query_id
stringlengths
32
32
passage_id
stringlengths
32
32
query
stringlengths
2
182
passage
stringlengths
137
1.88k
label
int64
0
1
74a63d450ad3d21517b6fe7afeaa424c
70f54be1d53d91f502de84bf38067b42
የድሬዳዋ የስፖርት ተቋማት ድጋፍ ማድረጋቸውን ቀጥለዋል
ዳንኤል እና መሐሪ አድሐኖም ለአቅመ ደካማ አረጋውያን ድጋፍ አድርገዋል፡፡የኮሮና ቫይረስን ለመግታት እና ለቅድመ ጥንቃቄ ይረዳ ዘንድ በርካቶች በቁሳቁስ እና በገንዘብ ድጋፋቸውን ማድረግ ቀጥለዋል፡፡ በስፖርቱ ዘርፍ የተሰማሩ የተለያዩ አካላትም እየተረባረቡ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ለደደቢት እየተጫወተ የሚገኘው የመስመር ተከላካዩ ዳንኤል አድሐኖም እና ለከፍተኛ ሊጉ ሶሎዳ ዓድዋ እየተጫወተ የሚገኘው ወንድሙ መሐሪ አድሐኖም በዓድዋ ከተማ ለሚገኙና ከቤታቸው መውጣት ለማይችሉ አቅመ ደካማ አረጋዊያን ገንዘብ በማውጣት ቁሳቁሶች እና ምግቦችን ዛሬ ከሰዓት ለግሰዋል፡፡
0
aa18916339f8331564abe27223ffb77a
aa18916339f8331564abe27223ffb77a
የአሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ ይካሄድ ይሆን ?
የ2011 የውድድር ዘመን የፕሪምየር ሊጉ ቻምፒዮን መቐለ 70 እንደርታ እና የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊው ፋሲል ከነማ መካከል የአሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ ጨዋታ መቼ ይካሄድ ይሆን?የፕሪምየር ሊጉ ዐቢይ ኮሚቴ ዛሬ ባደረገው የመጀመርያው ስብሰባ በዚህ ጨዋታ ዙርያ ምንም እንዳልተነጋገረ አረጋግጠናል። ይህ ውድድር አዲሱን የፕሪምየር ሊግ ኮሚቴን የማይመለከት እና በቀድሞ የሊግ ኮሚቴ የሚመራ በመሆኑ ጉዳዩን ሳይመለከቱት እንደቀሩ ሰምተናል።ፌዴሬሽኑ በዚህ ውድድር ዙርያ ያሰበው ነገር ካለ ብለን ለማጣራት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው ያልተሳካ ሲሆን የውድድሩ መካሄድ አለመካሄዱን አስመልክቶ በቀጣይ መረጃዎችን ካገኘን የምንመለስበት ይሆናል።በፌዴሬሽኑ ትኩረት ማጣት በተለያዩ ጊዜያት አንዴ እየተካሄደ ሌላ ጊዜ ደግሞ ሳይካሄድ እየቀረ ሲቆራረጥ የቆየው የኢትዮጵያ አሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ ጨዋታ ዘንድሮም የመካሄዱ ነገር አጠራጣሪ አድርጎታል።
1
0185ba9f3910d149c7afaa7c270d04c4
b82fe68eb69d7af72d987d0d6a3a3590
20ኛው የአማራ ክልል የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም በደብረብርሃን እየተካሄደ ነው
አዲስ አበባ ፣ መስከረም 22 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) 2ኛው የኢሬቻ የሰላም ፎረም በሸራተን አዲስ እየተካሄደ ነው።የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ኦሮሞ ወደ ቀደመ ማንነትና እሴቶቹ እንዲመለስ የክልሉ መንግስት በከፍተኛ ሁኔታ እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።ወንድማማችነትን ማጠናከር እና ነፃነትን ማረጋገጥ እጅጉን አስፈላጊ ነው ብለዋል አቶ ሽመልስ።የገዳ ስርአትን በትምህርት ስርአቱ ውስጥ ለማካተት የተደረገውን ጥረት ያነሱት ርዕሰ መስተዳድሩ ገዳ የሁሉም የህይወት አካል እንዲሆን በተግባር እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በበኩላቸው በቀጣይ አመት በተሻለ እና ባማረ ሁኔታ እናከብር ዘንድ ዘንድሮን በጥንቃቄ ማሳለፍ ያስፈልጋል ብለዋል። የኢሬቻን በዓል በተሻለ ለማስተዋወቅ እና ግንዛቤ ለመፍጠር እና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በማይዳሰሱ ቅርስነት ለማስመዝገብ ዓለም አቀፍ እና ሃገር አቀፍ ፎረሞች እንደሚካሄዱም በመድረኩ ተገልጿል፡፡በመድረኩ ላይ ጥናታዊ ፅሁፎች ቀርበው ውይይት የሚካሄድባቸው ይሆናል፡፡በፎረሙ ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው፣ የተለያዩ ሃገራት ዲፕሎማቶች፣ የፌደራልና የክልል አመራሮች፣ የዩኔስኮ ተወካዮች፣ አባ ገዳዎችን ጨምሮ 250 ተሳታፊዎች ተገኝተዋል፡፡የገዳ ስርአት 2009 ዓ.ም አዲስ አበባ በተካሄደው 11ኛው የዩኔስኮ የማይዳሰሱ ቅርሶች ጉባኤ ላይ በቅርስነት መመዝገቡ ይታወሳል፡፡በሀብታሙ ተክለስላሴ
0
045d4566da2c238e36fc9358a97eb9fe
429151a4a2c20fd888cbd186a3544086
መከላከያ ምንያምር ጸጋዬን ዋና አሰልጣኝ አድርጎ ሾመ
