query_id
stringlengths 32
32
| passage_id
stringlengths 32
32
| query
stringlengths 2
182
| passage
stringlengths 137
1.88k
| label
int64 0
1
|
---|---|---|---|---|
7cb557d37735176d2068596ce6daa261
|
538f02c913041a5956c7af993dbd63d9
|
በአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ የተጠረጠሩ 2 ሰዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ
|
የታዋቂው ድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያን ተከትሎ በተቀሰቀሰው ተቃውሞና አለመረጋጋት የ166 ሰዎች ህይወት ማለፉን በትናንትናው ዕለት ፓሊስ አስታውቋል።ድምፃዊው ሰኞ ሰኔ 22፣ 2012ዓ.ም ገላን አካባቢ መገደሉን ተከትሎ 145 ሰላማዊ ሰዎችና 11 የፀጥታ ኃይሎች መሞታቸውን የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፖሊስ ኮሚሽነር ግርማ ገላን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል።ምክትል ፖሊስ ኮሚሽነሩ ከዚህም በተጨማሪ 167 የሚሆኑ ግለሰቦችም ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል ብለዋል። ከአለመረጋጋቱና ሁከቱም ጋር በተያያዘ 1 ሺህ 84 ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ኮሚሽነሩ ግርማ አክለው ገልፀዋል።ባለስልጣናቱ ለህይወት መጥፋት ምክንያት ያሉት ከፀጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት እንዲሁም በተለያያዩ ብሔሮች መካከል በተፈጠረ ሁከት የተያያዘ ነው ተብሏል።ከዚህም በተጨማሪ በአዲስ አበባ የስምንት ነዋሪዎችና የሁለት ጸጥታ አስከባሪዎች ህይወት ማለፉን የከተማዋ ፖሊስ ማስታወቁ የሚታወስ ነው። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው ከሰሞኑ በብሔራዊ ቴሌቪዥን ቀርበው በሰጡት መግለጫ ነዋሪዎች "ህይወታቸው ያለፈው "በቦምብ፣ ጥይት፣ በድንጋይ እና በመሳሰሉት ነው" ብለዋል። ከዚህም በተጨማሪ 57 የሚሆኑ የፌደራል እና የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት ላይ ጉዳት መድረሱንና ብረትነታቸው የግለሰብ እና የመንግሥት የሆኑ 250 ተሽከርካሪዎች ተሰባብረዋል፣ 20 ተሽከርካሪዎች ተቃጥለዋል ሲሉም አክለዋል
| 0 |
e1f9ecfa49b7798b7db43013f1f721a9
|
58b7a2c56b6392ed0626196010781863
|
የኢትዮዽያ ብሄራዊ ቡድን በሀዋሳ ዝግጅቱን እያደረገ ይገኛል
|
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በዚህ ሳምንት መጨረሻ የወዳጅነት ጨዋታ ለማድረግ ወደ ሞሮኮ ያመራል፡፡ ቡድኑ ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ ለቦትስዋና 51ኛ አመት የነፃነት በአል ምክንያት በማድረግ ወደ ጋቦሮኒ አቅንቶ የወድጅነት ጨዋታ አድርጎ 2ለ0 ተሸንፎ መመለሱ ይታወሳል፡፡ቡድኑ በዚህ ሳምንት መጨረሻ ወደ ሞሮኮ ራባት አቅንቶ ጨዋታውን ለማድረግ በካፒታል ሆቴል መቀመጫውን በማድረግ በኢትዮጵያ ወጣቶች እና ስፖርት አካዳሚ ዝግጅቱን እያደረገ መሆኑ ሲገለፅ ጨዋታው የሚደረገው ከሞሮኮ የቻን ብሄራዊ ቡድን ጋር መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስታውቋል፡፡ ሙሉ የትራንስፖርት እና የሆቴል ወጪ በሞሮኮ እግር ኳስ ፌደሬሽን እንደሚሸፈን የታወቀ ሲሆን የሞሮኮ ብሄራዊ ቡድን በ2018 በሚደረገው የቻን ውድድር ላይ እንደ መካፈሉ የወዳጅነት ጨዋታውን ለማድረግ መፈለጉ ተሰምቷል፡፡የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ በሚቀጥለው ሳምንት እንደሚደረግ የታወቀ ሲሆን በቦትስዋናው የወዳጅነት ጨዋታ ላይ የነበሩ ተጨዋቾች በዚህኛውም ጨዋታ ላይ እንደሚሳተፉ ለማወቅ ተችሏል፡፡
| 0 |
cb071aa65e485a410ba9921588868ef1
|
cb071aa65e485a410ba9921588868ef1
|
ጎንደር የሚገኙ የወልቃይት ጠገዴ ተፈናቃዮች
|
ከወልቃይት ጠገዴ ተፈናቅለው ጎንደር ከተማ በጊዚያዊ መጠለያ ጣቢያ ውስጥ የሚገኙት ተፈናቃዮች መንግሥት አፋጣኝ ምላሽ ይስጠንና ወደቀያችን እንመለስ ሲሉ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
ቁጥራቸው ከሁለት መቶ በላይ የሚሆኑ አብዛኛዎቹ ደግሞ በአፍላ የወጣትነት የዕድሜ ክልል የሚገኙ እነዚህ ተፈናቃዮች በጎንደር ከተማ በ አንድ ግለሰብ ቤት ውስጥ በተዘጋጀላቸው ጊዚያዊ መጠለያ ውስጥ ነው ያሉት - በተጨናነቀ ሁኔታ።
| 1 |
8e4af691d8ba4fc5ef0f36c04c4c1ff4
|
b6119b077ed5871f0ed591778e168121
|
ቻምፒየንስ ሊግ ፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ 1ኛው ዙር ተሸጋገረ
|
ለአራት ተከታታይ አመት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግን ማሸነፍ የቻለው እና በቀጣይ አመት በፕሪምየር ሊጉ እና በአፍሪካ ሻምፒየንስ ሊጉ ተፎካካሪ ለመሆን የተለያዩ ተጨዋቾችን በማስፈረም እንዲሁም ውላቸው ያለቀ ተጨዋቾችን ውል በማደስ ላይ የሚገኘው ቅዱስ ጊዮርጊስ የፊት መስመር አጥቂውን ሳላዲን ሰኢድንም ውል አድሷል፡፡ሰኔ 30 ኮንትራቱ የተጠናቀቀው ሳላዲን ሰኢድ ስሙ ከተለያዩ የግብፅ ክለቦች ጋር ተያይዞ ሲዘገብ የቆየ ሲሆን ተጨዋቹ በተለይ ወደ ግብፅ አምርቶ ከአል ማስሪ ጋር ድርድሮችን ያደረገ ቢሆንም ሁለቱ ክለቦች ስምምነት ላይ ሳይደርሱ ቀርተዋል፡፡ፈረሰኞቹ ተጨዋቹን ለሁለት አመት በቡድናቸው ለማቆየት የተስማሙ ሲሆን ተጨዋቹ በተለይ በዚኛው አመት ካሳየው የአፍሪካ ቻምፒየንስ ሊግ ብቃት እንዲሁም ካስቆጠራቸው ጎሎች(7 ቻምፒየንስ ሊግ፣15 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ)አንፃር በቀጣይ ቡድኑን ይጠቅማል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ቅዱስ ጊዮርጊሶች ከዚህ በፊት ለአለም ብርሃኑ፣አብዱልከሪም መሃመድ ፣፡ሙሉአለም መስፍን ፣ ጋዲሳ መብራቴ ፣ ታደለ መንገሻ እንዲሁም አሜ መሐመድን ወደ ክለባቸው መቀላቀል የቻሉ ሲሆን አስቻለው ታመነ ፣ ሳላዲን በርጌቾ ፣ ደጉ ደበበ እና ናትናኤል ዘለቀ ለሁለት አመት ፤ አበባው ቡጣቆ እና በኃይሉ አሰፋ ለአንድ አመት ውላቸውን ማራዘማቸው የሚታወሰ ነው፡፡
| 0 |
e6842eac327c63bef3dc7b47481d73e9
|
e6842eac327c63bef3dc7b47481d73e9
|
ትራምፕ አሜሪካ ከዓለም ጤና ድርጅት ጋር ያላትን ግንኙነት አቋረጡ
|
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 22 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዋሽንግተን ከዓለም ጤና ድርጅት ጋር ያላትን ግንኙነት እያቋረጡ መሆኑን አስታወቁ።የፕሬዚዳንቱ ውሳኔ የዓለም ጤና ድርጅት ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ ቻይናን ተጠያቂ አላደረገም ከሚል የመነጨ ነው ተብሏል።ፕሬዚዳንቱ ቻይና ድርጅቱ ላይ ጫና እያሳረፈችና እየተቆጣጠረችው ነው ሲሉም ወቅሰዋል።ትራምፕ በኋይት ሃውስ በሰጡት መግለጫ “ዛሬ ከዓለም ጤና ድርጅት ጋር ያለንን ግንኙነት እናቋርጣለን” ብለዋል።ከዚህ ባለፈም ለድርጅቱ ይደረገ የነበረውን ድጋፍ ወደ ሌሎች አካላት እናዞረዋለንም ነው ያሉት።የዓለም ጤና ድርጅትንም “የቻይና አሻንጉሊት” ሲሉ ወርፈውታል።ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የዓለም ጤና ድርጅት ያለው ነገር ባይኖርም ከዚህ ቀደም በትራምፕ ይቀርብበት የነበረውን ውንጀላ ሲያጣጥል ቆይቷል።ቻይና በበኩሏ ከዚህ ቀደም አሜሪካ በራሷ ስህተት ለኮሮና ቫይረስ መጋለጧን ስትገልጽ ቆይታለች።ዋሽንግተን የራሷን ስህተት በመሸፈንና ቻይናን በመኮነን ማካካሽ ትፈልጋለች ስትልም ትወቅሳለች።አሜሪካ ለዓለም አቀፉ የጤና ድርጅት በየአመቱ ከፍተኛውን ገንዘብ ስትሸፍን ቆይታለች።ቻይና በበኩሏ የዓለም ጤና ድርጅት የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ለሚያደርገው ጥረት 2 ቢሊየን ዶላር እንደምትሰጥ ቃል መግባቷ ይታወሳል።የአሁኑ የትራምፕ ውሳኔ ከመቸ ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ ግን የታወቀ ነገር የለም።አሜሪካ በፈረንጆቹ 1948 የተቀላቀለችውን ዓለም አቀፍ ተቋም በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ አሳውቃ የመውጣት መብት እንዳላት በሃገሪቱ ኮንግረስ ስምምነት የተደረሰበት የውሳኔ ሃሳብ ያመላክታል።ምንጭ፦ ሬውተርስ እና ቢቢሲ
| 1 |
28d912f13211e641cf909ce3f7f8d57e
|
769dc5b6ddc8c73a8169263f10187cef
|
የዓለም ህፃናት ቀን በሃዋሳ ከተማ ተከበረ
|
አዲስ አበባ፣ መስከረም 9፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) አለም አቀፉ የፅዳት ቀን በአዲስ አበባ በፅዳት ዘመቻ ንቅናቄ ተከበረ።ከማለዳው 12 ሰአት ጀምሮ በመንግስት ተቋማት፣ በትምህርት ቤቶች እና በሀይማኖት ተቋማት የፅዳት መርሃግብር ተካሂዷል።የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤን ጨምሮ በርካታ የከተማ አስተዳደሩ የስራ ኃላፊዎች በየአካባቢያቸው በንቅናቄው ተሳትፈዋል።ወይዘሮ አዳነች በዛሬው እለት ከ1 ሚልዮን በላይ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የአለም ማህበረሰብን በመቀላቀል አካባቢያቸውንና ከተማቸውን እያፀዱ መሆኑን ተናግረዋል።በዛሬው እለት ትምህርት ቤቶችን የማጽዳት እና የጸረ ተሕዋሲያን ኬሚካል ርጭት ስራ መካሄዱንም ነው ያመለከቱት።“ባሳለፍነው ዓመት ታትረው የጽዳት ስራ ሲሰሩ የነበሩ ነዋሪዎቻችንን እያመሰገንኩ ከዛሬ ጀምሮ ሁላችንም በመተባበር እና በአንድነት መንፈስ አዲስ አበባ ስሟን እና ክብሯን የሚመጥን ጽዳት እንዲኖራት በእንዲህ ቀን ዘመቻ ሳይሆን ሁሌም በማጽዳት ለነዋሪዎቿ ምቹ ለቱሪዝም ሳቢ ከተማ እድናደርጋት ጥሪዬን አቀርባለው” ብለዋል በመልዕክታቸው።በዛሬው ፅዳትን በመጠበቅ የተሻለ አፈፃፅም ያላቸው አካባቢዎች እውቅና እንደሚሰጣቸው ተጠቁሟል።
| 0 |
7e71ca1672a2c534deea09375fd4402d
|
1f41877a474435b61b26da52a50119d5
|
የህዳሴው ግድብ አዲሱ የሀገራችን ገጽታ ግንባታ አምባሳደር ነው – አቶ በረከት
|
አዲስ አበባ ፣መስከረም 26 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን ከዳር ለማድረስ የገቢ ማሰባሰብ ስራው በሰፊ ንቅናቄ እየሰራ መሆኑን ገልጿል።የከተማዋ የታላቁ የኢትዮጵያ ህደሴ ግደብ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ÷ በበጀት አመቱ ከ789 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ለማሰባሰብ አቅዶ ባለፉት 3 ወራት ብቻ ከ500 ሚሊየን ብር በላይ መሰብሰብ መቻሉን ለፋና ብሮድካስቲግ ኮርፖሬት አስታውቋል።የፅህፈት ቤቱ ሀላፊ አቶ ምስክር ነጋሽ በእነዚህ ወራት የተሰበሰበው ገቢ በአመቱ ከታቀደው በላይ ገቢ ሊሰበሰብ አንደሚችል አመላካች ነው ብለዋል።ለዚህም ምክንያቱ የሁሉም ኢትዮጵያያን አሻራ ያረፈበት ግድቡ የመጀመሪያ ዙር የውሀ ሙሌት መጠናቀቅ እና ለገቢ ማሰባሰቢያ በሀገሪቱ ሁሉም ቦታዎች የሚዞረው ዋንጫ ነው ብለዋል።የከተማ አስተዳደሩ የህዳሴው ዋንጫን በአስሩም ክፍለከተሞች በማዘዋወር ገቢ እየሰበሰበ ይገኛል።ይህም ህብረተሰቡ ለግድቡ የሚያደርገውን ድጋፍ እንዲያጠናክር እንዳገዘውም የፅህፈት ቤቱ ሀላፊ ተናግረዋል።የህዳሴው ግድብ ግንባታ ከተጀመረ አንስቶ እስከባለፈው አመት መጨረሻ ከ 1 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን አቶ ምስክር ነጋሽ አክለው ገልጸዋል።በዙፋን ካሳሁን
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
| 0 |
5a64bd21cb77b2b6d71259460d68f73e
|
45078e30f0a4e4ebe5e42cb422770362
|
ለጋሾች በጦርነት ለታመሰችው የመን ገንዘብ እንዲያዋጡ ተጠየቀ
|
ከ70 በላይ ስደተኞችን አሳፍራ ወደ የመን ስትጓዝ በሰጠመችው ጀልባ ህይወታቸውን ባጡ ኢትዮጵያውያን ሞት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን የውጪ ጉዳይ ሚንስቴር ገለፀ።የውጪ ጉዳይ ሚንስቴር መስሪያቤቱ ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንዳሉት ሚንስቴር መስሪያቤቱ በተከሰተው አደጋ ክፉኛ አዝኗል።ለሟች ቤተሰቦችም መፅናናትን ይመኛል ብለዋል ቃል አቀባዩ ።ሚንስቴሩ በአደጋው ለህልፈት የበቁትን ኢትዮጵያውያንን ማንነትና የአደጋውን መንስኤ አጣርቶ ዝርዝር መግለፃ በቅርቡ እንደሚሰጥም ነው አምባሳደር ዲና የተናገሩት ።በብዛት ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን አሳፍራ ወደ የመን ስትጓዝ የነበረች ጀልባ ሰጥማ 70 የሚደርሱ ሰዎች ለህልፈት መዳረጋቸው እና ለጀልባዋ መስጠም ምክንያት የሆነውበጊዜው የነበረው ከባድ ንፋስ እና ማእበል እንደሆነ የየመን የፀጥታ ሀላፊዎች መግለፃቸውም አይዘነጋም ።በየአመቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች የመን ለመግባት የቀይ ባህርን ሲያቋርጡ አብዛኛዎቹ ህይወታቸውን እንደሚያጡ ተያይዞ ተጠቅሷል። (ኤፍ.ቢ.ሲ)
| 0 |
1b6595ad82a3693c932147b1b10b3905
|
41b0f91f3e13ac789ccb9c429a4a448b
|
ከዛሬ ጀምሮ ከቤት ውጪ በሁሉም ቦታዎች ጭምብል የመልበስ ግዴታ ተግባራዊ እንዲሆን መመሪያ ጸደቀ፡፡
|
በአማራ ክልል ከቤት ውጭ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል አድርጎ መንቀሣቀስ ግዴታ ሆነ የክልሉ የኮሮናቫይረስ መከላከልና መቆጣጠር ግብረ ሃይል ሰብሳቢ ዶ/ር ሙሉነሽ አበበ የቫይረሱ ስርጭት አሳሳቢ እየሆነ በመምጣቱ ነው አስገዳጅ ውሳኔ የተወሰነው ብለዋል።የክልሉ ርዕሰ መዲና በሆነችው ባህር ዳር ግን አስገዳጅ ውሣኔከተወሰነ በዋላ የከተማዋ ነዋሪዎች ከበፊቱ የተሻለ ተጠቃሚ ቢታይም ብዙ የግዴታ ድንጋጌ የሚያስፈልጋቸው ተግባራት እንዳሉ ያነጋገርናቸው ነዋሪዎች ገልፀዋል።።
| 0 |
9da7d7e3e32e83f347998cbbed8e44f7
|
ce7f033dc9d02089dec92eb440c15e72
|
ከ 14 ሺህ በላይ ዜጎች ለሥራ ወደ ውጭ አገር ሄደዋል
|
አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 14 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢንጂነር ታከለ ኡማ ከኢትዮጵያ ውጭ የነበሩ ወገኖች በሚመለሱበት ጊዜ ወደ ህብረተሰቡ ከመቀላቀላቸው በፊት በለይቶ ማቆያ ማዕከላት በሚቆዩባቸው ጊዜዎች ወጪያቸውን መሸፈን ለማይችሉ ዜጎች ሙሉ ወጪያቸውን መንግስት እንደሚሸፍን አስታወቁ።ኢንጂነር ታከለ በፌስ ቡክ ገጻቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ መንግስት ከተለያዩ ሃገራት ወደ ኢትዮጵያ ለሚገቡ መንገደኞች እና ወገኖች የለይቶ ማቆያ ማዕከል ማዘጋጀቱን አስታውቀዋል።በዚህ ወቅትም ለቆይታ ጊዜው ወጪያቸውን መሸፈን ለማይችሉ ዜጎች የከተማ አስተዳደሩ ሙሉ ወጪያቸውን እንደሚሸፍን ገልጸዋል።ኢንጂነር ታከለ አያይዘውም በመተሳሰብ ራስን መጠበቅ እንደሚገባ ጠቅሰዋል።ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!
