query_id
stringlengths
32
32
passage_id
stringlengths
32
32
query
stringlengths
2
182
passage
stringlengths
137
1.88k
label
int64
0
1
c43652cd62aef52661a1dca06bedb180
57f46a4d93d88333d36fa305f3d70932
ድሬዳዋ ከተማ አሰልጣኙን በቋሚነት አስቀጥሏል
ድሬዳዋ ከተማ የቀድሞ የመሐል ተከላካዩን ወደ ስብስቡ ቀላቅሏል፡፡ለድሬዳዋ ከተማ በ2011 የተጫወተው ፍቃዱ ደነቀ አዲሱ ፈራሚ ሆኗል። የቀድሞው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተከላካይ የባንክን መፍረስ ተከትሎ በመቐለ እና ድሬዳዋ የአንድ ዓመት ቆይታ ካደረገ በኋላ በተሰረዘው የውድድር ዓመት ደግሞ በወልዋሎ ሲጫወት ቆይቶ ለአሰልጣኝ ፍሰሀ ጡዑመልሳኑ ክለብ በአንድ ዓመት ውል ፈርሟል።
0
6b369a7f19b13f6293137c26c25b5deb
1f0b1f5af0c69aee5b6d6f64df2053dc
የመገናኛ ውሀ ልማት – ቦሌ ወረዳ 17 ጤና ጣቢያ የመንገድ ፕሮጀክት ግንባታ በተያዘው በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) 42 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የደብረ ብርሃን አንኮበር የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመፋጠን ላይ መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን አስታወቀ።በመንገድ ፕሮጀክቱ የስራ እንቅስቃሴ የአፈር ሙሌትና፣ ድልዳሎ፣ የውሃ መፋሰሻ ቱቦ ቀበራ የሰብ ቤዝ ስራ እንዲሁም የቤዝ ኮርስ ማምረት ስራ እየተካሄደ ይገኛልም ነው የተባለው።የደብረብርሃን አንኮበር የመንገድ ፕሮጀክት ስራ ከ1 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነባ ሲሆን ወጪው በመንግስት የሚሸፈን ነው።በቀጣይ ሶስት ወራት ውስጥም ወደ አስፋልት ንጣፍ ስራ ይሸጋገራል ነው የተባለው።መስመሩ ከሚያስተናገደው የተሽከርካሪ ብዛት፣ ማህበራዊና ኢኮኖማዊ ፋይዳ አኳያ እንዲሁም ከከተማው ቀጣይ እድገት ጋር አልሞ በአስፋልት ደረጃ እንዲገነባ እየተደረገ መሆኑ ተጠቁሟል።የፕሮጀክቱ የጎን ስፋት በዞን ከተማ ደብረብርሃን 30 ሜትር ፣ በወረዳ አንኮበር 17 ሜትር በቀበሌ 12 ሜትር ሲሆን በገጠር 10 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተሰራ ነው።በተጨማሪም ግንባታው በውስጡ የመንገድ አካፋይ፣ እግረኛ መሄጃ እና የመንገድ አቃፊ ትከሻ በግራ እና በቀኝ እንደሚያካትት ከኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ያገኘኘው መረጃ ያመለክታል።ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
0
c6801694cde180ac47c22dc39f7751a4
fb71f8ce6ae69ff72e12ba2cedf6a934
​ከፍተኛ ሊግ | የዛሬ ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ተጠናቀዋል
ትናንት በ5ኛ ሳምንት ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡናን አስተናግደው ያለ ጎል በአቻ ውጤት በተጠናቀቀው ጨዋታ ድሬዎች ሁለት ወሳኝ ተጫዋቾቻቸውን በጉዳት አጥተዋል።የውድድር ዓመቱን ብዙ ጎሎችን በማስተናገድ አንድ ጨዋታ አሸንፎ፣ በአንድ ጨዋታ በአቻ ውጤት አጠናቆ ሦስት ጨዋታ ላይ ሽንፈት በማስተናገድ አጀማመሩ ያላማረለት ድሬዳዋ ከተማ በርከት ያሉ ተጫዋቾች በጉዳት አለመኖራቸው በቡድኑ ውጤት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያደረሰ እንደሆነ ይነገራል። ምንም እንኳ አንጋፋው ግብጠባቂ ሳምሶን አሰፋ ከረጅም ጊዜ ጉዳቱ በኋላ አገግሞ ወደ ሜዳ መመለሱ መልካም ዜና ቢሆንም በአንፃሩ የክለቡ የቡድኑ ሁለት ወሳኝ ተጫዋቾች ጉዳት ማስተናገዳቸው አሳዛኝ ዜና ሆኗል።ከድሬዳዋ ከተማ ጋር በግሉ ስኬታማ ዓመታትን እያሳለፈ የሚገኘው የኃላ ደጀኑ በረከት ሳሙኤል ጎድኑ ላይ የመሰንጠቅ ጉዳት አጋጥሞት ከእነ ህመሙ ወገቡን በፋሻ ታስሮ ወደ ሜዳ ቢገባም እስከ 72ኛው ደቂቃ ድረስ ተጫውቶ ከዚህ በላይ መቀጠል ባለመቻሉ በዘሪሁን አንሼቦ ተቀይሮ መውጣት ችሏል።ሌላኛው የቡድኑ ወሳኝ ተጫዋች እየሆነ መምጣቱን በዚህ ዓመት በተጫወተባቸው ጨዋታዎች ላይ አቅሙን እያሳየ የሚገኘው ወጣቱ አጥቂ ሳሙኤል ዘሪሁን በጨዋታው የመጨረሻ ደቂቃ 86ኛው ደቂቃ ላይ ባጋጠመው የእግር ጉዳት በዳኛቸው በቀለ ተቀይሮ ለመውጣት ተገዷል።ከዚህ ቀደም በጉዳት ሆነው ከሜዳ ከራቁት ተጫዋቾች በተጨማሪ የሁለቱ ቁልፍ ተጫዋቾች በጉዳት ምክንያት በቀጣይ ሳምንታት አገልግሎት የማይሰጡ መሆናቸው ለድሬዳዋዎች የውድድር ዓመቱን ፈታኝ እንዳያደርግባቸው ተሰግቷል። የጉዳት መጠናቸው ለምን ያህል ጊዜ ከሜዳ እንደሚያርቃቸው ለጊዜው የታወቀ ነገር ባይኖርም ለሳምንታት ከሜዳ እንደሚርቁ ተገምቷል።በድሬዳዋ ከተማ በአሁኑ ወቅት ያሬድ ሀሰን፣ ምንያህል ተሾመ እና ረመዳን ናስር በጉዳት የማይጫወቱ ሌሎች ተጫዋቾች ናቸው።
0
de8ef1f20a01a38df120acfce333ab87
66e7165d285820c946719ca3957fea68
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ዛሬ በምክር ቤቱ ተገኝተው በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ይሰጣሉ
ትውልዱ ለነገ የሚያስፈልገውን የእውቀት ስንቅ ለመያዝ ዛሬ ላይ እርስ በርስ መማማር እንዳለበት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ጥሪ አቀረቡ።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት ዛሬ ማለዳ በአምቦ መሰናዶ ትምህርት ቤት ተገኝተው ለተማሪዎች ንግግር ባደረጉበት ጊዜ ነው።ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ እንደተናገሩት፤ አምቦ የነጻናትና የትግል ማዕከል ናት፤ አሁን የተገኘው ነጻነትም የወጣቶች መስዋዕትነት ውጤት ነው።የተከፈለው መስዋዕትነትም በከንቱ ሳይቀር አሁን ላይ በአገሪቱ የእኩልነትና ነጻነት ጮራ እንዲፈነጥቅ ማስቻሉን ገልጸዋል።”አሁን ያለንበት ጊዜ ነጻነታችን በትግል ያገኘንበት ነው” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ነገን እያሰቡ መዘጋጀት ካልተቻለ ባለንበት ሁኔታ ለረዥም ጊዜያት መቆየት እንደሚያስቸግር ጠቁመዋል።ተማሪዎች ከታሪክ መልካም መልካምን በመማር አገሪቱን በመገንባት የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል።ይህ ትውልድ ነገ የሚመጣውን ተረድቶ እርስ በርስ መማማር ከቻለ ከራስ አልፎ ለሌሎች መትረፍ እንችላለን ሲሉም ተማሪዎቹን መክረዋል።ለተማሪዎች ክላሽ መሸከም ለነገ ትርጉም ስለማያመጣ ትኩረታቸው ደብተር እና እስክርቢቶ መያዝ ላይ እንዲሆንም አሳስበዋል።”ትናንት ነጻነት ስለሚያስፈልገን ክላሽ ተሸክመን ነበር” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ፤ አሁን ላይ ነጻነት በመስፈኑ ተማሪዎች የሚከፍሉት መስዋዕትነት ሌት ከቀን ማጥናት ብቻ እንደሆነ ተናግረዋል።በመካከላቸው የማያስፈልጉ ነገሮች እንዳይፈጠሩ መጠንቀቅ እንዳለባቸውም መክረዋል። (የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት)
0
eadb468d76c6022e0792b806e6865b4a
fe3d805ce59393ae9e9e98949c773a01
76 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከኬንያ ተመለሱ
ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ሃገራቸውን ጥለው በመሰደድ ኢትዮጵያውያን ቀዳሚውን ደረጃ የያዙ ሲሆን ዋነኛ የስደት መዳረሻቸውም ሳውዲ አረቢያ መሆኗ ተገለፀ፡፡ የአለማቀፉ የስደተኞች ተቋም (IOM) ከትናንት በስቲያ ባወጣው ሪፖርቱ፤ በሚያዚያ ወር 2011 ብቻ ወደተለያዩ ሀገራት በህገወጥ መንገድ ከተሰደዱ የምስራቅ አፍሪካ ዜጐች መካከል ኢትዮጵያውያን 68 በመቶ ድርሻ እንዳላቸውም ተጠቁሟል፡፡ በስደት በሁለተኛነት የተቀመጡት ሶማሊያውያን ሲሆኑ 27 በመቶ ድርሻ አላቸው ብሏል - ሪፖርቱ:: ኢትዮጵያውያን ስደተኞቹ የተለያዩ የስደት መስመሮችን የሚጠቀሙ ሲሆን አንዱና ዋነኛው በሆነው የጅቡቲ መስመር ከሚጓዙ ስደተኞች መካከል 84.3 በመቶ ያህሉ መዳረሻቸውን ሳውዲ አረቢያ ያደረጉ ናቸው ተብሏል፡፡ ጅቡቲም ከምታስተናግዳቸው ስደተኞች ውስጥ 99.6 በመቶ ኢትዮጵያውያን ናቸው ብሏል - ሪፖርቱ፡፡ ጅቡቲን መሸጋገሪያ አድርገው ከሚጠቀሙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች መካከል 58.8 በመቶዎቹ ወንዶች ሲሆኑ፤ ከእነዚህ ውስጥ 18.5 በመቶዎቹ ለወጣትነት እድሜ ያልደረሱ ታዳጊዎች መሆናቸውን ሪፖርቱ ጠቁሟል፡፡ 96 በመቶ የሚሆኑት ስደተኞች፤ የስደታቸው ምክንያት የኢኮኖሚ ችግር መሆኑን በጥናት ማረጋገጡን የጠቆመው አይ ኦ ኤም፤ 4 በመቶዎቹ “በግጭት ምክንያት ነው የምንሰደደው” የሚል ምላሽ ሰጥተውኛል ብሏል፡፡ ከእነዚህ ስደተኛ ኢትዮጵያውያን 83 በመቶ የሚሆኑት በእግራቸው ለበርካታ ቀናት ተጉዘው ጅቡቲ እንደሚደርሱ፣ በመኪና የሚጓዙት 10 በመቶ ያህል ብቻ እንደሆኑም ተመልክተናል ብሏል - ተቋሙ በሪፖርቱ፡፡ ኢትዮጵያውያን የሚጠቀሙት ሌላኛው የስደት መስመር በኤልዳሃር አድርጐ ሱዳን የሚደርሰው ሲሆን በዚህ መስመር ከሚጓጓዙ የምስራቅ አፍሪካ ዜጐች 82 በመቶ ድርሻ ኢትዮጵያውያን ሲወስዱ፤ 7 በመቶ ሶማሊያውያን፣ 4 በመቶ ደግሞ ኤርትራውያን ቀሪዎቹ የተለያዩ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ዜጐች እንደሆኑ ሪፖርቱ አመላክቷል፡፡
0
61ecedf874f7a1ecfac8510332ad657b
e11304f1ce3674a7539f88f2089b56ae
ግጭት ባለባቸው አካባቢዎች በሴቶችና በሕፃናት ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃት እንዲቆም ተጠየቀ
የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የክልሉን ሰላም ለማረጋገጥ ልዩ ትኩረት በመስጠት እንደሚሰራ ገልጸዋል።የክልሉ መንግስት ካቢኔ ትላንት ባካሄደው 4ኛ መደበኛ ስብሰባው ወቅታዊ ሁኔታዎችን ጨምሮ በሌሎች ጉዳዮች ላይ በመወያየት ውሳኔዎችን ማሳለፉን የክልሉ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ለዋልታ በላከው መግለጫ አስታውቋል።ካቢኔው በሰላም ጉዳይ ላይ ትኩረት ሰጥቶ የተወያየ ሲሆን በተለይም በምእራብ ኦሮሚያ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች ላይ ባጋጠመው የፀጥታ ችግር ዙሪያ መክሯል ነው የተባለው።በዚህም ያጋጠመውን የፀጥታ ችግር ተከትሎ እየደረሰ ያለው የሰው ህይወት መጥፋት እና የዜጎች መፈናቀል እንዲቆም ብሄራዊ የደህንነት ምክር ቤት ያሳለፈውን ውሳኔ ሙሉ በሙሉ እንደሚደግፍ እና ስራ ላይ እንዲውል እንደሚሰራ አስታውቋል።የክልሉ ህዝብ የህግ የበላይነት እንዲከበር እና የሀገሪቱ ሰላም እንዲሰፍን እያቀረበ ባለው ጥያቄ መሰረትም እርምጃዎች መውሰድ መጀመራቸውን እና ይህም ተጠናክሮ የሚቀጠል መሆኑን ገልጿል።እስካሁን በተወሰደው እርምጃም በዜጎች ላይ አሰቃቂ ወንጀል የፈፀሙ ከ200 በላይ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን እና የተቀሩትንም በቁጥጥር ስር በማዋል ለህግ የማቅረብ ስራ እንደሚሰራ አስታውቋል።የሰላም ጉዳይ ከሁሉም ጉዳይ በላይ ቅድሚያ የሚሰጠው በመሆኑ በግጭቱ ምክንያት ችግር ያጋጠማቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች ለመርዳት ሰፋፊ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም የክልሉ መንግስት አስታውቋል።ከቤት ንብረታቸው ለተፈናቀሉ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚደረገው ድጋፍም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም ገልጿል።በዜጎች ላይ እየተፈፀመ ያለው ግድያ እንዲቆም እና ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ለሚሰሩ የፀጥታ ሀይሎች ድጋፍ እንደሚደረግም ነው የክልሉ መንግስት ካቢኔ ያስታወቀው።ችግሩን ከምንጩ ለመቅረፍ እየተከናወነ ባለው ስራ ውስጥ ህብረተሰቡ ለጥፋት ሀይሎች በር ለመክፈት የሚጥሩትን በንቃት እንዲጠብቅ እና እንዲከላከለም ጥሪ አቅርቧል።በተጨማሪም ክልሉ መንግስት ካቢኔ የኦሮሚያ ክልል የመንግስት ሰራተኞችን እንደ አዲስ ለመመደብ የቀረበ ረቂቅ የውሳኔ ሀሳብ ላይም ተወያይቶ አቅጣጫ አስቀምጧል።
0
58559e9ae641fd009dfc933f6ca764da
7f9324f00362689548c04f23b1683dff
ፕሪሚየር ሊግ ፡ አዳማ ከተማ ወደ መሪነት ሲመለስ መከላከያ ደረጃውን በከፍተኛ ደረጃ አሻሽሏል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ መካከለኛ-ሰሜን ዞን 20ኛ ሳምንት ቀሪ ጨዋታዎች ዛሬ ተካሂደው መከላከያ እና ልደታ ድል ቀንቷቸዋል፡፡ ቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ ሽንፈት አጋጥሞት ወደ ማጠቃለያ ውድድሩ የመግባት ተስፋው ጨልሞበታል፡፡በ9፡00 ላይ ቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲን የገጠመው ልደታ ክፍለከተማ 1-0 በማሸነፍ ደረጃውን አሻሽሏል፡፡ በሁለተኛው አጋማሽ የልደታን የድል ግብ ከመረብ ያሳረፈችው ፍጹም ኪሮስ በፍፁም ቅጣት ምት ነው፡፡ ጨዋታው በቂ የግብ እድሎች ባይስተናገዱበትም በሁለቱም ቡድኖች በኩል ድንቅ እንቅስቃሴ ፣ የኳስ ፍሰት እና የተጫዋቾች የግል ክህሎቶች ታይተውበታል፡፡በ2ኛው ዙር ውጤቱ ያሽቆለቆለው ቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ 16 ነጥቦች ላይ ረግቶ ወደ ማጠቃለያው ዙር የማለፍ ተስፋው ጨልሟል፡፡ ኤሌክትሪክ በቀጣዩ ሳምንት 1 ነጥብ ካገኘ ወደ ማጠቃለያ ዙር ማለፉን ያረጋግጣል፡፡11፡30 ላይ መከላከያ ቅዱስ ጊዮርጊስን ሁለት ጊዜ ከኋላ ተነስቶ ድል አድርጓል፡፡ ከአመቱ ምርጥ ጨዋታዎች አንዱ የሚያሰኝ ድንቅ እንቅስቃሴ በታየበት ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ በሄለን ሰይፉ የፍጹም ቅጣት ምት ጎል ቀዳሚ ቢሆንም የምስራች ላቀው ከቀኝ መስመር የተገኘውን ቅጣት ምት በግሩም ሁኔታ አስቆጥራ የመጀመርያው አጋሽ 1-1 ተጠናቋል፡፡ የሁለተኛው አጋማሽ እንደተጀመረ ተቀይራ ወደ ሜዳ የገባችው ሜሮን አብዶ በጥሩ ሁኔታ ተመስርቶ የመጣውን ኳስ ከርቀት በመምታት ግሩም ግብ አስቆጥራ ቅዱስ ጊዮርጊስን በድጋሚ መሪ አድርጋለች፡፡ከግቡ መቆጠር በኋላ ጫና ፈጥረው የተንቀሳቀሱት መከላከያዎች በመጨረሻም ሰምሮላቸው ምስር ኢብራሂም ባስቆጠረቻቸው ተከታታይ ግቦች 3-2 በሆነ ማሸነፍ ችለዋል፡፡ ሎዛ አበራ (2) መሰሉ አበራ (2) ብሩክታዊት ግርማ (ፍቅም) ፣ ብዙሃን እንዳለ ፍፁም ኪሮስ (ፍቅም) ምስር ኢብራሂም (2) ፣ የምስራች ላቀው | ሄለን ሰይፉ (ፍቅም) ፣ ሜሮን አብዶ ልደታ ክ/ከተማ ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (አአ ስታድየም) ደደቢት ከ ኢትዮ ኤሌክትሪክ (አአ ስታድየም) ሙገር ሲሚንቶ ከ ቅድስት ማርያም ዩኒቨርሰቲ (አአ ስታድየም) ዳሽን ቢራ ከ መከላከያ (ጎንደር) ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ኢትዮጵያ ቡና (አአ ስታድየም)
0
272073d2a19b6f06c3303e020e06f6fe
7ee05a667932a80e03ea53d240c7b070
በአዲስ አበባ ከ2 ሺህ 300 በላይ ተገጣጣሚ የመማሪያ ክፍሎች ሊገነቡ ነው
አዲስ አበባ ፣ጥቅምት 12 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በግለሰብ ቤት ውስጥ የተከማቸ ከ2 ሚሊየን በላይ አዲሱ የብር ኖት መያዙን ፖሊስ አስታወቀ።ጥቅምት 7 ቀን 2013 ዓ.ም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ልዩ ቦታው ዶምቦስኮ ትምህርት ቤት አካባቢ በግለሰብ ቤት ውስጥ የተከማቸ ገንዘብ ስለመኖሩ ህብረተሰቡ ለፖሊስ ባደረሰው መረጃ መሠረት መያዙ ተገልጿል።በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የልዩ ልዩ ወንጀሎች ምርመራ ቡድን ሀላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ይርጋ ተካ እንደገለፁት ÷ በህዝብ ጥቆማ የተያዘው 2 ሚሊየን 222 ሺህ አዲሱ የብር ኖት የተያዘው የብሄራዊ ባንክ መመሪያን በመተላለፍ በግለሰብ እጅ እንዲኖር ከሚፈቀደው በላይ ሆኖ በመገኘቱ ነው።ህብረተሰቡ የገንዘብ ዝውውር መመሪያውን በመተግበር ተባባሪ እንዲሆን እና መመሪያውን በመተላለፍ የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦችን እንዲጠቁም ጥሪ ማቅረባቸውንም ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።ወቅታቂ የገንዘብ ዝውውርን አስመልክቶ የባንክ አዋጅ 591/2008 እንደሚያስረዳው በአንድ ግለሰብ እጅ መገኘት ያለበት የብር መጠን 1ነጥብ 5 ሚሊየን እና ከዚያ በታች ሲሆን ይህንን ተላልፎ ከተጠቀሰው የብር መጠን በላይ ይዞ የተገኘ ግለሰብ ገንዘቡ እንደሚወረስ በግልጽ ተቀምጧል። የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
0
acc11ed819fe7c27682baf6ed43364e3
acc11ed819fe7c27682baf6ed43364e3
መቐለዎች ወደ አዲስ አበባ አላመሩም
በነገው ዕለት በኢትዮጵያ ዋንጫ ከፋሲል ከነማ ለመጫወት መርሃግብር የወጣላቸው መቐለ 70 እንደርታዎች እስካሁን ወደ አዲስ አበባ እንዳልተጓዙ ታውቋል።የሊጉ ቻምፒዮን ጨዋታው ወደሚካሄድበት አዲስ አበባ ያልተጓዘው የውድድሩ ስርዓት አልተከበረም በሚል ነው። በውድድሩ ስነ-ስርዓት ባለሜዳው በዕጣ መታወቅ እያለበት ጨዋታው በገለልተኛ ሜዳ እንዲካሄድ መወሰኑ አግባብ እንዳልሆነ የገለፁት የክለቡ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሽፈራው ተክለሃይማኖት ፌዴሬሽኑ መጀመርያ በዕጣ ይለያል ብሎ በደምቡ እንዳሰፈረው በዛ መሰረት መካሄድ እንዳለበት ገልፀዋል።በመቐለ ውሳኔ ምክንያት የዐፄዎቹ እና ምዓም አናብስት ጨዋታ የመካሄዱ ነገር አጠራጣሪ የሆነ ሲሆን አዳዲስ ለውጦችን ተከታትለን የምናቀርብ ይሆናል።
1
96dbec9a5f9b43778316d366efabed7c
70f191889fe0ec7de07ecaba6ee4c328
የህግ ማስከበሩን ተግባር ዓላማ ለዓለም አቀፉ ህብረተሰብ ለማስረዳት የተከናወነው የዲፕሎማሲ ስራ ውጤታማ እንደነበር ተገለጸ
የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የህዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ዝናቡ ቱኑ የመስሪያ ቤቱን የአንድ መቶ ቀናት እቅድን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫውን የሰጡ ሲሆን የህግ የበላይነትን ለማስጠበቅና በፍትህ ስርዓቱ የሚታዩ ማነቆዎችን ለመፍታት ተቋሙ ከመቼውም በላቀ ሁኔታ አገራዊ ለውጡን ለማስቀጠል የህግ እና የፍትህ ማሻሻያ ሰራዎችን በመስራት ላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡የወንጀል ድርጊቶችን ትኩረት ሰጥቶ በመከላከል ተቋሙ የተሰጠውን አገራዊ ኃላፊነት ለማሳካት የባለ አንድ ገጽ እቅድ በማዘጋጀት ወደ ተግባር መግባቱን ጠቁመዋል፡፡የሕግ የበላይነት አለመረጋገጥና ደካማ የፍትህ ሥርዓት፣ የሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ጥሰት፣ ደካማ የፍትህ አገልግሎት አሰጣጥ እና ሕገ ወጥነትና ስርዓት አልበኝነት በመከላከል እና በመቆጣጠር የሕግ የበላይነትና የፍትህ ሥርዓትን ግንባታን ማጠናከርና አስፈላጊነትን በእቅዱ መነሻ ሃሳቦች ዙሪያ አብራርተዋል፡፡የፍትህ አግልግሎት በማሻሻል እና የሰው ሃብት አቅም በመገንባት ሶስት ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በመስጠት በህዘዝብና በመንግሰት አመኔታን ያተረፈ ጠንካራ ተቋም ለመገንባት በመሰራት ላይ መሆኑንም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የባለአንድ ገጽ እቅድ በአገራችን የተጀመረውን ለውጥ ዳር ለማድረስ የሰብአዊ መብት ጥሰት በፈፀሙ ሰዎች የሕግ ተጠያቂነት የማረጋገጥ፣ የታራሚዎችን መብት አያያዝ ማሻሻል፣ የይቅርታና ምህረት አሰጣጥ ሥርዓቱን በተሟላ መልኩ ለመተግበር እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡በተጨማሪም በማህበራዊ ድረ-ገጽ የሚታዩ የጥላቻ ንግግር ወንጀል ላይ ሕግ ማውጣትና መተግበር እንዲሁም ሕገ ወጥነት፣ ስርዓት አልበኝነትና የመንጋ ፍትህን ለመቆጣጠር ከአሁን በፊት ታይተው የማይታወቁ ህጎችን የማርቀቅና የማሻሻል ስራዎችን አቅዶ ውጤታማ ለመሆን የሕግና የፍትህ አማካሪ ምክር ቤት በማጠናከርና የሰው ሀይል በማደራጀት በመስራት ላይ ይገኛልም ብለዋል፡፡ዳይሬክተሩ ከጋዜጠኞች ለተነሱ ወቅታዊ ጥያቄዎች ዙሪያ መልስ የሰጡ ሲሆን የወንጀል ፍትህ አስተዳደርን በማጠናከር የህዝብና የመንግስት ንብረት የሚዘውሩ ግለሰቦችን እና በመንግሰት ፕሮጀክቶች ላይ የሚደረገው ምርመራ ተጠናክሮ እንደሚቀጠልና ለዚህም ስኬት የመላው ህብረተሰብ ክፍል የነቃ ተሳትፎ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡
0
6a19fe21ea39203bcc03f8ec773ebd2d
fdad086afd4772872833ce888045070a
አመራሩ ህብረተሰቡን ጥያቄ በመመለስ ለልማትና ለዴሞክራሲ እንዲነሳ ማድረግ አለበት-ጠቅላይ ሚኒስትር