ሀዋሳ ከተማ ቅዱስ ዘሪሁንን የክለቡ የግብ ጠባቂ አሰልጣኝ በማድረግ ቀጥሯል፡፡የረጅም ዓመት የክለቡን አምበል እና ተጫዋች የነበረውን ሙሉጌታ ምህረትን በቅርቡ ሀይቆቹ በዋና አሰልጣኝነት መንበር ለአንድ ዓመት ከግማሽ ወራት ቆይታ መቅጠራቸው ይታወሳል፡፡ አሰልጣኙም ከተቀጠረ በኃላ ከዚህ ቀደም አብሮት የተጫወተው እና የተስፋ ቡድን አሰልጣኝ የነበረውን ብርሀኑ ወርቁ (ፈየራ) ሁለተኛ ረዳት አሰልጣኝ አድርጎ መምረጡ ይታወሳል፡፡ የግብ ጠባቂ አሰልጣኝ ፍለጋ ላይ የቆየው ክለቡም ወጣቱን አሰልጣኝ ቅዱስ ዘሪሁንን የክለቡ የግብ ጠባቂ አሰልጣኝ በማድረግ በአንድ አመት የውል ኮንትራት መሾሙን የክለቡ ስራ አስኪያጅ አቶ ኡቴሳ ኡጋሞ ለሶከር ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡በተጫዋችነት ዘመኑ ለደቡብ ፖሊስ፣ ለባቱ ከተማ፣ አርሲ ነገሌን ለመሳሰሉ ክለቦች ከዚህ ቀደም የተጫወተው አሰልጣኝ ቅዱስ እግር ኳስን ካቆመ በኋላ በሀዋሳ ከተማ ውስጥ የታዳጊ ህፃናትን ከማሰልጠን አንስቶ ወጣት ታዳጊ ቡድኖችን በወሰደው የሲ ላይሰንስ እና የግብ ጠባቂ የአሰልጣኝነት ስልጠና መሠረት ረዘም ላለ ዓመት እያሰለጠነ በርካታ ተጫዋቾችን አፍርቷል ፡፡ አሰልጣኙ ከዚህም በተጨማሪ የደቡብ ክልል የእግርኳስ ቡድኖችን በተለያየ ወቅት በዋና አሰልጣኝነት የመራ ሲሆን በያዝነው አመት ተሰናባቹን አሰልጣኝ አዲሴ ካሳን ያለምንም ኮንትራት በቅርብ ርቀት ሲያገለግል ከቆየ በኃላ ነው በይፋ የተሾመው፡፡
0
744d93b75113bbfe48ee3d5947bfdf8a
84d6525eb2f5f7cfb49c5236a139100c
ለአፍሪካ ዕድገት ጥቃቅኑን የሥራ ዘርፍ መደገፍ
የጥረት ኮርፖሬት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አምላኩ አስረስ በሥራ አመራር አፈጻጸማቸው የክብር ፕሮፌሰር ማዕረግ ተሰጣቸው፡፡ባሕር ዳር፡ ታኅሣሥ 08/2013 ዓ.ም (አብመድ) መቀመጫውን እንግሊዘ ሀገር ኦክስፎርድ ያደረገው የአውሮፓ የንግድ ጉባዔ (Europe Business Assembly (EBA)) የተባለ ተቋም ለጥረት ኮርፖሬት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አምላኩ አስረስ ዘውዴ የክብር የፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጣቸው፡፡በሥራ አመራራቸው የምጣኔ ሀብታዊና ማኅበራዊ ዕድገት ለማምጣት፣ በማስተማርና ምርምር ዘርፍ ውጤታማ የተቋም ስነ አመራርን በመተግበር ተቋሞቻቸውን ወደ ከፍታ በማድረስ ለተመረጡ በሚሰጠው “የሶቅራጠስ ሽልማት” ለዶክተር አምላኩ አስረስ ዘውዴ የክብር ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ተሰጥቷቸዋል፡፡ዶክተር አምላኩ አስረስ ቀደም ሲል በመሯቸው የአማራ መልሶ መቋቋም ድርጅትንና የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ላይ አመርቂ ውጤትያስመዘገቡ ሲሆን የባንክ ኢንደስትሪን ጨምሮ በልዩ ልዩ ተቋማት የሥራ አመራር ቦርድ ዳይሬክተር በመሆን እስካሁን ድረስ እያገለገሉ ያሉና በተቋማቱ ዕድገት ላይ አሻራቸውን በማሳረፍ ላይ የሚገኙ መሪ ናቸው፡፡ዶክተር አምላኩ አስረስ የከፍተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በእርሻ ኢኮኖሚክስ ከመጀመሪያ እስከ ሶስተኛ ድግሪያቸውን በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ተከታትለዋል፡፡የግብርና ባለሙያ ሆነው በሰሩበት የወጣትነት ዘመናቸው “ታታሪና መልካም ስነምግባር ያለው ኤክስፐርት ናቸው” ሲሉ የሥራ ባልደረቦቻቸው ይመሰክራሉ ፡፡እ.አ.አ ከ ግንቦት ወር 2018 ጀምሮ 19 ኩባንያና 10 ፕሮጀክቶችን ከ 11 ሺህ በላይ ሰራተኞች ጋር ለሚያስተዳድረውና በችግር ውስጥ ተዘፍቆ የቆየውን ጥረት ኮርፖሬትን በዋና ሥራ አስፈጻሚነት እንዲመሩም ተሰይመዋል፡፡
0
25a956093105b40fe359426aeb7fc977
25a956093105b40fe359426aeb7fc977
ሰመራ የፌዴሬሽኑ ምርጫን ለማስተናገድ ዝግጅቷን ማጠናቀቋ ተገለፀ
የሰው ሰር መገኛ ምድር አፋር የፊታችን እሁድ በሚደረገው የፌዴሬሽን ምርጫ እንግዶቿን ለመቀበል ዝግጅቷን ማጠናቀቋን አዘጋጅ ኮሚቴው አሳወቀ።የኢትዮዽያ እግርኳስ ፌዴሬሽንን ለቀጣዩ አራት አመታት የሚመሩት ፕሬዝዳንት እና ስራ አስፈፃሚ አባላትን ለመምረጥ ከመስከረም 30 ጀምሮ በተለያዩ ምክንያቶች ሳይደረግ ቆይቶ በእግርኳሱ የበላይ አካል ፊፋ አስገዳጅ ውሳኔ መሰረት የፊታችን እሁድ ግንቦት 26 በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ ሊደረግ የመጨረሻ ቀጠሮ ተይዞለታል።