https://t.me/fanatelevision
| 0 |
e7040581ff446865e0965c216185eaf4
|
e7040581ff446865e0965c216185eaf4
|
አየር መንገዱ በቀጥታ የሚፈጸምን የትኬት ሽያጭ ማቆሙን አስታወቀ
|
አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 18 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቀጥታ የሚፈጸምን የትኬት ሽያጭ ማቆሙን አስታወቀ።አየር መንገዱ ለጣቢያችን በላከው መግለጫ ለየትኛውም ጉዞ የሚፈጸምን የትኬት ሽያጭ በኢንተርኔት አማካኝነት እንደሚሰጥ አስታውቋል።እርምጃው እየተስፋፋ የመጣውን የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት በማለም የተወሰደ መሆኑንም ገልጿል።በዚህም የትኬት መሸጫ ቢሮዎች ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ ለጊዜው ይዘጋሉ ነው ያለው።ደንበኞችም አገልግሎቱን አየር መንገዱ ባዘጋጃቸው የሞባይል መተግበሪያዎችና በባንኮች ማግኘት እንደሚችሉም ነው የገለጸው።
| 1 |
db9c0866569aa589be97c65d0f0af6e6
|
5658b16a095aa038f12988793353671e
|
የደቡብ ሱዳን መንግሥት ዛሬ ጁባ የሚገቡትን የአማጽያኑን ቀዳሚ ቡድን ለመቀበል በዝግጅት ላይ ይገኛል
|
በጁባና በሌሎችም ዋና ዋና ከተሞች የሚሰፍረው ኃይል ቁጥር ላይ የተስማሙት የደቡብ ሱዳን ተቀናቃኝ ወገኖች አጠቃላይ ስምምነቱን ተግባራዊ ለማድዐግ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ገለጡ።የተቃዋሚዎቹ መሪዎችም ግጭቱ ከተቀሰቀሰ ከሁለት ዓመታት በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ጁባ ሊጓዙ ተስማምተዋል።እስክንድር ፍሬው ዝርዝሩን አቅርቦታል፣ ከተያያዘው የድምጽ ፋይል በመጫን ያዳምጡ።
| 0 |
2738b7cba7aded0402c328070be8d51b
|
b81470746d29950a72fefe1e2e8b7416
|
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት የአራት አባላቱን ያለመከሰስ መብት አነሳ
|
አዲስ አበባ ፣ ጥር 13 ፣ 2012(አዲስ አበባ) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት ባካሄደው 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ አዋጆችን መርምሮ አጽድቋል።ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ጉባኤ የወረዳና የቀበሌ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት የምክር ቤት አባላት ቁጥር መወሰኛ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ አጽድቋል፡፡በተጨማሪም የክልሉ መንግስት የአስፈፃሚ አካላት የ6 ወር የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ አሻድሊ ሀሰን ለጉባኤው አባላት ቀርቧል፡፡ርዕሰ መስተዳደሩ በሪፖርታቸው ባለፈው ግማሽ ዓመት በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ተከስተው የነበሩ የፀጥታ መደፍረስ ችግሮች በተሰራው ስራ ተቀርፈው አንፃራዊ ሰላምና መረጋጋት መስፈኑን አመላክተዋል፡፡ከአጎራባች ክልል ህዝቦች ጋር የነበረውን የቆየ ግንኙነት ለማጠናከር አልፎ አልፎ የተፈጠሩ አለመግባባቶችን በዕርቅና በይቅርታ በመፍታት አበረታች ለውጦች መመዝገባቸውንም ተናግረዋል፡፡በክልሉ መተከል ዞን አካባቢ የተፈናቀሉትን ወደ ቀያቸው መመለስና በዘላቂነት ለማቋቋም በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ያነሱት ርዕሰ መስተዳድሩ፥ በእርሻ ዝግጅት ወቅት በአንዳንድ አካባቢዎች ተከስቶ የነበረው የፀጥታ ችግር እና አርሶ አደሩ እና ባለሃብቶች ወደ ስራ ባለመግባታቸው ምክንያት አፈፃፀሙ ዝቅ ማለቱን አስረድተዋል።በትምህርት ዘርፉም በክልሉ 312 ሺህ 396 ተማሪዎች ከቅድመ መደበኛ እስከ 2ኛ ደረጃ ባሉ ትምህርት ቤቶች ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ እንደሚገኙም ተጠቅሷል፡፡መከላከልን መሰረት ያደረገ የጤና ፖሊሲ ተቀርፆ ወደ ትግበራ ከተገባ በኋላም የእናቶችንና የህፃናት ሞትን ለመቀነስ በትኩረት እየተሰራና መልካም ውጤት እየተመዘገበ መሆኑም ተመላክቷል።በከተማና በገጠር ለ15 ሺህ 814 ወጣቶች ጊዜያዊና ቋሚ የስራ እድል ለመፍጠር መቻሉንም ከክልሉ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።በክልሉ የተለያዩ ቀበሌወች ወረዳ እንዲሆኑ እና የስም ለውጥ በማድረግ እና በክልሉ 474 ቀበሌ የነበሩት አዳዲስ ቀበሌዎች ተጨምረው 518 ቀበሌ በመሆን እንዲጸድቅ መወሰኑ ተነግሯል፡፡
| 0 |
34a0547bf82c0a8b2103ce20f9952a92
|
2053bc5d069ff88023fab2409af97109
|
ፍልስጤም ከአሜሪካ እና እስራኤል ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ግንኙነት አቋረጠች
|
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 19/2005 (ዋኢማ) – ኢትዮጵያ ከኦማን ጋር ያላትን ግንኙነት የበለጠ አጠናክራ ለመቀጠል እንደምትሻ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ዛሬ ገለጹ። ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ በኢትዮጵያ የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን የኦማን አምባሳደር አብደላ ሐመትን በብሔራዊ ቤተ-መንግሥት ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት እንደገለፁት ኢትዮጵያ ከአገሪቱ ጋር ያላት ግንኙነትን ወደላቀ ደረጃ ለማሳደግ ፍላጎት አላት። ከኦማን ጋር ያለው መልካም የሆነ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በኢንቨስትመንትና በባህል ይበልጥ በማጠናከር የትብብር አድማሷን ማስፋት እንደምትፈልግ አመልክተዋል። የአገሮቹ ግንኙነት በተለይም በንግድ መስክ መልካም የሚባል እንደነበር ፕሬዚዳንት ግርማ አስታውሰዋል። አምባሳደር ሐመት በበኩላቸው አገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር መልካም የሚባል ግንኙነት እንዳላትና አገሮቹ ያላቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ጠንካራ ፍላጎት እንዳላትም ገልጸዋል። የጅማን ቤተ-መንግሥት ሲጎበኙ የተመለከቷቸው ጽሁፎችና ቅርፃ ቅርፆች በኦማንና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን የቆየ ወዳጅነት እንደሚያመለክቱ አስታውቀዋል።እንደ ኢዜአ ዘገባ በቀጣይም ኢትዮጵያና ኦማን ያላቸውን ሁለንተናዊ ግንኙነት ወደፊትም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥረት እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል። አምባሳደር ሐመት ተቀማጭነታቸው ሰንዓ፣ የመን ሆኖ ኢትዮጵያን ያገለገሉት ላለፉት 13 ዓመታት እንደነበር የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አስታውቋል።
| 0 |
6b08d200d0424fb066eb31fd557a3db1
|
ff95ded7f9003289593fcf097db7465b
|
በቻይና የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር ከ7 ሺህ በላይ ደረሰ
|
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 14፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ የኮሮና ቫይረስ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 3 ሺህ 105 መድረሱን የከተማዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ አስታወቀ። በአዲስ አበባ በ24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ 31 ሰዎች ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል ነው የተባለው። በአዲስ አበባ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተገናኘ በህክምና ማዕከል ህክምና ሲከታተሉ የነበሩ 1 ሴት ህይወታቸው ማለፉም ነው የተገለፀው። በሌላ በኩል ደግሞ በትላንትናው እለት 67 ሰዎች ከአዲስ አበባ ከኮሮና በሽታ አገግመዋል፡፡
| 0 |
a4bc0d4f7f9d3ffb0ef576b028325840
|
bfe7986cb0f417de403c498f0ed93084
|
ራክሲኦ ግሩፕ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የግል የመረጃ ቋት ማዕከል ሊገነባ ነው
|
በኦሮሚያ ክልል በአሰላ አካባቢ 100 ሜጋ ዋት የሚያመነጭ የንፋስ የኤሌክትሪክ ኃይል ፕሮጀክት ሊገነባ ነው። የንፋስ ኃይል በመጠቀም ለማመንጨት የታቀደው የኤሌክሪክ ኃይል ፕሮጀክት በመጪዎቹ ሁለት ዓመታት የሚጠናቀቅ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱን ዕውን ለማድረግ የሚያስፈልገው 146 ሚሊዮን ዩሮ (ከ5.8 ቢሊዮን ብር በላይ) የበጀት ፍላጎትም ከዴንማርክ መንግሥት በዕርዳታና በድጋፍ መልክ ተገኝቷል። ለፕሮጀክቱ ከሚያስፈልገው 146 ሚሊዮን ዩሮ ውስጥ 117.3 ሚሊዮን ዩሮ ያህል ዳንሴክ ግሩፕ ከተሰኘው የዴንማርክ ባንክ በብድር የተገኘ ሲሆን፣ የተቀረውን የገንዘብ መጠን ደግሞ የዴንማርክ መንግሥት በዕርዳታ ለመስጠት ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ስምምነት ተፈራርሟል። ፕሮጀክቱ የሚጠይቀውን አጠቃላይ ወጪ በድጋፍና በብድር ለመደገፍ የዴንማርክ መንግሥትና ዳንሴንክ ግሩፕ የተሰኘው ባንክ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ስምምነት የፈጸሙ ሲሆን፣ ይህንንም ስምምነት የሕዝብ የወካዮች ምክር ቤት ባለፈው ሳምንት ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ አፅድቆታል። በብድር መልክ የተገኘው 117.3 ሚሊዮን ዩሮ የአምስት ዓመታት የዕፎይታ ጊዜን ጨምሮ በ20 ዓመታት ጊዜ ውስጥ የሚከፈል ነው፡፡ የዴንማርክ መንግሥት በብድሩ የሚከፈለውን ወለድ ለመሸፈን በመስማማቱ፣ ከብድር ወለድ ክፍያ ነፃ መሆኑን በሁለቱ ወገኖች መካከል የተፈረመው የስምምነት ሰነድ ያስረዳል። የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቱን ዕውን ለማድረግ የሚያስፈልጉ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ተርባዮኖች በሙሉ ከዴንማርክ የሚገዙ ሲሆን፣ ዕቃዎቹን የማቅረብና ፕሮደክቱን በበላይነት የማስተዳደር ኮንትራት ሲመንስ ከተባለው የዴንማርክ ኩባንያ ጋር መፈረሙን ሪፖርተር ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በምሥራቅ ኦሮሚያ በኢተያ ወረዳ የሚገነባ ነው። ፕሮጀክቱ 100 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም የሚኖረው ሲሆን፣ እያንዳንዳቸው 3.45 ሜጋ ዋት የሚያመነጩ 84 ሜትር ከፍታ ያላቸው 29 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ተርባይኖች ይኖሩታል ተብሏል። የፕሮጀክቱ ግንባታ አገሪቱ በአሁኑ ወቅት ከንፋስ ኃይል እያመነጨች ያለውን 324 ሜጋ ዋት የኃይል መጠን ከፍ እንደሚያደርገው፣ የአሰላውና በአይሻ እየተገነባ ያለው 120 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም የሚኖረው የንፋሰ ኃይል ማመንጫ ሲጠናቀቅ፣ አገሪቱ ከንፋስ ኃይል የምታገኘው አጠቃላይ የኤሌክትሪክ ኃይል 544 ሜጋ ዋት እንደሚደርስ ይጠበቃል።
| 0 |
7df528be5c1785296ae0b416f3ebcd27
|
4c008b895c02165578b1a21db63076fb
|
አሜሪካ ለታይዋን የጦር መሳሪያ ሽያጭ ማጽደቋ ተገለጸ
|
በያዝነው ሳምንት መጀመሪያ አካባቢ በሶርያ የተፈጸመውንና የደርዘኖቹን ሕይወት የቀጠፈውን የኬሚካል ጋዝ ጥቃት ተከትሎ አሜሪካን የሚሳኤል የጥቃት እርምጃ በሶሪያ መንግስት ላይ ፈጽማለች፡፡የአሜሪካን ባለስልጣናት እንደገለጹት የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን ጥዕዛዝ ተከትሎ 59 የሚሆኑ ክሩዝ ሚሳኤሎችን በሶሪያው የኬሚካል ጦር መሳሪያዎች መገኛ የሆነውን ቦታ እንዳወደሙ ታውቋል፡፡የአሜሪካ መከላከያ መስሪያ ቤት ፔንታጎን እንደገለፀው፣ ሚሳኤሎቹ የተወነጨፉት በሜዲትራንያን ባህር ላይ ከሚገኝ የአሜሪካ የጦር መርከብ ላይ ነው፡፡የፔንታጎኑ ቃል አቀባይ ካፒቴን ጄፍ ዳቪስ ለዘጋቢዎች እንደተናገሩት ጥቃቱ የተሰነዘረው ትላንት ከምሽቱ 2፡40 እንደሆነና በጥቃቱም አውሮፕላኖች፣ የአውሮፕላን መጠለያዎች፣ ነዳጅ፣ የሎጂስቲክ መጋዝን፣ የአየር መቃወሚያ ሲስተሞች እንደወደሙ ታውቋል፡፡ ጥቃቱ ሶሪያ የኬሚካል የጦር መሳሪያዎች ዳግም እንዳትጠቀም በሚያስችል ደረጃ አውድሞታል፡፡የአሜሪካን ባለስልጣናት የአሳድ መንግስት የተከለከሉ የጦር መሳሪያ ኬሚካሎችን እንደተጠቀመ ገልጸዋል፡፡በጥቃቱ ስድስት ወታደሮች መገደላቸውንም ታውቋል፡፡በማክሰኞው የኬሚካል ጥቃት 26 ሕጻናትን ጨምሮ 86 ንጹሐን ሰዎች ህይወታቸው እንዳለፈ ይታወሳል፡፡
| 0 |
6eba8eb7ecd48634b05e0a51736e2a54
|
6eba8eb7ecd48634b05e0a51736e2a54
|
በደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች ሃያ አራት የሕክምና ጣቢያዎች ተዘረፉ
|
ደቡብ ሱዳን ውስጥ ታጣቂ ቡድኖች፣ ባለፈው ዓመት ከመንፈቅ ውስጥ ሃያ አራት የሕክምና መስጫ ጣቢያዎቻችንን ዘርፈውብናል፣ መንግሥት የተሻለ ጥበቃ ያድርግልን ሲሉ የሕክምና በጎ አድራጎት ድርጅቱ ድንበር የለሽ ሃኪሞች ዋና ኃላፊ ጠየቁ።የሜዲሳን ሳን ፍሮንቲዬ /MSF/ ዓለምቀፍ ፕሬዚዳንት ጆዋን ሊዩ፣ ደቡብ ሱዳን ያሉትን የሕክምና ጣቢያዎች ይጎበኙ ሲሆን ከሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ጋር ተወያይተዋል፡፡“የሚያሳዝነው ተፋላሚዎቹ ወገኖች፣ የሕክምና ጣቢያዎችን መጠበቅ ሲገባቸው፣ አዘውትረው አላማ ማድረጋቸው ነው” ብለዋል።
| 1 |
317de1fa472d3483e5fb4dc03f763cdf
|
6cce9abb9a740ced9bb7d62ed90cb49c
|
የተለያዩ ተቋማት በ’ገበታ ለሀገር’ ለመሳተፍ ገንዘብ ገቢ አደረጉ
|
አዲስ አበባ ፣ ህዳር 2 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለሃብቱ አቶ ወርቁ አይተነው ለጀግናው የመከላከያ ሰራዊትና ለአማራ ልዩ ሀይል 100 የስጋ በሬዎችንና 200 ኩንታል ፉርኖ ዱቄት ድጋፍ አደረጉ።ድጋፉን የባላሃብቱ ተወካይ አቶ ሲሳይ ታደሰ በጎንደር ከተማ ተገኝተው ለሎጂስቲክ ኮሚቴው አስረክበዋል።ተወካዩ ባለሃብቱ አሁን ያደረጉት ድጋፍ ጊዜያዊ እንደሆነና መንግስት የጀመረውን ህግ የማስከበር ተግባር በድል እስከሚያጠናቅቅ ድረስ በቀጣይ ድጋፋቸውን አጠናክረው ይቀጥላሉ ማለታቸውን ከማዕከላዊ ጎንደር ዞን ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።ድጋፉን የተረከቡት የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የጎንደር ቀጠና ሎጂስቲክ ኮሚቴ አስተባባሪ አቶ ባንቲሁን መኮንን በበኩላቸው የመከላከያ ሰራዊት ከክልሉ ልዩ ሃይልና የሚሊሻ አባላት ጋር በመሆን በተለያዩ ግንባሮች እየወሰደ ያለውን እርምጃ ለማገዝ ባለሃብቱ ያደረጉት ድጋፍ ከመንግስትና ከሃገር መከላከያ ሰራዊት ጎን መቆማቸውን ያሳዩበት ነው ብለዋል።በተመሳሳይ በጅማ ዞን የጌራ ወረዳ ነዋሪዎች ለሀገር መከላከያ ሰራዊት የ28 ሰንጋዎችን ድጋፍ አድርገዋል።ድጋፉን የወረዳው ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ ሃሺምና አባገዳዎች በኢፌዴሪ ምድር ሃይል ተገኝተው አስረክበዋል።በወረዳው ነዋሪዎች የተደረገውን ድጋፍ የተረከቡት የመከላከያ ህብረት ሎጂስቲክ ዋና መምሪያ ሃላፊ ሜጀር ጄኔራል አብዱራህማል እስማኤል አሎ ፤ የተደረገው ድጋፍ ለሰራዊቱ ሞራል በመሆን ግዳጁን በአጭር ጊዜ እንዲያጠናቅቅ ያስችለዋል ብለዋል።በተያያዘም የጅማ ከተማ ነዋሪዎች “የሀገር መከላከያ ሠራዊታችንን መርዳት ሀገራችንን መርዳት ነው” በሚል መሪ ቃል ለሃገር መከላከያ ሰራዊት ድጋፍ አድርገዋል፡፡ድጋፉን የከተማዋ ባለሀብቶች፣ የትራንስፖርት ማህበራት፣የታክሲ እና የባጃጅ አሽከርካሪዎች፣ የሃይማኖት ተቋማት፣ የንግድ ማህበረሰብ፣ ታዋቂ ግለሠቦች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ናቸው ያደረጉት፡፡በዚህም በጥሬ ገንዘብ 4 ሚሊየን 368 ሺህ 660 ብር እንዲሁም በቁሣቁስ ደግሞ ከ20 በላይ የጭነት አይሱዙ የተለያዩ የምግብ ግብዓቶችን አበርክተዋል፡፡ካደረጉት ድጋፍ ባለፈም በቀጣይ አራት ሚሊየን ብር ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገብተዋል፡፡
| 0 |
5e3fa8004595140ab0de6dfba91eea63
|
f5fc13bf8f1433bbb0926d2b4d1ff3c9
|
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጌዴኦ ተፈናቅለው በመጠለያ ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን ጎበኙ
|
አዲስ አበባ፣ መስከረም 9፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ጎበኙ።በኦሞ ወንዝ ላይ እየተገነባ የሚገኘው ይህ የኤሌከትሪክ ኃይል ማመንጫ ግንባታው 37 በመቶ መጠናቀቁን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አመልክተዋል።ፕሮጀክቱ በከፍተኛ ሁኔታ ተጓትቶ የቆየ እንደነበርና በቅርቡ ሥራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ነው የገለፁት።በዓመት የ6 ሺህ 400 ጊጋዋት አወርስ መጠን ያለው ኃይል እንደሚያመነጭ ይጠበቃል።እስካሁን ለ4 ሺህ ያህል ሰዎች የሥራ ዕድል ያስገኘ ሲሆን፥ ፕሮጀክቱ ግንባታው ሲቀጥል ለተጨማሪ ሰዎች ሥራን ይፈጥራል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።ግድቡ ከአዲሱ የኮይሻ ፕሮጀክት ጋር ተዳምሮ አካባቢውን ወደ ልህቀት ያደርሳልም ነው ያሉት።
| 0 |
e04777920efaac054e009ea2e84d7a4b
|
bdf24e8306739c0eb1564698d9aa5a81
|
ቱርክ በሰሜን ሶሪያ አዲስ ወታደራዊ ዘመቻ ልታካሂድ እንደምትችል ገለፀች
|
የሩሲያው ፕሬዘዳንት ቪላድሚር ፑቲን ሩሲያ በ2ኛው የአለም ጦርነት የተቀዳጀችውን የድል በአል ለማስታወስ ልታካሂድ የነበረውን ወታደራዊ ትርኢት በኮሮና ቫይረስ ምክንየት ማራዘሟን አስታውቀዋል፡፡
ፈጣን የሆነውን የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በቁጥጥር ስር ለማድረግ እየታገለች ያለችው ሩሲያ በትርኢት ልታከብር የነበረው 75ኛውን የድል በአሏን ነበር፡፡
ፕሬዘዳንት ፑቲን ምንም እንኳን የቫይረሱ ስርጭት እስካሁን ከፍተኛ ደረጃ ላይ ባይደርስም ተጋላጭነቱ ግን ከፍተኛ ነው በማለት የሀገሪቱ የደህንነት ስብሰባ ላይ ተናግረዋል፡፡
ስለዚህ ወታደራዊ ትርኢትና ብዙ ህዝብ የሚሳተፍበት ዝግጅት እንዲያደርጉ መብት እንደማይሰጣቸው ገልጸዋል፡፡
ፕሬዘዳንቱ በየአመቱ በግንቦት ወር የሚከበረው የድል በአል ለሩሲያውያን ቅዱስ ነው፤ በዚህ አመት መጨረሻ ይከበራል የሚል ቃል ገብተዋል፡፡
ሩሲያ ናዚን ያሸነፈችበት ቀን በሺዎች የሚቆጠሩ ወታደሮችና ታንኮች በሬድ ስኩየር ትርኢትያሳያሉ፤ ወታደራዊ ጄቶችም በሞስኮ ሰማይ ላይ ያንዣብባሉ፡፡
በዘንሮው በአል ላይ የሕንድ፣ የፈረንሳይ፣የኩባና የቬንዟላን ጨምሮ የ17 ሀገራት መሪዎች እንደሚገኙ ሩሲያ ባለፈው አመት ገልጻ ነበር፡፡
ፕሬዘዳንት ፑቲን የአሜሪካውን ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕን ጋብዘውም ነበር፤ነገርግን አሜሪካ የደህንነት አማካሪዋን እልካሁ ብላ ነበር፡፡
በሩሲያ እስካሁን 232 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሲሆን 27,938 ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ ተጠቅተዋል፡፡
| 0 |
1e4587cb9017b5567b571071e6f3ac71
|
099debd1037a56683b5e28d2d95e9dc9
|
የታዳሽ አረንጓዴ ልማት በኢትዮጵያ በሚል ርዕስ በሮም የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስተባባሪነት ዓለም አቀፍ ዌቢናር ተካሄደ
|
አዲስ አበባ፣ ህዳር 25፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እና የሚዲያ ሚና በቀውስ ጊዜ በሚል ርዕስ በሰላም ሚኒስቴር አመቻችነት የበይነ መረብ ውይይት ተካሄደ።ውይይቱን የከፈቱት የሰላም ሚኒሰትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል ከዓለም ዓቀፍ እና የሀገር ውስጥ የሚዲያ ባለሙያዎች ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ውይይት መካሄዱ እጅግ ጠቃሚ ነው ብለዋል።የሚዲያ ባለሙያዎች የሚዲያን ሰላም የማስፈንም ሆነ ጥፋት የማስከተል አቅም በሚገባ ተገንዝበው በተለይም በአስቸጋሪ ወቅቶች ጊዜ ኃላፊነት በተሞላበት መልኩ ትክክለኛ መረጃን የማቀበል ስራቸውን በአግባቡ መወጣታቸው ለሰላም ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አመልክተዋል።በተጨማሪም ሚኒስትሯ ለተሳታፊዎቹ በወቅታዊው የኢትዮጵያ ሰሜናዊ ክፍል ህግ የማስከበር ሂደትና ተዛማጅ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።በውይይቱ ፕሮፌሰር አን-ፊትስ ጄራለድ ከካናዳ፣ ዶክተር ጌታቸው ድንቁ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ባለስልጣን አቶ ድጋፌ ደባልቄ ከካናዳ እንዲሁም ወይዘሮ ቬነስ ናራያን ከለንደን በርዕሱ ዙሪያ ሀሳባቸውንና ልምዳቸውን ለተሳታፊዎች ማካፈላቸውን ከሰላም ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
| 0 |
2f3f099f329ec2255a39d0ce7452fb05
|
14bb71eac3c86404534eae8ebb645af7
|
የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ለማስፈጸም በተዘጋጀው ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ
|