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ቅዳሜ ግንቦት 25 ቀን 2010 ዓ.ም. ባደረገው መደበኛ ስብሰባ የአገሪቱን የጸጥታ ሁኔታ ከገመገመ በኋላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ አጸደቀ፡፡ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ ረቂቁ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተልኮ መጽደቅ ይኖርበታል ሲሉም የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ኃለፊ አቶ ፍጹም አረጋ በትዊተር ገጻቸው ላይ አስፍረዋል፡፡የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የካቲት 9 ቀን 2010 ዓ.ም. ለሁለተኛ ጊዜ መታወጁ ይታወሳል፡፡
0
2e74f91e4d0f295c2fdf69ff86770622
e11304f1ce3674a7539f88f2089b56ae
ሕዝቡ አካባቢውን በንቃት እንዲጠብቅ የአማራ ክልል መንግስት ጥሪ አቀረበ
የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የክልሉን ሰላም ለማረጋገጥ ልዩ ትኩረት በመስጠት እንደሚሰራ ገልጸዋል።የክልሉ መንግስት ካቢኔ ትላንት ባካሄደው 4ኛ መደበኛ ስብሰባው ወቅታዊ ሁኔታዎችን ጨምሮ በሌሎች ጉዳዮች ላይ በመወያየት ውሳኔዎችን ማሳለፉን የክልሉ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ለዋልታ በላከው መግለጫ አስታውቋል።ካቢኔው በሰላም ጉዳይ ላይ ትኩረት ሰጥቶ የተወያየ ሲሆን በተለይም በምእራብ ኦሮሚያ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች ላይ ባጋጠመው የፀጥታ ችግር ዙሪያ መክሯል ነው የተባለው።በዚህም ያጋጠመውን የፀጥታ ችግር ተከትሎ እየደረሰ ያለው የሰው ህይወት መጥፋት እና የዜጎች መፈናቀል እንዲቆም ብሄራዊ የደህንነት ምክር ቤት ያሳለፈውን ውሳኔ ሙሉ በሙሉ እንደሚደግፍ እና ስራ ላይ እንዲውል እንደሚሰራ አስታውቋል።የክልሉ ህዝብ የህግ የበላይነት እንዲከበር እና የሀገሪቱ ሰላም እንዲሰፍን እያቀረበ ባለው ጥያቄ መሰረትም እርምጃዎች መውሰድ መጀመራቸውን እና ይህም ተጠናክሮ የሚቀጠል መሆኑን ገልጿል።እስካሁን በተወሰደው እርምጃም በዜጎች ላይ አሰቃቂ ወንጀል የፈፀሙ ከ200 በላይ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን እና የተቀሩትንም በቁጥጥር ስር በማዋል ለህግ የማቅረብ ስራ እንደሚሰራ አስታውቋል።የሰላም ጉዳይ ከሁሉም ጉዳይ በላይ ቅድሚያ የሚሰጠው በመሆኑ በግጭቱ ምክንያት ችግር ያጋጠማቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች ለመርዳት ሰፋፊ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም የክልሉ መንግስት አስታውቋል።ከቤት ንብረታቸው ለተፈናቀሉ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚደረገው ድጋፍም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም ገልጿል።በዜጎች ላይ እየተፈፀመ ያለው ግድያ እንዲቆም እና ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ለሚሰሩ የፀጥታ ሀይሎች ድጋፍ እንደሚደረግም ነው የክልሉ መንግስት ካቢኔ ያስታወቀው።ችግሩን ከምንጩ ለመቅረፍ እየተከናወነ ባለው ስራ ውስጥ ህብረተሰቡ ለጥፋት ሀይሎች በር ለመክፈት የሚጥሩትን በንቃት እንዲጠብቅ እና እንዲከላከለም ጥሪ አቅርቧል።በተጨማሪም ክልሉ መንግስት ካቢኔ የኦሮሚያ ክልል የመንግስት ሰራተኞችን እንደ አዲስ ለመመደብ የቀረበ ረቂቅ የውሳኔ ሀሳብ ላይም ተወያይቶ አቅጣጫ አስቀምጧል።
0
19f19cd24ab70fe60aec39c103485797
4a3c3827a4c25b0192ad698e84999af7
ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ለአገራቸው አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ የሚያስችል ሓሳብ አቀረቡ
ኢዜማ ኢትዮጵያውያን በሚኖሩባቸው ከ70 በላይ የአለም ሀገራት የአለማቀፍ የድጋፍ ማህበር እያደራጀ መሆኑን ትናንት በሰጠው መግለጫ አስታወቀ፡፡ ከተመሠረተ 5 ወራት ያስቆጠረው የኢትዮጵያ ዜጐች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በሀገር ውስጥ በ400 የምርጫ ወረዳዎች አባላትንና ደጋፊዎችን አደራጅቶ ለቀጣዩ ምርጫ ዝግጁ ማድረጉን በዚሁ መግለጫው ያስታወቀ ሲሆን፤ የአለማቀፍ ድጋፍ ማህበሩንም የሚያደራጀው በሀገር ቤት የተጠቀመውን የማደራጃ ስልት ተጠቅሞ መሆኑን አስገንዝቧል:: ኢትዮጵያውያን ይኖሩባቸዋል ተብለው በተለዩ ከ70 በላይ ሀገራት በየከተሞቹ የደጋፊ ማህበር ም/ቤት የሚቋቋም ሲሆን፤ የእነዚያ ም/ቤቶች አባላት የሆኑ ግለሰቦች አመራርነት ተመርጠው የክፍለ አለም ደጋፊ ማስተባበሪያ የሚኖረው አደረጃጀት ነው ተብሏል፡፡ ይህን አደረጃጀት ለመፍጠርም በየከተሞቹ የሚገኙ ደጋፊዎች መሠረታዊ ማህበራትን እንዲመሠርቱ ፓርቲው ጥሪ አቅርቧል፡፡ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በሀገር ውስጥ እንደሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሁሉ በሀገራቸው ጉዳይ እኩል ይመለከታቸዋል” ሲል ፓርቲው በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን በተመለከተ ባዘጋጀው ፖሊሲው ላይ ያስቀመጠ ሲሆን፤ እስካሁንም በሀገሪቱ እየታየ ላለው የለውጥ ተስፋ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ግዙፍ አስተዋጽኦ አበርክተዋል ብዬ አምናለሁ ብሏል፡፡ በቀጣይም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ጉዳይ የማይተካ ሚና እንደሚጫወቱ ፓርቲው በመግለጫው አመልክቷል፡፡
0
a1431f42dbcdf4fa432060040cc11cf8
5202b2cd391e4426f53b5079ab6c417a
የአሰልጣኞች አስተያየት | ሲዳማ ቡና 1-1 ኢትዮጵያ ቡና
ሲዳማ ቡና የ2013 የውድድር ዓመት ዝግጅቱን የሚጀምርበት ቀን ታውቋል።የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ2013 የውድድር አመት ታህሳስ 3 እንደሚጀምር የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አክሲዮን ማህበር ዛሬ ለክለቦች በላከው ደብዳቤ የገለፀ ሲሆን ክለቦችም ወደ ልምምድ መግባት እንዲችሉ ይፋ አድርጓል፡፡በዚህም መሠረት ለ2013 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ቅድመ ዝግጅት ለመጀመር ሲዳማ ቡና ቀኑን ይፋ ማድረጉን የክለቡ አሰልጣኝ ዘርአይ ሙሉ ለሶከር ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡ ጥቅምት 2 እና 3 የክለቡ ተጫዋቾች፣ አሰልጣኞች እና ጠቅላላ የቡድኑ አባላት የሜዲካል ምርመራ እንዲሁም የኮቪድ 19 ምርመራን በማድረግ ሁለቱንም የጤና ምርመራዎች አልፈው ነፃ የሚሆኑ አባላት በጠቅላላ ወደ ካምፕ ከገቡ በኃላ ጥቅምት 5 በሀዋሳ ስታዲየም ልምምዳቸውን ለመጀመር መዘጋጀታቸውን አሰልጣኙ ነግረውናል፡፡ሲዳማ ቡና ከመቐለ 70 እንደርታ እና ፋሲል ከነማ ቀጥሎ ሦስተኛው የዝግጅት ጊዜውን ያሳወቀ ክለብ ሆኗል፡፡
0
96293fb2e4a1f4208270341f54671292
96293fb2e4a1f4208270341f54671292
ዶክተር ወልዳይ አምሃ በተሽከርካሪ አደጋ ህይወታቸው አለፈ
ኢትዮጵያ ማይክሮ ፋይናንስ ዳይሬክተር የነበሩት ታዋቂው የምጣኔ ሃብት ባለሙያ ዶክተር ወልዳይ አምሃ ትናንት በደረሰባቸው የተሽከርካሪ አደጋ ህይወታቸው አለፈ።ዶክተር ወልዳይ ከሞጆ ወደ አዲስ አበባ በግል ተሽከርካሪያቸው በመጓዝ ላይ ሳሉ ከሻሸመኔ ወደ ሞጆ ይጓዝ ከነበረ ተሳቢ ኤሮትራክ ጋር በመጋጨታቸው አደጋው መድረሱ ተገልጿል።በአደጋው እርሳቸውን ጨምሮ የሶስት ሰዎች ህይወት አልፏል።በምስራቅ ሸዋ ዞን የሉሜ ወረዳ ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ምክትል ኮማንደር አስቻለው ዓለሙ እንደገለጹት፤ ከአደጋው በኋላ የኤሮ ትራኩ ሾፌር ተሰውሯል። ፖሊስ ሹፌሩን ለማግኘት ክትትል እያደረገ እንደሚገኝና የአደጋው መንስኤም በመጣራት ላይ ነው።ዶክተር ወልዳይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተባባሪ ፕሮፌሰር የነበሩ ሲሆን፤ የማይክሮ ፋይናስ ማህበርን ለ10 ዓመት በኃላፊነት አገልግለዋል።በተጨማሪም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የስራ አመራር ቦርድ ዳይሬክተር በመሆን አገልግለዋል።በፋይናንስና ግብርና ዘርፍም የተለያዩ ምርምሮችን በመስራት ለአገራቸው አስተዋፅኦ ማበርከታቸው ይታወሳል።ዶክተር ወልዳይ አምሃ ባለትዳርና የሶስት ልጆች አባት ነበሩ (ኢዜአ)፡፡
1
e17bb0e174811ec6dadf56bd220b5aef
e17bb0e174811ec6dadf56bd220b5aef
ኢትዮ ቴሌኮም በበጀት አመቱ ከ47 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ አገኘ
አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 23 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮ ቴሌኮም በ2012 በጀት አመት 47 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱ ተገለጸ።የኩባንያው ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ በሰጡት መግለጫ ÷ ገቢው ከእቅዱ 105 ነጥ ብ 1 በመቶ ብልጫ አለው ብለዋል።ይህም ከባለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር በ31 ነጥብ 4 በመቶ ብልጫ መኖሩን ጠቁመው ÷ ተቋሙ ከውጭ የስልክ ጥሪ 147 ነጥብ 7 ሚሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማግኘቱን ገልጸዋል።ከዚያም ባለፈ 10 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ብድር መመለስ ተችሏልም ነው ያሉት።የኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ቁጥርም ከባለፈው አመት በ5 ነጥብ 8 በመቶ አድጎ 46 ነጥብ 2 ሚሊየን መድረሱንም አንስተዋል።በፋሲካው ታደሰ
1
74ae0d7af1aeda4d6ba2c35def0ee89c
f3aff38e872110db7a15d95483478994
በአማራ ክልል ግጭት ተፈጥሮባቸው የነበሩ አካባቢዎች በመረጋጋት ላይ ናቸው
በአማራ ክልል በተለይም በምዕራብ ጎንደር ዞን የቅማንት ብሔረሰብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች የተከሰተውንና ከ50 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ሞትና ለበርካቶች መፈናቀልና ለንብረት ውድመት ምክንያት በሆነው ግጭት ሳቢያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የተገኙበት በጎንደር ከተማ ዓርብ ታኅሳስ 5 ቀን 2011 ዓ.ም. ምክክር ተካሄደ፡፡በምክክሩ ለሳምንታት ያህል ያጋጠመውን ግጭት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ዓላማ ያነገበ ውይይት ተካሂዷል፡፡ በተለይ ከኅዳር 23 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ በነበረው ግጭት ከ50 በላይ ዜጎች ከሁለቱም ማኅበረሰቦች መሞታቸውን፣ ከ500 በላይ ቤቶችና የእህል አውድማዎች መቃጠላቸውን የክልሉ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሰማሃኝ አስረስ ለሪፖርተር አረጋግጠዋል፡፡ በተጨማሪም ብዛት ያላቸው ዜጎች መፈናቀላቸው ታውቋል፡፡በግጭቱ ምክንያት ባጋጠመው ችግር ትምህርት ቤቶችና የተለያዩ የመንግሥት ተቋማት ተዘግተዋል፡፡ ግጭቱን ለማስቆም ታኅሳስ 5 ቀን 2011 ዓ.ም. በጎንደር በተደረገው የውይይት መድረክ፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ ከማዕከላዊ ምዕራብና ከሰሜን ጎንደር ዞኖች የተወጣጡ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሽማግሌዎች መገኘታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡‹‹ይህ ሕዝብ አብሮ ኖሯል፣ ተዋልዷል፣ ደም አስተሳስሮታል፤›› ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ፣ ‹‹ይህ ቀን አልፎ ነገ አብሮ መኖሩ አይቀርም መሪና ድርጅት ግን ያልፋሉ፡፡ ሕዝብና ታሪክ ግን በዘመናት ይቀጥላልና በሚያልፍ የመሪነት ዘመናችን የማያልፍ የታሪክ ጠባሳ እንዳንተው ልንጠነቀቅ ይገባል፤›› ብለዋል፡፡ከውይይቱ መጠናቀቅ በኋላ ባለ አምስት ነጥብ የአቋም መግለጫ የወጣ ሲሆን፣ በቀጣይ ችግሩን በቋሚነት ለመፍታት ይሠራበታል ተብሏል፡፡ ‹‹በኅብረተሰቡ መካከል ዕርቀ ሰላም ለማውረድ ይሠራበታል፤›› ሲሉ አቶ አሰማሃኝ ተናግረዋል፡፡በግጭቱ ለተጎዱ ዜጎች መንግሥት ከሚያደርገው ዕገዛ በተጨማሪ፣ ሕዝቡ ዕርዳታ እንዲያደርግ ተጠይቋል፡፡ግጭቱ ከተከሰተ በኋላ የመከላከያ ሠራዊት በአካባቢው መሰማራቱ ይታወሳል፡፡ ከዚህም ጋር በተያያዘ ሪፖርተር በስልክ ያነጋገራቸው የአይከል ከተማ ነዋሪዎች እንዳመለከቱት፣ አሁንም የፀጥታው ሁኔታ አስተማማኝ አይደለም፡፡ነዋሪዎቹ የፌዴራል መንግሥት በአካባቢው ያሰማራው የመከላከያ ሠራዊት በቂ ባለመሆኑ፣ በየቦታው የሕይወት መጥፋትና የንብረት ውድመት እንዳለ ተናግረዋል፡፡
0
4ac0c656791137e5f8ce776a982964e9
4ac0c656791137e5f8ce776a982964e9
ኢትዮጵያ የመንግሥታቱ ድርጅት በኤርትራ ላይ የጣለውን ማዕቀብ እንዲነሳ ጥያቄ አቀረበች
ኢትዮጵያ የመንግስታቱ ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት በኤርትራ ላይ የጣለውን ማዕቀብ እንዲያነሳ ይፋዊ ጥያቄ አቀረበች።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዶክተር አብይ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት ነው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት በኤርትራ ላይ የጣለውን ማዕቀብ እንዲያነሳ ጥያቄ ያቀረቡት ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በኤርትራ በነበራቸው ቆይታ ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር የተለያዩ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል።በስምምነታቸው ወቅትም በኤርትራ ላይ የተጣሉ ማዕቀቦች እንዲነሱና በአለም አቀፍ የፖለቲካ መድረክ እየደረሰባት ያለው መገለል እንዲያበቃ፥ ኢትዮጵያ ትሰራለች ማለታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ መግለጻቸው ይታወሳል።
1
ebebc953a289f7a171ad5baf25e00c54
ebebc953a289f7a171ad5baf25e00c54
በትግራይ ክልል ሁሉም ወረዳዎችና ከተሞች የኮሮና ቫይረስ የቤት ለቤት ዳሰሳ ከሚቀጥለው ሰኞ ጀምሮ ሊካሄድ ነው
አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 3 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በትግራይ ክልል ሁሉም ወረዳዎችና ከተሞች የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ያለመ የቤት ለቤት ዳሰሳ ከሚቀጥለው ሰኞ ሚያዚያ 5 ቀን 2012 ጀምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት እንደሚካሄድ የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ።የቢሮው ሀላፊ ዶክተር ሓጎስ ጎደፋይ እንደገለፁት፥ በዳሰሳው 23 ሺህ የጤና ባለሙያዎች ይሳተፋሉ።ህብረተሰቡ ቫይረሱ የሚያስከትለው ጉዳት፣ ለመከላከል የሚያስችል ግንዛቤና በክልሉ የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በሚመለከት ያለው ግንዛቤ በእያንዳንዱ ቤት ይዳሰሳል ነው ያሉት።በተጨማሪም ከክልሉ ውጭ የመጡ ሰዎች ካሉ እያንዳንዱን ቤት በመፈተሽ ምርመራ ይደረግላቸዋል።ሁሉም ባለሙያ በክልሉ ባሉት 92 ወረዳዎች የተመደበ ሲሆን፥ በዚህም በገጠር በቀን ከ15 እስከ 20 እንዲሁም በከተማ ከ25 እስከ 30 ቤቶች ለማጥናት እቅድ ተይዟል ብለዋል።ዳሰሳው በመቐለ ከተማ ነገ እንደሚጀመር በመጠቆምም ህብረተሰቡ ለዳሰሳው እገዛ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
1
71eb0315a0981775792229908322962d
71eb0315a0981775792229908322962d
በአይቮሪኮስት የእርስ በርስ ጦርነት ለተወነጀሉ በተሰጠ ምህረት ሲሞን ባግቦ ይገኙበታል
የአይቮሪኮስት ፕሬዚዳንት አላሳን ዋታራ ከሰባት ዓመታት በፊት የብዙ ሰዎች ደም ካፋሰሰው የእርስ በርስ ጦርነት በተያያዙ ጥፋቶች ለተወነጀሉ ሰዎች ትናንት በሰጡት ምህረት ተጠቃሚዎች መካከል አንዷ የቀድሞ የሀገሪቱ ቀዳማዊት እመቤት ሲሞን ባግቦ መሆናቸው ታወቀ።ሲሞን ባግቦ በብጥብጡ በተጫወቱት ሚና የሀገር ደኅንነትን አደጋ ላይ በመጣል ወንጀል ተከሰው በሃያ ዓመት እሥራት እንዲቀጡ ተፈርዶባቸው እንደነበር ይታወሳል። ባለፈው ዓመት ደግሞ በሰብዓና ላይ ወንጀል በመፈፀም በተመሰረተባቸው ክስ ከወንጀሉ ነፃ ተብለዋል።አቃቤ ሕጎች በወቅቱ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሎራን ባግቦ ተቃዋሚዎች ላይ የበቀል ጥቃት የሚፈፅም ቡድን አድራጅተው የጦር መሳሪያና ሄሊኮፕተርም ጭምር እየሰጡ ሲንቀሳቀሱ ነበር ብለው ወንጅለዋቸዋል።ሎራን ባግቦ በፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በአላሳን ዋታራ መሸነፋቸውን አልቀበልም ካሉ በኋላ አአአ በ2011 በተቀሰቀሰው ብጥብጥ ቁጥራቸው ወደ ሦስት ሺህ የሚጠጋ ሰዎች ተገድለዋል። ያን ተከትሎ ተይዘው ለሄጉ የዓለምቀፍ ወንጀል ፍርድ ቤት ተሰጥተው በሰብዕና ላይ ወንጀል በመፈፀም ክስ ሂደት ላይ ናቸው።
1
bfd2b46d43af241340fec73c696996c9
efe959c6ed6d1d8f6ac008ee782ad6e5
የባቡር ፕሮጀክቱን የሀገሪቱ ኪሳራ ከመሆን በመታደግ የኢኮኖሚ ማሳለጫ እንዲሆን የፉክክር ምዕራፎችን መዝጋት እንደሚያስፈልግ የአዋሽ-ወልድያ-ሀራ ገበያ የባቡር ፕሮጀክት አስታወቀ።
አዲስ አበባን ከኤርትራዋ ምፅዋ ጋር ለሚያገናኘው የባቡር መስመር ፕሮጀክት ጥናት ወጪ ለመሸፈን የጣሊያን መንግስት መስማማቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ገለጹ።በጣሊያን ጉብኝት እያደረጉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከጣሊያን አቻቸው ጁሴፔ ኮንቴ ጋር ተወያይተዋል።መሪዎቹ ከውይይቱ በኋላ በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ጣልያን አዲስ አበባን ከምፅዋ ለሚያገናኘው የባቡር መስመር ፕሮጀክት የመጀመሪያ ጥናት ወጪ ለመሸፈን ተስማምታለች።አዲስ አበባ እንደ ስሟ እንድትሆንና ነዋሪዎች ወጥተው ሲገቡ የሚዝናኑበትን ቦታ ከመፈለግ አንጻር በአዲስ አበባ በሚገኙ ኤምባሲዎች የተወሰነ ቦታቸውን ለህዝብ መዝናኛ ፓርክ እንዲያውሉ ጥያቄ ቀርቧል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጣልያን መንግስትም ለዚህ ቅን ምላሽ መስጠቱን ተናግረዋል።በሌላ በኩል ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር የተጓዘው የልዑካን ቡድን በሮም ከጣሊያን ባለሃብቶች ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡(ኢዜአ)
0
e70dffde9690661b9f093fa8ec139404
9af513754d9a81919bc2d973d7758157
የግለሰቦችን ፎቶግራፎች በማቀናበር በማህበራዊ ገጾች ላይ ለቋል የተባለ ተጠርጣሪ ግለሰብ ተያዘ
ሲንጋፖር ፖሊሶች የማህበራዊ ገጾችን ይዘት ማጥፋት የሚችሉበት ህግ ማውጣቷ እያነጋገረ ነው፡፡ ሲንጋፖር የሀሰት ዜናዎችን ለመቆጣጠር ያሳለፈችው አወዛጋቢ ህግ ፖሊሶች በማህበራዊ የትስስር ገጾች እና ግለሰቦች በቡድን የሚደረጉትን የመልዕክት ልውውጦችን ሳይቀር ማጥፋት የሚያስችል ስልጣን የሚሰጥ ነው ተብሏል፡፡መንግስት ‘’የህዝብን ፍላጎት ጋር ተጻራሪ የሆኑ’’ የሀሰት ዜናዎች ናቸው ብሎ ያመነባቸውን ማስወገድ ወይም እርማት እንዲሰጣቸው ማዘዝ እንደሚችል ተነግሯል፡፡ቅጣቱ ዜጋውን ከሀሰተኛ ዜናዎች የሚጠብቀው ነው ሲል ባለስልጣኑ ገልጿል፡፡ይሁን እንጂ ተቺዎች እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ህጉ በህብረተሰቡ ነጻነት ላይ ከባድ ስጋት እንደሚፈጥር ይናገራሉ፡፡በተጨማሪም በአንዳንድ መተግበሪያዎች ላይ ማለትም ዋትስ አፕ፣ ቴሌግራምና ሌሎች ላይ ህጉ እንዴት ተግባራዊ እንደሚደረግ ግልጽ አይደለም ይላሉ፡፡በሲንጋፖር መንግስት የሀሰት ዜና ነው ብሎ ባመነባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ሆኖ የተገኘ አንድ ግለሰብ በከባድ ቅጣት ወይም እስከ አምስት ዓመት በሚደርስ እስራት እንደሚቀጣ ተገልጿል፡፡እንዲሁም የሀሰት አካውንቶች በመክፈትና የሀሰት ዜናዎችን በማሰራጨት ሲጠቀም የተገኘ እስከ 1 ሚሊዮን ዶላር እና እስከ 10 አመት የእስር ቅጣት ይጠብቀዋል ተብሏል፡፡ህጉ ከማኅበራዊ ሚዲያዎች እስከ የዜና ዌብሳይቶች ላይ ተግባራዊ እንደሚሆን ተነግሯል፡፡በዘር እና በሃይማኖት ላይ ቀውስ የሚያስከትሉ የሀሰት ዜናዎችን ለመቆጣጠር ህጉ አስፈላጊ መሆኑን የሲንጋፖር መንግስት አስታውቋል፡፡ሲንጋፖር በቅርብ ወራት የሀሰት ዜናዎችን እና የጥላቻ ንግግሮችን በተመለከተ ጠንካራ ህጎችን ካሳለፉ እንደ ሩሲያ፣ ፈረንሳይ እና ጀርመን ካሉ አገራት ጋር ተቀላቅላለች ተብሏል፡፡ምንጭ ፡- ቢቢሲ
0
70e9bf641dcf8e2a650c73234f1d4fde
2b20512a33122152518592bfe98984d3
የሀይማኖት አባቶች ለዘመን መለወጫ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላለፉ
የኢፌዲሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን አዲሱ ዘመን በኢትዮጵያ የታላቅነት ጉዞ ብስራት የሚታወጅበት እና የብልፅግና መሰረት በጋራ የሚጣልበት እንደሚሆን በአዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ገለጹ።ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የ2012 ዓ. የዘመን መለወጫ በዓልን አስመልክተው ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።በመልክታቸው በአዲሱ ዘመን በሃገራችን የታላቅነት ጉዞ ብስራት የሚታወጅበት እና የብልጽግና መሰረት በጋራ የምንጥልበት ይሆናልም ብለዋል።በአሮጌው ዓመት ከድህነት የሚመነጩ እና ወደ ፊት የማያራምዱ እኩይ አስተሳሰቦችን አራግፈን መሻገር ይኖርብናል በማለት የብሩህ ተስፋ መልዕክት የሰነቀ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።“ማቅ አውልቀን ግምጃ እንልበስ!” በሚል ቅን እሳቤ ለኢትዮጵያ ስኬት እጅ ለእጅ ተያይዘን መረባረብ እንደሚገባም አመልክተዋል።ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አዲሱ ዘመን ለሁላችንም የሰላም፥ የስራ፥ የአንድነት፥ የትብብርና የብልጽግና እንዲሆን ተመኝተዋል።የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጽህፈት ቤትም አዲስ ዓመትን አስመልክቶ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል።ዘመኑ የሰላም የደስታና የብልጽግና እንዲሆንም ተመኝቷል።በ2011 ዓ.ም በኢኮኖሚ፣ፖለቲካ፣ ማህበራዊና የውጭ ግንኙነት መስኮች ጉልህና ወሳኝ ስኬቶች የተመዘገቡበትና አገራዊ ፈተናዎች የተመዘገቡበት መሆኑም ፅህፈት ቤቱ አስታውሷል።ያለፈውን ዓመት መለስ ብሎ በመቃኘት ለመጪው ዘመን ለኢትዮጵያ ብልጽግና ከመላው ኢትዮጵያውን ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኑንም ፅህፈት ቤቱ አረጋግጧል።የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርም የ2012 ዓ.ም የዘመን መለወጫን አስመልክቶ በአገር ውስጥም በውጭም ለሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፈ ሲሆን ዘመኑ የሰላምና የስኬት እንዲሆን ተመኝቷል።የተለያዩ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች፣ የመንግስት ድርጅቶችና ተቋማት፣ የግል ድርጅቶችና ታዋቂ ግለሰቦች የአዲስ ዓመት የመልካም ምኞት መግለጫቸውን ማስየተላለፋቸውን ጠቅሶ የዘገበው ኢዜአ ነው።
0
4a8a714e0384d66bd47bf7b6c8a55f2c
3f084ca49defe29d031f4fd4d77c74ce
በሚያዚያ ወር ከወጪ ንግድ ከ329 ሚሊዮን በላይ የአሜሪካን ዶላር ገቢ ተገኘ
አዲስ አበባ ፣ ነሀሴ 28 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በተያዘው የ2013 በጀት አመት ከአገራዊ ወጪ ንግድ 3 ነጥብ 91 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ለማግኘት በእቅድ መያዙን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል።ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ድጋፍና ክትትል ከሚያደርግባቸው የግብርና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች ውስጥ 2 ነጥብ 918 ቢሊየን ከግብርና እና 587 ነጥብ 5 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር የሚሆነውን ደግሞ ከማኑፋክቸሪንግ እንደሚጠብቅ አስታውቋል።ከዚያም ባለፈ ሚኒስቴሩ ከምርት አቅርቦት እስከ ወጪ ንግድ ባለው የግብይት ሰንሰለት በየደረጃው ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ ተግዳሮቶችን በቅንጅት በመፍታት ከዘርፉ የወጪ ንግድ የሚገኘውን የውጭ ምንዛሪ ገቢ ማሳደግ ዓላማው መሆኑንም አስታውቋል።ይህንን መሰረት አድርጎም የኮቪድ-19 ወረርሽን ለግብርና ምርቶች ያለው አዎንታዊ እና አሉታዊ ተፅእኖን ጨምሮ የአምስት ዓመታት የግብርና ምርቶች የምርት እና ምርታማነት ትንተና፣ የአምስት ዓመታት የወጪ ንግድ የዕቅድ አፈፃፀም ትንተና ፣የ2012/13 ምርት ዘመን የግብርና ምርቶች አቅርቦት ትንበያ ግምት፣የግብርና ምርቶች በአለም አቀፍ ገበያ ያላቸው ፍላጎት እና ሌሎችም ጉዳዮችን ለተዘጋጀው እቅድ በመነሻነት የታዩ መሆናቸው ተመላክቷል።እቅዱን ለማሳካትም የምርት አቅርቦትንና ጥራትን ማሳደግ ፣ የአሰራር ስርዓቶችን ማሻሻል፣ የህግ ማዕቀፎችን ማጠናከር፣ የፋይናንስ ስርዓት ማሻሻል የህገ- ወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ መቆጣጠር እና የገበያ መዳረሻዎችን ማስፋት ትኩረት ተሰጥቷቸው ከሚተገበሩ ዋና ዋና ተግባራት መካከል ተጠቃሽ መሆናቸውን ከንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
0
c79dbc4bafd1c8d181f9545f48d72c77
ad5ce7478a5513e8d8892f48e2542785
በአዲስ አበባ በተያዘው ዓመት 73 ሺህ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ይጠናቀቃሉ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ8ኛ ክፍል ፈተና ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት እንደሚሰጥ ተገለጸ፡፡በዛሬው ዕለት በወጣው መርኃግብር መሠረት ተማሪዎች በየተመደቡባቸው ትምህርት ቤቶች ፈተናቸውን እየወሰዱ ይገኛሉ።በከተማ አስተዳደሩ 156 የፈተና ጣቢዎች እንዳሉና 73 ሺህ 45 ተማሪዎች ለፈተና እንደተቀመጡ ታውቋል፡፡
0
464d3cd72c1b39e405e5e309cb552ade
be58ce3a884d080200bc0bffd651a5f6
በደቡባዊ ሶማሊያ የኮሌራ ወረርሽኝና ርሃብ
በምሥራቅ አፍሪካ የተከሰተው ድርቅ ብዙ ቁጥር ያላቸው ሰዎች በገደለባት ሶማሌላንድ መንግሥቱ የልማት ሥራዎችን አቁሞ የገንዘብና አስተዳድራዊ ትኩረቱን ህይወት በማዳን ሥራ ላይ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡ምክትል ፕሬዚዳንቱ ለቪኦኤ ሶማሊኛ ዝግጅት ክፍል እንደገለፁት ሁኔታው አፋጣኝ ምላሽ ካላገኘ ወደለየለት ቸነፈርና እልቂት ያመራል ብለዋል፡፡ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
0
14fa76b68a194fb385ed942f01398354
c7aa149c2323ea59ab66c2478bfa6d44
በነዳጅ ችርቻሮ ንግድ ላይ ለመሰማራት አራት ኩባንያዎች ፈቃድ ወሰዱ
የአዲስ አበባ የምግብ፣ የመድሃኒት እና ጤና ክብካቤ ቁጥጥርና አስተዳደር ባለሥልጣን ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር አካሂዷል፡፡ ባለሥልጣኑ ከጥር 1 እስከ 10፤2011 በአዲስ አበባ ከተማ ካሉ 870 የመድሃኒት ችርቻሮ ድርጅቶች ውስጥ ከተመረጡ 10 በመቶ ወይም 86 በሚሆኑ ድርጅቶች ላይ ጥናት ላይ የተመሠረተ ክትትልና ቁጥጥር አድርጓል ።ባለሥልጣኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር ለማድረግ የተነሳው ቀደም ሲል ባካሄደው የክትትልና ቁጥጥር ሥራ ወይም የኦዲት ኢንስፔክሽን ግኝትን መሠረት እንደሆነም ገልጿል ፡፡ በመድረኩም ባለሥልጣኑ በክትትሉ ወቅት ያገኛቸውን ክፍተቶች ለባለድርሻ አካላት አቅርቧል፡፡ ይህም በዘርፉ የተሰማሩ ባለሙያዎችና ባለሀብቶች ክፍተታቸውን አይተው በቀጣይ እንዲያስተካክሉ ለማስቻል ነው ተብሏል፡፡ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ከቁጥጥርና ክትትል ሥራዎች በተጨማሪ በ2011 በጀት ዓመት መድሃኒቶች በህብረተሰብ ጤና ላይ ጉዳት እንዳያደርሱና ጤናቸውን ለማስጠበቅ እየሠራ እንደሆን ገልጸዋል፡፡በቀጣይ የታዩ ክፍተቶችን በማያስተካክሉት የመድሃኒት ችርቻሮ ድርጅቶች ላይ እርምጃ መውሰዱን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግሯል፡፡በውይይት መድረኩ ላይ ከተሣተፉ ባለድርሻ አካላትም ለባለሥልጣኑ የተለያዩ ጥያቄዎች ተነስተው ምላሽ ተሰጥቷል፡፡
0
e307e1d444af4616386fde2b494fb77d
e307e1d444af4616386fde2b494fb77d
በቱርክ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ 20 ሰዎች ለህልፈት ተዳረጉ
አዲስ አበባ ፣ ጥር 16 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በቱርክ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ 20 ሰወች መሞታቸው ተነገረ።በምስራቅ ቱርክ በደረሰው አደጋ ከሞቱት በተጨማሪ ከ900 በላይ ሰዎች መቁሰላቸውም ነው የተነገረው።በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 8 የተመዘገበው የመሬት መንቀጥቀጥ ወደ 30 የሚጠጉ ህንጻዎች ማፍረሱን ፖሊስ አስታውቋል።የሃገር ውስጥ ሚኒስትሩ ሱሌይማን ሶይሉ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች በፍርስራሽ ውስጥ የተቀበሩ 30 ሰዎችን እየፈለጉ ነው ብለዋል።በፈረንጆቹ 1999 በሰሜን ምዕራብ የሃገሪቱ ክፍል የደረሱ ሁለት የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋዎች ለ18 ሺህ ሰዎች ህልፈት ምክንያት መሆናቸውን ዘገባዎች ያመላክታሉ።ቱርክ በአቀማመጧ ምክንያት በተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ታስተናግዳለች።ምንጭ፦ አልጀዚራ
1
4838990001dc1164164862e3fad7462f
3b635c296e78f0d432ebce773926cd19
በተለያዩ ኢንቨስትመንት ዘርፎች ለሚሠማሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያን መንግሥት ድጋፍ ያደርጋል -ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከጥቅምት 21 ጀምሮ በፈረንሳይና ጀርመን ጉብኝት ሊያደረጉ መሆኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ መለስ አለም በሠጡት መግለጫ እንደተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአውሮፓ በሚኖራቸው ቆይታ ከፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኤማኑኤል ማክሮን እና ከጀርመኗ መራሂተ መንግስት አንጌላ ሜርክል ጋር በተለያዩ የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ውይይት ያደርጋሉ ፡፡ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ በጀርመን ፍራንክፈርት በሚኖራቸው ቆይታም 25ሺህ ከሚሆኑ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ዲያስፖራዎች ጋርም እንደሚወያዩ ቃል አቀባዩ ጠቁመዋል ፡፡ጠቅላይ ሚንስትሩ በጀርመን ነዋሪ ከሆኑት ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም ጋር የአገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታን በተመለከተ እንዲሁም በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው መጥተው ባላቸው እውቀትና ገንዝብ ስለሚሠሩበት ሁኔታም ውይይት እንደሚደረግ ተገልጿል ።እንደ ቃልአቀባዩ ገለጻ የዓለም አቀፍ ዲፕሎማቶችና ተቋማት በአፍሪካ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ጋር ለመሥራት ያላቸውም ፍላጎት በመጨመሩ ጠቅላይ ሚንስትሩ በአውሮፓ ቆይታቸው ከአይኤም ኤፍ ኃላፊዎችም ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል ብለዋል ።ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ በፈረንሳይና ጀርመን ለሚያደርጉትም የሥራ ጉብኝትም ኢምባሲዎችና የዲያስፖራ ማህበራት ሙሉ ዝግጅት ማጠናቀቃቸውም ተገልጿል ።
0
10cc09900e68898bd7d94b76b5e4cc82
9d101d685b38072785d84b6352feceb9
የሀገርን ሰላም በማስፈን የዲሞክራሲ ግንባታ ሂደት ግቡን እንዲመታ የሴቶች ሚና የጎላ መሆኑ ተገለፀ
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 2/2005 (ዋኢማ) – በኦሮሚያ ተከታታይና ቀጣይነት ያለውን ፈጣን ዕድገት ለማረጋገጥ በተያዘዉ ጥረት በየደረጃው የሚገኙ ኮሙኒኬተሮች የበኩላቸዉን ጥረት እንዲያደርጉ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አስገነዘቡ ። በዞኖች፣ በከተሞችና በክልል ደረጃ ያሉ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች የተሳተፉበት የዉይይት መድረክ ትናንት በአዳማ አባገዳ አዳራሽ ተካሂዷል ። ርዕሰ መስተዳድር አቶ አለማየሁ ኦቶምሳ በዉይይቱ ላይ እንተናገሩት በክልሉ በየደረጃዉ የሚገኙ ኮሙኒኬተሮች የመንግስት ፖሊሲና ስትራተጂ ዎችን በአግባቡ ተግባራዊ በማድረግ በህብረተሰቡ ዘንድ ግንዛቤን የማዳበር ሃላፊነት አለባቸዉ ። በህዝቦች ማዕበል የታጀበ ፈጣን ልማትን ወደፊት ለማራመድ ከክልል እስከ ወረዳ ድረስ ያሉ ኮሙኒኬተሮች የሚዲያና የህዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች የሚጫወቱት ሚና የማይተካ ነው ብለዋል ። ባለፉት ሁለት አስርተ ዓመታት በተከታታይ የተመዘገበውን የክልሉንም ሆነ አጠቃላይ የአገሪቷን ፈጣን ዕድገት በአስተማማኝ መሰረት ላይ ለማስቀጠል የተቀናጀ የህዝቦች ሁለንተናዊ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን የገለጡት ርዕሰ መስተዳድሩ ኮሚኒኬተሮቹ በልማቱ የሚፈጠረውን የህዝብ ማዕበል በመምራትና ብሔራዊ መግባባት በማምጣት ላይ የማይተካ ሚና በመጫወት የድርሻቸውን መወጣት ይገባቸዋል ብለዋል። የክልሉ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ በመንግስት ፖሊሲና ስትራተጂ ላይ በየደረጃው የሚገኙት የህዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች በተለይም በአመለካከትና በልማቱ የትኩረት አቅጣጫ ላይ ጥልቅ ዕውቀትና የዳበረ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ማድረግ እንደሚገባው ርዕሰ መስተዳድሩ አስገንዝበዋል። ከወቅቱ ልማታዊ እንቅስቃሴ ጋር መጓዝ የሚችል የሚዲያና የህዝብ ግንኙነት ሃይል ለመፍጠር ቢሮው ቅንጅታዊ አሰራር እስከታችኛው መዋቅር ድረስ በመዘርጋት መስራት እንደሚገባውም አሳስበዋል ። እንደ ኢዜአ ዘገባ በውይይቱ የተሳተፉ የዞን፣ የከተሞችና የክልሉ ቢሮዎች የህዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች በበኩላቸው እንደገለጹት ዘርፉ በአገር ልማት የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታና መልካም አስተዳደር በማስፈን ላይ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጠዋል።
0
ef4f05190abcefed537af2bd57f8f58a
ef4f05190abcefed537af2bd57f8f58a
የትግራይ ክልል ተፈናቃዮችን ለመርዳት የ160 ሚሊዮን ተማፅኖ ቀርቧል
ከሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ ክልል በግጭቱ ሳቢያ ከቀያቸው ለሸሹ ስደተኞች የሚያስፈልገውን አጣዳፊርዳታ ለማቅረብ የ.ተ.መ.ድ የስድተኞች ኮሚሽነር እና 30 የሰብዓዊ ረድዔት አጋሮቹ የ160 ሚሊዮን ዶላር አስቸኳይ ድጋፍ ተማጽነዋል። ገንዘቡ ለስደተኞቹ እስከመጪው የአውሮፓውያን 2021 ዓመተ ምህረት አጋማሽ የሚዘልቅ ርዳታ ለማቅረብየሚውል መሆኑን ዩ.ኤን.ኤች.ሲ.አር አመልክቷል“የተጠየቀው አስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍ ቀያቸውን እየለቀቁ ወደሌላ ሃገር የሚሰደዱ ሰዎች እንቅስቃሴከቀጠለ መደረግ ያለበትን ዝግጅት ለማጠናከርም ይውላል” ብሏል።ባለፉት ስድስት ሳምንታት ድንበር አቋርጠው ሱዳን የገቡት ኢትዮጵያውያን ከ56 ሺሕ በላይ መሆናቸውንያመለከተው ድርጅቱ፤ በቅርብ ቀናት የሚገቡት ቁጥር ቀንሶ በቀን 500 የሚጠጉ ሰዎች ይገባሉ ብሏል።“በዚህ ደረጃ የገዘፈ የስደተኛ እንቅስቃሴ ባልታየበት እጅግ የራቀ አካባቢ ለረድዒት ድርጅቶች ሥራ እጅግፈታኝ ሆኗል” ሲል የተ. መ.ድ የስደተኞች ኮሚሽነር አስረድቷል።
1
dc7aebe95730ac8a8e8e96505ac599c6
dc7aebe95730ac8a8e8e96505ac599c6
ተጨማሪ 9 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው ተረጋገጠ፡፡
ባሕር ዳር፡ ሚያዝያ 10/2012 ዓ.ም (አብመድ) በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 105 ደርሷል፡፡ባለፉት 24 ሰዓታት ምርመራ ከተደረገላቸው 659 ሰዎች መካከል 9 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር ገለጸ። በዚህም በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች አጠቃላይ ቁጥር 105 ደርሷል።
1
867dcde21e3a622e154169cb519a9032
26aa7479de93d2e223d4f989941c0445
በ10 ሚሊየን ዶላር ለሚገነባው የመድሀኒት ፋብሪካ የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ
የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን መደወላቡና ደሎመና ወረዳዎች ተገኝተው የመሰረተ ልማት ሥራዎችን እየጎበኙ ነው።ምክትል ፕሬዚዳንቱ በጉብኝታቸው በመደወላቡ ወረዳ የተገነባውን የመደወላቡ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን መርቀው ሥራ ያስጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃል።በተጨማሪም በደሎመና ለሚገነባው የመስኖ ፕሮጀክት የመሰረት ድንጋይ እንደሚያስቀምጡ ታውቋል።በምክትል ፕሬዚዳንቱ የመሰረተ ልማት ጉብኝት ላይ የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (የኦዲፒ) ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዲሱ አረጋን ጨምሮ የክልሉ የካቢኔ አባላትና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች መገኘታቸው ተመልክቷል።በተጨማሪም የኦሮሚያ ብሮድካስቲግ ኔትወርክ (ኦ.ቢ.ኤን ) የባሌ ኤፍኤም ሬድዮና ቴሌቪዥን ስርጭት የሚሆን ስቱዲዮ ለመገንባት በባሌ ሮቤ ከተማ የመሰረት ድንጋይ አስቀምጠዋል።አቶ ሽመልስ በትናንትናው ዕለት በክልሉ ወቅታዊ ጉዳይና በኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ላይ በባሌ ሮቤ ከተማ ከሕብረተሰቡ ጋር መወያየታቸው ይታወሳል መረጃዉ የኢዜአ ነዉ።
0
9fd71266b9fe98409e3b9e8da8ae5acb
7d1c2d13ac6682d0f241b0c9a52363df
ናይጀሪያ የኮሮና ቫይረስ ውጤትን ከ40 ደቂቃ ባነሰ ጊዜ የሚያሳውቅ መመርመሪያ ሰራች
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን መግታት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከጃክ ማ ጋር ተወያዩ።በአፍሪካ ኖብል ኮሮና (COVID19) ሊያስከትል የሚችለውን የጤና ጉዳት ለመከላከል ቅድመ ዝግጁነት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።ዛሬ ጠዋት ከጃክ ማ ጋር በአፍሪካ የCOVID19ን ስርጭት ለመግታት በጋራ ለመሥራት በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ መስማማታቸውን ነው ያመለከቱት።ለእያንዳንዱ የአፍሪካ ሀገር ከ10 ሺህ እስከ 20 ሺህ የሚደርሱ ኮሮናን መመርመሪያ ኪቶችን እና 100 ሺህ ማስኮችን ለማሰራጨት ከኢትዮጵያ ጋር ለመተባበር በመምረጣቸው ጃክ ማንን አድንቀዋል።የሚደረገው ድጋፍ በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎችን ለመንከባከብ የሚያስችሉ መመሪያዎችን አካትተው በቅርቡ የተዘጋጁ መጽሐፎችን ይጨምራል።የCOVID19 ስርጭትን ለመግታት ቁሳዊ ድጋፍን ከዕውቀት ጋር ማጣመር እንደሚያስፈልግም ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በፌስቡክ ገፃቸው ያስታወቁት።
0
9bf0463ccff23d58495db131dd9fe989
9bf0463ccff23d58495db131dd9fe989
የቅዳሜው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ደጃፍ የተቃውሞ ትዕይንትና ዓላማ
የኢትዮጵያውያን “የጋራ ግብረ-ኃይል” የተባለው ቡድን ባለፈው ቅዳሜ ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባካሄደው የተቃውሞ እንቅስቃሴ ከኢትዮጵያውያኑ ውጭ የተለየ ትኩረት ስቧል።የተቃውሞ እንቅስቃሴውን ያካሂዱ ከነበሩት ሰዎች ሁለቱ “ሕግ ተላልፋችኋል” በሚል ታስረዋል። ይሁንና እስሩ “በኢትዮጵያ እየተፈጸመ ነው” ባሉትና ለተቃውሞ ለወጡበት ዋና ጉዳይ ትኩረት ለመሳብ ታስቦ የተከናወነ መሆኑን ከአስተባባሪዎቹ ይናገራሉ። በጊዜው በቦታው የተፈጠረውን ሁኔታ ጨምረው ይህ ዓይነቱ የእምቢተኝነት አቋም መግለጫ ለቆሙለት ዓላማ የተለየ ትኩረት ለመሳብ አንዱ ዓይነተኛ ዘዴ መሆኑንም ጨምረው አመልክተዋል።
1
d7161c0ce19e1e93af85f783e943b408
d7161c0ce19e1e93af85f783e943b408
መንግስት የጦር መሳሪያ ሊያስፈታ ነው የሚለው ቅስቀሳ ከእውነት የራቀ ነው ተባለ