ሰመራ ከአንዴም ሁለቴ ምርጫውን ለማካሄድ በተሰጣት እድል መሰረት ለሆቴል እና ለመስተንግዶ ከፍተኛ ወጪ በማውጣት እንግዶቿን ለመቀበል እየተጠባበቀች ባለችበት ወቅት ምርጫው በመራዘሙ ከፍተኛ ኪሳራ እንዳስተናገዱ የሚገልፁት የአዘጋጅ ኮሚቴ አባላት በአሁኑ የመጨረሻ የምርጫ ቀጠሮ የፊታችን እሁድ ግንቦት 26 ሰመራ ላይ የሚደረገውን ምርጫ በጥሩ ሁኔታ ለማካሄድ እንደተዘጋጁ ገልፀዋል።” ምንም እንኳ ወቅቱ ለክልሉ ህዝብ የረመዳን ፆም ወር መሆኑ አስቸጋሪና አድካሚ ቢያደርግም የሚመጡት የስብሰባ ተሳታፊዎችን በሙሉ በጥሩ እንግዳ ተቀባይነት ባህል ተቀብሎ ለመሸኘት በሆቴል፣ በመስተንግዶ፣ በትራንስፖርት እና በሌሎች አስፈላጊ ጉዳዮች ሁሉ የክልሉ አስተዳደር እና ህዝብ ዝግጅታቸንን አጠናቀን እንግዶቻችንን ለመቀበል እየጠበቅን እንገኛለን።” በማለት የአዘጋጅ ኮሚቴው አባል የአፋር ክልል እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝደንት አቶ መሀመድ ያዮ ለሶከር ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
1
edff9455f8cacaf95de4460381168011
edff9455f8cacaf95de4460381168011
ለኔዘርላንድ ኩባንያ የተሰጠውን የጤፍ የባለቤትነት መብት ለማሰረዝ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ክስ እንዲመሠርት ተወሰነ
የኢትዮጵያን የባለቤትነት መብት በመጣስ ለኔዘርላንድ ኩባንያ የተሰጠውን የጤፍ አዘገጃጀት ፓተንት (መብት) ለማሰረዝ ሲደረግ የቆየው ድርድርና ውይይት ባለመሳካቱ፣ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ መደበኛ ክስ እንዲመሠረት መወሰኑን የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂነር) ግንቦት 7 ቀን 2010 ዓ.ም. ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዘጠኝ ወራት ሪፖርት ሲያቀርቡ፣ በአምስት የአውሮፓ አገሮች ለኔዘርላንድ ኩባንያ በጤፍ ዱቄት አዘገጃጀት የተሰጠውን የባለቤትነት መብት ለማሰረዝ ብዙ ጥረትና አድካሚ ውይይቶች ቢደረጉም ምንም ውጤት ሊገኝ አለመቻሉን ገልጸዋል፡፡‹‹በተለይም ባለፉት ዘጠኝ ወራት ሰፊ ሥራዎች ከተሠሩ በኋላ አገራችን በጤፍ መስክ ያጣችውን መብት ለማስመለስ፣ ወደ ፍትሕ አካላት መሄድ ብቸኛው መፍትሔ መሆኑን ታምኖበታል፤›› ሲሉ ለምክር ቤቱ አስረድተዋል፡፡‹‹ወደ ፍትሕ አካላት መሄድን ሚኒስቴር መሥሪያ ቤታችን በፅኑ በማመኑ ክስ እንዲመሠረት ለጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ጥያቄና ሰነዶችን ያቀረበ መሆኑን ምክር ቤቱ እንዲያውቅልን እወዳለሁ፤›› ሲሉ ሚኒስትሩ አስረድተዋል፡፡ከጤፍ ዝርያና አዘገጃጀት ጋር በተለይም ለሚኒስትሩ ተጠሪ በሆነው የኢትዮጵያ አዕምሮአዊ ንብረት ጽሕፈት ቤት አማካይነት፣ ሄልዝ ኤንድ ፕርፎርማንስ ኢንተርናሽናል ከተባለው ኩባንያ ጋር ሲወዛገብ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በጣሊያን፣ በእንግሊዝ፣ በጀርመን፣ በኦስትሪያና በኔዘርላንድ የተሰጠውን የባለቤትነት መብት ለማሰረዝ በቀጥታ ድርድርና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ጥረት ሲደረግ መቆየቱን፣ የአዕምሮአዊ ንብረት ጽሕፈት ቤት ሲገልጽ ነበር፡፡ይህ ጉዳይም በፓርላማም በተደጋጋሚ ጥያቄ ሲያስነሳ እንደነበር፣ መንግሥት የባለቤትነት መብቱን እንዲያስመልስ ግፊት ሲደረግ መቆየቱ በመደበኛ ስብሰባው ወቅት ተጠቅሷል፡፡ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ የተባለውን ክስ መቼ እንደሚጀምርና በየትኛው ዓለም አቀፍ የፍትሕ ተቋም የክስ መዝገብ እንደሚከፍት ባይገለጽም፣ ክሱ በአጭር ጊዜ እንደሚጀመር ተጠቁሟል፡፡
1
d8fb67a88358aa7614eeecb133a9abcb
4a1b433e0767dfb149311749c24422a8
የስቅለት በዓል በመላው አለም በሚገኙ ክርስቲያኖች ዘንድ በድምቀት ይከበራል
በመላው የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት የሚከበረውን የትንሳኤ በዓል ያለምንም ስጋት እንዲከበር ለማድረግ አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅቶችን ማጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ ።የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮማንደር ፋሲካው ፈንታ ለዋሚኮ እንደገለጹት የዘንድሮ የትንሳኤ በዓል ከዋዜማው አንስቶ በሰላምና በደስታ እንዲከበር ለማድረግ ፖሊስ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት ቅድመ ዝግጅቶችን በሙሉ አጠናቋል ።ከትንሳኤ በዓል ጋር ተያይዞ በአዲስ አበባ ከተማ ህዝብ በሚበዛባቸው የገበያ ፣ የመዝናኛና የትራንስፖርት ሥፍራዎች ላይ በቂ ቁጠጥርና ክትትል ለማድረግ እንዲቻል ኮሚሽኑ ዝግጅቶች ሲያካሄድ መቆየቱን ኮማንደር ፋሲካው ተናግረዋል ።