበሩ ኒው ዮርክ የሚገኘው ቤተሰባቸው አመልክቷል።
| 0 |
fd09acd7c632730278c05cda455b123a
|
6dc7cab810df71a5197bbc34531b270f
|
የሩስያ ልዑክ ጎንደርን እየጎበኘ ነው።
|
አዲስ አበባ ፣ መስከረም 30 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበር አካባቢ ያለውን ሠላም ለማረጋገጥ በጋራ እንደሚሠሩ የሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ ወታደራዊ ልዑክ ገለጸ፡፡የሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ ወታደራዊ ልዑክ በድንበር አካባቢ ሠላምን ለማረጋገጥ በሚቻልበት አግባብ በባሕር ዳር ከተማ ምክክር እያካሄደ ነው፡፡የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ፅሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ እርዚቅ ኢሳ አትዮጵያና ሱዳን በባህል፣ በኢኮኖሚ በከፊልም በቋንቋና በሃይማኖት እንደሚቀራረቡ ተናግረዋል፡፡ሁለቱ ሀገራት ድንበር አካባቢ አልፎ አልፎ የሚስተዋለውን የፀጥታ ችግር ለመከላከል የሚረዳ የተሳካ ውይይት እንደሚያደርጉም ተስፋቸውን ገልጸዋል፡፡ በቅርቡ የሱዳን ባለሀብቶች በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የተሳካ ጉብኝት ማድረጋቸው ሀገራቱ ግንኙነታቸውን በኢኮኖሚያዊ ትስስር ለማጠናከር እየሄዱበት ያለውን ርቀት ማሳያ ነው ብለውታል፡፡ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ወታደራዊ ልዑክ መሪ ብርጋዴር ጄኔራል ሙሉዓለም ዓድማሱ እና የሱዳኑ ከፍተኛ ወታደራዊ ልዑክ መሪ ሜጀር ጄኔራል ሷልህ አብደላ ኢሳቅ በሁለቱ ሀገራት ድንበር አካባቢ ያለውን ሰላም ለማረጋገጥ በጋራ እንደሚሠሩ አስታውቀዋል፡፡በቆይታቸውም በሀገራቱ ድንበር አካባቢ አልፎ አልፎ የሚስተዋሉ የፀጥታ ችግሮችን በጋራ ለመፍታት የተሳካ ውይይት በማድረግ በትብብር እንደሚሠሩ መግለጻቸውን አብመድ ዘግቧል፡፡
| 0 |
5921d93fdf96c1c86ce616398715ce0a
|
f303272910bec94e29b6047ac333e44c
|
አፍሪካ በጋዜጦች
|
አፍሪካ በጋዜጦች የተሰኘው ፕሮግራማችን ስለ አፍሪካ ከተፃፉት፣ የተወሰኑትን ጨምቆ ያቀርባል።ሁኔታዎች የተረጋጉ ቢመስሉም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲቀጥል ተደረገ ይላል ዋሽንግተን ፖስት ጋዜጣ፣ ጀርመን የአፍሪካ ፀጥታንና ልማትን ለማጠናከር ማቀድዋ ሮይተርስ ገለፀ፣ የህንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ በአፍሪካውያን ተማሪዎች ላይ የሚፈፀመውን ጥቃት እንዳወገዙ ጋርዲያን ጋዜጣ ጠቆመ የሚሉትን ርዕሶችን በዛሬው ቅንብራችን የምንመለከተው።ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
| 0 |
d2dbbf004e0e605c9c6ccda6b83ce802
|
17d725686f806a720bf551909197799f
|
ሃያ ሺ የሚጠጉ አባወራዎች ዘመናዊ የፍሳሽ ማስወገጃ ተጠቃሚ መሆናቸው ተጠቆመ
|
ከአዲስ አበባ ከተማም ሆነ ከክልል ለሚመጣ በዳግማዊ ምንሊክ ሆስፒታል የሚደረገው የአስከሬን ምርመራ ውጤት መዘግየት ከፍተኛ ችግር መፍጠሩ ተጠቆመ፡፡አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በደረሱ የተለያዩ አደጋዎች ሕይወታቸው ያለፉ ሰዎችን አስከሬን ምርመራ ውጤት ለማግኘት፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከሁለት ወራት በላይ እየጠበቀ መሆኑን የሰው መግደልና ወንጀል ምርመራ ዲቪዚዮን አባላት ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ከሰኔ ወር ጀምሮ የምርመራ ውጤት ማግኘት ባለመቻሉ፣ ለኢንሹራንስና ለተጨማሪ ምርመራ እንዲሁም ለተለያዩ ጉዳዮች ማስረጃ ለማቅረብ የሟች ቤተሰቦች እየተንገላቱ መሆኑን የዲቪዚዮኑ ባልደረቦች ገልጸዋል፡፡ብቸኛ በሆነው የዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታል የሚደረገውን የአስከሬን ምርመራ ውጤት፣ ከስፓኒሽኛ ቋንቋ ወደ እንግሊዝኛና ወደ አማርኛ የሚተረጉም አንድ ባለሙያ ብቻ በመኖሩ፣ ለችግሩ ምክንያት መሆኑም ተገልጿል፡፡ የሆስፒታሉ አብዛኛዎቹ የአስከሬን ምርመራ ባለሙያዎች የኩባ ዜጎች መሆናቸው ይታወቃል፡፡በተለይ ከክልል በሪፈራል ወደ አዲስ አበባ መጥቶ ሕይወቱ ያለፈ ሰው፣ ቤተሰቦቹ ከፍተኛ ችግር ውስጥ እየገቡና የፖሊስ ኮሚሽኑን በማስቸገር ላይ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ ይዘውት የመጡትን ገንዘብ በሕክምናና በምርመራ ውጤት በመጨረስ ወደ ልመና የሚገቡ እንዳሉም ተጠቁሟል፡፡የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በተደጋጋሚ ደብዳቤ ከመጻፍ ባለፈ ምንም ማድረግ አለመቻሉንና ከአቅሙ በላይ እንደሆነበትም እየገለጸ ነው፡፡የዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታል ዋና ሥራ አስኪያጅ ሪፖርተር አነጋግሯቸው፣ ‹‹እኔ እስከማውቀው ድረስ ምንም የተፈጠረ ችግር የለም፤›› በማለት አስተባብለዋል፡፡ የሆስፒታሉን ሜዲካል ዳይሬክተር ለማግኘት የተደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡
| 0 |
51b351a0b49e198a4b7e770e6e47412b
|
25d30bf2152ec0b3620d9e0605c37223
|
ኢትዮጵያ በሕዳሴው ግድብ ድርድር ሰበብ የዓባይ ወንዝ ተጠቃሚነቷን የሚገድብ ስምምነት እንደማትቀበል አቶ ገዱ አንዳርጋቸው አረጋገጡ።
|
አዲስ አበባ ፣ ጥር 22 ፣ 2012 (ኤፍ. ቢ. ሲ) በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ ለቀናት በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ደረጃ በዋሽንግተን ዲሲ ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብፅ ድርድር ተጠናቀቀ። ባለፈው ማክሰኞ ተጀምሮ በሁለት ቀናት ውስጥ መጠናቀቅ የነበረበት ድርድሩ እስከ ዛሬ ድረስ ቀጥሎ ነበር። ሚኒስትሮቹ ድርድራቸውን ዛሬ ሲያጠናቅቁ የጋራ መግለጫ በማውጣት መሆኑንም ነው የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ማምሻውን የገለፁት። በዋሽንግተኑ ውይይት ላይ የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸውን ጨምሮ የሁሉም ሀገራት የውጭ ጉዳይ እና የውሃ ሚኒስትሮች፣ የውኃ ዘርፍ እና የህግ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል። በተጨማሪም የአሜሪካ የግምጃ ቤት ኃላፊ እና የአለም ባንክ ተወካዮች በታዛቢነት ተሳትፈዋል። በድርድሩ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን የውሃ ሙሌት እና አለቃቀቅ በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ትኩረት የተደረገ ሲሆን፥ በድርቅ ( Drought)፣ በአመታት የተራዘመ ድርቅ (prolonged drought) እንዲሁም በተራዘመ አመታት አነስተኛ የወንዝ ፍሰት (prolonged periods of dry years) ወቅት የሚኖረው የአሞላል ሥርዓት ላይ መሰረታዊ መግባባት መደረሱን ነው የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያስታወቀው። ስምምነት ያልተደረሰባቸው ቀሪ ጉዳዮች በቀጣይ ውይይቶች መፍትሄ የሚያገኙ ሲሆን፥ የሙሌት እና ውሃ አለቃቀቅ ዝርዝር ረቂቅ ሰነድ እንደሚዘጋጅ ገልጿል። በሕዳሴው ግድብ የውሃ አሞላል እና አለቃቀቅ ላይ የሚደረገው ድርድር በግድቡ ብቻ ላይ የተወሰነ መሆኑን፣ እንዲሁም የሀገራችንን ነባር እና የወደፊት በአባይ ወንዝ የመጠቀም መብት በሙሉ የሚያስከብር ማድረግ የኢትዮጵያ መንግስት የማይቀየር አቋም መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በኢትዮጵያ ሕዝብ ገንዘብ እየተሰራ የሚገኘው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ራስን ችሎ የመልማት መብት እንዲሁም የትብብር መገለጫ ነው ብሏል ሚኒስቴሩ። መንግስት ግንባታውን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያደርገው ጥረት የቅድሚያ ትኩረት የሚሰጠውም ነው ብሏል። መንግስት በቀጣይ በጉዳዩ ዙሪያ ዝርዝር መረጃዎችን ለሕዝብ እንደሚያሳውቅ አመልክቷል።