መንግስት የጦር መሳሪያ ሊያስፈታ ነው የሚለው ቅስቀሳ ከእውነት የራቀ መሆኑን የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ በምዕራብ እና በማዕከላዊ ጎንደር ዞኖች አንፃራ ሰላም መስፈኑንም ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡ኮሚሽኑ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው በሁለቱ ዞኖች አንፃራዊ ሰላም መታየቱን ያስታወቀው፡፡ በአካባቢው የነበረውን አለመረጋጋት ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ለመመለስ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ ክልከላ እና ሌሎች እገዳዎች ከተላለፉበት ቀን ጀምሮ በሰውም ይሁን በንብረት ላይ ይደርስ የነበረው ጉዳት መቀነሱን ገልፃል፡፡የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘላለም ልጃለም እንደጠቆሙት የፌደራል እና የክልል የፀጥታ ሀይሎች ከህብረተሰቡ ጋር እየሰሩት ባለው ተግባር በቡድን ሲፈፀሙ የነበሩ የግድያ እና የንብረት ማጥፋት ወንጀሎች ቀንሰዋል፡፡ከእገዳው በኋላ በጥምረት በተሰራው ስራም 11። ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ተናግረዋል። አሁንም አልፎ አልፎ በግለሰብ ደረጃ የሚፈፀሙ ወንጀሎች መኖራቸውንም ጠቁመዋል። አብመድ እንደዘገበው ከአሁን ቀደም ታግተው የነበሩ ግለሰቦችም ሙሉ በሙሉ መለቀቃቻን ኮሚሽነሩ አረጋግጠዋል፡፡ከጎንደር መተማም ይሁን ከጎንደር ሁመራ የተሽከርካሪ መጓጓዣ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡ በጎንደር ከተማ ከአሁን ቀደም የጥይት ተኩስ ይሰማ ነበር ያሉት ኮሚሽነር ዘላለም እገዳው ከተደረገ ወዲህ መቀነሱን አመላክተዋል፡፡ይህ ደግሞ የፀጥታ ሀይሉ ከማህበረሰቡ ጋር በጋራ ሆኖ በመስራቱ የመጣ ነው፤ የጎንደር ከተማ ወጣቶች ለሰላም እያሳዩ ያሉት ትብብርም የሚደነቅ ነው ብለዋል፡፡ወንድማማች ህዝቦቹ ካለፈው ጥፋት ተምረው በጋራ ችግሮቻቸውን ለመቅረፍ እየተወያዩ መሆናቸውም ታውቋል።እገዳ በተደረገባቸው አካባቢዎች የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ መከልከሉን ምክንያት አድርገው መንግስት የጦር መሳርያ ሊያስፈታ ነው እያሉ ቅስቀሳ የሚያደርጉ አካላት አሉ፡፡ “ቅስቀሳው ከእውነት የራቀ ነው፤ ብጥብጥ በመፍጠር ክልሉን ለማዳከም የታለመ ሀሳብ በመሆኑ ማህበረሰቡ በአሉባልታዎች እንዳይታለል” ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
1
a10a4066f3c2aef75969d8ca88327678
a10a4066f3c2aef75969d8ca88327678
አአ U-17 | አዳማ እና ኤሌክትሪክ በሰፊ የጎል ልዩነት አሸንፈዋል
የአአ እግርኳስ ፌዴሬሽን ከ17 ዓመት በታች ውድድር የ12ኛ ሳምንት አራት ጨዋታዎች በዕለተ ቅዳሜ ሲከናወኑ አዳማ ከተማ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ በሰፊ ግብ ልዩነት አሸንፈዋል።5:00 ሰዓት ላይ በኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ ሜዳ ላይ በተደረገ ጨዋታ አዳማ ከተማ ከቅዱስ ጊዮርጊስን 5-1 አሸንፏል። አዳማ ከተማ ተስፋ በተጣለበት በፍራኦል ጫላ አራት፣ እንዲሁም ነቢል ኑሬ ተጨማሪ አንድ ግብ አዳማ ከነማ በሰፊ ግብ ልዩነት ቅዱስ ጊዮርጊስን 5 -1 አሸንፈዋልጰ የድንቅ ክህሎት ባለቤቱ ፍራኦል የውድድሩን ከፍተኛ ግብ አግቢነት እየመራ ይገኛል።3፡00 ሰአት ላይ ኢ/ወ/ስ/አካዳሚ ከ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ያገናኝው ጨዋታ በኢትዮ ኤሌክትሪክ 5-2 አሸናፊነት ተጠናቋል ።በሌሎች ጨዋታዎች ሀሌታ አፍሮ ፅዮንን 2-1ሲያሸንፍ ሠለም በመከላከያ 2-0 ተሸንፏል።ኢትዮጵያ መድን ከኢትዮጵያ ቡና የመድን ስራ አስኪያጅ አበባው ከልካይ ስርዓተ ቀብረቸው ዛሬ በመፈፀሙ ጨዋታው ነገ 06:00 ጃንሜዳ ይካሄዳል።
1
03be7cca23cefe3e1eee46923791bee5
a9c181c47a868dfb1e4895d534a156fb
የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲ አሰሪዎች ፌዴሬሽን ጥምረት ይፋ ሆነ
በኢትዮጵያ ከ2 ሚልዮን በላይ የሚሆኑ ዜጎች ለአደጋ በሚያጋልጡ የስራ ዘርፎች እንደሚገኙ የኢትዮጵያ ኢንዳስትሪ አሰሪዎች ኮንፌደሬሽን ገለፀ፡፡ በስራ ላይ በሚገጥሙ አደጋዎች በሃገር አቀፍ ደረጃ ምን ያክል ሰዎች እንደሚጎዱ በውል ባይጠናም በየዓመቱ ግን የስራ ላይ አደጋዎች እየጨመሩ መምጣታቸውን ዓለም አቀፍ የሙያ ደህንነት እና ጤንነት ቀን ሲከበር ተገልጿል፡፡የኢትዮጵያ ኢንዳስትሪ አሰሪዎች ኮንፌደሬሽን ዋና ጸሃፊ አቶ ዳዊት ሞገስ እንዳሉት በኢትዮጵያ ከ2 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ዜጎች ለአደጋ አጋላጭ በሆኑ የስራ ዘርፎች ተሰማርተው ይገኛሉ፡፡የትምህርት ደረጃቸውም ዝቅተኛ መሆኑ ችግሩን ያጎላዋል ብለዋል፡፡በስራ ላይ ባሉ ሰራተኞች እየደረሰ ያለው ጉዳት እየጨመረ መጥቷል ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ም/ፕሬዚዳንት አቶ አያሌው አህመድ ናቸው፡፡በግንባታ ላይ በየዓመቱ በርካቶች ለህልፈተ ህይወት እየተዳረጉ ነው ያሉት አቶ አያሌው ችግሩን ለመቀነስ ህጎች እንዲወጡና እንዲሻሻሉ ተግባራዊም እንዲሆኑ መደረግ እንዳለበት ጠቁመዋል፡፡ባለፈው ዓመት በተደረገ አለም አቀፍ ጥናት 374 ሚሊዮን ዜጎች በስራ ላይ ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን 2 ነጥብ 78 ሚሊዮኑ ደግሞ ህይወታቸው አልፏል፡፡
0
ffcfadf59948c037181c82bc4ef7d7ea
06538099417b6ce2b3fa47d19e37872a
ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ውጥኖች ስኬት የደን ሽፋን መጨመር ጉልህ ሚና አለው
– በዘንድሮ የክረምት ወቅት ከ6 ነጥብ 8 ቢሊዮን በላይ የተለያዩ አገር በቀልና የውጪ ዝርያ ያላቸው የዛፍ ችግኞችን እየተተከሉ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ በሚኒስቴሩ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ኤርሚያስ ባዩ ለዋልታ እንደገለጹት የችግኞቹ ተካለይ እየተካሄደ ያለው በተለያዩ ክልሎች ውስጥ በተዘጋጀው ከሁለት ሚሊዮን ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ነው። በ2005 ዓ.ም የበጋ ወቅት ለአፈርና ውሃ ጥበቃው የሚያገለግሉ የእርከን ሥራዎች ሲከናወኑ እንደነበር የተናገሩት አቶ ኤርሚያስ በክረምቱ ወራት ደግሞ የችግኝ ተከላው በመላ አገሪቱ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል ።በበጋ ወቅት በመላው አገሪቱ በተከናወነው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ከ171 ሚሊዮን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች መሳተፋቸውን አቶ ኤርሚያስ አስረድተዋል፡፡ ባለፉት በሁለት ዓመታ ውስጥ በ13 ሚሊዮን 720ሺ ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና የውሃ ጥበቃ ሥራዎች መከናወናቸውንም ተናግረዋል።እንደ ባለሙያው ገለጻ በ2004 ዓ.ም የበጋ ወቅት በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች ከተተከሉት ከ4.5 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ውስጥ 70 በመቶ የሚሆኑት መጽደቃቸውን አቶ ኤርሚያስ ። በየዓመቱ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ የዛፍ ችግኞችን በመትከልና የተጎዱ መሬቶችን መልሰው እንዲያገግሙ በማድረግ የደን ሽፋኑ ከ11 በመቶ በላይ መድረሱን አቶ ኤርሚያስ አስረድተዋል። በአምስት ዓመቱ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የአገሪቱን የደን ሽፋን 13 በመቶ ለማድረስ በአረንጓዴ ልማት ስትራቴጂ መሠረት ችግኞችን በመትከል ፤በመንከባከብና የተፈጥሮ ሃብትን በዘላቂነት ለማልማት ፈርጀ ብዙ እንቅስቃሴዎች እየተካሄዱ መሆኑን ባለሙያው አስረድተዋል።
0
4fd9ae61eaa9b5ab8e2de01a0f857b85
7373dff381b91d0eca7265d4408d3478
ኢትዮጵያ እና ጅቡቲ የመንገድ ፣ የወደብ አገልግሎቶችን እና የመኪና ማቆሚያ ጣቢያዎችን ይዘት ለማሻሻል ተስማሙ
አዲስ አበባ ፣ መስከረም 21 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የብሄራዊ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ዘርፍ ፖሊሲ እንዲሁም የሞተር አልባ ትራንስፖርት ስትራቴጂ ይፋ ሆነ።የብሄራዊ ትራንስፖርት ፖሊሲ፣ የሎጅስቲክስ ዘርፍ ፖሊሲ እና የሞተር አልባ ትራንስፖርት ስትራቴጂን የሚመለከት መርሀ ግብር እየተካሄደ ነው።የትራንስፖርት ሚኒስትሯ ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት ዓመታት በአማካኝ አስር በመቶ የኢኮኖሚ እድገትና ከፍተኛ የህዝብ ቁጥር እድገት ይመዘገብባቸዋል ተብለው ከሚታሰቡ ሃገራት አንዷ መሆኗን ተናግረዋል።በተለይም የትራንስፖርት ዘርፉ ያለው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ከፍተኛ በመሆኑ የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማጎልበት እንዲቻል ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ቀረፃ ላይ በትኩረት ሲሰራ መቆየቱን አንስተዋል፡፡በዚህ ረገድ የብሄራዊ ትራንስፖርት ፖሊሲው መርህ ካደረጋቸው ጉዳዮች የዘርፉ አጠቃላይ ልማትና እድገትን የሚደግፍ፣ ደህንነታቸው የተጠበቀ ብሎም ከብክነትና ከአካባቢ ብክለት የፀዳ አገልግሎት መስጠት እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል፡፡ የመሰረተ ልማት ዝርጋታዎችና አገልግሎቶችን ተፈጥሯዊ ሥነ ምህዳርን የማይጎዱ ማድረግ እንዲሁም ዘመናዊ፣ ፈጣን፣ ወጪ ቆጣቢና ተደራሽ የማድረግና የትራንስፖርት መሰረተ ልማት ግንባታዎችን ለማበርከት የተዘጋጀ መሆኑንም ጠቁመዋል።የሞተር አልባ ትራንስፖርት ስትራቴጂው መንገዶችን ለሰዎች በሚመች ሁኔታ እንዴት መጠቀም እንደሚቻል የሚያሳይና ተደራሽነት፣ ፍትሀዊነትና ዘላቂ ልማትን መሰረት አድርጎ የተዘጋጀ መሆኑንም ነው የገለፁት። እነዚህን ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች በመተግበር በቀጣይ ዓመታት አጠቃላይ የሃገሪቱን የመንገድ ሽፋንና ጥራት ለማሻሻል ይሰራል ብለዋል።በመርሀ ግብሩ የህዝብ ተወከዮች ምክር ቤት አባላት፣ የፌደራልና የክልል አመራሮችና የልማት አጋሮችን ጨምሮ ሌሌችም ባለድርሻ አካላት መገኘታቸውን የኢዜአ ዘገባ ያመላክታል።
0
e22cc2f8082f74c55f8b2c6bcd4ed8f4
27ab262d0a93988c1e5e8c57a4c7fa73
“የኢትዮጵያ የማዕድን ልማት ማዕከል” በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተቋቋመ
ረ/ፕ ነብዩ ባዬ ለብሔራዊ ቴአትር አቶ ተስፋዬ ሽመልስ ለብሔራዊ ባህል ማዕከል ተሹመዋል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትርና የኢትዮጵያ ብሔራዊ የባህል ማዕከል አዳዲስ ዳይሬክተሮችን አገኘ፡፡ በዚሁ መሰረት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቴአትር ጥበባት ትምህርት ክፍል ዲን በመሆን ለረጅም ጊዜ ሲያገለግሉ የነበሩት ረዳት ፕ/ር ነብዩ ባዬ ለብሔራዊ ቴአትር ዋና ዳይሬክተርነት እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትርን ለረጅም ዓመታት የመሩት አቶ ተስፋዬ ሽመልስ ለብሔራዊ ባህል ማዕከልነት ዳይሬክተርነት ተሹመዋል፡፡ ሹመቱ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደምብ ቁጥር 2574/2003 አንቀፅ 7(1) መሰረት የተካሄደና የሹመቱ ደብዳቤ በኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አሕመድ የፀደቀ መሆኑም ታውቋል፡፡ ረዳት ፕ/ር ነብዩ ባዬ በሹመቱ ምን እንደተሰማቸው ተጠይቀው ሲመልሱ “ቴአትር የጀመርኩት በ12 ዓመቴ ነው፡፡ ህይወቴ ከሙያው ጋር የተቆራኘ ነው” ካሉ በኋላ፣ በየትኛውም ዓለም ያለ የቴአትር ባለሙያ የመጨረሻ ግቡ የአገሩን ብሔራዊ ቴአትር ማገልገል ነው እኔም የአገሬን ብሔራዊ ቴአትር እንዳገለግል በመመረጤ ደስታና ክብር ተሰምቶኛል ብለዋል፡፡ “አቶ ተስፋዬ ሽመልስ በበኩላቸው የተሾምኩበት ቦታ እንደ ባለሙያ ትልቅ ቦታ ነው” ያሉ ሲሆን በስራ ቆይታዬ በሌሎች አለማት ያየኋቸውን የባህል ማዕከላት አገሬ ላይ እውን ለማድረግ እሰራለሁ ብለዋል፡፡ አክለውም ቦታው የአንድን አገር ባህል ለማሳደግ ታሪካችንን ለማጉላት እና ያሉንን ጠንካራና የጋራ እሴቶች ለማጉላት ብዙ የሚያሰራ በመሆኑ በቦታው ላይ በመሾሜ ደስተኛ ነኝ ብለዋል፡፡
0
70cbfe384d58c6cf189ec49893a90094
8514c86b518194d9a3c7b56df9a8ec52
80 ህገ-ወጥ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በሶማሌ-ላንድ ሲያዙ፣ ሰባት መሞታቸው ታወቀ
የሜክሲኮ መንግስት የድንበር ቁጥጥሩን ማጠናከሩ ተገለጸ፡፡እርምጃው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሜክሲኮ ምርቶች ላይ የ5 በመቶ ቀረጥ ለመጣል መዛታቸውን ተከትሎ የተወሰደ ነው ተብሏል፡፡የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ህገ-ወጥ ስደተኞችን ለመከላከል ጠንካራ ዕርምጃ ለመውሰድ ሜክሲኮ መስማማቷን ገልፀው ነበር፡፡የሜክሲኮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርሴሎ ኤብራርድ ሀገራቸው በደቡባዊው ድንበር 6 ሺህ የፀጥታ አካላትን እንደምታሰማራ ገልፀዋል፡፡የፀጥታ ቁጥጥሩ ቢጠናከርም ስደተኞች ግን አሁንም ከሜክሲኮ ወደ አሜሪካ ለመግባት ጥረት እያደረጉ መሆኑ ተገልጿል፡፡(ምንጭ፡-ፍራንስ 24)
0
3a3671ed62c6b0128b1804662570d7e6
3a3671ed62c6b0128b1804662570d7e6
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ጥቅምት 27 ይጀመራል
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ አዲሱ የውድድር ዘመን ጥቅምት 27 ቀን 2009 እንደሚጀመር ታውቋል፡፡ፌዴሬሽኑ ለክለቦች በላከው ደብዳቤ መሰረት የውድድሩን እጣ የማውጣት ስነስርአት መስከረም 24 ቀን 2009 እንደሚያከናውን ሲያስታውቅ የክለቦች ምዝገባ እና ፍቃድ ከመስከረም 18-26 ይከናወናል፡፡ተሳታፊ ክለቦች ለዳኞች እና ታዛቢዎች የሚከፈለውን ገንዘብ ከመስከረም 15 እስከ ጥቅምት 5 እንዲያጠናቅቁ ቀነ ገደብ የወጣላችሁ ሲሆን የተጫዋቾች ምዝገባ እስከ ውድድሩ መጀመር ድረስ ይቆያል፡፡በተጠናቀቀው የውድድር ዘመን 17 ክለቦች በሁለት ዞን ተከፍለው ውድድር ያካሄዱ ሲሆን በዘንድሮው አመት ቁጥሩ እስከ 22 ሊደርስ እንደሚችል ተገምቷል፡፡ አምና ከተሳተፉት መካከል ሲዳማ ቡና እና ጥሩነሽ ዲባባ አካዳሚ ላይሳተፉ እንደሚችሉ ሲጠበቅ እንደ አአ ከተማ እና ጅማ አባቡና ያሉ አዳዲስ ቡድኖች ይካተታሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
1
112364962482bfe9fd0dbc90a96db9b9
21a3b192db550136b3ab385283273904
ኢራን ትምህርት ቤቶችንና የባህል ማዕከላትን ዘጋች፡፡
ዋና ጽ/ቤቱን ፓሪስ ያደረገው ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች ቡድን ትላንት ባወጣው ዓመታዊ ሪፖርቱ፣ ኢራን ደረጃዋ ከቀድሞ በ6 ወርዶ ከ180 ሃገሮች አሁን 170ኛ ቦታ ላይ ትገኛለች ብሏል።ኢራን እአአ በ2018 ደረጃዋ ወደ ግርጌ ሊወርድ የቻለውም በተለይም በማኅበራዊ ሚዲያ የሚጠቀሙ ባለሞያና አማተር ጋዜጠኞችን በብዛት ይዛ በማሠሯ መሆኑ ተመልክቷል።ለጋዜጠኞች መብት ተከራካሪው ቡድን ያወጣው ሪፖርት አክሎም ኢራን በዓለም ጋዜጠኞችን በብዛት ከሚያስሩ ሃገሮች አንዷ ናት ብሏል።
0
6fbb8e39d81cd5a0a04c70f494cca759
b60374775d7c21de0a3197595707441b
በትግራይ የታቀደው 28ሚሊየን ኩንታል ሰብል ምርት ሊሳካ ይችላል
አዲስ አበባ ፣ መስከረም 21 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአፋር እና ሶማሌ ክልሎች የተከሰተውን የበረሃ አንበጣ ባለበት ለመቆጣጠርና ወደ አማራ፣ ኦሮሚያ እና ትግራይ ክልሎች በመዛመት ሰብል ላይ ጉዳት እንዳያደርስ እየተሰራ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡በአሁኑ ወቅት የበረሃ አንበጣው በአፋር ክልል በ26 ወረዳዎችና በምስራቅ አማራ አጎራባች ወረዳዎች እና በሶማሌ ክልል በሲቲ ዞን በሚገኙ በአይሻ፣ አወበሬ እና ሽንሌ ወረዳዎች ዳግም ተከስቷል ነው ያለው ሚኒስቴሩ፡፡የዘንድሮው የበረሃ አንበጣ መንጋ ወረርሽኝ እስካሁን በሰብል ላይ ጉዳት ባያደርስም ግጦሽና በቁጥቋጦ ላይ ጉዳት እያስከተለ ይገኛል ተብሏል፡፡በዚህም በአፋር እና ሶማሌ ክልሎች የተከሰተውን የበረሃ አንበጣ ባለበት ለመቆጣጠርና ወደ አማራ፣ኦሮሚያ እና ትግራይ ክልሎች በመዛመት ሰብል ላይ ጉዳት እንዳያደርስ የግብርና ሚኒስቴር ከክልሎች ጋር ጠንካራ አደረጃጀት በመፍጠር እና አስፈላጊውን የኬሚካል፣ የተሽከርካሪዎች፣ የአሰሳ ሄሊኮፕተሮችና የመርጫ አውሮፕላኖች እንዲሁም በቂ ባለሙያዎችን በመመደብ ከዓለም አቀፍ አጋር አካላት ጋር በመሆን የመቆጣጠር ስራ እየሰራ ይገኛል፡፡የበረሃ አንበጣውን ለመከላከል በተደረገው ሁለገብ እንቅስቃሴ ከሰኔ 2011 ጀምሮ በ1 ሚሊየን 307 ሺህ 306 ሄክታር መሬት ላይ አሰሳ ተካሂዶ 528 ሺህ 880 ሄክታር መሬት ላይ መከሰቱን በማረጋገጥ የግጦሽና የእርሻ መሬት ላይ በሰው ኃይል የሚሠራና በመኪና በተጠመደ መርጫ መሳሪያ በአውሮፕላን በመታገዝ የፀረ-ተባይ ኬሚካል ርጭት በማካሄድ እንዲሁም ህዝቡን በማሳተፍ በባህላዊ ዘዴ ጉዳት እንዳያደርስ የመከላከል ስራ ተሰርቷል፡፡የበረሃ አንበጣው በ2011/12 ዓ.ም ምርት ላይ 3 ነጥብ 5 ሚሊየን ኩንታል ወይም ከዓመቱ ምርት ውስጥ አንድ በመቶ የሚሆን ምርት ላይ ጉዳት ማድረሱን ከግብርና ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
0
a8faf315bd99df4ebf352ba930dd8182
ab7f7d7e385dce17952e0a1d49dc9c5e
ለጌዴዖ ዘላቂ መፍትኄ ተጠየቀ
ለዘመናት በአብሮነት የኖሩ ሕዝቦችን ለመነጣጠል ጥረት የሚያደርጉ ጥፋተኞችን አጋልጦ በመስጠት ኅብረተሰቡ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ተጠየቀ፡፡በኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የተመራ ቡድን በሸዋ ሮቢት ከተማ ስለአካባቢው ሰላም ውይይት እያካሄደ ነው፡፡በሰሜን ሸዋ ዞን ሸዋ ሮቢት ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው ውይይት ከሁለቱም አጎራባች አካባቢዎች የኅብረተሰብ ክፍሎችና በየደረጃው ያሉ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እየተሳተፉ ነው፡፡የውይይቱ ዓላማ በሰሜን ሸዋ ዞን እና ኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳድር አጎራባች አካባቢዎች እየተፈጠረ ላለው የሰላም እጦት መፍትሔ መፈለግ ነው፡፡
0
a064fbbf62794f0af14d0ba4271a56dd
76fce9cf0907b1e8fa08946f53917765
ሀዲያ ሆሳዕና የአማካይ ስፍራ ተጫዋች አስፈረመ
ሀዲያ ሆሳዕና የሄኖክ አርፊጮ፣ ፀጋሰው ዴሌሞ እና መስቀሉ ለቴቦን ውል አራዝሟል፡፡ከዚህ ቀደም በክለቡ ቆይታ የነበረው እና 2011 ላይ ወደ ወላይታ ድቻ አምርቶ ከተጫወተ በኃላ በድጋሚ ወደ ቀደም ክለቡ ተመልሶ ጥሩ ግልጋሎትን ሰጥቷል።ሁለተኛው ውሉን ያራዘመው ተጫዋች ተከላካዩ ፀጋሰው ዴሌሞ ረዘም ያለ ጊዜን በክለቡ ያሳለፈ ሲሆን ዘንድሮ ባሳየው መልካም እንቅስቃሴ መነሻነት አሁንም ዳግም በክለቡ ቆይታን ለማድረግ ውሉን አድሷል፡፡የመስመር ተከላካዩ መስቀሉ ለቴቦ ውሉን ያራዘመ ሌላኛው ተጫዋች ነው፡፡ አርባምንጭ ከተማን ለቆ ወደ ቀደም ክለቡ በተሰረዘው የውድድር ዓመት ዳግም የተመለሰው ተጫዋቹ ተጨማሪ ዓመት በክለቡ ለማሳለፍ ቅድመ ስምምነት ፈርሟል፡፡ስለ ውል መራዘሙ ተጫዋቾቹም ሆነ የክለቡ ስራ አስኪያጅ አቶ መላኩ ማዶሮ ለሶከር ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል፡፡
0
3d64d4e8037291c37f966202243f679b
3d64d4e8037291c37f966202243f679b
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ 27ኛ ሳምንት – ቀጥታ የውጤት መግለጫ
(10:00 ባህርዳር)(08:00 አርሲ ነገሌ)(08:00 አበበ ቢቂላ)(09:00 ሰበታ – 28ኛ ሳምንት)(10:00 አበበ ቢቂላ – 28ኛ ሳምንት)(09፡00 አበበ ቢቂላ)(09፡00 አበበ ቢቂላ ስታድየም)(09፡00 ቡራዩ)ኢትዮጵያ መድን 2-0 አዲስ አበባ ፖሊስ(09:00 መድን ሜዳ) ወልድያ ከ ሙገር ሲሚንቶ (ወልድያ) አማራ ውሃ ስራ ከ ሱሉልታ ከተማ (ባህርዳር) አክሱም ከተማ ከ ኢትዮጵያ ውሃ ስፖርት (አክሱም) ድሬዳዋ ፖሊስ ከ ነቀምት ከተማ (ድሬዳዋ) ሀላባ ከተማ ከ ጅማ አባ ቡና (ሀላባ) ወራቤ ከተማ ከ ጂንካ ከተማ (ወራቤ) ደቡብ ፖሊስ ከ ሻሸመኔ ከተማ (ሀዋሳ) ጅማ ከተማ ከ አዲስ አበባ ከተማ (ጅማ) ነገሌ ቦረና ከ ፌዴራል ፖሊስ (ነገሌ ቦረና)
1
6eb3b519349ef832ddc9bf3042373e53
6eb3b519349ef832ddc9bf3042373e53
ብሪታንያ ሩሲያን አስጠነቀቀች
ባለፈው ዓመት ሶልስበሪ ውስጥ በሰርጌ ስክሪፓል ላይ ለደረሰው ጥቃት ተጠያቂዎች የሆኑት ሁለቱ ሩስያውያን ለፍርድ መቅረብ እንዳለባቸው፣ ቴሬሳ May ለሩስያው መሪ እንዳሳሰቡ፣ ዛሬ ዐርብ ከቢሯቸው ይፋ የሆነው መግለጫ አመልክቷል።የጠቅላይ ሚኒስትር May አስተያየት የተሰማው፣ ኦሳካ ጃፓን በሚካሄደው፣ የጂ20 ጉባዔ ጎን ከፕሬዚደንት ፑቲን ጋር በተገናኙበት ወቅት ነው።