በአዲስ አበባ ከተማ ከበዓሉ ጋር ተያይዞ ጠጥቶ ማሽከርከርን ለመቆጣጣር ከዋዜማው አንስቶ የትራፊክ ፖሊሶች እንደሚሠማሩ የገለጹት ኮማንደር ፋሲካው የትራፊክ ፍሰት መስተጓገል እንዳይፈጠር በአግረኛ ፣ በሞተረኛና በተሽከርካሪ የታገዘ ጥብቅ ቁጥጥር ይደረጋል ብለዋል ።ህብረተሰቡ በአቅራቢያው አጠራጣሪ ነገሮችን በሚያይበት ጊዜ እንደ ከዚህ ቀደም ሁሉ የነጻ የስልክ መሥመሮች የሆኑትን 991 እና 0111 1101 11 የስልክ መሥመሮችን በመጠቀም ወዲያውኑ ለፖሊስ እንዲያሳውቅ ኮማንደሩ ጥሪ አቅርበዋል ።በመጨረሻም ኮማንደር ፋሲካ ለመላው የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች የትንሳኤ በዓል የሰላም ፣ የደስታና የፍቅር እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል ።
0
1a5190b7f2c96ff60d47e6c7015357e8
1d87ae94990ab650f05f4d07c6d5bf12
ሊግ ዋንጫ ፡ የአዳነ ግርማ የመጨረሻ ደቂቃ ግብ ቅዱስ ጊዮርጊስን ወደ ግማሽ ፍፃሜው አሸጋግሮታል
በ2፡00 በተደረገው ጨዋታ ሆሳእና ከነማ ጅማ ከነማን 3-1 አሸንፏል፡፡ትላንት በተላለፈ ውሳኔ 4 ጨዋ እና 3 ሺህ ብር ተቀጥተው የነበሩት የጅማ ከነማው አሰልጣኝ ፋንታዬ አባተ የጨዋታ ቅጣቱ ተነስቶላቸው ቡድናቸውን ቢመሩም ከመሸነፍ አልዳኑም፡፡ግብ በማስቆጠር ቅድሚያውን የያዙት ጅማዎች ሲሆኑ አሸናፊ ይታየው በ17ኛው ደቂቃ ባስቆጠረው ግብ መምራት ችለው ነበር፡፡ በ24ኛው ደቂቃ ሀብቶም ገ/እግዚአብሄር ግብ አስቆጥሮ ሆሳእና ከነማን አቻ አድርጓል፡፡ ከእረፍት መልስ በ62ኛው ደቂቃ የጨዋታው ኮከብ ዱላ ሙላቱ ሆሳእናን መሪ ሲያደርግ ጨዋታው ሊገባደድ ሽርፍራፊ ሴኮንዶች ሲቀሩ አምረላ ደልታ የሆሳእናን ድል አስተማማኝ አድርጎታል፡፡ከጨዋታው በኋላ የሆሳእና ከነማው አሰልጣኝ ግርማ ታደሰ በሰጡት አስተያየት ወደ ፕሪሚር ሊጉ ከመግባት የሚያግዳቸው ነገር እደሌለ ተናግረዋል፡፡ ‹‹ ጅማ ከነማን እንደምናሸንፍ አስቀድመን ተናግረን ነበር፡፡ ነገር ግን በሜዳ ላይ ፈትነውን ነበር፡፡ እኛም ያገኘናቸውን እድለች በአግባቡ አልተጠቀምንም፡፡ በማሸነፋችን ደስተኞች ነን፡፡››‹‹ በግማሽ ፍፃሜው የምንገጥመውን ቡድን በሚገባ እናውቀዋልን፡፡ (ሀላባ ከነማ) ከዞናችን የመጣ ቡድን በመሆኑ አጨዋወታቸውን እናውቀዋለን፡፡ ወደ ፊት ከመጓዝ የሚያግደን ነገር የለም›› ብለዋል፡፡የተሸናፊው ቡድን አሰልጣኝ ፋንታዬ አባተ በበኩላቸው በስነልቡናው ረገድ አለመዘጋጀታቸው ውጤት እናዳሳጣቸው ተናግረዋል፡፡ ‹‹ ከሼር ኢትዮጵያ ጋር በተፈጠረው ውዝግብ ምክንያት ተረብሸናል፡፡ ያንን እያሰብን ወደ ሜዳ ስለገባን በስነልቡናው ረገድ የማሸነፍ ዝግጁነት አልነበረንም፡፡ በጨዋታው የበለጠው ቡድን አሸንፏል፡፡ ሆሳእናዎች እንኳን ደስ አላችሁ፡፡ የድሬዳዋ ህዝብንም ማመስገን እፈልጋለሁ፡፡ ›› ብለዋል፡፡ሆሳእና ከነማ በግማሽ ፍፃሜው ሃላባ ከነማን የሚገጥም ሲሆን ካሸነፈ በታሪኩ ለመጀመርያ ጊዜ ፕሪሚየር ሊግ መግባቱን ያረጋግጣል፡፡ ሁለቱ ቡድኖች እርስ በእርስ የሚጫወቱ በመሆናቸው አንድ የደቡብ ክለብ ፕሪሚየር ሊግ ከመግባቱ በተጨማሪ ከሁለቱ አንዳቸው በፕሪሚየር ሊጉ የተሳተፉ 43ኛው ክለብ ይሆናሉ፡፡ ፎቶ – ከላይ የሆሳእና ተጫዋቾች ከድሉ በኋላ ፣ መካከል – የሆሳእናው አሰልጣኝ ግርማ ፤ ከታች የጨዋው ኮከብ ተብሎ በድሬዳዋ ስፖርት ኮሚሽን እና ወጣቶች ቢሮ በጋራ የተመረጠው ዱላ ሙላቴ
0
7387134f898552c5027f0b9c8a90645a
e3e25937fc1f48288c1e9aca2b9b5684
የሃገር ሽማግሌዎች የሕወኃት ቡድን ከጅምሩ ልዩነቶች በሰላም እንዲፈቱ ምንም አይነት ፍላጎት አልነበረውም
"በኢትዮጵያ ያለው ሰላም፤ አገሪቱ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሥር ያለች አላስመሰላትም" ሲሉ የ28ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ስብሰባ ታዳሚዎች ተናገሩ።የመሪዎቹ ስብሰባም በተለያዩ ኩነቶች ለየት ባለ መልኩ እንደተካሄደ የስብሰባው ተሳታፊዎች ገልጸዋል።ኢትዮጵያ ባጋጠማት ሁከትና ግርግር ከመስከረም 28 ጀምሮ የአገሪቱን ሰላምና ደኅንነት ለመጠበቅ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጇ የሚታወስ ነው።በመንግሥታቱ ድርጅት የአፍሪካ ልዩ አማካሪ ማገድ አብድላዚዝ ለኢዜአ እንዳሉት "አገሪቱ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሥር ያለች አትመስልም፤ ምንም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምልክት የለም"።በከተማዋ በተለያዩ ቦታዎች በመሄድ ምንም አይነት የጸጥታ ችግር እንዳላጋጠማቸውና ሌሎችም ወደፈለጉበት ቦታ ያለምንም ገደብና ቁጥጥር በመሄድ አገልግሎት ሲያገኙ መቆየታቸውን ገልጸዋል።"