| 0 |
2917c512a8a4ca69045c268042323530
|
2917c512a8a4ca69045c268042323530
|
ሰፊ ችግር ነበረበት የተባለው የማላዊ ምርጫ ሊደገም ነው
|
የማላዊ ፍርድቤት የባለፈው አመት ምርጫ ሰፊ ችግር ነበረበት በማለት ውጤቱን ከሰረዘው በኋላ ሀገሪቱ በመጭው ግንቦት ወር በድጋሚ ምርጫ እንደምታካሄድ ሲጂቲኤን ዘግቧል፡፡
የምርጫ ጊዜ ሰሊዳውን ያስቀመጠው የሀገሪቱ ፓርላማ ሲሆን ፓርላማው ይህን ለመወሰን የምርጫ ደንቡን አሻሽሏል፡፡
የተሻሻለው ህግ አስገላጊውን አብላጫ ድምጽ ያገኘ እጩ ከሌሌ በስተቀር ምርጫ በ30 ቀናት ውስጥ እንዲካሄድ ይፈቅዳል፡፡
ፕሬዘዳንት ፒተር ሙታሪካና የሀገሪቱ የምርጫ ኮሚሽን ፍርድቤቱ ዉሳኔውን እንዲቀለብስ አቤት ብለዋል፡፡
ሙታሪካ የፓርላማውን ውሳኔ ማጽደቅ ወይንም አለማጽደቅ ወሳኔ ላይ ለመድረስ 21 ቀናት አሏቸው፡፡
የኪንያ ፍርድቤት እ.ኤ.አ. በ2017 በኬንያ የነበረውን ፕሬዘዳንታዊ ምርጫው እንዲሰረዝ ካደረገ በኃላ በአፍሪካ የምርጫ ውጤት ተሰርዞ ሲደገም ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡
የማላዊ ፓርላማ የአሁኖቹ የምርጫ ኮሚሽነሮች ቢቀየሩ የሚል ኃሳብ ሰጥቷል፡፡
| 1 |
7ce3a08f7267a315b3b6057ea278f573
|
2ac0d6046042faf6d243e67b79673bb2
|
የኢራን የኑክሌር አገልግሎት ዩራንየምን የማዳበር ሥራ መቀጠሉን አስታወቀ
|
ባሕር ዳር፡ መስከረም 10/2012 ዓ.ም (አብመድ) የኢትዮጵያ ባሕር ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ፤ ነገር ግን ለሜቴክ በዱቤ የሰጠው የ2 ቢሊዮን ብር ዱቤ አገልግሎት እንዳልተከፈለው ገልጿል፡፡የኢትዮጵያ ባሕር ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ባለፈው የበጀት ዓመት 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ትርፍ ማግኘቱን ገለጸ፡፡ የአገልግሎቱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሮባ መገርሳ እንዳስታወቁት ባለፈው ዓመት አማካይ የኮንቲነር የወደብ ቆይታ 6 ቀን ከ6 ሰዓት ነበር፡፡
| 0 |
28f80cc824631ed774ad5adfb2614a2c
|
c7d304018c47a16935952018ba248631
|
በአዲስ አበባ ለሰው ሕይወት አደጋ የሆኑ ጉድጓዶች እንዲከደኑ ትዕዛዝ ተሰጠ
|
ሰኞ ሐምሌ 22 ቀን 2011 ዓ.ም. በመላ አገሪቱ 200 ሚሊዮን ችግኞች የሚተከሉበት መርሐ ግብር ተይዟል፡፡ ‹‹አገራዊ የአረንጓዴ ልማት ድርጊት መርሐ ግብር›› በመባል በሚታወቀው አረንጓዴ አሻራ የማኖር ሥነ ሥርዓት፣ በችግኝ ተከላ የዓለም ክብረ ወሰን ለመስበር ዕቅድም ተይዟል፡፡ በመላ አገሪቱ በአጠቃላይ አራት ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታስቦ እስካሁን 2.7 ቢሊዮን ችግኞች መተከላቸውን የውኃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር በቅርቡ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል፡፡ ለማኅበራዊ ምርታማነት፣ ተጋላጭነትን ለመቋቋም፣ ለአየር ንብረት ተፅዕኖ መቀነስና መላመድ፣ ጤናን ለማሻሻል፣ ለዱር እንስሳት ከለላ፣ ለብዝኃ ሕይወት ከለላ፣ ለውኃ ማንፃትና ከለላ፣ እንዲሁም ለኢኮኖሚ ጠቀሜታ (ደንና ግብርና) ሲባል በሚከናወነው መርሐ ግብር በመላ አገሪቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ይሳተፉበታል ተብሏል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ለችግኝ ተከላው 2.8 ሚሊዮን ጉድጓዶች መዘጋጀታቸው ተገልጿል፡፡ ነዋሪዎች በ116 ወረዳዎች በችግኝ ተከላው የሚሳተፉ ሲሆን፣ ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡም የመትከያ ቦታ መዘጋጀቱ ታውቋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በተለያዩ ጊዜያት ችግኞችን ሲተክሉ መሰንበታቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ከተለያዩ የውጭ አገር እንግዶች ጋርም ሲተክሉ ነበር፡፡ ሰኞ ሐምሌ 22 ቀን 2011 ዓ.