ም/ቤቱ ባካሄደው 73ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈምክር ቤት በቅድሚያ በማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር ተዘጋጅተው በቀረቡ ከፍተኛ ደረጃ የድንጋይ ከሰል ማዕድን እና አነስተኛ ደረጃ የክሮማይት ማዕድን ማምረት ፈቃድ ስምምነቶች ላይ የተወያየ ሲሆን፤ ስምምነቶቹ በህጉ መሰረት መሟላት የሚገባቸው ጉዳዮች ከተሟሉ በኋላ እንደተዘጋጁ ተገልጿል፡፡ምክር ቤቱም በቀረቡት የከፍተኛ እና የአነስተኛ ደረጃ የማዕድን ማምረቻ ፈቃድ ስምምነቶች ላይ ከተወያየ በኋላ በስራ ላይ እንዲውሉ መወሰኑ ተመልክቷል፡፡በመቀጠልም ምክር ቤቱ በሰው የመነገድና ሰውን በህገ ወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በተዘጋጀ ረቂቅ አዋጅ ላይ ውይይት የተደረገበት ሲሆን፤ በዚህ ዙሪያ የሚደርሱ ወንጀሎች በዜጎች ላይ የከፋ ጉዳት እንዳያስከትሉ ጠቅላይ ዓቃቤ ህግ ወንጀሎቹን ለመከላከል የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ አዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ለውሳኔ አቅርቧል፡፡ምክር ቤቱም በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ በዝርዝር ከተወያየ በኋላ ማሻሻያዎችን በማዕከል ይፀድቅ ዘንድ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ ወስኗል፡፡እንዲሁም የማሪታይም ጉዳይ ባለስልጣን የተለያዩ የማሪታይም አገልግሎቶችን ለመስጠት የሚያወጣውን ወጪ ተመጣጣኝ በሆነ መልኩ የአገልግሎቱ ቀጥተኛ ተጠቃሚ የሆነው ተገልጋይ እንዲሸፍን ለማድረግ የሚያስችል የህግ መሰረት መኖሩ አስፈላጊ መሆኑን በመግለፅ፤ የገንዘብ ሚኒስቴር የአገልግሎት ክፍያውን ለመወሰን የሚያስችል ረቂቅ ደንብ አዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ ያቀረበ ሲሆን፤ ምክር ቤቱም ደንቡ ላይ ተወያይቶ በስራ ላይ እንዲውል መወሰኑን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
| 0 |
fc7686c36e2fa73605a67ef1c48d1ca8
|
0a197c22679e700e1a1e2b6d74bd00c2
|
በመንግስት ብቻ ተይዘው የነበሩ ትላልቅ ተቋማትን በሙሉ ወይም በከፊል አክሲዮን/ሽርክና የመሸጡን ተግባር ከኢትዮ-ቴሌኮም እንደሚጀምር ተገለጸ፡፡
|
በዳንሻ፣ በተርካን፣ በሁመራ፣ በሽራሮ፣ ማይጸብሪ እና ማይካድራ በከፊል የቴሌኮም አገልግሎት ጀምሯል።በአላማጣ አካባቢ ሙሉ በሙሉ የቴሌኮም አገልግሎት ጀምሯል።በተቀሩት የትግራይ አካባቢዎች የቴሌኮም አገልግሎት ለማስጀመር የተጎዱ የቴሌኮም መሰረተ ልማቶችን በመጠገን ፣ መልሶ በማቋቋም እንዲሁም መደበኛ የኃይል አቅርቦት ለማግኘት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር እየሰራ መሆኑንና አማራጭ የኃይል አቅርቦት በመጠቀም በሁሉም የክልሉ አካባቢ የቴሌኮም አገልግሎት በአጭር ጊዜ ለማስጀመር ጥረት እያደረገ መሆኑን ዛሬ አሳውቋል።
| 0 |
e6bf3c1a4f372142d6538f09b658741a
|
6af5f58e74c94f8913816b21b7043b0c
|
የአውሮፕላን ነዳጅን ጨምሮ ሌሎች የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ባለበት እንደሚቀጥል ተገለጸ
|
በመጪው የፈረንጆች አመት 2019 በአለማችን የሚገኙ አየር መንገዶች በድምሩ 885 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ያገኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅና ይህም በታሪክ ከፍተኛው ገቢ እንደሚሆን አለማቀፉ የአየር ትራንስፖርት ማህበር አያታ ማስታወቁን ፋይናንሺያል ታይምስ ዘግቧል፡፡አለማቀፉ የአየር ትራንስፖርት ማህበር አያታ ያወጣውን መረጃ ተቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ በመጪው አመት የተሸለ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴና የነዳጅ ዋጋ ቅናሽ ይኖራል ተብሎ ከመገመቱ ጋር በተያያዘ የአለማችን አየር መንገዶች አጠቃላይ ትርፍ ከአምናው በ10 በመቶ ያህል ጭማሪ በማሳየት 35.5 ቢሊዮን ዶላር ያህል ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡አለማችን አየር መንገዶች በመጪው የፈረንጆች አመት የሚያጓጉዟቸው መንገደኞች ቁጥር አምና ከነበረው በ5.6 በመቶ በማደግ 4.6 ቢሊዮን ይደርሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ ማህበሩ መግለጹንም ዘገባው አመልክቷል፡፡ በ2018 በበርሜል 73 ዶላር የሚሸጠው የአውሮፕላን ነዳጅ ዋጋ በመጪው አመት ወደ 65 ዶላር ዝቅ ይላል ተብሎ እንደሚጠበቅ የጠቆመው ዘገባው፣ የአለማችን አየር መንገዶች በአመቱ ለነዳጅ ብቻ 200 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ደርጋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም አክሎ ገልጧል፡፡
| 0 |
d2322528716d6edce35c10cc5005ae68
|
253e131424e02e688a0dd22ba0f4b624
|
ከደምስቆ ወጣ ብሎ በሚገኝ የተከበበ አካባቢ የአየር ድብደባ ተካሄደ
|
በመጪው ጥቅምት በፖላንድ ጊዲኒያ በሚደረገው የ2020ቱ ግማሽ ማራቶን ውድድር የሚሳተፉ አትሌቶች ለመለዬት ዛሬ የማጣሪያ ሩጫ በሰንዳፋ ተካሂዷል።በማጣሪያው ላይ አስር ወንድና አስር ሴት አትሌቶች መሳተፋቸውን የኢትዮጵያ አትሌቲከስ ፌዴሬሽን በማኅበራዊ ገጹ አስታውቋል፡፡በዚህ ውድድር የተካፈሉ አትሌቶች አምና በሀገር ውስጥ ከተደረገ ግማሽ ማራቶንና በኢንተርናሽናል ደረጃ ባላቸው ውጤት የተመረጡ መሆኑንም ፌዴሬሽኑ አስታውቋል፡፡መነሻውን ከበኬ ከተማ ወጣ ብሎ ፍፃሜውን ሰንዳፋ ከተማ ባደረገው የ15 ኪሜ የማጣሪያ ውድድር በሴቶች➊ኛ የለም ዘርፍ የኋላ 50:14.87❷ኛ ነፃነት ጉደታ 50:17.45❸ኛ ዘይነባ ይመር 50:29.80❹ኛ አባ በል የሻነህ 50:38.10❺ኛ መሰረት ጎላ 50:59.13❻ኛ መድህን ገ/ስላሴ 51:14.10በወንዶች➊ኛ ሀይለማርያም ኪሮስ 42:58.55❷ኛ አንዱዓምላክ በልሁ 43:02.36
| 0 |
12c281e030f6a1bcbbce897fc384226a
|
f51d99ac6dd43d9d2ab4877260e26941
|
ፕሬዚዳንት ትራምፕ ጄምስ ኮሚን ማባረራቸው “ትክክል ነው” ሲሉ ይናገራሉ
|
አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 15፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የዴሞክራቶች እጩ ፕሬዚዳንት ጆ ባይዳን የ2020 የአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫን ካሸነፉ የፕሬዚዳንት ትራምፕ አስተዳደር የጨለማ ዘመን እንዲያበቃ እሰራለሁ ሲሉ ቃል ገብተዋል።ጆ ባይዳን ላለፉት አራት ዓመታት አሜሪካን ያስተዳደሯት ዶናልድ ትራምፕ ለረጅም ጊዜ አሜሪካን በጨለማ ውስጥ እንድትቆይ አድርገዋል በማለት ወቅሰዋቸዋል።የቀድሞው የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ÷ ትራምፕ ከፍ ያለ ፍርሃት፣ ቁጣ እና መከፋፈልን ፈጥረዋልም ብለዋል።በትውልድ ከተማቸው ዊልሚግተን ባደረጉት ንግግር የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት እንድሆን እምነታችሁ ከሆነ በጎ የሆነ ነገር እንጅ ጎጂውን ተግባር አልፈፅምም ነው ያሉት።የ77 ዓመቱ እጩ ፕሬዚዳንት እየተካሄደ በሚገኘው የጠቅላላ ምርጫ ዘመቻ በተሰበሰበ የቅድመ ምርጫ ውጤት ዶናልድ ትራምፕን እየመሩ ይገኛሉ።
ሆኖም ሪፐብሊካኑ ዶናልድ ትራምፕ በቀጣዮቹ 75 ቀናት ልዩነቱን የማጥበብ እድል እንዳላቸው ቢቢሲ በዘገባው አስታውሷል።
| 0 |
d3020fa6d029d2d3460195bb69f7720e
|
d3020fa6d029d2d3460195bb69f7720e
|
የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ሰራተኞች ለገበታ ለሀገር የአንድ ወር ደመወዛቸውን ለገሱ
|
አዲስ አበባ ፣ ነሀሴ 13 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ሰራተኞች ለገበታ ለሀገር የአንድ ወር ደመወዛቸውን መለገሳቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለፁ። እያንዳንዱ የጽህፈት ቤቱ ባልደረባ አሻራውን እየተወ መሆኑን በመግለፅ እናንተም እንዲሁ እንደምታደርጉ ተስፋ አደርጋለሁ ነው ያሉት። በዛሬው ዕለት በገበታ ለሀገር ኢትዮጵያውያን የሚፈልጉትን የገንዘብ መጠን እንዲያዋጡ የተዘጋጀውን የባንክ ሂሳብም ይፋ መሆኑ የሚታወስ ነው፡፡ በዚህም የ10 ሚሊየን እና የ5 ሚሊየን ብር ገቢ ለማድረግ እንዲሁም ከሀገር ውስጥ ማንኛውም መጠን ያለውን ገንዘብ አስተዋጽዖ ለማድረግ የባንክ ሂሳብ ቁጥር፦ 1000339911267 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዲስ አበባ ቅርንጫፍ እንዲጠቀሙ ተጠይቋል። እንዲሁም ከሃገር ውጭ ለሚገኙ ወገኖች በ0100101300591 የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ መጠቀም ይችላሉ፡፡በተጨማሪም መላው ኢትዮጵያውያን የሚፈልጉትን ያህል የገንዘብ መጠን ለማዋጣት ወደ 333 አጭር የጽሑፍ መልዕክት በመላክ አሻራቸውን እንዲያሳርፉም ጥሪ ቀርቧል።።
| 1 |
7032dabb8fadc0381d9d97097f64e22f
|
17f4d480146b9bf698a42ae7ad7c2f16
|
ዋልያዎቹ በመቐለ ልምምዳቸውን ጀምረዋል
|
በ2019 የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣርያ ከጋና፣ ኬንያ እና ሴራሊዮን ጋር የተደለደለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በነገው እለት ሁለተኛ የማጣርያ ጨዋታውን ሀዋሳ ስታድየም ላይ ያከናውናል። ዋልያዎቹ ከነሀሴ ሶስት ጀምሮ በሀዋሳ ከትመው ዝግጅት ሲያደርጉ የቆዩ ሲሆን ሰኞ እለት የተጫዋቾች ቁጥር ወደ 23 ተቀንሰው ልምምዳቸውን ቀጥለዋል። በዛሬው እለትም ረፋድ 4:00 ላይ በሀዋሳ ዓለም አቀፍ ስታድየም አከናውነዋል። 32 ያህል ደቂቃዎች በፈጀው የልምምድ መርሐ ግብርም ቀለል ያሉ ከኳስ ጋር የተያያዙ ስራዎች ስርተዋል።ከማክሰኞ ጀምሮ በሀዋሳ ልምምዱን እያደረገ የሚገኘው የሴራሊዮን ብሔራዊ ቡድንም በተመሳሳይ በዛሬው እለት ሁለት ጊዜ ልምምድ ያከናወነ ሲሆን በቆሙ ኳሶች ላይ ያተኮረ ስራ ሲሰሩ ተስተውለዋል። ጨዋታውን በዋና ዳኝነት የሚመሩት ቱኒዚያዊው ሳዶክ ሴሌሚ፣ ረዳቶቹ ሊቢያዊው አቲያ አምሳድ እና ቱኒዚያዊው አይመን ኢስማይል እንዲሁም ቱኒዚያዊው አራተኛ ዳኛ ነስረላህ ጃኦዋዲ ከነገው ጨዋታ በፊት ልምምዳቸውን በሀዋሳ ዓለም አቀፍ ስታድየም 09:00 ላይ ሰርተዋል። የነገ 10 ሰዓቱ የማጣርያ ጨዋታ የሚደረግበት የሀዋሳ ዓለም አቀፍ ስታድየም የመግቢያ ዋጋዎች ይፋ የተደረጉ ሲሆን እንደየደረጃቸው 10 ብር፣ 50 ብር እና 100 ብር ይከፈልባቸዋል። በስታድየሙ የተገጠመው ስክሪን በነገው እለት አገልግሎት እንደሚሰጥም ይጠበቃል። በቀጥታ ስርጭት በኩል የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የመዝናኛ ቻነል የሚያስተላልፍ ሲሆን የደቡብ ቴሌቪዥንም ፍቃድ ካገኘ እንደሚያስተላልፈው ተነግሯል።
| 0 |
ba15ba6c7ab3a3bda129c5e101c87be4
|
d6d494b3ce738605851abc42c872416c
|
በሱማሌ ክልል በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ9 ሰዎች ህይወት አለፈ
|
አዲስ አበባ፣ ጥር 27፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በቡኖ በደሌ ዞን ዴዴሳ ወረዳ ትናንት ምሽት በደረሰ የትራፊክ አደጋ የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ።አደጋው የደረሰው የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-80032-ኢት የሆነ የጭነት ተሽከርካሪ በመገልበጡ መሆኑን የዞኑ ፖሊስ የትራፊክ ደህንነት ዲቪዥን አስተባባሪ ኢንስፔክተር በኃይሉ ገዛኸኝ ገልጸዋል።ተሽከርካሪው ሰዎችና እህል ጭኖ ከበደሌ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ እንዳለ በወረዳው መዲና ደምቢ ሲደርስ መገልበጡንም ተናግረዋል።በአደጋው ሾፌሩን ጨምሮ ተሳፍረው የነበሩ አራት ሰዎች ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን፥ የሟቾችንም አስከሬን ቤተሰቦች እንዲረከቡ መደረጉንም ጠቅሰዋል።በወቅቱ በመንገድ ላይ የነበረና በተሽከርካሪው ተገጭቶ ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰበት አንድ ታዳጊ ወጣት በወረዳው ጤና ጣቢያ የህክምና እርዳታ እየተደረገለት መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል።ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!
https://t.me/fanatelevision
| 0 |
24b0278bfb8d6a6b83f0b5af43d0d61d
|
5e4f4d2506d0ad3e873771366ac047eb
|
ከስደት ተመላሽ ዜጎችን ወደ ስራ ማስገባት ላይ ያለውን የቅንጅት ክፍተት መፍታት ይገባል ተባለ
|
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን ከመማር ማስተማር ባሻገር ለፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑ የምርምር እና የጥናት ውጤቶችን በማቅረብ የላቀ ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ የፌደራልና አርብቶ አደር ጉዳዮች ሚኒስትሩ አቶ ካሳ ተክለብርሃን ተናገሩ።የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ባለፉት 25 አመታት በትምህርት ዘርፍ በተመዘገቡ ስኬቶች እና ባጋጠሙ ችግሮች ላይ ትናንት ውይይት አድርገዋል።ሚኒስትሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት መምህራኑ የጥናት ውጤቶችን በማቅረብ የበኩላቸውን ሊወጡ ይገባል።በውይይቱ ላይ ባለፉት 25 አመታት በዘርፉ ከፍተኛ እመርታ መታየቱ ተጠቅሷል።በአሁኑ ወቅት በሃገሪቱ እንዳለ ከሚታመነው 1 መቶ ሚሊየን ህዝብ ውስጥ 30 ሚሊየን ያክሉ የትምህርት ገበታ ላይ የሚገኝ ነው ተብሏል በመድረኩ ላይ።የትምህርት ተደራሽነትን ከማስፋት አኳያ ውጤት ቢመዘገብም ጥራትን ማስጠበቅ ላይ ክፍተቶች መኖራቸውም በመድረኩ ተገልጿል።በተለይም በ1ኛ እና በ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ ጥራትን በከፍተኛ ሁኔታ ማረጋገጥ ይገባልም ነው የተባለው።የውይይቱ ተሳታፊ መምህራን በበኩላቸው ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መስፋፋታቸው መልካም መሆኑን ጠቅሰው፥ የአመራሮች ምደባ ላይ ያለው ክፍተት መስተካከል አለበት ብለዋል።ውይይቱ በነገው እለትም በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ቀጥሎ ይካሄዳል።(ኤፍቢሲ)
| 0 |
c1d94c46eefa52f39897cc80c16706ef
|
6a77adbfdce29e1a627b440c458a6db1
|
ኢትዮጵያዊ ዳኞች የቻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታ ለመምራት ወደ ሱዳን ያመራሉ
|
የአፍሪካ እግርኳስ ኮንፌድሬሽን (ካፍ) በሳምንቱ መጨረሻ በሚደረጉት የ2017 ቶታል ቻምፒየንስ ሊግ እና ኮንፌድሬሽን ዋንጫ ጨዋታዎች የሚመሩ ዳኞችን ይፋ አድርጓል፡፡ኢትዮጵያዊያን ዳኞች በቻምፒየንስ ሊግ እና ኮንፌድሬሽን ዋንጫ የአንደኛ ዙር ጨዋታዎችን እንዲመሩ ከተመረጡ አፍሪካዊያን ዳኞች መካከል ናቸው፡፡ በካፍ ቻምፒየንስ ሊግ የአንደኛ ዙር ጨዋታ ሶስ ላይ ዕሁድ የቱኒዚያው ቻምፒዮን ኤቷል ደ ሳህል ከኮትዲቯሩ አሶሴሽን ስፖርቲቭ ደ ታንዳ ጋር በስታደ ኦሎምፒክ ደ ሶስ የሚያደርጉትን ጨዋታ እንዲመራ የፊፋ ኢንተርናሽናል የመሃል ዳኛ ባምላክ ተሰማ በካፍ ተሹሟል፡፡ ባምላክ ረዳቶች የሆኑት ክንዴ ሙሴ እና ትግል ግዛው ሲሆኑ በአራተኛ ዳኛነት ዘካሪያስ ግርማ ተመርጧል፡፡ ረዳት ዳኞች ትግል እና ክንዴ ከዚህ ቀደም በቅድመ ማጣሪያ የቻምፒየንስ ሊግ ናይሮቢ ላይ የተስካር እና ኤኤስ ፖር ሉዊ 2000 ጨዋታን መምራታቸው ይታወሳል፡፡የዲ.ሪ. ኮንጎው ሳንጋ ባላንዴ ሉቡምባሺ ላይ የሱዳኑን አል ሂላል ኦባያድን የሚያስተናግድበትን የስታደ ኪባሳ ማሊባ ጨዋታ እንዲመራ ሃይለየሱስ ባዘዘው ተመርጧል፡፡ የ2007 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ኮከብ ዳኛ ሃይለየሱስ ባዘዘው በተመሳሳይ ውድድር በቅድመ ማጣሪያውን ኪጋሊ ላይ የሩዋንዳውን ራዮን ስፖርት እና የደቡብ ሱዳኑን አል ሰላም ጨዋታን መምራቱ ይታወሳል፡፡ የሃይለየሱስ ረዳቶች ሆነው የተመረጡት ተመስገን ሳሙኤል እና ክንፈ ይልማ ናቸው፡፡ በአራተኛ ዳኛነት የ2008 የፕሪምየር ሊጉ ኮከብ ዳኛ በላይ ታደሰ ሆኗል፡፡በተያያዘ ዶሊሲ ላይ በሚደረገው ኤሲ ሊዮፓርድስ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ጨዋታን እንዲመሩ ኮትዲቯራዊያን ዳኞች ተሹመዋል፡፡ የመሃል ዳኛ ጃን ጃክዌስ ንጋምቦ እና ረዳቶቻቸው ኦሊቨር ካቤኔ እና ባባካ ማምፓሲ ጨዋታን ይመራሉ፡፡ አዲስ አበባ ላይ የሚደረገው የመልስ ጨዋታ ሶማሊያዊያን ዳኞች የሆኑት ሃሰን መሃመድ ሃጊ እና ረዳቶቻቸው አህመድ ፋራህ እና አብዱላሂ አዊስ ሆነዋል፡፡
| 0 |
2885deb6f0c188ca3971e902c91bda5e
|
016cf55cdcd7c191ce894cf8f2ca051a
|
የኦሮምያ ብልፅግና ፓርቲ ውሳኔዎች
|
በአማራ ክልል በባህርዳር ከተማ “የሰማዕታት ኃውልት” ተብሎ በሚጠራው ግቢ ውስጥ “የክልሉንሕዝብ የማይወክልና ማንነቱን የማይገልፅ ነው” ተብሎ የታመነበት ኃውልት በአማራ ክልል ከፍተኛ አመራር እንዲወገድ በመወሰኑ ባለፈው ቅዳሜ ማስወገዱን የአማራ ክልል የብልፅግና ፓርቲ ገልጿል።ሌሎችንም ስያሜዎችንና ምልክቶችን የመቀየር እንቅስቃሴ መጀመሩን የባህርዳር ከተማ አስተዳደርአስታውቋል።የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ በለውጡ ለህዝብ ከገባቸው ቃሎች መካከል “የተሳሳቱ ታሪኮችናትርክቶችን ማረም” የሚል ይገኝበታል። በዚህም መሠረት በዚህ ሣምንት በአማራ ክልል በባህርዳር ከተማ የክልሉን ህዝብ የማይወክልና የማይገልፅ ነው ተብሎ የታመነበትን ስያሜዎችንና ምልክቶችንየመቀየር እንቅስቃሴ መጀመሩን የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ የሰው ህይልና ፋይናንስ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ጌትነትአይቼው ገልፀዋል።(ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)
| 0 |
daa4323d81dd43747519ea5c7b1e82b4
|
a23dd39c5debc303c2c601bfc7edc8cd
|
ሁለት ተጨማሪ ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተገለጸ
|
አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 19 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ከተያዙ16 ሰዎች ውስጥ አንዱ ሙሉ በሙሉ ማገገሙን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ።ዶክተር ሊያ ጉዳዩን አስመልክተው በፌስቡክ ገጸቸው ባወጡት መረጃ፥ በአሁኑ ወቅት በለይቶ ማቆያ ያሉ አጠቃላይ ሰዎች13 መሆናቸውን ገልጸዋል።ከታማሚዎች ውስጥ አንዱ ሙሉ በሙሉ ከቫይረሱ ማገገሙን የገለጹት ሚኒስትሯ፥በጽኑ የታመመ ሰው አለመኖሩን አስታውቀዋል።በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ከተያዙ 16 ሰዎች ውስጥ ሁለት ጃፓናውያን ወደ ሀገራቸው መመለሳቸው ይታወቃል።
| 0 |
89d18a03096e0f7cef8a4d14b82558e6
|
231dcf4e5f65311a0e32e335efdd7652
|
የምሥራቅ አፍሪካ ድርቅ የምግቦች ዋጋ እንዲያሻቅብ አድርጓል
|
-ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የቀጠናው አገራትን ድርቅ ከመቋቋም ባለፈ የተቀናጀ የውኃ ሃብት ልማት አጠቃቀም ስርዓት እንዲኖርም አስተዋጽኦው የላቀ እንደሚሆን የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግስታት /ኢጋድ/ አባል አገራት የውሃ ሃብት ምሁራን ተናገሩ።በሱዳን ካርቱም ዩኒቨርሲቲ የደንና ውሃ ሃብት ልማት ምሁር ፕሮፌሰር አልኑር አብደላ ግድቡ በአህጉሪቱ ድርቅን ለመከላከል ድርሻው የላቀ በመሆኑ ፕሮጀክቱ ከስኬት እንዲደርስ እያንዳንዱ ባለድርሻ አካል የድርሻውን ሊወጡ ይገባል።በተለይም በምስራቅ አፍሪካ በተደጋጋሚ የሚከሰተውን ድርቅ ለመቋቋም አስተዋጽኦው የጎላ ይሆናልም ብለዋል፡፡ግድቡ ወደ ወሳኝ ምዕራፍ ለማሸጋገር እያንዳንዱ የአህጉሪቱ ማህበረሰብ የፕሮጀክቱ አካል መሆን አለበት ያሉት ፕሮፌሰር አልኑር፥ አንዳንድ ማህበረሰቦች ስለ ግድቡ ያላቸው የተሳሳተ አመለካከት ለመቀየር የውሃ ሃብት ምሁራን ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።የኢጋድ አባል አገራት የውኃ ሃብት ዕቅድና ቁጥጥር ኮሚሽነርና የዩጋንዳ የውሃ ሃብት አጠቃቀም ልማት ዳይሬክተር ዶክተር ካሊስት ትንዲሙጋያ በበኩላቸው የግድቡ መሰራት ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለቀጠናው አገራትም የውሃ ሃብታቸውን ሙሉ በሙሉ በመጠቀም የኢኮኖሚ እድገታቸውን የሚያረጋገጥ ነው ብለዋል፡፡የቀጠናው አገራት በተለይም ኬንያና ዩጋንዳ ከኢትዮጵያ ኃይል ለመውሰድ የታላቁ ህዳሴ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ግድብን እየተጠባበቁ እንደሚገኙም ገልጸዋል።ፕሮጀክቱ በአህጉሪቱ ኢኮኖሚዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ትስስር ከመፍጠሩ ባለፈ የተቀናጀ የውሃ ሃብት ልማት እንዲኖር በማድረግ ድርቅን ለመከላከል አስተዋጽኦው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል።የውኃና መሬት ልማት ማዕከል ምክትል ዳይሬክተርና የኢትዮጵያ ውሃ አጋርነት ዋና ፀሓፊ ዶክተር አጠና አላምረውም የህዳሴው ግድብ ስራው ሲጠናቀቅ በሚፈጥረው ሰው ሰራሽ ሃይቅ ለአሳ ሃብት ዕድገት ወሳኝ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።የታችኛው የተፋሰሰ አገራት ግድቡ አገራቱ በደለል እንዳይሞሉ የሚያደርግ መሆኑንም አስገንዝበዋል።በአሁኑ ወቅት የታላቁ ህዳሴ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ 46 በመቶ ተጠናቋል።(ኢዜአ)
| 0 |
960ecd4ffa16adf795af6ab873c81305
|
281da497b6a66d8c42d6e4b9efa9d6a1
|
የትምህርት ተቋማት የአካዳሚ ቴክኒክ ረዳቶችን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች የሚቀርፍ መመሪያ እየተዘጋጀ ነው
|