ከዚህ በመለስ ስብሰባውም በሰላም ተጠናቋል፤ ሰላምን የሚያደፈርስ ምንም አይነት ችግር አላየሁም" በማለት አስተያየት ሰጥተዋል። "ኢትዮጵያ ሕብረ-ብሄራዊት አገር ብትሆንም ሁሉም በአንድ ላይ የሚኖሩ ህዝቦች ናቸው" ያሉት አማካሪው "የተለያዩ አመለካከቶች በተለያዩ የአፍሪካ አገራት ይደመጣሉ፤ ይሁንና ይህም ኢትዮጵያን አልጎዳትም "ብለዋል።28ኛው የመሪዎች ስብሰባ የተለየ እንደሆነና ስብሰባው የመንግሥታቱ ድርጅት ዋና ጸኃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝን መቀበሉን ለአብነት አንስተዋል። የመንግሥታቱ ድርጅትና የአፍሪካ ኅብረት በሰላምና ደኅንነት፣ በልማት እንዲሁም በሰብዓዊ መብት ላይ ተቀራርበው እንዲሰሩ የሚያስችሉ ውሳኔዎች ተላልፈውበታል ነው ያሉት።በኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝቦች ለስብሰባው ታዳሚዎች የተደረገውን እንግዳ አቀባበልም ምስጋና ሊቸራቸው ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።በአፍሪካ ኅብረት የኢንዱስትሪ ክፍል ኃላፊ ሃሰን ሁሴን በበኩላቸው "በኢትዮጵያ ሰላም አለ፤ በአገሪቱ ያለው ሁኔታም መልካም ነው" ብለዋል።ይህም አገሪቱ ሰላምና ልማት በማረጋገጥ ረገድ በትክክለኛ ጎዳና ላይ መሆኗን አመላካች እንደሆነ ጠቁመዋል።ስብሰባው በሰላም እንዲጠናቀቅ የኢትዮጵያ መንግሥት የጸጥታ ኃይሎችን በተገቢው መልኩ በመመደብ የተደረገው ርብርብ የሚበረታታ መሆኑን አንስተዋል።በዚህም ስብሰባው በሰላም ለማጠናቀቅ መቻሉን ነው ያስረዱት።28ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ስብሰባ፤ የኅብረቱን ሊቀ መንበርና ሌሎች በርካታ አህጉራዊ ውሳኔዎችን በማሳለፍ በትላንትናው ዕለት ተጠናቋል። (ኢዜአ)
0
c35b8cf7ae5ee13034a0993916a040f6
7224edbc2604030582eb06bf2d8b66f3
ለሃጅ እና ኡምራ ተጓዦች ቅድመ ሁኔታዎችን ማመቻቸት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ
አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 30 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ድጋፍ ለሚሰጡ የጤና እና ሌሎች ባለሙያዎች የህይወት መድን ሽፋን ለመስጠት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ።ስምምነቱን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ እና የኢትዮጵያ መድን ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ነጻነት ለሜሳ ፈርመዋል፡፡በስምምነቱ መሰረትም የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በተለያዩ የጤና ተቋማት ለሚሰሩ የጤና እና ለሌሎች ባለሙያዎች የህይወትና የአደጋ መድን ሽፋን ይደረግላቸዋል።ይህም በለይቶ ማቆያ፣ በኳራንቲን፣ በላብራቶሪ ምርመራ ማዕከል፣ በፈጥኖ ምላሽ ቡድን፣ በድንገተኛና በሌሎች ክፍል የሚሰሩ ባለሙያዎችን ይሸፍናል ተብሏል።ጎን ለጎንም ጽዳቶች፣ የአንቡላስ ሹፌሮችና ሌሎችም ፊት ለፊት የሚሰሩ ባለሙያዎች በዚሁ የህይወት መድን ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ከጤና ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
0
f382801c8a2ecd0cca4c573642f3bf9e
ab60b8859ca91d97e981d6457c4dffbe
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ጊዜያዊ ዋና ፀኃፊ ዛሬ ሾመ
በትናንትናው ዕለት በአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ኒጅርን ከጨዋታ ብልጫ ጋር ያሸነፈው ብሔራዊ ቡድኑ የማበረታቻ ሽልማት እና የምሳ ግብዣ ተደረገለት።ቡድኑ ከኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን እና ኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በተቀናጀ ሁኔታ ዛሬ ረፋድ ላይ በአያት ሪጀንሲ ሆቴል የምሳ ግብዣ የማበረታቻ ሽልማት እየተደረገለት ነው። በፕሮግራሙ የኢፊድሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ክቡር አቶ ኤሊያስ ሽኩር፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕረዚዳንት አቶ ኢሳይያስ ጅራ፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተ/ም/ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ እና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል ።በሽልማቱ ጉዳይ ዝርዝር መረጃ ባይወጣም ለብሔራዊ ቡድኑ ከፍተኛ የገንዘብ ሽልማት ሊበረከትለት እንደሚችል ሰምተናል።©ሶከር ኢትዮጵያ