1
df6769e3e6822fd3e212c34a21ba08d7
b8005a6bf07bb764f46465bfa9474cd3
ወላይታ ድቻ ግብ ጠባቂ አስፈርሟል
ከፕሪምየር ሊጉ ከመውረድ በመጨረሻው ጨዋታ የተረፈው ወላይታ ድቻ የ3 ተጫዋቾችን ፊርማ እንዳጠናቀቀ አስታውቋል።የክለቡ ስራ አስኪያጅ አቶ አሰፋ ሁሊሶ ለሶከር ኢትዮጵያ እንደገለፁት ሳምሶን ቆልቻ፣ ታሪክ ጌትነት እና ኄኖክ ኢሳይያስ ለክለቡ ፈርመዋል።ሳምሶን ቆልቻ በ2006 ወላይታ ድቻ ወደ ፕሪምየር ሊግ እንዲያድግ ካስቻሉ ተጫዋቾች መካከል የሚጠቀስ ሲሆን አንድ የውድድር ዓመትም ከክለቡ ጋር በሊጉ ማሳለፍ ችሎ ነበር። በ2008 በደሴ ከተማ፣ በ2009 በሀዲያ ሆሳዕና እንዲሁም በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት በቻምፒዮኑ ጅማ አባ ጅፋር አሳልፎ ወደ ቀድሞ ክለቡ በመመለስ በ2 ዓመት ኮንትራት ተቀላቅሏል።ኄኖክ ኢሳይያስ በአንድ ዓመት ኮንትራት ድቻን ተቀላቅሏል። የቀድሞው የደደቢት አማካይ ባለፈው የውድድር ዓመት መጀመርያ ወደ ሽረ እንዳሥላሴ ካመራ በኋላ በግማሽ ዓመት ወደ ጅማ አባ ቡና አቅንቶ ጥሩ ጊዜ በማሳለፍ የተጠናቀቀውን ዓመት በሌላው የጅማ ክለብ ጅማ አባ ጅፋር አሳልፏል። በተለያዩ ሚናዎች የሚጫወተው ኄኖክ ለአሰልጣኝ ዘነበ ፍስሀ አማራጮች እንደሚፈጥር ይጠበቃል።ሌላው ለቡድኑ የፈረመው ግብ ጠባቂው ታሪክ ጌትነት ነው። ታሪክ በ2004 ወደ ዋናው ቡድን ካደገ ወዲህ የተጫዋችነት ዘመኑን በደደቢት ያሳለፈ ሲሆን ለብሔራዊ ቡድንም በተደጋጋሚ የመጠራት እድል አግኝቷል። ግብ ጠባቂው በድቻ የአንድ ዓመት ኮንትራት ተፈራርሟል።ክለቡ ካስፈረማቸው ተጫዋቾች በተጨማሪ ኮንትራታቸው የተገባደዱ 5 ተጫዋቾችንም ውል አድሷል። አብዱልሰመድ ዓሊ፣ ያሬድ ዳዊት፣ ሙባረክ ሽኩር፣ ጸጋዬ ብርሀኑ እና ውብሸት ዓለማየሁ ውላቸው የታደሰላቸው ተጫዋቾች ናቸው።የክለቡ ስራ አስኪያጅ አቶ አሰፋ ባለፈው ዓመት የተከሰቱ የዝውውር ስህተቶችን ላለመድገም ተጠንቅቀው በዝውውር መስኮቱ እንደሚሳተፉና ተጨማሪ ተጫዋቾችን በቀጣይ ጊዜያት ለማስፈረም እንደሚንቀሳቀሱ ለሶከር ኢትዮጵያ ገልፀዋል።
0
9bc6bbf35341ebf870fe5f93dc3ffef4
77cdc91e35c907e7ac6ed549f79bca43
በእናቶች ሞት ቅነሳ ውጤት እየተመዘገበ ነው፦ጤና ጥበቃ
የሶማሌ ክልላዊ መንግስት በክልሉ ሰላምና ፀጥታ እንዲረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ በመሥራቱ ውጤት እየተመዘገበ መምጣቱን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ገለጹ።የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሃመድ የመንግስታቸውን የአምስት ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ለክልሉ ምክር ቤት አቀርበዋል።በሪፖርታቸውም አዲሱ የክልሉ አመራር ሥራ ከጀመረ ወዲህ በክልሉ ሲስተዋል የነበረው ብጥብጥ፣ ረብሻና አለመረጋጋት በሙሉ እንዲወገድ መስራቱን አመልክተዋል።በክልሉ ሊከሰቱ የነበሩ ሰላሳ የጎሳ ግጭቶች በውይይት እንዲፈቱ በመደረጉ በአሁኑ ወቅት በክልሉ ውስጥ መረጋጋት እየታየ መምጣቱን ተናግረዋል።የመንግስታዊ መዋቀሩን እስከታች ድረስ በማጠናከር በቀድሞ የክልሉ መንግስት መስተዳድር በህዝብ ሀብት ላይ ዝርፊያ ፈጽመዋል ተብለው የተጠረጠሩ የ1 መቶ ግለሰቦች የባንክ ሒሳብ ቁጥር መዘጋቱንም አንስተዋል።በተጨማሪም 117 ግለሰቦች እና ሰባት ድርጅቶች ደግሞ በምርመራ ሂደት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል ።በርዕሰ መስተዳድሩ በቀረበው የአምስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤቱ አባላት ጥያቄዎችና እና አስተያየቶች ተነስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል።(ኢዜአ)
0
2ae20e7b1ca9a91fbc225a45d11eafab
e129068e68d952d9a7bb903e18a03628
ከሀገር የሸሸ ገንዘብን ለማስመለስ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑ ተገለፀ
የጥረት ኩባንያ አካል የሆነው አምባሰል የንግድ ስራዎች ድርጅት በአማራ ክልልና ከክልሉ ውጭ ለተፈናቀሉ የአማራ ክልል ተወላጆች መልሶ ማቋቋሚያ የሚሆን የ5 ሚሊዮ ብር ድጋፍ አደረልጓል፡፡የአምባሰል የንግድ ስራዎች ድርጅት ባህርዳር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ አበረ ይንገስ መጋቢት 5 በተዘጋጀ የርክክብ ስነ-ስርዓት ላይ የ5 ሚሊዮን ብር ቼክ ለክልሉ ምግብ ዋስትናና አደጋ መከላከል ኤጀንሲ ሰጥተዋል፡፡በርክክብ ስነ-ስርዓቱ ስራ አስኪያጁ በክልሉ ከተለያዩ አካባቢወች ተፈናቅለው በመጠለያ ለሚገኙ ዜጎች ችግራቸው እስኪፈታ ድረስ ቀጣይ ድጋፎችን እንደሚያደርጉ ተናግረዋል፡፡ኩባንያው የግብርና ምርቶችን ወደ ውጭ ኤክስፖርት በማድረግ ከማህበረሰቡ ጋር ካለው ጥብቅ ዝምድና አንፃር ለእነዚህ ተፈናቃዮች ድጋፍ ማድረጋችን ማህበራዊ ኃላፊነታችን ነው ሲሉም ገልፀዋል፡፡ የአማራ ክልል ምግብ ዋስትናና አደጋ መከላከል ኤጀንሲ ምክትል ኃላፊ የሆኑት አቶ አማረ ክንዴ በበኩላቸው አሁን ላይ በአማራ ክልል በተለይም ከማዕከላዊና ከምዕራብ ጎንደር አካባቢ የተፈናቀሉ ከ90ሺ በላይ የሚሆኑ ዜጎች በ13 መጠላያ ጣቢያወች መኖራቸውን ገልፀው ዜጎችን በዘላቂነት ለማቋቋም ሰፊ ስራዎች እየተሰሩ ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡አምባሰል የንግድ ስራዎች ድርጅት ላበረከተው 5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ በተፈናቃዮች ስም ምስጋና አቅርበዋል፡፡አቶ አማረ አክለውም ተፈናቃዮችን ለማቋቋም በርካታ ስራወች እየተሰሩ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ 150ሺ ቆርቆሮ ከመጭው ቅዳሜ ጀምሮ ወደ ተጎጂዎች አካባቢ መጓጓዝ እንደሚጀምር ተናግረዋል፡፡በቼክ ርክክብ ስነ-ስርዓቱ ቾይዝ ውኃን ጨምሮ ሌሎች ተቋማትም የተለያዩ ድጋፎችን አድርገዋል፡፡አምባሳል የንግድ ስራዎች ድርጅት በባህር ዳር ከተማ በተከሰተው የእሳት አደጋ ከቤት ንብረታቸው ለተፈናቀሉ ሰዎች 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡ጥረት ኮርፖሬት በተመሳሳይ ለተፈናቃዮቹ የ 10 ሚሊየን ብር ማድረጉ የሚታወስ ነው፡፡/የአማራ ብዙሃን መገናኛ/
0
002968b327792b747ce61d2fc110fd0e
002968b327792b747ce61d2fc110fd0e
አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾችን ወደ ዋናው ቡድን አሳደገ
ያለፉትን ዓመታት ለታዳጊዎች ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት እና ወደ ዋናው ቡድን በማሳደግ ስኬታማ እየሆነ የመጣው አዳማ ከተማ ሁለት ተጫዋቾችን ከተስፋ ቡድኑ አሳደገ።ከ17 እና ከ20 ዓመት በታች ቡድኖቹ በወጥነት ያለፉትን አምስት ዓመታት ውጤታማ ውድድሮችን በማድረግ ብቻ ሳይሆን ወደ ዋናው ቡድን ታዳጊዎችን በማሳደግ በሊጉ ካሉ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ክለቦች አንዱ የሆነው አዳማ ከተማ ብሩክ ቦጋለ እና ዳግም ታረቀኝን በአረንጓዴ መታወቂያ (ቲሴራ) አሳድጓል።ብሩክ ቦጋለ የግራ መስመር ተከላካይ ሲሆን ያለፉትን ሦስት ዓመታት ከ17 ቡድን ጀምሮ በመጫወት ተስፋ የሚጣልበት ተጫዋች ነው። ብሩክ በአዳማ ዋናው ቡድን ከተጫወተ በኋላ ወደ ወላይታ ድቻ በማምራት አሁን በከፍተኛ ሊግ ለገላን ከተማ በመጫወት ላይ የሚገኘው የወንደሰን ቦጋለ ታናሽ ወንድም ነው። ሌላው ወደ ዋናው ቡድን ያደገው ዳግም ታረቀኝ የአጥቂ ስፍራ ተጫዋች ሲሆን በአዳማ ከታችኛው የእድሜ እርከን ጀምሮ ያደገ ከመሆኑ ባሻገር በ2010 ከ20 ዓመት በታች ውድድር ላይ በከፍተኛ ጎል አስቆጣሪዎች ስም ውስጥ ተፎካካሪ ከነበሩ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነበር።አዳማ ከተማ ከታዳጊ እና ወጣት ቡድኑ ከ2006 ጀምሮ ታከለ ዓለማየሁ፣ ከነዓን ማርክነህ፣ ቡልቻ ሹራ፣ ሱራፌል ዳኛቸው፣ በረከት ደስታ፣ መናፍ ዐወል እና ፉአድ ፈረጃ የመሳሰሉ ተጫዋቾን ያፈራ ሲሆን በሲዳማ ቡና እየተጫወተ የሚገኘው ዮናታን ፍስሐም መነሻው አዳማ ከተማ ነበር።
1
2845fa69e11126252eeb094b0f9bd050
f8f55ad92f0ca9f67161b9d12c5883f8
አሰልጣኝ ዘላለም ሽፈራው ለድሬዳዋ ከተማ አሰልጣኝነት ከስምምነት ደርሰዋል
አሰልጣኝ ተመስገን ዳናን በዋና አሰልጣኝነት የቀጠረው ደቡብ ፖሊስ የመጀመሪያ ተጫዋች በማድረግ ዘላለም ታደለን አስፈረመ፡፡በርካታ ወጣት ተጫዋቾችን ወደ ክለቡ በአዲስ መልክ እንደሚያመጣ የሚጠበቀው ደቡብ ፖሊስ በአንድ ዓመት ውል ነው የመሀል የተከላካይ ስፍራ ተጫዋቹን ያስፈረመው፡፡ ዘላለም ከሀዋሳ ከተማ የታዳጊ ቡድን እስከ ዋናው ድረስ ከዚያም በወላይታ ድቻ፣ ሲዳማ ቡና እና ሀድያ ሆሳዕና ተጫውቶ ያሳለፈ ሲሆን በ2011 ወደ ፕሪምየር ሊግ ባደገው ወልቂጤ ከተማ አሳልፏል።በፎርማት ለውጡ ምክንያት በፕሪምየር ሊጉ መሰንበቱን ያረጋገጠው ደቡብ ፖሊስ ትላንት በይፋዊ ጋዜጣዊ መግለጫ ተመስገን ዳናን የክለቡ አዲስ አሰልጣኝ አድርጎ መቅጠሩ ይታወሳል፡፡
0
ddc611e0a0a5922da0b66fce16054c04
ddc611e0a0a5922da0b66fce16054c04
የኢትዮጵያ ወታደሮች አሜሶምን ሊቀላቀሉ ነው
አዲስ አበባ፤ ህዳር 2/2006 (ዋኢማ) – የኢትዮጵያ ወታደሮች በሶማሊያ የአፍሪካ የሰላም ማስከበር ጦርን በመቀላቀል በአልሸባብ ላይ ለሚደረገው ዘመቻ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ጠቅላይ ሚንስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ ገለፁ፡፡ጠቅላይ ሚንስትሩ የኬኒያውን ምክትል ፕሬዘዳንት ዊሊያም ሩቶን በፅፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡በቅርቡ በኢትዮጵያ ላይ የደረሰው አዲስ የሽብር ስጋትም መንግስት አስተማማኝ መረጃ ያለው እንደሆነና በሁሉም አቅጣጫ በሽብርተኝነት ላይ የተጀመረውን ዘመቻ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ጠቅላይ ሚንስትር ሀይለማሪያም ደሳለኝ አረጋግጠዋል፡፡የኬኒያውን ምክትል ፕሬዘዳንት ዊሊያም ሩቶን በበኩላቸው ኢትዮጵያ የአፍሪካ የሰላም ማስከበር ጦርን በመቀላቀል ሽብርተኝነትን ለመዋጋት ያሳየችውን ፍላጎት አድንቀዋል፡፡ሁለቱ መሪዎች በድንበር አካባቢ ስለሚነሱ ግጭቶች የተወያዩ ሲሆን በአካባቢው የሚኖሩ አርብቶ አደሮች የአኗኗር ስልትን በመቀየር ግጭቶችን ለመቀነስ እንደሚቻል ጠቁመዋል፡፡በአለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ጉዳይ ኢትዮጵያ ያሳየችውን አቋም የኬንያ ህዝብና መንግስት የማይረሱት ውለታ እንደሆነ ምክትል ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ገልፀዋል፡፡ጠቅላይ ሚንስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ በበኩላቸው ጉዳዩ የኬኒያ ብቻ ሳይሆን የመላው አፍሪካ ጉዳይም ጭምር መሆኑን ገልፀው ከእንግዲህ አፍሪካ ከአህጉሪቱ ውጭ ለሚመጣ ጫና ቦታ የላትም ብለዋል ሲል ካፒታል ኤፍ ኤምን ጠቅሶ ኢሬቴድ ዘግቧል፡፡
1
4d90bc5e9310856cdd56fa3baa7cc901
89a5c5b2a454d22edab34422e52a1575
​አርባምንጭ ከተማ እዮብ ማለን በአሰልጣኝነት ሾመ
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ደቡብ-ምስራቅ ዞን ዛሬ በተደረጉ ጨዋታዎች ፍፃሜውን አግኝቷል፡፡ ድሬዳዋ ከተማ እና አርባምንጭ ከተማም ወደ ማጠቃለያው ዙር ማለፋቸውን አረጋግጠዋል፡፡ቀደም ብሎ ቻምፒዮንነቱን ያረጋገጠው ሀዋሳ ከተማ ወደ አሰላ ተጉዞ በጥሩነሽ ዲባባ አካዳሚ 1-0 ተሸንፏል፡፡ በሌሎች ውጤት ላይ የተመሰረተ የማለፍ ተስፋ የነበረው ጥሩነሽ ዲባባ አካዳሚ ድል ቢቀናውም አርባምንጭ እና ድሬዳዋ ነጥብ በመጋራታቸው ሳያልፍ ቀርቷል፡፡ወደ ይርጋለም የተጓዘው አዳማ ከተማ በሲዳማ ቡና 4-1 ተሸንፏል፡፡ አዳማ ከተማ ጨዋታውን በድል ቢያጠናቅቅ ወደ ማጠቃለያ ውድድሩ ማለፉን ያረጋግጥ ነበር፡፡አርባምንጭ ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ ባደረጉት ጨዋታ ካለግብ አቻ ተለያይተው ወደ ማጠቃለያው ውድድር ተያይዘው አልፈዋል፡፡ የመጨረሻው ሳምንት ውጤቶች እና ግብ አግቢዎች የሚከተሉት ናቸው፡- ተራማጅ ተስፋዬ ፣ አይዳ ኡስማን ፣ አረጋሽ ፀጋ ፣ ትርሲት መገርሳ | አብነት ጎበና ናርዶስ ጌትነት
0
46b1e55bfd11f287f8cb8f460aa574eb
46b1e55bfd11f287f8cb8f460aa574eb
ጅቡቲ ከኢትዮጵያ ጋር የሚያገናኛትን የባቡር መስመር ዝርጋታ ጀመረች
-ጅቡቲ ከኢትዮጵያ ጋር የሚያገናኛትን የባቡር መስመር ፕሮጀክት ይፋ አደረገች።አዲሱ የጅቡቲ-ኢትዮጵያ የባቡር መስመር ፕሮጀክት በ3ኛው የአገራቱ የጋራ ትብብር የምክክር መድረግ ላይ ይፋ የተደረገ ሲሆን ፥ የባቡር መስመሩ ከጅቡቲ ከተማ በመነሳት- በድሬዳዋ- አዲስ አበባ የሚዘልቅ ነው ።ሁለቱን አገራት የሚያገናኘው የባቡር መስመር 600 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚያስወጣ ሲሆን፥ ገንዘቡም ከቻይና ኤግዚም ባንክ በብድር መገኘቱ ነው የተመለከተው።የቻይናው የሲቪል ምህንድስና ግንባታ ኮርፖሬሽን (ሲ ሲ ኢ ሲ ሲ) የባቡር መስመሩን የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ስራዎችን የሚያከናውን መሆኑም ተገልጿል ።የኢትዮጵያ የትራንስፖርት ሚንስትር አቶ ወርቅነህ ገበየሁ ይህ የባቡር መስመር ዝርጋታ የአገራቱን ማህበረ ኢኮኖሚ ትስስሮች በማጠናከር ረገድ ከፍተኛ ድርሻ እንደሚኖረው ነው ይፋ በማድረግ ስነ ስርዓቱ ላይ የተናገሩት ።በተጨማሪም አዲሱ የባቡር መስመር የአገራቱን የግብይት ተግባራት ለማሳለጥ ከማገዙም ባለፈ ጅቡቲን በኢትዮጵያ በኩል ደቡብ ሱዳንን በማገናኘት ረገድም ሚና እንደሚኖረው የጅቡቲው የትራንስፖርት ሚንስትር ሚስትር ሙሳ አህመድ ተናግረዋል።የጅቡቲ የባቡር ድርጅት ዳይሬክተር በበኩላቸው ፥ አጠቃላይ የባቡር መስመር ዝርጋታው ሁለት ዓመታትን እንደሚፈጅ ገልጸዋል።(ኤፍ ቢ ሲ)
1
b4da2967e8e5c459f377aea65c7b8026
715fdf4b495bb69139de852cfcb2c8a4
ለህዳሴው ግድብ ግንባታ እንዲነሱ የተደረጉ ካሳ ስላልተከፈላቸው እየተመለሱ ነው ተባለ
በአማራ ክልል የሚገኙ ዩኒየኖች፣ የህብረት ስራ ማህበራትና የአደራጅ መስሪያ ቤት ሰራተኞች ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ማሰሪያ ከ11 ሚሊዮን ብር በላይ የቦንድ ግዥ መፈጸማቸዉን የክልሉ ህብረት ስራ ማህበራት ማስፋፊያ ኤጀንሲ አስታወቀ ። የኤጀንሲዉ የህዝብ ግንኙነት ዋና የስራ ሂደት መሪ አቶ ሞላ ትዕዛዙ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት የቦንድ ግዥውን የፈጸሙት በክልሉ የሚገኙ ስምንት ዩኒየኖች፣ 702 መሰረታዊ የህብረት ስራ ማህበራትና በየደረጃው የሚገኙ የአደራጅ ተቋማት ሰራተኞች ናቸው። ከተፈጸመው የቦንድ ግዥ ውስጥም ከስድስት ነጥብ ስድስት ሚሊዮን ብር የሚበልጠውን መሰረታዊ የህብረት ስራ ማህበራት፣ ከሦስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ብር በላይ የሚሆነውን ደግሞ ስምንት ዩኒየኖች ተግባራዊ አድርገዋል ። በተጨማሪም የአደራጅ ተቋማት የሆኑት የክልሉ ህብረት ስራ ማስፋፋፊያ ኤጀንሲና በስሩ የሚገኙ የዞንና የወዳ ጽህፈት ቤቶች ሰራተኞች ከወር ደመወዛቸው ለሁለተኛ ጊዜ ከአንድ ሚሊዮን 100ሺህ ብር በላይ በማዋጣት የቦንድ ግዥ ማከናወናቸውን ተናግረዋል ፡፡ በዚህ ዓመት ለህዳሴው ግድብ ማሰሪያ የሚሆን ገንዘብ ካለፈው ዓመት በተሻለ መልኩ ሊዋጣ የቻለው ፕሮጀክቱ የተነደፈውን የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በማሳካት የሀገራችንን የህዳሴ ጉዞ ማፋጠን እንደሚያስችል በሁሉም ዘንድ በቂ ግንዛቤ በመፈጠሩ እንደሆነም አስረድተዋል፡፡ ባለፈው ዓመት ለህዳሴው ግድብ ማሰሪያ ዩኒየኖች፣ የህብረት ስራ ማህበራትና የአደራጅ መስሪያ ቤት ሰራተኞች በመጀመሪያው ዙር ከ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ የቦንድ ግዥ መፈጸማቸውን አቶ ሞላ አስታውቀዋል፡፡ በአማራ ክልል ተደራጅተው የሚንቀሳቀሱ 56 ሁለገብ የገበሬዎች የህብረት ስራ ማህበራት ዩኒየኖችና ከስምንት ሺህ የሚበልጡ መሰረታዊ የህብረት ስራ ማህበራት እንደሚገኙም ታውቋል ።
0
6b45f929980281b3532fc6e5e89e377d
01aae8f6e571d4cab69176f25098706d
አቶ አገኘሁ ተሻገር ለተለያዩ የስራ ሀላፊዎች ሹመት ሰጡ
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ሙላቱ ተሾመ ለ12 አምባሳደሮች ሹመት ሰጡ።የፕሬዚዳንቱ ጽህፈት ቤት ለዋልታ በላከው መግለጫ፤ ፕሬዚዳንት ሙላቱ ኢትዮጵያን በውጪ አገሮች ለሚወክሉ አምባሳደሮች ሹመት ሰጥተዋል።ፕሬዚዳንቱ ሹመት የሠጡት ኢትዮጵያን በውጭ አገሮች ለሚወክሉ 11 የባለሙሉ ሥልጣን አምሳደሮች እና አንድ አምባሳደር እንደሆነ መግለጫው ያመለከተው።በዚህ መሰረት ባለሙሉ ስልጣን አምበሳደር ሆነው የተሾሙት አቶ ካሣ ተክለብርሃን፣ ወይዘሮ አስቴር ማሞ፣ ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያም፣ አምባሳደር ብርሃነ ገብረክርስቶስ፣ ፕሮፌሰር መርጋ በቃና፣ አቶ ዓሊ ሱለይማን፣ ፕሮፌሰር አድማሱ ፀጋዬ፣ አምባሳደር ተበጀ በርሄ፣ አቶ መታሰቢያ ታደሰ፣ አቶ ሙሉጌታ ዘውዴ እና ወይዘሮ ሉሊት ዘውዴ ናቸው።አቶ እውነቱ ብላታ ደግሞ በአምበሳደርነት ተሹመዋል።የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት አንቀጽ 71 ንኡስ አንቀጽ 3፤ አገሪቷን በውጪ አገሮች የሚወክሉ አምባሳደሮችና ሌሎች መልዕክተኞች በጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅራቢነት ሹመት የሚሰጡት ፕሬዚዳንቱ መሆናቸውን ደንግጓል።
0
82f2b9070dadace45d03c4a8b561541f
4a23b8c2d19e5be370504a0a69304655
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ የ8ኛ ክፍል ፈተና ከታህሳስ 26 እስከ 28 እንደሚሰጥ ተገለፀ
ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 10/2013 ዓ.ም (አብመድ) በባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ለሚገኙ የ12ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የማካካሻ ትምህርት መስጠት መጀመሩን መምሪያው አስታውቋል፡፡በባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ለሚገኙ ለ12ኛ እና ለ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ሀገራዊና ሀገር አቀፍ ዜና ፈተና ከመወስዳቸው በፊት ለ45 ቀናት የሚቆይ የማካካሻ ትምህርት ከጥቅምት 09/2013 ዓ.ም ጀምሮ መስጠት መጀመሩን የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት መምሪያ ምክትል ኃላፊ መላክ ጀመረ ተናግረዋል፡፡“ዛሬ ተቀብለን ማስተማር የጀመርነው የኮሮናቫይረስን ለመከላከል የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል የተጠቀሙ ተማሪዎችን ብቻ ነው፡፡ ከትምህርት ሚኒስቴር የተላከው ጭምብል እስከዛሬ ባይደርሰንም ወላጆች ለልጆቻቸው በገዙት ተጠቅመን ነው ማስተማር የጀመርነው” ብለዋል አቶ መላክ። መማርም ሆነ ማስተማር የሚቻለው ጤና ሲኖር ብቻ ስለሆነ ተማሪዎች ያለማንም ክትትል ጭምብል እንዲጠቀሙም ጥሪ አቅርበዋል፡፡በሚቀጥለው ሳምንት ከ1ኛ ክፍል በስተቀር ሁሉም ትምህርት ቤቶች ለሦስት ሳምንታት የማካካሻ ትምህርት እንደሚወስዱ የተናገሩት ምክትል መምሪያ ኃላፊው ከማካካሻው ትምህርት በኋላ የ2013 ትምህርት ዘመን ሙሉ በሙሉ የመማር ማስተማር ሂደቱ እንደሚቀጥል አስገንዝበዋል፡፡ወረርሽኙን ለመከላከል ሲባል ትምህርት ሚኒስቴር ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የመንግሥት ትምህርት ቤቶች ከአንድ እስከ ሦስት ፈረቃ እንዲሁም የግል ትምህርት ቤቶች ደግሞ በአንድ እና ሁለት ፈረቃ ብቻ ማስተማር እንደሚቀጥሉ አቶ መላክ ጠቁመዋል፡፡
0
5684aac177eb2417e87b318d37e6ba87
044e05ae15dc2cea678eecc619debd6d
አሜሪካ በቻይና ዲፕሎማቶች ላይ የጉዞ ክልከላ ማዕቀቦችን ጣለች
አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 6፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) አሜሪካ የኔቶ አባል በሆነችው ቱርክ ላይ ማዕቀብ መጣሏን አስታወቀች፡፡ማዕቀቡ አንካራ ባለፈው አመት ከሩሲያ የገዛችውን ከምድር ወደ አየር ተወንጫፊ ሚሳኤልን ተከትሎ የተጣለ ነው ተብሏል፡፡እንደ አሜሪካ አገላለጽ ቱርክ የገዛችው መሳሪያ ከሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) ቴክኖሎጅ ጋር አብሮ የማይሄድና የማይጣጣም ነው፡፡ውስብስብ ነው የሚባሌውና ዘመናዊው ኤስ 400 ሚሳኤል ለቃል ኪዳኑ ጥምረት አደጋ ነው ስትልም አሜሪካ ገልጻለች፡፡የአሁኑ ማዕቀብም በቱርክ የጦር መሳሪያ ግዥ እና ተዛማጅ ጉዳዮች ላይ የተጣለ መሆኑን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታውቋል፡፡ቱርክ በበኩሏ ማዕቀቡን ተገቢነት የሌለው በማለት አሜሪካ በጉዳዩ ላይ እንድታስብበት ጠይቃለች፡፡ጉዳዩን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት እንደምትሞክርም የሃገሪቱ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ገልጿል፡፡አሜሪካ ቀደም ብላ ቱርክን ከሩሲያ ከገዛችው የሚሳኤል ሲስተም ጋር ተያይዞ ከኤፍ -35 ተዋጊ አውሮፕላኖች የግዥ ስምምነት ሰርዛታለች፡፡ምንጭ፡-ቢቢሲከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