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) መንግስት ያስቀመጠውን የክፍያ መመሪያ ለተላለፉ 21 የግል ትምህርት ቤቶች የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ መስጠቱን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ስልጠና ጥራት ሙያ ብቃትና ምዘና ማረጋገጫ ባለስልጣን አስታወቀ።የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ሸዊት ሻንካ በሰጡት መግለጫ፥ የኮረና ቫይረስ ወረርሽኝን ተከትሎ ከመጋቢት 7 2012 ዓ.ም ጀምሮ በሀገር አፍ ደረጃ ትምህርት መዘጋቱን አስታውሰው፤ የግል ትምህርት ቤቶች በትምህርት ሚኒስተር ውሳኔ መሰረት ክፍያ እንዲቀበሉ መደረጉን ገልፀዋል።የትምህርት ሚኒስቴር የግል ትምህርት ቤቶች ለትምህርት አገልግሎቱ የሚያስከፍሉት ክፍያ ከ50 እስከ 75 በመቶ እንዲሆን በተወሰነው መሰረት አብዛኞቹ ትምህርት ቤቶች ይህንኑ ተግባራዊ በማድረግ ላይ መሆናቸውንም አስታውቀዋል።ይሁን እንጂ በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ እውቅና ካገኙ 1 ሺህ 580 ትምህርት ቤቶች መካከል 21 የሚሆኑት ህብረተሰቡን ሙሉ ክፍያ በመጠየቅ ላይ መሆናቸው በመረጋገጡ በአንድ ሳምንት ውስጥ ማስተካከያ እንዲያደርጉ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው አስገንዝበዋል።እነዚህ21 ትምህርት ቤቶች በተሰጣቸው ማስጠንቀቂያ መሰረት ከመንግስት የወረደውን መመሪያ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው አሳስበው ይህንን በማይተገብሩ ትምህርት ቤቶች ላይ ፍቃድ እስከ መሰረዝ የሚደርስ እርምጃ እንደሚወሰድም ነው የገለጹት።ወይዘሮ ሸዊት አክለውም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በስድሰት ክፍለ ከተሞች በሚገኙ 36 ትምህርት ቤቶች ዳሰሳ ከማድረጉ ባሻገር በሁሉም ክፍለ ከተሞች ቁጥጥር የሚያደርግ ቡድን አዋቅሮ በመንቀሳቀስ ላይ መሆኑንም አስታውቀዋል።ወላጆች ልጆቻቸው ትምህርት ቤቶቹ ቴሌግራምን ጨምሮ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች የሚሰጡትን ትምህርትም ሆነ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አማካይነት በተለያዩ የትምህርት መስጫ መንገዶች የሚተላለፉ ትምህርቶችን በአግባቡ እንዲከታተሉ ማድረግ እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል።
| 0 |
bc2baac60bbe031a1628ac96e4ac6d92
|
edf57f0ff7a832a1e066fa1c3270ca21
|
ምክትል ጠ/ሚ ደመቀ መኮንን ከአውሮፓ ህብረት የውጭ ጉዳይ እና የፀጥታ ፖሊሲ ከፍተኛ ተወካይ ጋር ተወያዩ
|
አዲስ አበባ፣ ህዳር 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከኡጋንዳው ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ ጋር ተወያዩ።በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ የቀጠናው ሀገራት መንግስት የጀመረውን ህግና ህገ መንግስት የማጽናት ጥረት እንዲደግፉ የጠቅላይ ሚንስትሩን መልዕክት ለፕሬዚዳንቱ አድርሰዋል።ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ ጋር በነበራቸው ቆይታም በትግራይ እየተካሄደ ባለው ህግ የማስከበር ዘመቻ ዙሪያ ገለፃ አድርገዋል።ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ በዚሁ ወቅት፥ ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አህጉር ቅኝ ያልተገዛች ሀገር መሆኗን በማስታወስ፤ ይህም ለምስራቅ አፍሪካ ቀጠና ኩራት መሆኑን ጠቅሰዋል።የሀገሪቷ ሰላም ለቀጠናው ወሳኝ መሆኑን ፕሬዚደንቱ ተናግረዋል፡፡በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ ከስድስት በላይ በሚሆኑ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ጉብኝት በማድረግ ላይ ይገኛል።ይህ በእንዲህ እንዳለ ዩጋንዳ ለማሸማገል እንዳሰበችና ለዚሁ ሲባል የልዑካን ቡድን እንደሚጓዝ የሚያትትና በኢትዮጵያም ሆነ በዩጋንዳ ያልተሰበና ተቀባይነት የሌለው የሐሰት መረጃ በፅንፈኛው ቡድን ተፈብርኮ በአንዳንድ የመገናኛ ብዙሃን በመሰራጨት ላይ እንዳለ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማስታወቁ አይዘነጋም።
| 0 |
6cb643583ea9d2f850e766846453e44f
|
300c5598235cfd3b92fbc19758cbc823
|
ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የዓለም ኢኮኖሚ ፎረም ለአፍሪካ ላይ ለመሳተፍ ደቡብ አፍሪካ ገቡ
|
የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ በፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎዛ በዓለ ሲመት ላይ ለመገኘት ወደ ደቡብ አፍሪካ አቀኑ፡፡ደቡብ አፍሪካ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ የተመረጡትን ስድስተኛውን መሪዋን የፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎዛን በዐለ ሲመት በነገው ዕለት ታከብራለች፡፡በዚሁ ስነስርዐት ላይ ለመሳተፍ ፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ዛሬ ከቀትር በኋላ ወደ ደቡብ አፍሪካ ማቅናታቸው ከፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡የበዐለ ሲመቱ ስነስርዐት በፕሪቶሪያ በሚገኘው ሎፍተስ ቨርስፊልድ ስታዲየም የሚከናወን ሲሆን፣ የሀገራትና የመንግስታት መሪዎች፣ የአለም አቀፍ ድርጅት ተወካዮች እንዲሁም በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ደቡብ አፍሪካውያን እንደሚሳተፉ ይጠበቃል፡፡ከሁለት ሳምንት በፊት በሀገሪቱ በተካሄደው አጠቃላይ ምርጫ የአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስ ማሸነፉን ተከትሎ ከትናንት በስቲያ የሀገሪቱ ፓርላማ ሲሪል ራማፎዛን በፕሬዝዳንትነት መሰየሙ ይታወሳል፡፡
| 0 |
08dd567a7a374116d143174677c1ffe2
|
c0724748c96ecb4fa5c86fe4c58f0524
|
መቐለ ከተማ 5ኛ ተጫዋቹን አስፈርሟል
|
መቐለ ከተማ የሶስት ተጫዋቾችን ዝውውር ማጠናቀቁ ታውቋል። ዮናስ ገረመው፣ ሳሙኤል ሳሊሶ እና ቢያድግልኝ ኤልያስ ለክለቡ የፈረሙ ተጫዋቾች ናቸው።የቀድሞው የብሔራዊ ቡድን ተከላካይ ቢያድግልኝ ኤልያስ በ2005 ከሲዳማ ቡና ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ካመራ በኋላ በፈረሰኞቹ ቤት ለ4 የውድድር ዘመን ቆይቶ ወደ አርባምንጭ በማቅናት የግማሽ ዓመት ቆይታ ካደረገ በኋላ ወደ ጅማ አባ ቡና ቀጥሎም የተጠናቀቀውን የውድድር ዓመት ባሳለፈበት ወልዲያ ተጫውቷል። ተጫዋቹ በመቐለ የፍቃዱ ደነቀ እና አሌክስ ተሰማን ጥምረት ሰብሮ የመሰለፍ ፈተና ይጠብቀዋል።ከጅማ አባ ጅፋር ጋር ድንቅ የውድድር ዓመት ያሳለፈውና ከክለቡ ጋር ቻምፒዮን የሆነው ዮናስ ገረመው ወደ መቐለ ከተማ የተዛወረ ሌላው ተጫዋች ነው። ዮናስ ሀላባ ከተማን ለቆ በ2006 ኢትዮጵያ ቡና ካመራ በኋላ በ2008 በድሬዳዋ ከተማ፣ በ2009 በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቆይታ አድርጓል። በጅማም ከአንድ ዓመት በላይ ሳይዘልቅ ወደ መቐለ አምርቷል። በውድድር ዓመቱ በፈጣሪ አማካይ እጦት የተቸገረው መቐለ ከተጫዋቹ ፊርማ ተጠቃሚ እንደሚሆን ይጠበቃል።ሳሙኤል ሳሊሶ ሌላው የመቐለ ፈራሚ ነው። በመሀል አማካይ እና የመስመር አጥቂነት መጫወት የሚችለው ሳሙኤል ሼር ኢትዮጵያን ለቆ ወደ መከላከያ ካመራበት 2007 ጀምሮ ያለፉትን 4 የውድድር ዘመናትን በጦሩ ቤት የቆየ ሲሆን በመቐለ ከቀድሞ አሰልጣኙ ገብረመድህን ኃይሌ ጋር የመገናኘት እድል አግኝቷል።መቐለ ከተጠቀሱት ተጫዋቾች በተጨማሪ ጋብሬል አህመድን ባለፈው ሳምንት ማስፈረሙ የሚታወስ ነው።
| 0 |
7546e750a0005921382e504b5c74e831
|
7546e750a0005921382e504b5c74e831
|
የደቡብ ሱዳን የኢኮኖሚ ቀውስ
|
የደቡብ ሱዳን ፓውንድ የዶላር ምንዛሬ ማሽቆልቆሉን እንዳይቀጥል ለመከላከል በውጭ ገንዘብ መገበያየት ብሔራዊ ባንኩ ለማገድ ማቀዱ ተሰማበቅርብ ሳምንታት እና ወራት በሀገሪቱ የምግብና ሌላም መሰረታዊ አቅርቦቶች ዋጋ በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን ተከትሎ ነውየደቡብ ሱዳን ብሄራዊ ሸንጎ የንግድ ዘርፍ ኮሚቴ የብሔራዊ ባንክ ገዥውን የገንዘብ ሚኒስትሩንና ሊሎችም የሚመለከታቸው ባለስልጣናት ጠርቶ በጉዳዩ ላይ እንዳነጋገረ ተገልጿልለዋጋ መናሩ ምክንያቱ የዓለም የነዳጅ ዋጋ መቀነስ እና በሀገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች ያለው ግጭት መሆኑን ነው የብሄራዊ ባንክ ገዥው የተናገሩት
| 1 |
f940c0f4aea73b3666c3e6e15ef4ea77
|
f01bf793a455ebea21ad874e51ddf911
|
ኢትዮጵያ መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገራት ተርታ ለመሰለፍ ለኢንዱስትሪ ትኩረት መስጠት እንዳለባት ተገለጸ
|
መጋቢት 1 ቀን 2007 ዓ.ም. ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው የኢንዱስትሪ ፓርኮች ረቂቅ አዋጅ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ቢኖረውም፣ ከሕገ መንግሥቱ ድንጋጌዎች ጋር የሚቃረኑ አንቀጾችን የያዘ በመሆኑ እንዲስተካከል የፓርላማ አባላት ጠየቁ፡፡የቀረበው ረቂቅ አዋጅ አገሪቱ የቀረፀቻቸውን ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች መሠረት በማድረግ ከ40 እስከ 50 ዓመታት ባሉት ጊዜያት ውስጥ በኢንዱስትሪ የዳበረችና ዜጎቿም ከፍተኛ ገቢ ያላቸው እንዲሆኑ እንዲሁም፣ እስከ 2017 ዓ.ም. ባለው የስትራቴጂው ምዕራፍ አገሪቱ ከድህነት ተላቃ መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገሮች ጎራ መቀላቀል እንድትችል ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ተገልጿል፡፡ረቂቅ አዋጁ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች እንዲከናወን የሚፈቅድ ነው፡፡ የኢንዱስትሪ ፓርኮች በመሬት አጠቃቀም ላይ የሚታየውን የኪራይ ሰብሳቢነት አደጋ ለማስቀረት፣ የሎጂስቲክስና የጉምሩክ አገልግሎት ችግሮችን ለማስወገድ፣ መሠረት ልማቶችን በማሟላት የአገር ውስጥና የውጭ ባለሀብቶች በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ያለብዙ ውጣ ውረድ እንዲሳተፉና በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ምርትና ኤክስፖርት ተግባር እንዲሸጋገሩ የሚያስችል መሆኑን የአዋጁ መግቢያ ይገልጻል፡፡የረቂቅ አዋጁ ክፍል አንድ አንቀጽ ሁለት ንፁስ አንቀጽ ሦስት ለመሬት የሚሰጠው ትርጓሜ አግባብነት ላይ የፓርላማ አባላት ጥያቄያቸውን አንስተዋል፡፡ ‹‹መሬት ማለት ለኢንዱስትሪ ፓርክ ልማት ዓላማ የተሰየመ ማንኛውም መሬት ነው፤›› ይላል፡፡የምክር ቤቱ የመከላከያና የውጭ ደኅንነት ጉዳዮች ቋሚ ኮሜቲ ሰብሳቢ አቶ ተሰፋዬ ዳባ በረቂቁ ላይ የተቀመጠው ድንጋጌ፣ ሕገ መንግሥቱ ለክልሎች የሰጠውን መሬት የማስተዳዳር መብት ጋር የሚጣረስ መሆኑን በመጠቆም ማስተካከል እንደሚገባው ጠቁመዋል፡፡የረቂቅ አዋጁ ድንጋጌዎች የኢንዱስትሪ ፓርኮች የሚሰየሙት በፌዴራል መንግሥት መሆኑንና ፓርኮቹ ደግሞ በኢትዮጵያ ግዛት ወሰን ውስጥ የሚፈጸም በመሆኑ፣ የክልሎችን መሬት የማስተዳደር መብት ይጋፋል ብለዋል፡፡የተነሳው ጥያቄና ሌሎች የረቂቁን አንቀጾች በዝርዝር በመመልከት የውሳኔ ሐሳብ ይዞ እንዲቀርብ፣ ለኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ረቂቅ አዋጁ ተመርቷል፡፡
| 0 |
3b427905912c526cb1fc1ab54089bb1f
|
c746e3acd0e86033bae5c5d5b90ed3b4
|
ሕመምተኛ መስለው ሕዝብ በማታለል 350 ሺሕ ብር ሰብስበዋል የተባሉ ተከሰሱ
|
በአየር መንገድ የደንበኞች አገልግሎት ሱፐርቫይዘር መሆኑ የተገለጸው አቶ ሀብታሙ አሻግሬ የውጭ ዜጎችን በሕገወጥ መንገድ በመላክ ክስ ተመሠረተበት፡፡ ደሳለኝ አስመላሽ፣ ሜሮን ተሾመ፣ ቢንያም መኮንን፣ ዳንኤል መሓሪና ሩታ ደበሳይ የተባሉ ኤርትራውያንና አንድ ናይጄሪያዊ በሐሰተኛ ሰነድ ካናዳ እንዲሄዱ በማድረጉ መሆኑን ክሱ ያስረዳል፡፡የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ዓቃቤ ሕግ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ችሎት ያቀረበው ክስ እንደሚያስረዳው፣ ተከሳሹ ሥራው የፈጠረለትን አጋጣሚ በመጠቀም ተጓዦቹ አሟልተው መቅረብ የነበረባቸውን የጉዞ ሰነድ ሳያሟሉ እንዲያልፉ አድርጓል፡፡አውሮፕላን ላይ መሳፈር የሚያስችላቸውን የይለፍ ወረቀት (Boarding Pass) ይዘው መቅረብ የነበረባቸው ስድስቱ ሰዎች አለመያዛቸውን ሲገልጹለት፣ 23,000 ብር በመቀበል የሌላ የአየር መንገድ ሠራተኛ የይለፍ ቃል (ፓስወርድ) በመጠቀም፣ የተጓዦቹን ስም በቦርዲንግ ፓስ ላይ በመሙላት እንዲያልፉ ማድረጉን ክሱ ይገልጻል፡፡ተጓዦቹ በተሰጣቸው ሕገወጥ የይለፍ ወረቀት ሕጋዊ ተጓዦች መስለው በመሳፈር ወደ ካናዳ መጓዛቸውንም ክሱ ይገልጻል፡፡ ስድስቱም ተጓዦች ካናዳ እንደገቡ በሕገወጥ መንገድና ሰነድ መጓዛቸው በመረጋገጡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በእያንዳንዳቸው ተጓዦች 3,200 ዶላር በድምሩ 19,200 ዶላር እንዲቀጣ ማድረጉ ተገልጿል፡፡ ተከሳሹ በፈጸመው ሥልጣንን ያላግባብ መጠቀምና በመንግሥት ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ ሙስናና ወንጀል መክሰሱን የኮሚሽኑ ክስ ያብራራል፡፡
| 0 |
c896241a5c1a8052c331d6ee07c07021
|
1d3e08e05c5547c8caca16d367edb1a1
|
በሳውዲ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው የሚመለሱበት ለአንድ ወር መራዘሙን ሚኒስቴሩ አስታወቀ
|
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 19፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)189 ኢትዮጵያውያን ዛሬ ከቤሩት ወደ አገራቸው ተመለሱ፡፡ዛሬ ከቤሩት ወደ ሃገራቸው የተመለሱት 189 ኢትዮጵያውያን ሰነድ አላባ መሆናቸው ታውቋል፡፡ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ ሰነድ አልባ ዜጎችን ወደ አገራቸው የመመለሱ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ከቤሩት የኢትየጵያ ቆንስላ ጄኔራል ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል ፡፡
| 0 |
603f941a1b0cab1da992c858f13d9493
|
56b0db158715e62aa98c309af434d366
|
ጋዜጠኛ ፍቅሩ ወልዱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ
|
የ ‹‹ኮፒ፣ ከት እና ፔስት›› ፈጣሪ እንዲሁም የኮምፒውተር ተመራማሪ የነበረው ላሪ ቴስለር በ74 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፡፡ቴስለር በግኝቱ ኮምፒውተርን በቀላሉ ለመጠቀም የሚያስችሉትን እንደ ‹‹ኮፒ፣ ከት እና ፔስት››ን በመፍጠር ብዙዎች ኮምፒውተርን በቀላሉ ለመጠቅም እንዲቻላቸው አድርጓል፡፡የኮምፒውትር ተመራማሪው ‹‹በከት እና ፔስት ›› ፈጣሪነቱ ይታወቅ እንጂ በርካታ የፈጠራ ባለቤት እንደሆነም ይነገርለታል፡፡ላሪ ቴስለር በ1945 በኒዎክር የተወለደ ሲሆን ከኮምፒውተር ጋር የተያያዘው ስራውን የጀመረው በ1960ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ በሲሊከን ቫሊ ኩባንያ ነበር፡፡የቴስለርን ሕልፈተ ሕይወት የሰሙ የቀድሞ ባልደረቦቹም ኮምፒውተርን ለመጠም ቀላል ስላደረክልን እና ስለ ሰራኸው ስራ እናመስግንሃለን ብለውታል፡፡ተመራማሪው ቴስለር ከሰራባቸው የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች መካከል አፕል፣ አማዞን፣ ያሆ እና ሌሎችም ተጠቃሾች ናቸው፡፡
| 0 |
8ab793604e94743fc2e706994ccd2d39
|
8ab793604e94743fc2e706994ccd2d39
|
11 ሺህ 902 የቡራዩ ተፈናቃዮች ወደ መኖሪያ ቀያቸው ተመለሱ
|
ከቡራዩ ተፈናቅለው ከነበሩት 15 ሺህ 86 ዜጎች መካከል በተፈጠረው መረጋጋት 11 ሺህ 902 የሚሆኑት ወደ መኖሪያ ቀያቸው መመለሳቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።በአዲስ አበባ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን ቡራዩ ከተማ በተፈጠረው መረጋጋት በአስተዳደሩ አማካኝነት 11 ሺህ 902 ያህል ተመልሰዋል፡፡በመሆኑም በአዲስ አበባ በአሁን ወቅት በመጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙት 1 ሺህ 514 መሆናቸው ተገልጿል።የከተማዋ አስተዳደር ላለፉት ስምንት ቀናት ተፈናቃዮች በጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያነት የቆዩባቸውን ዘጠኝ ትምህርት ቤቶች በትላንትናው እለት ጽዱ በማድረግና በዛሬው ዕለት ለሚጀምረው የመማር ማስተማር ዝግጁ ተደርጓል ተብሏል።በስድስቱ ክፍለ ከተሞች ከነበሩት 20 ጊዜያዊ የመጠለያ ጣቢያዎች መካከል 17ቱ ተዘግተው ቀሪዎቹ ተፈናቃዮች በሶስት የመጠለያ ጣቢያዎች ይገኛሉ ተብሏል።በቀሪዎቹ ሶስቱ መጠለያ ጣቢያዎቹ ለተፈናቃዮቹ ሁሉን አቀፍ አገልግሎትና መረጃ የሚሰጥ የጣቢያ ኮሚቴ የተቋቋመ ሲሆን፥ አስፈላጊውን አገልገሎት በቅርበት መስጠቱን እንደሚቀጥል ተገልጿል።የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ለተፈናቃዮቹ ባለፉት ቀናት ሲያደርጉት ለቆዩት ድጋፍ የከተማ አስተዳደሩ ምስጋና አቅርቧል። (ኤፍ.ቢ.ሲ)
| 1 |
0d5d8210c5b7e516a92f2e84c3a31cfd
|
acb25a9bf187b77535501e3bb53c3c78
|
አሜሪካ በኢራን ይደገፋሉ ባለቻቸው ታጣቂወች ላይ አፀፋዊ እርምጃ ወሰደች
|
አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 9 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት አሜሪካ በኢራን ላይ የተጣለው የጦር መሳሪያ እገዳ እንዲራዘም ያቀረበችውን የውሳኔ ሃሳብ ውድቅ አደረገ፡፡ምክር ቤቱ ሌሊቱን ባደረገው ስብሰባ ዋሽንግተን በቴህራን ላይ ላለፉት 13 አመታት የተጣለው የጦር መሳሪያ እገዳ ይራዘም በሚል ያቀረበችውን ሃሳብ ውድቅ አድርጎታል፡፡ዶሚኒካን ሪፐብሊክ ብቸኛዋ የአሜሪካን የውሳኔ ሃሳብ የደገፈች ሃገር ሆናለች፡፡በአንጻሩ ሩሲያ እና ቻይና የውሳኔ ሃሳቡን በመኮነን ተቃውመውታል፡፡ብሪታንያ፣ ጀርመን እና ፈረንሳይን ጨምሮ 11 ሃገራት ደግሞ ድምጸ ተአቅቦ አድርገዋል፡፡የውሳኔ ሃሳቡ ተግባራዊ ይደረግ ዘንድ ከ15ቱ የምክር ቤቱ አባላት የዘጠኙ ይሁንታ ያስፈልገው ነበር፡፡ምንጭ፣ አልጀዚራ
| 0 |
290b7b336e68f79e934196f0590f1db1
|
fd1f198e33d96b832436d17bf6307965
|
ኢራን ዩራኒየም ማበልጸግን አጠናክራ መቀጠሏ ተገለጸ
|
ባለፈው ረቡዕ ከተነሳ ብዙም ሳይቆይ ተከስክሶ የ176 ሰዎችን ህይወት በቀጠፈው የአይሮፕላን አደጋ የኢራን እጅ አለበት የሚለውን ክስ ኢራን እንደማትቀበለው አስታውቃለች፡፡
የአደጋውን መንስኤም አሜሪካ እንድታጣራ ኢራን ጥሪ አቅርባለች፡፡ ሮይተርስ እንደዘገበው ጥሪው የደረሰው የአሜሪካው የትራንስፖርት ደህንነት ቦርድ ጥያቄውን ተቀብሎ አጣሪ ቡድን እንደሚመድብ አሳውቋል፡፡
የተለያዩ ሀገራት ኢራን በተኮሰችው ሚሳይል አይሮፕላኑ ተመቶ ሳይወድቅ እንዳልቀረ ግምታቸውን የገለጹ ሲሆን የአሜሪካ መገናኛ ብዙሃንም ከደህንነት ተቋማት ያገኘነው መረጃ አይሮፕላኑ ተመቶ መውደቁን ያሳያል ብለው በሰፊው ዘግበዋል፡፡
በዛሬው እለት ደግሞ አይሮፕላኑ ሲመታ ያሳያሉ የተባሉ የቪዲዮ ማስረጃዎችም ተለቀዋል፡፡
ይሁንና የሚወጡ መረጃዎች ሁሉ በኢራን ላይ የተከፈቱ የስነልቦና ጦርነቶች ናቸው እንጂ እውነት አይደሉም በሚል ኢራን አስተባብላለች፡፡ በአደጋው ህይወታቸውን ያጡ ዜጎች ያሏቸው ሀገራትም ተወካዮቻቸውን ልከው ከቦይንግ ጋር በጋራ የጥቁር ሳጥኑን መረጃ እንዲመረምሩ ጥሪ አቅርባለች፡፡
የኢራን ሲቪል አቪዬሽን ተቋም አውሮፕላኑ ከመነሳቱ ከሁለት ቀናት በፊት ፍተሻ የተደረገለት ቢሆንም የቴክኒክ ችግር ስለገጠመው ተከስክሷል ብሏል፡፡
ምንጭ፡- ሮይተርስ
| 0 |
d32432d623180a3ed34c50b1607ee461
|
77cdc91e35c907e7ac6ed549f79bca43
|
ብዙዎች የታገሉለት ዓላማ በጥቂቶች መጠለፉን የፈንቅል አመራር ገለጹ
|
የሶማሌ ክልላዊ መንግስት በክልሉ ሰላምና ፀጥታ እንዲረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ በመሥራቱ ውጤት እየተመዘገበ መምጣቱን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ገለጹ።የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሃመድ የመንግስታቸውን የአምስት ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ለክልሉ ምክር ቤት አቀርበዋል።በሪፖርታቸውም አዲሱ የክልሉ አመራር ሥራ ከጀመረ ወዲህ በክልሉ ሲስተዋል የነበረው ብጥብጥ፣ ረብሻና አለመረጋጋት በሙሉ እንዲወገድ መስራቱን አመልክተዋል።በክልሉ ሊከሰቱ የነበሩ ሰላሳ የጎሳ ግጭቶች በውይይት እንዲፈቱ በመደረጉ በአሁኑ ወቅት በክልሉ ውስጥ መረጋጋት እየታየ መምጣቱን ተናግረዋል።የመንግስታዊ መዋቀሩን እስከታች ድረስ በማጠናከር በቀድሞ የክልሉ መንግስት መስተዳድር በህዝብ ሀብት ላይ ዝርፊያ ፈጽመዋል ተብለው የተጠረጠሩ የ1 መቶ ግለሰቦች የባንክ ሒሳብ ቁጥር መዘጋቱንም አንስተዋል።በተጨማሪም 117 ግለሰቦች እና ሰባት ድርጅቶች ደግሞ በምርመራ ሂደት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል ።በርዕሰ መስተዳድሩ በቀረበው የአምስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤቱ አባላት ጥያቄዎችና እና አስተያየቶች ተነስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል።(ኢዜአ)
| 0 |
daeda52a11ce4d7c7ab8adea1eb0d956
|
2cef70812db9f7784cff92a3263f5c07
|
የግብርና ሚኒስቴር የመኸር ምርት እንዳይባክን እየሠራሁ ነው አለ
|
ለ2011/ 2012 የመኸር እርሻ የሚያስፈልገው የማዳበሪያ አቅርቦት ከውጭ ተገዝቶ እየተጓጓዘ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።ለምርት ዘመኑ ከአንድ ሚሊዮን 160 ሺ በላይ ኩንታል የዘር ፍላጎት መቅረቡንም ገልጿል፡፡ በሚኒስቴሩ የግብርና ግብዓት ግብይት ዳይሬክቶሬት በግዢ የሚቀርቡ የግብርና ግብዓቶች ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ዘውዱ ስሜ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደተናገሩት፣ በ2011/12 የምርት ዘመን
አንድ ሚሊዮን 613 ሺ 246 ሜትሪክ ቶን
ማዳበሪያ ይሰራጫል ተብሎ ይጠበቃል።በአሁኑ ወቅትም አንድ ሚሊዮን 278 ሺ 982 ሜትሪክ ቶን
ከውጭ ለማስገባት እቅድ ተይዞ እስካሁን አንድ ሚሊዮን 175 ሺ ሜትሪክ ቶን
የማዳበሪያ ግዢ ተከናውኗል፡፡ በቅርቡ ተጨማሪ ግዢ ለማከናወን ጥያቄ መቅረቡን ባለሙያው ጠቅሰው፣ በአሁኑ ወቅት 100 ሺ ሜትሪክ ቶን
የማዳበሪያ ግዢ መታዘዙን አስታውቀዋል፡፡ ባጠቃላይም እስካሁን አንድ ሚሊዮን 27 ሺ 847 ሜትሪክ ቶን
ማዳበሪያ ሀገር ውስጥ መግባቱን ገልጸዋል። ከተገዛው ማዳበሪያ ጅቡቲ ወደብ ላይ የደረሰው 796 ሺ 230 ነጥብ