0
172a84c90543f82984e7b8fde1376fe2
717de06cf99ad1adb89925837f58dd33
በካናዳ በተፈጸመ ጥቃት የ16 ሰዎች ህይወት አለፈ
አዲስ አበባ፣መጋቢት 1፣2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በሰሜን ሸዋ ዞን መሀል ሜዳ ከተማ በአንድ ግለሰብ በተወረወረ ቦምብ የሶስት ሰዎች ህይወት ማለፋን ፖሊስ አስታወቀ።የከተማ አስተዳደሩ ፓሊስ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ጥላሁን ደበበ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት፥ ድርጊቱ ትናንት ምሽት አንድ ሰዓት አካባቢ በከተማዋ 03 ቀበሌ በሚገኝ አንድ መጠጥ ቤት ነው የተፈጸመው።በተፈጸመው የቦምብ ጥቃትም የሶስት ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን፥ ሶስት ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል።ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ወደ ደብረ ብርሃን ሪፈራል ሆስፒታል ተልከው ህክም እየተደረገላቸው መሆኑንም ጠቁመዋል።ግለሰቡ ከፈጸመው የቦንብ ጥቃት በተጨማሪ በሽጉጥና በጩቤ 13 ሰዎችን ማቁሰሉ ተነግሯል።ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር ለማዋል ፖሊስ ክትትል እያደረገ መሆኑን ዋና ኢንስፔክተር ጥላሁን ደበበ ተናግረዋል።በአበበ የሸዋልዑል
0
eb5de7e87c5b0b864c1e23be2a10077b
eb5de7e87c5b0b864c1e23be2a10077b
ሰላማዊ ሰልፎቹ በሰላም ተጠናቅቀዋል፡፡
ሰላማዊ ሰልፎቹ በሰላም ተጠናቅቀዋል፡፡ዛሬ መስከረም 4/2012 ዓ.ም በአማራ ክልል በተለያዩ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፎች ተካሂደዋል፡፡በጎንደር፣ በወረታ፣ በደብረ ታቦር፣ በመቄት፣ በደሴ፣ በኮምቦልቻ፣ በነፋስ መውጫ፣ በመካነ እየሱስ፣ በመካነ ሰላም በምዕራብ በለሳ፣ በጎንደር ዙሪያ ወረዳ እና በሌሎችም ከተሞች ነው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ኃይማኖት ተከታይ ምዕመናን ዛሬ ሰላማዊ ሰልፍ ያካሄዱት፡፡
1
4db6bdcbe18cdef382b474563853960b
f4a95fb38889b417c85810c2e05e8034
90 ሺህ ሀሰተኛ የብር ኖቶችን በመጠቀም 20 ኩንታል ጤፍ የገዙት ግለሰቦች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 20፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ 300 ሺህ ብር የሚጠጋ ነባሩንና አዲሱን ሐሰተኛ የገንዘብ ኖት መያዙን አስታወቀ፡፡ፖሊስ ነባሩን የገንዘብ ኖት ከሁለት ተጠርጣሪዎች ሐሰተኛ የሆነ ባለ መቶና ባለ አምሳ 174 ሺህ 350 ብር ይዟል፡፡ከአንድ ግለሰብ ደግሞ ከ200 ሺህ በላይ ሐሰተኛ አዲሱ ባለ መቶና ባለ ሁለት መቶ የብር ኖት መያዙን ነው የገለጸው፡፡እንዲሁም ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሰረት 14 ሺህ 800 ሐሰተኛ ባለ መቶና ባለ ሃምሳ የአሜሪካ ዶላር ይዟል፡፡በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ የህገ-ወጥ ገንዘብ ዝውውር ቁጥጥር ዲቪዥን ኃላፊ አቶ ሽመልስ ጥበቡ በሐሰተኛ ነባሩ የብር ኖት አንድ የክስ መዝገብ እንዲሁም በሐሰተኛ አዲሱ የብር ኖት ደግሞ አራት የክስ መዝገቦችን በመክፈት እያጣራ መሆኑን ከኮሚሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
0
669adca6d195095da20a580a73273753
2b464374c357fa2e0311f20fa9c79baf
ተጨማሪ 54 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው የ5 ሰዎች ህይወት አልፏል
አዲስ አበባ፣ መስከረም 22፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ 6 ሺህ 916 የላቦራቶሪ ናሙና ምርመራ 890 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው መረጋገጡን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።በዚህም በአጠቃላይ እስካሁን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 76 ሺህ 988 ደርሷል።በሌላ በኩል ባለፉት 24 ሰዓታት ከኮሮና ቫይረስ ጋር ተያይዞ የ 3 ሰዎች ህይወት አልፏል።በዚህም በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ህይወታቸው ያለፈ ሰዎቸ ቁጥር 1 ሺህ 208 መድረሱን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በፌስቡክ ገፃቸው ላይ ያሰፈሩት መረጃ ያመለክታል።በ24 ሰዓታት ውስጥ 247 ሰዎች ከበሽታው ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ እስካሁን ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 31 ሺህ 677 ደርሷል።እንዲሁም 296 ፅኑ ህሙማን የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል ተብሏል።