0
e769e5fc351315710f9222f940cb09b7
e769e5fc351315710f9222f940cb09b7
በኬንያ የቱሪስት መዳረሻ ሥፍራን እየጎበኙ የነበሩ ሰዎች በጎርፍ መወሰዳቸው ተሰማ፡፡
ባሕር ዳር፡ ነሐሴ 27/2011 ዓ.ም (አብመድ) በአደጋው የሁለት ሰዎች ህይዎት አልፏል፤ የቀሪዎችም ቢሆን ያሰጋል ብሏል ፖሊስ፡፡ውብ እና ልዩ መልከዓ ምድራዊ ገጽታን የተላበሰ የጎብኝዎች መዳረሻ ሥፍራ ነው፤ ሄልስ ጌት ተብሎ የሚጠራው የኬንያ ብሔራዊ ፓርክ፡፡ በተለይም ደግሞ በውስጡ ገባር ወንዞች የሚጋልቡበት ሸለቋማው ክፍል በውስጡ ለማለፍ የሚያስፈራ ግን ደግሞ የሚያጓጓ እንደሆነ ነው የሚነገረው፡፡ እናም በኬንያውያኑም ሆነ በውጭ ሀገራት ጎብኝዎች ተመራጭ መዳረሻ ሥፍራ ነው፡፡
1
194a21a36b66dd053efdc75b966f54a9
194a21a36b66dd053efdc75b966f54a9
ኢትዮጵያ ለፍቅረኞች ቀን አከባበር ወደ ውጭ ከላከችው የአበባ ምርት ከ21 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ ተገኘ
– ኢትዮጵያ በዘንድሮው የፍቅረኞች ቀን (ቫላንታይን) ቀን አከባበር ወደ የተለያዩ የዓለም ሀገራት በላከችው የአበባ ምርት ከ21 ሚሊየን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ገቢ ማግኘቷን የኢትዮጵያ ሆርቲካልቸር ልማት ኤጀንሲ አስታወቀ።የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዓለም ወልደገሪማ እንደገለፁት፤ ሀገሪቱ 21 ሚሊየን 435 ሺ 620 ዶላር ገቢውን ያገኘችው 246 ሚሊየን 549 ሺ 647 የሚሆን የአበባ ዘንግ ለዓለም ገበያ የቫላንታይን አከባበር ወቅት ነው።ገቢው ከፍተኛ መሆኑን የገለፁት አቶ አለም፤ ሀገሪቱ በዚህ ወቅት ለዓለም ገበያ ባቀረበችው የአበባ ምርት ይህን ያህል ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ስታገኝ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው በማለት ተናግረዋል።በዘንድሮው የቫላንታይን አከባበር ለዓለም ገበያ የቀረበው አበባ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ የቫላንታይን ወቅት ጋር ሲነፃፀር በገቢ 3 ነጥብ 74 ሚሊየን ዶላር ሲሆን፤ ይህም ከ21 በመቶ በላይ እድገት ማሳየቱን ገልፀዋል።ለውጭ ገበያ የቀረበው የአበባ መጠን ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በመጠን 35 ነጥብ 8 ሚሊየን ዘንግ ጭማሪ እንዳለው ተናግረዋል።በዋናነት 85 በመቶ የሚሆነው የአበባው ምርት የተላከው ለአውሮፓ ገበያ መጠሆኑን ጠቁመው፤ ቀሪው 15 በመቶ በአሜሪካ፣ ኖርዌይ፣ ካናዳ፣ ጃፓን፣ ሳውድ አረቢያና ሌሎች ሀገራት የተላከ መሆኑን ዳይሬክተሩ መናገራቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።
1
fa7f9a7a1c599e96a346857767fcbff7
91f807c3d80db6bf4a7d86f4b9701ae0
በኮንጎ 4መቶ ሺሕ ሕፃናት ከባድ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ገጠማቸው
አዲስ አበባ፡- የአየርላንድ መንግሥት የምግብ እጥረት ለሚያጋጥማቸው ወገኖች የሚውል የ325 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ። የኢትዮጵያ መንግሥት እና የአየርላንድ መንግሥት ትናንት በገንዘብ ሚኒስትር የ325 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ በተፈራረሙበ ወቅት የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ አድማሱ ነበበ እንደገለጹት፤ የተገኘው የገንዘብ ድጋፍ የምግብ እጥረት ለሚያጋጥማቸው ወገኖች ማቋቋሚያ የሚውል ነው። በተለይም በገጠራማው የአገሪቱ ክፍል ያሉ ወገኖች የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኙ ይደረግበታል። ከ1990ዎቹ ጀምሮ ከተለያዩ ለጋሽ አገራት በሚገኝ የገንዘብ ድጋፍ የተጀመረው የሴፍቲኔት ፕሮግራም በአራት ክልሎች ሲሰራበት የቆየ ሲሆን አሁን የተገኘው የገንዘብ ድጋፍ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር እስከ 2020 ድረስ የሚቆይ እንደሆነም ተገልጿል። ፕሮግራሙ በአማራ፣ ትግራይ፣ ኦሮሚያ እና የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልል ተግባራዊ የሚሆን ነው። እንደ ሚኒስትር ዴኤታው ገለጻ፤ በሴፍቲኔት ፕሮግራሙ በተያዘው ዓመት በ382 የተለዩ ወረዳዎች ሰባት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን የምግብ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ወገኖችን ለመደገፍ ታቅዷል። የተለዩት ወረዳዎች በአፋር፣ አማራ፣ ድሬዳዋ፣ ሐረር፣ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል፣ ሶማሌ፣ ትግራይ እና ኦሮሚያ ክልሎች ውስጥ የሚገኙ ናቸው።አዲስ ዘመን ቅዳሜ ጥቅምት 15/2012 ዋለልኝ አየለ
0
7a6da71948f86efe229dd43fbbacafbb
7a6da71948f86efe229dd43fbbacafbb
በአዲስ አበባ በነገው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ራሱን ከኮሮና ቫይረስ እየጠበቀ እንዲሳተፍ ጥሪ ቀረበ
አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 25 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ በነገው ዕለት በሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ራሱን ከኮሮና ቫይረስ እየጠበቀ እንዲሳተፍ ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ ዑማ ጥሪ አቀረቡ።ምክትል ከንቲባው በነገው ዕለት በሚተከለው 2 ሚሊየን ችግኝ ዙሪያ ለከተማው ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡ከችግኝ ተከላው ጎን ለጎን የከተማዋ ነዋሪዎች በመዲናዋ እየተስፋፋ የመጣውን የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ለመከላከል ከጤና ሚኒስቴርና ከከተማዋ ጤና ቢሮ እየተሰጡ ያሉ መመሪያዎችን በአግባቡ እንዲተገብሩ አሳስበዋል።በከተማዋ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ሊተከል በእቅድ ከተያዘው 7 ሚሊየን ችግኝ መካከል ከ4 ነጥብ 6 ሚሊየን በላይ የሚሆነው ከ1 ሚሊየን በላይ ሰዎችን በማሳተፍ መተከሉን አንስተዋል።የጋራ ቤታችን የሆነችውን አዲስ አበባን በጋራ እንገንባ ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ ከሚተከሉት ችግኞች መካከል ለምግብነት የሚውሉ የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኞች በመኖራቸው ለከተማ ግብርና የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ያበረክታሉም ነው ያሉት፡፡ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ ኡማ የታላቁ ህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ዙር የውሃ ሙሌት በአጭር ጊዜ መጠናቀቁ የችግኝ መትከል ጥቅሙን ከወዲሁ የሚያመላክት ነው ብለውታል።በመሆኑም በነገው ዕለት የከተማዋ ነዋሪዎች በመኖሪያ አካባቢያቸው እና ለተከላ በተዘጋጁ ስፍራዎች ላይ አሻራቸውን እንዲያሳርፉ ጥሪ አቅርበዋል።በአዲስ አበባ በነገው ዕለት ከንጋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ የ2 ሚሊየን ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ይከናወናል።በምስክር ስናፍቅ
1
2b0f100a0c117e9fafaabeb6359bd545
33bfd27c581283b48d5a2c2780dbc887
የኮሮናቫይረስን ለመከላከል የኤርትራ ዝግጅት
የኢቦላ በሽታን አስቀድሞ ለመከላከል የሚያስችል ሰፊ ዝግጅት መደረጉን ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ደ መቀ መኮነን ገለፁ፡ምክትል ጠቅላይ ሚንስትሩ በኮተቤ አካባቢ የሚገኘውን የኢቦላ ህክምና ማዕከል ሲጎበኙ እንዳሉት፣ መንግስት በሽታው የተከሰተባቸውን ሀገራት ተሞክሮን ያካተተበት የመከላከል ዝግጅት ተጠናክሮ ቀጥሏል፡በክልሎችም ኢቦላን የመከላከልና የመቆጣጠር ስራ በከፍተኛ አመራር እየተሰራ መሆኑን የገለፁት አቶ ደመቀ፣ ኢቦላን የመከላከልና የመቆጣጠር ስራን የሚመራው ብሄራዊ ኮሚቴ በሽታውን ለመከላከል የሚያስፈልጉ ግብአቶች እያሟላ ነው ብለዋል፡እስካሁንም የኢቦላ በሽታ ወደ ኢትዮጵያ አለመግባቱን ምክትል ጠቅላይ ሚንሰትሩ ገልፀዋል፡ምልክቱ ከታየም በአስቸኳይ ምላሽ ለመስጠት ሆስፒታልና 65 አልጋዎች መዘጋጀታቸውን የጤና ጥበቃ ሚንስትሩ ዶ/ር ከሰተ ብርሀን አድማሱ ተናግረዋል፡፡ (ኢብኮ)
0
886189c77a687ddbfc833555d267deb0
886189c77a687ddbfc833555d267deb0
በህንድ ምርጫ ናሬንዲራ ሞዲ አሸነፉ
በህንድ በተካሄደ ምርጫ ናሬንዲራ ሞዲ ህንድን ለቀጣይ አምስት ዓመታት ለመምራት ማሸነፋቸውን ማወቅ ተችሏል። በገዥው ባሂራቲያ ጄናታ ፓርቲ የሚመራው ብሔራዊ ዲሞክራሲያዊ ጥምረት 345 መቀመጫዎችን በማግኘትም እየመራ ነው። ፓርቲው አሊያም ጥምረቱ ሀገር ለመምራት በታችኛው ምክር ቤት ካሉት 543 መቀመጫዎች በትንሹ 272 መቀመጫዎችን መያዝ የሚጠበቅበት ሲሆን አብላጫውን አግኝቷል። ሞዲ በአውሮፓውያኑ 2014 አብዛኛውን ድምፅ ያገኙ ሲሆን አሁን ላያሸንፉ ይችላሉ የሚል ጥርጣሬ ነበር። ሞዲ ምንም እንኳን አገሪቷን በመሩበት ወቅት በተለያዩ ጉዳዮች ተቃውሞ ሲቀርብባቸው ቢቆዩም ድላቸውን እውን አድረገውታል። እንደ ቢቢሲ ዘገባ የተቃዋሚ ፓርቲ ቃል አቀባይ ጀቪር ሸርጊል ለቢቢሲ እንደተናገሩት "ውጤቱ በጣም አስደንጋጭ ነው" ብለዋል። በምርጫውን እንሸነፋለን ብለው እንዳልጠበቁ የተናገሩት ቃል አቀባዩ በምርጫ ቅስቃሳችን ጥሩ እንዳልነበሩ አምነዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀደም ብለው በትዊተር ገፃቸው ላይ "ሕንድ በድጋሚ አሸነፈች" ሲሉ ያስታወቁ ሲሆን ንግግር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
1
ef8504983035cb91618619edcbcdd81f
ba3c550657aafeff9c8f7440a087085b
በአዲስ አበባ ከተማ ለኢሬቻ በዓል የሚዘጉ መንገዶችን ፖሊስ ይፋ አደረገ
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 26፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)የሀላባ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ የሴራ በዓል በአዲስ አበባ ተከበረ፡፡በዚህ በዓል ላይ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው ፣ የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ እና የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ ኡማ ተገኝተዋል፡፡ኢንጅነር ታከለ ኡማ በበዓሉ ላይ ለታደሙ የሃላባ ብሔረሰብ ተወላጆች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡በአዲስ አበባ የሚኖሩ የሃላባ ብሔረሰብ ተወላጆች የከተማ አስተዳደሩ የሚሰራቸውን ስራዎች በቀጣይነት እንደሚደግፉ ተናግረዋል፡፡በበዓሉ ላይ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፣የብሔረሰቡ ተወላጆች እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታዳሚ ሆነዋል፡፡የሴራ በዓል በየዓመቱ በታህሳስ ወር ወይም በብሄረሰቡ አጠራር መንገሳ በሚባለው ወር የሚከበር በዓል መሆኑን ከከንቲባ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
0
62e2548a85dcd83c629e74a24079e1b6
15579aab1e984cadc9911f65315d7913
ህዝቡ ፅንፈኝነትን ሊከላከል እንደሚገባ ተጠቆመ
በምግብና መጠጥ የኢንዱስትሪ ዘርፍ እምቅ ሀብት ቢኖርም በሚፈለገው መጠን ውጤታማ እንዳልሆነ ተጠቆመ ፡፡የግብዓት እጥረት፣ የጥራት መጓደልና የአቅም ማነስና መሰል ተግዳሮቶች የዘርፉን ውጤታማነት እየተፈታተኑ እንደሚገኝ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ሚኒስቴሩ በምግብና መጠጥ ዘርፍ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት አፈፃፀምና በ2010 ዕቅድ ዙርያ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ባደረገው ውይይት በዘርፉ የተሠማሩ ባለሃብቶች የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ በሥራቸው ላይ እንቅፋት እንደሆነባቸው ገልፀዋል፡፡
0
e296311ba6ee22e80c9740487a47e2fe
f18a06bd120a9b1178494803cb967d31
ልዮ መርምሪ ሮበርት ሞለር የመጀመሪያ መግለጫ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በሮበርት ሙጋቤ ሞት የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀው፤ ለዚምባቡዌ ህዝብና መንግስት መፅናናትን ተመኝተዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ የቀድሞው የዚምባቡዌ ፕሬዚዳንት ሮበርት ጋብሬል ሙጋቤን የአፍሪካ የነፃነት መሪ ሲሉ ገልጸዋቸዋል፡የቀድሞ የዝምባቡዌ ፕሬዝዳንት ሮበርት ሙጋቤ በ95 ዓመታቸው በትናንትናው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ይታወሳል፡፡ህልፈታቸውን ተከትሎም የተለያዩ ሀገራት መሪዎች የተሰማቸውን ሀዘን በመግለፅ ላይ ናቸው፡፡ይህ በእንዲህ እንዳለ በዚምባቡዌ ለሶስት ቀናት የሚቆይ ብሄራዊ የሀዘን ቀን የታወጀ ሲሆን፤ የሀገሪቱ አንጋፋ ፓርቲ ዛኑ ፒኤፍም የጀግና ክብር ሰጥቷቸዋል፡፡
0
0aa6f4ddf2d7e9cd1c0638ae9573c8d3
7cea6a2c0212ae51c567b897b47d13f9
ጃክ መቶ ዓመቱን ደፈነ
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 30/2005 (ዋኢማ) – የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት በ6ኛ መደበኛ ጉባኤው ለ2006 በጀት ዓመት ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት እና የተለያዩ አዋጆችንና ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቀቀ፡፡ምክር ቤቱ የሶስት ቀናት ቆይታውን ሲያጠናቅቀ ለ2006 የበጀት ዓመት 1 ቢሊዮን 5 መቶ 76 ሚሊዮን 5 መቶ 18 ሺህ 2 መቶ 33 ብር ያጸደቀ ሲሆን ከፀደቀው ብር ውስጥም 3 መቶ 47 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር ለመደበኛ ፣ 2 መቶ 47 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ለካፒታል እንደዚሁም 6 መቶ 5 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር ደግሞ ለወረዳዎች እንዲሆን ወስኖል፡፡የተመደበው ብር ከባለፈው በጀት ዓመት ሲነጻጸር የ37 ሚሊዮን በ5 መቶ 18 ሺህ 2 መቶ 33 ብር ብልጫ አለው፡፡በጉባኤውም አቶ ፈቃዱ ታደሰን የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አድርጉ ሲሾም 8 የካቢኔ አባላትም ክልሉ የነደፈውን የልማት እቅድ ለማሳካት ይቻላቸው ዘንድ ቀደም ሲል ይሰሩበት ከነበረው የሀላፊነት ቦታ እንዲሸጋሸጉ በክልሉ ር/መስተዳድር የቀረበውን የሽግሽግ ጥቄንተቀብሎአጽድቋል፡፡እንደዚሁም የክልሉ ገቢዎች ባለስልጣን የካቢኔ አባል እንዲሆን የቀረበውን ሀሳብ ምክር ቤቱ የተቀበለው ሲሆን የምክትል ኦዲት ቢሮ ሀላፊ፣ የመገናኛ ብዙሀን ኤጀንሲ ዋና ስራ አስኪያጅ ሹመትን ደግሞ ተወያይቶ አፅድቋል፡፡ምክር ቤቱ 17 ነጥብ ያካተተ የውሳኔ ሀሳብ ላይ ውይይት አድርጎ በጋራ ለመስራት በመወሰን ጉባሄውን አጠናቋል ሲል የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮን ጠቅሶ ኢሬቴድ ዘግቧል፡፡
0
61789527d58ead0653aaad6a35ac8f49
16932d70701a5cb20c2844cdb5c6fa55
የእንቦጭ አረም በኑሮዋቸው ችግር እየፈጠረባቸው መሆኑን አርሶ አደሮች ገለፁ
አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 22 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) አርሶ አደሮችን በገበያ ተኮር የግብርና ልማት በማሰማራት ኑሯቸውን የተሻለ ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ተመስገን ጥሩነህ አስታወቁ።ርዕሰ መስተዳድሩና የክልሉ ምክር ቤት አፈጉባኤ ወይዘሮ ወርቅሰሙ ማሞ በደቡብ ጎንደር ዞን ደራ ወረዳ መንደርን የመቀየር ፕሮጀክት ጎብኝተዋል::ርዕሰ መስተዳድሩ በትንሽ መሬት ብዙ መጠቀም እንደሚቻልም አይተናል ፤ የአትክልትና ፍራፍሬ፣ የዶሮ፣ ከብት ማድለብ እና ባዮ ኬሚካል በተቀናጀ መልኩ እየተሰራ ነው ብለዋል::የአካባቢው አርሶ አደሮች በአነስተኛ ማሳ ቲማቲም እያለሙ መሆኑም ተጠቁሟል።ከዚህ በፊት ማሳቸውን በጫት ተክል ይሸፍኑት እንደነበር የተናገሩት አርሶ አደሮቹ ከሁለት ዓመታት ወዲህ በፕሮጀክቱ በመደገፍ ከአንድ ዙር በ136 ካሬ ሜትር ቲማቲም ከ30 ሺህ ብር በላይ እያገኙ መሆኑን መናገራቸውን ከደቡብ ጎንደር ዞን ኮሙዩኒኬሽን ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል ።ቤተሰብ ፣ መንደር ፣ ቀብሌ ፣ ወረዳ ሲቀየሩ ሀገር ይቀየራል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ደራ ወረዳ ባየነው ነገር ተደስተናልም ነው ያሉት::
0
9d5bb6693dfded6583cd6ff919118214
93ba40fe823e0c75d40387fba6970e96
በፕሪምየር ሊጉ ወልቂጤ ፣ ጅማ አባ ጅፋርና ሲዳማ ቡና ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 11፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 4ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በዛሬው በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች እለት ተካሂደዋል።በዚሁ መሰረት ውጤቶቹም፦ባህር ዳር ከተማ 4-1 ድሬ ደዋ ከተማሲዳማ ቡና 1-2 መቐለ 70 እንድርታወልዋሎ አዲግራት ዩንቨርሲቲ 0-0 ጅማ አባ ጅፋርፋሲል ከነማ 3-0 ሀድያ ሆሳህናቅዱስ ጊዮርጊስ 0-0 ስሁል ሽረአዳማ ከተማ 2-2 ወላይታ ዲቻወልቂጤ ከነማ 0-1 ሰበታ ከተማ በሆነ ውጤት ተጠናቀዋል።
0
b6a4d4fac5f0b35cfdd5c9eb31f6d52f
b6a4d4fac5f0b35cfdd5c9eb31f6d52f
በእነ አቶ ጌታቸው አሰፋ የክስ መዝገብ በ26 ተከሳሾች ላይ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ምስክር ማሰማት ጀመረ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በእነ አቶ ጌታቸው አሰፋ የክስ መዝገብ በተከሰሱ በ26 የቀድሞ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ሰራተኞች ላይ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የዐቃቤ ህግ ምስክር ማሰማት ጀመረ።በእነ አቶ ጌታቸው አሰፋ የክስ መዝገብ በ26 የቀድሞ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ሰራተኞች በተከሰሱበት በአዋጅ ከተሰጣቸው ስልጣን ውጪ ሰዎችን በመያዝና በማሰር ስልጣንን ያለ አግባብ መገልግል ወንጀል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ከመጋረጃ ጀርባ ማንነታቸው የማይገለፅ ምስክሮችን ዛሬ ማሰማት ጀምሯል።በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡት አጠቃላይ 22 ተከሳሾች ሲሆኑ፥ አቶ ጌታቸው አሰፋ፣ አቶ አፅበሃ ግደይ፣ አቶ አሰፋ በላይ እና ሺሻይ ልኡል በሌሉበት ነው ጉዳያቸው የታየው።ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ በምስክር ጥበቃ አዋጅ 699/ 2003 መሰረት ጥበቃ የሚያስፈልጋቸው እና ማንነታቸው የማይገለፅ 29 ምስክሮችን ያዘጋጀ ሲሆን፥ በዛሬው እለት ሶስቱን አቅርቧል።በዚህም አንድ ምስክር መሰማት ተጀምሮ ያልተጠናቀቀ ሲሆን፥ በሚታየው የቪዲዮ ማስረጃ ጥራት ጉድለት ምክንያት ቀሪ ምስክሮቸን ከመጋረጃ ጀርባ ለመስማት ፍርድ ቤቱ ለመስከረም 12 ቀን 2013 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።በታሪክ አዱኛ
1
8fa74653956148282bcb8e8c48cc83c9
0b6e22fb5fd8e3f65945e403109a29da
ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ከእነ ትጥቃቸው በመግባታቸው የተፈረደባቸው የመከላከያ ሠራዊት አባላት በይግባኝ ፍርዳቸው ተቀነሰላቸው