ም. ደግሞ በደቡብ ክልል በወላይታ ዞን በሶዶ ከተማ ዳሞት ተራራ ላይ፣ ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር ችግኝ እንደሚተክሉ ታውቋል፡፡ በምሥሉ ላይ የሚታየው የዳሞት ተራራ ሲሆን፣ ችግኞቹ ደግሞ በሶዶ የደንና ዕፅዋት ልማት ፕሮጀክት የፈሉ ናቸው፡፡
| 0 |
05face34cdf3cbc2c115cc87aa105bf0
|
9711082c4432684c48ef12a77c32197e
|
ወልዲያ አርብ ወደ ውድድር ይመለሳል
|
ከወድድር አመቱ ጅማሮ አንስቶ ባልተረጋጋ ሁኔታ እየተወዳደረ የሚገኘው ወልዲያ ስፖርት ክለብ ከሰሞኑ በተደጋጋሚ ከአንድ ወር በላይ ጊዜ ቡድኑን እንዲቀላቀሉ ጥሪ ቢደረግላቸውም ፍቃደኛ አልሆኑም በማለት በመተዳደርያ ደንቡ መሰረት በሦስቱ ተጨዋቾቹ ላይ የሁለት አመት ቅጣት ማስተላለፉ እና ቅጣቱ ተገቢ አይደለም በሚል ተጫዋቾቹ ቅሬታቸውን ለፌዴሬሽኑ ዲሲፕሊን ኮሚቴ ማቅረባቸው ይታወቃል።ክለቡ አለብኝ በሚላቸው ክፍተቶች ላይ የዝውውር መስኮቱ መከፈቱን ተከትሎ ሦስት ተጨዋቾች ወደ ክለቡ ያመጣ ሲሆን ቅጣት ያስተላለፈባቸው ተጫዋቾችን ጨምሮ መያዝ የሚፈቀድለትን የተጫዋች ብዛት በስብስቡ ይዟል። ሆኖም ቅጣት ያስተላለፈባቸው ተጫዋቾች ለቡድኑ ግልጋሎት የማይሰጡ በመሆናቸው በምትካቸው አዳዲስ ተጫዋቾች ለማስፈረም ወደ ፌዴሬሽን በሚያመሩበት ወቅት የተጫዋቾቹ ጉዳይ እልባት ሳያገኝ ውል መፈፀም እንደማይችሉ ተገልጾላቸዋል። ይህ የፌዴሬሽኑ ምላሽም ተገቢ አይደለም በማለት ቅሬታቸውን ማሰማታቸውን የክለቡ ስራ አስኪያጅ አቶ ገረመው ለሶከር ኢትዮጵያ ገልፀዋል።” የዲሲፕሊን ኮሚቴ የመጨረሻ ውሳኔ ምንም ይሁን ምን እየጠበቅን ነው። ክለቡ ውድድር ውስጥ ሆኖ ከፍተኛ የሆነ የተጫዋቾች ቁጥር ማነስ እንዳለበት እየታወቀ ተጨዋች እንዳናስፈርም መደረጉ አግባብነት የለውም። ፌዴሬሽኑ በውሳኔው የሚፀና ከሆነም ቡድኑ በቀጣይ በሚኖሩት ተከታታይ ወሳኝ ጨዋታዎች ለሚገጥመው የውጤት መጥፋት ኃላፊነቱን እንዲወስድ ስንል ደብዳቤ አስገብተናል” ብለዋል ።በሦስቱ ተጨዋቾች (ፍፁም ገብረማርያም፣ ታደለ ምህረቴ እና ያሬድ ብርሀኑ) እና በክለቡ መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት ለመፍታት የዲሲፕሊን ኮሚቴው ዛሬ ማምሻውን የመጨረሻ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
| 0 |
500000cffb5e248b1f90f5681aae5bc6
|
500000cffb5e248b1f90f5681aae5bc6
|
የኢትዮጵያ ከ23 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ዝግጅቱን ጀመረ
|
መጋቢት 12 ለቶኪዮ ኦሊምፒክ አንደኛ ዙር የማጣርያ ጨዋታውን ከማሊ ጋር በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚያደርገው የኢትዮጵያ ከ23 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ዛሬ ዝግጅቱን ጀምሯል።በመጀመርያው ጥሪ ለ33 ተጫዋቾች ባሳለፍነው ሳምንት ጥሪ ያደረጉት አሰልጣኝ አብርሃም መብራቱ ዛሬ በይፋ ከ09:30 ጀምሮ በአዲስ አበባ ስታድየም በመገኘት ዝግጅታቸውን ጀምረዋል።በዛሬው የልምምድ መርሐግብር ላይ ጥሪ ከተደረገላቸው 33ቱም ተጫዋቾች የተገኙ ሲሆን አሚን አህመድ የተባለ በሀገር እንግሊዝ የሚኖር በታችኛው ዲቪዚየን (Mousehle AFC) የሚጫወት ትውልደ ኢትዮጵያዊ ከቡድኑ ጋር የተካተተ ሌላ ተጫዋች ሆኗል። በዛሬው ዕለት ሁለት ሰዓት በቆየው ልምዳቸው በግማሽ ሜዳ ለሁለት ተቧድነው እንዲጫወቱ በማድረግ ተጫዋቾቹ አሁን ያሉበትን ደረጃ ለማየት ተሞክሯል።