0
de28d748b9111ffb69a843d852788780
de28d748b9111ffb69a843d852788780
ትረምፕ ፑቲን ጠላቴም ወዳጄም አይደሉም አሉ
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ የሩስያው አቻቸው ቭላዲሚር ፑቲን ጠላቴም ወዳጄም አይደሉም ብለዋል። በመጪው ሰኞ ሄልሲንኪ ተገናኝተው እንደሚነጋገሩ ይታወቃል።“ጠላቴም ወዳጄም አይደሉም በሚገባ አላውቃቸውም ሁለቴ ተገናኝተን በተነጋገርንበት ወቅት ግን በጥሩ ተግባብተናል” ሲሉ ዛሬ ብራሰልስ በሚካሄደው የሰሜን አተልንቲክ ቃል ኪዳን ሀገሮች ድርጅት ጉባኤ ጎን ባደረጉት ቃለ-መጠይቅ ተናግረዋል።ትረምፕ አያይዘውም ፑቲን ተፎካካሪ ናቸው። ወዳጅ ሊሆኑ የሚችሉበት ጊዜ ሊኖር ይችላል። ነገር ግን በሚገባ አላውቃቸውም” ብለዋል።ትረምፕ ከፑቲን ጋር ሲገናኙ ስለ ስትራቴጃዊ የመሳርያ ቅነሳ ውል፣ ሩስያ የመካከለኛው ርቀት የኑክሌር ኃይሎች ውል ስለመጣስዋና ካች አምና ዩናይትድ ስቴስ በተካሄደው ምርጫ ላይ ጣልቃ ስለመግባትዋ ጉዳይ አነሳለሁ ብለዋል።
1
4bd2bac712b0eb00f14675dcf6b1862c
cc920b999201673a0921111eca2ce78d
በ178 ሚሊየን ብር የተገነባው የኮምቦልቻ አጠቃላይ ሆስፒታል ተመረቀ
የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በባህርዳር ፈለገ ሕይህወት ሪፈራል ሆስፒታል ግቢ የተገነባውን የአማራ ክልል የህክምና ኦክስጅን ማምረቻና ማከፋፈያ ማዕከልን መርቀው ከፈቱ።በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይም የፌዴራልና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።ፕሬዚዳንቷ በምረቃው ላይ እንደተናገሩት በባህርዳር የተገነባው የኦክስጅን ማምረቻና ማከፋፈያ ማዕከል ከክልሉ አልፎ ለሀገሪቱም የሚያኮራ ተግባር ነው።የማዕከሉ መገንባት የኦክስጅን አገልግሎት በወቅቱ ማግኘት ባለመቻላቸው ረጅም ዕድሜ መኖር እየቻሉ በአጭር የሚቀጩ ባርካታ ወላድ እናቶችና ህጻናትን ከሞት መታደግ የሚያስችል ነው።“ማዕከሉ የመንግስትና የግል ባለሃብቱ ህብረት የታየበት በመሆኑ በምሳሌነት ሊወሰድ ይገባል”ብለዋል።የዓለም ጤና ድርጅት ኦክስጅንን መሰረታዊ መድኃኒት ነው ብሎ በመመደቡ ኦክስጅን አቅርቦት በቀላሉ የሚገኝ ዘላቂና አስተማማኝ እንዲሆን ኢትዮጵያ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች ነው።“የክልሉ መንግስት መሰል የልማት ስራዎችን በማስፋፋት የክልሉን ህዝብ ህይወት በዘላቂነት ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው” ያሉት ደግሞ የክልሉ ርዕሰ-መስተዳደር ዶክተር አምባቸው መኮንን ናቸው።የማዕከሉ ስራ መጀመር ከዚህ ቀደም በክልሉ ህዝብ ጤና ላይ ይደርስ የነበረውን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ጠቀሜታው የጎላ እንደሆነም አስረድተዋል።“የአማራ ክልል መንግስት የክልሉን ህዝብ ህይወት በዘላቂነት የሚያሻሽሉ የክልሉን ዕምቅ የመልማት አቅም ወደ ተግባር በመቀየር የህዝቡን የኑሮ ደህንነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ ነው”ብለዋል።የፌዴራል ጤና ሚኒስትር ዶክተር አሚር አማን በበኩላቸው በክልሉ በባህርዳርና በደሴ ሆስፒታል የተገነቡ የኦክስጅን ማምረቻና ማከፋፈያ ማዕከላት ስራ መጀመር የኦክስጅን ተደራሽነትን በማሳደግ በኩል ሚናው ከፍተኛ ነው።የዓለም ጤና ድርጅት የህክምና ኦክስጅንን እጅግ አስፈላጊ ከሆኑ መድሃኒቶች በማለት ከሚዘረዝራቸው ውስጥ እንደሚመደብ ገልጸው “ጽኑ ህሙማን ኦክስጅንን በግብዓትነት ይፈልጋሉ” ብለዋል።“በኢትዮጵያ በብዙ የጤና ተቋማት ውስጥ አስተማማኝ የኦክስጅን አቅርቦት እጥረት እንዳለ ጥናቶች ያሳያሉ” ብለዋል።በባህርዳርና በደሴ ተገንብተው ዛሬ የተመረቁት የኦክስጅን ማምረቻና ማከፋፈያ ማዕከላት በቀን እያንዳንዳቸው ከ120 በላይ ኦክስጅን ሲሊንደር የማመረት አቅም እንዳላቸውም ታውቋል።በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣በክልሉ መንግስት፣ በጀኔራል ኤሌክትሪክ ፋውንዴሽንና ግራንድ ቻሌንጅስ ካናዳ በተባሉ ድርጅት ትብብር የተገነቡት ሁለቱ ማዕከላት አጠቃላይ 80 ሚሊዮን ብር ወጭ እንደተደረገባቸውም ለማወቅ ተችሏል፡፡ምንጭ፡-ኢዜአ
