query_id
stringlengths
32
32
passage_id
stringlengths
32
32
query
stringlengths
2
182
passage
stringlengths
137
1.88k
label
int64
0
1
eccc709e719b6bec1f421c6101ffa643
57741413ece8327129c7173880b06b3e
ኮቪድ-19 በዩናይትድ ስቴትስ
ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ በኮቪድ-19 ምክንያት እየደረሰ ያለው ዕለታዊ የሞት ጉዳት ሰኔ 24 አካባቢ ከአሁኑ በእጥፍ ሊያሻቅብ እንደሚችል የመንግሥቱ የበሽታዎች መቆጣጠሪያ ተቋም ያወጣውን የጥናታዊ ትንበያ ሰነድ ዋይት ሃውስ አጣጥሎታል። ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ እስካሁን ለአዲሱ ክኮሮናቫይረስ እየታገለጠ ያለው 25 ሺህ የሚደርስ ቁጥር ያለው ሰው እንደሆነ ይነገራል። የበሽታዎች መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከላት /ሲዲሲ እንደሚለው ደግሞ የያዝነው የአውሮፓ ወር May መጨረሻ አካባቢ ዕለታዊ የመጋለጥ መጠን ወደ 2መቶ ሺህ እንደሚያሻቅብ ተንብያል። ይህንን የራሱን የመንግሥቱን ትንበያ ግን የዋይት ኃውስ ቤተ መንግሥት ቃል አቀባይ ጄዱ ዲሪ እንደማይቀበሉት ተግረዋል። የዋይት ኃውስ መግለጫ ቁጥሩ እንደሚጨምር ባያስተባብልም ሊሆን የሚችለው አሁን ካለበት 1ሺህ 7መቶ በወሩ መጨራሻ ሦስት ሺህ ቢደርስ እንደሆነ ያመለክታል።
0
122bb9ce16b49a541fb0c3bbb6bb376a
9a7167cd3de5e9d8661409afe9410e90
ዓለምቀፍ የኒውክሊየር መሳሪያዎች አስወጋጅ ዘመቻ የኖቤል የሰላም ሽልማት
አቶ አባተ ካሳ ከዚህ ዋሽንግተን ዲሲ .. “የፋይዳ ትንታኔ” የተሰኘው በሥራ አመራር ላይ ያተኮረ መጽሃፍ ደራሲ እና በቅርቡም “ኢትዮክራሲ” በሚል ርዕስ አዲስ የመንግሥት አስተዳደር ሥርዓት የሚያስተዋውቅ ጽሁፍ ለንባብ ያበቁ ባለሞያ ናቸው።አቶ ክቡር ገና የኢንሽዬቲቭ አፍሪካ ድሬክተር እና የፓን አፍሪካ ንግድ ምክር ቤት ሥራ አስፈፃሚ ድሬክተር ናቸው።
0
f4611fe0c4725c965bd77edf7ab7bd60
f4611fe0c4725c965bd77edf7ab7bd60
‹‹የዓባይ ተፋሰስ አገሮች በዓባይ ውኃ ላይ ከመተባበር ውጪ አማራጭ የላቸውም››
የዓባይ ተፋሰስ አገሮች የዓባይ ውኃን በተመለከተ ከመተባበር ውጪ አማራጭ እንደሌላቸው በመግለጽ፣ አሥሩም የተፋሰሱ አገሮች ለዚህ እንዲሠሩ የሱዳን ውኃና ኤሌክትሪክ ምክትል ሚኒስትር ጥሪ አቀረቡ፡፡ሚኒስትሯ ዶ/ር ታቢታ በትረስ በካርቱም ባለፈው እሑድ የዓባይ እንዲሁም የናይል ቤዚን ኢኒሼቲቭ የተቋቁመበትን 14ኛ ዓመት በተከበረበት ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ የውኃ አስፈላጊነት ከኢኮኖሚያዊ ጥቅም ባሻገር በተፋሰሱ አገሮች ውስጥ የሚኖሩ ሕዝቦች የመኖር ጥያቄ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡በዚህ ተፋሰስ ውስጥ የሚኖሩ ሕዝቦችና ኢኮኖሚያቸው ከግብርና ጋር በተለይም በዓባይ ወንዝ ላይ ከተመሠረተ ግብርና ጋር የተቆራኘ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ከግብርና መሬት ባለፈ ውኃ በተፋሰሱ አገሮች ለሚኖሩ 340 ሚሊዮን ሕዝቦች ወሳኝ መሆኑን፣ ከተጠቀሰው ሕዝብ ቁጥር ግማሽ ያህሉ የዓባይን ተፋሰስ ተንተርሶ ኑሮውን የመሠረተ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ከግብርና በተጨማሪ የተፋሰሱ ሕዝቦች በአሁኑ ወቅት የኃይል አቅርቦት ፍላጐታቸው በመጨመሩ፣ የዓባይ ወንዝም ለዚህ ዋነኛ መፍትሔ መሆን እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡ ‹‹በመሆኑም ዘላቂ በሆነ መንገድ ውኃውን ለመጠቀም የተፋሰሱ አገሮች ከመተባበር ውጪ ሌላ አማራጭ የላቸውም፤›› ብለዋል፡፡በናይል ቤዚን ኢኒሼቲቭ የ14ኛ ምሥረታ በዓልና የዓባይ ቀን ላይ አሥሩም የተፋሰሱ አገሮች የውኃ ሚኒስትሮች የተገኙ ሲሆን፣ ላለፉት አምስት ዓመታት ራሷን ከኢኒሼቲቩ አግልላ የነበረችው ግብፅ በውኃ ሚኒስትሯ አማካይነት በዓሉን ታድማለች፡፡ይህ በእንዲህ እንዳለ በሚቀጥለው ሳምንት በካርቱም የኢትዮጵያ የግብፅና የሱዳን ቴክኒክ ኮሚቴ እንደሚገናኝ ባለፈው እሑድ ዕትማችን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ በዚህ ስብሰባ የኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብን በተመለከተ ዓለም አቀፍ የባለሙያዎች ቡድን ያቀረበውን ምክረ ሐሳብ እንዲተገበሩ ከተመረጡ ድርጅቶች መካከል ፕሮፖዛላቸውን መምረጥ ዋነኛ አጀንዳው ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ከተመረጡት ሰባት የአምስት የአውሮፓና የአውስትራሊያ ኩባንያዎች መካከል፣ አራት ኩባንያዎች ሰነዶቻቸውን ለኮሚቴው ማስገባታቸው ታውቋል፡፡ ከእነዚህ ኩባንያዎች መካከል አንድ ወይም ሁለት ኩባንያዎችን የመምረጥ ኃላፊነት በቴክኒክ ከሚቴው ላይ ተጥሎበታል፡፡
1
17c00ec2d8c6512528d7d06b91980b6d
4de39f7ebed8986054e67fedd69e4a23
የዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም አመራር ወቅቱንና ኃላፊነታቸውን የሚመጥን ነው – ጠ/ሚ ዐቢይ
ማህበራቱ በኢትዮጵያ ህክምና ማኅበር ፕሬዚዳንት ዶክተር ገመቺስ ማሞ በኩል ባስተላለፉት መልዕክት ዶክተር ቴድሮስ ቢመረጡ ለዓለም ጤና የተሻለ እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።ዶክተር ቴድሮስ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት አገሪቷን የሚሌኒየሙን የልማት ግብ በጊዜው ማሳካት ከቻሉ ጥቂት አገራት አንዷ እንድትሆን አስችለዋታል ነው ያሉት።በወቅቱ የህፃናት ሞትን በሁለት ሦስተኛ፣ በወባ የሚከሰት ሞትን በ75 በመቶ፣ በኤች.አይ.ቪ የሚሞቱትን በ70 በመቶ፣ በሳንባ ነቀርሳ የሚሞቱትንም በ64 በመቶ መቀነስ እንዳስቻሉም ነው የተናገሩት።በአገሪቷ 3 ሺህ 500 የጤና ማዕከላትና 16 ሺህ የጤና ኬላዎችን በማቋቋም የጤና አገልግሎትን ተደራሽ ማድረግ መቻላቸውንና የጤና ባለሙያ ማሰልጠኛ ማዕከላትን ከሦስት ወደ 33 እንዳሳደጉ አስታውሰዋል።16 ሺህ 500 የነበሩትን የጤና ባለሙያዎች በሰባት እጥፍ ማሳደግ መቻላቸው የጤናውን ዘርፍ የመምራት አቅማቸውን የሚያሳይ በመሆኑ በዋና ዳይሬክተርነት ቢመረጡ ይህንን ልምዳቸውን እንደሚጠቀሙ እምነታቸውን ገልጸዋል።ዶክተር ቴድሮስ በተለይ በሚታወቁበት የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም 38 ሺህ ባለሙያዎችን አሰልጥነው ወደ ስራ በማስገባት የጤና አጠባበቅ ስርዓቱ ማህበረሰባዊ መሰረት እንዲኖረው ማድረጋቸውንና ለጤና መድህን ሽፋን መጀመር መሰረት መጣላቸውን አውስተዋል።ግሎባል ፈንድን ጨምሮ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትን የመሩት ዶክተር ቴድሮስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅትም በአፍሪካ ኅብረት በኩል ኢቦላን ለመቋቋም በተደረገው ርብርብ ኢትዮጵያ የበኩሏን ጉልህ አስተዋፅኦ እንድታበረክት አድርገዋል።
0
b15fefb8d06acd8514d5303e970eca4d
9f4da65b13a7832adc260935ac6899d7
አንድ የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አባል ከኤርትራ ጋር ግንኙነት ለማደስ ሀሳብ አቀረቡ
በትናንትናው ዕለት በሺዎች የሚቆጠሩ የተሰናባቹ ትረምፕ ደጋፊዎች ከሕግ አሰከባሪዎች ጋር ግብግብ ገጥመው የተወካዮቹን ምክር ቤት ቢወሩም ከሰዓታት በኋላ ተመልሰው ገብተው ስብሰባውን ያስቀጠሉት የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አባላት ባለፈው ኅዳር የተካሄደው የአሜሪካው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ አሸናፊ ዴሞክራቱ ጆ ባይደን መሆናቸውን ማረጋገጫ ሰጥተዋል፡፡የተሰናባቹ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ ደጋፊዎች፣ የዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ምክር ቤትን በመውረር፣ ሕግ አውጭዎቹ የምክር ቤት አባላት ስብሰባቸውን በማቋረጥ፣ ህንጻው ለቀው እንዲወጡ ካስገደዷቸው በኋላ የምክር ቤቶቹ አባላት ሁኔታዎች ተመልሰው በቁጥጥር ሥር እስኪውሉ ጠብቀው ወደ ምክር ቤቱ በመግባት ሕገ መንግሥታዊ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ባደረጉት የድጋሚ ስብሰባ ማረጋገጫውን ሰጥተዋል።በረብሻው ወቅት ከአዳራሹ እንዲወጡ ቢደረገም እዚያው ምክር ቤቱ ውስጥ መቆየታቸው የተነገረው ተሰናባቹ ምክትል ፕሬዚዳንት ማይክ ፔንስ በአመፁ ምክኒያት ተቋርጦ የነበረውን ስብሰባ በድጋሚ ሲያስጀመሩ፤ “ዛሬ በዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት ታሪክ የጨለማው ቀን ነበር፡፡ ይሁን እንጂ የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት ፖሊሶች፣ የፌደራል፣ የክፍለ ግዛቶችና የአካባቢው ህግ አስከባሪዎች ምስጋና ይግባቸውና እነሱ ባደረጉት ፈጣን ጥረት አመጹ በቁጥጥር ሥር ውሏል፡፡” ሲሉ ተደምጠዋል።በመጨረሻም የየክፍለ ግዛቶቹ ተወካዮች ለባይደን 306 እንዲሁም ለትራምፕ 232 ድምጽ የሰጡ መሆናቸው መረጋገጡን ይፋ አድርገዋል፡፡
0
a94ba54170ecf20e537184fb01cb9e65
c87a701f64ec7ed210b8320a10bd2a9f
ቱርክ በየዩናይትድ ስቴትስ ሸቀጣ ሸቀጥ የቀረጥ ክፍያ ከፍ ልታደርግ ነው
ቻይና የ50 ቢልዮን ዶላር ቀረጥ በዩናይትድ ስቴትስ ዕቃዎች ላይ የመደንገግ ዕቅድ እንዳላት ዛሬ አስታወቀች። ዩናይትድ ስቴትስ ለደነገገችው ተመሳሳይ ቀረጥ ምላሽ መሆኑ ነው።ቻይና የወሰደችው እርምጃ በ106 የአሜሪካ ምርቶች ላይ በ25 ከመቶ ከፍ የሚል ቀረጥ ይደነገጋል። የአይሮፕላን፣ የመኪኖችና የቦለቄ ምርቶችን ያካትታል።የቻይና የንግድ ሚኒስቴር እርምጃ እንደሚወስድ ያስታወቀው ዩናይትድ ስቴትስ ቀረጥ ከፍ የምተዳርግባቸውን የቻይና እቃዎች ዝርዝር ከጠቀሰች ከ11 ሰዓታት ያነሰ ጊዜ ካለፈ በኋላ ነው። መቼ በተግባር ላይ ይውላል? የሚለው ጥያቄ የሚወሰነው የአሜሪካ ቀረጦች መተግበር ላይ መሆኑን የንግድ ሚኒስቴሩ ጠቁሟል።የዩናይትድ ስቴስ ፕሬዚዳንት ትረምፕ በቻይና ምርቶች ላይ የ50 ቢልዮን ዶላር ቀረጥ እንደሚደነገጉ ባለፈው ወር አስታውቀዋል። ትላንት ደግሞ በ1,300 ዕቃዎች ላይ ቀረጥ እንዲጣል የአሜሪካ የንግድ ተወካዮች ሃሳብ አቅርበዋል።
0
28d912f13211e641cf909ce3f7f8d57e
5a054839bd0c17bb04cad387e935ce37
የዓለም ህፃናት ቀን በሃዋሳ ከተማ ተከበረ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) 8ኛው የኢፌድሪ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ቀን በምእራብ ዕዝ ተከበረ።ቀኑ የተከበረው የምዕራብ ዕዝ መከላከያ ሰራዊት በደቡብ ጎንደር ዞን ጉና በጌምድር ወረዳ ያስገነባው የበጌምድር 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን ጨርሶ በማስመረቅና ለማህበረሰቡ በማስረከብ ስነ ስርዓት ነው።የመከላከያ ሠራዊት በዓል “የሀገራችን ልዓላዊነትና የህዝብችንን ሠላም በፅናት እንጠብቃለን” በሚል መሪ ቃል የምዕራብ ዕዝ ቀኑን ያከበረው።የምዕራብ ዕዝ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከወር ደሞዛቸው በማዋጣት ባሰባሰቡት ገንዘብም ትምህርት ቤቱ መገንባቱን ዛሬ በርክክቡ ላይ ተገልጿል።በ22 ሚሊየን ብር ወጪ በ10 ወራት ውስጥ ተገንብቶ የተጠናቀቀው ትምህርት ቤቱ ስምንት ህንፃዎች ያሉት ሲሆን፥ 40 የመማሪያ ክፍሎችን ይዘዋል። በናትናኤል ጥጋቡ
0
02882ba9efbc0c7aa8ee38a43f3c3367
fa72cac38e175974b0320d3476406045
በአዲስ አበባ ዙሪያ በግዳጅ ላይ ያሉ ልዩ የጥበቃ መከላከያ ሰራዊት አባላት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 152005 ( ዋኢማ) – የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም በግብፅ ጊዜያዊ መንግስት አዲስ ከተሾሙት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ናቢል ፋህሚ ጋር በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ተወያዩ።የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ በስልክ ባደረጉት ውይይት በግድቡ ዙሪያ ከኢትዮጵያ ፣ ሱዳንና ግብፅ ባለሙያዎች የተካተቱበት አለም ዓቀፍ የባለሙያዎች ቡድን የጥናት ውጤት አስተያየት ላይ መነጋገራቸው ታውቋል።በሌላ በኩል የቀድሞ የግብፅ የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስተር ሞና ኡመር ከጠቅላይ ሚኒስትር ሐይለማርያም ደሳለኝ ጋር ለመምከር ዛሬ አዲስ አበባ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
0
beee7e7893145ec105cd6cb0ad309985
fb85a43017c4f1e687a0f31b1edb792d
ኢትዮጵያ ሁለተኛዋን ሳተላይት አመጠቀች
የናይጄሪያው ጽንፈኛ ቡድን ቦኮ ሃራም ከሁለት ዓመታት ገደማ በፊት ከጠለፋቸው “የቺቦክ ልጃገረዶች“ መካከል ሁለተኛዋን አስለቀቅን ብሎ የጦር ሃይሉ የተናገረውን ልጃገረዶቹ እንዲለቀቁ የሚሟገቱ ወገኖች ሃሰት ብለውታል።የናይጄሪያ የጦር ሰራዊት ባወጣው መግለጫ በቦርኖ ክፍለ ሃገር ዳምቦአ አካባቢ ሐሙስ ያስለቀቃት ሳራ ሉካ የምትባል ልጅ ከቺቦክ የመንግስት ትምህርት ቤት ከተጠለፉት 219 ልጃገረዶች አንዷ ናት ብሎ ነበር።የተጠለፉት የቺቦክ ልጃገረዶች ወላጆች ማህበር ሊቀመንበር ያኩቡ ንኬኪ ለአሜሪካ ድምጽ ሲናገሩ "ርግጥ ነው ሉካ የሚባሉ ሁለት ልጆች ከቺቦክ ተጠልፈዋል፣ ሴራ ሉካ የምትባለው ግን አይደለችም" ብለዋል።የሁለት መቶዎቹም ልጆች ዝርዝር መዝገብ በዕጄ አለ። ይቺ ልጅ የቺቦኳ አይደለችም ብለዋል።የናይጄሪያ የጦር ሰራዊት በቦኮ ሃራም ቪዲዮዎች ሲታዩ የነበሩት ተጠላፊዎች እንደለበሱት ያለ ሰማያዊ ሂጃብ የለበሰች ልጅ ፎቶግራፍ ያወጣ ሲሆን ቢዩ ከተማ ህክምና እየተደረገላት መሆኑን ተናግሯል።የመጀመሪያዋ የተለቀቀች የቺቦክ ልጃገረድ የአስራ ዘጠኝ ዓመቷ አሚና አሊ ማክሰኞ ዕለት ከአራት ወር ህጻን ልጇ ጋር በሲቪል የአካባቢው ጥበቃ ሰዎች ሳምቢሳ ደን ውስጥ ተገኝታለች።የናይጄሪያ ፕሬዚደንት ማሀማዱ ቡሃሪ አሚናና እናቷን ተቀብለው ያነጋገሩ ሲሆን የተቀሩትን የቺቦክ ልጃገረዶች ለማስለቀቅ የተቻለንን ሁሉ እናደርጋለን ማለታቸው ተጠቅሷል።
0
fcc95492f96bc2e039c9c276a2af6f48
44a22288b36a58a2028a2468079a4c22
የጉራጌ ዞን እና የስልጤ ዞን ተወላጆች የዘንድሮውን የዒድ አል-አድሃ ዓረፋ በዓል ባሉበት እንዲያከብሩ ጥሪ ቀረበ
በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 27ኛ ሳምንት ትላንት ያልተካሄደውና ነገ አዳማ ላይ በዝግ ይካሄዳል የተባለው የቡና እና መቐለ ጨዋታ ወደ ሐሙስ መሸጋገሩን ፌዴሬሽኑ አስታውቋል።በፌዴሬሽኑ መግለጫ መሠረት ጨዋታው የቀን ለውጥ ሲደረግበት በአዳማ አበበ ቢቂላ በዝግ እንዲደረግ የተወሰነው ውሳኔ ግን ፀንቷል።በ27ኛ ሳምንት በአዲስ አበባ ስታዲየም ግንቦት 25/2011ዓ.ም ሊካሄድ የነበረው የኢትዮጵያ ቡና እና የመቐለ 70 እንድርታ ጨዋታ በጸጥታ ስጋት ምክንያት ጨዋታው መሰረዙ ይታወቃል፤ የሊግ ኮሚቴ ጨዋታው በጸጥታ ስጋት ምክንያት አለመካሄዱን ተከትሎ ግንቦት 27/2011ዓ.ም በአዳማ አበበ ቢቂላ ስታዲየም ያለ ተመልካች /በዝግ እንዲካሄድ መወሰኑ ይታወቃል፤ ይህንንም ተከትሎ የኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ ውሳኔውን በመቃወም ደብዳቤ ያስገባ ሲሆን ጉዳዩን የተመለከተው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ቀደም ሲል የተሰረዘው ጨዋታ ከመንግስት ጸጥታ ኃይል በደረሰ መረጃ የደህንነት ስጋት በስታዲየም እንዳለ በማሳወቁ በመሆኑ እና አሁንም በድጋሚ በተደረገው ውይይት ይህ ጉዳይ በጥብቅ ሊታይ የሚገባው በመሆኑ እና የመንግስት የጸጥታ ኃይልም የሁለቱ ክለብ ደጋፊዎች ባሉበት ጨዋታው መካሄድ የሌለበት መሆኑን በጥብቅ አስገንዝቦናል። የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታን ግንቦት 27/2011ዓ.ም ለማካሄድ የዒድ አል ፈጥር በዓል ስለሆነ የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ሐሙስ ግንቦት 29/2011 ዓ.ም በአዳማ አበበ ቢቂላ ስታዲየም በ9 ሰዓት ያለ ተመልካች በዝግ ይካሄዳል።
0
5a5208ec1dc37703a4122d08a2b948fe
5a05f2bfeea235449f0401ad0dafb982
ኢትዮጵያ የአልሸባብን የሽብር ጥቃት ለማስቆም ጥረቷን እንደምትቀል ገለፀች
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሶማሊያ ጦር በወሰደው እርምጃ 14 የአልሸባብ ታጣቂዎች መገደላቸው ተሰምቷል።የጦር ሀይሉ እርምጃውን የወሰደው ከዋና ከተማዋ ሞቃዲሾ በስተሰሜን 30 ኪሎ ሜትር ርቃ በምትገኘው ባላድ ከተማ የሽብር ቡድኑ ዛሬ ጠዋት ጥቃት መፈጸሙን ተከትሎ ነው ተብሏል።የመንግስት ቃል አቀባይ እስማኤል ሙክታር ኡመር ÷ የሽብር ቡድኑ በፈጸመው ጥቃት አንድ የመንግስት ወታደር መሞቱን እና ሰባት ዜጎችም መቁሰላቸውን ነው የተናገሩት።የአልሸባብ የሽብር ቡድንን ጥቃት ተከትሎ በባልድ ከተማ የነበረው ሁኔታ መረጋጋቱንም ቃል አቀባዩ ጨምረው ገልጸዋል።የአልሸባብ ታጣቂዎች በባልድ ከተማ ባደረሱት ድንገተኛ ጥቃት የአካባቢውን የመንግስት ዋና መስሪያ ቤት እና የፖሊስ ጣቢያዎችን ተቆጣጥረው እንደነበረም የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል።የሀገሪቱ ጦር አልሸባብን ከሥረ መሰረቱ ለመንቀል በቅርብ ወራት በማዕከላዊ እና በደቡባዊ የሀገሪቱ ክልሎች ተከታታይ ዘመቻ ቢያደርግም ታጣቂ ቡድኑ የሚያደርሰውን ጥቃት አጠናክሮ መቀጠሉ ይነገራል።ምንጭ፦ ሲ.ጂ.ቲ.ኤን የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
0
fb2680ab7b6b74bd7891e8b1df8a9ad2
f28812caaf8eb67c72883c8f1360260c
የኮቪድ-19 በሽታ ስርጭትን ለመከላከል የሚያግዝ ደቦ የተሰኘ የሰዎች ንክኪ መለያ የአንድሮይድ ስልክ መተግበሪያ ይፋ ማድረጉን የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ
አዲስ አበባ ፣ ህዳር 29 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ለኢትዮጵያውያን ስደተኞች ሁለገብ መረጃ የሚያቀርብ “የጉዞ ስንቅ” የተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ በዛሬው ዕለት ይፋ ሆኗል፡፡በዓለም አቀፉ የስራ ድርጅት ተዘጋጅቶ ይፋ የተደረገው መተግበሪያ ለስደተኞች የተሟላ መረጃ መስጠት የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡ስደተኞች መረጃ ባለማግኘታቸው ምክንያት ለእንግልት እንደሚዳረገው ድርጅቱ በዚህ ወቅት ገልጿል፡፡አዲሱ የሞባይል መተግበሪያ ግን ከስደት ሕይወት ጋር በተገናኘ የሥራ ዕድል አማራጮችን፣ የየሃገራት ህግጋትንና የሚደርሱ ችግሮችን በዘርፉ ከሚሰሩ ተቋማት እና ኤምባሲዎች ጋር በማስተሳሰር መረጃዎችን በማቅረብ ለስደተኞች እገዛ ያደርጋል ነው የተባለው፡፡መተግበሪያው በእንግሊዝኛ፣ አማርኛ፣ በአፋን ኦሮሞ እና በትግርኛ ቋንቋዎች አገልግሎት እዲሰጥ ተደርጎ ነው የተዘጋጀው፡፡የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዲዔታ ወይዘሮ አየለች እሸቴ የሞባይል መተግበሪያው ተደራሽ እንዲሆን ይሰራል ማለታቸውን ኢቢሲ ዘግቧል፡፡ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
0
bd64591a5cb9396dc4cf254aae263882
588d60495bfa9daf7c42c812956232cf
የአፕል አይፎን እና የሳምሰንግ ጋላክሲ
ወጣት የምርምር እና የሥነ ጽሁፍ ሰው ነው። በጀርመኑ የድሬስደን የቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የኮምፒውተር ምሕንድስና ተባባሪ ፕሮፌሰር ተማራማሪ እና የኢንርጂ ቤተሙከራ ኃላፊም ነው።በሳይንስ እና ምርምር፣ በፍልስፍና እና እንዲሁም በጽነ ጽሁፉ ዓለም ገናና ዕውቅና ያላቸውን የአራት ቀደምት ጠቢባን፡- ዕውቁን የፊዚክስ ሊቅ የአልበርት አንስታይንን፤ ሕቡዉን የአንጎል ክፍል በሚያጠናው የሥነ ልቦና ምርምር ዘርፍ መሥራችትነት የሚታወቀውን የሲግመንድ ፍሮይድን፣ የገናናውን ደራሲ ጋዜጠኛ እና ፈላስፋ የቴዎዶር ዶስቶየቭስኪን እና እንዲሁም የሌላውን እውቅ ብዕረኛ የሊዮ ቶልስቶይን የሕይወት ፍልስፍናዎች የሚመረምረውን The Reason For Life የተሰኘ መጽሃፉን ጨምሮ .. ምርምር እና ጥናት በሚያደግበት የሞያ መስክና እንዲሁም በልቦለዱ ዓለም በርከት ያሉ መጻሕፍት ጽፏል።ዋልተንጉስ ዳርጌ ይባላል።በተከታዩ ምጥን ወጋችን ከዶ/ር ዋልተንጉስ ዳርጌ እና ሥራዎቹ ጋር እናስተዋውቃችሁ።
0
ab0d0db2e05ad54136971136619a786e
ab8f95ca1439330f12af6fd07616043d
ዳያስፖራው ተሳትፎ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ማሻሻል የሚያስችል ፕሮጀክት ሊተገበር ነው፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ የአረጋዊያንና አቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ ስራ በዛሬው ዕለት በይፋ ተጀመረ፡፡የከተማዋ ምክትል ከንቲባ ኢንጀነር ታከለ ኡማ የክረምት የበጎ ፈቃድ ስራ አካል የሆነው የመንግስት ትምህርት ቤቶችን የማደስ ስራ በዛሬው ዕለት በይፋ አስጀምረዋል፡፡በክረምቱ የከተማ አስተዳደሩ ከ488 በላይ የመንግስት ትምህርት ቤቶችን ለማደስ በያዘው ዕቅድ መሠረት ነው ኢንጅነር ታከለ ኡማ የመነን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዕድሳትን በዛሬው ዕለት በይፋ ያስጀመሩት፡፡የመነን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዕድሳት ወጪ ሙሉ በሙሉ በከተማ አስተዳደሩ እንደሚሸፈን እና እድሳቱም በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ምክትል ከንቲባው ተናግረዋል፡፡የመነን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በከተማ አስተዳደሩ የአዳሪ ትምህርት ቤት እንዲሆን በተወሰነው መሠረት ከሚቀጥለው የትምህርት ዘመን ጀምሮ በትምህርታቸው ላቅ ያለ ውጤት ያመጡ 500 ሴት ተማሪዎችን ተቀብሎ የሚያስተምር ይሆናል፡፡ሁለቱ የአዳሪ ትምህርት ቤቶች፣ የመነን እና ኢትዮ-ጃፓን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለተማሪዎች ምቹ የሆኑ የመማሪያ ክፍሎች፣ ደረጃቸውን የጠበቁ ቤተ-መፅሐፍት እና ቤተ-ሙከራዎችን እንዲሁም የተመቻቹ የማደሪያ ክፍሎች የሚኖራቸው ይሆናልም ነው የተባለው፡፡በዕድሳት መርሃ-ግብሩ ላይ የትምህርት ቤቱ የወላጅ ኮሚቴ፣ መምህራን እና የአከባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል፡፡በሌላ በኩል ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ቃኘው ሻለቃ አደባባይ አከባቢ በመገኘት የአረጋዊያን እና አቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ ስራ አስጀምረዋል፡፡በዛሬው ዕለትም በአከባቢው ለረዥም ጊዜያት የአልጋ ቁራኛ የነበሩ አቅመ ደካማ እናት መኖሪያ ቤት ዕድሳት አስጀምረዋል፡፡ዕድሳቱን በ10 ቀናት ውስጥ በማጠናቀቅ ለባለንብረቷ እንደሚያስረክቡም ኢንጅነር ታከለ ኡማ ተናግረዋል፡፡የከተማ አስተዳደሩ በክረምት የበጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር 1 ሺህ ለሚሆኑ አረጋዊያን ቤት የማደስ ስራ እንደሚሰራ አስታውቀዋል፡፡ መረጃው የአዲስ አበባ ከንቲባ ጽህፈት ቤት ነው፡፡