58 ሜትሪክ ቶን መሆኑን ባለሙያው አመልክተው፣ ከዚህ ውስጥ 701 ሺ 887 ያህሉ
ወደ ሀገር ውስጥ ገብቶ ወደ ክልሎች እንዲጓጓዝ መደረጉን ገልፀዋል። እንደ ባለሙያው ገለጻ፤ለአርሶ አደሩ ማዳበሪያ ለሚያቀርቡት መሰረታዊ የህብረት ሥራ ማህበራት 631 ሺ 457 ሜትሪክ ቶኑን
ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 236 ሺ 099 ሜትሪክ ቶኑን
ለአርሶ አደሩ እንዲደርስ ተደርጓል። በተመሳሳይ በሚኒስቴሩ የግብርና ግብዓት ግብይትና የገጠር ፋይናንስ ዳይሬክቶሬት በብዛት የሚቀርቡ የግብርና ግብዓቶች ግብይት ከፍተኛ ባለሙያ ወይዘሮ ስመኝ ተጫኔ በበኩላቸው የምርጥ ዘር አቅርቦት ዝግጅትን አስመልክተው እንደተናገሩት፣ የብእር እህል፤ ጥራ ጥሬና የቅባት እህል በተያዘው የሰብል ዘመን አንድ ሚሊዮን 160 ሺ 521 ኩንታል የዘር
ፍላጎት ቀርቧል፤በዚሁ መሰረት ለአርሶ አደሩ የመኸር እርሻ አስፈላጊው ምርጥ ዘር እየቀረበ ይገኛል። በአንዳንድ አካባቢዎች የድቃይ በቆሎ ዘር እጥረት ማጋጠሙን የተናገሩት ባለሙያዋ፣ ይህንንም ለመፍታት እየተሰራ እንደሆነና በቅርቡ ለአርሶ አደሩ የሚሰራጭበት ሁኔታ እንደሚመቻችም ጠቁመዋል። አዲስ ዘመን ግንቦት 6/2011ራስወርቅ ሙሉጌታ
| 0 |
f4cf12473a70ba766b2e62494ae5e733
|
e9cf6256ee86724fa8f8b99f7311056c
|
በመቶዎች የሚቆጠሩ የካሜሩን ወጣቶች በፈጸሙት ጥቃት አንድ ሰዉ ሲሞት አያሌ ሌሎች ቆስለዋል
|
የካሜሩን ባለሥልጣናት በዚህ ሳምንት ቦኮ ሃራም በጦር ሰራዊት ሰፈር ላይ ካደረሰው ህይወት ያጠፋ ጥቃት ተከትሎ ከናይጄሪያ ጋር በሚያውስነው ድንበር ላይ የሚኖሩ ማኅበረሠቦች አሁንም ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እያሳሰቡ ናቸው።ሞኪ ኤድዊን ኪንዲዜጋ ከጦር ሰራዊቱ ጋር ተጉዞ ለቪኦኤ ያጠናቀረውንን ዘገባ ቆንጂት ታየ ታቀርበዋለች።
| 0 |
aedfca951ef970a97e4ca0bd7009859d
|
4c8986e44bd889b486d6473c78ae9dc7
|
በሶስት ቀናት ውስጥ ብቻ 3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሰዎች የመራጭነት ካርድ ወስደዋል
|
ኢትዮጵያ በይፋ ብር ከቀየረች ጊዜ ጀምሮ 14 ቢሊዮን ብር ወደ ባንክ ገቢ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዋና ገዥ ዶ/ር ይናገር ደሴ ከኢትዮጵያ ፕሬስ ደርጅት(ኢፕድ)ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ አስታውቀዋል፡፡
ዶ/ር ይናገር አዲሱ ብር በመላ አገሪቱ ባሉ የባንክ ቅርንጫፎች 99 ነጥብ 9 በመቶ መዳረሱን በቃለ ምልልሱ አንስተዋል፡፡ በዚህም ምክንያት በሁሉም ባንኮች 580 ሺህ ዜጎች የባንክ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸውን ዶ/ር ይናገር ገልጸዋል፡፡
በ580 ሺህ አዲስ የሂሳብ አካውንቶች ውስጥም በ14 ቀናት ውስጥ ብቻ 14 ቢሊዮን ብር ወደ ባንክ ገቢ መደረጉን ያነሱት ገዥው በነባር አካውንት ውስጥ የገባው የገንዘብ መጠንን በተመለከተ ደግሞ ተጠቃሎ ይፋ ይሆናል ብለዋል፡፡
መንግስት ሙስናን ለመካከልና ከኢኮኖሚ ውጭ ያለውን ብር ወደ ባንክ ለማስገባት በማሰብ አዲስ የብር ኖት ለውጥ ማድረጉን አስታውቋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ የብር ለውጥ መደረጉን ይፋ ባደረጉበት ወቅት 2.9 ቢሊዮን የብር ኖቶች መታተማቸውንና ለህትመቱም 3.7 ቢሊዮን ብር ወጭ መደረጉን መግለጻቸው ይታወሳል፡፡በብር ቅያሬው ከዚህ በፊት ያልነበረ ባለ 200 ብር ኖት የተዋወቀ ሲሆን ነባሮቹ ባለ10፣ባለ50 እና ባለ100 ብር በአዲስ ገጽታ ተቀይረው አገልግሎት ላይ ውለዋል፡፡
አሮጌውን ብር በአዲስ ቀይሮ ለመጨረስ የሶስት ወር የጊዜ ገደብ ተቀምጧል፡፡
| 0 |
d797d857a5d0a5e13c51f14f386e008d
|
d797d857a5d0a5e13c51f14f386e008d
|
የሶማሌ ክልል መንግሥት ለክልሉ ልዩ ሀይል ዘመናዊ ተሽከርካሪዎችን አበረከተ
|
አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል መንግሥት በክልሉ የሰፈነውን አስተማማኝ ሰላም የበለጠ ለማጠናከር ለክልሉ ልዩ ሀይል 78 ዘመናዊ ተሽከርካሪዎችን አበረከተ።ክልሉ ካለው የተለያዩ መልከዓ ምድራዊ አቀማመጥ ጋር በተያያዘ ተሽከርካሪዎቹ የዜጎችን ሰላም ለማረጋገጥ አስፈላጊ እንደሆኑ ተገልጿል።በአጠቃላይ በበጀት ዓመቱ ለክልሉ ሰላም መረጋገጥ ሲባል በ277 ሚሊየን ብር ወጪ 300 ዘመናዊ ተሽከርካሪዎች ተገዝተዋል ተብሏል፡፡በመጀመሪያ ዙርም ወደ ሀገር ከገቡ 150 ተሽከርካሪዎች ውስጥ 78ቱ ዛሬ የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ሀሰን መሀመድ ለሶማሌ ክልል ልዩ ሀይል ዋና አዛዥ ረዳት ኮሚሽነር መሀመድ አህመድ ማስረከባቸውን የሶማሌ ክልል ቴሌቪዥን ዘግቧል፡፡ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
| 1 |
67758485e606bb582fed672705159346
|
0519eaf8c5a22fef501e560fb9fab0f9
|
አዳማ ከተማ ዋና እና ምክትል አሰልጣኞችን ቀጥሯል
|
ሊጀመር ከ2 ሳምንት ያነሰ ጊዜ የቀረው የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ ላይ አዳማ ከነማ ለመሳተፍ ፍቃደኛ መሆኑን የአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል፡፡የአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን በዘንድሮው ውድድር ላይ እንዲካፈሉ ጥያቄ ያቀረበላቸው ክለቦች አዳማ ከነማ እና ወላይታ ድቻ ሲሆኑ አዳማ ከነማ ፍቃደኛነቱን ሲገልፅ ወላይታ ድቻ እስካሁን ምላሽ አለመስጠቱን የፌዴሬሽኑ ምክትል ፕሬዝዳንት ዮናስ ሃጎስ ለሶከር ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡ከነሃሴ 22 እስከ ጥቅምት 7 በአዲስ አበባ ስታድየም የሚደረገው ውድድር የምድብ ድልድል መስከረም 18 ወይም 19 የሚወጣ ሲሆን የስፖንሰር ሺፕ ጉዳዮችም በእለቱ ይፋ ይደረጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ አምና በካስቴል ቢራ ስፖንሰርነት የተካሄደው ውድድር በዚህ አመት በአምበር ቢራ ስፖንሰር እንደሚደረግ ቢነገርም ፌዴሬሽኑ ከማረጋገጥ ተቆጥቧል፡፡ኢትዮጵያ ቡና በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ማቅማማቱ የተነገረ ቢሆንም በመጨረሻ ግን ለመሳተፍ መወሰኑን ክለቡ አስታውቋል፡፡አዳማ ከነማ ከብሄራዊ ሊጉ ካደገ ወዲህ ከሌሎች ክለቦች በተሻለ ውድድሮች ማካሄዱን ቀጥሏል፡፡ ሁለት ጊዜ በሴካፋ ክለቦች ዋንጫ ላይ ሲካፈል አሁን ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ ላይ ለመሳተፍ ወስኗል፡፡
| 0 |
e74680c760e15e9f82267f6627fb1e15
|
e74680c760e15e9f82267f6627fb1e15
|
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ሱዳን ሶስትዮሽ የብሄራዊ ኮሚቴ ሰብሰባ ዛሬ ይጀመራል
|
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ፣ ግብፅ እና ሱዳን ሶስትዮሽ የብሄራዊ ኮሚቴ ሰብሰባ ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ቀናት ይካሄዳል ።የግብፁ የውሃ እና መስኖ ሚኒስትር ሆሳም ሞጋሃዚ በስብሰባው ለመታደም ዛሬ አዲስ አበባ ይገባሉ።ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ እንደሚያመላክተው በሶስትዮሽ ውይይቱ ፤ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ የሚደረገውን የማህበራዊ እና አካባቢያዊ እንዲሁም የሃይድሮሞሎጂ ጥናትን የሚያካሂደው ቡድን ይቋቋማል።የግብፅ እና የሱዳን የውሃ ሚኒስትሮችም የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን እንደሚጎበኙ ተጠቁሟል ።የምስራቅ ናይል የቴክኒክ ቀጠና ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ፈቅ አህመድ ነጋሽም ጉብኝቱ፤ በሶስቱ ሀገራት መካከል መተማመንን እንደሚፈጠር ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል። (ኤፍ.ቢ.ሲ.)
| 1 |
a5c7f30cc9232a6d24006f3179d92370
|
593c0f89ee50a003dc9b2abceb9aa392
|
የፌዴራል ፖሊስ፣ ፀረ ሙስና ኮሚሽንና ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረሙ
|
በትግራይ ክልል የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የሚያስፈጽመውና የሚያስተገብረው ግብረሃይል፣ ፖሊስ ወይንም ሌላ ማንኛውንም የጸጥታ ኃይል ትጥቅ እንዲፈታ የማዘዝ ስልጣን እንደተሰጠው ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አስታወቀ።ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 26/2013 ዓ.ም (አብመድ) ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ዛሬ በተወካዮች ምክር ቤት በጸደቀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አተገባበርና የአፈጻጸም ወሰን ላይ ለጋዜጠኞች ማብራሪያ ሰጥተዋል።
| 0 |
0e590fff593830484bb6556803f05b8b
|
fa8e3b4df1cfbfe13511ec32a8caef39
|
አዲሱ የስደተኞች አዋጅ ስደተኞችንና የተጠለሉበትን ሀገር የሚጠቅም መሆኑ ተገለጸ
|
ባሕር ዳር፡ ታኅሣሥ 02/2013 ዓ.ም (አብመድ) ኢትዮጵያ ስደተኞችን ተቀብላ በማስተናገድ የቆየ ልምድ አላት፤ በአሁኑ ወቅት ከደቡብ ሱዳን፣ ከሶማሊያ፣ ከኤርትራ እና ከሱዳን መጥተው በ26 የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ለሚኖሩ ስደተኞች አስፈላጊው ጥበቃና እንክብካቤ እየተደረገላቸው መሆኑን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ማጣሪያ አመላክቷል።ምግብ ነክ እና ምግብ ነክ ያልሆኑ ግብዓቶች እንደ መጠለያ፣ሕክምና፣ውኃ፣ የንጽሕና መጠበቂያ፣ትምህርት እና ሌሎች አገልግሎቶችን ጨምሮ ስደተኞቹ በአግባቡ እያገኙ መሆኑንም አስታውቋል።
| 0 |
b4d44199c4b3e3e057028388755d92e8
|
6d0b57dcda905d5e2f0d15976193592b
|
7ኛው የመከላከያ ሠራዊት ቀንን አስመልክቶ ህዝባዊ ውይይት በአዳማ እየተካሄደ ነው
|
አዲስ አበባ ፣ህዳር 3፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሐረማያ እና የአርሲ ዩኒቨርሲቲ በወቅታዊ ሃገራዊ ጉዳይ ላይ ውይይት በማድረግ ለመከላከያ ሠራዊት ያላቸውን አጋርነት ገልፀዋል።የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና የአስተዳደር ሰራተኞች በወቅታዊ ሃገራዊ ጉዳይ ላይ ውይይት በማድረግ ለመከላከያ ሠራዊት ያላቸውን አጋርነት በመግለጽ ለጀመረው ህግ የማስከበር ሂደት የአምስት ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርገዋል።የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ጀማል ዩሱፍ ÷ የሃገር መከላከያ ሠራዊት እያደረገ ላለው ጥረት ድጋፍ የሚሆን የአምስት ሚሊየን ብር መለገሱን አስታውቀው ከገንዘብ ድጋፉ ባሻገርም ደም በመለገስ አጋርነታቸውን እንደሚያሣዩ ተናግረዋል።የዩኒቨርሲቲው መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች በጦርነቱ ሊደርስ የሚችለውን ሰብአዊ ጉዳት በመገንዘብ ከወር ደሞዛቸው ላይ አስተዋፅኦ ለማድረግም ቃል ገብተዋል።በውይይት መድረኩ ላይ የተሳተፉ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች “ደሜ ለሃገሬ መከላከያ ሠራዊት” በሚል የደም ልገሳ አካሂደዋል።በተያያዘ ዜናም የአርሲ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ሰራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታ ላይ የሚመመክር መድረክ አካሂደዋል።የህወሓት ፅንፈኛ ቡድን በሰሜን እዝ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ የፈጸመው ጥቃትና ክህደት የቡድኑን አውሬያዊ ፀባይ ያጋለጠ ነው ብለዋል።በመድረኩም “የህወሓት ክህደትና ድብቅ አላማ” በሚል ሰነድ ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን ÷በሰነዱም የፅንፈኛው ቡድን ከምስረታ እስከ አሁን በኢትዮጵያ ፖለቲካ የነበረው ቦታና ሸፍጥ ተዳሷል።የአርሲ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ጀማል አልዬ ህወሓት በሀገር ፖለቲካ ላይ በስልታዊ የተንኮል ቀመር ራሱንና እሱ ያደራጃቸውን ቡድኖች ሲጠቅም መቆየቱን ጠቅሰዋል።ቡድኑ ዘረፋና ህገወጥ ስራው ሲቀርበት ሀገር የማፈራረስ ስራ መጀመሩንም አስረድተዋል።መንግስት ችግሮችን ለመፍታት በሆደ ሰፊነት ሲመለከት መቆየቱን የተናገሩት አስተዳዳሪው÷ ትዕግስት እንደፍርሃት የቆጠረው ወንበዴው ቡድን ባልታሰበ ሁኔታ ራሱን አሳልፎ በሰጠው ሰራዊት ላይ ጥቃት ማድረገሱን አንስተዋል።በተሾመ ኃይሉ እና በአፈወርቅ እያዩ
| 0 |
75722f23f378af7e59f2c46a0a927372
|
75722f23f378af7e59f2c46a0a927372
|
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ የዛሬ ውጤቶች እና የደረጃ ሰንጠረዥ
|
አማራ ውሃ ስራ 2-1 ሰበታ ከተማ (ባህርዳር)
ባህርዳር ከተማ 1-3 ሱሉልታ ከተማ (ባህርዳር)
ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ 4-2 ቡራዩ ከተማ (አዲግራት)09፡00 ወልድያ ከ አአ ፖሊስ (ወልድያ)ቅዳሜ ሚያዝያ 8 ቀን 2008ድሬዳዋ ፖሊስ 0-0 ናሽናል ሴሜንትእሁድ ሚያዝያ 9 ቀን 2008አአ ዩኒቨርሲቲ 1-2 ሀላባ ከተማ
ኢትዮጵያ መድን 0-1 መቐለ ከተማ
አክሱም ከተማ 1-4 ፋሲል ከተማ
ወሎ ኮምቦልቻ 1-1 ኢትዮጵያ ውሃ ስፖርት
ነገሌ ቦረና 0-0 ሻሸመኔ ከተማ
ወራቤ ከተማ 2-1 ፌዴራል ፖሊስ
ጅማ ከተማ 3-0 ባቱ ከተማ
ደቡብ ፖሊስ 8-1 ጂንካ ከተማ
| 1 |
f3ab034c8e35f70d32db4db7b41af782
|
f3ab034c8e35f70d32db4db7b41af782
|
አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ ከአረብ ሊግ ዋና ጸሀፊ ጋር ተወያዩ
|
አዲስ አበባ ፣ ህዳር 8 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በግብጽ የኢትዮጵያ አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ ከዓረብ ሊግ ዋና ጸሀፊ አህመድ አባኡል ጊሂት ጋር በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ተወያዩ፡፡በውይይታቸውም አምባሳደር ማርቆስ በኢትዮጵያ መንግስት የጀመረውን ህግና ህገ መንግስት የማስከበር ስራ በተመለከተ አብራርተዋል፡፡የኢትዮጵያን እና የግብፅ ግንኙነትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እንደሚሰሩ አምባሳደር ማርቆስ ለዋና ፀሀፊው ገልጸዋል ፡፡የዓረብ ሊግ ዋና ጸሀፊ አህመድ አባኡል በበኩላቸው÷ አምባሳደር ማርቆስ በኢትዮጵያ እና በግብፅ መካከል የተጠናከረ ግንኙነት እንዲኖር ለማስቻል ያላቸውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል ፡፡ዋና ፀሀፊው አያይዘውም የኢትዮጵያ ሰላም ለአፍሪካ ቀንድ እና ለቀይ ባህር አካባቢ ደህንነት ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልፀዋል ፡፡ከዚህ ባለፈም ዋና ጸሀፊው ከአምባሳደር ማርቆስ ተክሌ ጋር በቅንጅት ለመስራት መዘጋጀታቸውን ጠቁመው ÷ አምባሳደሩ ለዓላማቸው መሳካት የሚያደርጉትን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ እንደሆኑ መናገራቸውን በግብጽ ከኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
| 1 |
d95113b6f9a5085a4634925273a0f87a
|
9391cb1cf8fc1c1db2cc6956daf2925c
|
የኦስትሪያ መራሄ መንግስት ሰባስቲያን ከርዝ ኢትዮጵያን ሊጎበኙ እንደሆነ ተገለጸ
|
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ የፊታችን ነኀሴ 19 እና 20 ኢትዮጵያን ሊጎበኙ ነው። በጉብኝታቸው ወቅት ከአገሪቱ መሪዎች ጋር ስለ ጋራ ጉዳዮች ይወያያሉ፥ ከአፍሪቃ ኅብረት መሪዎችም ጋር ይገናኛሉ።የኢትዮጵያ መንግሥት ተቃዋሚዎች “ገዥው ኢህአዴግ ሰብአዊ መብቶችን ይረግጣል፥ ጋዜጠኞችን ያስራል፣ ተቃናቃኝ ፓርቲዎችን ያፍናል፣ ምርጫ አጭበርብሯል …” በማለት የፕሬዚዳንቱን ወደ ኢትዮጵያ መሄድ ይቃወማሉ፡፡ዩናይትድ ስቴትስ ከኢትዮጵያ ጋር በአካባቢ ፀጥታ፣ በልማት እና በንግድ የፖሊሲ ግንኙነት እንዳላት ይታወቃል፡፡ ከእነዚህ ጭብጦች አንፃር የፕሬዚዳንቱን ጉዞ አስመልክቶ የሚተነትኑና መልስ የሚሰጡ ሁለት ምሁራንን ለጥያቄዎ መልስ ዝግጅት ጋብዘናል።ከፕሬዚደንቱ የኢትዮጵያ ጉዞ ጋር በተያያዘ ለጥያቄዎቻችሁ መልስና ማብራሪያ የሚሰጡት ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማሪያም በካሊፎርኒያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሣይንስና የሕግ ፕሮፌሰር፣ እንዲሁም ዶክተር መሃሪ ታደለ ማሩ የምሥራቅ አፍሪቃ አገሮች የጋራ ልማት ባለሥልጣን - ኢጋድ በአፍሪቃ ኅብረት የፀጥታ ጉዳዮች ተንታኝ ናቸው፡፡ጥያቄዎችዎን በ202-205-9942 በውስጥ መሥመር 14፤ እንዲሁም በኢሜል [email protected] ብለው አሁኑኑ አድርሱን፡፡
| 0 |
716e0d550374dbf37781afa673a05cc7
|
28caf4132d78c97dc8a12889c4b3e23e
|
በኢትዮጵያ የምግብ እጥረት ለማሟላትና ዜጎችን ለመርዳት የዘጠና ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻ ተጀመረ
|
በኳታር ዶሃ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለሕዳሴ ግድብ ግንባታ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናገሩ።በኳታር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ስለ ግድቡ ግንባታ ወቅታዊ መረጃ እንዲያገኙ የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ትናንት ተካሂዷል፡፡በኳታር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የግድቡ ግንባታ ከተጀመረ አንስቶ ሌሎች ድጋፎችን ሳይጨምር ከ35 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማድረጋቸው ታውቋል፡፡ይሁን እንጅ በግድቡ ላይ ተከስቶ በነበረው የቴክኒክ፣ የአስተዳደርና ሌሎች ችግሮች ምክንያት ድጋፋቸው ተቀዛቅዞ መቆየቱ ተገልጿል፡፡ የማስተካከያ እርምጃ መወሰዱን ተከትሎ ደግሞ ድጋፋቸውን እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል፡፡በኳታር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ስለ ግድቡ ግንባታ ወቅታዊ መረጃ እንዲያገኙ የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ትናንት ሐምሌ 26/2011 ዓ.ም በኢትዮጵያ ኢምባሲ አዘጋጅነት ተካሂዷል።ተሳታፊዎችም ሁሉም ዜጋ ምንም ዓይነት ቅድመ ሁኔታ ሳያስቀምጥ በአዲስ ሞራል የአገራዊ አንድነት ምልክት የሆነውን የሕዳሴ ግድብ ተረባርቦ ከፍጻሜ ማድረስ እንደሚገባ ስምምነት ላይ መድረሳቸው ታውቋል፡፡ኢትዮጵያውያኑ ለግድቡ ግንባታ የሚያደርጉትን ድጋፍም አጠናክረው እንደሚቀጥሉ መናገራቸወኘ ከኳታር የኢትዮጵያ ኢምባሲ ያገኘውን መረጃ ጠቅሶ የዘገበው የአማራ መገናኛ ብዙሃን ነው።
| 0 |
17f116d438cba820d1af4458c62e0131
|
17f116d438cba820d1af4458c62e0131
|
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚያስገኘውን ሠፊ የልማት ዕድል ለመጠቀም ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገለፀ
|
አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 12፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከሚያስገኘው ዘርፈ-ብዙ የመጠቀም ዕድል የክልሉን ሕዝብ ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ ተናገሩ፡፡የታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ሲጠናቀቅ በሚፈጠረው “የሕዳሴ ኃይቅ” ዙሪያ የሚከናወኑ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ያካተተ ክልላዊ የ5 ዓመት ስትራቴጂክ ረቂቅ ዕቅድ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ውይይት አካሂደዋል፡፡ስትራቴጂክ ዕቅዱ ግደቡ ሲጠናቀቅ እንደ ሀገር ከሚከናወኑ የተለያዩ የልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ለክልሉ ይዞት የሚመጣውን ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ወደ ተግባር ለመቀየር የሚስችል መሆኑም ተመልክቷል፡፡የክልሉ ምክትል ርዕሰ-መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ “በለውጡ አመራር በተወሰደው የማስተካከያ እርምጃ የግድቡ የግንባታ በጥሩ ሂደት ላይ መሆኑ ሁሉንም አስደስቷል” ብለዋል፡፡ግድቡ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኝ በመሆኑ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ለክልሉ ይዞት የሚመጣው ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ የላቀ መሆኑን በመግለፅ በክልሉ ያለውን የመልማት አቅም ከዚህ ዕድል ጋር በማጣጣም ወደ ተጨባጭ ልማት መቀየር የሚያስችል ተገቢ ዝግጅት ከወዲሁ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡በክልሉ ያሉትን ቱባ የባህል እሴቶች፣ የቱሪዝም ሥፍራዎችንና የተፈጥሮ ሀብቶችን በአግባቡ በማልማት ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንዲያስገኙ ማድረግ ተገቢ ነው ያሉት ምክትል ርዕሰ-መስተዳድሩ ለዚህም ታላቁ የህዳሴ ግድብ ይዞት የሚመጣው ዕድል ትልቅ ድርሻ እንዳለውም ገልጸዋል፡፡ከዚህ ቀደም ዕድል ሳያገኙ የቆዩት የክልሉ ወጣቶች የግድቡ ውኃ በሚተኛበት የደን ምንጣሮ ሥራ መሳተፋቸውን የክልሉ መንግስት አንዱ የሀገራዊ ለውጡ ማሳያ አድርጎ እንደሚያዬውም መናገራቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።የግድቡ ግንባታ አስኪጠናቀቅ የክልሉ መንግስትና ሕዝብ የሚያደርጉትን ሁለንተናዊ ድጋፍ አጠናክረው አንደሚቀጥሉ ገልጸው ሀገራዊ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ትልቅ የጉብኝት ማዕከል በመሆኑ ክልሉ ከዚህ የሚያገኘውን ጠቀሜታ በአግባቡ ለመጠቀም ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ይገባል ብለዋል፡፡በውይይቱ የተሳተፉ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በበኩላቸው የሕዳሴ ግድብ እንደ ሀገር ከሚያስገኘው ጠቀሜታ ባሻገር ለክልሉ ልማት ሠፊ ዕድል ያመጣል ያሉ ሲሆን ይህንን ዕድል በአግባቡ ለመጠቀም ተቋማት የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