ከልምምዱ መጠናቀቅ በኋላ አሰልጣኝ አብርሃም መብራቱ ” የመጀመርያው የልምምድ ምዕራፍ ሲጠናቀቅ አስር ተጫዋቾችን እንቀንሳለን። የቀሩት ሃያ ሦስት ተጫዋቾች ከማሊ ጋር በሚኖረን የደርሶ መልስ ጨዋታ ከቡድኑ ጋር አብረው የሚቆዩ ይሆናል። ሲጠናቀቅ የምናሳውቀው ቢሆንም ከማሊ ጨዋታ አስቀድሞ ሁለት አልያም አንድ የአቋም መፈተሻ ጨዋታ ለማግኘት እየተነጋገርን ነው፤ እንደተጠናቀቀ እናሳውቃለን። ” ብለዋል። አክለውም ለብሔራዊ ቡድኑ ዝግጅት እንደፈተና እየተወሰደ ያለውና በመሐል ለሚደረገው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች ተጫዋቾቹ ወደየክለባቸው ያመራሉ ለሚለው ጥያቄ ” ተጫዋቾቹን አንለቅም፤ ከእኛ ጋር አብረው ይቆያሉ ” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
| 1 |
5f84926077d898dd9e313eec3a79ebc3
|
19f3dc068f49bb7c07462caac11affe0
|
የቡና የግብርናና የላይቭ ስቶክ ኤግዚቢሽን ይከፈታል
|
አዲስ አበባ፦
የቡና ዋጋ በዓለም ገበያ ዕለት ከዕለት ቅናሽ እያሳየ በመሆኑ በኤክስፖርቱ ላይ ተፅዕኖ አሳድሯል ተባለ። አቶ ትዕዛዙ ኢዶሳ፤ በቡናና ሻይ ባለስልጣን የገበያ መረጃና ቁጥጥር ተወካይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለፁት፣ ከአሥራ አንድ ዓመት ወዲህ የዓለም የቡና ዋጋ ዕለት ከዕለት እየቀነሰ በመምጣቱ በኤክስፖርቱ ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ ይገኛል። ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ በመጠን 195 ሺህ አምስት መቶ 74 ቶን ቡና ኤክስፖርት ለማድረግ ታቅዶ፤ 151 ሺህ 211 ነጥብ አምስት ቶን ኤክስፖርት ማድረግ ተችሏል። ይህም ከገቢ አንፃር ሲታይ 498 ነጥብ ስምንት ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን ተናግረዋል። ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የምርትም ሆነ የስቶክ ችግር የሌለ በመሆኑ በመጠን የተሻለ አፈፃፀም ተመዝግቧል። ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት በዓለም የቡና ዋጋ ከዕለት ዕለት በከፍተኛ መጠን እየቀነሰ በመምጣቱ በገቢ ረገድ የቡና ዋጋ በከፍተኛ መጠን ቅናሽ አሳይቷል። የኒዎርክን ገበያ ስንመለከት የቡና ዋጋ ከአሥራ አንድ ዓመት ወዲህ ታይቶ በማይታወቅ መጠን ቅናሽ እያስመዘገበ ይገኛል። ይህም እንደ ሀገር ኤክስፖርቱ እንዲቀዛቀዝ ምክንያት መሆኑን አቶ ትዕዛዙ ገልፀዋል። የቡናና ሻይ ባለስልጣን ቡና፤ ቅመማ ቅመምና ሻይ ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሰራ እንደመሆኑ አጠቃላይ በሦስቱ ምርቶች በዘጠኝ ወራት ውስጥ በመጠን 158‚039 ነጥብ ዘጠኝ ቶን ምርት ኤክስፖርት በማድረግ 507 ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት ተችሏል። ምንም እንኳን የቡና ዋጋ ዕለት ከዕለት ቅናሽ እያሳየ የመጣ ቢሆንም ከሦስቱ የምርት ዓይነቶች በኤክስፖርት መጠኑ ቡና ቀዳሚ ሲሆን፤ ሻይ ሁለተኛ ደረጃ፤ ቅመማ ቅመም ደግሞ በሦስተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አቶ ትዕዛዙ አስታውሰዋል።አዲስ ዘመን ሚያዝያ 23/2011
| 0 |
1c699b8cbef520ca5445c76523257a7a
|
b33b545536294bb59feae97b7a18660a
|
ጠ/ሚ ዐቢይ ከኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ተወያዩ
|
የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በሶማልያና ኬንያ ሪፖብሊኮች የሦስት ቀናት የሥራ ጉብኝት አጠናቀው ባለፈው ቅዳሜ ወደ ሀገራቸ ተመልሰዋል።ከኬንያው ርዕሰ ብሄር ኡሁሩ ኬንያታ ጋር ግንኑነታቸውን ስለማጠናከርና ሁለቱን ሀገሮች ስለሚጠቅም የክልላዊ እደገት እንደተነጋገሩ ተዘግቧል። በሁለቱም ሀገሮች መካከል ያለውን የትብብር ዕድል መሰረት በማድረግ በንግድና በመዋዕለ-ነዋይ ዘርፎች አጋርነት እንዲዳብር ለመስራት ተስማተዋል። በሶማልያ ሰላምና መረጋጋት እንዲኖር ለመጣርም ተስማምተዋል ተብሏል።ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ባቀረቡት ግብዣ መሰረት ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በመጪው ጥር ወር ኤርትራን ይጎበኛሉ።ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ዛሬ ደግሞ አቡ ዳቢ ሄደው ከአልጋወራሽ ሼኽ ሞሐመድ ቢን ዛይድ ጋር ተገናኝተዋል።
| 0 |
0961134e83446f4610c0bd5f5c7d5d02
|
8821c50888d1026149aaddf85e81ae24
|
ሦስቱን ክልሎች የሚያገናኝ የመንገድ ግንባታ ተጀመረ
|
አዲስ አበባ፣ግንቦት 9፣2012(ኤፍ.ቢ.ሲ)የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ከሀይሌ ጋርመንት ጀሞ እየተገነባ ያለውን መንገድ ጎብኝተዋል።መንገዱ አዲስ አበባና አምቦ መስመርን የሚያገናኝ ነውም ነው የተባለው።ከዚያም ባለፈ መንገዱ የአዲስ አበባ መውጪያዎችን ከኦሮሚያ አጎራባች ከተማዎች የሚያገናኙ መንገዶችን የመገንባት አንዱ ክፍል መሆኑ ተጠቁሟል።የሀይሌ ጋርመንት —ጀሞ መንገድ ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ ሲሆን በቀጣይም ሁለተኛው ምእራፍ ግንባታ የሚቀጥል ይሆናልም ነው የተባለው።በመጠናቀቅ ላይ ያለው መንገድ 4ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን 6 ተሽከርካሪዎች ማስተናገድ የሚችል 60 ሜትር ስፋት ያለው መሆኑም ነው የተመላከተው።ከዚያም ባለፈ መንገዱ የእግረኛ መጓጓዧና የብስክሌት መጓጓዧ ያካተተ ነው ተብሏል።የመንገዱ ግንባታ በአካባቢው የሚታየውን የትራፊክ መጨናነቅ ለመቀነስ የታሰበና እንዲሁም አዲስ አበባን ከሚያዋስኑ የኦሮሚያ ከተማዎች ጋር በዘመናዊ መንገድ በማስተሳሰር የንግድ ስርአቱን ለማቀላጠፍ ያለመ መሆኑን ከከንቲባ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
| 0 |
1c8e3dea5262fb95ed9c980c6ae85f43
|
511dcff407cf3b83ab63585d10b2dc70
|
ኳታር በሶማሊያ አየር ክልል ያላትን የበራራ ቁጥር አሳደገች
|
የኢትዮጵያ መንግሥት የድርቅ አደጋ ላጋጠማቸው የሶማሊያ ዜጎች የሰብዓዊ ድጋፍ ማድረጉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው ኢትዮጵያ በድርቅ ለተጎዱ የሶማሊያ ዜጎች ሰባት ሺህ ኩንታል ሩዝ ድጋፍ አድርጋለች።ከዚህም በተጨማሪ አምስት ሺህ ኩንታል ዱቄት፣ 30 ሺህ ጣሳ የዱቄት ወተትና 300 ኩንታል ኃይል ሰጪ ብስኩት ለሶማሊያ ድጋፍ ማድረጓ ነው የገለጸው።በቅርቡ በሶማሊያ በተከሰተው ድርቅ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሶማሊያዊያን ለከፋ ችግር በመጋለጣቸው የአገሪቱ መንግሥት የድጋፍ ጥሪ ማቅረቡ የሚታወስ ነው።ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ለሶማሊላንድ አስተዳደርም የአልሚና የኃይል ሰጪ ምግቦች እርዳታ ማድረጓ አይዘነጋም።ሁለቱ ድጋፎች ኢትዮጵያ ለጎረቤት አገራት ያላትን ወዳጅነትና የችግር ደራሽነት ያረጋገጠችበት መሆኑ ተገልጿል።ኢትዮጵያ ከደቡብ ሱዳንና ከኤርትራ የሚመጡ ስደተኞችን በመቀበልም የመጠለያ እና የማኅበራዊ አገልግሎቶችን በማቅረብ ላይ መሆኗ ይታወቃል።ይህም ኢትዮጵያ ለጎረቤት አገሮች ሕዝቦች ያላትን አክብሮትና ከአገራቱ ጋር ጠንካራ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ለመፍጠር ያላትን ፍላጎት ያመላክታል ነው የተባለው።ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከ800 ሺህ በላይ የጎረቤት አገራት ስደተኞችን ማስጠለል ችላለች-(ኢዜአ) ።
| 0 |
e7616f5a0db85a4239d5a56f9f3688d9
|