0
0e546e00b2b21ed7e72cbd61800eb5ff
ed81dfa149e200dd1b1b82abaa63d7d1
የኦሮሚያ ክልል አሲዳማ መሬትን በኖራ በማከም ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ ፓርቲዎች ያቀረቡለትን አቤቱታዎች መነሻ በማድረግ፣ ክልሎችና የፖሊስ ኮሚሽኖች ምላሽ እንዲሰጡ በደብዳቤ መጠየቁን አስታወቀ፡፡ ክልሎቹና የፖሊስ ኮሚሽኖች ትግራይ፣ አማራ፣ ደቡብና ኦሮሚያ ናቸው፡፡በትግራይ ክልል ላይ አቤቱታ ያቀረበው የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ትዴፓ) መሆኑን የገለጸው ቦርዱ አቤቱታውም እስር፣ ማስፈራራትና የቢሮ መዘጋት ነው ብሏል፡፡ በአማራ ክልል ላይ አቤቱታ ያቀረበው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ፓርቲ (ኢዜማ) ደግሞ የስብሰባዎች መሰናከል በጎንደርና በደብረ ብርሃን እንዳጋጠመው፣ የፀጥታ ኃይሎችም ለስብሰባዎች መሰናከል ትብብር ማድረጋቸውን ማመልከቱን ቦርዱ አስታውቋል፡፡ በኦሮሚያ ክልል ላይ አቤቱታ ያቀረቡት የኦሮሚያ ብሔራዊ ፓርቲ (ኦብፓ)፣ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) እና የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) የአባላት እስራት፣ የቢሮ መዘጋት፣ የታፔላ መነቀል፣ ማስፈራራትና የመሥራቾች ፊርማ መነጠቅ በተለያዩ የኦሮሚያ ክፍሎች እንደ ደረሱባቸው መግለጻቸውን ቦርዱ አስረድቷል፡፡ በደቡብ ክልል ላይ አቤቱታ ያቀረበው የጌዴኦ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ጌሕዴድ) መሆኑን፣ የተፈጸመበት ድርጊትም ሰነድ መነጠቅና የማሟያ ፊርማ ማሰባሰብ ሒደት መደናቀፍ እንደሆነ ከምርጫ ቦርድ ለመረዳት ተችሏል፡፡ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ያቀረቡትን አቤቱታ በማያያዝ፣ የሚመለከታቸውን የመንግሥት አካላት ጉዳዩን ከሚያስረዱ ሰነዶች ጋር የካቲት 26 እና 27 ቀን 2012 ዓ.ም. በቦርዱ ጽሕፈት ቀርበው እንዲያስረዱ ደብዳቤ መላኩን አስታውቋል። ለአቤቱታዎቹ ምላሽ እንዲሰጡ ጥሪ የደረሳቸው ተቋማትም የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት መስተዳድር፣ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት መስተዳድር፣ የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን፣ የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን፣ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን ዝዋይ ባቱ ከተማ ፖሊስ መሆናቸውን ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ገልጿል፡፡ምርጫ ቦርድ የክልሎቹንና የፖሊስ ኮሚሽኖቹን ምላሽና የራሱን ውሳኔ በመገናኛ ብዙኃን አማካይነት ይፋ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
0
aaf955d345e075e1a936b52e20a4b744
3b45056c9a96b908f5bd6e8b65c81f7e
አቶ ሽመልስ አብዲሳ ከጅቡቲ የንግድ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ
በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከተከለከሉ ድርጊቶች የማይቆጠቡት ላይ አስተማሪ እርምጃ እንወስዳለን ሲሉ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ ገልፀዋል፡፡ፕሬዚዳንት ሽመልስ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የተቋቋመው ግብረ ሀይል ስራው ያለበትን ደረጃ በገመገመበት ወቅት ባደረጉት ንግግር “የኮሮናቫይረስ /ኮቪድ-19/ ስርጭቱ እየሰፋ መምጣቱ ልዩ ትኩረት የሚሻው ጉዳይ ነው” ብለዋል፡፡ኮቪድ-19 በዓለም ላይ እያሳደረ ያለውን ጉዳት እያዩ ያለንበትን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በመተላለፍ የቫይረሱ ስርጭት እንዲባባስ በሚያደርጉ ሰዎች ላይ አስተማሪ የሆነ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡በሌላ በኩል የኮሮናቫይረስ ተጠርጣሪዎችን ከቤት በመደበቅ በሽታው እንዲስፋፋ እያደረጉ ያሉ ሰዎች ላይም አስፈላጊው እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ተናግረዋል፡፡የኮቪድ 19 ስርጭትን ለመከላከል ከገበያ ስፍራዎች ጋር በተያያዘ ያለው እንቅስቃሴ የተሻለ ቢሆንም ከበሽታው ክብደትና የስርጭት ባህሪይ ጋር ሲነፃፀር በቂ እንዳልሆነም ገልፀዋል፡፡የዋጋ ጭማሪ በማድረግ የኑሮ ውድነት እንዲፈጠር በሚያደርጉ ነጋዴዎች ላይም የተጀመረው እርምጃ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ኢንዱስትሪዎች ሥራ ማቆም እንደሌለባቸው የገለፁት ፕሬዚዳንት ሽመልስ፤ ሰራተኞች ከበሽታው ራሳቸውን የሚጠብቁበት ሁኔታን የማመቻቸት ስራ ቀጣይነት እንዲኖረው አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡ወቅቱ ግንቦት ወር ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በድርቅ ምክንያት የውሀ እጥረት እንዳያጋጥም ሁሉም አካላት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸውም መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡“እንደ ክልላችን የኢኮኖሚ ውድቀት እንዳያጋጥም በየትኛውም መስክ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴው መቆም የለበትም” ብለዋል።የኮቪድ 19 አደገኛነትና የስርጭቱን ፍጥነት በመገንዘብ የእምነት አባቶች፣ ህዝብና በረመዳን የጾምና ሶላት ወር ውስጥ የሚገኙ የእምነት ተቋማት አጥብቀው እንዲፀልዩ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የግብረ ሀይሉ ሰብሳቢ አቶ አዲሱ አረጋ በዚህ ወቅት ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ ቤት ለቤት በተሰራው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ 33.5 ሚሊዮን ሰዎች ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል፡፡ስድስት መቶ የገበያ ስፍራዎች የተዘጋጁ መሆኑንም ገልፀው፣22 ሆስፒታሎችም ኮሮና ቫይረስ ላይ ትኩረት ሰጥተው እየሰሩ ሙሆኑንም የክልሉን ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዋቢ አድርጎ ኢዜአ ዘግቦታል፡፡
0
728feab46b0d432cca85265cc922e49e
728feab46b0d432cca85265cc922e49e
የጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ግድብ እየሞላ በመምጣቱ ውሃ ከግድቡ በየደረጃው እንደሚለቀቅ ተገለፀ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ግድብ እየሞላ በመምጣቱ ውሃ በየደረጃው ለመልቀቅ የሚያስችል የሙከራ ስራ ተከናውኗል፡፡ይህም ከግድቡ የሚለቀቀው ዉሃ ወደፊት በታችኛው ተፋስስ ላይ ጎርፍ እንዳያስከትል ለመቆጣጠር እና ውሃውን በተመጠነ መልኩ በመልቀቅ በክረምቱ መጨረሻ ላይ ግድቡ ሙሉ እንዲሆን ለማድረግ መሆኑን የጣቢያው ስራ አስኪያጅ አቶ ሃብታሙ ሰሙ ገልፀዋል፡፡ውሃ ከግድቡ በየደረጃው እንዲለቀቅ መደረጉ በተፋሰሱ ውስጥ የጎርፍ መቆጣጠር ስራ ለማከናወን እንደሚያግዝም ጠቁመዋል፡፡ግድብ የመጣውን ጎርፍ ሁሉ እንደመጣ ላለመልቀቅና የተመጠነ የውሃ ፍሰት እንዲኖር ለማድረግም በየጊዜው እየተቆጣጠሩ መልቀቅ ክረምቱ ሲጠነክር ሊከሰት የሚችለውን ጎርፍ ለመቆጣጠር እንደሚያግዝ አስረድተዋል፡፡አቶ ሃብታሙ ግድቡ መያዝ ከሚችለው 15 ቢሊየን ሜትር ኪዩብ ውሃ ውስጥ 12 ቢሊየን ሜትር ኪዩብ ውሃ የያዘ ሲሆን በሴኮንድ በአማካኝ 800 ሜትር ኪዩብ ውሃ ለመልቀቅ እቅድ ተይዟል፡፡ግድቡ ባለፈው ዓመት ህዳር ወር ከባህር ጠለል በላይ 882 ሜትር ላይ በመድረስ ከፍተኛ ውሃ መያዝ የቻለ ቢሆንም አሁን ላይ ግን ከዚህ መጠን ጋር ተመሳሳይ ውሃ መያዙን ተናግረዋል፡፡ይህም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከሦስት ወር አስቀድሞ ከባህር ጠለል በላይ 892 ሜትር ላይ በመድረስ ሊሞላ እንደሚችል ያመለክታል፡፡ውሃው ከአሁኑ ካልተለቀቀ ነሐሴ 4 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ ሙሉ በሙሉ ሊሞላ እንደሚችልም ስራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ግድቡ አሁን ሳይለቀቅ ቆይቶ ከሞላ በኋላ የሚለቀቅ ከሆነ ከላይኛው የጊቤ ተፋሰስ የሚመጣውን ጎርፍ ሁሉ ለመልቀቅ ስለሚያስገድድ በታችኛው ተፋሰስ ላይ የጎርፍ መጥለቅለቅ ሊያስከትል ይችላል ብለዋል፡፡ይሁንና የግድቡ ውሃ በየቀኑ እየጨመረ ስለሚሄድ ውሃ የመልቀቅ ሂደቱን ቀስ በቀስ መጥኖ በማከናወን ከግድቡ በታችኛው ተፋሰስ በሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ አደጋ እንዳያስከትል እንደሚደረግ አስታውቀዋል፡፡ግድቡ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ውሃ ሲለቅ የመጀመሪያው ሲሆን የውሃ መልቀቅ ሂደቱ እስከመቼ ሊቆይ እንደሚችል የታወቀ ነገር እንደሌለ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል አስታውቋል።
1
592fa761b271318d2bbf488eb4b5e003
592fa761b271318d2bbf488eb4b5e003
በመተከል ኦነግ ሸኔን በመርዳት ተጠርጥረው የታሰሩ እንዳሉ ተነገረ
ከኦሮሞ ነፃነት ሸማቂዎች ጋር ግንኙነት እንዳላቸው የተጠረጠሩ የቤተሰብ አባሎቻቸው ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ለወራትና ለሳምንታት መታሰራቸውን በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን የሚገኙ አንዳንድ ነዋሪዎች ተናግረዋል።የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኮሙዩኒኬሽንስ ኃላፊ አቶ መለሰ በየነ በበኩላቸው በአንዳንድ ወረዳዎች መንግሥት ኦነግ ሸኔ ብሎ የሚጠራቸው ታጣቂዎች እንቅስቃሴ መኖሩን ገልፀው ታሰሩ ስለተባሉ ሰዎች ግን መረጃ እንደሌላቸው አመልክተዋል።
1
d489ad35d312b507e6fb4a2f97763e2d
295ef0f4fde4144eca431b1eb2d87245
ትግራይ፡ የአየር ጥቃት በመቀለ ከተማ አቅራቢያ መፈጸሙ ተነገረ
ደቡባዊ ሶማሊያ ውስጥ በተካሄደ የአየር ጥቃት ሁለት የአልሻባብ ተዋጊዎች መገደላቸውንና አንድ ሰው መቁሰሉን የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ዕዝ አስታወቀ።ጥቃቱ የተካሄደው ጂሊብ የምትባል የመካከለኛው ጁባ ክፍለ ሃገር ከተማ ውስጥ መሆኑን ነው አፍሪኮም የተናገረው።ይህ የዩናይትድ ስቴትስ ኃይሎች ሶማሊያ ውስጥ በዚህ የአውሮፓውያን ዓመት ያካሄዱት አራተኛ የአየር ጥቃት መሆኑ ነው።
0
a7dbfccbb7d73a3f9b9ba4991f13a355
a7dbfccbb7d73a3f9b9ba4991f13a355
ብሔራዊ ባንክ በውክልና ሒሳብ ማንቀሳቀስ የሚከለክለውን መመርያ አሻሻለ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለብር ኖቶች ለውጥ ባወጣው መመርያ በውክልና ሒሳብ ማንቀሳቀስ የማይቻል መሆኑን የሚደነግገውን በማሻሻል፣ ከመስከረም 4 ቀን 2013 ዓ.ም. በፊት ሕጋዊ ውክልና ያላቸው ሰዎች ሒሳብ ማንቀሳቀስ (ገቢ ማድረግ) እንደሚችሉ አስታወቀ፡፡ ብሔራዊ ባንክ ሰኞ መስከረም 11 ቀን 2013 ዓ.ም. ባወጣው ማሻሻያ፣ ከዚህ ቀደም ከአምስት ሺሕ ብር በላይ በውክልና ማንቀሳቀስ አይቻልም የሚለውን ሽሮታል፡፡ በዚህ መሠረት ከመስከረም 4 ቀን 2013 ዓ.ም. በፊት በተገኘ ሕጋዊ ውክልና ሒሳብ ማንቀሳቀስ ይቻላል፡፡ ብሔራዊ ባንክ የብር ለውጡ ይፋ ከተደረገ በኋላ በየዕለቱ የሚያጋጥሙ ክስተቶችን በተመለከተ፣ ከሁሉም የባንክ ፕሬዚዳንቶች ጋር እየተመካከረ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ችግሮች ሲያጋጥሙም በጋራ መፍትሔ ለመፈለግ በትብብር እየተሠራ መሆኑን፣ ይህም መመርያ የተሻሻለው ከባንኮች በቀረበ ሐሳብ መሠረት እንደሆነ ታውቋል፡፡ብሔራዊ ባንክ በየሦስት ቀናት ከባንኮች ፕሬዚዳንቶች ጋር በሚያደርገው የጋራ ምክክር በገንዘብ ለውጥ ሒደቱ እንደ ችግር የታዩ ጉዳዮች ላይ ከመነጋገር በተጨማሪ፣ ባንኮች የፀጥታ ኃይሎችን ዕርዳታ ሲፈልጉ ብቻ የፀጥታ ኃይሎች እንዲሰማሩ ስምምነት ላይ የተደረሰበትም ጉዳይ ተጠቃሽ ነው፡፡ በዚህ መሠረት ከ1.5 ሚሊዮን ብር በታች ሕጋዊ ገንዘብ ሳይረጋገጥ ተይዞ መውረስ እንደማይቻል ውሳኔ ላይ መድረሱን መረዳት ተችሏል፡፡
1
c463eb28f5548562e61708ab2cc3388d
c463eb28f5548562e61708ab2cc3388d
አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በአልጀርስ ከዓለም አቀፍ ስደተኞች ድርጅት ሃላፊዎች ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ህዳር 22፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በአልጀርስ ከዓለም አቀፍ ስደተኞች ድርጅት ሃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል።አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በአልጀርስ የሚገኘው የዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት ኃላፊ ፓውሎ ካፑቶና የኘሮጀክት ኃላፊ ከሆኑት ፍላቪያ ጂኦርዳኒ ጋር ነው የተወያዩት።በበቆይታቸውም ኢትዮጵያውያን ከዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት ድጋፍ ማግኘት በሚችሉበትና በወቅታዊው የኢትዮጵያ መንግሥት ሕግ ማስከበር ዙሪያ የተወሰዱ እርምጃዎችን አስመልክቶ ውይይት ማድረጋቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በዚሁ ወቅት፥ ከመካከለኛው ምስራቅ ወደ አልጄሪያ በተለያየ ምክንያት በስደተኝነት የመጡ ኢትዮጵያውያን ክብራቸው ተጠብቆና ተገቢው ድጋፍ ተደርጐላቸው ወደ ሃገራቸው እንዲመለሱ በዓለም ዓቀፉ ስደተኞች ድርጅት አልጄሪያ ቢሮ ለተደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።የፌደራል መንግስት ሕግንና ሥርዓትን በማስከበር እንቅስቃሴው አጥፊው ቡድንና የሕወሃት ጁንታ የተቆጣጠረውን የትግራይ ክልል ዜጐች ለጉዳት ሳይጋለጡ በኃላፊነትና በጥንቃቄ በአጭር ጊዜ ነፃ ለማውጣት መቻሉንም አብራርተዋል።በአሁኑ ወቅትም በግጭቱም ምክንያት የተፈናቀሉ ዜጐችን ወደ ተረጋጋ ሕይወት እንዲመለሱ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ ፓውሎ ካፑቶ በበኩላቸው፥ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ የአዲስ አበባው ዓለምዓቀፍ በስደተኞች ጽህፈት ቤት በኃላፊነት መስራታቸውን አስታውሰዋል።ተቋማቸው በስደትና ስደት ተመላሾች ጉዳይ ዙሪያ ምንግዜም ቢሆን ዜጐች ክብራቸው ተጠብቆ ወደ ሀገራቸው የሚመለሱበትን ሁኔታ ማመቻቸት እንዲሁም ህገ-ወጥ የሠዎች ዝውውርን ለማስቀረትም የተለያዩ ሥራዎችን እንደሚሠራም ገልፀዋል።ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል www.youtube.com/fanatelevision ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
1
1d1346639c2014701310416ad92cbe2e
1d1346639c2014701310416ad92cbe2e
የጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አዳዲስ ሹመቶች
ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በካቢኒያቸው አዲስ ሽግሽግና የሥራ ምድብ አደረጉ። የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ለማ መገርሳ ተነሱ። የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ሆነው ተሾሙ። በሌላ በኩል ደግሞ ሽግሽጉ ብዙ ሊያስገርምና ሊያስደንቅ እንደማይገባ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለማቀፍ ግንኙነቶች መምህር ገለፁ።በመንግሥት መገናኛ ብዙሃን ዛሬ በተቀዳሚ ዜናነት በተደጋጋሚ ሲነገር እንደተሰማው ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለ11 ሰዎች አዳዲስ ሹመት ሰጥተዋል።
1
4fabef73e2e19affa979dfc803f2a2c2
4fabef73e2e19affa979dfc803f2a2c2
ማይክል ጃክሰን ከሞቱ የአለማችን ዝነኞች ለ6ኛ ጊዜ በገቢ መሪነቱን ይዟል
በህይወት ከሌሉ የአለማችን ዝነኞች ከፍተኛውን ገቢ በማግኘት ላለፉት አምስት አመታት በመሪነት የዘለቀው የፖፕ ሙዚቃ ንጉስ ማይክል ጃክሰን ዘንድሮም በ313 ሚሊዮን ፓውንድ አመታዊ ገቢ በአንደኛ ደረጃ ላይ መቀመጡ ተዘግቧል፡፡ማይክል ጃክሰን ከኤሚ ሚዩዚክ ፐብሊሺንግ በተባለው አሳታሚ ኩባንያ ውስጥ ካለው የአክስዮን ድርሻና በህይወት ሳለ የሰራቸውን ሙዚቃዎች ለማሳተም ከኩባንያዎች ጋር የተደረጉ ስምምነቶችን ጨምሮ በድምሩ 313 ሚሊዮን ፓውንድ ማግኘቱን የዘገበው ፎርብስ መጽሄት፤ ድምጻዊው ከዚህ አለም በሞት ከተለየበት እ.ኤ.አ 2009 በኋላ ባሉት አመታት በድምሩ 1.8 ቢሊዮን ፓውንድ ገቢ ማግኘቱን የጠቆመው ዘገባው፣ በህይወት ከሌሉ የአለማችን ዝነኞች በገቢ የሁለተኛነት ደረጃን የያዘው ሌላው ዘመን አይሽሬ ድምጻዊ ኤልቪስ ፕሪስሊ ሲሆን፣ ኤልቪስ ባለፉት 12 ወራት ጊዜ ውስጥ 31 ሚሊዮን ፓውንድ ገቢ ማግኘቱን አመልክቷል፡፡ በተወለደ በ42 አመቱ እ.ኤ.አ በ1977 ከዚህ አለም በሞት የተለየው ኤልቪስ ፕሪስሊ ባለፉት 12 ወራት የተጠቀሰውን ገቢ ያገኘው ከቀድሞ ሙዚቃዎቹ ሽያጭና ከሌሎች ገቢዎች እንደሆነ ተነግሯል፡፡ዝነኛው የጎልፍ ተጫዋች አርኖልድ ፓልመር በ27 ሚሊዮን ፓውንድ የሶስተኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ፣ ታዋቂው ካርቱኒስት ቻርለስ ሹልዝ በ26 ሚሊዮን ፓውንድ አራተኛ፣ የሬጌው ሙዚቃ ንጉስ ቦብ ማርሌ ደግሞ በ18 ሚሊዮን ፓውንድ አምስተኛ ደረጃን ይዘዋል፡፡በፎርብስ መጽሄት የዘንድሮ የአለማችን ሟች ዝነኞች ገቢ ዝርዝር ውስጥ ከተካተቱት ሌሎች ዝነኞች መካከል እውቋ የፊልም ተዋናይ ማርሊን ሞንሮ የምትጠቀስ ሲሆን፣ በ11 ሚሊዮን ፓውንድ የ11ኛ ደረጃን ይዛለች፡፡
1
3a5585126b10eb71b9bae04d7cecb65b
931844ad670f7e6827bc05eb9498438c
የብረታ ብረት ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አደረገ
የብረታ ብረት ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ከፍተኛ ኃላፊዎች በመንግሥት ላይ 319,475,287 ብር ጉዳት በማድረስ ተጠርጥረው በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 15ኛ ወንጀል ችሎት ክስ ተመሠረተባቸው፡፡በክሱ የተካተቱት የሜቴክ የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር ሜጄር ጄኔራል ክንፈ ዳኘው፣ የሜቴክ የቀድሞ ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የግብይትና ሽያጭ ኃላፊ ብርጋዴር ጄኔራል ጠና ቁርንዲ፣ የአዳማ እርሻ መሣሪያዎች ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ የቀድሞ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኮሎኔል ደሴ ዘለቀ፣ የአዳማ እርሻ መሣሪያዎች ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ የቀድሞ ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የኮርፖሬሽኑ ማርኬቲንግና ሰፕላይ ኃላፊ ኮሎኔል ጌትነት ጉድያ፣ የአዳማ እርሻ መሣሪያዎች ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ የቀድሞ ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የኮርፖሬት ኒው ቢዝነስ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኮሎኔል ጎይቶም ከበደ፣ በንግድ ሥራ የሚተዳደሩት ቸርነት ዳና፣ እሌኒ ብርሃኑና ረመዳን ሙሳ ናቸው፡፡ተከሳሾቹ የተጠቀሰውን ገንዘብ በመንግሥት ላይ ጉዳት አድርሰዋል የተባለው በሜቴክ ሥር ለሚገኘው የአዳማ እርሻ መሣሪያዎች ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ አገልግሎት የሚውሉ ትራክተሮች ግዥ ወቅት፣ ከኮርፖሬሽኑ የግዥ አፈጻጸም መመርያ ውጭና ያለጨረታ ግዢ እንዲፈጸም በማድረጋቸው መሆኑን ዓቃቤ ሕግ በክሱ በዝርዝር ገልጿል፡፡
0
886a61f479fa5059d82a15f50ed3e369
b861db637da339d0c22dbb3589a4aad2
አንበሳ አውቶብስ ተጨማሪ 50 ተጣጣፊ አውቶብሶች ግዢ አካሄደ
አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 20 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ከጀሞ 2 እስከ ጀኔራል ዊንጌት የሚገነባው የፈጣን አውቶብስ መንገድ ተጀመረ።የመንገዱን ግንባታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ አስጀምረውታል።መንገዱ በአጠቃላይ 20 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን ወደ ሁለት አቅጣጫ የሚዘረጋ ነው ተብሏል።የፈጣን አውቶብስ መንገዱ አዲስ ከተማ፣ ልደታ፣ ቂርቆስና ኮልፌ በመሳሰሉ ቦታዎች የአውቶብስ መቆሚያዎች ይኖሩታልም ነው የተባለው።በቀጣይም ከ20 በላይ የአውቶብስ የፍጥነት መንገድ መንገድ ፕሮጀክቶች መታቀዳቸውን ኢንጂነር ታከለ ኡማ ተናግረዋል።አያይዘውም የከተማ አስተዳደሩ የትራንስፖርት ችግርን ለመፍታት የብዙሀን ትራንስፖርትን ማዘመንና ማሳደግ ላይ ያተኩራልም ነው ያሉት።ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜና በተቀመጠላቸው የጥራት ደረጃ እንደሚጠናቀቁ መናገራቸውን ከአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።የአውቶብስ የፍጥነት መንገድ ፕሮጀክቱን የፈረንሳይ ኩባንያ የሚያከናውነው ይሆናል።