| 1 |
52a5609d5812feba5d3232cb02f99a6f
|
4e293b934e8a51db2dccdd136e6d2b6c
|
ምርት ገበያው በሰኔ ወር 62 ሺህ 542 ቶን ምርት አገበያይቷል
|
-የተንዳሆ ስኳር ፋብሪካ በጥር ወር ስኳር ማምረት እንደሚጀምር የስኳር ኮርፖሬሽን አስታወቀ ። የኮርፖሬሽኑ የኮምኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ዘመድኩን ተክሌ ለዋልታ እንደገለጹት በዘንድሮ የበጀት ዓመት አጋማሽ ላይ የፋብሪካው የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ ተጠናቆ በጥር ወር ስኳር ማምረት ይጀምራል።በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እየተገነባ ያለው ይህ ፋብሪካ በአሁኑ ወቅት የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታው ከ85 በመቶ በላይ መጠናቀቁን አቶ ዘመድኩን ተናግረዋል፡፡ ፋብሪካው እስከ ሰኔ መጨረሻ ድረስ 123 ሺ ቶን ስኳር ያመርታል ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል። አቶ ዘመድኩን አያይዘው እንደገለጹት ለፋብረካው አስፈላጊ ከሆነው በ50ሺ ሄክታር መሬት የሸንኮራ አገዳ ልማት ውስጥ እስካሁን በ11ሺ ሄክታር መሬት ላይ ልማቱ ተካሂዷል።በስኳር ልማቱ አካባቢ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግም የጤና ኬላዎች ፤ የውሃ መጠጥና የመንገድ ግንባታዎች መከናወናቸውን የጠቀሱት አቶ ዘመድኩን ለአርብቶ አደሩ የመስኖ ልማት የሚውል 12 ሺ ሄክታር መሬት መሠጠቱንም ገልጸዋል።የተንዳሆ ስኳር ፋብሪካ ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር በኩል አበረታች ሚና እየተጫወተ እንደሆነ የሚገልጹት አቶ ዘመድኩን እስካሁን ከ10ሺ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዚያዊ የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል።የተንዳሆ ስኳር ፋብሪካ በሙሉ አቅሙ ማምረት ሲጀምር በቀን 26ሺ ቶን አገዳ በመፍጨት በዓመት 619 ሺ ቶን ስኳር ምርት በማቅረብ አሁን በነባር ፋብሪካዎች የሚመረተውን የስኳር ምርት መጠን እጥፍ የማድረግ አቅም እንዳለው አቶ ዘመድኩን ተናግረዋል።በተጨማሪም ፋብሪካው ከስኳር ተረፈ ምርቱ 120 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሃይልና በዓመት 63ሺ ኪዩቢክ ሜትር ኤታኖል ያመርታል ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ዘመድኩን መናገራቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል፡፡
| 0 |
b73b5fcaaaef7b43b6641c92153ef062
|
7224edbc2604030582eb06bf2d8b66f3
|
ከብራዚል በመጡ ባለሙያዎች የአሰልጣኞች ስልጠና ነገ ሊሰጥ ነው
|
አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 30 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ድጋፍ ለሚሰጡ የጤና እና ሌሎች ባለሙያዎች የህይወት መድን ሽፋን ለመስጠት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ።ስምምነቱን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ እና የኢትዮጵያ መድን ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ነጻነት ለሜሳ ፈርመዋል፡፡በስምምነቱ መሰረትም የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በተለያዩ የጤና ተቋማት ለሚሰሩ የጤና እና ለሌሎች ባለሙያዎች የህይወትና የአደጋ መድን ሽፋን ይደረግላቸዋል።ይህም በለይቶ ማቆያ፣ በኳራንቲን፣ በላብራቶሪ ምርመራ ማዕከል፣ በፈጥኖ ምላሽ ቡድን፣ በድንገተኛና በሌሎች ክፍል የሚሰሩ ባለሙያዎችን ይሸፍናል ተብሏል።ጎን ለጎንም ጽዳቶች፣ የአንቡላስ ሹፌሮችና ሌሎችም ፊት ለፊት የሚሰሩ ባለሙያዎች በዚሁ የህይወት መድን ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ከጤና ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
| 0 |
cad9eb14aebf4baea96483026f3402d0
|
3355b92c6eb11532482bff986126b3da
|
አዲሱ የወልድያ ሼክ መሃመድ ሁሴን አላሙዲ ስታድየም ገፅታ
|
ሶማልያ አዲስ ፕሬዚዳንት መርጣለች፤ ትናንት ነው የሶማሊያ ፓርላማ በሁለተኛ ዙር ምርጫ ሞሐመድ ዐብዱላሂ ሞሐመድን የመረጣቸው። አዲሱ ፕሬዚደንት የተመረጡት የቀድሞውን ፕሬዚደንት ሃሰን ሼክ መሃሙድን 184 ለ97 በሆነ ድምፅ ብልጫ አሸንፈዋቸው፡፡ሞሐመድ ዐብዱላሂ ሞሐመድ በምርጫው ማሸነፋቸው ይፋ ከተደረገ በኋላ ወዲያውኑ ቃለ መሃላቸውን ፈፅመዋል።አዲሱ ፕሬዚዳንት ባደረጉት አጭር ንግግር“የዚህ ድል ባለቤት የሶማልያ ህዝብ ነው። ይህ ድል አንድነቷ የተጠበቀ፣ ሰላማዊና የተረጋጋች ሶማልያን የመገንባት ሥራ የሚጀመርበት ነው። ለዲሞክራሲና የፀረ - ሙስና ዘመቻም የምንያያዝበት ነው” ብለዋል።አስረካቢው ፕሬዚዳንት ሃሰን ሼክ ሞሐመድም ትናንት ሽንፈታቸውን ተቀብለው ለተተኪያቸው መልካም ምኞት በማስተላለፋቸው አድናቆትን አትርፈዋል።ያ ሁሉ በጎ ጎን ሆኖ ሳለ ሶማልያ አሁንም በሀገር ዓቀፍ ደረጃ አንድ ሰው አንድ ድምፅ ምርጫ የማካሄድ ግቡዋ ጋ አልደረሰችም። የፀጥታው ጉዳይም አሁንም ትልቅ ፈተናዋ ነው። ባለፈው ዓመት የፓርላማ አባላት በጎሳ መሪዎችና በክልል ተወካዮች መመረጥ ነበረባቸው። ፕሬዚደንታዊ ምርጫውን ጨምሮ የምርጫዎቹ ሂደት ድምፅ በሰፊው በገንዘብ ተቸብችቦበታል የሚሉ ውንጀላዎች አጥልተውበታል።ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
| 0 |
055cc9711f8925eb2c99ef3dc8079216
|
de5e28e0594fba709b964a62df6dbd18
|
የዐብይ አሕመድ አንድ ዓመት
|
አዲስ አበባ፣ ህዳር 21፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 5ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዓመት የስራ ዘመን 2ኛ ልዩ ስብሰባውን አካሄደ።ምክር ቤቱ ልዩ ስብሰባውን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት በሚገኘው መሰብሰቢያ አዳራሽ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት አካሄዷል።የምክር ቤቱ አባላት የህወሓት የጥፋት ቡድን እና ኦነግ ሸኔ በሽብርተኝነት እንዲፈረጁ ጠይቀዋል።ሁለቱ ቡድኖች በቅንጅት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሽብር ድርጊት ላይ የተሰማሩ መሆናቸውን ገልፀው በጥፋታቸው እንዳይቀጥሉም በሽብርተኝነት እንዲፈረጁ ነው አባላቱ የጠየቁት፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በወቅታዊ የሃገሪቱ ጉዳዮች ላይ ከምክር ቤቱ አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
| 0 |
53c201ba26447183d4ab276805702ed2
|
6032e4e95b09526f883eb6194d7da13a
|
የሀይማኖት ተቋማት መማክርት ጉብኤና የሃገር ሽማግሌዋች ውይይት ከትግራይ ክልል አመራሮች ጋር
|
አዲስ አበባ፣ ህዳር 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በሀረሪ ክልላዊ መንግስት “ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ለመከላከያ ሰራዊታችን!” በሚል መሪ ቃል ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት እየተደረገ ነው።ምክትል ርዕሰ መስተዳድርወይዘበህዝባዊ የውይይት መድረኩ ላይ ወቅታዊ የሀገራዊ ሁኔታን በሚመለከት ውይይት እንደሚደረግ የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል፡፡በውይይት መድረኩም የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ፣
ሚስራ አብደላ፣ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ሮ አዲስአለም በዛብህን ጨምሮ የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባገዳዎች፣ የሀይማኖት አባቶችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
| 0 |
cf117c07e4cb52696cdf7983f48ee9a6
|
f4775baf36545e21096e1a28fca5d183
|
በ4ዐ ሚሊየን ዩሮ የሚገነባው የልብ ህክምና ማዕከል የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ
|
አዲስ አበባ፣ ህዳር 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የጀርመን ኤምባሲ ለጦር ሀይሎች ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 1 ሚሊየን ዩሮ የሚያወጣ የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ ፡፡የሆስፒታሉ የመድሃኒትና ህክምና መሳሪያዎች አቅርቦት መምሪያ ሀላፊ ብርጋዴር ጄኔራል ይልማ መካንቴ የተደረገው ድጋፍ ለሆስፒታሉ አገልግሎት አሰጣጥ ከፍ ያለ አስተዋፅኦ እንዳለው ገልፀዋል፡፡ይህም የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ይበልጥ ያጠናክራል ብለዋል ፡፡የጀርመን መከላከያ ሰራዊት ቴክኒካል አማካሪ ቡድን ሀላፊ ኮሎኔል አንደሬ ስኮፊስ በበኩላቸው ድጋፉ ወደ ፊትም እንደሚቀጥልና የሀገራቱን ወታደራዊ ግንኙነት ማሳያ እንደሆነ መግለፃቸውን ከመከላከያ ሰራዊት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
| 0 |
9761b4a7f595e4965e55cdad9d488b4d
|
e57ddcd8e86db65f3979ed2678f71872
|
ፋሲል ከነማ ናይጄርያዊያን አጥቂዎች አስፈርሟል
|
ፋሲል ከነማ እና የደጋፊ ማኅበሩ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመግታት የሚውል የ360 ሺህ ብር ድጋፍ አድርገዋል።በኮሮና ቮይረስ ወረርሽኝ አማካኝነት ለሚፈጠረው ችግር ክለቦች እና አጠቃላይ የስፖርት ቤተሰቡ ድጋፍ እያደረጉ የሚገኙ ሲሆን ፋሲል ከነማ እግርኳስ ክለብም የበኩሉን ድጋፍ አድርጓል። የፋሲል ከነማ ዋናው እና የታዳጊ ቡድን ተጫዋቾች፣ አሰልጣኞች እና አጠቃላይ አባላት 260,000 ብር፣ የደጋፊ ማኅበሩ 100,000 ብር በአጠቃላይ 360,000 ብር ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን የኮሮና ቮይረስ ስርጭትን ለመግታት ለሚደረገው ርብርብ በቀጣይም መሰል ድጋፎች እንደሚያደርጉ ገልፀዋል።
| 0 |
f507944737f694ee1256f7bd92e4627a
|
fe79e81ef5847754d3b7a2c1557bec15
|
በሀገር አቀፍ ደረጃ ኢኮኖሚያዊ ምክንያት ሳይኖር የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ ከ25 ሺህ በላይ የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ ተወሰደ
|
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 6፣ ቀ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)በምርቶችና ሸቀጦች ላይ አለአግባብ የዋጋ ጭማሪ እንዳይኖር ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ እንደሚያስፈልግ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ገለጹ።ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት ከክልልና ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ኃላፊዎች ጋር መደበኛ የቪዲዮ ኮንፈረንስ ውይይት ባካሄዱበት ውቅት ነው ተብሏል።ብዙ ጊዜ ለወቅታዊ የዋጋ ንረት ምክንያት የሚሆነው የንግድ ዘርፉ የመንግስት ተቋማት ቁጥጥር መለላት ነው ም ነው የተባለው፡፡ስለሆነም ህብረተሰቡንና የንግድ ማህበረሰቡን ያሳተፈ ዘላቂነትና ተከታታይነት ያለው የቁጥጥር ሥርዓት መዘርጋትና የባለሙያዎችን የስራ እንቅስቃሴ መከታተልና መደገፍ ያስፈልጋል፡፡ከዚያም ባለፈ የህገ-ወጥ ንግድ ኮንትሮ ባንድ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራት የተወሰዱ እርምጃዎች በመገምገም የተገኘውን ውጤት እየለኩ መሄድ እንደ አንድ ቁልፍ ተግባር አደርጎ መውሰድ እንደሚገባ ም ሚኒስትሩ አሳስበዋል፡፡ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የወጪ ንግድ ምርቶች ላይ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንዳለባቸው የጠቆሙት ሚኒስትሩ÷ በኮሮና ቫይረስ መከሰት ምክንያት በምርቶችና ሸቀጦች ላይ ያለአግባብ የዋጋ ጭማሪ እንዳይኖር ጥብቅ ቁጥጥር ከማድረግ ጎን ለጎን አቅርቦት ማሻሻልና ትስስር መፍጠር ላይ ትኩረት ተደርጎ መስራት ይገባልም ነው ያሉት።በመጨረሻም የኮቪድ-19 ሥርጭትን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠር እና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀንስ የወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እና አዋጁን ለማስፈጸም የወጣውን ደንብ ለማስፈጸም በሚኒስትሮች ኮሚቴ የወጣ የግብይት ዘርፍ መመሪያ ላይ ውይይት ማድረጋቸውንየንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
| 0 |
c34921e4a1e5045568b35d0e1b18b6ed
|
8850736548d34594fcba7ab816bfd01e
|
የአዳማ ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ጠንካራ ቅድመ ዝግጅት ማድረጉን የጤና ሚንስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ አስታወቁ
|
አዲስ አበባ ፣ የካቲት 30 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ።ቫይረሱን ለመቆጣጠር የተቋቋመው ብሄራዊ የሚኒስትሮች ኮሚቴ ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት ስራውን ገምግሟል።በዚህ ወቅትም ቫይረሱ እስካሁን ድረስ ወደ ኢትዮጵያ ባይገባም የክትትልና የመቆጣጠር ስራ እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል።ቁጥጥሩ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያን ጨምሮ በ30 የየብስ በሮች እየተደረገ መሆኑም ነው የተገለጸው።ቫይረሱ ምናልባት በኢትዮጵያ ቢከሰት የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል እጥረት ሊያጋጥም ስለሚችል፥ በሃገር ውስጥ ተመርቶ ለውጭ ገበያ ይቀርብ የነበረው ጭምብል እንዲቆም ተደርጓልም ነው የተባለው።ከዚህ ጋር ተያይዞ የህክምና ተቋማት ዝግጁ የተደረጉ ሲሆን፥ በአዲስ አበባ የየካ ኮተቤ ሆስፒታል ይህን ህክምና ብቻ እንዲሰጥ ተለይቷል።ሆስፒታሉ በአንድ ጊዜ 300 ሰዎችን የማስተናገድ አቅም ያለው ሲሆን፥ በሂደት አቅሙ በእጥፍ የሚጨምር ነው ተብሏል።ከዚህ ባለፈም በቢሾፍቱ የመከላከያ ሆስፒታል ለዚህ ስራ ተለይቶ የተዘጋጀ ሲሆን፥ በክልሎች እና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ባሉባቸው አካባቢዎችም የቅድመ ዝግጅት ስራ እየተከናወነ ይገኛል።ቫይረሱ ዓለም ላይ ከተከሰተ ወዲህም በኢትዮጵያ ሊካሄዱ ታስበው የነበሩ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶች መሰረዛቸውም ታውቋል።በአላዛር ታደለትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!
https://t.me/fanatelevision
| 0 |
2377dab2eeba189ea2bda2fa45e4809a
|
55997b1779ec075521b38e10477fa622
|
የመን ያሉ ኢትዮጵያዊያን የድረሱልን ጥሪ እያሰሙ ነው
|
የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ያውጣውን መግለጫ ተከትሎ “መግለጫው የህዝቡን መሰረታዊ ጥያቄ ያነሳ አይደለም፣ ከዚህ በመነሳት አስራ ሁለተኛው መደበኛ ጉባዔ እንዴት እንደሚሆን ማወቅ ይቻላል” ያሉ ወገኖች ድምፃቸውን እያሰሙ ነው።የውይይቱ ተካፋዮች ለረጅም ጊዜ በድርጅቱ አመራር ውስጥ የነበሩና አሁን ከፍተኛ ትምህርት ላይ ያሉት አቶ ቹቹ አለባቸው፣ እንዲሁም አቶ ወንድወሰን ለገሰ እሳቸውም በድርጅቱ አመራር ውስጥ የነበሩ ሲሆኑ ሁለቱም በድርጅቱ ውስጥ የህዝብን መሰረታዊ ጥያቄ ሲያነሱ እንደነበሩና ከድርጅቱ እንደተባረሩ ይናገራሉ። አቶ ምግባሩ ከበደ ደግሞ የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና የገጠር ፖለቲካ አደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊ ናቸው።።
| 0 |
ed73cdd1829d0ceb9f010281e0ac95d7
|
ed73cdd1829d0ceb9f010281e0ac95d7
|
በወልዲያ በተከሰተው ግጭት የሞቱት ሰዎች ቁጥር ሰባት ደረሰ
|
በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ወልዲያ ከተማ ትናንት ጥር 12 ቀን 2010 ዓ.ም. እና ዛሬ ጥር 13 ቀን 2010 ዓ.ም. በፀጥታ ኃይሎችና የቃና ዘገሊላ በዓልን ለማክበር በወጡ ሰዎች መካከል በተከሰተው ግጭት እስካሁን የሰባት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር አማረ ጎሹ ለአማራ ቴሌቪዥን በሰጡት የስልክ ማብራሪያ ገለጹ፡፡አንድ የፀጥታ ኃይል አባልና ሌሎች ስድስት ሰዎች ሞተዋል ያሉት ኮማንደሩ፣ ሁለት የፖሊስ አባላት ከፍተኛ የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው ገልጸዋል፡፡ በአጠቃላይ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው 15 ሰዎች መሆናቸውንም ኮማንደሩ አስታውቀዋል፡፡ኮማንደሩ አክለውም ዛሬ ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ጀምሮ በነበረ ግጭት መኪኖች፣ ቤቶችና ሆቴሎች መቃጠላቸውን ተናግረዋል፡፡ የክልሉ የፀጥታ ኃይል ግጭቱ እዚህ ደረጃ ሳይደርስ ለማስቆም ጥረት ሲደረግ የነበረ ቢሆንም፣ የተወሰኑ የበዓሉ ተሳታፊዎች የፖሊስ አባላትን አሳደው በድንጋይ ለመደብደብ ባደረጉት ሙከራ ይህን ያክል ጉዳት ሊደርስ ችሏል ብለዋል፡፡
| 1 |
d7c55818f289bfeb2dbdc374d9e8aa63
|
2d24af05d891df52c4f6f3357da07c2d
|
ምንተስኖት አሎ ቱርክ ገብቷል
|
የመሀል እና የመስመር ተከላካዩ ቢያድግልኝ ኤልያስ ሰበታ ከተማን ተቀላቅሏል፡፡ኢትዮጵያ ከ31 ዓመታት በኋላ በተሳተፈችበት የ2013 አፍሪካ ዋንጫ ላይ ከነበሩ ተጫዋቾች አንዱ የሆነው ቢያድግልኝ በሲዳማ ቡና ያሳየውን ድንቅ አቋም ተከትሎ ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ በማምራት ጥሩ ጊዜ በክለቡ አሳልፏል። ከፈረሰኞቹ ጋር በ2008 ከተለያየ በኋላም በአርባምንጭ ከተማ፣ ጅማ አባ ቡና እና ወልዲያ እንዲሁም ያለፉትን ሁለት ዓመታት ደግሞ በመቐለ 70 እንደርታ በመጫወት አሳልፏል፡፡ “ሰበታ ከተማን በመቀላቀሌ ደስ ብሎኛል። በምወደው አሰልጣኝ የመሰልጠን ዕድሉን በማግኘቴም ውስጤ ደስታ ተፈጥሯል፡፡ በሚኖረኝ ቆይታ ጥሩ ነገሮችን አሳያለሁ ብዬ አስባለሁ።” በማለትም አስተያየቱን በአጭሩ አጋርቶናል፡፡ሰበታ ከተማ ከቢያድግልኝ በፊት ምንተስኖት አሎ፣ ሙሉቀን ደሳለኝ፣ መሳይ ጳውሎስ፣ ዳንኤል ኃይሉ፣ ዱሬሳ ሹቢሳ፣ ቡልቻ ሹራ፣ ፍአድ ፈረጃ እና እስራኤል እሸቱን ማስፈረሙ ይታወሳል፡፡© ሶከር ኢትዮጵያ
| 0 |
cabc37519f50d287b9edd10eac79a0b7
|
2f97fdec28d66c883be502bb5824dccc
|
የልዩ ተሰጥኦ ልማት ኢንስቲቲዩት በዚህ አመት ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር እንደሚጀምር ተገለጸ
|
ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በየብስ የሚያገናኛትን ግዙፍ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አጠናቃ፣ በመጪው መስከረም 1 ቀን 2012 ዓ.ም እንደምታስመርቅ ተገለጸ፡፡ ባለፈው አመት ነሐሴ ወር መጨረሻ ላይ የተጀመረው የ90 ኪ.ሜትር የመንገድ ግንባታ በአሁኑ ወቅት 90 በመቶ መጠናቀቁን የዘገበው ኤርትሪያን ፕሬስ፤ ቀሪው 10 በመቶ በቀጣይ ሁለት ሳምንታት ውስጥ ይጠናቀቃል ብሏል፡፡ ኤርትራን ከኢትዮጵያ በየብስ እንደሚያገናኝ የተነገረለት ይኼው መንገድ፤ ቀደም ሲል በ6 ሜትር ስፋት የተሰራ ሲሆን አሁን በተደረገው ማሻሻያና ተጨማሪ ግንባታ፣ በእጥፍ ጨምሮ፣ ከ12 እስከ 20 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጓል፤ 25 አዳዲስ ድልድዮችም ተገንብተዋል ተብሏል፡፡በሁለቱ አገራት ግንኙነት ላይ ወሳኝ ሚና እንዳለው በሚነገርለት በዚህ የመንገድ ግንባታ ላይ በርብርብ የተሳተፉት 5 የኤርትራ የመንገድ ኮንስትራክሽን ኩባንያዎችን ጨምሮ የአገሪቱ መከላከያ ሀይል መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡ የመንገዱ እድሳትና ግንባታ አንድ አመት የፈጀ ሲሆን ሙሉ ወጭው በኤርትራ መንግስት መሸፈኑ ታውቋል፡፡ በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘው የመንገድ ግንባታው በአዲሱ ዓመት መስከረም 1 እንደሚመረቅና አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ኤርትሪያን ፕሬስ ዘግቧል፡፡
| 0 |
7a60d6491428c7799dc9d121f96eb029
|
4d83e9b3dca4d5d586414a617b8e4298
|
የሽረ ስታዲየም እድሳት ተጀመረ
|