ባሕር ዳር፡ ግንቦት 30/2012 ዓ.ም (አብመድ) የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 5ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 5ኛ ልዩ ስብሰባውን ነገ ሊያካሂድ ነው፡፡በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ የሚደረገው የዕለቱ ልዩ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶክተር) በተገኙበት ነው የሚካሄደው፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር አባላት ለሚነሱላቸው የተለያዩ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እንደሚሰጡ እንደሚጠበቅ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማኅበራዊ ገጹ አስታውቋል፡፡
0
1fc08f6b0e812667b8edc1926e3ab963
1fc08f6b0e812667b8edc1926e3ab963
በአማራ ክልል ሁሉንም መሠረተ ልማቶች ያሟላ የአርሶ አደሮች መንደር ሊገነባ ነው፡፡
አርሶ አደሮችን በአንድ ላይ በማሰባሰብ የልማት ተጠቃሚ የሚያደርግ አሠራር መጀመሩን አልማ አስታወቀ፡፡የአማራ ልማት ማኅበር (አልማ) የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ሞገስ እንደገለጹት በጎንደር ዙሪያ ወረዳ ደረስጌ ማሪያም ቀበሌ ለዚሁ ተግባር 130 ዘመናዊ መኖሪያ ቤቶችን ለመገንባት ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ መረጃ ዘመናዊ መንደሩ የንጹህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት፣ በጸሃይ ብርሃን እና በነፋስ 24 ሰዓት የሚሰራ የኃይል አቅርቦት፣ ትምህርት ቤት፣ የሰው እና የእንስሳት የህክምና መስጫ ተቋማት፣ መንገድ፣ የአርሶ አደሮች ማሰልጠ እና የኢንተርኔት አገልግሎትን ጨምሮ ሌሎች መሠረተ ልማቶች የሚሟሉለት ነው፡፡ ሥራው አሜሪካ ለአፍሪካ የምታደርገውን የገንዘብ ድጋፍ በልማት ለመቀየር ታስቦ ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል እንደሆነም ነው ያስረዱት፡፡
1
5f76b3da913cbd673e987a414372dea2
e4f79aa6f32df71c0fb20eebca874cb7
በማንነት ጥያቄያችን ብቻ ከእስርና መንገላታት ነጻ መውጣታችን አስደስቶናል- በከሃዲው ህወሓት ታስረው የነበሩ
አዲስ አበባ ፣ የካቲት 18፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ሰለባ የሆኑ 104 ኢትዮጵውያን በዛሬው ዕለት ከታንዛኒያ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።ተመላሾቹ ኢሪንጋ በሚባለው ግዛት በሚገኝ እስር ቤት ውስጥ የቆዩ መሆናቸውን በታንዛኒያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል።በቅርቡ ሞሮጎሮ፣ ሩቩማ፣ ንጆም፣ ቤምቤያ እና ሶንግዌ በሚባሉ የታንዛኒያ ግዛቶች ታስረው የነበሩ 294 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው መመለሳቸው ይታወሳል።
0
01329852887896c6c3c255dc6a0cec99
01329852887896c6c3c255dc6a0cec99
ጋምቤላ ውስጥ የክልሉ ተወላጅ አሜሪካዊ ጨምሮ አራት የአኙዋክ ብሄረሰብ አባላት ታሰሩ
ጋምቤላ ውስጥ አንድ የክልሉ ተወላጅ አሜሪካዊ ጨምሮ ቢያንስ አራት የአኙዋክ ብሄረሰብ አባላት መታሰራቸው ተሰምቷል። ከኑዌር ብሄረሰብ በኩልም ፕሬዚዳንቱን የማይደግፉ የታሰሩ እንዳሉ ነው ምንጮች የሚናገሩት። ትውልደ ኢትዮጵያ አሜሪካዊው ዶ/ር ማኝ ኚያንግ ሚኔሶታ ክፍለ ሀገር የሚኖሩ የስነ ልቦና ሀኪም እንደሆኑ ተገልጿል።
1
0de352bef2e8c6a96730a364ed224f15
bf4c7689df4ef2318e129fa07dd7a7d4
ዶናልድ ትራምፕ ወደ ዋይት ሐውስ ተመልሰዋል
አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 29፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢራን በኢራቅ በሚገኝ የአሜሪካ ዓየር ሀይል የጦር ሰፈር ላይ የባለስቲክ ሚሳኤል ጥቃት ፈፀመች።የአሜሪካ የመከላከያ መስሪያ ቤት ፔንታጎን ሁለት የጦር ሰፈሮች ጥቃት እንደተፈፀመባቸው አስታውቋል።የኢራን የመንግስት ቴሌቪዥን ጣቢያ የባለስቲክ ሚሳኤል ጥቃቱ የተፈፀመው ባለፈው ሳምንት የሀገሪቱ ግንባር ቀደም ወታደራዊ መሪ የሆኑት ቃሲም ሶሊማኒ በአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትእዛዝ ለመገደላቸው የተሰጠ አፀፋ መሆኑን ዘግቧል።በአካባቢው የሚገኙ የትኛውም የአሜሪካ ወዳጅ የሆነ እና የዋሽንግተንን ወታደሮች እያስተናገደ የሚገኝ ሀገር ሁሉ ኢላማ መሆኑንም ቴሂራን አስጠንቅቃለች።በጥቃቱ ምን ዓይነት ጉዳት እንደደረሰ እስካሁን ግልፅ የተደረገ ነገር የለም።ዋይት ሀውስ በጉዳዩ ላይ ባወጣው መግለጫ ፕሬዚዳንት ትራምፕ በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ የተሰጣቸው ሲሆን፥ በሁኔታው ላይ ከብሄራዊ የደህንነት ቡድናቸው ጋር እየመከሩ መሆኑን ነው ያስታወቀው። ምንጭ፦ ቢቢሲ
0
56e5f8af6f2a2aa70380514162a23965
56e5f8af6f2a2aa70380514162a23965
“ባለፉት ሃያ ሰባት ዓመታት ፌዴራሊዝም በተግባር አልነበረም” – አቶ ታዬ ደንደአ የኦዴፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል
አዲስ አበባ፡- ባለፉት ሃያ ሰባት ዓመታት በኢትዮጵያ የፌዴራሊዝም ሥርዓት በተግባር አልነበረም ሲሉ የኦዴፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ ታዬ ደንደአ በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ከምትታተመው ዘመን መጽሄት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ገለጹ። አቶ ታዬ “ባለፉት 27 ዓመታት በአማራና ኦሮሚያ ክልልም ሆነ በአጋር ድርጅቶች ዘንድ የድርጅት ሊቀመንበር ማን ይሁን የሚለውን የሚወስነው ማን እንደነበር ይታወቃል። ይሁንና ‹በፊት ፌዴራሊዝም ነበር አሁን ሊፈርስ ነው፤ የብሔረሰቦች መብት ይከበር ነበር አሁን ወደ ኋላ ሊመለስ ነው› የሚል ቅስቀሳና ድራማ እየተሠራ ነውም” ብለዋል። “በተጨባጭ ፌዴራሊዝም አልነበረም ሕገ መንግሥቱም በተግባር ሲከበር አልታየም። የብሄር ብሔረሰቦች መብትም ምናባዊ እንጂ ተጨባጭ አልነበረም። በሕገ መንግሥቱ እጅግ ወሳኝ ሰብአዊ መብቶች ተቀምጠውበታል ነገር ግን ሰዎች ሲኮላሹና ያለጥፋታቸው በሐሳብ ምክንያት ብቻ ይታሰሩ ነበር። እኔ ለዚያ ምስክር ነኝ” ሲሉም አክለዋል። አፈና ላይ ነበረን። አሁን የለውጡ መንግሥት የታፈነውን ሲከፍተው ፈነዳ፤ ፈንድቶ ግን አላመለጠም። መንግሥት እያስታመመና እያስታገሰ እዚህ ድረስ መጥቷል። ይሄንን ግልጽ ማድረግ ያስፈልጋል ሲሉም ተናግረዋል። የአቶ ታዬ ደንደአን ሙሉ ቃለ ምልልስ በዘመን መጽሄት የጥቅምት 2012 ዓ/ም ዕትም ላይ ያገኙታል።አዲስ ዘመን ህዳር 5/2012በጋዜጣው ሪፖርተር
1
47b01b83a6a7d51129561a759c253541
61d49de9b8468b157c937ab434c46536
የኢትዮጵያ፣ የሱዳንና ግብጽ የሶስትዮሽ የጋራ ስብሰባ በአዲስ አበባ ተጀምሯል
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 15 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋቂ ማሃማት ኢትይጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ በቴክኒክ ደረጃ የሚያደርጉትን ድርድር ለመቀጠል መስማማታቸውን አወደሱ።ሊቀ መንበሩ ሃገራቱ በህዳሴው ግድ ዙሪያ ከሰሞኑ ያሳዩትን አቋም አድንቀው፥ የሶስትዮሽ ድርድሩን ለመቀጠል መስማማታቸውን እንደሚያበረታቱም ገልጸዋል።ድርድሩም በትብብር መርህ፣ በመግባባትና በግልጽነት ሃገራቱ በፈረንጆቹ 2015 ለፈረሙት የትብብር መርህ ማዕቀፍ ተፈጻሚነት ይረዳልም ነው ያሉት።ኮሚሽኑም ሶስቱ ሃገራት በህዳሴው ግድብ ዙሪያ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋገጥ ስምምነት ለመድረስ የሚያደርጉትን ጥረት ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑንም ገልጸዋል።
0
6cd93ad5665fc731ee104d764e4ac60c
6cd93ad5665fc731ee104d764e4ac60c
በአፍጋኒስታን ካቡል በአጥፍቶ ጠፊ ቦምብ አምስት ሰዎች ተገደሉ
ዛሬ በአፍጋኒስታን ዋና ከተማ በካቡል አንድ አጥፍቶ ጠፊ ቦምብ ታጣቂ ጥቃት አድርሶ በትንሹ አምስት ሰዎችን ሲገድል ሌሎች ዘጠኝ አቁስሏል።በከተማዋ ከሚገኝ አንድ ባንክ ውጪ ጥቃቱ የደረሰው የአፍጋኒስታን ጦር ሠራዊት አባላትና የሌሎች የደኅንነት ተቋማት ሠራትኞች ወርሃዊ ደሞዛቸውን ለመቀበል ተራ ይዘው እየጠበቁ ባለበት ወቅት መሆኑን የዓይን ምስክሮች ተናግረዋል።ታሊባን ለጥቃቱ ኃላፊነት ወስዷል።ይህ የዛሬው ከባድ ጥቃት የተፈጸመው አፍጋኒስታን የኢድ-አልፈጢርን በዓል ለማክበር እየተዘጋጀች ባለችበት ወቅት መሆኑም ታውቋል፡፡ይህ በእንዲህ እንዳለ የዩናይትድ ስቴትስ ድሮኖች ሌሊቱን ባደረሱት ጥቃት ሕጻናትና ሴቶችን ጨምሮ 13 ሲቪሎችን መግደላቸውንና ሌሎች ሠባት ማቁሰላቸውን የሂራት ክልላዊ መንግሥት ቃል አቀባይ ጄላኒ ፋርሃድ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።
1
0e3a81d39e16c9503a9ecedf2546985b
0e3a81d39e16c9503a9ecedf2546985b
ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ ኢትዮጵያ ለሊቢያ ሰላም ድጋፍ እንደምታደርግ ገለፁ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 7፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከሊቢያ ከፍተኛ ምክር ቤት ሊቀ-መንበር ካሊድ አል-ሚሽሪ እና ከልዑካን ቡድናቸው ጋር ተወያይተዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ በውይይቱ ወቅት ኢትዮጵያ ለሊቢያ በዓለም አቀፍ እንዲሁም ክልላዊ ተቋማት አማካኝነት ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን አስታውቀዋል።ሊቢያውያን በሀገራቸው ሰላም እንዲሰፍን ለማድረግ እንዲበረቱና በአንድነት ጥረት እንዲያደርጉም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።ሊቀ-መንበሩ ካሊድ አል-ሚሽሪ በበኩላቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኖቤል ሰላም ሽልማትን በማግኘታቸው ደስታቸውን በመግለፅ በአመራራቸው ያስገኟቸውን ለውጦች አስመልክቶ አድናቆታቸውን ገልጸዋል።እንዲሁም በሊቢያ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ለሚደረገው ቀጣይ ጥረት እገዛ እንዲያደርጉ መጠየቃቸውን ከጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡።
1
91a509a8e3b706898365d16d0e1a63cb
4862ca20a9ebc3f4e49e6dc773dc189c
ጠ/ር አብይ አሕመድ እና ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የክብር ሽልማት ተሰጣቸው
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በሱዳን ይፋዊ የስራ ጉብኝት በማድረግ ላይ መሆናቸው ተነገረ።ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጉብኝቱን የሚያደርጉት በሱዳን የሽግግር መንግስት ሉአላዊ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሌተናል ጄኔራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን በቀረበላቸው ግብዣ ነው።በፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የተመራው የኤርትራ መንግስት ልኡካን ካርቱም ሲገቡም ሉአላዊ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሌተናል ጄኔራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን አቀባበል አድርገውላቸዋል።ፕሬዚዳንት ኢሳያስ በካርቱም ቆይታቸውም የሶስት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት የሚያደርጉ መሆኑን የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረመስቀል በትዊተር ገፃቸው አስታውቀዋል።ፕሬዚዳንቱ በሱዳን ቆይታቸውም የኤርትራን እና የሱዳንን የሁለትዮሽ ትብብሮችን ማጠናከር በሚቻልባቸው ላይ የሚመክሩ ሲሆን፥ በቀጠናዊ ትብብር እና ውህደት ዙሪያ ውይይቶችን እንደሚያደርጉም አስታውቀዋል።#FBCየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
0
edd208ecf5ad38c5d888036a10b4eb64
16c30f4f6fba9827d2a0cd8d18acb982
የጦር መሣሪያዎችን በድብቅ ይዘው ሲያጓጉዙ የተደረሰባቸው ተጠርጣሪዎች መታሰራቸው ተጠቆመ
በዛምቢያ በማዕድን ፍለጋ ዘርፍ የተሰማሩ 31 ዜጎቿ ያላግባብ መታሰራቸው ቀር እንዳሰኛት ቻይና ገለጸች ።ዛምቢያ በበኩሏ ቻይናውያኑ ህግን በመተላለፋቸው ምክንያት ነው ለእሥር መዳረጋቸውን ተናግራለች ፡፡ ቻይናውያን መታሠራቸው የሁለቱን አገራት ግንኙነት እንዳያሻክር ተሰግቷል፡፡ዛምቢያ በማዕድን ፍለጋ ላይ የተሳተፉ ዜጎቿ በዛምቢያ ባለስልጣናት ለእስር መዳረጋቸውን በመጠቆም ቻይና ለዛምቢያ ወቀሳ አቅርባለች፡፡በዛምቢያ በማዕድን ፍለጋ ዘርፍ የተሰማሩ 31 ዜጎቿ ያለአግባብ መታሰራቸው ቻይናን ቅር አሰኝቷል፡፡የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ከፍተኛ ባለሥልጣን ዛምቢያ ቻይናውያኑን ለማሠር ምንም ምክንያትና ማስረጃ የላቸውም በማለት ድርጊቱን አውግዘዋል፡፡ቻይናውያኑ በአናሳ ዕድሜ ላይ የሚገኙ ልጆችን ቀጥረዋል እንዲሁም ያለተፈቀደ የሚሸት ዕፅዋትን ይዘው ተገኝተዋል በሚል መከሰሳቸውን ቢቢሲ በዘገባው አመልክቷል፡፡ቻይና በዛምቢያ በተለይም በመዳብ ማዕድን ዘርፍ በከፍተኛ ደረጃ ኢንቨስት እንደምታደርግ መረጃው ይጠቁማል፡፡ቻይናውያኑ ከዛምቢያ መዲና ሉሳካ በስተሰሜን 420 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ቺንጎላ ከተማ ነው በቁጥጥር ሥር ውለው የታሰሩት፡፡የዛምቢያ የአገር ውስጥ ሚኒስትር ስቴፈን ካፕዮንጎ ‹‹ወደ ዛምቢያ የሚመጡ የውጭ ዜጎች የአገሪቱን ህግ አክብረው ሊሰሩ ይገባል፡፡ ህግን ሲተላለፉ ዝም ብለን አናያቸውም፡፡ ህግ የሚጥሱ አካላት ተጠያቂ ይሆናሉ›› በማለት ቻይናውያኑ የታሰሩት ህግን ተላልፈው በመገኘታቸው እንደሆነ ገልፀዋል፡፡በቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር ሊን ሶን ጊታን ህገ ወጥንትን መከላከል ተገቢነቱ እንደማያጠያይቅ ገልፀው ዜጎቻቸው የታሰሩበት ምክንያት ግን በማስረጃ የተደገፈ አይደለም ብለዋል፡፡ክሱን በተመለከተ ማንም ዓይነት ማስረጃ አለመቅረቡን ቻይና ማስታወቋን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ለእስር ከተዳረጉት ውስጥ ነፍሰ ጡርና በወባ በሽታ እየታመሙ ያሉ ሰዎች እንደሚገኙባቸው ተመልክቷል፡፡ እኤአ በ2010 ሁለት የቻይና የማዕድን ኩባንያ ሥራ አስኪያጅ ሠራተኞች ላይ በተተኮሰ ጥይት የግድያ ሙከራ ተደርጎ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት በዛምቢያ የከሰል ማዕድን ዘርፍ አካባቢ በተነሳ ተቃውሞ አንድ የቻይና ኩባንያ ሥራ አስኪያጅ በዛምቢያ የማዕድን ሠራተኞች መገደላቸው በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን መዘገቡ የሚታወስ ነው ፡፡
0
e2443fc6130bc810df8e42fc85010879
3967758a4649b241b61035d92daf0b9c
በደሴ ከተማ የተነሳ ድንገተኛ የእሳት አደጋ ከ86 በላይ የቤተሰብ አስተዳዳሪዎችን ለጉዳት ዳረገ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ ባለፈው ቅዳሜ በደረሱ ሁለት የእሳት አደጋዎች የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ ንብረት ወደመ።የከተማው እሳትና ድንገተኛ አደጋ መከላከልና መቆጣጠር ባለስልጣን አደጋውን ለመቆጣጠር ባከናወነው ተግባር 25 ሚሊዮን ብር የሚገመት ኃብት ማዳን ችሏል።አደጋዎቹ የደረሱት በቦሌና በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተሞች መሆኑን የባለስልጣኑ ህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ስለሺ ተስፋዬ ለኢዜአ ተናግረዋል።በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተክርስቲያን አጠገብ የሚገኝ መኖሪያ ቤት ላይ በደረሰው አደጋ የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ ሁለት ሰዎች ደግሞ ከባድ የአካል ጉዳት ገጥሟቸዋል።በዚሁ አደጋ 300 ሺህ ብር የሚገመት ንብረት የወደመ ሲሆን 10 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ንብረትን ግን ማዳን ተችሏል ብለዋል።የቤተክርስቲያኑ የምዕመናን መቀመጫዎች በአደጋው መቃጠላቸውም ነው የተናገሩት።አደጋውን ለመቆጣጠር 51 ሺህ ሊትር ውሃ፣ 10 ከባድና ቀላል የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪዎች እንዲሁም 50 የአደጋ መቆጣጠር ሰራተኞች ተሳትፈዋል፤ በ45 ደቂቃ ውስጥም እሳቱን ማጥፋት ተችሏል ሲሉም ገልፀዋል።በቦሌ ክፍለከተማ ወረዳ 4 ልዩ ቦታው በፀጋ ሆስፒታል አካባቢ የተነሳው ሁለተኛው የእሳት አደጋ በ29 ቤቶች ላይ ጉዳት አድርሷል፤ 5 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረትም አውድሟል።ከዚህም ሌላ በአደጋው 63 ሺህ 500 ብር በጥሬ ገንዘብ የወደመ ሲሆን 33 ሺህ ብር በጥሬ ገንዘብ ለማዳን እንደተቻለም አብራርተዋል።እሳቱን ለማጥፋት በተደረገው ርብርብ በአጠቃላይ 15 ሚሊዮን ብር የሚገመት ኃብት ማዳን መቻሉንም ነው የህዝብ ግንኙነት ባለሙያው የተናገሩት።በዚህ አካባቢ የተነሳውን እሳት ለማጥፋት 76 ሺህ ሊትር ውሃ፣ ስምንት ከባድና ቀላል የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪዎችና 53 የአደጋ መቆጣጠር ሰራተኞች ተሰማርተዋል። አደጋውን መቆጣጠር የተቻለው በአራት ሰዓት ውስጥ ነው ተብሏል። (ኢዜአ)
0
5500fa651d7928d317d9ebad05a5868d
21afd769c0150bafb5b2bcf759460554
በዩናትድ ስቴትስ ለፕሬዝዳንትነት ውድድር በሚደረገው ቅድመ ምርጫ፣ ትራምፕ እና ሂላሪ አሸነፉ
የዩናይትድ ስቴትሱ ተመራጭ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንደ ሌሎቹ ምርጫዎቻቸ ሁሉ፣ እኒህኛውም አወዛጋቢ ናቸው ተባለ።የባንክራፕሲ/የንግድ ክስረት/ ተከራካሪ ጠበቃ የሆትን ዴቪድ ፍሬድማንን ነው፣ ዶናልድ ትራምፕ ለእሥራኤል አምባሳደርነት ያጩት።ፍሬድማን ከምርጫው በኋላ ባደረጉት ንግግር እሥራኤል ዋና ከተማ ኢየሩሳሌም ውስጥ ባለው የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ሥራቸውን ለመቀጠል ፈቃደኛ እንደሆኑ ገልፀዋል።ዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ የሚገኘው ቴልአቪቭ ነው። ፍልስጥኤማውያንም ሆኑ እስሥራኤላውያን ግን፣ ዋና ከተማችን ኢሩሳሌም ነው እንደሚሉና ይህም፣ የሰላም ድርድሩ አካል ሆኖ መቆየቱ ይታወቃል።በዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ወቅት የዶናልድ ትራምፕ አማካሪ የነበሩት ፍሬድማን የዩናይትድ ስቴትስን ኤምበሲ ከቴልአቪቭ ወደ ኢየሩሳሌም አዛውራለሁ ሲሉ ይህ ደግሞ፣ በተለይም ከአረቡ ዓለም፣ ቀላል ያልሆነ ዓለማቀፍ ተቃውሞ እንደሚገጥመው ይታመናል።
0
f28ec75e39cbcfc35a1a68947b0ba83b
2ae61836945ce15609ca3081fabc683d
የጣልያናዊው እግርኳስ ተጫዋች ፓውሎ ሮሲ ህይወት አለፈ
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን አምስት የብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው ገልጾ ሚዲያዎች በቫይረሱ የተያዙትን ተጫዋቾች ማንነት ባለመግለፅ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቋል።የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ይፋ ያደረገው መረጃ ይህንን ይመስላል:-– ትናንት ማምሻውን የኮቪድ 19 ምርመራ ካደረጉ 36 የቡድኑ አባላት መካከል 5ቱ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሲሆን፤ 5ቱም ራሳቸውን አግልለው ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል።– የተቀሩት 31 የቡድኑ አባላት ማምሻውን የካፍ አካዳሚ ገብተዋል። በነገው እለትም የመጀመሪያ ልምምዳቸውን ከረፋዱ 3ሰዓት የሚጀምሩ ይሆናል።– ከ72 ሰዓታት በኋላ ኮቪድ Negative የሆኑት ተጫዋቾች እና የቡድኑ አባላት በሙሉ ምርመራ የሚደረግላቸው ይሆናል።– ቡድኑን ዘግይተው የተቀላቀሉት ተከላካዩ አንተነህ ተስፋዬ እና ሱራፌል ዳኛቸው እንዲሁም የቡድኑ ወጌሻ በነገው እለት የኮቪድ ምርመራ የሚደረግላቸው ይሆናል።ማሳሰቢያበተለያዩ አማራጮች የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ተጫዋቾችን ዝርዝር የማግኘት እድሉ ያላችሁ የሚዲያ አካላትም ሆነ ግለሰቦች ለእያንዳንዱ ተጫዋች የግል ህይወት ነጻነት ሲባል እና በስነ ልቦናም እንዳይጎዱ የተጫዋቾቹን ስም ይፋ ባለ ማድረግ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ ስንል በጥብቅ እናሳስባለን።
0
78fe8d2dfa08acf62de68c3f4b3fbdbb
78fe8d2dfa08acf62de68c3f4b3fbdbb
አሜሪካዊ ደራሲ ፕሊፕ ሮት በሰማኒያ አምስት ዓመቱ አረፈ