0
23e44d1d5b97f5f0a78b0b4b20cc2aa6
15b8ab3e1cb00d91dc01d42c103a694a
ፖሊስ መምህር ግርማን በነፍስ ግድያ በመጠርጠሩ በዋስ አልተፈቱም
ፖሊስ ለተጨማሪ ምርመራ ለ14 ቀናት እንዲራዘም ያቀረበውን ጥያቄ ጉዳዩን የሚያየው የሃዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ወንጀል ችሎት አልተቀብለውም፡፡ዳሩ ግን ፖሊስ ይግባኝ ማለት እንድሚችል ገልጦ፤ ለነሃሴ 14/2011 ዓ/ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡የሲዳማ ዞን ምክር ቤት በጠራው አስቸኳይ ጉባዔ በዞኑ ተከስቶ ከነበረው የፀጥታ ችግር ጋር በተያያዘ ከሥልጣን በታገዱት የዞኑ አስተዳዳሪ ቃሬ ጫውቻ ምትክ የተሾሙትን የአቶ ደስታ ሌዳሞን ሹመት አፀደቀ፡፡ምክር ቤቱ በህግ የበላይነት፣ በፀጥታ፣ በወቅታዊ ሁኔታዎችና በውሳኔ ሕዝብ አፈፃፀም ሂደት ዙሪያ መምከሩንም አፈ-ጉባዔው ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት መግለጫ ገልፀዋል፡፡
0
5de104a60a43061b302cb13ad41361dd
f25df3b390c0970c87d5f7a8da9e1f65
የወረቀት ላይ ፈተና እድሜ እንደማይኖረው ተገለጸ
ካፍ ወደ ኤሊት ደረጃ የሚያድጉ ዳኞችን ለመለየት የሚያከናውነው ፈተና ላይ ኢትዮጵያዊው ኢንተርናሽናል ዳኛ ቴዎድሮስ ምትኩ ኤሊት ቢ ፈተናን አጠናቆ ወደ ሀገር ቤት ተመልሷል።በሩዋንዳ በተከናወነው ስልጠና እና ፈተና ላይ ከ36 የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ የተወጣጡ ዳኞች ሲሳተፉ ኢትዮጵያዊው ኢንተርናሽናል ዳኛ ቴዎድሮስ ምትኩም የኢሌት ቢ ስልጠናን አጠናቆ ተመልሷል። ስልጠናው የተለያዩ እርከኖች የነበሩት ሲሆን ከአንዱ እርከን ወደ ሌላኛው ለማለፍ ፈተናዎች ተሰጥተዋል። በአካል ብቃት ፈተና የተጀመረው ይህ ስልጠና 40 ሜትርን በ6 ሰከንዶች ለስድስት ጊዜ በመደጋገም ማጠናቀቅ የመጀመርያው ሲሆን 75 ሜትርን በ17 ሰከንዶች ማጠናቀቅ እና በ25 ሰከንድ እረፍት 10 ጊዜ ደጋግሞ ማጠናቀቅ መቻል ቀጣዩ ፈተና ነበር።ይህን ፈተና ያለፉት ሰልጣኞች ወደ ክፍል በመግባት ስልጠና የወሰዱ ሲሆን ስልጠናው በየቀኑ የቪድዮ ፈተናም እንደነበረው ለማወቅ ተችሏል። ከጨዋታ ውጪ ፣ ቴክኒካል ፋውል ፣ በሆልዲንግ፣ በፍፁም ቅጣት ምት ክልል ውስጥ የሚፈጠሩ ጥፋቶች እና ኳስን በእጅ የመንካት ጥፋቶች ላይ ያተኮረ ነበር። በዚህም በ2018 የኢንተርናሽናል ባጅ ያገኘው ቴዎድሮስ ምትኩ አህጉራዊ ውድድሮች ላይ ለመዳኘት ዕድል የሚፈጥርለት የኤሊት ቢ ደረጃ ማደግ ችሏል።
0
8da2dff013bce5578ffdd89eb1ccc9c4
8da2dff013bce5578ffdd89eb1ccc9c4
ቦይንግ ኩባንያ 144 ሽሕ 500 ዶላር ካሳ በነብስ ወከፍ ሊከፍል ነው
የአሜሪካው አውሮፕላን አምራች ኩባንያ ቦይንግ ባሳለፍነው ዓመት ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነው ቦይንግ 737 ማክስ 8 ከአዲስ አበባ ናይሮቢ በጉዞ ላይ ባጋጠመው አደጋ 157 ሰዎች ሕይወት መጥፋቱን ተከትሎ ለተጎጂ ቤተሰቦች በነብስ ወከፍ 144ሽሕ 500 ዶላር ካሳ ሊከፍል እንደሆነ ይፋ ሆኗል።ኩባንያው ባሳለፍነው ዓመት ሰኔ ወር ላይ ለመክፈል ከተስማማው 100 ሚሊዮን ዶላር ውስጥ የሚሰጥ ሲሆን ከዚህም ውስጥ ግማሹ ደግሞ አደጋው በደረሰበት አካባቢ ለሚገኘው ማኅበረሰብ የትምህርት ቤትና ሌሎች መሰረተ ልማቶች ማስገንቢያ የሚውል እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል። በአደጋው 35 የተለያዩ አገራት ዜጎች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን የሚከፈለው ካሳ በበቂ ሁኔታ የሚክስ አይደለም የሚሉ ወገኖችም ከወደ አሜሪካ እየተሰማ ነው።
1
778d307771ef966e5606ade47bb1bc5c
8bf894ef74f503a10a74aa8a8697589a
በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ በከባድ ዝናብ ምክንያት ለ330 ቤተሰቦች ተፈናቀሉ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በደቡብ ክልል በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ የጣለውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ በተከሰተ የጎርፍና ጭቃ ናዳ አደጋ የ10 ሰዎች ህይወት አለፈ።የጋሞ ዞን ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ረታ ተክሉ እንደተናገሩት፥ በጋጮ ባባ ወረዳ ጋፄ ጎሎ ቀበሌ ከማለዳው 1 ሰዓት ገደማ በጣለው ዝናብ ነው አደጋው የደረሰው።እንደ ኮማንደር ረታ ተክሉ ገለፃ፥ በዚሁ ወረዳ በጊና ቀበሌ ከተራራ አከባቢ በተከሰተ ናዳና ጎርፍ የሁለት አባወራ ቤትና አትክልት ከነ ሙሉ ንብረቱ በናዳው ተሸፍሏል።አደጋውን ተከትሎም እስካሁን ባለው መረጃ የ10 ሰዎች ህይወት ማለፉ የተረጋገጠ ሲሆን፥ የሟቾች ቁጥር ከዚህ ሊጨምር እንደሚችል ከጋሞ ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።በተመሳሳይ በጋሞ ዞን ገረሴ ወረዳ ጋርባንሳ ጋሎ ቀበሌ ከባድ ዝናብ ተከትሎ በተከሰተ የጎርፍና ጭቃ ናዳ ሶስት ቤቶች መስጠማቸውንም ጽህፈት ቤቱ አስታውቋል።ዝናቡ መቀጠሉ እንዲሁም የናዳው ሁኔታም እንዳልቆ የተገለፀ ሲሆን፥ ይህም የአስከሬን ፍለጋውንም አዳጋች እንዳደረገውም ነው።#FBCየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
0
ce638b1afb8fa0df635b0879dae5e536
ce638b1afb8fa0df635b0879dae5e536
ብሔራዊ ባንክ የወጋገን ባንክ ምክትል ፕሬዚዳንት ሹመት አፀደቀ
በዳዊት እንደሻውወጋገን ባንክ አቶ ደሳለይ እንበዛ በምክትል ፕሬዚዳንትነት እንዲሾሙለት ያቀረበውን ጥያቄ ብሔራዊ ባንክ አፀደቀ፡፡ አቶ ደሳለይ በምክትል ፕሬዚዳንትነት የአገልግሎት ክዋኔ ዘርፉን ይመራሉ፡፡በሹመቱ መሠረት አቶ ደሳለይ ከአሁን በፊት በቦታው የነበሩትን አቶ አሰፋ ተፈራን ይተካሉ፡፡ ከአሁን ቀደም ቦታውን ሲመሩት የነበሩት አቶ አሰፋ፣ ከአንድ ወር በፊት ከቤተሰብ ጋር በተያያዙ የግል ምክንያቶች መልቀቃቸው ታውቋል፡፡አቶ አሰፋ በምክትል ፕሬዚዳንትነት ላለፉት ሁለት ዓመታት ቆይተዋል፡፡ ሹመታቸውም ወጋገን ባንክ አጠቃላይ የአስተዳደር መዋቅረ ለውጥ ካደረገ በኋላ የመጣ ነው፡፡የአስተዳደር መዋቅር ለውጡ ዲሎይት በተባለው ዓለም አቀፍ አማካሪ ኩባንያ አማካይነት ከተደረገ ጥናት በኋላ የመጣ ሲሆን፣ የመዋቅር ለውጡም ድሮ ያልነበሩ የምክትል ፕሬዚዳንትነት ቦታዎችን አስተዋውቋል፡፡ በዚህም መሠረት የኮርፖሬት፣ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ የአገልግሎት ክዋኔ፣ እንዲሁም የድጋፍ ዘርፎች በምክትል ፕሬዚዳንቶች እንዲመሩ ተዋቅረዋል፡፡ ከዚህ በፊት ባንኩ ሁለት የምክትል ፕሬዚዳንት ቦታዎች እንደነበሩት ይታወሳል፡፡አሁን የተሾሙት አቶ ደሳለይ ከአሁን ቀደም በባንኩ የተለያዩ ኃላፊነቶች ለአሥር ዓመታት ያገለገሉ ናቸው፡፡ ለባለፉት አራት ዓመታት ደግሞ የብድር ግንኙነት ዳይሬክተር ሆነው ሠርተዋል፡፡በተጨማሪም የወጋገን ሽሬ እንዲሁም ተክለ ሃይማኖት (አዲስ አበባ) ቅርንጫፍ ኃላፊ ሆነው በተለያዩ ጊዜያት ሠርተዋል፡፡በ30ዎቹ መጨረሻ የዕድሜ ክልል የሚገኙትና የሦስት ልጆች አባት የሆኑት አቶ ደሳለይ አሁን ባገኙት ሥልጣን መሠረት የዓለም አቀፍ ባንኪንግን፣ የቅርንጫፎችንና ከብድር ጋር የተገናኙ ሥራዎችን በዋናነት ይመራሉ፡፡በ1990 ዓ.ም. መጀመርያ በ16 ባለአክሲዮኖች በ30 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል የተመሠረተው ወጋገን ባንክ፣ በሰኔ 2008 ዓ.ም. ባወጣው ሪፖርት መሠረት የተከፈለ ካፒታሉ 1.7 ቢሊዮን ብር ደርሷል፡፡በአሁን ወቅት ባንኩ 2,349 የአክሲዮን ባለቤቶች አሉት፡፡ ዋና መሥሪያ ቤታቸውን በአሁኑ ወቅት እየገነቡ ከሚገኙት ባንኮችና ኢንሹራንስ ኩባንያዎች መካከል አንዱ የሆነው ወጋገን ባንክ፣ እስካሁን ለዋና መሥሪያ ቤቱ ሕንፃ ግንባታ ወደ አንድ ቢሊዮን ብር ውጪ አውጥቷል፡፡አብዛኛው ሥራ የተጠናቀቀለት የባንኩ ዋና መሥሪያ ቤት ሕንፃ በቀጣዩ ዓመት ሙሉ ለሙሉ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
1
dcb4823e57a12225670cb5566e5587b0
602a565e2edd4eba2107905ba6176105
የሶማሊያ ፓርላማ ቃለ - መሃላ ፈፀመ
የደቡብ ሱዳኑ አማጽያን መሪ ሪያክ ማቻር ለዚያች አገር አዲስ ምዕራፍ ጅማሮ በታለመ ዕቅድ ትላንት ጁባ ላይ ዳግም የአገሪቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ያደረጋቸውን ቃለ መሃላ ፈጸሙ። ይሁንና በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለው እርስ-በእርስ ያለመተማመን በቀጣዩ የሽግግር ወቅት ላይ እንዳያጠላ ሥጋት አሳድሯል። ጂል ክሬግ ከናይሮቢ ያጠናቀረችው ዘገባ ዝርዝሩን ይዟል። አሉላ ከበደ ያቀርበዋል። ከረዥም ጥበቃ በኃላ በመጨረሻው ትላንት ከጁባ የአውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ሞቅ ያለ አቀባበል የጠበቃቸው የቀድሞው የደቡብ ሱዳኑ አማጽያን መሪ አዲሱ ምክትል ፕሬዝዳንት ሪያክ ማቻር ከተቀናቃኛቸው ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ጋር አዲስ የጋራ መንግስት ለመመስረት ነው የተመለሱት። ዝርዝሩን ከዚህ ያድምጡ፤
0
f695a8c6e93a68f10a0cb12f9a293f91
c5db8eb44b6821b0d495426eaf493fba
የዙና ትሬዲንግ ስራ አስኪያጅ በ14 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጡ
ፕላቶ የተባለቺው የናይጀሪያ ግዛት ዋና አስተዳዳሪ የነበሩትና በአሁኑ ወቅት የኮንግረስ አባል የሆኑት ጆሽዋ ዳሪዬ፣ በ3.2 ሚ ዶላር ዝርፊያ ተከከስሰው የ14 አመታት እስር እንደተፈረደባቸው ተዘግቧል፡፡ባለስልጣኑ እ.ኤ.አ ከ1999 እስከ 2007 የፕላቶ ግዛት ዋና አስተዳዳሪ ሆነው በሚሰሩበት ወቅት ለግዛቲቱ የአካባቢ ጥበቃ የተመደበውን 3.2 ሚሊዮን ዶላር ዘርፈው፣ ለግል ጥቅማቸው ማዋላቸው በመረጋገጡ፣ የእስር ቅጣቱ እንደተጣለባቸው ቢቢሲ ዘግቧል፡፡በተመሳሳይም ታራባ የተባለቺው የናይጀሪያ ግዛት ዋና አስተዳዳሪ የነበሩት ጆሊ ናይሜ፣ ከሁለት ሳምንታት በፊት በሙስና ተከስሰው፣ የ14 አመታት እስር እንደተፈረደባቸው ዘገባው አስታውሷል፡፡
0
4ec1e236c7d6c42096f2e6ca06728c0d
4ec1e236c7d6c42096f2e6ca06728c0d
የ100 ቀን እቅድ ተግባራዊ መደረጉ ውጤታማ አድርጎናል- የገቢዎች ሚኒስቴር ሰራተኞች
የ100 ቀን እቅድ ተግባራዊ መደረጉ ውጤታማ እንዳደረጋቸው የገቢዎች ሚኒስቴር ሰራተኞች ለዋልታ ቴሌቪዥን ገልጸዋል፡፡እንደ ሰራተኞቹ ገለጻ እቅዱ በስራዎቻቸው ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ከማስቻሉም በላይ ስራን የማሳደር ባህልን አስቀርቷል፡፡በሌላም በኩል አሰራሩ በኔት ዎርክ ቢተሳሰርና ዲጂታል ቢሆን ይበልጥ ውጤታማ እንደሚሆንም ሰራተኞቹ ጠቁመዋል፡፡በተጨማሪም ከባንክ እና መሰል የፋይናንስ ተቋማት ጋር በጋራ መስራት ቢቻል የተገልጋይን መጨናነቅ እንደሚቀንስም አስረድተዋል፡፡ዋልታ ያነጋገራቸው ተገልጋዮችም የአገልግሎት አሰጣጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡
1
933003b6339f4fb8bc6ded934ec7674c
933003b6339f4fb8bc6ded934ec7674c
በዱባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል
አዲስ አበባ፣ ጥር 15 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በዱባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች ተከታትለው በመግባት አሸናፊ ሆነዋል።በወንዶች አትሌት ኦሊቃ አዱኛ 2 ሰዓት ከ6 ደቂቃ ከ15 ሰከንድ በመግባት ውድድሩን በአንደኝነት አጠናቋል።ኬንያዊው አትሌት ኤሪክ ኪፕሮኖ 2ኛ ደረጃን ሲይዝ ከ3ኛ እስከ 10ኛ ያለውን ደረጃ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ተከታትለው በመግባት ውድድሩን በበላይነት አጠናቀዋል።በዚህም መሰረት ፀዳት አበጀ 3ኛ፣ ሌንጮ ተስፋዬ 4ኛ፣ ይታያል አጥናፉ 5ኛ፣ ይሁንልኝ አዳነ 6ኛ፣ አይቼው በንቲ 7ኛ፣ ሰይፉ ቱራ 8ኛ፣ ጫሉ ደሶ 9ኛ እንዲሁም ዘውዱ ሀይሉ 10ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቀዋል።በሴቶች ምድብ ደግሞ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1ኛ እስከ 9ኛ ደረጃ ተከታትለው በመግባት ውድድሩን በበላይነት ማጠናቀቅ ችለዋል።በዚህም መሰረት አትሌት ወርቅነሽ ደገፋ 2 ሰዓት ከ19 ደቂቃ ከ37 ሰከንድ በመግባት ውድድሩን በአንደኝነት ስታጠናቅቅ፤ አትሌት ጉተኒ ሾሜ 2 ሰዓት ከ20 ደቂቃ ከ11 ሰከንድ በመግባት 2ኛ፣ አትሌት በዳቱ ሂርጳ 2 ሰዓት ከ21 ደቂቃ ከ54 ሰከንድ በመግባት 3ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።እንዲሁም አትሌት ትዕግስት ባያቸው፣ አትሌት ደራ ዲዳ፣ አትሌት ሀዊ ፈይሳ፣ አትሌት ብዙነሽ ዳባ፣ አትሌት ኦብሴ አብደታ እና አትሌት ቡዜ ድሪባ ከ4ኛ እስከ 9ኛ ደረጃ ተከታትለው በመግባት ውድድሩን በበላይነት አጠናቀዋል።
1
239ca5c749eadd0e2256d60ac8bd2335
239ca5c749eadd0e2256d60ac8bd2335
የሱዳን ባለሀብቶች ልዑክ ቢሾፍቱ ገባ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)የሱዳን ባለሀብቶች ልዑክ በአማራ ክልል ያካሄደው ጉብኝት አጠናቆ በኦሮሚያ ክልል ጉብኝት ለማድረግ ቢሾፍቱ ከተማ ገባ።የባለሀብቶች ልዑክ ቢሾፍቱ ሲገባ የኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ አቶ ከበደ ዴሲሳ እና የሀገር ሽማግሌዎች አቀባበል አድርገውለታል። በዚህ ወቅት ንግግር ያደረጉት የቢሮ ሃላፊው እንደዚህ አይነት ጉብኝት ቱሪዝም ዘርፍ ኢንቨስትመንትን ከማነቃቃት ባሻገር የሁለቱን ሀገራት ህዝቦች አብሮነት እና ወንድማማችነት የበለጠ እንደሚያጠናከር ገልፀዋል። የሱዳን ባለሀብቶች ልዑክ መሪ ኦማር አሊ በበኩላቸው የኢትዮጵያ እና የሱዳን ህዝቦች በባህልም ሆነ በአኗኗር እንደ አንድ ህዝብ ናቸው ብለዋል። በአማራ ክልል ጎርጎራን ጨምሮ የተለያዩ አካባቢዎችን የጎበኘው ልዑክ በኦሮሚያ ክልል በሚኖረው ቆይታም የቱሪዝም መዳረሻዎችን እና አማራጭ መስህቦችን ይጎበኛል ተብሎ ይጠበቃል። በዚህም የአቢያታ ሻላ ሀይቅን፣ አዋሽ ፓርክ ፣ የባሌ ብሄራዊ ፓርክ እና ሌሎች የቱሪዝም መስህብ አማራጮች እንደሞጎበኝ ነው የተነገረው። እነዚህ የሱዳን ባለሀብቶች በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎችበሀገራቸው እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ ሲሆን ከጉብኝቱ በኋላ በጎበኟቸው አካባቢዎች በቱሪዝም ዘርፍ ኢንቨስት እንደሚያደርጉ ተነግሯል። በብዙዓለም ቤኛ
1
67b5cf62eb86c009773d620db3b813de
46f14bc8710ef64aaafa6a94fe85ad78
ሴካፋ 2017፡ ቡሩንዲ ሳትጠበቅ ከዩጋንዳ ጋር ነጥብ ተጋርታለች
ከሀምሌ 12 እስከ 19 በሩዋንዳ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ ዝግጅት የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሰላም ዘርዓይ 22 ተጫዋቾችን ጠርታለች። የተጠሩት አመዛኝ ተጫዋቾች በአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ላይ ያገለገሉ ሲሆኑ ወሳኛ አጥቂ ሎዛ አበራ ለሙከራ ወደ ስዊድን በማምራቷ እንዲሁም ሌላኛዋ አጥቂ ረሒማ ዘርጋ ከዝርዝሩ ተዘለዋል።የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ በነገው እለት የሚጠናቀቅ ሲሆን ከዕሁድ ጀምሮ ተጫዋቾች ተሰባስበው አዲስ አበባ ለልምምድ ምቹ ባለመሆኑ ምክንያት አዳማ፣ ቢሾፍቱ አልያም ሀዋሳ በአንዱ ከተማ ዝግጅታቸውን እንደሚያደርጉ ተገልጿል።የተመረጡ ተጫዋቾች ዝርዝርግብ ጠባቂዎችገነት አክሊሉ (ደደቢት)፣ ታሪኳ በርገና (ጥረት ኮርፖሬት )፣ ንግስት መዐዛ (ኢ/ንግድ ባንክ)ተከላካዮችመሰሉ አበራ (ቅዱስ ጊዮርጊስ)፣ ብዙዓየሁ ታደሰ (ጊዮርጊስ)፣ ቤተልሄም ከፍያለው ( ኤሌክትሪክ)፣ አሳቤ ሙሶ (ጥረት ኮርፖሬት)፣ መስከረም ካንኮ ( ደደቢት)፣ ታሪኮ ደቢሶ (ንግድ ባንክ)አማካዮችቤዛዊት ተስፋዬ (ቅዱስ ጊዮርጊስ)፣ አለምነሽ ገረመው (ኤሌክትሪክ)፣ አረጋሽ ካልሳ (ኢትዮ/ወጣቶች አካዳሚ)፣ እመቤት አዲሱ (መከላከያ)፣ ሰናይት ቦጋለ (ደደቢት)፣ ብርቱካን ገ/ክርስቶስ (ደደቢት)፣ ትዕግስት ዘውዴ (ደደቢት)፣ ዙለይካ ጁሀድ ( ንግድ ባንክ)፣ ህይወት ደንጊሶ (ንግድ ባንክ)አጥቂዎችሴናፍ ዋቁማ (አዳማ ከተማ)፣ ምስር ኢብራሂም (ጥረት ኮርፖርት)፣ ምርቃት ፈለቀ (ሀዋሳ ከተማ)፣ ልደት ቶሎአ (ሀዋሳ ከተማ)በ5 ሀገራት መካከል በሚደረገው የዘንድሮው ሴካፋ ውድድር ኢትዮጵያ ሐምሌ 14 ላይ ከዩጋንዳ ጋር ትጫወታለች።
0
fa984036185d2fc6fe035a4e7e3ef095
fa984036185d2fc6fe035a4e7e3ef095
አማካዩ ከሲዳማ ቡና ጋር ተለያይቷል
ከሲዳማ ቡና ጋር የተለያየው የአማካይ ሥፍራ ተጫዋቹ ትርታዬ ደመቀ ከሲዳማ ቡና ቀጣይ ማረፊያው በቅርቡ ይታወቃል፡፡በአርባምንጭ ከተማ የእግር ኳስ ህይወቱን የጀመረው ይህ ተጫዋች 2009 ክለቡን ከለቀቀ በኃላ ወደ ሲዳማ ቡና አምርቶ እስከ ተሰረዘው 2012 የውድድር አመት ድረስ በክለቡ በመጫወት አሳልፏል፡፡ ትርታዬ ከሲዳማ ቡና ጋር የነበረው የውል ጊዜ በማብቃቱ የክለቡን አመራሮች እና ደጋፊዎች በማመስገን መለያየቱን ለሶከር ኢትዮጵያ በላከው መልዕክት ገልጿል፡፡“ከሲዳማ ቡና ጋር ጥሩ ዓመታትን አሳልፊያለሁ፡፡ አሁን ግን አዲስ ባህል አዲስ የሆነ ክለብ ፈልጌ ተለያይቻለሁ። በክለቡ ለነበረኝ ጊዜ የክለቡን አመራሮች እና አሰልጣኞች እንዲሁም ውብ የሆነውን ደጋፊ ማመስገን እፈልጋለሁ፡፡ የእኔም ቀጣይ ክለብ በአጭር ቀን ውስጥ አሳውቃለሁ።”
1
3361515613aee80b129e6dd6758acb4d
60cfdc9ca8a0677399bee12dc186b8d2
ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የ2 ሚሊየን ብር የማበረታቻ ሽልማት ተበረከተ
ደደቢት በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ ከተሰማራው ትራንስ ኢትዮጵያ ጋር ወደፊት የሚታስ የአጭር ጊዜ የስፖንሰርሺፕ ውል ዛሬ በካፒታል ሆቴል ተፈራርሟል፡፡ስምምነቱን የፈረሙት የደደቢት እርኳስ ክለብ ፕሬዝዳንት አቶ ወልዳይ በርሄ እና የትራንስ ኢትዮጵያ ስራ አስኪያጅ አቶ ተፈሪ ዘውዱ ሲሆኑ ለ6 ወር በሚቆየው የስፖንሰር ሺፕ ስምምነት ትራንስ ለደደቢት 4 ሚልዮን ብር ይከፍላል፡፡ በስምምነቱ ላይ ትራንስ ኢትዮጵያ በቀጣዩ አመት ወደ ክለቡ የኮርፖሬት አባልነት የሚያድግ ሲሆን ክለቡን በቀጣዮቹ አመታት በተለያዩ ተቋማት ባለበትነት ስር እንዲተዳደር የማድረግ አላማ ያለው ነው ተብሏል፡፡በጋዤጣዊ መግለጫዎች ላይ ፣ ደደቢት በሜዳው በሚያደርጋቸው ጨዋታዎች እና በክለቡ ኦፊሴላዊ ፎቶዎች ላይ የትራንስ ኢትዮጵያ አርማ የያዘ ባነር እንደሚኖር ከደደቢት በኩል ተገልጧል፡፡ በትራንስ በኩል የስፖርት ልማትን ለመደገፍ እና ኩባንያውን የማስተዋወቅ አላማ በመያዝ ደደቢትን ስፖንሰር እንዳደረገ ታውቋል፡፡ደደቢት ይህን መሰል ስምምነት ሲፈራረም 2008 ከገባ በኋላ ለሶስተኛ ጊዜ ነው፡፡ መሰቦ ሲሚንቶ የማልያ ስፖንሰር በመሆን በ4 ሚልዮን ብር ለአንድ አመት ስፖንሰር የሆነ ሲሆን ከሳምንታት በፊት ሱር ኮንስትራክሽን 2.3 ሚልዮን ብር የሚያወጣ የተጫዋቾች ማጓጓዣ አውቶብስ በስፖንሰር መልክ አበርክቷል፡፡በፕሮግራሙ መጨረሻ የደደቢት ሴቶች ቡድን አባላት በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ አንደኛ ዙር ላስመዘገቡት ውጤት የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ በዚህም መሰረት እንደየአስተዋፅኦዋቸው ከ7-4 ሺህ ብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡
0
5303809eca8c5924e23e86057e69c7fe
c5160be1fc7b4a1bbcc43f8ba8593d3a
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በነገው ዕለት ከ9 ሺህ 600 በላይ ተማሪዎችን ያስመርቃል
አዲስ አበባ፣ ህዳር 17፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በዓለም አቀፍ ደረጃ ኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 60 ሚሊየን ማለፉ ተገለጸ።እንደ ጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ መረጃ ከሆነ እስካሁን በወረርሽኙ የተያዙ ሰዎች 60 ሚሊየን 420 ሺህ 355 ደርሷል።ከእነዚህ መካከል 38 ሚሊየን 704 ሺህ 716 የሚሆኑት ደግሞ ከወረርሽኙ ማገገማቸው ተሰምቷል።ወረርሽኑ ከተከሰተበት ካለፈው ዓመት ጀምሮ በመላው ዓለም የ1 ሚሊየን 421 ሺህ 650 ሰዎችን ህይወት አልፏል።ወረርሽኙ እየተስፋፋባቸው ከሚገኙ ሀገራት መካከል አሜሪካ ዋነኛ መሆኗን መረጃዎች ያሳያሉ።አስካሁን ድረስ በአሜሪካ ከ12 ሚሊየን በላይ ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ፣ በህንድ ከ9 ሚሊየን በላይ፣ በብራዚል ከ6 ሚሊየን በላይ፣ በፈረንሳይና በሩሲያ ከ2 ሚሊየን በላይ፣ በስፔን እና በእንግሊዝ ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ፣ በጣልያን፣ በአርጀንቲና፣ በኮሎምቢያ እና በሜክሲኮ ከ1 ሚሊየን በላይ ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል፡፡እስካሁን ከፍተኛ ሞት ከተመዘገበባቸው ሃገራት መካከል አሜሪካ 262 ሺህ 266፣ በብራዚል 170 ሺህ 769፣ በህንድ 135 ሺህ 223 ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል።በአፍሪካ ደግሞ በደቡብ አፍሪካ 775 ሺህ 502 ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ 716 ሺህ 444 ሰዎች ማገገማቸውን ነው የተሰማው።ይህም በደቡብ አፍሪካ በወረርሽኙ የሚያገግሙ ሰዎች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን ነው መረጃዎቹ የሚያሳዩት።