በኢትዮዽያ ከፍተኛ ሊግ የምድብ ሀ 11ኛ ሳምንት ሽረ ላይ መካሄድ የነበረበት የሽረ እንዳስላሴ እና ባህርዳር ከተማ ጨዋታ በፌዴሬሽኑ ሊግ ኮሚቴ ውሳኔ መሰረት ጥር 20 (እሁድ) ለገጣፎ ላይ በ08:00 ላይ ሊደረግ መርሀ ግብር ቢወጣለትም በከተማው በተደረገው የግማሽ ማራቶን ውድድር ምክንያት የፀጥታ አካላት በበቂ ሁኔታ ባለመኖሩ በሚል ምክንያት መካሄድ ሳይችል መቅረቱ ይታወሳል።ፌዴሬሽኑ ይህን ጨዋታ እንዲካሄድ ሌላ የመርሀ ግብር ለውጥ አድርጎ አዲስ አበባ ላይ ጥር 22 (ዛሬ) በ07:00 በኦሜድላ ሜዳ እንዲደረግ በወሰነው መሰረት የሁለቱም ቡድን ተጫዋቾች ፣ አመራሮች ፣ ደጋፊዎች ፣ የህክምና ቡድን እና የጨዋታውን አመራሮች እንዲሁም በቂ የፀጥታ ኃይል በሜዳው ተገኝቶ ነበር። ጨዋታው እንደሚካሄድ በማሰብም የሁለቱም ቡድኖች ተጫዋቾች ወደ ሜዳ ገብተው ልምምዳቸውን ጨርሰው ዳኞችም ለመጫወት ብቁ መሆናቸውን ቲሴራቸውን ተመልክተው እያረጋገጡ ባለበት ቅፅበት የፀጥታ አካላት ከበላይ አካል በተሰጠ ትዕዛዝ መሰረት ጨዋታው እንዳይደረግ የሚል ውሳኔ አሳልፈው ጨዋታው ሳይጀመር እንዲቋረጥ ተደርጓል።የባህርዳር ከተማ ክለብ አመራሮች በውሳኔው እጅግ አዝነው ሜዳውን ለቀው የወጡ ሲሆን ቅሬታቸውንም ለጨዋታው ኮሚሽነር አቅርበዋል። ረጅም ርቀት አቋርጠው ክለባቸውን ለመደገፍ የመጡ ጥቂት የማይባሉ የባህርዳር ከተማ ደጋፊዎች ከአንዴም ሁለቴ ጨዋታው በመቋረጡ ከፍተኛ እንግልት እንደደረሰባቸው ተናግረው ፌዴሬሽኑ ውድደሮችን የመምራት አቅሙ ላይ ችግሮች እንዳለበት ገልፀዋል። በሽረ እንዳስላሴ በኩል ደግሞ አስቀድመው ጨዋታው ከጥር 22 በኋላ በአአ ስታዲየም መካሄድ እንዳለበት በተደጋጋሚ ብንጠይቅም ፌዴሬሽኑ በእንቢተኝነት ውሳኔ በመወሰኑ ጨዋታው ለመቋረጥ በቅቷል ብለዋል።ፌዴሬሽኑ በቀጣይ ጨዋታው መቼ እንደሚደረግ አላሳወቀም፡፡
| 0 |
b7323fe0166fbd209ee15ae379332869
|
200025d6a1cd9a6ee0021a587e992197
|
በአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ አራተኛ ቀን ጨዋታዎች አባ ጅፋር እና ባህር ዳር አሸንፈዋል
|
በክረምቱ የዝውውር መስኮት ጅማ አባ ጅፋርን ከተቀላቀሉ ተጫዋቾች መካከል ይስሀቅ ይስሀቅ መኩርያ አንዱ ነው።
ይስሀቅ ያለፉትን ሁለት ዓመታት በፋሲል ከነማ በአማካይ ተከላካይነት እና በመሀል አማካይነት ተጫውቶ ያሳለፈ ሲሆን
ጅማ አባ ጅፋር በክረምቱ የዝውውር መስኮት የአማካይ ስፍራ ተጫዋቾቹ መልቀቃቸውን ተከትሎ ያለበትን ክፍተት ይሸፍናል ብሎ በማመን አስፈርሞት ነበር።ሆኖም ከክለቡ አመራሮች እንዳገኘነው መረጃ በቅድመ ውድድር ዝግጅት በአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ ላይ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች የተጨዋቹ አቋም እንደተጠበቀው ሆኖ ባለመገኘቱ ውሉ እንደተቋረጠ ሰምተናል። በሌላ በኩል ተጨዋቹ ለሶከር ኢትዮጵያ በሰጠው አስተያየት በክለቡ አመራሮች የተሰጠው አስተያየት ተገቢ እንዳልሆነ የተናገረ ሲሆን ከቡድኑ የተቀነሰውም እግር ኳሳዊ ባልሆነ ምክንያት መሆኑን እንደሚያምን ተናግሯል።
| 0 |
606691727b299834873e7b856d391765
|
3d5a7780d31b8c66bb4d1771ab497853
|
ከጅቡቲ ወደ ኢትዮጵያ ድንበር የተዘረጋው የባቡር መስመር ተመረቀ
|
በጋዜጣው ሪፖርተር አዲስ አበባ ፦ የኤሊዳአር በልሆ ወረዳ የመካከለኛ መስመር የኤሌክትሪክ ዝርጋታ ተጠናቆ ተመረቀ፡፡ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው ፣ የኤሊዳአር በልሆ ወረዳ የመካከለኛ መስመር የኤሌክትሪክ ዝርጋታ ተጠናቆ ተመርቋል ፤በቅርቡ ስራ ይጀምራል ፡፡የጋላፊ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ አብዱ አሊ በምረቃው ወቅት ፣ፕሮጀክቱ ተጠናቆ አገልግሎት ላይ መዋሉ ለጉምሩክና ኢሚግሬሽን አገልግሎት የላቀ ጥቅም ይሰጣል ብለዋል። ከዚህ በፊት የጉምሩክና ኢሚግሬሽን አገልግሎት ሥራዎች በጄኔሬተር ይሰጥ እንደነበር አስታውሰው ÷ ስራዎችን በተያዘለት ጊዜና በተገቢው መንገድ ለማከናወን ይቸገሩ እንደነበር አመልክተዋል፡፡የፕሮጀክቱ መጠናቀቁ ስራዎቻቸውን በተቀላጠፈ መልኩ ለማከናወን እንደሚረዳቸውም ጠቁመዋል፡፡የኤሊዳአር ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የአቅም ግንባታ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብደላ ሱሌ በበኩላቸው አገልግሎቱ በወረዳዋ የኢኮኖሚ መነቃቃት እና ለወጣቶችም የስራ እድል እንደሚፈጥር አስታውቀዋል፡፡በምርቃቱ ላይ የተገኙት የአፋር ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ስራ አስፈፃሚ አቶ ያሲን አሊ ፣ ፕሮጀክቱ በተያዘለት በጀትና በሚፈለገው ጊዜ መጠናቀቁ ለስራው መቀላጠፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው አስታውቀዋል።የኤሌክትሪክ መስመሩ ኢትዮጵያ በጅቡቲ ድንበር ከምትጠቀምባቸው ወደቦች አንዱ የሆነው የታጁራ ወደብ ምስረታ ጋር ተያይዞ የተዘረጋ ነው ፡፡አዲስ ዘመን ህዳር
30/2013
| 0 |
47321db720e733ee86fc6ba92c3df15a
|
59f0e0b622f5535ed51ffead891765a8
|
በቻይና ውሃን ግዛት ተጨማሪ 19 ጊዜያዊ ሆስፒታሎች ሊገነቡ ነው
|
በቻይና ሁቤይ ግዛት በአዲሱ የኮሮና ቫይረስ የሚያዙና የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር በክፍተኛ መጠን መጨመሩ ተገለጸ፡፡በሁቤይ ግዛት በአዲሱ አደገኛ ቫይረስ 242 ሰዎች ሕይወታቸው ማለፉና ይህም ከወረርሽኙ መቀስቀስ አንስቶ ከፍተኛው አሀዝ መሆኑ ታውቋል፤ በቻይና በኮሮና ቫይረስ የሞቱትን ሰዎች ቁጥር ከ1 ሺህ 350 እንዲበልጥም አድርጎታል፡፡ 14 ሺህ 840 ሰዎች ደግሞ በበሽታው መያዛቸው ተረጋግጧል፤ በአጠቃላይ በቻይና በቫይረሱ የተጠቁት ሰዎች ቁጥርም ወደ 60 ሺህ ተጠግቷል፡፡በሁቤይ የኮሙዩኒስት ፓርቲው ኃላፊ ተነስተውም በሻንጋይ ፓርቲ ኃላፊ ተተክተዋል፤ የውኃን ከተማ የፓርቲ ኃላፊም ከኃላፊነታችው ተነስተዋል፡፡ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በተነሳባት ሁቤይ ግዛት እንዲህ ዓይነት ፖለቲካዊ እርምጃ ሲወሰድ ከወረርሽኙ በኋላ የመጀመሪያው ነው ተብሏል፡፡ምንጭ፡- ቢቢሲበአብርሃም በዕውቀት
| 0 |
a847be708a2192653f47c274e470c78c
|
a847be708a2192653f47c274e470c78c
|
የጌዲኦና ጉጂ ተፈናቃዮች ቁጥር 970,000 ደርሷል ተባለ
|
በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞንና በደቡብ ክልል ጌዲኦ ዞን ካለፈው ሚያዝያ ወር አንስቶ በተቀሰቀሱ ግጭቶች ከመኖሪያቸው የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር 970 ሺህ ያህል መድረሱን አለማቀፉ የስደተኞች ድርጅት ትናንት ባወጣው መረጃ አስታውቋል፡፡በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ በተከሰቱ ግጭቶች ከደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች ክልል ጌዲኦ ዞን 822 ሺህ 187፣ ከኦሮምያ ክልል ጉጂ ዞን ደግሞ 147 ሺህ 40 ሰዎች መፈናቀላቸውን ያስታወቀው ድርጅቱ፣ ተፈናቃዮቹ ትምህርት ቤቶችንና የመንግስት ተቋማትን ጨምሮ በተለያዩ ስፍራዎች ተጠልለው እንደሚገኙ አመልክቷል፡፡አለማቀፉ የስደተኞች ድርጅት ባለፉት ግንቦትና ሰኔ ወራት ባደረገው ጥናት በመላ አገሪቱ 1.7 ሚሊዮን ዜጎች በአገር ውስጥ ተፈናቅለው እንደሚገኙና ከእነዚህም መካከል 1.2 ሚሊዮን ያህሉ በግጭት ሳቢያ የተፈናቀሉ መሆናቸውን ማረጋገጡን ዥንዋ ዘግቧል፡፡
| 1 |
d8a2569e32ab3fb3a6029b1945c2adda
|
7873b01e587e60dfcc6526c2eeb168f8
|
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የመጨረሻ ልምምዱን አከናውኗል
|
ከሶማሊያ አቻው ጋር ነገ በአዲስ አበባ ስታድየም በአፍሪካ ዞን የኦሊምፒክ ቅድመ ማጣርያ ጨዋታውን የሚያደርገው ከ23 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን የመጨረሻ ልምምዱን ሰርቷል።ከጥቅምት 21 ጀምሮ ዝግጅቱን አጠናክሮ እየሰራ የሚገኘው የኢትዮጵያ ከ23 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ባሳለፍነው ሳምንት አርብ ከሱዳኑ አል ሒላል ኦቢዬድ ጋር የወዳጅነት ጨዋታ በማድረግ 2-0 በሆነ ውጤት ማሸነፉ ይታወቃል።የቡድኑን አቅም ለማሳደግ በማሰብ ከዋናው ብሔራዊ ቡድን አማኑኤል ገ/ሚካኤል እና ተመስገን ካስትሮ ተካተው የነበረ ሲሆን በተጨማሪም ከንዓን ማርክነህ ከባለፈው እሁድ ጀምሮ ከቡድኑ ጋር ተቀላቅሎ ልምምድ መስራት መጀመሩን ለማወቅ ችለናል።በዛሬው ጠዋት 03:30 በጀመረው የመጨረሻ ልምምድ ጊዜም ሁሉም የብሔራዊ ቡድኑ አባላት በሙሉ ጤንነት ላይ በመሆን ቀለል ያሉ ልምምዶችን ሰርተዋል። ከዋና ብሔራዊ ቡድን ጥሪ የተደረገላቸው አማኑኤል ገ/ሚካኤል ፣ ተመስገን ካስትሮ እና ከንዓን ማርክነህ ደግሞ ዛሬ እረፍት ተሰጥቷቸው በልምምድ ወቅት ያልነበሩ ቢሆንም ለነገው ጨዋታ ዝግጁ መሆናቸው ተነግሮናል።ነገ በ10:00 አዲስ አበባ ስታድየም የሚደረገውን የኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ጨዋታ ቱኒዚያዊያኑ ጉዊራት ሀይተም (ዋና) ፣ ረምዚ ሔርች (ረዳት) እና ኸሊል ሀሰን (ረዳት) የሚመሩት ይሆናል። ከዚህ በተጨማሪ የስቴዲየም የተመልካች መግቢያ ዋጋ በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መደበኛ የመግቢያ ዋጋ መሠረት እንደሆነ ፌዴሬሽኑ አሳውቋል።
| 0 |
67939861f3027b8e97637bcde83ce0c5
|
a8700cc74bb3312179942cd67771a09e
|
የህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ውይይት በአዲስ አበባ ተካሄደ
|
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር በትናንትናው እለት ቀጥሎ መካሄድ ጀምሯል።የኢትዮጵያ፣ የሱዳን እና የግብፅ የውሃ ሚኒስትሮች የተሳተፉበት የሶስትዮሽ ድርድሩ በቪዲዮ ኮንፍረንስ መካሄድ መጀመሩንም ነው የኢፌዴሪ የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ያስታወቀው።የአፍሪካ ህብረት በሚመራው ድርድሩ ላይም ታዛቢዎች እና የአፍሪካ ህብረት የመረጣቸው የዘርፉ ባለሙያዎች ተሳታፊ መሆናቸውም ተገልጿል።በሶስትዮሽ ድርድሩ ላይም የኢፌዴሪ የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ፥ ኢትዮጵያ እንደ ከዚህ ቀደሙ ፍትሓዊና ምክንያታዊ ተጠቃሚነትን መሠረት ባደረገ እንዲሁም ሁሉንም ወገን ተጠቃሚ ባደረገ መልኩ ድርድሩን ለመቋጨት ትሰራለች ብለዋል።የኢትዮጵያ፣ የሱዳን እና የግብፅ መሪዎች ባስቀመጠጡት አቅጣጫ መሰረትም በግድቡ የውሃ ሙሌት እና በሌሎች ጉዳዮች ላይ አጠቃላይ ስመምነት ላይ መድረስ እንደሚገባም ገልፀዋል።የሶስቱ ሀገራት የውሃ ሚኒስትሮች የህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር አካሄድ ላይ ከስምምነት የደረሱ ሲሆን፥ ድርድሩም ለቀጣይ ሁለት ሳምንታት ቀጥሎ የሚካሄድ ይሆናል።በሁለት ሳምንታት የድርደር ሂደቱም ከሶስቱ ሀገራት የውሃ ሚኒስትሮች ስብሰባ በተጓዳኝ የዘርፉ ባለሙያዎች ስብሰባዎች እንዲሁም ከታዛቢዎች እና ከዘርፉ ባለሙያዎች ጋር ምክክሮች እንደሚደረጉም ነው የተመላከተው።በአፍሪካ ህብረት መሪነት ለ11 ቀናት ሲካሄድ የቆየው የታላቁ ህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ባሳለፍነው ሐምሌ 6 2012 ዓ.ም መቋረጡ ይታወሳል።ድርድሩ ተቋርጦ የቆየውም በሱዳን በኩል በቀረበው የይዘግይልኝ ጥያቄ መሠረት ሲሆን፥ ከትናንት ከሰዓት ጀምሮ መካሄድ ጀምሯል።#FBCየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
| 0 |
f3501cb24bbff77798b63702f59ed5e2
|
f3501cb24bbff77798b63702f59ed5e2
|
አሜሪካ ኢትዮጵያና ኤርትራ ግንኙነታቸውን ለማሻሻል የጀመሩትን እንቅስቃሴ እደግፋለሁ አለች
|
አሜሪካ ኢትዮጵያና ኤርትራ ግንኙነታቸውን ለማሻሻል የጀመሩትን እንቅስቃሴ ለመደገፍ ዝግጁ መሆኗን ገለጸች።ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ሐምሌ 1 እና 2 ቀን 2010 ዓ.ም በኤርትራ አስመራ ባደረጉት ጉብኝት ከአገሪቷ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር አገራቱ ያለባቸውን አለመግባባት ወደ ጎን በማድረግ ግንኙነታቸውን ማጎልበት በሚችሉበት ላይ ተወያይተዋል።አገራቱ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን በድጋሚ ለመጀመር በኢኮኖሚና ሌሎች መስኮች በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት መፈራረማቸውና መሪዎቹ ለሁለቱ አገራት ህዝቦች ተጠቃሚነት ለመስራት ከመግባባት ላይ ደርሰዋል።አሜሪካም የሁለቱ አገራት መሪዎች ውይይት ለሰላምና ለደህንነት ቁርጠኛ መሆናቸውን የሚያሳይና ይህንንም እንደምታደንቅ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ ማይክ ፖምፒዮ በኩል ገልጻለች።የሁለቱ አገራት ስምምነት ለ20 ዓመት የቆየውን ጦርነት በይፋ እንዲቆም ያደረገ እንደሆነም አስታውቃለች።ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድና የኤርትራ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ዜጎቻቸውን ወደ ሰላም፣ ብልጽግናና ፖለቲካዊ ማሻሻያ የሚመራ ብርታት የተሞላበት ቁርጠኝነታቸው ምስጋናዋን አቅርባለች።ሁለቱ አገራት ግንኙነት መጀመራቸውና የተፈራረሙት የሰላምና የወዳጅነት ስምምነት የአገራቱ ዜጎች የጋራ ህልም በሆነው የኢኮኖሚ፣ ፖሊቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች የቀረበ ትስስር እንዲያተኩሩ መልካም እድልን እንደሚፈጥርም ተገልጿል።ኢትዮጵያና ኤርትራ የጀመሩትን ሂደት አሜሪካ ለመደገፍ ዝግጁ እንደሆነች ገልጻ፤ ሁሉም አካላት በቀጣይ ጊዜያት በግልጽነትና በመተማመን እንዲሰሩ ጠይቃለች።በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል ሰላም መኖር ለአፍሪካ ቀንድና ለቀይ ባህር መረጋጋት፣ ሰላም፣ ደህንነትና ልማት መሰረት እንደሚሆን ነው የአሜሪካ መንግስት ያስታወቀው።
| 1 |
3a85d2f095f29de7d4a763fcb064e19d
|
3254facc96272236d657b06cf7995ea3
|
ሀዲያ ሆሳዕና አይቮሪኮስታዊውን አጥቂ አስፈረመ
|
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 5፣ 2013 (ኤፍቢሲ) በ2013 የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታ ሀዲያ ሆሳዕና አሸነፈ፡፡ሀዲያ ሆሳዕና ዛሬ ረፋድ ጨዋታውን ከወላይታ ድቻ ጋር አኳሂዷል፡፡በጨዋታውም ሀዲያ ሆሳዕና ወላይታ ድቻን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ረቷል፡፡የወላይታ ድቻን አንድ ግብ ቸርነት ጉግሳ በመጀመሪያው አጋማሽ አስቆጥሮዋል፡፡ሀዲያ ሆሳዕናን አሸናፊ ያደረጉትን ግቦች ደግሞ ዳዋ ሁቴሳ እና ዱላ ሙላቱ በ60 ኛው እና በ79ነኛው ደቂቃ ማስቆጠር ችለዋል፡፡ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
| 0 |
1dcf7c5cd2188c7a49b11d5fea39f6ae
|
1dcf7c5cd2188c7a49b11d5fea39f6ae
|
የሰራዊታችን የአሸናፊነት ሚስጥር ህዝባዊነቱ ነው- ጠ/ሚ ኃይለማርያም
|
Normal 0 false false false MicrosoftInternetExplorer4 /* Style Definitions */
table.MsoNormalTable
{mso-style-name:”Table Normal”;
mso-tstyle-rowband-size:0;
mso-tstyle-colband-size:0;
mso-style-noshow:yes;
mso-style-parent:””;
mso-padding-alt:0in 5.4pt 0in 5.4pt;
mso-para-margin:0in;
mso-para-margin-bottom:.0001pt;
mso-pagination:widow-orphan;
font-size:10.0pt;
font-family:”Times New Roman”;
mso-ansi-language:#0400;
mso-fareast-language:#0400;
mso-bidi-language:#0400;}አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 30/2005 (ዋኢማ) – የሃገር መከላከያ ሠራዊትን የመፈጸም አቅም ወደላቀ ደረጃ ለማሳደግ የተከናወኑት ስራዎች በትክክለኛው አቅጣጫ ላይ እንደሚገኙ የአ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የጦር ሃይሎች ጠቅላይ አዛዥ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ገለጹ፡፡የሃገር መከላከያ ከፍተኛ አመራሮችና የሥራ ሃላፊዎች ያለፈውን ዓመት የሥራ አፈጻጸም በጥልቀት የገመገሙ ሲሆን በአዲሱ ዓመት ዕቅድ ላይም ውይይት አካሂደዋል፡፡በውይይቱ ላይ የተገኙት የጦር ሃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ኃይለማርያም ደሳለኝ እንደገለጹት ባለፈው ዓመት የሠራዊቱን ግዳጅ የመፈጸም ብቃት ለማጎልበት የተከናወኑት ሁሉን አቀፍ የአቅም ግንባታ ሥራዎች ስኬታማ ነበሩ፡፡ በቀጣዩም ዓመትም ይሄው ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ አስታውቀዋል፡፡የመከላከያ ሰራዊታችን ትልቁ የአሸናፊነት ሚስጥር ህዝባዊ ባህሪው ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባለፈው ዓመት የሀገር መከላከያ ሰራዊን ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች ሲከበር ለህዝብ እይታ የቀረበው የሰራዊቱ አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴ የሠራዊቱን የወትሮ ዝግጁነት፤ የብቃት ደረጃና ተልዕኮን የመፈፀም አቅም ያመላከተ ነው ብለዋል፡፡የሰራዊት ቀኑ የኢትዮጵያ ህዝቦች በሠራዊቱ ይበልጥ እንዲተማመኑና ድጋፋቸውን አጠናክረው ለመቀጠል ያላቸውን ቁርጠኝነት ያረጋገጡበት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ኢትዮጵያ የነደፈችው ፈጣን ዕድገት የማስመዝገብ ስትራቴጂ የህዝቡን ፍትሐዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ የገለጹት ጠቅላይ ሚንስትሩ ከፍተኛ ጥረት የሚጠይቀውን የኢትዮጵያን ህዳሴ የማረጋገጥ ሥራ በህዝቦች ዙሪያ መለስ ተሳትፎ ተጠናክሮ በመቀጠል ላይ መሆኑን አመልክተዋል፡፡በቀጣዩም ዓመት ሠራዊቱ የህዝቡን የልማት ጉዞ የሚያደናቅፉ ሃይሎችን በጽናት በመታገል ህገ-መንግሥታዊ ተልዕኮውን በተለመደው ህዝባዊ ኃላፊነት እንዲወጣ የጦር ሃይሎች ጠቅላይ አዛዥ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡ (መከላከያ ሚኒስቴር)
| 1 |
d24ebec03dcf9835df215730a335cad3
|
ff5a4aab402557cc8acb599d5762ac02
|
በመዲናዋ ለወጣቶች 5 ቢሊየን ብር የሚገመት የገበያ ትስስር ለመፍጠር እየተሰራ ነው
|
አዲስ አበባ ፣ መስከረም 5 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ ) ዘንድሮ ለየት ባለ ሁኔታ የአዋሽ ወንዝ ሞልቶ ያስከተለው የጎርፍ አደጋ በርካታ ጉዳቶችን እያደረሰ ነው።ወንዙ አቅጣጫ በቀየረበት አፋር ክልል ደግሞ ዜጎች እንዲፈናቀሉና ንብረታቸው እንዲወንድም ከማድረጉ ባለፈ የደረሱ ምርቶችን ከጥቅም ውጪ አድርጓል።የተከሰተው የውሀ ፍሰት ባስከተለው የጎርፍ አደጋ በአንድ ወረዳ ብቻ ከ14 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ የደረሰ ምርት አውድሟል።በዚህም የሸንኮራ አገዳና ጥጥ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ምርቶች መሆናቸው ተገልጿል።አብዛኛው ከጥቅም ውጪ የሆነው የደረሰና ከመስከረም አራት ጀምሮ ሊሰበሰብ የነበረ ምርት መሆኑም ተመላክቷል።ከዚያም ባለፈ በደረሰው ውድመት በእርሻ ልማት ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶችና አርሶ አደሮች ለከፍተኛ ችግር እየተዳረጉ መሆናቸው ተገልጿል።በዚህም የአሚባራ መካከለኛ አዋሽ የእርሻ ልማት ድርጅትን ብቻ ከ 1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ወድሞበታል።ድርጅቱ በስሩ በተለያየ መንገድ ቀጥሮ የሚያሰራቸው 5 ሺህ የሚደርሱ ሰራተኞች ስራ መፍታታቸው ተነግሯል ።በ6 ሺህ 17 ሄክታር መሬት ከ1 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት የደረሰ ምርት የወደመ ሲሆን÷ በመገልገያ እቃዎች ላይም ከ300 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት መውደሙ ተገልጿል።የገጠመውን ችግር ለመፍታትም የክልል እና የፌዴራል መንግስት ከፍተኛ ርብርብ እያደረጉ መሆኑ ነው የተገለፀው።በኃይለኢየሱስ ስዩም
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
| 0 |
9119c06b82f78b4977c623a029fe8acd
|
162934865a685426a3901235b90d27f6
|
በበጀት አመቱ ከ2 ቢሊየን 823 ሚሊየን በላይ ኪሎ ዋት ስዓት የኢነርጂ ሃይል ብክነትን በመቀነስ 1 ቢሊየን ብር ማዳን ተቻለ
|
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 10 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት 9 ወራት ከወጪ ንግድ ከ2 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ።ሚኒስትሩ በበጀት አመቱ ዘጠኝ ወራት 2 ነጥብ 68 ቢሊየን ዶላር ገቢ ለማግኘት አቅዶ 2 ቢሊየን 900 ሺህ ዶላር ማግኘቱን አስታውቋል።አፈፃጸሙ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ10 በመቶ ጭማሪ እንዳለውም ገልጿል።በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ዓለም ላይ የንግድ ግንኙነት የተቀዛቀዘ ቢሆንም ኢትዮጵያ እያመረተች ያለው ለምግብነት የሚውሉ ምርቶች በመሆናቸው ገቢው ሊጨምር መቻሉን በንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ወንድሙ ፍላቴ ተናግረዋል።ዳይሬክተሩ አበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ እና ጫት በዘጠኝ ወራት ከተያዘላቸው እቅድ በላይ አፈፃጸም ያስመዘገቡ ሲሆን የብዕርና አገዳ እህሎች፣ የተፈጥሮ ሙጫና ዕጣን፣ ቡና፣ ኤሌክትሮኒክስ እንዲሁም ጨርቃ ጨርቅና አልባሳት የእቅዳቸውን 75 በመቶ አፈጻጸም አሳይተዋልም ነው ያሉት።እንዲሁም ታንታለም፣ የቅባት እህሎች፣ የጥራጥሬ ሰብሎች፣ ስጋ፣ ቅመማ ቅመም፣ ባህር ዛፍ እና ሻይ ቅጠል የእቅዳቸውን ከ50 እስከ 74 በመቶ ገቢ ማስገኘታቸውን ጠቅሰዋል።በአንፃሩ ወርቅ፣ ቆዳና የቆዳ ውጤቶች እንዲሁም የቁም እንስሳት የእቅዳቸውን ከ50 በመቶ በታች አስመዝግበዋል ማለታቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።#FBCየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
| 0 |
f2784573f3448fc5c888359b443b544f
|
f7f051bb8c0043994fed9680df7c47d4
|
በሳዑዲ ፈቃድ የሌላቸው ዜጎች በቀሩት ቀናት ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ጥሪ ቀረበ
|