be03875dc64c919d1780d32a8c13c331
|
ቲፒ ማዜምቤ የኮንፌድሬሽን ካፕ ቻምፒዮን ሆነ
|
በተለያዩ ከተሞች ሲካሄድ የቆየው የ2011 ዓ.ም የኢትዮጵያ ቮሊቦል የወንዶች ፕሪሚየር ሊግ ወላይታ ድቻ ቻምፒዮን ሆኖ አጠናቋል። ወላይታ ድቻ በአጠቃላይ የፕሪሚየር ሊግ ውድድሮች 35 ነጥብ በመሰብሰብ ቻምፒዮን እንደሆነ የኢትዮጵያ ቮሊቦል ፌዴሬሽን ያደረሰን መረጃ ያሳያል፡፡ ወላይታ ድቻን ተከትሎ የመዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ 34 ነጥብ በመሰብሰብ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቅ ችሏል፡፡ ሰላሳ ነጥቦችን መሰብሰብ የቻለው ሙገር ሲሚንቶ ሦስተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል፡፡ ፕሪሚየር ሊጉ መጠናቀቁን ተከትሎ በተለያዩ ዘርፎች በውድድር ዓመቱ ኮከብ የሆኑ ቡድኖችና ተጫዋቾች እንዲሁም አሰልጣኞች ተሸላሚ ሆነዋል፡፡ በዚህም መሰረት
የዓመቱ ኮከብ አሰልጣኝ
በመሆን ተፈራ በላቸው
ከመዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ
ተሸላሚ ሲሆኑ፣ የዓመቱ
ምስጉን ዳኛ ተስፋዬ
ስለሺ ሆነው ተመርጠዋል፡፡
የዓመቱ ኮከብ ቡድን
መሪ አየለ ድራሞ
ከ ወላይታ ድቻ፣
የዓመቱ ኮከብ ሴተራ
አሸናፊ ደምሴ ከ ወላይታ
ድቻ፣ የዓመቱ ኮከብ
ሊብሮ ኃ/ሚካኤል ተስፋዮሐንስ
ከ ወላይታ ድቻ፣
የዓመቱ ኮከብ ስፓይከር
እስጢፋኖስ ዳልጋ ከመዳ
ወላቡ ዩኒቨርሲቲ፣ የዓመቱ
ኮከብ ሁለገብ ተጫዋች
ሰለሞን ፍቃዱ ከፌዴራል
ማረሚያ ቤቶች፣ የፀባይ
ዋንጫ ተሸላሚ መዳ ወለቡ
ዩኒቨርሲቲ፣ የዓመቱ የልዩ
ዋንጫ ተሸላሚ ሐበሻ
ሲሚንቶ በመሆን ፕሪሚየር
ሊጉ ተጠናቋል፡፡አዲስ ዘመን ሰኔ 13/2011ቦጋለ
አበበ
| 0 |
81f3134672ba14e2c9105bcd9d16f9cb
|
98980b5c819d5fec56d59b223432baf8
|
አአ ከተማ ዋንጫ | ባህር ዳር ከተማ ድል አድርጓል
|
ነገ በባህር ዳር ዓለማቀፍ ስታዲየም ኮትዲቯርን የሚገጥሙት ዋሊያዎቹ ከአንድ ሰዓት በፊት ባህር ዳር ደርሰዋል።ከትላንት በስትያ በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ማዳጋስካርን የገጠሙት ዋሊያዎቹ ሁለተኛ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታቸውን ነገ በባህር ዳር ዓለማቀፍ ስታዲየም 10:00 ላይ ያከናውናሉ። ለዚህ ጨዋታ ቡድኑ ትላንት አመሻሽ አዲስ አበባ የገባ ሲሆን ከአንድ ሰዓት በፊት ጨዋታው ወደሚደረግበት ከተማ ተጉዟል።7:00 ሰዓት በባህር ዳር አየር ማረፊያ የደረሰው ቡድኑ በከተማው ደጋፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል። 20 ተጨዋቾችን በመያዝ ወደ ባህር ዳር ያመራው ልዑካኑ ዋና አሰልጣኙን በበረራው እንዳላካተተ ተሰምቷል። አሰልጣኝ አብርሃም መብራቱ ከተጨዋቾቹ ጋር ወደ ባህር ዳር እይጓዙ እንጂ በቀጣይ በረራ ወደ ባህር ዳር እንደሚያመሩ ተሰምቷል።ብሄራዊ ቡድኑ ዛሬ 11 ሰዓት ነገ ጨዋታውን በሚያከናውንበት ባህር ዳር ዓለማቀፍ ስታዲየም ቀለል ያለ ልምምዱን እንደሚሰራ ተነግሯል።በተያያዘ ዜና የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተጋጣሚ የሆነው የኮትዲቯር ብሄራዊ ቡድን አመሻሽ ባህር ዳር እንደሚገባ ተሰምቷል። ሶከር ኢትዮጵያ ከቡድኑ (ኮትዲቯር) ልዑካን በፊት አርብ ባህር ዳር የገባውን አስተባባሪ ጠይቆ እንደተረዳው ከሆነ ዝሆኖቹ ልምምድ ለመስራት እንዳላሰቡ ተጠቁሟል። ቡድኑ አመሻሽ ባህር ዳር ገብቶ፣ ነገ ጨዋታውን አከናውኖ በዛው ምሽት ወደ አዲስ አበባ እንደሚያመራ ተገልጿል።ከኮትዲቯር ብሄራዊ ቡድን ጋር በተያያዘ የክሪስታል ፓላሱ የመስመር አጥቂ ዊልፍሬድ ዘሃ ከነገው ጨዋታ ውጪ እንደሆነ ተነግሯል።ነገ 10:00 የሚደረገውን ጨዋታ የአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት (አማራ ቲቪ) በቀጥታ እንደሚያስተላልፍ ተጠቁሟል።
| 0 |
a153cc927923e24a3549a28a8d1f1297
|
377c70c719117558d987fa6e6c8cb4ad