0
234c07b6a61fa5f685619f909e448082
b7d7beccfcc87113e384b7eb12bd3ea4
በአዲሱ የኤክሳይስ ታክስ ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ ከአምራቾች ጋር ውይይት ተካሄደ
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 21 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌደራል መንግስት የ2012 በጀት ዓመት የተጨማሪ በጀት ላይ ተወያይቶ አፀደቀ።በዚህ መሰረት የፌደራል መንግስት የ2012 በጀት ዓመት የተጨማሪ በጀት ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ ሰፊ ውይይት በማድረግ አዋጅ ቁጥር 1203/2012 ሆኖ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።የኮሮና ወረርሽኝን የኢኮኖሚ ጫናን ለመቋቋም ከውጭ ሀገራት በሚገኝ 28 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር እና ከሀገር ውስጥ ምንጮች በሚገኝ 20 ቢሊየን ብር ለመቋቋም መታቀዱን የገንዘብ እና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ተናግረዋል።ሚኒስትሩ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት መንግስት ጥንቃቄ የተሞላበት የብድር ሂደት ይከተላል ማለታቸውን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባለፈው የካቲት 9 ቀን 2012 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው ለ2012 በጀት ተጨማሪ 27 ነጥብ 89 ቢሊየን ብር ሆኖ እንዲፀድቅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መምራቱ ይታወሳል።በተጨማሪም ምክር ቤቱ የሰው ሀብትና ቴከኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኤሌክትሮኒክ ትራንዛክሽንን ለመደንገግ የቀረበን ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ መርምሮ አዋጁን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።ከዚህ ባለፈም የጂኦተርማል ሀብት ልማት አዋጅን ለማሻሸል የቀረበ አዋጅን በሙሉ ድምጽ አፅድቆታል።እንዲሁም የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ከሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅን ለማሻሻል የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ እና የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስልን ህጋዊ ሰውነት ለመስጠት የቀረበ ረቂቅ አዋጅ ለህግ፣ ፍትህ እና ዴሞኪራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በአብላጫ ድምጽ ተመርቷል።በተጨማሪም የልዩ የመንግስት ዕዳ ሰነድ ረቂቅ አዋጅ የተመለከተ አዋጅን በአብላጫ ድምጽ ለገቢ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ረቂቅ አዋጅ ቁጥር 38/2012 ሆኖ መርቶታል።#FBCየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
0
9f4418f3306237e3a6f70ae3ee3938f9
9dba5ba43e5d2f857623c081971970f0
የሃገር-በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃዎች ለውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ፍሰት ምቹ ዕድል እንደሚፈጥሩ ም/ጠ/ ሚ አቶ ደመቀ ገለፁ
አዲስ አበባ፡- ኢትዮጵያ ባለፈው አንድ ዓመት ከአንድ ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር በላይ የውጭ ብድር ዕዳ መክፈሏን የገንዘብ ሚኒስትር ዲኤታ ገለጹ።ሚኒስትር ዲኤታው ዶክተር ኢዮብ ተካልኝ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደተናገሩት፤ ባለፉት ዓመታት መከፈል ሲገባው ሳይከፈል የቆየ አንድ ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር የውጭ ዕዳ ክፍያ ተፈጽሟል። ባለፈው አንድ ዓመት የውጭ እዳ በመክፈል ረገድ የተሰራው ስራ የተከማቸ የውጭ ዕዳ ከመክፈል አኳያ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አመላካች ነው ያሉት ዶክተር ኢዮብ፤ ዕዳ የመክፈል ስራው በቀጣይ ዓመታትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።እንደ ዶክተር ኢዮብ ማብራሪያ፤ በቀጣይ ሶስት ዓመታት የሚካሄደው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ኢትዮጵያ የብድር እዳዋን ለመክፈል የሚያስችል የኢኮኖሚ ቁመና ያላት ሀገር እንድትሆን ማድረግ ግብ ነው። በአሁኑ ወቅት ከ45 እስከ 50 በመቶ የሚሆነው ከወጪ ንግድ የሚገኘው የውጭ ሚንዛሬ ግኝት ለብድር ክፍያ እየዋለ ነው። ለቀጣይ ሶስት ዓመታት የሚካሄደው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጪ ንግዱን ከፍ በማድረግና ብድሮችን በማሸጋሸግ ከወጪ ንግድ የሚገኘው 20 ወይም 30 በመቶ የሚሆነው የውጭ ሚንዛሬ ግኝት ብቻ ለውጭ እዳ መክፈያ እንዲውል ለማድረግ ያስችላል፤ ለዚህም በጥብቅ ይሰራል ብለዋል። ከገንዘብ ሚኒስትር ዲኤታው ዶክተር ኢዮብ ተካልኝ ጋር የተደረገውን ሙሉ ቃለ ምልልስ በገጽ ዘጠኝ ይመልከቱ።አዲስ ዘመን መስከረም 8/2012 መላኩ ኤሮሴ
0
b925497a95eb1939766b34cd6e6a6aa1
afb87a70cda1a97531250eb8b25a63b6
የእንየው ካሳሁን ማረፍያ የዐፄዎቹ ቤት ሆኗል
ከብርቱካናማዎቹ ጋር ያለውን ውል ያጠናቀቀው አማካዩ ኤልያስ ማሞ ቀጣይ ማረፍያ በቀጣይ ቀናት ይታወቃል።ባለፈው ዓመት በዚህ ወቅት ድሬዳዋ ከተማን የተቀላቀለው ኤልያስ ከክለቡ ጋር ያለው ውል መጠናቀቁን ተከትሎ ከቡድኑ ጋር ለመቀጠል ውሉን ያራዝማል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረ ቢሆንም ከቡድኑ ጋር ልምምድ አለመጀመሩን ተከትሎ ከክለቡ ጋር የመቀጠሉ ጉዳይ እርግጥ አልሆነም። ከሌሎች የፕሪምየር ሊጉ ክለቦችም ጋር ስሙ እየተነሳ የሚገኘው ይህ የቀድሞ የቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ኢትዮጵያ ቡና፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ጅማ አባጅፋር እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አማካይ ከብርቱካናማዎቹ ጋር ውሉን ያራዝማል ወይስ ወደ ሌሎች ክለቦች ይዘዋወራል የሚለው ጉዳይ በቀጣይ ቀናት ይለይለታል።በውድድር ዓመቱ በአስራ አምስቱንም የሊግ ጨዋታዎች ቡድኑን በቋሚነት ያገለገለው እና በሁለት ጨዋታዎች ብቻ ተቀይሮ የወጣው ኤልያስ ማሞ በሊጉ አንድ ግብ ሲያስቆጥር ለሁለት ግቦች አመቻችቶ አቀብሏል።©ሶከር ኢትዮጵያ
0
10bd68887aa078d2357f25560df231d5
10bd68887aa078d2357f25560df231d5
“ሀገራችን ላይ እየኖርን አይመስለኝም” ከታክሲ አሽከርካሪዎች አንዱ
በአዲስ አበባ የመንገድ ትራፊክ ደኅንነት ደንብን ለማስከበር ከአምስት ዓመት በፊት የወጣውና በከፊል ሲተገበር የነበረው ሕግ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ እንቅስቃሴ በመጀመሩ የአዲስ አበባ ታክሲ አሽከርካሪዎች በሙሉ በዛሬው ዕለት ሥራ የማቆም አድማ መተው ውለዋል፡፡ፌደራሉ የትራንስፖርት ባለሥልጣን ትናንት ባወጣው መግለጫ ትግበራው ለሦስት ወር መራዘሙን አስታውቋል፡፡አሽከርካሪዎቹ ደግሞ “ለሦስት ወር ማራዘም መፍትኄ አይደለም ዘላቂ መፍትሄ እንፈልጋለን” ይላሉ፡፡አሽከርካሪዎችን የአዲስ አበባን ፖሊስ ኮሚሽንን ያነጋገረችው ጽዮን ግርማ ተከታዩን ዘገባ አጠናቅራለች፡፡ዝርዝሩን ከተያያዘው ድምጽ ያድምጡ፡፡
1
85772cf226e9447a29ae46b093634e82
4991df727b3ec162917f59eff8ccc07a
ፋብሪካው በአራት ደቂቃ አንድ ባለሶስት እግር ተሽከርካሪ እየገጣጠመ ነው
የመተሃራ ስኳር ፋብሪካ በያዝነው በጀት ዓመት በካይዘን የስራ አመራር ፍልስፍና እየተመራ አንድ ነጥብ ሶስት ሚሊዮን ኩንታል ስኳር ለማምረት እየተረባረበ መሆኑን ገለፀ፡፡የመተሃራ ስኳር ፋብሪካ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዘነበ ይማም ፋብሪካው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 798 ሺህ ኩንታል ስኳር ማምረቱን ገልጸው ዘንድሮ በካይዘን የስራ አመራር ፍልስፍና እየተመራ አንድ ሚሊዮን 300 ሺህ ኩንታል ስኳር ለማምረት እየተረባረበ ነው ብለዋል።ፋብሪካው በ100 ሚሊዮን ብር በጀት በውጭ ኮንትራክተሮች ሙሉ እድሳት እየተደረገለት መሆኑንም ገልጸዋል።ከስኳር ምርት በተጨማሪ 10 ሚሊዮን 261 ሺህ 363 ሊትር ኢታኖልና 25 ሺህ ኩንታል ፍራፍሬ አምርቶ ለገበያ ለማቅረብ እየሰራ መሆኑን ዋና ስራ አስኪያጁ አስረድተዋል፡፡በካይዘን የስራ አመራር ፍልስፍና በፋብሪካው የነበሩ ችግሮች ተለይተው በመታወቃቸውና የሠራተኛው ውሳኔ ሰጪነት በማጎልበት ለጥራት ልዩ ትኩረት በመስጠትና ወጪ ቆጣቢ የአሰራር ስልት በመቀየስ በአዲስ መንፈስ ለተሻለ ምርታማነት ሰፊ መነቃቃት መጀመሩንም አስታውቀዋል።የመተሃራ ስኳር ፋብሪካ ህዝብ አደረጃጀት፣ ህዝብ ግንኙነትና ማህበራዊ ጉዳዮች ሃላፊ አቶ ሲሳይ ደርበው በበኩላቸው በፋብሪካው ሠራተኞች ዘነድ የነበረው የአስተሳሰብ ችግር በመስተካከሉ፣ የመለዋወጫ አቅርቦት ችግር በመፈታቱና በሠራተኛውና በማኔጅመንቱ መካከል የጋራ መግባባት በመፈጠሩ ፋብሪካው እቅዱን ለማሳካት በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።እንደ ኢሬቴድ ዘገባ ከመተሃራ ስኳር ፋብሪካ ሰራተኞች መካከል አቶ ወንድሙ ሰንበቶ፣አቶ ጌታቸው ባንትይዋል፣ ወይዘሮ ውቤ ካሳና አቶ ጉልማ ሰቦቃ የታላቁን መሪ የአቶ መለስ ዜናዊ ራዕይ ለማሳካት በየተሠማራንበት የስራ መስክ ሁሉ ጠንክረን በመስራት የፋብሪካችንን ምርታማነት እናሳድገዋለን ብለዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
0
473426492b4d6a031ffd60ee457b9f7a
69416a5b1103ed43e4ec141199347ebf
በአፋር እና በኢሳ ሶማሌዎች መካከል የተፈጠረው ግጭት
ዛሬ እሁድ መስከረም 17 ቀን 2013 ዓ.ም በአርሜኒያ እና በአዘርባጃን መካከል በናጎርኖ-ካራባክ አወዛጋቢ ስፍራ ግጭት የተቀሰቀሰ ሲሆን ይህም በደቡብ ካውካሰስ መረጋጋት ላይ ስጋት ፈጥራል፡፡ አካባቢው ነዳጅ እና ጋዝን ወደ ዓለም ገበያዎች የሚያጓጉዙ መተላለፊያ የቧንቧ መስመሮች የሚገኙበት መሆኑ ደግሞ ስጋቱን ያባብሰዋል፡፡ ከዚህ ቀደም እ.ኤ.አ. በ 1990 ዎቹ ጦርነት ያካሄዱት ሁለቱም ወገኖች በተፈጠረው ውጊያ የሰዎች ህይወት ማለፉን አስታውቀዋል፡፡ በአዘርባጃን ውስጥ የሚገኝ እና በአርመኖች ብሄረሰብ የሚተዳደረው ናጎርኖ-ካራባክ የተሰኘ ተገንጣይ ክልል አመራሮች ወታደራዊ አዋጅ በማወጅ ወንዶቻቸውን ለውጊያ ማዘጋጀታቸውን አዘርባጃን ስለመግለጿ የሮይተርስ ዘገባ ያሳያል፡፡ ይህን ተከትሎ አዘርባጃን በናጎርኖ-ካራባክ ላይ የአየር እና የመድፍ ጥቃት አድርሳለች ስትል አርሜኒያ ትከሳለች፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ በተፈጠረው ዉጊያ አዘርባጃን ለአርሜኒያ ጥይት ምላሽ እንደ ሰጠች እና እስከ ሰባት መንደሮችን እንደተቆጣጠረች ብትገልጽም የግጭቱ መንስኤ ናጎርኖ-ካራባህ ይህንን አስተባብሏል፡፡ በአብዛኛው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሚገኙባት አርሜኒያ እና በዋነኝነት የእስልምና እምነት ተከታዮች ሀገር በሆነችው አዘርባጃን መካከል የተፈጠረው ግጭት እንዲረግብ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች ተጀምረዋል፡፡ ሩሲያ አፋጣኝ የተኩስ አቁም ጥሪ ያቀረበች ሲሆን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ደግሞ ሁለቱ ሀገራት ለድርድር እንዲቀመጡ ጠይቀዋል፡፡ ፈረንሳይ ፣ ጀርመን እና የአውሮፓ ህብረት ሀገራትም ሁለቱ ሀገራት ችግራቸውን በድርግር እንዲፈቱ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ሁለቱም ሀገራት እ.ኤ.አ. በ1991 ከመፍረሷ በፊት የሶቪየት ህብረት አካል ነበሩ፡፡ ናጎርኖ-ካራባህ የሶቪየት ህብረት በ 1991 ስትፈርስ በተቀሰቀሰ ግጭት ከአዛርባጃን የተገነጠለ ግዛት ነው፡፡ እ.ኤ.አ. በ 1994 የተኩስ አቁም ስምምነት ቢደረግም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከተገደሉ እና ብዙ ሰዎች ከተፈናቀሉ በኋላ አዘርባጃን እና አርሜኒያ በተደጋጋሚ በናጎርኖ-ካራባክ እና በድንበሮቻቸው ጥቃት ተፈጽሞብኛል በሚል እስከ አሁንም እርስ በርሳቸው ይካሰሳሉ፡፡ በዛሬው ግጭት ከሁለቱም ወገን ንፁኃንን ጨምሮ የሰዎች ህይወት ማለፉ ቢገለጽም ስለ ሞቱት ሰዎች ቁጥር እና ስለ ደረሰው አጠቃላይ ጉዳት ዝርዝር መረጃ አልወጣም፡፡
0
48cc18ad2578d8ef518af97e5cf00796
48cc18ad2578d8ef518af97e5cf00796
ኦኪኪ አፎላቢ በከፍተኛ ክፍያ ዛሬ የጅማ አባጅፋር ንብረት ሆኗል
የክለቡ ፕሬዝዳንት አቶ አጃይብ አባመጫ ኦኪኪ አፎላቢ በዛሬው ዕለት የግላቸው ማድረጋቸውን ለሶከር ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ስኬታማ ጊዜ ካሳለፉ የውጭ ተጫዋቾች መካከል አንዱ የሆነው ናይጄሪያዊው አጥቂ ኦኪኪ አፎላቢ የሊጉ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነትን በ23 ግቦች ካጠናቀቀ በኃላ ውስብስብ በሆኑ አወዛጋቢ ጉዳዮች ታክለውበት ወደ ግብፁ ኢስማኤል ቢያመራም እምብዛም የመጫወት ዕድል ባለማግኘቱ ዳግም ወደ ኢትዮጵያ ተመልሷል፡፡ ዳግም ከተመለሰ በኋላ የቀድሞው ክለቡን በስፋት ይቀላቀላል ቢባልም በርካታ ክለቦች እሱን ፈላጊ በመሆናቸው ወደ ጅማ የመዘዋወሩን ጉዳይ አጠራጣሪ አድርጎት ቆይቶ ነበር፡፡ትላንት በተስተካካይ መርሀ ግብር በሜዳው ከድሬዳዋ ከተማ ጋር 3-3 በተለያየበት ጨዋታ ከ84ኛው ደቂቃ በኋላ በስታዲየሙ ውስጥ የተገኘው ኦኪኪ ለክለቡ መፈረሙን ያረጋገጡት አቶ አጃይብ አባመጫ የተጫዋቹ የዝውውር ሂደት ከታክስ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ረጅም ጊዜን እንደፈጀባቸው ተናግረዋል፡፡ “እሱ ያለን ታክስ ሳይቆረጥ ንፁህ ገንዘብ ሊሰጠኝ ይገባል ነው። እኛ ደግሞ በመንግስት አሰራር መሠረት ታክስ ተቆርጦ የሚደርሰውን ገንዘብ አስቀመጥንለት ነበር። ተጫዋቹን ልንፈልግ የቻልንበት ምክንያት ደግሞ ደጋፊው ለሱ ካለው ፍላጎት አኳያ ነው። ትላንት እኔው ራሴ ትኬት ቆርጬለት ነው የመጣው። ዛሬ ደግሞ ያለውን ነገሮች ሁሉ አጠናቀናል፡፡ እሱ ባለን ነው የሄድነው፤ ምክንያቱም የደጋፊውም ጥያቄዎች ስላሉ እሱ መሄድ ባለበት ነው እኛም የሄድነው።” ብለዋል፡፡ ኦኪኪ ወርሀዊ ወደ 300 መቶ ሺህ ብር ክፍያን ክለቡ እንደሚፈፅምለትም ጭምር ተናግረዋል፡፡የኦኪኪን መምጣት ተከትሎ የውጭ ተጫዋቾች ቁጥሩ ወደ ስድስት ከፍ ያለበት ጅማ አባጅፋር አጥቂው ቢስማርክ አፒያን ሊቀንሰው እንደሚችል ሶከር ኢትዮጵያ ያገኘችው መረጃ ይጠቁማል፡፡
1
56c67ed75dfc7a272c8d2e0d971013ae
56c67ed75dfc7a272c8d2e0d971013ae
ኮቪድ-19 በዓለም
የዓለም የጤና ድርጅት ካለፈው ታህሳስ ወር አንስቶ በዓለም ደረጃ ካለው፣ 10ሚሊዮን የኮቪድ-19 በሽተኞች ቁጥር 60 ከመቶው በያዝነው ሰኔ ወር ላይ እንደተከሰተ ገልጿል።ይህም የቫይረሱ መዛመት እየከፋ መሄዱንና ፍጥነቱም እየቀነሰ አለመሆልኑን እንደሚያስይ የጤናው ድርጅት አስገንዝቧል። በየቀኑ ከ160ሺህ በላይ አዲስ የቫይረሱ በሽተኞች እየተመዘግቡ መሆናቸውን፣ የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ገልጸዋል። ሀገሮች ዓለምቀፉን ወረርሽኝ ለመታጋል፣ ማድረግ ያለባቸውን ተግባሮች ዘርዝረዋል። “እያንዳንዱ በኮሮና ቫይረስ የሚጠረጠር ሰውን ለይቶ ማቆየት፣ ምርመራ ማካሄድናማከም፣ ከቫይረሱ በሽተኞች ጋር የተነካኩ ሰዎችን ፈልጎ ማግኘት እንደሚያስፈልግ፣ የጤና ሰራተኞችን ማሰልጠንና ለሥራቸው የሚያስፈልጉ ቁሶችን ማቅረብ እንዲሁም ማኅበረሰቦች ራሳቸውን እንዲከላከሉ ማስተማር ግድ እንደሚል፣ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም መክረዋል።የአፍና የአፍንጫ መሽፈኛ ጭምብል ማድረግ ከበሽታው ያድናል ያሉት ዶ/ር ቴድሮስ፣ ኮቪድ-19ኝን የመከላከሉን ተግባር በተሟላ መልኩ የማይፈጽሙ ሃገሮች ከባድ ሁኔታ ይጠብቃቸዋል በማለት አስጠንቅቀዋል።
1
2c3366a2be825acebef80c650a919e8f
1fcd8d655de0514eb7c950b4dae427a3
በዓለም አቀፍ አደገኛ ዕፅ አዘዋዋሪነት የተጠረጠሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 22 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ)በህገወጥ የቴሌኮም ማጭበርበር ድርጊት የተጠረጠሩ 11 ግለሰቦች ከነመሳሪያቸው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የብሄራዊ መረጃ ደህንነት አገልግሎት አስታወቀ፡፡የብሄራዊ መረጃ ደህንነት አገልግሎት ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው ከውጭ አገር ወደ ኢትዮጵያ የሚደረጉ የስልክ ጥሪዎችን በኢትዮ ቴሌኮም ሳተላይት ኔትወርክ በኩል ማለፍ ሲገባቸው ፤ህገወጥ የቴሎኮም መሳሪያዎችን ህጋዊ ፈቃድ ሳይኖራቸው ወደ አገር ውስጥ በማስገባትና ዓለምአቀፍ ጥሪዎችን በመጥለፍ በራሳቸው መሰመሮች ለደንበኞች እያቀረቡ ህገወጥ ድርጊት ሲፈጽሙ የነበሩ ተጠርጣሪዎች ናቸው በቁጥጥር ሰር የዋሉት፡፡ግለሰቦቹም የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ከኢንፎርሜሽን መረጃ መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ጋር በቅንጅት በተደረገ ጥናትና ክትትል ነው ከተለያዩ ሕገወጥ መሳሪያዎች ጋር ሊያዙ የቻሉት ተብሏል፡፡ለዚህ ህገወጥ ተግባር ሲጠቀሙባቸው የነበሩ 11 ጌትዌይ (ሲምቦክስ)፣ 26 ቲፕሊንክ፣ 1 ሺህ 339 ሲም ካርዶች፣ 20 ፍላሽ ዲሰክ፣ 11 ላፕቶፕ እና ሌሎች ህገወጥ የቴሌኮሙኒኬሽን መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ያመለከተው መግለጫው ህገወጥ ድርጊቱ ኢትዮ ቴሌኮምን በአመት እስከ 137 ሚልየን ብር እንደሚያሳጣው ተጠቁሟል፡፡ህብረተሰቡም እንደዚህ አይነት ህግወጥ ተግባራት ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችን ሲመለከተ አካባቢው ለሚገኙ የፀጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠት የተለመደ ትብብራቸውን እንዲያደርጉም ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጥሪ አቅርቧል፡፡የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ከኢንፎርሜሽን መረጃ መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ጋር ከዚህ በፊት በቅንጅት ባደረጋቸው ተከታታይ ኦፕሬሽኖች መሰል የቴሌኮም ማጭበርበር ድርጊቶችን ማስቀረቱ ይታወሳል፡፡
0
9c2232c04cd06b15f634488c8efc836a
080736c6ada565707ebfedb3c4436155
ግብጽ በሲናይ ለተከሰከሰው የሩስያ አውሮፕላን የሽብርተኛ ተግባር ማስረጃ እንዳልተገኘ አስታወቀች
በአማራ ክልል በተጭበረበረ የትምህርት ማስረጃ ሲገለገሉ የቆዩ 322 የመንግስት ሰራኞች በተሰጣቸው የይቅርታ ጊዜ እራሳቸውን ማጋለጣቸውን የክልሉ ሰቪል ሰርቪስና ሰው ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ አወቀ እንየው እንዳስታወቁት በተጭበረበረ የትምህርት፣ መንጃ ፈቃድ፣ የብቃት ማረጋገጫና የሥራ ልምድ ማስረጃዎች በተደራጀ መንገድ የማጋለጥ ስራ እየተከናወነ ነው።በክልሉ በርከት ያለ የተጭበረበረ የትምህርት ማስረጃ መኖሩ በተካሄደ ጥናት በተረጋገጠው መሠረት በዚህ ድርጊት የተሳተፉ ግለሰቦች ከሰኔ 15 ቀን ጀምሮ ባለው አንድ ወር ጊዜ ውስጥ ራሳቸውን እንዲያጋልጡ የይቅርታ ጊዜ ተሰጥቷል፡፡በዚሁ መሠረትም እስከ ሐምሌ 15 ቀን 2009 ባለው ጊዜ 322 ግለሰቦች እራሳቸውን አጋልጠዋል፡፡በተጭበረበረ ማስረጃ የደረጃ እድገትና ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞች ያገኙና በተሠጠው የይቅርታ ጊዜ ተፀፅተው እራሳቸውን ያጋለጡ የመንግስት ሰራተኞች ምንም ዓይነት ቅጣት ሳይወሰንባቸው በሚያሟሉት የስራ መደብ ይመደባሉ ተብሏል፡፡በተጭበረበረ ማስረጃ በቀጥታ የተቀጠሩ ግለሰቦች ግን ቅጥራቸው እንደሚሰረዝ አስታውቀዋል፡፡በአማራ ክልል የተጀመረው ሃሰተኛ ማስረጃዎችን የማምከን ተግባር ቀጣይነት ባለው መንገድ የሚከናወን መሆኑን ገልፀዋል፡፡
0
4ce35d46ccda0aeb2db8caf9ae7a6c5e
4ce35d46ccda0aeb2db8caf9ae7a6c5e
በተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ 69ኛ ጠቅላላ ጉባኤ የመሪዎች ንግግር፤
የተባበሩት መንግስታት ድርድት ዋና ጸሐፊ ባን ኪ ሙን ከኢትዮጽያዉ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ ጋር ኢትዮጵያ በአካባቢ ጉዳዮች ስለምትጫወተዉ ገንቢ ሚና ተነጋግረዋል። ዋና ጸሀፊዉ ኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳን ተፋላሚ ወገኖችን በመሸምገል እንዲሁም በሶማሊያ ሰላም እንዲሰፍን ለምታደርገዉ ተሳትፎ አመስግነዋል።በምእራብ አፍሪቃ ኢቦላ ከተሰፋፋባቸዉ አገሮች የጊኒ ፕሬዚደንት ወረርሺኙ አገራቸዉ ላይ እያደረሰ ያለዉን የኢኮኖሚ ቀዉስ ጠቅሰዉ ተናግረዋል። የአይሲል ሰፊ ግዛት የያዘባትና ዓለምአቀፍ ሥጋት የሆነባት የኢራቅ ፕሬዚዳንት እና ከመካከለኛው ምሥራቅ ውጥረት ተዋንያን የአንዷ ግዛት የፍልስጥዔም ፕሬዚዳንት እንዲሁም ተሰናባቹ የናሚቢያ ፕሬዚዳንትም የሃገራቸውን የሚሌኒየም የልማት ግቦች የስኬት ታሪክ፣ የአፋሪካን የኢቦላ፣ የፀጥታና የአየር ንብረት ፈተናዎች አንስተዋል፡፡ ዝርዝሩን ከዘገባው ይከታተሉ።
1
62e00f1faea646ca77e204a6e387a4fe
62e00f1faea646ca77e204a6e387a4fe
ኢትዮጵያና አየርላንድ ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማሳደግ እየሰሩ መሆናቸውን ገለጹ