ለሐጅ ሃይማኖታዊ ሥነ ሥርዓት ወደ መካ የተጓዙ ምዕመናንን ጨምሮ ለተጓዦች የምሥጋና አቀባበል ዝግጅት ያደረጉ 180 ኢትዮጵያውያን፣ ባለፈው ሳምንት በሳዑዲ ዓረቢያ ጂዳ ከተማ የፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ፡፡በእንዲህ ዓይነት ሃይማኖታዊ ጉዞዎች ላይ መሰባሰብና ማመስገን የተለመደ መሆኑን በመጠቆም ክስተቱን ለሪፖርተር ያስረዱት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የቆንስላ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄኔራል አቶ ዮሐንስ ሸዴ፣ በሥፍራው የተሰባሰቡ ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ያላቸውን ሰዎች ጨምሮ ሁሉም በቁጥጥር ሥር እንደዋሉ ገልጸዋል፡፡ ይሁን እንጂ በዕለቱ በጂዳ የሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽሕፈት ቤት ጉዳዩን በመከታተል፣ 70 የመኖሪያ ፈቃድ ያላቸው ኢትዮጵያውያን ወዲያውኑ እንዲፈቱ ማድረጉን አስረድተዋል፡፡ አሥር ያህል ተጓዦችና ሌሎች ታሳሪዎችም በተከታታይ ቀናት እንዲፈቱ መደረጋቸውንም አክለዋል፡፡‹‹እስከ 100 የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን እስካሁን በቁጥጥር ሥር ይገኛሉ፡፡ ሆኖም ፈቃድ የሌላቸው በመሆናቸው ከሳምንት በኋላ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ይደረጋል፤›› ሲሉ አቶ ዮሐንስ አስረድተዋል፡፡ከዚህ ውጪ ተጓዦችን ከነዋሪዎች ጋር ያገናኘው ስብሰባ ከማኅበራዊ ሚና የዘለለ ሌላ ዓላማ አልነበረውም ሲሉ አክለዋል፡፡ጉዳዩን አስመልክቶ መግለጫ ያወጣው የቆንስላ ጽሕፈት ቤቱ፣ ‹‹የቆንስላ ጽሕፈት ቤቱ ስለክስተቱ መረጃ ከደረሰው ወቅት አንስቶ የሃይማኖት አባቶች፣ ዲፕሎማቶች፣ ምሁራንና ታዋቂ ግለሰቦችን ያካተተ አጣሪ ኮሚቴ እንዲዋቀር በማድረግ፣ ጉዳዩን የማጣራት ሥራ የጀመረ ከመሆኑም ባሻገር የኢፌዴሪ መንግሥትም ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለው እንደሆነ ለመግለጽ እንወዳለን፤›› ብሏል፡፡የተዋቀረው የአጣሪ ኮሚቴም የጉዳዩን መነሻ ምክንያት ለማወቅ እየሠራ እንደሚገኝም ቆንስላ ጽሕፈት ቤቱ ገልጿል፡፡የዘንድሮ የሐጅ ጉዞ ሐምሌ 5 ቀን ዓ.ም. የተጀመረ ሲሆን፣ 15 ሺሕ የሚጠጉ ተጓዦች ወደ ሥፍራው ማቅናታቸው አይዘነጋም፡፡ የሳዑዲ ዓረቢያ የሐጅ ሚኒስቴር ለኢትዮጵያ የሐጅ ጉዞ የሰጠው ኮታ 43,337 ቢሆንም፣ ከዚህ ቀደም ከአሥር ሺሕ በላይ ምዕመናን ተጉዘው እንደማያውቁ ይነገራል፡፡
| 0 |
dfb5fdddba325226a4bd137468d6906e
|
f7d07d00250c76487984b2262290f4a7
|
ከ20 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከድል መልስ ዝግጅቱን እየከወነ ይገኛል
|
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች የሴቶች ብሄራዊ ቡድን ለአለም ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያ ከቡሩንዲ አቻው ጋር በቡጁንቡራ ባደረገው ጨዋታ በመጀመሪያው የጨዋታ አጋማሽ 4 ለባዶ እየመራ ወጥቶ ፣ ከረፍት መልስ ተጨማሪ አንድ ግብ በማስቀጠር በድምር ውጤት 5 ለ 0 አሸንፏል፡፡
ምርቃት ፈለቀ፣ታሪኳ ዴቢሶ፣ አረጋሽ ካልሳና ረድኤት አራቱን ግቦች ሲያስቆጥሩ፣ የታንዛኒያ ተከላካይ ደግሞ በራሷ ላይ አንዱን ግብ ማስቆጠሯን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል ፡፡
ብሔራዊ ቡድኑ ከሜዳው ውጭ በሰፊ የጎል ልዩነት ማሸነፉ ከ20 ዓመት በታች ለአለም ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያ የሚያደርገውን ጉዞ የሚያሳምርለት ነው፡፡
ምንጭ፡- የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን
| 0 |
4da51cc7b17e391e886e4a8009d89880
|
3fe0d4d9853d9ecb2eb81405a4bade95
|
የናይጀርያ ወታደራዊ ሃይል ቦኮ ሐራምን እስከ መጪው ታህሳስ ወር ባለው ጊዜ እንደሚደመስስ አስታወቀ
|
የመጀመሪያው የአዲሱ ብሔራዊ ጦር ልምምድ ተጠናቆ የፊታችን ጥር ወር ሥራውን ይጀምራል፤ የአውሮፓ ሕብረት ወታደራዊ አሰልጣኞች በቀጣዩቹ ሁለት ዓመት ውስጥ እስከ 2ሺሕ ወታደሮችን አሰልጥነው ያወጣሉ ተብሎም ይጠበቃል። የማዕከላዊ አፍሪካ ሠራዊት፣ በማካሄድ ላይ ባለው የነፍስ-አድን ልምምድ፤ የተራቀቀ ትርዒት በማሳየት ላይ ይገኛል።ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
| 0 |
708fe31672ede4fcea7d40af3d6e56f1
|
708fe31672ede4fcea7d40af3d6e56f1
|
ለዜጎች የሚደረገው ጥንቃቄና ሰብዓዊ ድጋፍ የሚደነቅ ነው – የትግራይ ተወላጆች
|
በአዳማ ከተማ የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች በመንግስት እየተወሰደ ባለው የህግ ማስከበር ሂደት እና በሀገሪቱ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡በውይይቱ በንጹሃን ዜጎች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ እየተደረገ ያለው ጥንቃቄ እና የሰብዓዊ ድጋፍ የሚደነቅ መሆኑን ተወላጆቹ ተናግረዋል፡፡በከተማዋ ደህንነታቸው እና መብታቸው ተጠብቆ ለረዥም አመታት መኖራቸውን ያነሱት ተወላጆቹ አጥፊው የትህነግ ቡድን ላይ በመንግስት እየተወሰደ ያለውን እርምጃ እንደሚደግፉ ተናግረዋል፡፡በውይይቱ የትግራይ ህዝብ ነጻነት ግንባር (ትህነግ) ፅንፈኛ ቡድንን መንግስት ለህግ ለማቅረብ እየሠራ ነው ያሉት የአዳማ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አለማየሁ ቱሉ በህግ የማስከበር ተግባሩ የትግራይ ህዝብ እና ትህነግ አንድ እንዳልሆኑ በተግባር የታየበት ነው ብለዋል፡፡በዚህም በከተማዋ በርካታ ብሄር ብሄረሰቦች ተዋደው እና ተከባብረው የሚኖሩባት እንደመሆኑ ይህ ሰላማዊ የሆነ አካሄድ ለማስቀጠል እንደሚሰራም ኃላፊዊው ተናግረዋል፡፡የትህነግ ቡድን አባላትን ለህግ ለማቅረብ የሚደረገው ሂደት በመደገፍ ለሀገር ሰላም መረጋገጥ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የድሻውን መወጣት እንደሚገባም ተገልጿል፡፡ (በብዙአየሁ ወንድሙ)
| 1 |
a901fa06493ff94f14dfc3a5da29881f
|
ae2a7c041d20545009f7293cbac324ae
|
አቶ ኤርሚያስ አመልጋ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ፍርድ ቤት ቀረቡ
|
‹‹የተጠረጠርንበት ጉዳይ ከተዘጋ በኋላ ማን ለምን እንዳሰረን አናውቅም››አቶ በረከት ስምዖንና አቶ ታደሰ ካሳ ከጥረት ኮርፖሬት ኩባንያዎች ጋር በተያያዘ በከባድ የሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት አቶ በረከት ስምዖንና አቶ ከበደ ካሳ፣ የዋስትና መብታቸውን ለማስከበር ጥያቄ ማቅረብ እንደሚችሉ ፍርድ ቤት ነግሯቸው እየተዘጋጁ ቢሆንም፣ የክልሉ የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ዓቃቤ ሕግ የመቃወሚያ አቤቱታ አቅርቦባቸዋል፡፡ የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ማክሰኞ መጋቢት 24 ቀን 2011 ዓ.ም. በተጠርጣሪዎች ላይ ሲደረግ የነበረውን የምርመራ መዝገብ ለዘጋው የባህር ዳርና አካባቢው ከፍተኛ ፍርድ ቤት ባቀረበው የዋስትና መቃወሚያ እንደገለጸው፣ ሁለቱ ተጠርጣሪዎች የሚከሰሱበት የሕግ አንቀጽ የፀረ ሙስና አዋጅ ቁጥር 881 አንቀጽ 13 (3) ነው፡፡ ይኼ ድንጋጌ ደግሞ ከአሥር ዓመታት እስከ 25 ዓመታት ሊያስቀጣቸው የሚችል ድንጋጌ መሆኑንም አክሏል፡፡ በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩና ከአሥር ዓመታት በላይ በሚያስቀጣ ወንጀል የተከሰሰ ሰው ደግሞ ዋስትና ስለሚከለከል፣ እነ አቶ በረከት ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ውድቅ እንዲደረግ ፍርድ ቤቱን ጠይቋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ አቶ በረከትና አቶ ታደሰ ባቀረቡት የመቃወሚያ ክርክር እንደተናገሩት፣ እነሱ ነፃ ሰዎች ናቸው፡፡ ክስም የለባቸውም፡፡ ከሳሽም የለም፡፡ የተጠረጠሩበት ጉዳይና ሲደረግባቸው የከረመው የምርመራ መዝገብ ተዘግቷል፡፡ ለምን ፍርድ ቤት እንደቀረቡ እንደማያውቁ፣ ክስ ሳይመሠረትባቸው በተዘጋ መዝገብ በምንና በየትኛው የሕግ አግባብ እንደታሰሩ እንደማያውቁ ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል፡፡የግራ ቀኙን ክርክር የሰማው የባህር ዳርና አካባቢው ፍርድ ቤትም፣ የክርክሩን ሐሳብ ከተገቢው የሕግ አግባብ ጋር መርምሮ ለመወሰን ለሐሙስ መጋቢት 26 ቀን 2011 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
| 0 |
83a691f6bef338204ca65f5e011cfdbb
|
642f388ca317dcb491bd4fbbf54fe3e7
|
በዶ/ር መረራ ጉዲና ላይ የቀረበው ክስ እንዲሻሻል ብይን ተሰጠ
|
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሣይንስና ዓለምአቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል ተባባሪ ፕሮፌሰር ዶክተር መረራ ጉዲና የሥራ ኮንትራት መቋረጥ ከትምህርት ክፍሉ ሊቀመንበር ተቃውሞ ገጥሞታል።“…በዚህ ሁኔታ በኃላፊነቴ መቀጠሉ ከሞራል አንፃር ተቀባይነት የሉም…” ያሉት የዚሁ የፖለቲካ ሣይንስና ዓለምአቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል ሊቀመንበር ዶክተር ካሣሁን ብርሃኑ የመልቀቂያ ደብዳቤ አስገብተዋል።“…የዩኒቨርሲቲው ውሣኔ ፖለቲካዊ ነው…” ያሉት ዶክተር መረራ ጉዲና በበኩላቸው ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት እንደሚወስዱ ተናግረዋል።ለዝርዝሩ የእስክንድር ፍሬውን ዘገባ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
| 0 |
4ca44eb82418d402bd8d3b6f01e7b860
|
730303449cb29aaa6b359cf98fd424b4
|
የድርጊት መርሃ ግብሩ የሰብአዊ መብቶችን በተቀናጀ መልኩ ለማስከበር የተዘጋጀ ነው -መንግስት
|
የለውጡን የአንድ አመት ጉዞ በማስመልከት ሀገር አቀፍ ህዝባዊ የውይይት መድረክ በባህር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡በውይይቱ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ዶክተር አምባቸው መኮንንን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የባህርዳር ከተማ ነዎሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡በዚህ ሀገር አቀፍ የውይይት መድረክም በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያተኩሩ ፅሁፎች ይቀርባሉ፡፡በመድረኩ ዶክተር አለማየሁ ዋሴ፣ አቶ ሙላቱ ገመቹ፣ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ፣ አቶ ዮሐንስ ቧያለው፣ አቶ ልደቱ አያሌው፣ አቶ ደሴ ጥላሁን፣ ዶክተር አረጋዊ በርኼ፣ ዶክተር ንጉሴ ምትኩ፣ አቶ በለጠ ሞላ እና ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ናቸው ጹሑፎቻቸውን የሚያቀርቡት፡፡መርሃ ግብሩ በአማራ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት እና በባህር ዳር ወጣቶች ትብብር የተዘጋጀ ነው ተብሏል፡፡ (ኤፍ.ቢ.ሲ)
| 0 |
626ea5b8e6e20248303b357fb189100a
|
626ea5b8e6e20248303b357fb189100a
|
በሁለት ወራት ብቻ ለ74 የኢንቨስትመንት ፈቃድ መስጠቱን ከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ፡፡
|
ባሕር ዳር፡ መስከረም 26/2013ዓ.ም (አብመድ) በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር በኢንቨስትመንት የተሰማሩ ባለሀብቶች ከ31 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል አስመዝግበዋል፡፡በተያዘው ዓመት ከ300 በላይ ለሚሆኑ ፕሮጀክቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ለመስጠተ ማቀዱን የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ገለጸ፡፡ ባለፈው ዓመት የ3 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላላቸው 112 ኢንቨስትመንቶች ፈቃድ ለመስጠት ታቅዶ ነው ከ245 በላይ ፈቃድ የተሰጠው፡፡ በበጀት ዓመቱ ፈቃድ የተሰጠው ወደ 17 ቢሊዮን ብር ገደማ ላስመዘገቡ ባለሀብቶች ነው፡፡ ከእነዚህም መካከል ወደ 90 በመቶ ገደማ የሚሆኑት በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የሚሠማሩ መሆናቸውን የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ጽሕፈት ቤት አስታውቀዋል፡፡ በተለይ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ፣ የአልባሳት እና ጨርቃጨርቅ፣ የእንጨት እና ብረታብረት ሥራ፣ የኬሚካል ቅመማ ዘርፎች የተሻለ ተሳትፎ እንዳላቸው የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ ብርሃን ገብረሕይወት አስታውቀዋል፡፡ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ከግምት ውስጥ በማስገባትም በተያዘው ዓመት ከ300 በላይ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ለመስጠት ታቅዷል፡፡ ባለፉት ሁለት ወራትም ለ74 የተለየዩ ፕሮጀክቶች ፈቃድ መሰጠቱ ታውቋል፡፡በአካባቢው አስተማማኝ ሰላም መስፈን፣ ሰፊ የኢንቨስትመንት አማራጭ እና አስተማማኝ ግብዓት መኖር፣ ማኅበረሰቡ ኢንቨስትመንቱን በባለቤትነት መንከባከቡ እና የመንግሥት ፈጣን መሥተንግዶ መኖር እቅዱን በውጤታማነት ለማሳካት አስቻይ ሁኔታዎች መሆናቸውም ተመላክቷል፡፡በሌላ በኩል በ2012 በጀት ዓመት የታዩ ክፍተቶችን ለማስተካከል ጠንከር ያለ ግምገማ መደረጉን አቶ ብርሃን አንስተዋል፡፡ በተለይም የመብራትና የውኃ መሠረተ ልማቶች አለመሟላት ቀዳሚ ችግሮች ናቸው፡፡ በከተማ አስተዳደሩ የሚፈቱ ችግሮች በፍጥነት እንደሚስተካከሉ ያነሱት የጽሕፈት ቤት ኃላፊው የመብራት ችግሩ እንዲፈታ ለክልሉ ጥያቄ መቅረቡን አመልክተዋል፡፡ቦታ አጥሮ ማስቀመጥም ሌላው ችግር ነው፡፡ በከተማዋ ካለው የቦታ እጥረት አንጻር አጥረው የሚቀመጡ ባለሀብቶችን እየተከታተሉ መሬት እየተቀማ ለሌሎች ባለሀብቶች እየተላለፈም ነው፡፡ ባለፈው ዓመት በሊዝ ውላቸው መሠረት ፈጥነው ግንባታ ያልጀመሩ 80 ባለሀብቶችን በመቀማት በፍጥነት ለሚያለሙ ባለሀብቶች መተላለፉ ለዚህ አብነት መሆኑም ተመላክቷል፡፡
| 1 |
026bd329fa0da76c7073b753aee7a539
|
ed78aa9eb4bf95923fe79fea5e8ac5b6
|
ሀድያ ሆሳዕና አጥቂ አስፈረመ
|
ወደ ፕሪምየር ሊጉ የተመለሰው ሀዲያ ሆሳዕና ሦስት አዳዲስ ተጫዋቾችን ማስፈረሙን አስታውቋል።
ሆሳዕና ካስፈረማቸው መካከል ሁለቱ ተጫዋቾች ዓመቱን በከፍተኛ ሊግ ለአርባምንጭ በመጫወት ያሳለፉትና ከዚህ ቀደም የክለቡ ተጫዋቾች የነበሩት የመስመር ተጫዋቹ መስቀሉ ለቴቦ እና ተከላካዩ በረከት ወልደዮሀንስ ናቸው።ሌላው ክለቡን የተቀላቀለው የመስመር ተጫዋቹ ሱራፌል ዳንኤል ነው። በመስመር ተከላካይነት እና አጥቂነት መጫወት የሚችለው ሱራፌል ድሬዳዋ ከተማን ከለቀቀ በኋላ በ2011 ለአዳማ ከተማ በመጫወት ማሳለፉ ይታወሳል።ከሦስቱ ፈራሚዎች በፊት ሄኖክ አርፊጮ፣ ደስታ ጊቻሞ፣ አብዱሰመድ ዓሊ፣ ብሩክ ኤልያስ እና ይሁን እንዳሻውን ወደ ቡድኑ የቀላቀለው ሀዲያ ሆሳዕና የአሰልጣኝ ግርማ ታደሰን ውል ማራዘሙ የሚታወስ ሲሆን የስምንት ተጫዋቾች ውል መታደሱንም ለማወቅ ተችሏል። ከነዚህም መካከል ቡድኑ ወደ ፕሪምየር ሊግ እንዲያድግ ቁልፍ ሚና የተወጡት ትዕግስቱ አበራ፣ ሱራፌል ጌታቸው፣ ዮሴፍ ደንገቱ ፣ ፍራኦል መንግስቱ እና እዮኤል ሳሙኤል ይጠቀሳሉ።
| 0 |
0c4597102ca57106a867c0137e00153a
|
6e735edea7c4e3b6c17ed37a94adc0e4
|
ባለፉት 24 ሰዓታት ለ1 ሺህ 764 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 11 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል
|
አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 21 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰአታት ለ18 ሺህ 060 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 1 ሺህ 186 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ። ከዚህ ባለፈም ባለፉት 24 ሰአታት የ 20 ሰዎች ህይወት ማለፉን የገለፁት ሚኒስትሯ በቫይረሱ ሳቢያ ለህልፈት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር 745 ደርሷል። በተጨማሪም ባለፉት 24 ሰአታት 518 ሰዎች ሲያገግሙ ይህን ተከትሎም ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 16 ሺህ 819 ደርሷል። አሁን ላይ 330 ሰዎች ደግሞ በፅኑ ህክምና ክፍል ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛሉም ነው ያሉት። በኢትዮጵያ እስካሁን ለ831 ሺህ 470 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 46 ሺህ 407 ሰዎች ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል። ከዚህ ውስጥ 16 ሺህ 819ኙ ሲያገግሙ 28 ሺህ 831 ሰዎች ደግሞ የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል። #FBCየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
| 0 |
3b4b6d4f503e5df1049a6ba2470e2d04
|
e57c14cc0d962d35f19b2f00deb4570a
|
የደቡብ ሱዳን የመገበያያ ገንዘብ
|
የተመድ ዋና ፀሃፊ በደቡብ ሱዳን ጉዳይ ላይ ከሱዳን መሪዎች ጋር ውይይት ካካሄዱ በኋላ በአፍሪካ የኢኮኖሚ አዳራሽ በሠጡት መግለጫ እንደተናገሩት ሁለቱ ተቀናቃኝ ወገኖች ለደቡብ ሱዳን ህዝብን ለማቆም ሲባል እየቀጠለ የመጣውን ጦርነት ማቆም ይገባቸዋል ብለዋል ።እንደ ባንኪሙን ገለጻ የደቡብ ሱዳን ህዝብ ለአንድ ዓመት ከግማሽ ያህል ለአለአስፈላጊ ጮርነት መዳረጉን ገልጸው የሁለቱ ተቀናቃኝ ወገኖች መሪዎች ቁርጠኝነት ጦርነቱን ለማቆምና የደቡብ ሱዳንን መጸኢ ዕድል ለመወሰን ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል ።ባንኪሙን በዛሬው ዕለት ከሱዳን መሪዎች ጋር ውጤታማ ውይይት ማካሄዳቸውን ጠቁመው የሱዳን መንግሥት የትኛውንም የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለማስወገድ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር ተባብሮ መሥራት እንዳለበት መነጋገራቸውን ገልጸዋል ።የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ዶክተር ዲላያሚዙማ በበኩላቸው የደቡብ ሱዳን ግጭት ላይ የሚደረገው ድርድር እየከፋ የመጣውን ሰብዓዊ ቀውስ ለማቆም ሲባል እንደገና መጀመሩን ጠቅሰው ኢጋድና የአፍሪካ ህብረት በሁለቱ ተቀናቃኝ ወገኖች መካከል የሚካሄደውን ሽምግልና ለመደገፍ የተጠናከረ ጥረት መቀጠሉን ገልጸዋል ።የተለያዩ የአፍሪካ መሪዎች ቀደም ሲል ሁለቱ ወገኖች የፈረሟቸውን ስምምነቶች ተግባራዊ እንዲያደርጉ ግፊት ለማሳደር ጥረት እያደረጉ መሆኑን ያስረዱት ዶክተር ዲላያሚዙማ የመጨረሻው አልባት እስኪገኝ ድረስ ጥረቱ ይቀጥላል ብለዋል ።በደቡብ ሱዳን በተፈጠረው ግጭት እስካሁን ድረስ 1ነጥብ 6 ሚሊዮን የደቡብ ሱዳን ዜጎች የተፈናቀሉ ሲሆን 6መቶ ሺ የሚሆኑት በጎረቤት አገራት ተጠልለው ይኖራሉ ።
| 0 |
9f9b35d2387faa0932a400ad684e48cd
|
71bde9fe46938d92e946e1025a57d2bd
|
አልቤንያ በደረሰው ርዕደ መሬት የሞቱት ሰዎች ብዛት 27 ደረሰ
|
ዩናይትድ ስቴትስ ሰሜናው ካሊፎርኒያ ሲነድ ይሰነበተው ሰደድ እሳት የገደለው ሰው ብዛት ቢያንስ አርባ ሁለት ደረሰ። በክፍለ ሃገሩዋ ታሪክ ከደረሱት ሁሉ ባጠፋው የሰው ህይወት ብዛት የከፋው ሆኗል።ፓራዳይዝ የምትባለውን ከተማ ለአራት ቀናት በተከታታይ ባዳረሳት ሰደድ እሳት ምክንያት እስካሁን ያልተገኙ በመቶዎች የተቆጠሩ ሰዎች እንዳሉ ባለሥልጣናት ገልፀዋል።ደቡባዊ ካሊፎርኒያ ውስጥ የደረሱት ቃጠሎውች ደግሞ ሁለት ሰዎችን ገድለዋል።የካሊፎርኒያ አገረ ገዢ ጄሪ ብራውን አስቸኳይ ጊዜ ያወጁ ሲሆን የገንዘብ ዕርዳታም ጠይቀዋል።ትናንት ሰኞ ማታ የካሊፎርኒያውን የሰደድ እሳት “ከባድ አደጋ” ብለው የገለጹት ፕሬዚደንት ዶናልድ ትረምፕ በቃጠሎው ለተጎዱ መርጃ የሚሆን ገንዘብ ከፌዴራል መንግኅት ወጪ እንዲደረግ ፈቅደዋል።
| 0 |
442a49c308da0d870d625e06ac74addb
|
442a49c308da0d870d625e06ac74addb
|
ፕሪምየር ሊግ | የተለያዩ የቅጣት ውሳኔዎች ተወስነዋል
|
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የስምንተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ትናንት መጠናቀቃቸውን ተከትሎ አወዳዳሪው አካል የተለያዩ የቅጣት ውሳኔዎችን አሳልፏል። ከአንድ ቀን እረፍት በኋላ ዘጠነኛ ሳምንቱን ነገ የሚጀምረው ሊጉ በ8ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በተከሰቱ ግድፈቶች ላይ የሚከተሉት ውሳኔዎች አሳልፏል።– የሰበታ ከተማ ቡድን መሪ የሆነው አቶ አንበስ መገርሳ ማከሰኞ ጥር 11 ቀን 2013 ክለቡ ከባህርዳር ከተማ ጋር ባደረገው የ8ኛ ሳምንት ጨዋታ ካለቀ በኋላ የዕለቱን ዳኛች አፀያፊ ስድብ መሳደባቸው ከዋና ዳኛውና ከጨዋታ ታዛቢ ሪፖርት የቀረበባቸው በመሆኑ የቡድን መሪው ለፈፀሙት ጥፋት በፌዴሬሽኑ የዲሲፕሊን መመሪያ መሠረት 6 ጨዋታ እንዲታገዱና 5000 ብር ቅጣት እንዲከፍሉ ወስኗል። አቶ አንበስ መገርሳ የሊግ ካምፓኒው የቦርድ አባል መሆናቸው ይታወቃል።-የሰበታ ከተማው ግብ ጠባቂ ሰለሞን ደምሴ ክለቡ ከባህር ዳር ከተማ ጋር ያደረገው ጨዋታ ካለቀ በኋላ የዕለቱን ዳኛች አፀያፊ ስድብ መሳደቡ ከዋና ዳኛውና ክጨዋታ ታዛቢ ሪፖርት
ቀርቦበታል። ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በፌዴሬሽኑ የዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት 3 ጨዋታ እንዲታገድ እና 3000 ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲከፍል ወስኗል።– ሌላው የሰበታ ከተማ ተጫዋች ያሬድ ሀሰን ከባህር ዳር ከተማ ባደረጉት ጨዋታ 71ኛ ደቂቃ ላይ ዳኛን አፀያፊ ስድብ በመሳድብ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል። በዚህም 3 ጨዋታ እንዲታገድ እና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 3000 እንዲከፍል ተወስኗል።
| 1 |
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.