የበርካታ ሽልማቶች ባለቤቱ ዕውቁ አሜሪካዊ ደራሲ ፕሊፕ ሮት በሰማኒያ አምስት ዓመቱ አረፈ።ሮት ከሃምሳ ዓመታት በላይ በዘለቀው የድርሰት ሕይወቱ የይሁዲ አሜሪካውያንን ተመክሮ የሚፈትሹ በርካታ ሥራዎቹን ጨምሮ ከሠላሳ በላይ መጽሐፍት ደርሷል።እአአ በ1959 የታተመው የአጫጭር ልቦለድ ድርሰቶች ስብስብ የተካተተበት የመጀመሪያው መጽሐፉ ‘Goodbye Columbus’ ለብሔራዊ ሽልማት በቅቷል።ከፍተኛ ተወዳጅት ያተረፈለት ልቦለድ ሥራው ታዲያ ከዚያ አሥር ዓመታት በኋላ የታተመው፤ መካከለኛ ገቢ ካላቸው ቤተሰቦች የሚወለድ አንድ የኒው ዮርክ ከተማ ነዋሪ ወጣት ታሪክ፣ የቁጥጥር አጠባቂ እናቱን እና ጾታ ነክ በሆኑ ጉዳዮች የሚዋጥበትን ጠባዩን የሚተርከው ‘Portnoy’s Complaint’ (በግርድፉ ወደ አማርኛ ሲመለስ የ ‘Portnoy’ ቅሬታዎች) የሚለው መጽሐፉ ነው።‘American Pastoral’ በሚል ርዕስ የደረሰው ሌላው ተወዳጅ ልቦለድ ድርሰቱ እአአ በ1998 ለ‘Pultizer’ ሽልማት በቅቷል። ሌሎች ታላላቅ ሽልማቶቹ ‘Man Booker’ የተሰኘው ዓለም አቀፍ ሽልማት፣ የ’Pen/ Faulkner’ ሽልማት እና ብሔራዊ የኪነጥበብ ሥራዎች ሽልማት (National Medal of Arts) ይገኙበታል።ሮት ባደረበት የልብ ሕመም ሲረዳ ከቆየ በኋላ በሚኖርባት የኒው ዮርክ ከተማ በትላንትናው ዕለት ማረፉን ጉዳይ አስፈፃሚው ይፋ አድርገዋል።
1
aff1169125024b83ccca7e6a0eed448f
cdde840473343b5e3390fc182a88957b
በከባድ የሙስና ወንጀል በተጠረጠሩት ላይ ፖሊስ የጠየቀው የምርመራ ጊዜ ተፈቀደ
የባህር ዳርና አካባቢው የጊዜ ቀጠሮ ፍርድ ቤት የምርመራ መዝገቡን ዘግቶታልየአማራ ክልል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ከጥረት ኮርፖሬት ኩባያዎች ጋር በተገናኘ በከባድ የሙስና ወንጀል ጠርጥሬያቸዋለሁ በማለት በቁጥጥር ሥር ያዋላቸውና በእስር ላይ ያሉት አቶ በረከት ስምዖንና አቶ ታደሰ ካሳ፣ የዋስትና ጥያቄ ማቅረብ እንደሚችሉ ጉዳዩን እየመረመረው ያለው የባህር ዳርና አካባቢው ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዓርብ መጋቢት 20 ቀን 2011 ዓ.ም. አስታወቀ፡፡ የባህር ዳርና አካባቢ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ችሎት ተጠርጣሪዎቹ የዋስትና መብት ጥያቄ ማቅረብ እንደሚችሉ ያስታወቀው፣ የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ከመርማሪ ቡድኑ የተረከበውን የምርመራ መዝገብ መዝጋቱን ከገለጸ በኋላ ነው፡፡የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ የምርመራ መዝገቡን ከመርማሪ ቡድኑ መረከቡን ገልጾ፣ ለክስ መመሥረቻ የ15 ቀናት ጊዜ እንዲፈቀድለት አቅርቧል፡፡ ተጨማሪ ቀናት የጠየቀውም ዓቃቤ ሕግ ከ600 ገጽ በላይ የሰነድ ማስረጃዎችንና ከ35 ገጽ በላይ የሙያ ማብራሪያ ማሰባሰቡን በመጠቆም፣ አደራጅቶ ክስ ለመመሥረት በቂ ጊዜ ስለሚያስፈልገው መሆኑን አስረድቷል፡፡አቶ በረከትና አቶ ታደሰ ለፍርድ ቤቱ ባቀረቡት የተቃውሞ አቤቱታ እንደተናገሩት፣ እነሱ በእስር ከቆዩበት ጊዜ አንፃር የዓቃቤ ሕግ ጥያቄ ተገቢ አይደለም፡፡ በቤተሰቦቻቸውና በእነሱም ላይ ዛቻና ማስፈራሪያ እየደረሰባቸው መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ ካለባቸው የደኅንነት ሥጋት አኳያ ጉዳያቸው ከባህር ዳር ውጪ ባለ ፍርድ ቤት እንዲታይላቸውም ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡ እንግልት እንደየደረሰባቸውና እነሱም ያሳወቁ ቢሆንም፣ የክልሉ መንግሥት ምላሽ አለመስጠቱ እንዳሳዘናቸውም አክለዋል፡፡የግራ ቀኙን ክርክር የሰማው ፍርድ ቤት ከተነጋገረ በኋላ ዓቃቤ ሕግ ከወሰደው ጊዜ አንፃር ክስ መሥርቶ መቅረብ ይችል እንደነበር ጠቁሞ፣ ክሱን በፈለገ ጊዜ ማቅረብ እንደሚችል በመንገር መዝገቡን መዝጋቱን ነግሮታል፡፡ ተጠርጣሪዎቹም የዋስትና መብት ጥያቄ ማቅረብ እንደሚችሉ በመንገር የዕለቱ ችሎት አብቅቷል፡፡
0
5841354064a411e40916c8e19115bbfc
178cbd69b21e28c1e970d607efe7d376
ባለፉት 24 ሰዓታት 712 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው የ7 ሰዎች ህይወት አልፏል
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 8 ሺህ 201 የላብራቶሪ ምርመራ 588 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 19 ሺህ 877 መድረሱንም የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ባወጡት መረጃ አመላክተዋል።ከዚህ ባለፈ የ7 ሰዎች ህይወት በቫይረሱ ምክንያት ያለፈ ሲሆን፥ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር 343 መድረሱንም አመላክተዋል።በሌላ መልኩ በትናንትናው እለት 309 ሰዎች ከኮሮና ቫይረስ ያገገሙ ሲሆን፥ በአጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 8 ሺህ 240 መድረሱም ተገልጿል።ከቫይረሱ ጋር በተያያዘ እስካሁን 452 ሺህ 427 ሰዎች ምርመራ የተደረገ ሲሆን፥ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 19 ሺህ 877 ደርሷል።አሁን ላይ ቫይረሱ ያለባቸው ሰዎች ቁጥር 11 ሺህ 292 ሲሆን፥ ከእነዚህም ውስጥ 187 ሰዎች በጽኑ የታመሙ መሆናቸውንም የጤና ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።እስካሁን በኢትዮጵያ 8 ሺህ 240 ሰዎች ከቫይረሱ ሲያገገሙ፤ የ343 ሰዎች ህይወት አልፏል፤ 2 ሰዎች ወደ ሀገራቸው መመለሳቸው ይታወሳል።#FBCየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
0
27c792ad2cb91b09191a73ea3b085d1a
27c792ad2cb91b09191a73ea3b085d1a
ብርሀኑ ግዛው በሉሲዎቹ አሰልጣኝነት ይቀጥላሉ
አሰልጣኝ ብርሀኑ ግዛው በኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ውላቸው እንደሚራዘም ተገለፀ፡፡የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በሐምሌ ወር 2012 መጨረሻ ላይ በኮቪድ 19 ወረርሺኝ የተነሳ ምንም አይነት ውድድሮች አይካሄዱም ማለቱን ተከትሎ በተለያየ የዕደሜ ዕርከን ውስጥ ተሹመው የነበሩ እንዲሁም የዋናው የወንድ እና ሴት ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኞች ውላቸው እንደማይራዘም ማሳወቁ ይታወሳል፡፡ሆኖም አሁን ላይ ፌዴሬሽኑ አሰልጣኞችን በአዲስ መልክም ሆነ ውል በማራዘም ላይ የሚገኝ ሲሆን አሁን ደግሞ ብርሀኑ ግዛው በሉሲዎቹ አሰልጣኝነት እንዲቀጥሉ ወስኗል። አሰልጣኙ ሀዋሳ ላይ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን እያሰለጠነ በፕሪምየር ሊጉ ውድድር ላይ የሚገኝ ሲሆን በያዝነው ሳምንትም አሰልጣኙ ወደ አዲስ አበባ አምርተው ውሉ የሚያራዝሙበትን ፊርማ ያኖራሉ ተብሏል፡፡
1
29342521bee3f09a71e5f592b99ae332
9d4426f36950f5ba15a78082eebc5856
ኢትዮጵያ ኢየሩሳሌም ውስጥ የቡና ኤግዚቢሽን አካሄደች፡፡
የአውሮፓ ሕብረቱ ካፌ ፕሮጄክት የኢትዮጵያን የቡና ምርት ለማሳደግ የሚያስችል የ15 ሚሊየን ዩሮ ፕሮጄክት ይፋ ማድረጉን አስታወቀ፡፡የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሳኒ ረዲ ፕሮጄክቱ ይፋ በተደረገበት ወቅት እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ከፍተኛ የቡና አምራች ሀገር ብትሆንም፣ ከዘርፉ የሚገኘው ጥቅም ከምርቱ አንፃር ዝቅተኛ በመሆኑ ፕሮጄክቱ ይህን ችግር በመቅረፍ ረገድ ጉልህ ሚና ይኖረዋል፡፡ የካፌ ፕሮጄክት አስተባባሪ አቶ ፍቅሩ አመኑ በበኩላቸው ፕሮጄክቱ በቡና ምርት ላይ የሚደረገውን የንግድና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ለማሳደግ ያግዛል ብለዋል፡፡ፕሮጄክቱ ለአምስት ዓመታት የሚቆይ ሲሆን በአማራ፣ ደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ሕዝቦች እንዲሁም ኦሮሚያ ክልሎች በሚገኙ 28 ቡና አምራች ወረዳዎች ተግባራዊ ይሆናል፡፡
0
acdc601cdbfd3d4253b4cb51e4ff905e
4576a505019fd4d7e65e2c4df25552b3
የግብርናውን ስራ የሚያዘምኑ 624 ማሽነሪዎችን ከቀረጥ ነጻ እንዲሆኑ ተፈቀደ
የኢፌድሪ የብረታብረት እና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን የቴክኖሎጂ ሽግግሩን በአስተማማኝ ሁኔታ እየመራ እንደሚገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ገለፁ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ከባድ የማምረቻ ማሽነሪዎችን በአዲስ አበባ ማምረት የጀመረውን የኢፌድሪ ብረታ ብረት እና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን የጥራት ማዕከልን በይፋ መርቀው ከፍተዋል፡፡ማእከሉ በአዲስ አበባ ሜክሲኮ አካባቢ የሚገኘው የህብረት ማኒፋክቸሪንግ እና ማሽን ግንባታ ኢንዱስትሪ በኢፌድሪ ብረታ ብረት እና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን ስር ከሚገኙ 16 ግዙፍ ኢንደስትሪዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ ኢንደስትሪው በስሩ ካቀፋቸው 7 ፋብሪካዎች መካከል ንኡስ የማሽን ግንባታም ይገኝበታል፡፡የተለያዩ የማምረቻ ማሽነሪዎችን ደረጃ በማሳደግ እና በማደስ ሲያቀርብ የቆየው የማሽን ግንባታ ፋብሪካው አሁን ደግሞ አዳዲስ ማሽነሪዎችን በራሱ ዲዛይን ነድፎ በማዘጋጀት ግዙፉ እና ዘመናዊ መሣሪያዎችን የመግጠም ስራውን ጀምሯል፡፡በይፋ የተመረቀው ሌላኛው የኮርፖሬሽኑ የጥራት ማዕከል ደግሞ በብረታ ብረት እና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን 16ቱም ኢንደስትሪዎች እና ኮርፖሬሽኑ በሚያካሂዳቸው ፕሮጀክቶች በሙሉ የጥራት እና የደረጃ ክትትል ስራውን ያከናውናል፡፡ተቋማቱን የጎበኙት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ ኮርፖሬሽኑ የቴክኖሎጂ ሽግግሩን በአስተማማኝ ሁኔታ ለመስራት ያስቻሉትን በርካታ ደረጃዎች እያሰፋ መሆኑን ገልፀዋል፡፡የዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ማዕከል የሆነው የኢፌዴሪ ብረታ ብረት እና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን በየዓመቱ ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል እየፈጠረ ነው፡፡የሰው ሃይልን በቴክኖሎጂ ደረጃ ለማብቃት የሚያስችሉ ስልጠናዎችን የሚሰጠው ኮርፖሬሽኑ በቅርቡ ህይወታቸውን በጎዳና ይመሩ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥኖ በማስመረቅ በተለያዩ የኮርፖሬሽኑ ተቋማት ማሰማራቱን ኢሬቴድ በዘገባው አንስቷል፡፡
0
7c2080aa460309d25ede470f8cc2b681
247872b83a15d2a45b7e83b30a531500
ግብጽ ከአስዋን ግድብ የምታባክነው ውሃ የህዳሴ ግድብን በተያዘለት ጊዜ መሙላት የሚያስችል ነው
– የኢትዮጵያና ግብፅ መሪዎች በታላቁ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ የሚያደርጉትን የሶስትዮሽ ውይይት በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመቀጠል ተስማሙ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ እና አዲሱ የግብጽ ፕሬዚዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ባሳለፍነው ሐሙስ ለአፍሪካ ሕብረት ስብሰባ በኢኳቶሪያል ጊኒ፣ ማላቦ በተገናኙበት ጊዜ ተነጋግረዋል፡፡ሁለቱ መሪዎች በአገራቱ ሁለትዮሽ ግንኙነት ዙሪያና በአባይን ወንዝ ጉዳይ ውይይት ማድረጋቸው ተጠቁሟል፡፡የሁለቱ አገራት የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በውይይትና አብሮ መስራት መርህ ላይ የተመሰረተ ግንኙነት ሊኖር እንደሚገባ መሪዎቹ መስማማታቸውን ከመሪዎቹ ውይይት በኋላ የወጡ መረጃዎች አመልክተዋል፡፡የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ በአባይ ወንዝ ላይ መጀመርን ተከትሎ በሁለቱ አገራት መካከል የነበረው ግንኙነት መቀዛቀዝ አሳይቶ የነበረ ቢሆንም ከቅርብ ወራት ወዲህ ግን ግንኙነታቸው እየተሻሻለ መጥቷል፡፡ኢትዮጵያና ሁለቱ የታችኛው የአባይ ተፋሰስ አገራት ግብጽና ሱዳን የዓለም አቀፉ የባለሙያዎች ቡድን ግድቡን አስመልክቶ ያወጣውን የምክር ሃሳብ ለመተግበር የሶስትዮሽ ኮሚቴ ማዋቀራቸው ይታወሳል፡፡ ከሶስት ዙር ውይይቶች በኋላ ግን ግብጽ ውይይቱን አቋርጣ ነበር፡፡በውይይቱ የኢትዮጵያ መንግስት ግድቡ በግብፅ ውሃ አጠቃቀም ላይ የሚያስከትለው ጉዳት ካለ ለመከላከል፤ በግብጽ መንግስት በኩል ደግሞ የኢትዮጵያን የልማት ፍላጎቶች ያገናዘበ ገንቢ የሆኑ ግንኙነቶችን እንዲፈጥር ተስማምተዋል፡፡ከዚህ በተጨማሪም ሁለቱ አገሮች በውሃ አጠቃቀም ዙሪያ የዓለም አቀፍ መርሆችን እንደሚያከብሩ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡
0
72eba76cf7caca57bf3a0e8b1d09d1ef
ba086034b310f2fa8496a18f3c2eb4ff
የአዲስ ዓመት የበጎ አድራጎት ተግባራት እንደ ባህል ተቆጥረው ሊቀጥሉ ይገባል -ምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር አቶ ደመቀ መኮንን
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 17፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት በድህነት ውስጥ ያሉ ዜጎችን ህይወት በመቀየርና ወደ ዘላቂ ልማት እንዲሸጋገሩ በማድረግ በኩል ትልቅ ሚና እንደነበረው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ገለጹ።ሁለተኛው የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት ዛሬ በደሴ ከተማ ይፋ ተደርጓል።ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ሁለተኛው ዙር የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክትን ዛሬ በደሴ ከተማ ይፋ አድርገዋል።የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት በከተማ በድህነት ውስጥ ያሉ ዜጎችን ህይወት በመቀየርና ወደ ዘላቂ ልማት እንዲሸጋገሩ በማድረግ በኩል ትልቅ ሚና እንደነበረው አቶ ደመቀ በዚህ ውቅት ገልጸዋል።በመርሃ ግብሩ አቅመ ደካማ ዜጎችን መርዳት ከልቦና ጋር የሚያስታርቅና የአዕምሮ እርካታ የሚሰጥ መሆኑንም ነው የተናገሩት።“ስንተባበር እና ስንከባበር የምንፈልጋትና የምንኮራባት ኢትዮጵያን መፍጠር እንችላለን” ያሉት አቶ ደመቀ፥ በሁለተኛው ዙር የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት የአቅመ ደካሞች ሕይወት በዘላቂነት እንዲለውጥ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ተመስገን ጥሩነህ በበኩላቸው፥ “መንግስት ድህነትን ለመቀነስ የሚያደርገውን ትግል ሁሉም ባለድርሻ አካል ሊደግፍ ይገባል” ብለዋል።የመጀመሪያው ዙር የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም የዜጎችን የሥራ ባህል ያሳደገና የከተሞችን ገጽታ የቀየረ መሆኑንም አንስተዋል።በሁለተኛው ዙር የከተሞች ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም ከቀድሞው ተሞክሮ በመውሰድ አፈጻጸሙ የተሻለ እንዲሆን በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።ሁለተኛው ዙር የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራምን ለማብሰር በደሴ ከተማ በተዘጋጀ መድረክ ላይ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ፣ የአማራ ክልል አፈ ጉባኤ፣ የክልል መስተዳድሮች እና ምክትል መስተዳድሮች፣ ሚኒስትሮች እንዲሁም የተለያዩ ከተምች ከንቲባዎችና የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች መገኘታቸውንም ኢዜአ ዘግቧል።
0
40ff1e7ac14ff4d6ea20ffad8827ceb0
0e24646fb793556219d2f665a71f478e
ሞሮኮ ወጣት ዜጎቿ ወደ ቱኒዝያ እንዳይሄዱ ከለከለች
የዚምባቡዌ ምክትል ፕሬዚዳንት ኮንስታንቲኖ ቺዌንጋ ባለቤት፣ ሜሪ ቺዌንጋ ባላቸውን በመግደል ሙከራና በከፍተኛ የገንዘብ ማጭበርበር ክስ እንደተመሰረተባቸው ተዘግቧል፡፡ ባለፈው ሰኞ በመዲናዋ ሃራሪ በሚገኝ ፍርድ ቤት የቀረቡት ሜሪ ቺዌንጋ፤ ባለፈው ሃምሌ ወር ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ባለቤታቸውን ኮንስታንቲኖ ቺዌንጋን ወደ ህክምና እንዳይሄዱ በመከልከል አንዲሁም ሆስፒታል ከገቡ በኋላም የተተከለላቸውን የህክምና መሳሪያ በመንቀል ለሞት ለመዳረግ ሞክረዋል በሚል መከሰሳቸውን አልጀዚራ ዘግቧል፡፡የ38 አመቷ ሜሪ ቺዌንጋ፣ ከዚህ በተጨማሪም፣ 1 ሚሊዮን ዶላር ያህል በማጭበርበር፣ ወደ ደቡብ አፍሪካ አሸሽተዋል በሚል የከፍተኛ ገንዘብ ማጭበርበርና የሙስና ክሶች እንደተመሰረቱባቸው የጠቆመው ዘገባው፤ ፍርድ ቤት በቅርቡ ውሳኔ ያስተላልፍባቸዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመልክቷል፡፡
0
3b099fbc15211b76d26b63beb1c9001e
3b099fbc15211b76d26b63beb1c9001e
"የትረምፕ አስተዳድር ከአፍሪካ ጋር መነጋገር ይኖርበታል" የዩናይትድ ስቴትስ እንደራሴ
ርሀብ የፖለቲካ አለመረጋጋት እና አሸባሪነት ብዙ የአፍሪካ ሀገሮች ውስጥ ጫና እየፈጠሩ ባሉበት በዚህ ወቅት የትረምፕ አስተዳድር ከአፍሪካ ጋር መነጋገር ይኖርበታል ሲሉ አንድ የዩናይትድ ስቴትስ አንጋፋ እንደራሴ አሳስበዋል።የሕግ መወሰኛው ምክር ቤት የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ ሊቀ መንበር ኤድ ሮይስ አንድ ቢልዮን የሚሆነው የአፍሪካ ሕዝብ ለአሜሪካ ምርቶችና ውጥኖች ገበያ የመሆን እምቅ አቅም አለው ብለዋል፡፡ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
1
5168aff2049216eb81d7404a78775de5
5168aff2049216eb81d7404a78775de5
ሀዋሳ ከተማ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር በነበረው ጨዋታ ዙሪያ ቅሬታውን አሰምቷል
ከአሰላ ወደ ቢሾፍቱ ተለውጦ 0-0 በተጠናቀቀው የሀዋሳ እና ቡና ጨዋታ ዙሪያ ሀዋሳ ከተማ በተጫዋቾቼ እና በመኪናችን ላይ ጥቃት ተፈፅሟል በማለት ቅሬታውን ለፌዴሬሽኑ አሰምቷል።በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 26ኛ ሳምንት ሀዋሳ ከተማ በሜዳው እንዳይጫወት በመቀጣቱ ምክንያት አሰላ ላይ ኢትዮጵያ ቡናን መግጠሙ ይታወሳል። ሆኖም ከመጀመሪያው አጋማሽ ጀምሮ በጣለው ዝናብ ምክንያት ሜዳው አላጫውት በማለቱ የዕለቱ ዳኞች ጨዋታውን ወደ አዳማ ለውጠውት የነበረ ሲሆን ምሽት ላይ በድጋሚ ቢሾፍቱ ላይ እንዲከናወን ተወስኖ ሁለተኛው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በቢሾፍቱ ተደርጎ 0-0 ተጠናቋል።ሆኖም ሀዋሳ ከተማ ጨዋታው ከተጠናቀቀ በኃላ ተጫዋቾች ወደ ክለቡ ባስ ሲገቡ በኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች በነሱም በባሱም ላይ ጥቃት መሰንዘሩን በመግለፅ ጉዳዩን ለዕለቱ ኮሚሽነር እና ለፌድሬሽኑ ማሳወቁን በቡድን መሪው አቶ ዱሬሳ ዱካሞ በኩል በተለይ ለሶከር ኢትዮጵያ ገልጿል። አቶ ዱሬሳ ጨምረውም በሰዓቱ የክለቡ ተጫዋቾች ያኦ ኦሊቨር ፣ እስራኤል እሸቱ እና ወንድምአገኝ ማዕረግ ላይ መጠነኛ ጉዳት በመድረሱ ወደ ህክምና ለመሄድ እንደተገደዱ ገልፀው ጉዳዩን በቢሾፍቱ ከተማ ፖሊስ መምሪያ በመገኘት እንዳስመዘገቡም አስረድተዋል።
1
5e1fbc1e856fb6cf5d9cf992856be6f2
78826919cff1c527548607ae507547f4
ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር አብይ አህመድና ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የኡምሀጅር-ሁመራ ድንበር መንገድን በይፋ ከፈቱ
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ጎንደር ከተማ ገብተዋል።ጠቅላይ ሚኒስተር ዶክተር አበይ ጎንደር ከተማ ሲደርሱም የክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣናት አቀባበል አደርገውላቸዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ጎንደር የገቡት በነገው እለት በአማራ ክልል ጉብኝት ለማድረግ ጎንደር የሚገቡትን የኤርትራውን ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂን ለመቀበል ነው።የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ከነገ ጀምሮ በጎንደር እና ባህር ዳር ከተሞች ጉብኝት ያደርጋሉ።ፕሬዚዳንት ኢሳያስ በነገው እለት ጎንደር ከተማ የሚገቡ ሲሆን፥ በቆይታቸውም በጎንደር እና አካባቢው የሚገኙ ታሪካዊ ቦታዎችን እና የልማት ስራዎችን እንደሚጎበኙ ይጠበቃል።የፕሬዚዳንቱ ጉብኝት በሃገር ደረጃ የተጀመረውን ግንኙነት እንደሚያጠናክረው ታምኖበታል።በጎንደር ከተማ በርካታ ኤርትራውያን በተለያየ ስራ ተሰማርተው ይገኛሉ።ከዚህ ቀደም በአማራ ክልል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ወርቅሰሙ ማሞ የተመራ የልዑካን ቡድን በአስመራ ጉብኝት ማድረጉ የሚታወስ ነው።(ኤፍቢሲ)
0