ኢትዮጵያና አየርላንድ የቆየ ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማሳደግ እየሰሩ መሆናቸውን ገለጹ።አየርላንድ በኢትዮጵያ የልማት ሥራዎችን በመደገፍ የጀመረችውን ተሳትፎ አጠናክራ እንደምትቀጥልም ገልፃለች።ፕሬዚዳንት ሙላቱ ተሾመ የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁት በኢትዮጵያ የአየርላንድ አምባሳደር ኤዲያን ኦሃራን ትናንት በብሔራዊ ቤተ-መንግሥት አሸኛኘት አድርገውላቸዋል።ፕሬዝዳንት ሙላቱ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት ኢትዮጵያና አየርላንድ ሁለንተናዊ ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማሳደግ እየሰሩ ነው።አየርላንድ ኢትዮጵያ ውስጥ የልማትና ሰብዓዊ ድጋፍ በማድረግ አጋርነቷን በተግባር ያስመሰከረች መሆኗንም ገልጸዋል።ይህን የልማት ትብብር አጠናክራ በመቀጠል በሰው ኃይል ልማት መስክ ድጋፍ እንድታደርግ በኢትዮጵያ በኩል ፍላጎት መኖሩን ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል።አምባሳደር ኤዲያን ኦሃራ በበኩላቸው አየርላንድ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ከ1984 ጀምሮ ለኢትዮጵያ ድጋፉዋን ስታደርግ ቆይታለች።በተለይ ሰብዓዊ ድጋፍ በማድረግና ከኢትዮጵያ የልማት ፍላጎት ጋር በሚጣጣሙ ፕሮጀክቶች ላይ ንቁ ተሳትፎ እያደረገች መሆኗን ገልጸዋል።አምባሳደሩ ባለፉት አራት ዓመታት በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ የሁለቱ አገራት ንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነት ለማጎልበት ጥረት ማድረጋቸውንም አንስተዋል።በተለይ ተደራራቢ ታክስን በማስቀረት የአገራቱን ንግድና ኢንቨስትመንት ፍሰት ለማሳለጥ ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸውን ተናግረዋል።በአሁኑ ጊዜ አየርላንዳውያን ባለሃብቶች ኢትዮጵያ ውስጥ አበባን በማምረትና ምግብን በማቀነባበር ሥራ እየተሳተፉ መሆናቸውን በማሳያነት ጠቅሰዋል።በቅርቡ በአገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች በተከሰተው ሁከት በአየርላንዳውያን ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ይዞታዎች ላይ ጉዳት መድረሱንም ተናግረዋል።ድርጊቱ አገራቸው ከምታደርገው ተሳትፎ የማያግዳት በመሆኑም በቅርቡ ተጠግነው የተሻለ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምሩ አምባሳደሩ አረጋግጠዋል።አየርላንድ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ 1994 ኤምባሲዋን ኢትዮጵያ ውስጥ ከፍታ እየሰራች ትገኛለች።(ኢዜአ)
1
649a5d4207f5552ee181c788d7fe2d20
5b0a44c7bfa1b053b73c77cdf0331636
ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ከጀርመን አምባሳደር ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ ፣ ህዳር 11 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በታንዛኒያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ዮናስ ዮሴፍ መቀመጫቸውን በታንዛኒያ ካደረጉ የተለያዩ ሃገራት አምባሳደሮች ጋር ተወያዩ።አምባሳደር ዮናስ በታንዛኒያ ከኳታር፣ የተባበሩት ዓረብ ኢሚሬቶች፣ አልጀሪያ እና ከአውሮፓ ህብረት ተወካዮች ጋር ተወያይተዋል።በውይይታቸው ወቅትም መንግስት በትግራይ ክልል እየወሰደ ስላለው ህግን የማስከበር ዘመቻ በተመለከተ ለአምባሳደሮቹ ገለጻ አድርገውላቸዋል።በዚህ ወቅትም ለእርምጃው መንስኤ ስለሆኑ ምክንያቶች፣ አጠቃላይ ሁኔታው እና የእርምጃውን ግብ በተመለከተ ገለጻ ማድረጋቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
0
80b0c0a38391ca51fef00ce4ce996acd
e84222a790df9b152478916801bc61e8
በኮምቦልቻ ከተማ እስከ አምስት ኮከብ የሚኖራቸው ስድስት ሆቴሎች ሊገነቡ ነው፡፡
አዲስ አበባ:- የአዲስ አበባ ሆቴል ባለቤቶች ንግድ ዘርፍ ማህበር በአዲስ መልክ ለሦስተኛ ዙር ያሳተመውን የሆቴልና ከተማ መመሪያ ይፋ አደረገ።መመሪያው በአዲስ አበባ ከተማ የቱሪስት ፍሰትን ለመጨመር እንዲሁም የማህበረሰቡንና የሀገርን ገቢ ከፍ ለማድረግ የሚጠቅም መሆኑ ተገለጸ።የማህበሩ ሥራ አስኪያጅ አቶ ቢኒያም ብስራት ማህበሩ ያሳተመውን የሆቴልና ከተማ መመሪያ አስመልክተው ትናንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣መምሪያው 120 ባህላዊና ዓለም አቀፍ ሆቴሎችን ጨምሮ በአዲስ አበባና አካባቢዋ የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎችን ከነስማቸው በዝርዝር የያዘና ስለሚሰጡት አገልግሎት የተሟላ መረጃ ያለው መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ሥራ አስኪያጁ እንዳብራሩት፤ይህ ሦስተኛው የአዲስ አበባ ከተማና ሆቴሎች ቱሪስት መመሪያ ባለፉት ጊዜያቶች ካዘጋጇቸው በብዙ መልኩ የተሻሉና የቱሪስት ፍሰቱንም የሚጨምር ሲሆን፣ ጎብኚዎች በከተማዋ የሚኖራቸው ቆይታ እንዲጨምር ያስችላል፡፡በተጨማሪም በከተማዋ የኮንፈረንስ ቱሪዝም እንዲያድግ የተለያዩ ለኮንፈረንስ ቱሪዝም የሚሆኑ ሀብቶች በማስተዋወቅ ትልቅ ሚና ይጫወታል።መመሪያው በድረ-ገጽ ለሁሉም ተደራሽና ከዚህ ቀደም ከነበረው በአጠቃቀም የተለየ መሆኑም በመግለጫው ተመልክቷል፡፡የከተማ መመሪያ በየዓመቱ እንደሚዘጋጅና ከዓመት ዓመት ደረጃውን በጠበቀና ጥናቶችን በማካተት እየተሻሻለ የሚቀርብ እንዲሁም የቱሪስት ፍሰቱ በሀገሪቱ እንዲጨምር አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑም ተገልጿል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 12/2011በሰሎሞን በየነ
0
b09729df439fa143cf21520e85c0bebf
714763f7ea9462e7854a3fd90fc457c3
ኢትዮጵያ ዘጠኝ መርከቦችን ተረከበች
ዋና ፅሕፈት ቤቱ ኒው ዮርክ የሚገኘው በእግሊዝኛ መጠሪያው Committee to Protect Journalists ወይም ከስሙ ምኅፃር ሲፒጄ እየተባለ የሚታወቀው ዓለምአቀፉ የጋዜጠኞች ደኅንነት ተሟጋች ድርጅት ሃሣብን የመግለፅ ነፃነት እንዲጠናከር ስላበረከቱት አስተዋፅዖ የዞን ዘጠኝ ፀሐፊዎችን ሸልሟል፡፡ሲፒጄ ዞን ዘጠኞችን ለሽልማት ማብቃቱን ያሳወቀው የመገናኛ ብዙኃን ነፃነት የዘንድሮ ተመራጮቹን ይፋ ሲያደርግ ሲሆን ዞን 9ኞችን ያጫቸው የመናገር ነጻነት በኢንተርኔት እንዲስፋፋ ላበረከቱት አስተዋፅዖ ነው።የዞን ዘጠኝ ፀሀፊዎች በዌብ ሳይታቸው ሕገመንግሥታዊ መብቶች እንዲከበሩ የሚሟገቱ ሲሆን በፀረ-ሽብ ሕጉ ህዝብን በማነሳሳት በኢትዮጵያ መንግሥት ክሥ ተመሥርቶባቸዋል፡፡ሁለቱ ፀሀፊዎች በፍትህ ምኒስቴር ክሳቸው ተቋርጦ የተፈቱ ሲሆን አራቱ አሁንም ታስረው ሦስቱ ስደት ላይ ይገኛሉ።ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች ደኅንነት ተሟጋች ቡድን - ሲፒጄ ለእነዚህ ወጣት የኢንተርኔት የመናገር ነፃነት ተሟጋቾች ከሌሎች ሦስት ጋዜጠኞች ጋር ዓለም አቀፉን ሽልማት የሰጠው መረጃ ለማድረስ በሙያቸው በጀግንነት ስላበረከቱት አስተዋፅዖ ነው።የስፒጄ የአፍሪካ ፕሮግራም አስተባባሪ ሱ ቫለንታይን ለቪኦኤ በሰጡት ቃል “ሽልማቱ ለዞን ዘጠኝ ፀሐፊዎች ሥራ ዕውቅና ይሰጣል፤ በአፍሪካ በማኅበረሰብ መገናኛ ብዙኃንና በዌብ ሳይቶች አማካይነት የመናገር ነፃነትን ለማስፋፋት የሚጫወቱትን ቁልፍ ሚና ያጎላል፤ በየሀገሮቹ ያሉ መረጃዎችን ለህዝብ ለማድረስ ዌብ ሳይቶች ያላቸውን ድርሻ ያሳያል” ብለዋል፡፡ከዞን ዘጠኝ በተጨማሪ ማሌዢያዊ የስላቅ ሰዓሊ ዙናር፣ ፓራጓያዊው ጋዜጠኛ ካንዲዶ ፊሁረዶ ሩዪዝ፣ ሶሪያዊው ቡድን ራቃ የዘንድሮው ሃሣብን የመግለፅ ነፃነት ተሸላሚዎች ሆነዋል።ሁሉም በዓለም ዙሪያ መረጃ የማግኘት ነፃነት፣ ሃሣብን የመግለፅ ነፃነት፣ የመገናኛ ብዙኃን ነፃነት እንዲከበር የሚሠሩ ባለሙያዎች መሆናቸውን ሲፒጄ አመልክቷል።
0
ded4e7fb88ddcfd4dda2874dc86a3f40
001d1beb40ae9c57ab51bd974bec21fc
የሶማልያ ጥቃት
የማስታወቂያ ሚኒስትሩ የማነ ገብረመስቀል ጉብኝቱን አስመልክተው በትዊተር መልዕክታቸው ሲገልጹ፣ “የኤርትራና ሶማልያ ግንኙነት፣ በወዳጅነት፣ በመከባበርና በአብሮነት ላይ የተመሠረተ ነው” ብለዋል።ይህ የዛሬው የፕሬዚዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ የሶማልያ ታሪካዊ የተሰኘ ጉብኝት፣ “የአትዮጵያ፣ የኤርትራና የሶማልያ መሪዎች ከሦስት ወራት በፊት አሥመራ ላይ ያደረጉት የሦስትዮሽ ምክክር አካል ነው” ተብሏል።የኤርትራው መሪ ዛሬ ሞቃዲሾ ሲገቡ የፀጥታ ጥበቃው በከፍተኛ ደረጃ የተጠናከረ እንደነበር ተዘግቧል።የሁለቱ ሃገሮች መሪዎች ተገናኝተው የተነጋገሩ ሲሆን፣ ፕሬዘዳንት ኢሳይያስ ቀጥሎ ወደ ኬንያ እንደሚያመሩ ተዘግቧል።
0
7f227e14f61db015e472ba5156b6f1e4
1d1dfd622617d17547d07694f552c7f6
ከደምበል ሃይቅና ከቆቃ ሃይል ማመንጫ ግድብ እንቦጭን የማስወገድ ዘመቻ ተጀመረ
Turkishweekly የተባለው በቱርክ የሚወጣ ድረ-ገጽ ኢትዮጵያ እአአ በ 2025 አም (ከ 10 አመታት በኋላ ማለት ነው) ከአለም አቀፍ የጠረፍ ጣብያ ጋር የመቀላቀል እቅድ አላት በሚል ርእስ ባቀረበው ጽሁፍ የኢትዮጵያ መንግስት በጠፈራ ሳይንስ ምርምርና በልማት የሚመደበውን መዋዕለ ነዋይ ከፍ እያደረገ ነው ይላል።በኢትዮጵያ የመጀመርያው የጠፈር ምርምር ማዕከል እስከ 2025 አም ባለው ጊዜ በአስር አመታት ውስጥ ማለት ነው ሳተላይት ለማምጠቅ ሲዘገጅ እንደቆየ ገልጿል።ማዕከሉን ከሶስት አመታት በፊት እንጦጦ ተረራ ላይ የመሰረተው የኢትዮጵያ የጠፈር ሳይንስ ማህበር እንደሆነ Turkis hweekly የተባለው ድረ-ገጽ ዘግቧል። --------የኢትዮጵያው የጠፈር ማህበር ከ 11 አመታት በፊት የተመሰረተው ከተለያዩ የሳይንሳ ዘርፎች በተሰባሰቡ ወዶ-ገቦች እንደሆነ አላማውም ስለጠፈርና ስለሳይንስ ጉዳዮች ህዝብን ለማንቃት እንደሆነ ድረ-ገጹ በዘገባው ጠቅሷል።Gulf Times የተባለ በቓታር የሚታተም እለታዊ ጋዜጣ ድረ-ገጽ በበኩሉ አዳማ ስላለው የነፋስ መብራት ሃይል ማመንጫ ጣብያ ሲዘገብ አዳማ የሚገኙት አለታማ ኮረብታዎች ነፋስ በሚባዛባት አከባቢ ከአህጉሪቱ ግዙፍ ከሚባሉት የነፋስ የመብራት ሃይል ማማንጫ ቦታዮች መሆናቸውን ይገልጻል።ባለፈው ወር በአዳማ የተጀመረው በነፋስ የኤለክትሪክ ሃይል ማመንጫ ተቋም የ 153 ሜጋዋት የመብራት ሀይል የማንጨት ብቃት አለው። ይህም ከሰሀራ በመለስ ካሉት በነፋሰ የመብራት ሃይል ማመንጫ ጣብያዎች ግዙፉ እንዲሆን ኢትዮጵይ ካሉት ሶስት ግዙፍ የነፋስ ማመንጫ ሃይሎችም አንዱና አዲሱ ያደርገዋል ሲል፣ Gulf Times ድረ ገጽ ጠቁሟል። --------የ New York Times ጋዜጣ ድረ-ገጽ ደግሞ በአፍሪቃ ያለው የኤለክትሪክ መብራት ማሰራጫ መረብ ድክመት የአህጉርዋን ኢኮኖሚ እያጫጨ ህዝቡንም እያበሳጨ ነው ሲል ባቀረበው ጽሁፍ ከሰሃራ በመለስ ያሉት የአፍሪቃ ሀገሮች አጠቃላይ የመብራት ሃይል ማመንጫ አቅም ከደቡብ ኮርያ ያነሰ ነው። ካለው የአፍሪቃ የመብራት ሃይል ማመንጫ መጠንም በመሰረተ-ልማቶች መቆርቆዝ ምክንያት አንድ አራተኛው አይሰራም ይላል። ሙሉውን ዘገባ ያድምጡ።
0
a396f3e701678bc1cf5c3221d9eb8440
bd57a7567b4b85e287218c7db1c3bd8c
የሰብዓዊ መብት ኮሚሽነሩ ከአገር አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ተወያዩ
በተለያዩ የአገሪቱ ጉዳዮች ላይ ድርድር ሲያደርጉት የቆዩት አስራ ስድስት የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በፀረ-ሽብር ህጉ ላይ ድርድር እያካሄዱ መሆኑ ተገለጸ ። ለወራት ያህል በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ሲወያዩ የቆዩት ፓርቲዎቹ ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ባልተቀበላቸው ነጥቦች ላይ መደራደራቸው ቀጥለዋል፡፡የፀረ ሽብር ህጉ ከህገ መንግስት ጋር የሚቃረን እና የዜጎችን ሰብአዊ መብት የሚጋፉ አንቀጾች ያሉት መሆኑን የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በዛሬው ዕለት ባደርጉት ውይይት የገለጹ ሲሆን ህጉ አስፈላጊ ቢሆንም ሊሻሻሉ እና ሊሰረዙ የሚገባቸው አንቀጾች አሉት የሚል ሐሳብ አቅርበዋል፡፡ የፀረ ሽብር ህጉ የሰብአዊ መብት ተማጓቾችን እና የጋዜጠኞች በነጻነት የመሥራት መብት ማዳከሙን የተቃዋሚ ፓርቲዎቹ በዛሬው ዕለት ባደረጉት ውይይት ጠቁመዋል ፡፡የገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ በበኩሉ ከአሁን በፊት የፀረ ሽብር ህጉ የዜጎችን እና የሀገርን ደህንነት ለማስጠበቅ ፋይዳው ከፍተኛ በመሆኑ ህጉ ላይ የሚደረግ ማንኛውንም ማሻሻያዎችን እንደማይቀበል ማስታወቁ ይታወሳል ፡፡በዛሬው ዕለት ተደራዳሪ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ያቀረቡትን የማሻሻያ ሓሳቦችን ኢህአዴግ በድርድሩ መቀበሉንና አለመቀበሉን የሚታወቀው በአጠቃላይ በሚሠጠው ምላሽ የሚገለጽ መሆኑን ተመልክቷል ።
0
e8856f65b880a657c4fd6744edb899ef
e8856f65b880a657c4fd6744edb899ef
የኢትዮጵያው አውሮፕላን አደጋ ረቂቅ ሪፖርት ቦይንግን ተጠያቂ አደረገ
ከአንድ ዓመት በፊት የተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን አደጋ ምክንያት የአውሮፕላኑ የዲዛይን ችግር እንደሆነ መርማሪዎች ለአሜሪካ መንግሥት መስሪያ ቤቶች ያዘጋጁት የአደጋው ረቂቅ ሪፖርት አመለከተ። ሮይተርስ እንደዘገበው የአሜሪካ ብሔራዊ የትራንስፖርት ደህንነት ቦርድ በረቂቅ ሪፖርቱ ላይ ቅሬታ ወይም እንዲለወጥ የሚያቀርበው ሃሳብ ካለው ዕድል እንደተሰጠው፤ ሪፖርቱ ይፋ ስላልተደረገ ማንነታቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ ሰዎች ተናግረዋል። የቦርዱ ቃል አቀባይ ኤሪክ ዌይስ ጊዜያዊው ረቂቅ ሪፖርትን እንደተቀበሉ ቢገልጹም ድርጅታቸው ለውጥ እንዲደረግ ይጠቅ እንደሆነ አስተያየት ከመስጠት ተቆጥበዋል። ቦይንግ ሪፖርቱን በተመለከተ ምላሹ ምን እንደሆነ በሮይተርስ ቢጠየቅም ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል። ረቂቅ ሪፖርቱን ቀድሞ ይፋ ያደረገው ብሉምበርግ ኒውስ እንዳለው የሪፖርቱ ማጠቃለያ ስለኢትዮጵያ አየር መንገድም ሆነ የበረራ ሰራተኞቹ አሰራርን በተመለከተ ውስን ወይም ምንም ነገር ባለማለቱ በምርመራው ላይ በተሳተፉ አንዳንድ ሰዎች ዘንድ ጥያቄን አስነስቷል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት በነበረው አውሮፕላን ላይ የደረሰውን አደጋ በተመለከተ የተዘጋጀው ረቂቅ ሪፖርት፤ በአውሮፕላኑ የበረራ መቆጣጠሪያ ሶፍትዌር ላይ በነበረ ችግርና በአብብራሪዎች ስህተት እንደተከሰከሰ በተነገረለት በተመሳሳዩ የኢንዶኔዢያው የላየን ኤር አውሮፕላን ሪፖርት ጋር መነጻጸሩ ተገልጿል። ከአንድ ዓመት በፊት ወደ ጎረቤት አገር ኬንያ ለመጓዝ ከአዲስ አበባ ከተነሳ ከስድስት ደቂቃዎች በኋላ የተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን የበረራ ቁጥር 302 የአውሮፕላኑ ሰራተኞችን ጨምሮ 157 ሰዎች ሞተውበታል። ከዚህ አሰቃቂ አደጋ በኋላም በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖች ከበረራ ውጪ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የበላይ ተቆጣታሪነት ስር ካናዳ ሞንትሪያል በሚገኘው የአቪዬሽን ኤጀንሲ ደንብ መሰረት፤ ኢትዮጵያ አደጋውን በተመለከተ የመጨረሻውን ሪፖርት በአደጋው አንደኛ ዕለት ይፋ ማድረግ ይኖርባታል። 32 ኬንያዊያን፣ 18 ካናዳዊያን፣ 18 ኢትዮጵያዊያንን ጨምሮ የ33 አገራት 157 ዜጎች ህይወታቸው ያለፈበትን የዚህን አደጋ አንደኛ ዓመት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመጪው ማክሰኞ አስቦት እንደሚውል ቢቢሲ አረጋግጧል።
1
040fbd0394e82091e7d9dc84b49a7a08
4b751b2cab07a2f6b12ec3fe832819c6
የካሜሩኑ ፕሬዚዳንት ፖል ቢያ ለተጨማሪ የሥልጣን ዘመን ይወዳደራሉ
የአንጎላው ፕሬዚዳንት ዣኦ ሎሬንኮ ከአንድ ዓመት ባላይ በሆነው የሥልጣን ጊዚያቸው ሙስናን ለማቆም ባደረጉት ጥረት ካለፉት የሀገሪቱ አስተዳደሮች የተሻለ ስኬት አስገኝተዋል ሲሉ መንግሥቱን አጥብቀው የሚነቅፉት ሳይቀሩ ተናግረዋል።ሎሬንኮ ባለፈው ዓመት መስከረም ወር ላይ ሥልጣን የያዙት የረዥም ጊዜ ፕሬዚዳንት የነበሩት ጆሴ ኤድዋርዶ ዶስ ሳንቶስ ጡረታ ከወጡ በኋላ ነበር። የቀድሞው ፕሬዚዳንት ቤተሰቦችና ወዳጆች እያንዳንዱን ወሳኝ ኩባንያንና የሀገሪቱን የኃብት ምንጮችን ይቆጣጠሩ እንደነበር ተዘግቧል።ሎሬንኮ ሥልጣን ላይ ከወጡ በኋላ ግን በዶስ ሳንቶስ አስተዳደር ወቅት የማይነኩ ተደርገው ይታዩ የነበሩት በርካታ ከፍተኛ ባለሥልጣኖችን እንደጠራረጉ ታውቋል። ዋናው ተጠቃሽ ምሳሌ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ልጅ ፊሎሜኖ በገንዘብ ማጭበርበርና በገንዝብ ዝውውር ተከሰው በያዝነው ሳምንት ታስረዋል። ሶቨሪን ዌልት ፋንድ የተባለውን ባንክ ይመሩ ነበር።
0
7211d8e4db3bcad504abe97d0e4e722a
ab84dce770195e68c934eabd8234f620
የቻይናው ግዙፍ የጨርቃጨርቅ ኩባንያ በኢትዮጵያ የጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ፓርክ የማቋቋም እቅድ እንዳለው ገለጸ
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 14፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከቻይናው ሲሲ.ኢ.ሲሲ (CCECC) ኩባንያ ጋር የኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ ስምምነት ተፈራረመ።ስምምነቱንም የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አህመድ ቡህ እና የሲሲ.ኢ.ሲሲ ኩባንያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጉዎ ቾንግፌንግ ትናንት በድሬዳዋ ከተማ ተፈራርመዋል።በትናንትናው እለት የተፈረመው ስምምነት በከተማዋ የቻይናው ሲሲ.ኢ.ሲሲ (CCECC) በመጀመሪያ ዙር በ370 ሄክታር መሬት ላይ የኢንዱስትሪ ፓርክ ለመገንባት የሚያስችለው መሆኑን የድሬደዋ ከንቲባ ዕህፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።የቻይናው ሲሲ.ኢ.ሲሲ በድሬዳዋ መልካጀብዱ አካበቢ 1 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የራሱን የኢንዱስትሪ ፓርክ ገንብቶ የቻይና በተለይም የድሬዳዋ እህት ከተማ ከሆነችው የኩንሻን ከተማ ባለሀብቶችን ለማምጣት አቅዶ እየሰራ መሆኑም ተገልጿል።አሁን የተደረሰው የ370 ሄክታር መሬት ስምምነት የመጀመሪያ ዙር እንደሆነ በፊርማ ስነስርዓቱ ወቅት ተገልጿል።በአጭር ጊዜ ውስጥ የመሬት ርክክቡ ተጠናቆ የግንባታ ስራው እንደሚጀመር በሚጠበቀው የኢንዱስትሪ ፓርክ ከግንባታው ጀምሮ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እንደሚፈጥር ይጠበቃል።የአካባቢው ነዋሪዎችን ጨምሮ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ለስራው መቀላጠፍ የበኩላቸውን አዎንታዊ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ በፊርማ ስነ ስርዓቱ ወቅት ጥሪ ቀርቧል።ከዚህ በፊት ምክትል ከንቲባ አህመድ ቡህ የድሬዳዋ እህት ከተማ በሆነችው ኩንሻን ከተማ ባደረጉት ጉብኝት ሁለቱ ከተሞች በቀጣይ የሚኖራቸውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ግንኙነት በተለይም የሲሲ.ኢ.ሲ.ሲ ኩባንያ የኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታን ለማስጀመር እና ኢንቨስትመንትን በተጠናከረ ሁኔታ ለማስቀጠል የሚያስችል ውይይት ማድረጋቸው ይታወሳል።
0
d6d48415e33a247fc3825e656c2c78c9
3e37025687b98234b39ca2db36e0bc8d
የዓለም ስደተኞች ጉባዔ በስዊዝ እየተካሄደ ነው
የዓለም የአየር ንብረት ከሚገባው በላይ እንዲሞቅ ምክንያት የሆኑትን ሰው ሰራሽ ችግሮችን በመቃወም የሚደረግ ከዚህ ቀደም ያልታየ ብዛት ያለው ሰልፍ እንደሚሆን ተገልጿል።የዛሬው ሰልፍ የተጀመረው በእስያ ዙርያ ሲሆን በብዙ መቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎችና ሌሎችም ተሳትፈውበታል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ስለጉዳዩ ለመነጋገር ጉባዔ ከመጀምሩ በፊት በአየር ንብረት ለውጥ ላይ ዕርምጃ እንዲወሰድ ጥሪ ለማደረግ ነው ሰልፎች የሚካሄዱት።አውስትራሊያ ላይ ብቻ በአንዳንድ የአከባቢ ባለሥልጣኖች፣ በትምህርት ቤቶችና በንግድ ተቋማት የተደገፉ 300,000 የሚሆኑ ልጆችና ጎልማሶች ተሰልፈዋል። በሀገሪቱ ታሪክ የተደረገ ትልቁ የአየር ሙቀት ተቃውሞ ነው ተብሏል።በዩናይትድ ስቴትስም ሰልፎች እየተካሄዱ ነው። አስተባባሪዎች እንደሚሉት ከ800 በላይ ሰልፎች እንዲካሄዱ ታቅዷል።አፍሪካ ውስጥ ደግሞ በናይሮቢ ኬንያ እንዲሁም በደቡብ አፍሪካ ከተሞች ጆሀንስበርጋና ፕሪቶርያ ፀረ የአየር ንብረት ሙቀት ሰልፎች ተካሂደዋል። አፍሪካ ከሁሉም በላይ የአየር ለውጥ ለሚያስከትለው ችግር የተጋለጠች መሆኗን የመከላከል አቅሟ ዝቅተኛ መሆኑ ተገልጿል። በሌሎች በርካታ ሀገሮችም ሰልፎች ተካሂደዋል።
0
d52772a9c0322e1318548db800fabd61
29708e6d31012389db52779830de8da8
የኦሮሚያ ትራንስፖርት ባለስልጣን በአዳማ የትራፊክ ኮምፕሌክስ የባለሙያዎችን ብቃት የማረጋገጥ ስራ እያከናወነ ነው
አዲስ አበባ፣ ህዳር 9፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በአራት ወራት ውስጥ 245 ኪሎ ሜትር ልዩ ልዩ የመንገድ ጥገና ስራዎችን ማከናወኑን አስታወቀ፡፡ባለስልጣኑ ለትራፊክ እንቅስቃሴ አስቸጋሪ የሆኑ ዋና ዋና፣ የቀለበት መንገድ እንዲሁም የውስጥ ለውስጥ እና አቋራጭ መንገዶችን የጉዳት መጠናቸውን በመለየት የጥገና ስራዎችን በስፋት እያከናወነ እንደሚገኝ ነው የገለፀው።በዚህም በአራት ወራት ውስጥ 13 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ፣ 220 ኪሎ ሜትር የድሬኔጅ መስመሮች ጽዳትና ጥገና፣ 9 ኪሎ ሜትር ጠጠር (አክሰስ) መንገድ፣ 3 ኪሎ ሜትር የእግረኛ መንገድና ከርቭ ስቶን የጥገና ስራዎች ተከናውኗል ነው ያለው ባለስልጣኑ፡፡በተጨማሪም በዘርፈ ብዙ የመንገድ ጥገና ስራዎች ውስጥ በቁጥር 889 የተበላሹ የመንገድ መብራቶች ጥገና የተደረገላቸው ሲሆን 220 አምፖሎች በአዲስ የመየቀር ስራ እንዲሁም ድልድይና የድጋፍ ግንብ፣ የእግረኛ መከላከያ አጥር የጥገና ስራዎችም ተከናውነዋል ተብሏል፡፡ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በ2013 በጀት ዓመት ከ525 ኪሎ ሜትር በላይ በተለያዩ ምክንያቶች ለብልሽት የተዳረጉ የአስፋልትና ሌሎች መንገድ የጥገና ስራዎችን ለማከናወን በዕቅድ የያዘ ሲሆን ይህም የከተማዋን መንገዶች ለእንቅስቃሴ ምቹ እና የትራፊክ ፍሰቱ የተሳለጠ እንዲሆን ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተጠቁሟል።