|
ተጨማሪ 604 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው 1 ሺህ 65 ሰዎች ደግሞ ከቫይረሱ አገግመዋል
|
አዲስ አበባ፣ታህሳስ 27፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ ለ3 ሺህ 934 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ 322 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ።ዶክተር ሊያ በፌስቡክ ገጻቸው እንደገለጹት 203 ሰዎች ደግሞ ከቫይረሱ አገግመዋል፡፡እንዲሁም ባለፉት 24 ሰዓታት በቫይረሱ ምክንያት 13 ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡እስካሁን ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች 112 ሺህ 813 ሲደርስ 1 ሺህ 963 ሰዎች ደግሞ ለህልፈት ተዳርገዋል፡፡በአሁኑ ጊዜ ቫይረሱ ያለባቸው 11 ሺህ 463 ሲሆኑ ከእነዚህ ውስጥ 245 ሰዎች ደግሞ በጽኑ የታመሙ መሆናቸውን ነው የገለጹት፡፡ወረርሽኙ ኢትዮጵያ ከገባ ጀምሮ ለ1 ሚሊየን 826 ሺህ 56 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጓል፡፡ከእነዚህም መካከልም 126 ሺህ 241 በወረርሽኙ የተያዙ ሲሆን አሁን ላይ 11 ሺህ 463 ሰዎች ቫይረሱ እንዳለባቸው ተገልጿል፡፡ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
| 0 |
e6d6ed82fa6110a24cf84a25fd7d29b2
|
69a34f1b1dc6585d2295de057a487315
|
ነውጠኛው ቡድን የጦር መሣሪያዎች ከኢራቅ እንደሚያገኝ አምነስቲ አስታወቀ
|
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 15፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ መንግስት ህገ ወጡ የህወሓት ቡድን በማይካድራ በንጹሃን ዜጎች ላይ የፈፀመውን ጭካኔ የተሞላበት ተግባር አወገዘ።የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ይፋ ባደረገው ሪፖርት፥ የህወሓት ፅንፈኛ ቡድን ሀይሎች በማይካድራ በንፁሃን ዜጎች ላይ የፈፀሙት ጭካኔ የተሞላበት ተግባር እና ከፍተኛ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ልብ ሰባሪ መሆናቸውን መንግስት አስታውቋል።የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ይፋ ያደረገው ሪፖርት ከዚህ ቀደም አምነስቲ ኢንተርናሽናል ያወጣውን ሪፖርት የሚያረጋግጥ መሆኑንም የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ያወጣው መግለጫ ያመላክታል።ተግባሩ ህገ ወጡ የህወሓት ቡድን በኢትዮጵያ እየፈፀመ ያለው ጭካኔ የተሞላበት ወንጀል ምን ያክል እንደሆነም የዓለም ህዝብ በድጋሚ ያረጋገጠበት ነውም ብሏል ባወጣው መግለጫ።የኮሚሽኑ ሪፖርት የማይካድራው ጥቃት ተራ የወንጀል ተግባር ሳይሆን በእቅድ እና በተቀናጀ መንገድ የተፈፀመ የሰብአዊ መብት ጥሰት ተግባር መሆኑንም ጠቅሷል።የህወሓት ሀይሎች ሳምሪ ከተባለ የትግራይ ወጣቶች ቡድን ጋር በማበር ዝግጅት በማድረግ እና በማቀድ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን መግደላቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ሪፖርት አረጋግጧልም ብሏል መንግስት።እንደ ኮሚሽኑ ሪፖርት የህወሓት ህገ ወጥ ቡድን የፈፀመው ተግባር በሰብአዊነት ላይ የተፈጸመ ወንጀል እና የጦር ወንጀል ሊሆን እንደሚችል አመላክቷል ብሏል።ዓለም አቀፉ ማህበረሰብም ይህንን ጭካኔ የተሞላበትን ከፍተኛ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት እንዲያወግዝም መንግስት ጥሪ አቅርቧል።
የዚህን ወንጀል ፈፃሚዎችም ለህግ የሚያቀርብ መሆኑንም መንግስት በመግለጫው አረጋግጧል።
| 0 |
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.