0
f6cac65d0e16da523b7be54d649c42a7
fa193496e6b534f601f7718efc94b8e0
በአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ እና ፈረሰኞቹ መካከል ድርድር ተካሄደ
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አዲሱ አሰልጣኝ በይፋ የሚገለፅበት ቀን እየራቀ ሃገሪቱም ካለ ብሄራዊ ቡድን 2 ወራትን አስቆጥራለች፡፡ ከፌዴሬሽኑ የሚወጡ ጭምጭምታዎች እንደሚያመለክቱት ግን ፌዴሬሽኑ ምርጫውን እንደጨረሰና ጎራን ስቴፋኖቪች በአሰልጣኝነት እንደተሾሙ እየተነገረ ነው፡፡ፌዴሬሽኑ ከ27 አመልካቾች ውስጥ የመጨረሻ 5 እጩዎችን መለየቱን ተከትሎ አርብ እለት የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ይታወቃል ተብሎ ቢጠበቅም የቴክኒክ ኮሚቴው ከ5ቱ እጩዎች ጋር ሊያደርግ ያሰበው የስካይፒ ቃለመጠይቅ በኢንተርኔት ኔትዎርክ ችግር ምክንያት ተራዝሟል፡፡አሰልጣኞቹን የመምረጥ ሃላፊነት የተሰጠው የቴክኒክ ኮሚቴው በመጀመርያ ካመለከቱት 27 አሰልጣኞች 10ሩን ቀጥሎን 10ሩን ኋላ ላይ ደግሞ 5ቱን ያስቀሩ ሲሆን አሰልጣኝ ዲዬጎ ጋርዚያቶ ከ5 እጩዎች ወጥተው አሁን ለመጨረሻ እጩነት የቀረቡት አሰልጣኞች ቁጥር 4 ደርሷል፡፡ የደሞዝ ድርድር ከተካሄደ በኋላ የሚመረጠው አሰልጣኝም ሰኞ ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል፡፡{jcomments on}
0
2f4895f96f5cbb9e24b93b9258d2c235
f5d0dea1e04b4da69572c9076773a748
የመስቀል እና የእሬቻ በዐል በሰላም እንዲከበር አስተዋፅዖ ላበረከቱ ዕውቅና ተሰጠ
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የቤተክርስቲያኗን አንድነት ለማምጣት ያደረጉትን አስተዋፅዖ ያደነቁት የባህር ዳር ሀገረስብከት ሊቀ-ጳጳስ አቡነ አብርሃም በዚህ ረገድ ያደረጉትን አስተዋፆ እንዲቀጥሉና አሁንም ቤተክርስቲያኗን እንዲታደጉ መልዕክት አስተላልፈዋል።በተመሣሣይ ሁኔታም በሰሜን ሸዋ፣ ደቡብ ወሎና ሰሜን ወሎም ወረኢሉ፣ መቅደላ፣ አምባሰል፣ ወልድያ፣ ላሊበላና ደብረብርሃንን ጨምሮ ከሃያ በላይ ከተሞች ውስጥ ሰልፎች መደረጋቸውንና ሁሉም በሰላም መጠናቀቃቸው ታውቋል።
0
e5215d634f3a2d19dee8d5df4f6ed469
fa72cac38e175974b0320d3476406045
ዶናልድ ትራምፕ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ የሰጡት አስተያየት ከእርሳቸው የማይጠበቅ ነው – ሴናተር ጄሰን ክሮው
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 152005 ( ዋኢማ) – የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም በግብፅ ጊዜያዊ መንግስት አዲስ ከተሾሙት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ናቢል ፋህሚ ጋር በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ተወያዩ።የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ በስልክ ባደረጉት ውይይት በግድቡ ዙሪያ ከኢትዮጵያ ፣ ሱዳንና ግብፅ ባለሙያዎች የተካተቱበት አለም ዓቀፍ የባለሙያዎች ቡድን የጥናት ውጤት አስተያየት ላይ መነጋገራቸው ታውቋል።በሌላ በኩል የቀድሞ የግብፅ የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስተር ሞና ኡመር ከጠቅላይ ሚኒስትር ሐይለማርያም ደሳለኝ ጋር ለመምከር ዛሬ አዲስ አበባ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
0
6bbdcf0f806e6ec90c79fc269660e639
f73ddb05d7549a48bdab21ae336b3812
ባለፉት 3 ዓመታት የእናቶችና ህጻናት ጤና አገልግሎት መሻሻል ታይቶበታል – ጤና ሚኒስቴር
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 11፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)የጠዳ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በዲፕሎማ መርሃግብር በህክምና ሙያ ያሰለጠናቸውን 579 ተማሪዎችን አሰመረቀ።ኮሌጁ በ14ተኛ ዙር በዲፕሎማ መርሃ ግብር በህክምና ያሰለጠናቸውን 579 ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡የኮሌጁ ዲን አቶ ዘመነ ሀብቱ ኮሌጁ በህክም ዘርፍ ብቃት ያላቸውን የህክምና ባለሙያዎች እያሰለጠነ ለጤና ስራው መሻሻል እገዛ እያደረገ ነው ብለዋል።በ14ተኛ ዙር 579 ተማሪዎችን በሰባት የሙያ ዘርፎች በዲፕሎማ ደረጃ ያስመረቀው ኮሌጁ ሁሉም ተማሪዎች የሙያ በቃት ምዘናን ያለፉ መሆናቸውን ዲኑ ገልጸዋል ።ኮሌጁ ለመጀመሪያ ጊዜ በአካባቢ ጤና ሙያ 81 ተማሪዎችን ያስመረቀ መሆኑን የተናገሩት አቶ ዘመነ ኮሌጁን ወደ ዩንቨርስቲ ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አብዱልከሪም መንግሥቱ የክልሉን የጤና ሽፋን ለማሳደግ በተደረገው ጥረት 82 ሆስፒታሎች 864 ጤና ጣቢዎችና 3ሺህ938 የጤና ኬላዎች አገልግሎት በመሰጠት ላይ ናቸው ብለዋል።በጤናው ዘርፍ የባለሙያዎች ዕጥረት እንዳይኖር በክልሉ 5 የጤና ሳይንስ ኮሌጆች ብቁ የሆኑ የጤና ባለሙያዎችን በማሰልጠን ቁልፍ ተግባር እየፈፀሙ መሆናቸውም ተነግረዋል።ሀላፊው ለተመራቂዎች በሰጡት የስራ መመሪያ እንደገለፁት በቀጣይ በጤናው ዘርፍ የታቀዱ አጀንዳዎችን ለማሳካት የዛሬ ተመራቂ ተማሪዎች ሙያዊ ሀላፊነታቸውን እንድትወጡ ሲሉም ጠይቀዋል።በምናለ አየነው
0
6246656b6d81a1c735a60de00b00632d
dbf9b17e383f25bd704e17f896e0a0fd
ለኢራን ይሰልል ነበር የተባለ ጥምር ዜግነት ያለው ግለሰብ ታሰረ
የአልቃይዳ መስራች ኦሳማ ቢን ላደን ወንድ ልጅ ሀምዛ ቢን ላደን፣ መሞቱን የአሜሪካ የስለላ ባለስልጣናት መናገራቸው ተገልጿል፡፡የሀምዛን ቢን ላደን አማሟት እንዴት እና የት እንደሆነ ግን የተባለ ነገር የለም፡፡የአሜሪካ መንግስት የካቲት ወር ላይ ሀምዛ የት እንዳለ ለጠቆመ የ1 ሚሊየን ዶላር ገንዘብ በጉርሻ መልክ እንደሚሰጥ ማስታወቁ ይታወሳል፡፡30 ዓመት ይሆነዋል ተብሎ የሚገመተው ሀምዛ ቢን ላደን በአሜሪካና ሌሎች ሀገራት ላይ ጥቃት እንዲፈፀም የሚጠይቅ የተንቀሳቃሽ ምስልና ድምፅ መልዕክት አስተላልፎ እንደነበር ተገልጿል፡፡በጉዳዩ ላይ ረቡዕ ዕለት በሪፖርተሮች የተጠየቁት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕም እና የኋይት ሃውስ የሀገር ደህንነት አማካሪ ጆን ቦልተን አስተያየታቸውን ከመስጠት ተቆጥበዋል።ሀምዛ ቢን ላደን እ.ኤ.አ.በ 2011 ግንቦት ወር ላይ በፓኪስታን በአሜሪካ ልዩ ሀይል የተገደለውን የአባቱን ገዳዮች ለመበቀል ጂሃዲስቶች ጥቃት እንዲፈፅሙ ጥሪ ማቅረቡ የሚታወስ ሲሆን÷ ሳዑዲ አረቢያ ዜግነት እንደነጠቀችውም አይዘነጋም፡፡የአሜሪካ መንግስት እንደሚለው እ.ኤ.አ.በ 2011 በፓኪስታን አቦታባድ በአባቱ ቤት በተደረገው ፍተሻ የተገኙ ሰነዶች እንደሚያሳዩት ሀምዛ አልቃይዳን እንዲመራ ታጭቶ ነበር።(ምንጭ፦ ቢቢሲ)
0
c5523690aa439830b3eed5dd773e7087
c5523690aa439830b3eed5dd773e7087
በወታደራዊ ስነምግባር ጥሰትና በኩብለላ ለተከሰሱ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ምህረት ተደረገ
በወታደራዊ ስነ ምግባር ጥሰትና ኩብለላ ወንጀሎች ለተከሰሱ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ምህረት ማድረጉን የመከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ።በሚኒስቴሩ የመከላከያ ኢንዶክትሪኔሽንና የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ብርጋዴር ጀኔራል ኪዱ አለሙ፥ እንደገለጹት መንግስት በሃገር አቀፍ ደረጃ የጀመራቸውን የለውጥ እንቅስቃሴዎች ለማስቀጠል መከላከያ ሰራዊት ለውጡን በመደገፍ እየሰራ ነው።በዚህም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቅርቡ ያጸደቀውን የምህረት አዋጅ መሰረት በወታደራዊ የስነ ምግባር ጥሰት ተከሰው በማረሚያ ቤት የሚገኙና ቀደም ሲል ከሃገር የኮበለሉ የሰራዊት አባላት ምህረት ተደርጎላቸዋል ብለዋል።የምህረት አዋጁ የሚመለከታቸው የሰራዊት አባላት ተቋሙ ባዘጋጃቸው አካባቢዎች ባሉ ጽህፈት ቤቶች በአካልም ሆነ በተዘጋጀ ፎርም ማመልከት እንደሚገባቸውም ገልጸዋል።በዚህም በተቋሙ አዲስ አበባና አካባቢዋ የሚገኙ ታራሚዎች ቤላ አካባቢ በሚገኘው የፍትህ ዳይሬክቶሬት ጽህፈት ቤት ሪፖርት ማድረግ እንደሚችሉ ጠቁመዋል።ከአዲስ አበባ ውጭ ላሉ ታራሚዎች ባሉበት ክልል በተጠባባቂ የፍትህ ዳይሬክቶሬት ጽህፈት ቤት ሪፖርት ማድረግ የሚችሉ ሲሆን፥ በወረዳና በዞን ላሉ ደግሞ በዞኑ በሚገኘው ጽህፈት ቤት ሪፖርት ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ነው ያሉት።በዚህም ከዛሬ ጀምሮ በአዲስ አበባ ጽህፈት ቤቱ ፎርሙን ማስሞላት እንደተጀመረ ጠቅሰው፥ በክልሎች ደግሞ ከነሃሴ አንድ ቀን ጀምሮ ባሉት ስድስት ወራት ውስጥ ሪፖርት ማድረግ እንደሚገባቸው ተናግረዋል።በተሰጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ሪፖርት አድርገው ያላጠናቀቁ ታራሚዎች የጊዜ ገደቡ ሲጠናቀቅ ሪፖርታቸው ተቀባይነት እንደማይኖረውም አሳስበዋል።(ኤፍ ቢ ሲ)
1
95a203354d46357b4501a46325c179e4
95a203354d46357b4501a46325c179e4
ቻምፒየንስ ሊግ፡ ወደ አንደኛውን ዙር የተቀላቀሉ 32 ክለቦች ታውቀዋል
የካፍ ቻምፒየንስ ሊግ ቅድመ ማጣሪያ የመልስ ጨዋታዎች በሳምንቱ መጨረሻ ተደርገዋል፡፡ በአብዛኞቹ ጨዋታዎች የተጠበቁት ክለቦች ወደ አንደኛው ዙር አልፈዋል፡፡ የኢትዮጵያ ተወካዩ ቅዱስ ጊዮርጊስ የሲሸልሱን ሴንት ሚሸልን 4-1 በሆነ የአጠቃላይ ውጤት አሸንፏል፡፡ የዩጋንዳው ቫይፐርስ በናይጄሪያው ኢኒየምባ 2-1 ተሸንፎ ከውድድሩ ውጪ ሆኗል፡፡ ሌላው የምስራቅ አፍሪካ ክለብ ጎር ማሂያ በማዳጋስካሩ ሲኤንኤፒኤስ ስፖርትስ 3-1 ተሸንፎ ከቻምፒየንስ ሊጉ በግዜ ተሰናብቷል፡፡ ስታደ ማሊያን፣ ኤኤስ ቪታ ፣ ክለብ አፍሪካ፣ ካይዘር ቺፍስ፣ ማሌሎዲ ሰንዳውንስ፣ አሴክ ሚሞሳ እና ኤምኦ ቤጃ ወደ ተከታዩ ዙር ያለፉ የተወሰኑ ክለቦች ናቸው፡፡ የብሩንዲው ቪታሎ ክለብ ሊኦሊን ከሜዳው ውጪ ባገባው አንድ ግብ ታግዞ በማሸነፍ ወደ አንደኛው ዙር አልፏል፡፡ በመጀመሪያው ዙር ከአሁኑ ተጠባቂ ሆኑ ጨዋታዎች ያሉ ሲሆን ጨዋታዎቹ በመጋቢት ወር ይካሄዳሉ፡፡ በዋይዳድ ካዛብላንካ እና ኤኤስ ዱዋአነስ መካከል ሊደረግ የነበረው የመልስ ጨዋታ ሌላ ግዜ በመታዘሙ ሳይካሄድ ቀርቷል፡፡ ዋይዳድ በመጀመሪያው ጨዋታ 2-0 አሸናፊ ነበር፡፡ የሁለቱ ቡድኖች አሸናፊ በመጀመሪያው ዙር ሲኤንኤፒኤስ ስፖርትስን ይገጥማል፡፡የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎችቅዱስ ጊዮርጊስ (ኢትዮጵያ) ከ ቲፒ ማዜምቤ (ዲ.ሪ. ኮንጎ)ዋሪ ዎልቭስ (ናይጄሪያ) ከ አል ሜሪክ (ሱዳን)ኤቷል ደ ኮንጎ (ኮንጎ ብራዛቪል) ከ ኢኤስ ሴቲፍ (አልጄሪያ)አል አሃሊ ትሪፖሊ (ሊቢያ) ከ አል ሂላል (ሱዳን)ኤኤስ ቪታ ክለብ (ዴ.ሪ. ኮንጎ) ከ ክለብ ፌሮቫያሪዮ ዲ ማፑቶ (ሞዛምቢክ)ማሜሎዲ ሰንዳውን (ደቡብ አፍሪካ) ከ ኤሲ ሊዮፓርድስ (ኮንጎ ብራዛቪል)ስታደ ማሊያን (ማሊ) ከ ኮተን ስፖርት (ካሜሮን)ኤፒአር (ሩዋንዳ) ከ ያንጋ አፍሪካ (ታንዛኒያ)ሲአርዲ ዱ ሊቦሎ (አንጎላ) ከ አል አሃሊ (ግብፅ)ክለብ አፍሪካ (ቱኒዚያ) ከ ኤምኦ ቤጄ (አልጄሪያ)ኦኤስ ኮሪብጋ (ሞሮኮ) ከ ኤቷል ደ ሳህል (ቱኒዚያ)ዜስኮ ዩናይትድ (ዛምቢያ) ከ ሆሮያ ኮናክሬ (ጊኒ)ኢኒያምባ (ናይጄሪያ) ከ ቪታሎ (ቡሩንዲ)ዩኒየን ዱዋላ (ካሜሮን) ከ ዛማሌክ (ግብፅ)ካይዘር ቺፍስ (ደቡብ አፍሪካ) ከ አሴክ ሚሞሳ (ኮትዲቯር)ሲኤንኤፒኤስ ስፖርትስ (ማዳጋስካር) ከ ዋይዳድ ካዛብላንካ (ሞሮኮ) / ኤኤስ ዱዋአኔስ (ሴኔጋል)
1
5da15495f6616af2554cf1efa2c11734
13eceed03f1ceb49837e5cf779d59130
የወልቂጤ ከተማ ምክትል ፕሬዝደንት በግላቸው ለኮሮና ቫይረስ የገንዘብ ድጋፍ አደረጉ
አዲስ አበባ፤ ህዳር 30 ፤2013 (ኤፍ ቢ ሲ) 18 ባንኮች እና የፋይናንስ ተቋማት ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ከ205 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረጉ።የባንኮቹ እና የፋይናንስ ተቋማቱ ፕሬዚዳንቶች እና ተወካዮች ድጋፉን ለአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ አስረክበዋል ።በኢትዮጵያ ባንኮች ማህበር አስተባባሪነት 18 ባንኮችን ጨምሮ የኢትዮጵያ መድህን ድርጅት ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ከ205 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ ማድረጋቸውን ከአዲስ አበባ ፕሬስ ሴክሬታሪያት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል ።በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ እንደገለፁት የፋይናንስ ተቋማቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለሀገር መከላከያ ሰራዊቱ ላደረጉት ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል ።የሀገር መከላከያ ሰራዊቱ ለሚያደረገው ህግን የሰላም ማስከበር እና ሌሎች እንቅስቃሴዎች የከተማ አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ወይዘሮ አዳነች ተናግረዋል፡፡በአዲስ አበባ የሚገኙ የፋይናንስ ተቋማት ያደረጉትን የገንዘብ ድጋፍ ምክትል ከንቲባዋ ለሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የውጭ ግንኙነት ኃላፊ ለሆኑት ኮለኔል የኑስ ሙሉ አስረክበዋል ።ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
0
b6b76c61ddb7454725ef8d85544a589d
2aa5575f8d5d40c720c48d572bcadc14
"ካልዓይ ጌቶች" ዳግ ኤምሆፍ
አዲስ አበባ ፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ህብረተሰቡ የአፍ እና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭምብሎችን በአግባቡ በመጠቀም የጤና ባለሙያዎችን እንዲያግዝ ጥሪ አቀረቡ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፌስ ቡክ ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የኮቪድ-19 ታማሚዎች ቁጥር በማሻቀብ ላይ መሆኑን አስታውቀዋል።በአሁኑ ወቅት የጽኑ ሕሙማን ክፍል ያለውን ዐቅም ሁሉ አሟጦ እየሠራ እንደሚገኝ ጠቁመው ፥ በዚህ ወቅት የጥንቃቄ እርምጃዎችን ቸል ማለት እንደማይገባም አሳስበዋል። ህብረተሰቡ የራሱን ሕይወት እንዲታደግ የሌሎችንም ሕይወት እንዲያተርፍም ጥሪ አቅርበዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 21/2013
0
61b185a72e11b18b6d6e3054e828a6b5
61b185a72e11b18b6d6e3054e828a6b5
ባለፉት 100 ቀናት ለ216 ሺህ 328 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ተደርጓል – የጤና ሚኒስቴር
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት 100 ቀናት ለ216 ሺህ 328 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ የላቦራቶሪ ምርመራ መደረጉን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።ምርመራው ከመጋቢት 4 ቀን እስከ ሰኔ 14 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ የተካሄደ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪም 32 ሚሊየን ሰዎች በቤት ለቤት ዳሰሳ መታየተቻውንም አስታውቋል።በእነዚህ ቀናቶች በተደረገ ምርመራም 4 ሺህ 532 ሰዎች ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል ነው ያለው።በተጨማሪም ንክኪ ያላቸው 31 ሺህ 573 ሰዎች ተለይተው 708 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸውም ገልጿል።እንዲሁም ከጥር 15 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ለ764 ሺህ 948 ተጓዞች ልየታ እና ክትትል ተደርጓልም ነው የተባለው።13 ሺህ 859 የመታከሚያ አልጋዎች የተዘጋጁ ሲሆን 4 ሺህ 500 የጤና ባለሙያዎች ተቀጥረው 12 ሺህ በጎ ፈቃደኞች መሰማራታቸውም ተጠቅሷል።ቫይረሱን ለመከላከልም 513 ሚሊየን ብር የሚያወጡ የግል መከላከያ ቁሳቁሶች በሃገሪቱ ተሰራጭተዋል።
1
f7711f0203599d50aba19cf1a56cc167
9c540a3433169ea7994d54f9a3ab9923
በውጭ አገራት የሚኖሩ ዜጎችን መብት ለማስጠበቅ መንግስት ከፍተኛ ትኩረት ይሰጣል ተባለ
በባሕሬን የኢፌዲሪ ቆንስል ጄኔራል ሆነው የተሾሙት አምባሳደር ጀማል በከር ስራቸውን በይፋ ለመጀመር ባሕሬን ማናማ መግባታቸው ተገልጿል።አምባሳደሩ ባሕሬን ኢንተርናሽናል አየር ማረፊያ ሲደርሱ የባሕሬን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተወካይና በአገሪቱ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አቀባበል አድርገውላቸዋል።አምባሳደር ጀማል ታኅሳስ 12 ቀን 2013 ዓ.ም ከባሕሬን የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አደራጅ ኮሚቴ አባላት ጋር ትውውቅ አድርገዋል፡፡የሚስዮኑ መከፈት በባሕሬን የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን መብትና ጥቅም ለማስጠበቅ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው የተናገሩት አምባሳደር ጀማል፤ ለተደረገላቸው ደማቅ አቀባበል አመስግነዋል።ሁሉም ዜጋ የአገሩ አምባሳደር መሆኑን በመጠቆም ዳያስፖራው ከቆንስላ ጄኔራል ጽህፈት ቤቱ ጋር በጋራ ተቀራርቦ እንዲሰራም ጥሪ አቅርበዋል።“የሚስዮኑ ዋነኛ ትኩረት ሁሉንም ዜጎች በቅልጥፍና፣ በፍትሃዊነትና በዕኩልነት የሚስተናገዱበትን አሰራር በመዘርጋት ዜጎችን ማገልገል ነው” ብለዋል።የነበሩ በጎ ስራዎችን በማስቀጠልና ካለፉት ስህተቶች በመማር ውጤታማ የዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲን ማሳካት እንደሚቻል ፅኑ እምነት እንዳላቸው ጠቅሰዋል።የውይይቱ ተሳታፊዎች ለአምባሳደሩና በሚስዮኑ ለተመደቡ ዲፕሎማቶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን ያስተላለፉ ሲሆን፤ መንግሥት በባሕሬን የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ችግር አዳምጦ ሚሲዮን እንዲከፈት ላቀረቡት ጥያቄ በጎ ምላሽ በመስጠቱና የረጅም ጊዜ ህልማቸው እውን በመሆኑ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል።የኮሙኒቲ አባላቱ ከቆንስላ ጽህፈት ቤቱ ጋር በትብብር ለመስራትና ሚስዮኑ አገልግሎቱን እስኪጀምር ድጋፋቸውን እንደሚቀጥሉም ቃል መግባታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።
0
5f6272f4d4963f06df44af1c7a3f6cdb
ea7d1a4d90fe839b18f5ae671c48b39d
የኤሌክትሮኒክ ፊርማ ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ ቀረበ
የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ከክልሉ ምክር ቤት ውጪ መሾም እንዲቻል፣ የከተማ አስተዳደሩን ቻርተር የሚያሻሽል ረቂቅ ለፓርላማው ቀረበ ።ከዚህ በተጨማሪም ዘንድሮ በአገሪቱ በተከሰቱ የፖለቲካ ቀውሶች ምርጫ ማካሄድ ባለመቻሉ፣ በሥራ ላይ የሚገኘው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤትና የከተማው ካቢኔ ምርጫ እስከሚደረግ በሥልጣን ላይ እንዲቆይ የሚፈቅድ ማሻሻያ ከተማዋን ባቋቋመው ቻርተር ላይ እንዲካተት ረቂቅ ቀርቧል።ፓርላማው ዛሬ ሰኔ 21 ቀን 2010 ዓም በቀረበው ማሻሻያ ላይ ተወያይቶ ለዝርዝር ዕይታ ለሕግና ፍትሕ አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መርቶታል።ይህ በዚህ እንዳለ፣ ፓርላማው በዛሬው ውሎው የምሕረት አሰጣጥና አፈጻጸም ሥነ ሥርዓት ረቂቅ አዋጅን አጽድቋል፡፡
0
8a6a0d92bfb2caa34c5bc1435030c8a8
8a24bf58e2297f1659ce5cc91df992c9
የአሰልጣኞች አስተያየት | ፋሲል ከነማ 2-0 ድሬዳዋ ከተማ
በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ሁለተኛ ሳምንት ጨዋታዎች መካከል አንዱ የነበረው የፋሲል ከነማ እና ሀዋሳ ከተማ ጨዋታ በአጼዎቹ 3-1 አሸናፊነት ተጠናቋል። ከጨዋታው በኋላ አሰልጣኞቹ የሰጡትን አስተያየት እነሆ!ሙሉ በሙሉ ዳኛውን መገምገም አልፈልግም። ጎል መሆኑን አፅድቆ ሁላችንም እየጨፈርን ባለበት ሰዓት ነው ያ ሁሉ ትርምስ የተፈጠረው። ቀደም ብሎ ግብ አይደለም ወይም ጥፋት ተሰርቶበታል ቢል አኛ ነበርን ተጠቃሚዎች። ጥፋት ተሰርቷል ቢል እንኳን ፌሽካ ነፍቻለሁ ካለ ፍጹም ቅጣት ምት እዛው ላይ በመስጠት ጨዋታውን መቆጣጠር ይችል ነበር። ነገር ግን እንደሰው ሊሳሳት ይችላል መቀበል ነው። እናም ያ አጋጣሚ ጨዋታውን ቀይሮታል ።ሁለተኛው ግብ ሲቆጠር ዳኛው ፊሽካ ነፍቷል። በዛ ምክንያት የኛ ተጫዋቾች ቆመዋል። በዛ ምክንያት ግቡ ተቆጠረ ግብ ነው ብሎ አፀደቀ፤ ሄደን ስናናግረው ፊሽካ መንፋቱን አመነ። የኛን አንድ ተጫዋቾች አስወጥቶ ግቡን ሻረው። ከዛ እንደገና ፍጹም ቅጣትምት ሰጠ። ቢሆንም ከ ሳጥን ውጭ ስለነበር ፍጹም ቅጣት ምት አያሰጥም ነበር። በዚህ ሁኔታ ሁለተኛ ግብ ተቆጠሮብናል። የተፈጠረው ነገር ደስ አይልም።በምን እንደሆነ አናውቅም፤ ለምን እንደተሰጠውም አናውቅም። ምን አልባት አሁን አዳነን በቀይ ሲያስወጣው ጥፋቱን ሰርቷል ብሎ ከሆነ ጥፋቱ የተሰራው ከፍጹም ቅጣት ምት ክልል ውጭ ነው። ግቡን ሲሽረው አዳነን አስወጣው። የግቡ መሻር ምክንያት አዳነ ይመስለኛል። ያ ቅጣት ምት ከሳጥን ውጭ ነበር መመታት የነበረበት። ካልሆነ ግን አዳነን ማስወጣት አልነበረበትም። የተምታታ ነገር ነው የተከሰተው። እንደ አጠቃላይ የዳኛው ውሳኔ ሙሉ በሙሉ ተፅዕኖ ነበረው። ተጫዋች በቀይ ወጥቶብናል። ያለ አግባባ ፍጹም ቅጣት ምት ተሰጥቶብናል። ምንም ጥርጣሬ የለውም ሙሉ ለሙሉ ተፅዕኖ አድርሶብናል።
0
d030fc72f61ced36eb8b4c0b1ee3ceae
33a5ece4fbf8b675b4bd2f1498a8c37c
አሜሪካ የጦር መርከቦቿን ወደ ኮሪያ ልሳነ ምድር አሰማራች
ሰሜን ኮርያ በመጪው ወር በደቡብ ኮርያ ፕዮንግያንግ ወደሚካሄደው የክረምት ኦሊምፒክ ውድድር የከፍተኛ ደረጃ ልዑካን ለመላክ ተስማምታለች። ይህ ስምምነት የተደረገው ዛሬ ሰሜንና ደቡብ ኮርያ ተገናኝተው በተነጋገሩበት ወቅት ነው። ንግግሩ የተካሄደው “የሰላም መንደር” በተባለው ጳንሙንጆም ላይ ነው። በኮርያ ልሳነ ምድር ይካሄድ የነበርውን ጦርነት ያቆመው ስምምነት እኤአ በ1953 ዓ.ም የተፈረመው በዚሁ ቦታ ላይ ነበር። ከፕዮንግያንግጉ ስብሰባ በኋላ ሰሜን ኮርያ የከፍተኛ ባለሥልጣኖች ልዑካንን፣ አትሌቶችንና ውድድሩን የሚያዳምቅ ቡድንን በመጪው ወር ወደ ሚጀመረው የኦሎምፒክ ውድድር የመላክ ዕቅድ እንዳላት የውኅደት ምክትል ሚኒስትር ገልጸዋል።
0
8ecce74a53da5dde370edaeb9739c1b9
8ecce74a53da5dde370edaeb9739c1b9
ዳያስፖራው ለዓለምአቀፉ ማኅበረሰብ ስለ ሕግ ማስከበር ዘመቻው በማስረዳት ጉልህ አስተዋጽኦ አበርክቷል – የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ
ዳያስፖራው ሐሰተኛ መረጃዎችን በማጋለጥ ዓለምአቀፉ ማኅበረሰብ የሕግ ማስከበር ዘመቻውን በትክክል እንዲገነዘብ ጉልህ አስተዋጽኦ ማድረጉን የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ አስታወቀ።ኤጀንሲው ዳያስፖራው ለሠብዓዊ ድጋፍ 80 ሚሊየን ብር የሚጠጋ የገንዘብና የአይነት ድጋፍ ማበርከቱንም ገልጿል።ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም በአገር መከላከያ ሠራዊት ላይ የተፈፀመውን ጥቃት ተከትሎ በህወሓት ቡድን ላይ የተወሰደው የሕግ ማስከበር ዘመቻ ተጠናቆ ተልዕኮው ወደ ‘ወንጀለኞችን የማደንና የመልሶ ግንባታ ምዕራፍ’ መሸጋገሩ ይታወቃል።የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት ሠራዊቱ ላይ በተፈፀመው ጥቃት የዳያስፖራው ስሜት የነበረው የመደናገጥ፣ የመጨነቅና ስለ ጉዳዩ ማብሪሪያ የመጠየቅ እንደነበር ለኢዜአ ገልጸዋል።ኤጀንሲው ሚሲዮኖችን፣ በውጭ አገሮች የሚገኙ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማኅበራት፣ በጎ አድራጎት ድርጅቶች ሌሎች የዳያስፖራ አደረጃጀቶችን በመጠቀም የተፈፀመውን ጥቃትና የሕግ ማስከበር ዘመቻውን አስመልክቶ ትክክለኛ መረጃ የማድረስ ስራ መከወኑን ተናግረዋል።
1
5a3e89ab0f0cb01d92af63391bf343ad
eb55d4b4f7594ab476cf5eac23f880d3
የኢፌዴሪ አየር ኃይል ለ1 ሺህ 29 የአየር ኃይል መኮንኖች የማእረግ እድገት ሰጠ
ዓርብ መስከረም 30 ቀን 2012 ዓ.ም. ጠዋት ከደብረ ዘይት አየር ኃይል የጦር ሰፈር ከተነሳ ጥቂት ደቂቃዎች በኋላ በደረሰበት የቴክኒክ ችግር በወደቀው ሱኮይ 27 ተዋጊ ጄት የሁለት አብራሪዎች ሕይወት ጠፋ፡፡ምንጮች ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ተዋጊ ጄቱ በአስተማሪና ሠልጣኝ ፓይለቶች አማካይነት ለልምምድ ከጠዋቱ አራት ሰዓት አካባቢ ከደብረ ዘይት ሐረር ሜዳ በመባል ከሚታወቀው የአየር ኃይል ጣቢያ በመነሳት ላይ ሳለ ሞተሩ በእሳት በመያያዙ በአዲስ አበባ አዳማ መንገድ አቅራቢያ ወድቋል፡፡ በአደጋው ሁለቱም አብራሪዎች ሕይወታቸውን እንዳጡ ታውቋል፡፡ ኢንስትራክተር አብራሪው ሻለቃ ሰብሪ ቶፊቅ ከተዋጊ ጄቱ ተስፈንጥሮ የወጣ ቢሆንም፣ ፓራሹቱ ሊዘረጋለት ባለመቻሉ ሕይወቱ እንዳለፈ ምንጮች ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ ሌላው በአደጋው ሕይወቱን ያጣው ሠልጣኝ አብራሪ ሻምበል ኃየሎም ተስፋይ መሆኑ ታውቋል፡፡ ሻለቃ ሰብሪ በ1999 ዓ.ም. ከኢትዮጵያ አየር ኃይል የበረራ ትምህርት ቤት በከፍተኛ ማዕረግ እንደተመረቀና አየር ኃይሉን ከአሥር ዓመት በላይ እንዳገለገለ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ድሬዳዋ ተወልዶ ያደገው ሻለቃ ሰብሪ በጂማ ዩኒቨርሲቲ የኢንጂነሪንግ ተማሪ የነበረ ቢሆንም፣ ለበረራ በነበረው ፍቅር የምሕንድስና ትምህርቱን አቋርጦ ወደ አየር ኃይል የበረራ ትምህርት ቤት እንደገባ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ በትምህርቱም በከፍተኛ ውጤት ያስመዘግብ እንደነበር ገልጸው፣ ሲመረቅ ከክፍሉ በአንደኛ ደረጃ እንዳጠናቀቀ ተናግረዋል፡፡ ሻለቃ ሰብሪ ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባት ነበር፡፡ሱኮይ 27 ተዋጊ አውሮፕላኖች የተገዙት በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ወቅት እንደነበር ይታወሳል፡፡
0
06a5d30200d09b29193095e573b8b737
dbe256379ecc25da113e81a152226f22
በ2018 ብቻ 2 ሺ 200 ስደተኞች በሜድትራንያን ባህር ሞተዋል
የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች መርጂያ ድርጅት (UNHCR) አብዛኞቹ ወደ አዉሮፓ የሚነጉዱት ሰዎች ከጦርነት ሕይወታቸዉን ለማዳን የሚሸሹ ናቸዉ፣ አሽባሪዎች አይደሉም ብሏል።አብዛኞቹ የሶሪያ ስደተኞች ፓርስ ላይ ጥቃት ከጣሉት ዓይነት ኢሰብአዊ አሸባሪዎች የሚሸሹ ናቸዉ። ሕይወታቸዉን ለማዳን ያልተለመዱ መንገዶችን በመጠቀም ወደ የአዉሮፓ ባህር ጠረፍ ለመድረስ የሚጥሩ ስደተኞች ናቸው ብለዋል።የመንግስትታቱ የስደተኞች መርጂያ ድርጅት (UNHCR) ቃል አቀባይ መሊሳ ፍለሚንግ (Melissa Fleming)፣ ጄኔቫ ከሚገኘዉ የድርጅቱ ዋና ማእከል ሊሳ ሺላይን የላከችዉን ዘገባ ትዝታ በላቸዉ ካጠናቀረችዉ ዘገባ ያድምጡ።
0
a0a3572b137659ba95c977ee08a7b60e
74afffcc693f67f0d0f362d4dca10eb2
በጂንካ ከተማ የጣለው ከባድ ዝናብ በአካባቢው መሰረተ ልማት ላይ ጉዳት አደረሰ
ከወደ ሜክሲኮ ባህረ ሰላጤ ከባድ ንፋስ ይዞት የሚነጉደው ከባድ ዝናብ ሀሪኬይን ሃርቪ ወደ ቴክሳስ ክፍለ ግዛት ጠረፍ አካባቢ እያመራ ነው።ባለሥልጣናት መጠነ ሰፊ ጥፋት ያስለክትላል ብለው ለሰጉበት ለዚህ ከባድ ንፋሳማ ዝናብ ውርጂብኝ እየተዘጋጁ ናቸው።ዝናቡ ቴክሳስ የብሱ ላይ ከሰዓታት በኋላ ቢሆንም ፍጥነቱ ግን እየጨመረ ነው። በሰዓት ከሁለት መቶ ኪሎ ሜትር በሚበልጥ ፍጥነት የሚውዘገዘግ ንፋስ የሚነጉደው ዝናብ ጠረፉን አካባቢ ቢያንስ ሰማኒያ ሴንቲ ሜትር ያህል በውሃ ያጥለቀልቃል ተብሎ ተሰግቷል።ሀሪኬይን ሃርቪ ቴክሳስ ላይ ከባድ ጉዳት እንደሚያደርስ የዩናይትድ ስቴትስ የፌዴራል አስቸኳይ ጉዳዮች አስተዳደር መሥሪያ ቤት ዋና ኃላፊ አስጠንቅቀዋል።ዋናው ሥጋታቸው ማስጠንቀቂያውን ቸል ብለው ቤታቸውን ላለመልቀቅ የወሰኑ ጠረፉ አካባቢ የሚኖሩ አንዳንድ ዜጎች መኖራቸው ነው ብለዋል፡፡
0
c3d66da209992a5815366f310af780ef
c9ba067d082d0a84400a24e19cf79551
በማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ የተመደበ የፌዴራል ፖሊስ ሁለት ባልደረቦቹን ገደለ
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 6፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጤና ሚኒስቴር፣ የፌደራል ፖሊስና የመድን ፈንድ አስተዳደር ኤጀንሲ የአስቸኳይ ሕክምና መመሪያ ለመተግበር ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱን የጤና ሚኒስትር ዲኤታ ወይዘሮ ሰሃረላ አብዱላሂ፣ የፌደራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር መላኩ ፋንታ እና የመድን ፈንድ አስተዳደር ኤጀንሲ ዳይሬክተር ወይዘሮ ወርቅነሽ ብሩ ናቸው የተፈራረሙት።በስምምነቱ መሰረት የተሽከርካሪ አደጋ የሚደርስባቸው ዜጎች አስቸኳይ ሕክምና የሚያገኙበት ስርዓት ይዘረጋል ተብሏል።አደጋው የደረሰባቸው ዜጎች እስከ ሁለት ሺህ ብር የሚያስወጣ ሕክምና በነጻ ማግኘት እንደሚችሉ በመመሪያው ተቀምጧል።የጤና ተቋማት መመሪያውን ስለመተግበራቸው ክትትል እንደሚደረግ በስምምነቱ ላይ ተካቷል።መድን ፈንድ አስተዳደር ኤጀንሲ ደግሞ ነጻ ሕክምናው ስለመኖሩ ግንዛቤ የሚፈጥሩ ስራዎችን ያከናውናል ነው የተባለው። የአስቸኳይ ሕክምና አገልግሎቱ ተግባራዊ እንዲሆን ተቋማቱ በቅንጅት የሚሰሩ ሲሆን የክልል ባለድርሻ አካላትም በጉዳዩ ላይ በጋራ እንደሚሰሩ ኢዜአ ዘግቧል።
0
d57dcc440653a9ecfbe8aabaedfc9830
d57dcc440653a9ecfbe8aabaedfc9830
የሰላም ወግ ብሄራዊ መግባባት ለዘላቂ ሰላምና ሃገር ግንባታ በሚል ርዕስ የውይይትና የምክክር መድረክ ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 30፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የሰላም ወግ ብሄራዊ መግባባት ለዘላቂ ሰላምና ሃገር ግንባታ በሚል ርዕስ የውይይትና የምክክር መድረክ ተካሂዷል፡፡በሰላም ሚኒስቴር አስተባባሪነት እየተካሄደ የሚገኘው የብሔራዊ የማህበረሰብ ተኮር የምክከር መድረክ አንዱ አካል የሆነው የታሪክ ምሁራንና የታሪክ ፀሐፊያን የምክክር መድረክ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ለአራት ቀናት በቢሾፍቱ ከተማ መካሄዱ ይታወሳል፡፡ የዚሁ አካል የሆነው ‘የሰላም ወግ ብሄራዊ መግባባት ለዘላቂ ሰላምና ሃገር ግንባታ በሚል ርዕስ የውይይትና የምክክር መድረክም ዛሬ ተካሂዷል። ባለብዙ ደርዝ የሆነውን የሃገሪቱን ችግር በእውቀትና በትክክለኛ ይዞታቸው ቃኝቶ መፍትሄ ማበጀት የበለጸገችውን ሃገር ለማየት እንደሚያስችል የሰላም ሚኒስትሯ ወይዘሮ ሙፈርያት ካሚል ገልጸዋል።ተደራራቢ የሃገሪቱ ችግሮች ውስጥ የሚጠቀሰው ታሪካዊ ይዘትም ፍጹም ነጻና በእውቀት ላይ ተመስርቶ ውይይት በማካሄድ ለብሄራዊ መግባባትና ለዘላቂ ሰላምና ሃገር ግንባታ ያግዛል ብለዋል።መድረኩ በተለያዩ የታሪክ እና ሌሎች የትምህርት መስክ ምሁራን የታሪክ የፖለቲካና የማህበራዊ ሳይንስ ጥናትና ምርምር ለብሄራዊ መግባባትና ለሃገር ግንባታ ያለውን አበርክቶ የዳሰሰ ነበር፡፡በመድረኩ የተለያዩ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ተሳታፊዎች ውይይት አድርገውበታል። በተስፋዬ ከበደከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
1
4facd7cfeeb0388872fd19b369090fb9
a7ea11e44dbc7ede5f71836497c3fb6f
‘‘ለሕገ ወጥ የሰዎች ደላላ ምንም ዓይነት ምሕረት አያስፈልግም፤ ይህ አገርን እንደማጥቃት ይቆጠራል።” ዶክተር ስዩም መስፍን
የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥና አጥፊዎች በህግ ፊት ቀርበው ተገቢውን ሁሉ እንዲያገኙ ያለማወላወል እንሰራለን ብለዋል።ጠ/ሚሩ ዶ/ር ዐብይ አህመድ አክለው ፈታኞቻችን ያልተገነዘቡት ነገር ቢኖር የተከፈለውን መስዕዋትነት ከፍለን የኢትዮጵያንና የህዝቦቿ ብልፅግና የምናረጋግጥ መሆናችንን እንገልፃለን ብለዋል።ይህ በእንዲህ እያለ ለርስ በርስ መተማመን ምንም ዓይነት ጥያቄ ቅሬታና ተቃውሞ ቢኖር በሰለጠነና ምንም ዓይነት ጥፋት በማያደርስ መልኩ ህግን ተከትሎ ማቅረብን ባህላችን እናድርግ ሲሉ ሊቀ ጳጳሳት ዘ ካቶሊካውያንና የዕርቀ ሰላም ኮሚሽን ሰብሳቢ ካርዲናል ብርሃነየሱስ ሱራፌል ጥሪ አሰምተዋል።
0
4de39f7ebed8986054e67fedd69e4a23
4de39f7ebed8986054e67fedd69e4a23
የጤና ማኅበራት ለዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ድጋፋቸውን እየገለጹ ነው
ማህበራቱ በኢትዮጵያ ህክምና ማኅበር ፕሬዚዳንት ዶክተር ገመቺስ ማሞ በኩል ባስተላለፉት መልዕክት ዶክተር ቴድሮስ ቢመረጡ ለዓለም ጤና የተሻለ እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።ዶክተር ቴድሮስ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት አገሪቷን የሚሌኒየሙን የልማት ግብ በጊዜው ማሳካት ከቻሉ ጥቂት አገራት አንዷ እንድትሆን አስችለዋታል ነው ያሉት።በወቅቱ የህፃናት ሞትን በሁለት ሦስተኛ፣ በወባ የሚከሰት ሞትን በ75 በመቶ፣ በኤች.አይ.ቪ የሚሞቱትን በ70 በመቶ፣ በሳንባ ነቀርሳ የሚሞቱትንም በ64 በመቶ መቀነስ እንዳስቻሉም ነው የተናገሩት።በአገሪቷ 3 ሺህ 500 የጤና ማዕከላትና 16 ሺህ የጤና ኬላዎችን በማቋቋም የጤና አገልግሎትን ተደራሽ ማድረግ መቻላቸውንና የጤና ባለሙያ ማሰልጠኛ ማዕከላትን ከሦስት ወደ 33 እንዳሳደጉ አስታውሰዋል።16 ሺህ 500 የነበሩትን የጤና ባለሙያዎች በሰባት እጥፍ ማሳደግ መቻላቸው የጤናውን ዘርፍ የመምራት አቅማቸውን የሚያሳይ በመሆኑ በዋና ዳይሬክተርነት ቢመረጡ ይህንን ልምዳቸውን እንደሚጠቀሙ እምነታቸውን ገልጸዋል።ዶክተር ቴድሮስ በተለይ በሚታወቁበት የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም 38 ሺህ ባለሙያዎችን አሰልጥነው ወደ ስራ በማስገባት የጤና አጠባበቅ ስርዓቱ ማህበረሰባዊ መሰረት እንዲኖረው ማድረጋቸውንና ለጤና መድህን ሽፋን መጀመር መሰረት መጣላቸውን አውስተዋል።ግሎባል ፈንድን ጨምሮ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትን የመሩት ዶክተር ቴድሮስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅትም በአፍሪካ ኅብረት በኩል ኢቦላን ለመቋቋም በተደረገው ርብርብ ኢትዮጵያ የበኩሏን ጉልህ አስተዋፅኦ እንድታበረክት አድርገዋል።
1
9609f585bc6c3e124f53a4f827a558de
a7aaa46bc7702d098e06997ada8e9f36
እቴጌ ጣይቱ ሆቴል ለአደጋ የተጋለጠ መሆኑን ማሳወቁን የእሳት አደጋ መከላከያ ባለሥልጣን አስታወቀ
አዲስ አበባ ፣መጋቢት 11፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዲስ አበባ ጎፋ ገብርኤል አካባቢ በደረሰ የእሳት አደጋ ሁለት የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ጉዳት ደርሶባቸዋል።በአዲስ አበባ ወረዳ 6 በተለምዶ ጎፋ ገብርኤል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በአንድ ጋራዥ ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ ሁለት የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ጉዳት ሲደርስባቸው፥ ከ2 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ደግሞ ወድሟል።የአዲስ አበባ እሳትና ድንገተኛ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ቡድን መሪ አቶ ጉልላት ጌታነህ፥ የእሳት አደጋው የደረሰው ትናንት ምሽት 2 ሰዓት ከ50 አካባቢ መሆኑን ገልጸዋል።የእሳት አደጋው በአንድ ጋራዥ ላይ የደረሰ ሲሆን እሳቱን ለማጥፋት ከተሰማሩት 71 የእሳት አደጋ ሰራተኞች መካከል ሁለቱ ቀላል ጉዳት አጋጥሟቸዋል ነው ያሉት ሀላፊው።ከዚህ ባለፈም ከ2 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ሲወድም ከ30 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ከቃጠሎው ማትረፍ መቻሉንም ተናግረዋል።እሳቱን ለመቆጣጠር አምስት ሰአታትን የፈጀ የማጥፋት ስራ የተከናወነ ሲሆን 250 ሺህ ሊትር ውሃ ጥቅም ላይ ውሏል።የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ ይገኛል ብለዋል።የእሳት አደጋውን በመቆጣጠር ሂደት የፌደራል እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አባላት እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች ከፍተኛ ርብርብ ማድረጋቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
0
491fc026d88e6af645555b22671c7060
491fc026d88e6af645555b22671c7060
ለታላቁ ህዳሴ ግድብ በልደታ ክ/ከተማ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ከ71 ሚሊየን ብር በላይ ተሰበሰበ
አዲስ አበባ ፣ መስከረም 5 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ከአዲስ አበባ ከተማ ልደታ ክፍለ ከተማ በአንድ ወር ብቻ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ከ71 ሚሊየን ብር በላይ መሰብሰቡ ተገለፀ፡፡የአዲስ አበባ ከተማ ልደታ ክፍለ ከተማ የህዳሴ ግድብ ዋንጫን ለአራዳ ክፍለ ከተማ ያስረከበ ሲሆን÷ በዚህ ወቅት የአዲስ አበባ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪ አቶ ጃንጥራር አባይን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡ይህን አስመልክቶም አቶ ጃንጥራር አባይ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው እንዳሉት በታላቁ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ በ2012 ዓ.ም በድፕሎማሲው በኩል ስኬት አስመዝግበናል፣ የመጀመሪያውን የውሃ ሙሌትም በድል አጠናቀናል።ያም ሆኖ በመጪው ሶስት አመታት ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ አሁንም የሁሉንም ርብርብ ይጠይቃል ያሉት አቶ ጃንጥራር ÷የተፈጠረውን ህዝባዊ መነቃቃት አስጠብቀን በ2013 ዓ.ም የግድቡን ወሳኝ ምዕራፍ እንሰራለን ነው ያሉት።ዛሬ በልደታ ክፍለ ከተማ የታዘብኩትም ይህንኑ ነው ያሉ ሲሆን ÷በክፍለ ከተማው በሁሉም ወረዳዎች የታላቁን ህዳሴ ዋንጫ በማዘዋወር ከሃምሌ 30 /2012 ጀምሮ ከ71 ሚሊየን ብር በላይ ተሰብስቧል ብለዋል።ለዚህም መላው የክፍለ ከተማ ነዋሪዎችን ፣ አመራሮችን እና ባለ ሀብቶችን አመስግነዋል።ዋንጫውንም ተረኛ የሆነው አራዳ ክፍለ ከተማ ተረክቧል፡፡ የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
1
f1ce85ae4fd842cbae49d2fbe597c9eb
ee3eed17fbe4b283bc4fbbc7c7d01974
አቶ ሽመልስ አብዲሳና ዶክተር ቀነዓ ያደታ የአሠላ ከተማ፣ አርሲ ዞንና የአሰላ ከተማ ነዋሪዎችን ድጋፍ ተረከቡ
ባሕር ዳር፡ ሰኔ 19/2012 ዓ.ም (አብመድ) የደሴ ከተማ አስተዳደር ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ለደሴ ከተማ ጤና መምሪያ፣ ለሰሜን ወሎ ዞንና ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ከአንድ ሺህ በላይ መጻሕፍት ለለይቶ ሕክምና መስጫ ማዕከላትና ለይቶ ማቆያዎች ድጋፍ አደረገ፡፡የመጻሕፍቱ ዋጋ 300 ሺህ ብር እንደሚደርስ ከመምሪያው የተገኙ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡
0
207d1286b8af9553e9ce0e90b38cfa64
207d1286b8af9553e9ce0e90b38cfa64
የኦሮሚያ ከተሞች ከንግድና ከማኅበራዊ እንቅስቃሴ ታቅበው ሰነበቱ
ከሰኞ የካቲት 26 ቀን 2010 ዓ.ም. ጀምሮ በማኅበራዊ ሚዲያ በተጠራ የሦስት ቀንና ከቤት ያለመውጣት አድማ፣ የኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ከተሞች ከንግድና ከማኅበራዊ እንቅስቃሴዎች ታቅበው ሰነበቱ፡፡ በተለይ ከሰኞ ጀምሮ በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞች በተጀመረው አድማ የመንግሥታዊ ተቋማት፣ የንግድ ማዕከላትና የትራንስፖርት እንቅስቃሴ በሙሉ ተገትቷል፡፡ ከተቋማት መዘጋት በተጨማሪ በተለያዩ ሥፍራዎች መንገዶች በመዘጋታቸው ለመንቀሳቀስ አዳጋች ሆኖ ነበር፡፡ነገር ግን የፌዴራል ትራንስፖርት ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ካሳሁን ኃይለ ማርያም ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ሰኞ የትራንስፖርት መቆራረጥ ቢኖርም በማግሥቱ ማክሰኞ የካቲት 27 ቀን 2010 ዓ.ም. ከጅማና ከአምቦ መስመሮች በስተቀር፣ ከአዲስ አበባ በሁሉም አቅጣጫዎች የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ተንቀሳቅሰዋል፡፡ በአምቦ ከሰኞ ቀደም ብሎ ግጭት የተስተዋለበት አድማ የተደረገ ሲሆን፣ በጅማ ከግጭት በመለስ የዩኒቨርሲቲ፣ የባንኮችና የኢንሹራንስ ኩባንያዎች የተለያዩ የንግድ መደብሮችና የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ተገቷል፡፡ይህ በዚህ እንዳለ በኦሮሚያ የተለያዩ ሥፍራዎች የሥራ ማቆም አድማ የቀሰቀሱና በተለያዩ የመንግሥት ኃላፊነቶች ላይ የሚገኙ ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ታውቋል፡፡ በቁጥጥር ሥር ከዋሉት የክልሉ ባለሥልጣናት መካከል የምሥራቅ ሐረርጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፣ የምሥራቅ ወለጋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ፣ የነቀምት ከተማ ከንቲባና ምክትል ከንቲባ፣ የምዕራብ ወለጋ ዞን ቄለም ወረዳ የፍትሕ አስተዳደር ኃላፊ ይገኙበታል ተብሏል፡፡ ቁጥሩ ለጊዜው ባይታወቅም በአምቦና በጅማ የሰው ሕይወት መጥፋቱን መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክና የግል ባንኮች ቅርንጫፎች መዘጋታቸውን ሪፖርተር ከኃላፊዎች መረዳት ችሏል፡፡ ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ የአምቦ ከተማ ነዋሪዎች ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ለሁለት ሌሊቶች ከተማው በተኩስ ሲናጥ ነበር፡፡
1
a65c872bb380c26cdc9f60fff53845c2
2c4536d147710100c4b546fc6c45be94
ለታገዱት 38 ድርጅቶች ገንዘብ ገቢ ማድረግ የሚፈልግ ማንኛውም ሰው በባንክ በኩል እንዲፈጽም ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አሳሰበ
አዲስ አበባ ፣ ህዳር 15 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)በትግራይ ክልል “በግፍ ተፈጽመዋል የተባሉ ወንጀሎችን” የሚያጣራ የምርመራ ቡድን ወደ ስፍራው በማቅናት ስራ መጀመሩን የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታወቀ።የሕወሓት የጥፋት ቡድን ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም በትግራይ ክልል በሚገኘው የአገር መከላከያ ሰራዊት የሰሜን እዝ ላይ የፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ መንግስት የሕግ ማስከበር ተግባር እየከናወነ ይገኛል።የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ በትግራይ ክልል እየተወሰደ ያለውን የሕግ ማስከበር እርምጃ አስመልክቶ ለውጭ አገራት ጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል።ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉ ማይካድራን ጨምሮ በትግራይ ክልል “በግፍ ተፈጽመዋል የተባሉ ወንጀሎችን” የሚያጣራ የምርመራ ቡድን አካባቢው ላይ ደርሷል ብለዋል።የሕወሓትን አመራሮች በከባድ ወንጀል ሊያስጠይቁ የሚችሉ ወንጀሎችን መፈጸማቸውን ጠቅላይ አቃቤ ህጉ አብራርተዋል።በተለይም የሰሜን እዝ ካምፖች ላይ የተፈጸመው ድርጊት የአገር የመከላከያ ሃይልን በማጥቃት የተፈጸመ በመሆኑ በከባድ ወንጀል የሚያስጠይቅ መሆኑን ገልጸዋል።በባህርዳርና በጎንደር ከተሞች የተፈጸሙት የሮኬት ጥቃቶችም በሽብርተኝነት ተግባር የሚያስጠይቁ መሆናቸውን ገልጸዋል።በሰሜን ዕዝ ላይ በተፈጸመው ጥቃት እጃቸው አለበት የተባሉ ተጠርጣሪዎች ላይ ፌዴራል ፖሊስና ጠቅላይ ቃቤ ህግ በፍርድ ቤት በኩል የእስር ማዘዣ እንዲወጣባቸው አድርጓል ብለዋል።እስካሁን በተደረገው ምርምራ ተጥርጣሪ ተብለው የተለዩ ሰዎች ቁጥር 167 መድረሱንም ገልጸዋል።የሕግ ማስከበር እርምጃው በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማዕቀፍ ውስጥ ሆኖ እየተከናወነ ስለመሆኑም አብራርተዋል።የግል ድርጅቶች ሆነው ለህወሃት ቡድን የወንጀል ድርጊት ተሳትፎ አድርገዋል የተባሉ 34 ተቋማት የባንክ ሒሳብ ጨምሮ ተንቀሳቃሽና የማይንቀሳቀስ ንብረታቸው ከሕዳር 7 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ መታገዱን ገልጸዋል።ተቋማቱ ብሔር ተኮር ጥቃትና የሽብር ድርጊት እንዲፈጸም የገንዘብ ድጋፍ በማቅረብ፣ ሕገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ ከሚንቀሳቀሰው የሕወሓት ቡድን ጋር ግንኙነት ፈጥረዋል ተብለው በመጠርጠራቸው መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል።የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
0
6af1871ded5a6f166e08ca008c9829de
1deaf4ed94c30e6cf5a19a08a344daa8
ራሱን በራሱ ፎቶ ግራፍ ያነሳው ዝንጀሮ "ሰልፊ" የፈጠራ ባለቤትነት ገንዘብ ሊጋራ ነው
ፈረንሳይ ማርሴይ ከተማ ውስጥ ትናንት ዕሁድ ሁለት ሴቶች በስለት ወግቶ የገደለው አጥቂ ጥቃቱን ከመፈፀሙ ሁለት ቀን በፊት ፖሊሶች አስረው የለቀቁት መሆኑ ተገለጠ።የፈረንሳይ ባለሥልጣናት እንደተናገሩት የተለያዩ ስሞች የሚጠቀመው ሰውዬ ዓርብ ዕለት የሊዮን ከተማ ፖሊሶች ከመደብር ዕቃ በመስረቅ ተጠርጥሮ ይዘውት በኋላ ግን በቂ ማስረጃ ባለመቅረቡ ለቀውታል።በዘገባዎች መሰረት ሰውየው ማርሴይ ዋናው ባቡር ጣቢያ ላይ አላህ ዋ ክበር እያለ እየጮኸ ሴቶቹን በስለት ከወጋ በኋላ ፖሊሶች በጥይት መትተው ገድለውታል።የእስልምና መንግሥት ብሎ ራሱን የሚጠራው ቡድን በራሱ የዜና አውታር በኩል ለማርሴዩ ጥቃት ኃላፊነት ወስዷል።
0
5641b98501d4d87444cdfc1b1e02879e
5641b98501d4d87444cdfc1b1e02879e
ጠ/ሚ ዐቢይ ከብሄራዊ የህግ ማስከበርና የደህንነት ንዑስ ኮሚቴ ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 28 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከብሄራዊ የህግ ማስከበርና የደህንነት ንዑስ ኮሚቴ ጋር ተወያዩበውይይታቸውም የሕግ ማስከበር እና የደኅንነት ንዑስ ኮሚቴውን የቅድመ ዝግጁነት ሥራና ክንውን በተመለከተ ግምገማ አካሂደዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ብሔራዊ የመከላከያ ሠራዊቱ ኮቪድ19 ሊያስከትል ለሚችለው የመጨረሻ አስከፊ ሁኔታ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት ማካሄዱንም አስታውቀዋል።
1
cbd803acce8c59a9117af75326ca9394
d9b3cdaeefa2cecff434a09ea90a7918
በአዲስ አበባ ከፈረንሳይ ፓርክ እስከ ፈረንሳይ አቦ ድረስ ያለው መንገድ ግንባታ ተጀመረ
ከኢትዮጵያ ኢንያ ድረስ የሚዘረጋው እና በኢትዮጵያ በኩል 437 ኪሎ ሜትሮችን የሚሸፍነው መስራቃዊ የኤሌክትሪክ መስመር ግንባታ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ በኩል ያለው ስራ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁ ተገለፀ። በቻይናው ኩባንያ ቻይና ኤሌክትሪክ ፓወር ቴክኖሎጂ የሚገነባው ፕሮጀክቱ ከወላይ ታ ሶዶ በመነሳት ኬንያ ድረስ የሚዘልቀው የኤሌክትሪክ መስመር 500 ኪሎ ቮልት የሚሸከም ሲሆን የኹለቱን አገራት የኃይል ማሰራጫዎችን የሚያገናኝ ይሆናል።በቀጣይ ደግሞ በኬንያ በኩል ያለው ፕጀክት የሚጠበቅ ሲሆን ይህም 622 ኪሊ ሚቴሮችን እንደሚረዝም ለማወቅ ተችሏል። በኬንያ በኩል ያለው መስመር ዝርጋታ በጀርመኑ ሲመንስ ኩባንያ እንደሚከናወንም ታውቋል። ለፕሮጀክቱ 1 ነጥብ 2 በሊዮን ዶላር ወጪ የሚደረግ ሲሆን ከዚህም ውስጥ 88 ሚሊዮን ዶላር በኬንያ መንግስት የሚሸፈን ሲሆን 32 ሚሊዮን ዶላር ደግሞ ከኢትዮጵያ መንግስት ወጪ ይደረጋል። ቀሪው ደግሞ 684 ሚሊዮን ከአለም ባንክ በተገኘ ብድር፣ 338 ሚሊዮን ዶላር ከአፍሪካ ልማት ባንክ እዲሁም 118 ሚሊዮን ዶላር ደግሞ ከፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ በሚገኝ ብድር ተግባራዊ ይሆናል።
0
fab2fe40c49ac96ec74858a30cc80a41
9d3d41972d52d25112256858c32d12d2
«ስለ ፍቅርና ትዳር እናስተምራለን¡»
ናይጄርያዊው አጥቂ ሳሙኤል ሳኑሚ ዘንድሮ ከደደቢት ጋር መልካም የውድድር ዘመን እያሳለፈ ይገኛል፡፡ በዛሬው ጨዋታ ሁለት ግቦች አስቆጥሮም በ12 ግብ የከፍተኛ ግብ አግቢነቱን ፉክክር ተቀላቅሏል፡፡ አጥቂው ከዛሬው ጨዋታ በኋላ ከሶከር ኢትዮጵያ ጋር አጭር ቆይታ አድርጎ ነበር፡፡ስለ ዛሬው ድልጨዋታው ጥሩ ነበር፡፡ ከጨዋታው በፊት አስበነው የገባነውን አሳክተን ድል አድርገን ወጥተናል፡፡፡፡ ስለ ኮከብ ግብ አስቆጣሪነት ክብርበርካታ ተጫዋቾች ለከፍተኛ ግብ አግቢነቱ እየተፎካከሩ ነው፡፡ እኔም ይህንን ክብር ለማሳካት እስከ መጨረሻው እተጋለሁ፡፡ ስለ ዮሃንስ ሳህሌጥሩ አሰልጣኝ ነው፡፡ የሚያሰለጥንበት መንገድ ተስማምቶናል፡፡ ቡድኑን ወደ ጥሩ መንገድ እየመራው ነው፡፡ ስለ አጥቂ ጥምረትከምርጥ አጥቂዎች ጋር እየተጫወትኩ ነው፡፡ ከጨዋታ በፊት እንነጋገራለን፡፡ በጋራ ጠንክረን እንሰራለን፡፡ስለ ቻምፒዮንነት ፉክክሩተስተካካይ ጨዋታዎች ይቀሩናል፡፡ ስለዚህ ከፉክክሩ አልወጣንም፡፡ እስከመጨረሻው ድረስ እንፎካከራለን፡፡
0
6e424b0b976fc06634faa5d53b4b8406
836c5035090c1cfc281c4ca340580ae9
ብሪታኒያ ማሽተትና ጣዕም ማጣትን የኮሮናቫይረስ ምልክቶች ዝርዝር ውስጥ አካተተች
የአውሮፓ ኅብረት፣ ከተወሰኑ ሃገራት በሚጓዙ መንገደኞች ላይ ተጥሎ የነበረውን ዕገዳ ትናንት ሲያነሳ አሜሪካውያን ታጓዦች ወደአውሮፓ ሀገሮች ለመግባት ከሚችሉት ዝርዝር ውስጥ አልተካተተም።የኮሮናቫይረስ መዛመት ከበረታባቸው ሀገሮች ዩናትድ ስቴትስ፣ ብራዚልንና ህንድን ከመሳሰሉት ሃገሮች የሚጓዙት፣ በአሁኑ ወቅት አውሮፓ መግባት አይችሉም ተብሏል።ቻይና ከአውሮፓ በሚጓዙት ሰዎች ላይ የጣለችውን ዕገዳ ካነሳች፣ ቻይናውያን አውሮፓ መግባት እንደሚችሉ ታውቋል።የአውሮፓ ህብረት ወደ አውሮፓ ለሚጓዝ በሚችሉትና በማይችሉት መንገደኞች ላይ ውሳኔ የሚሰጠው፣ በየሁለት ሳምንታቱ በሚያደርገው ግምገማ መሰረት ነው።ኮቪድ-19 ባለፈው ዓመት በቻይና ከተዛመተበት ጊዜ አንስቶ፣ ወደ 10.5 ሚልዮን የሚጠጉ ሰዎች፣ በቫይረሱ ተይዘዋል። የሞቱት ደግሞ 500ሺህ ናቸው።
0
bd642ad86fccae0edad47ef3c4252c56
6f5c30dbf825caf22b37420fd19061ce
በማዕከላዊ አፍሪካ አዲስ ታጣቂ ቡድን ተፈጠረ
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 29 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ፈረንሳይ በሰሜን አፍሪካ የአል ቃይዳን መሪ መግደሏን አስታወቀች።የሃገሪቱ መከላከያ ሚኒስትር ፍሎረንስ ፓርሊ በማሊ በተካሄደ ዘመቻ በሰሜን አፍሪካ የቡድኑ መሪ የሆነው አብድልማሌክ ድሮክዴል መገደሉን ተናግረዋል።በዘመቻው የእርሱ የቅርብ አጋር የሆኑ የቡድኑ አባላት መገደላቸውንም ነው የተናገሩት።ግለሰቡ በሰሜን አፍሪካ በተለይም በሳህል ቀጠና አካባቢ ከቡድኑ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ታጣቂ ቡድኖች የማደራጀትና የመምራት ሃላፊነትን ይወጣ ነበር ተብሏል።ቡርኪና ፋሶን ጨምሮ በአንዳንድ ሃገራት የደረሱ ጥቃቶችን ማቀናበሩንም መረጃወች ያመላክታሉ።ወደ ሰሜን አፍሪካ ከመምጣቱ አስቀድሞ በአፍጋኒስታን እና በኢራቅ ይንቀሳቀስ ነበርም ነው የተባለው።በፈረንጆቹ 2007 በአልጀሪያ በደረሰውና 22 ሰዎችን ለህልፈት በዳረገው የሽብር ጥቃት በሃገሪቱ ፍርድ ቤት በሌለበት የሞት ፍርድ ተበይኖበት ነበር።ፈረንሳይ በወሩ አጋማሽ አካባቢ በማሊ ይንቀሳቀስ የነበረን የአይ ኤስ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዥ መያዟን መግለጿ ይታወሳል።ምንጭ፦ ቢቢሲ
0
e4f89bf4e58cdb5436ea3e069407e0ee
27ca29905b6bf99223953ef7cfd91356
ምክር ቤቱ ልዩ ፓስፖርት ለያዙ ሰዎች ቪዛን ለማስቀረት የሚያስችል የስምምነት ረቂቅ አዋጅን ጨምሮ በርካታ አዋጆችን አፀደቀ
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ በጀመረው 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ አምስት ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ለተጨማሪ እይታ ለሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች መራ።ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው የዓመቱ የመጀመሪ ስብሰባው የኢትዮጵያ መንግሥት ከብራዚል፣ ከኳታር፣ ስፔንና ከማላዊ ሪፓብሊክ ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር የደረሰባቸውን ስምምነቶች ለማጽደቅ በቀረበ ረቂቅ አዋጅ ላይ መክሯል።በኢትዮጵያና በብራዚል መንግሥታት መካከል በትምህርት ዘርፍ ትብብር ለማድረግና የአየር አገልግሎት ስምምነትን ለማጽደቅ የቀረበ ረቂቅ አዋጅን ለተጨማሪ እይታ ለትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መርቶታል።ስምምነቱ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን የዕውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግር በማጠናከር ለብሄራዊ ኢኮኖሚ ያለውን ፋይዳ በጥልቀት እንዲዳስስ ምክር ቤቱ ለቋሚ ኮሚቴው እንዲመራ አድርጓል።በተመሳሳይ በአየር አገልግሎት መስክ ሁለቱ አገራት የደረሱት ስምምነት የአየር መንገዱን ዓለማቀፋዊ የገበያ ድርሻ ከማጠናከር አኳያ የሚኖረውን ጠቀሜታ በጥልቀት በቋሚ ኮሚቴው እንዲታይ መርቶቷል።በሌላ በኩል በኢትዮጵያና በኳታር መንግሥታት መካከል የተደረገውን የትብብር የጋራ ኮሚቴ ማቋቋሚያ ስምምነትን ለማጽደቅ የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ የውጭ ጉዳይ፣ መከላከያና ደህንነት ቋሚ ኮሚቴ በጥልቀት እንዲመለከተው ተመርቷል።ቋሚ ኮሚቴውም ስምምነቱ የሁለቱን አገራት ኢኮኖሚያዊ ትብብር ለማጠናከር ከሚኖረው ፋይዳ ባለፈ ሁለንተናዊ ጠቀሜታው በጥልቀት ይመለከተዋል።ምክር ቤቱ በዛሬ ውሎው በኢትዮጵያና ስፔን መንግሥታት መካከል የተደረሰውን የአየር አገልግሎት ስምምነት ለማጽደቅ የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ የትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በጥልቀት እንዲመለከተው ተደርጓል።በተጨማሪም ምክር ቤቱ በኢትዮጵያና በማላዊ ሪፐብሊክ መንግሥታት መካከል የተደረገውን የኢኮኖሚ፣ የንግድ፣ የባህልና የቴክኒክ ትብብር ስምምነትረቂቅ አዋጅ ተጨማሪ ምልክታ እንዲደረግበት ለውጭ ጉዳይ፣ መከላከያና ደህንነት ቋሚ ኮሚቴ ተመርቷል።የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ትናንት የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ለሁለቱም ምክር ቤቶች ያደረጉት የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ የቀረበውን የድጋፍ ሞሽን አጽድቋል። (ኢዜአ)
0
3bcf5db65046d4a1023663ee835a2e6f
4646ac4970408a6ed503a74d7733fbdf
አኅጉራዊው የመንገድ ፈንድ ማኅበር መቀመጫ አዲስ አበባ ሊሆን ነው
አዲስ አበባ፣ ህዳር 9፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በ4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ከ118 ኪ.ሜ በላይ ርዝመት ያላቸው የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን ለማከናወን ውል ተፈራረመ፡፡ባለስልጣኑ ከ118 ኪ.ሜ በላይ ርዝመት ያላቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች የውስጥ ለውስጥ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን ለማከናወን ነው ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ጋር በዛሬው ዕለት ውል የተፈራረመው፡፡የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሞገስ ጥበቡ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ዮናስ አያሌው የውል ስምምነቱን ተፈራርመዋል፡፡ግንባታቸውን ለማካሄድ የኮንትራት ውል ከተገባላቸው 8 የመንገድ ፕሮጀክቶች ውስጥ 50 ኪ.ሜ የሚሆነው በአስፋልት ኮንክሪት የሚሰራ ሲሆን ቀሪው 68 ነጥብ 4 ኪ.ሜ የሚሆነው ደግሞ በኮብል ንጣፍ የሚከናወን ይሆናል ተብሏል፡፡የመንገድ ፕሮጀክቶቹን ገንብቶ ለማጠናቀቅ በአማካኝ ከ12 እስከ 19 ወራት የተያዘላቸው ሲሆን ለግንባታ ወጪያቸውም ከ 4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ እንደተመደበላቸው ኢንጂነር ሞገስ ጥበቡ ገለጸዋል ፡፡የመንገድ ፕሮጀክቶች በቦሌ አራብሳ፣ በየካ ጣፎ፣ በጀሞ ጋራ ፣በኮዬ ፈጬ እና በጨፌ ኮንዶሚኒየም ቤቶች አካባቢዎች የሚገነቡ ሲሆን እያንዳንዳቸው ከ 11 እስከ 38 ነጥብ 9 ኪ.ሜ የሚደርስ ርዝመት እንዳላቸውም ከአዲስ አበባ ፕሬስ ሴክሬታሪያት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡የመንገድ ፕሮጀክቶቹ ሙሉ በሙሉ ግንባታቸው ሲጠናቀቅ ለጋራ መኖሪያ ቤት ተጠቃሚዎች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖራቸው የተጠቆመ ሲሆን የመንገድ ፕሮጀክቶቹ ጥራታቸውን ጠብቀው በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ አስፈላጊውን ድጋፍ እና ክትትል እንደሚያደርግ ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ዮናስ አያሌው በበኩላቸው ኮርፖሬሽኑ የመንገድ ፕሮጀክቶቹን በተያዘላቸው የኮንትራት ጊዜ በጥራት አጠናቆ ለማስረከብ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
0
f6b6a193c073a3e5d5ee42bb887ecc19
1271ea0fe3c032fd9d3cdbe97199044c
የሶማሌ ክልል የመጀመሪያው የጥናት ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው
አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 16 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)የፌደራል የዴሞክራሲ ተቋማት የጋራ የምክክር መድረክ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።በመድረኩ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ፣ ምክትል አፈ ጉባኤ ሽታዬ ምናለ፣ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት መአዛ አሸናፊ እንዲሁም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራሮችና ለህዝብ ተወካዮች ተጠሪ የሆኑ የዴሞክራሲ ተቋማት እየተሳተፉ ነው፡፡አቶ ታገሰ ጫፎ የምክክር መድረኩ እስካሁን የተከናወኑ ስራዎችና በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ በመምከር ለቀጣይ ስራ ጥሩ መሰረት የሚጣልበት መሆኑን ተናግረዋል።የሶማሌ ክልል ለውጡን ተከትሎ ቀደም ሲል በክልሉ የነበሩ ተግዳሮቶችን በመፍታት የተሻለ የሰላምና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን ማረጋገጥ መቻሉን የጠቆሙት አፈ ጉባኤው ምክር ቤቱ ለክልሉ የሚያስፈልገውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልፀዋል።የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ዑስማን በበኩላቸው÷ በኢትዮጵያ አስተማማኝ መሰረት ያለው የዴሞክራሲ ስርአት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የዴሞክራሲ ተቋማት ሚና እንዲያድግ ተቋማቱ ያሉባቸውን ችግሮች ለመፍታት ተኩረት ሰጥቶ መረባረብ ይገባል ብለዋል።በሀገሪቱ የዴሞክራሲ ተቋማት ያለባቸውን ሀላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ ለማስቻል ተቋማዊ አደረጃጀታቸውንና ነፃነታቸውን በማጠናከር በአሰራር፣ በሰው ሀይልና በቴክኖሎጂ መገንባት እንደሚገባም አንስተዋል፡፡የምክክር መድረኩ ለሁለት ቀናት የሚካሄድ ሲሆን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ5 አመት ረቂቅ ስትራቴጂ፣ የምርጫ ቦርድ ሪፎርምና በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን የሪፎርም ስራዎች ላይ ያተኮሩ ፅሁፎች ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸው የሶማሌ ክልል ቴሌቪዥን ዘግቧል፡፡ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
0
202b6bb92435d6e951e30576c09668b2
03f2395e4a2dee90f87c8a58573d62aa
ድርቁ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል በርትቷል
በሶማሌ ክልል ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሕጋዊ እውቅና ያላቸው አምስት የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ለመሥራት ጥቅምት 25/2012 ውይይት ማድረጋቸው ታወቀ።ድርጅቶቹ በሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ጽሕፈት ቤት ባደረጉት ውይይት በቀጣይ በጋራ የሚሠሩባቸውን ጉዳዮች በጹሑፍ የሚያዘጋጁ አምስት አባላት መሰየማቸውን የሶማሌ ዴሞክራሲዊ ፓርቲ አስታውቋል።በውይይቱ ላይ የተሳተፉት ፓርቲዎች የዲል ወቤ ሕዝቦች ዴሞራሲያዊ ንቅናቄ፣ዱቤና ደግነ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የምዕራብ ሶማሌ ዴሞክራሲ ፓርቲ፣ሶማሌ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲና የዴሞክራሲና ነፃነት ጥምረት መሆናቸው ዋልታ ዘግቧል።ከዚህ ቀደም በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ብሔራዊ ፓርቲዎች አብሮ ለመሥራት መስማማታቸው ይታወሳል።
0
cc99d3d25d33430802d323d7a81f91b0
8bb42ceb70831d362552351c2dc28528
ፋርማሲዎች የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ሊጀምሩ ነው፡፡
ባሕር ዳር፡ ሚያዝያ 24/2012 ዓ.ም (አብመድ) ከወራት በፊት የተከሰተው የኮሮና ቫይረስ በመላው ዓለም በመሠራጨት ለሕዝብ የጤና ስጋት ከሆነ በኋላ የየሀገራቱን የጤና ተቋማት አቅም ክፉኛ ፈትኗል፡፡ ቫይረሱ በኢትዮጵያ መከሰቱ ከተሰማ በኋላ በኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የተጀመረው ምርመራ እየሰፋ እስከ ክልሎች ደርሷል፡፡ አልፎ አልፎም በየአካባቢው የሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የቫይረሱን ምርመራ ለመጀመር የሚያስችላቸው አቅም ላይ እየደረሱ ነው፡፡በአማራ ክልል የኮሮና ቫይረስ ምርመራ በማድረግ የአማራ ክልል የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ቀዳሚው ነው፡፡ በክልሉ ሙያዊ ድጋፍ እየተደረገላቸየጎንደር ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የመመርመሪያ ማሽን አስገብቶ፣ አስፈላጊውን ክፍል አዘጋጅቶ እና ማረጋገጫ አግኝቶ ወደ ሥራ እየገባ ነው፤ የአማራ ክልል የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የላብራቶሪ ዳይሬክተር ማንአምኖት አገኝ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲም የብቃት ማረጋገጫ ለማግኝት በባለሙያዎች መታየቱን ገልጸዋል፡፡ በቀጣይም ‘‘የወልድያ፣ ደሴ፣ ደብረ ብርሃን፣ ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እና የደብረ ማርቆስ ሆስፒታል ሥራ ይጀምራሉ’’ ብለዋል፡፡ የአማራ ክልል የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ደሴ ቅርንጫፍም በቅርቡ የኮሮና ቫይረስ ምርመራ እንደሚጀምር አቶ ማንአምኖት ተናግረዋል፤ ለሁሉም ባለሙያዎች ስልጠና መሰጠቱንም ገልጸዋል፡፡በክልሉ የኮሮና ቫይረስ ምርመራ እየተደረገላቸው ያሉት የኅብረተሰብ ክፍሎች በቫይረሱ የሚጠረጠሩ እና ከእነርሱ ጋር ግንኙነት አላቸው ተብሎ የሚታሰቡ ናቸው፡፡ በክልሉ ያለው የመመርመሪያ ላብራቶሪ እነዚህን ተጠርጣሪዎች ሙሉ በሙሉ እየመረመረ መሆኑን ዳይሬክተሩ በተለይም ለአብመድ ተናግረዋል፡፡ በቀጣይም በየአካባቢው የሚቋቋሙት መመርመሪያ ማዕከላት አካባቢያዊ ትስስር ተፈጥሮላቸው በቅርብ የሚገኙ ናሙናዎችን ይመረምራሉ ተብሏል፡፡ ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ሲፈጠር ደግሞ ኢንስቲትዩቱ ድጋፍ ያደርጋል፡፡እስከቅርብ ጊዜ ድረስ በክልሉ ናሙና የሚሰበሰቡት የኢንስቲትዩቱ ባለሙያዎች ብቻ እንደነበሩም ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡ በቅርቡ በየዞኑ ለተመረጡ ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጥቷል፤ አስፈላጊው የጥንቃቄ ቁሳቁስ ከተሟላላቸው ወደ ሥራ እንደሚገቡም አቶ ማንአምኖት ተናግረዋል፡፡ የጥንቃቄ ቁሳቁሱን ለማሟላት ከወረዳ እስከ ክልል በተቀናጀ መንገድ መሥራት እንደሚያስፈልግም ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ዘጋቢ፡- ታዘብ አራጋው
0