0
2743498e6a91cbdf70d296e1c070018c
1e32719306c09c477001e9cd34f1d647
እስራኤል በሀማስ ይዞታዎች ላይ የአየር ጥቃት ፈፀመች
የእሥራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ነገ ማክሰኞ ማታ ዋይት ኃውስ እራት ሊበሉ ቀጠሮ እንደነበራቸውና፣ ለእሥራኤል ድጋፍ ከሚያሰባስበው በአሜሪካ-እሥራኤል ሕዝባዊ ጉዳዮች ኮሚቴ ላይ ቀርበው ንግግር ለማድረግም ዕቅድ እንደነበራቸው ታውቋል።የዩናይትድ ስቴትስ ጉብኝታቸውን መቋረጥ አስመልክተው በሰጡት ቃል፤ እሥራኤል ላይ ለደረሰው የጭካኔ ጥቃት ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስዱ ቃል ገብተዋል።ሀማስ በሚጠረጠርበት በዚህ ማዕከላዊ እሥራኤል ሰሜናዌ-ምሥራቅ ቴል-አቪቭ ውስጥ በሚገኝ መኖሪያ ቤት ላይ በደረሰው የሮኬት ጥቃት፣ ሰባት ሰዎች መቁሰላቸው የተለጸ ሲሆን፣ የእሥራኤል ጦር ኃይል በበኩሉ፣ ጋዛ ሰርጥ ውስጥ በሚገኙ የሀማስ ይዞታዎች ላይ የአጻፋ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል።
0
51b5bd90e6d87a3fb46a89b8d9b4ee58
2d7eb4bbc4509682b8ceb54aaaac5c40
የአፍሪካ አገራት 1 ትሪሊዮን ዶላር በሚደርሰው አለማቀፍ ንግድ ያላቸው ድርሻ 15 በመቶ ብቻ ነው
ባለፉት 2 አመታት ብቻ 170 ሺህ ያህል የተለያዩ አገራት ዜግነት ያላቸው ህጻናት ስደተኞች ወደ አውሮፓ አገራት በመግባት ጥገኝነት መጠየቃቸውንና በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ በአለም ዙሪያ ያለ ወላጅ ወይም ረዳት ብቻቸውን የተሰደዱ ህጻናት ቁጥር ከ300 ሺህ በላይ መድረሱን ዩኒሴፍ አስታውቋል፡፡ድርጅቱ ባለፈው ረቡዕ ባወጣው መግለጫ እንዳለው፤ የአለማችን ህጻናት ስደተኞች ቁጥር በአምስት እጥፍ ያህል ያደገ ሲሆን፣ እየተባባሰ በመጣው ደጋፊና ረዳት የሌላቸው ብቸኛ ህጻናት ስደተኞች ላይ የሚሳተፉ ህገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች በርካቶቹን ለባርነትና ለሴተኛ አዳሪነት እየዳረጉ ይገኛሉ፡፡ባለፈው አመትና በዘንድሮው የፈረንጆች አመት የመጀመሪያ ወራት በጀልባ ተሳፍረው ወደ ጣሊያን ከገቡት ህጻናት ስደተኞች መካከል 92 በመቶ የሚሆኑት ብቻቸውን የተጓዙ ወይም ወላጅ ዘመዶቻቸውን በስደት ጉዞ ላይ ያጡ እንደሆኑና አብዛኞቹም የኤርትራ፣ ጋምቢያ፣ ናይጀሪያ፣ ግብጽ እና ጊኒ ዜግነት ያላቸው እንደሆኑ ዩኒሴፍ አስታውቋል፡፡90 ሺህ ያህል የአፍሪካ ቀንድ አገራት ህጻናት በአገራቸው ውስጥና በአካባቢው አገራት ከተቀሰቀሱ የእርስ በእርስ ግጭቶች ለመሸሽ በአገር ውስጥ እና ከአገር ውጭ ብቻቸውን ለመሰደድ እንደተገደዱም ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡በተያያዘ ዜናም፣ በደቡብ ሱዳን የቀጠለውን የእርስ በእርስ ግጭት በመሸሽ በየቀኑ 100 ያህል የአገሪቱ ህጻናት ብቻቸውን ድንበር አቋርጠው ወደ ኡጋንዳ እንደሚሰደዱ ወርልድ ቪዥን የተባለው አለማቀፍ ተቋም ማስታወቁን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡እነዚሁ የአገሪቱ ህጻናት ያለምግብና መጠጥ እንዲሁም ደጋፊ ወላጅ ዘመድ ድንበር አቋርጠው ለቀናት በአስቸጋሪ ሁኔታ እንደሚጓዙና ለተለያዩ የከፉ ችግሮች እየተጋለጡ እንደሚገኙም ዘገባው ገልጧል፡፡
0
a9d895cf800ead725ff2a9f8982fb23b
8c828228e6800c418e34d038019aa314
ባለፈው ዓመት በክልሎች በተፈጠሩ ግጭቶች 1,200 በላይ ሰዎች መሞታቸው ተገለጸ
ካለፈው መስከረም አጋማሽ ጀምሮ በደቡብ ክልል ጂንካ በቦዲ ማህበረሰብ እና በፀጥታ ሃይሎች መካከል በተፈጠሩ ተከታታይ ግጭቶች 40 ያህል ሰዎች መገደላቸውን የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ ድጋፍ ማስተባበሪያ ሪፖርት አስታውቋል፡፡ በአካባቢው በሚኖሩ የቦዲ ማህበረሰብ እና በመከላከያ ሠራዊት መካከል የተፈጠረው ግጭት መነሻው ለጊቤ 3 ግድብ እና የስኳር ፕሮጀክት አካባቢው በመንግስት መፈለጉን ተከትሎ መሆኑን ሪፖርቱ አትቷል፡፡ የቦዲ ማህበረሰቦች የመንግስትን ምትክ ቦታ ሰጥቶ መልሶ ማስፈር ፕሮግራም በመቃወማቸው ግጭቱ ካለፈው መስከረም ወር ጀምሮ መከሰቱን ሪፖርቱ ይፋ አድርጓል፡፡ ይህ ግጭት ያዝ ለቀቅ እያደረገ እስካሁን 40 ያህል ሰዎች መገደላቸውን ማስተባበሪያ ጽ/ቤቱ የገለፀ ሲሆን መንግስት ለጉዳዩ አስቸኳይ እልባት እንዲያበጅለትም ጠይቋል፡፡ በዚህ ሪፖርት መሠረትም ካፈው መስከረም ወር አጋማሽ ጀምሮ በአፋር እና በደቡብ በተፈጠሩ የፀጥታ ችግሮች እና ጥቃቶች 57 ኢትዮጵያውያን መገደላቸውንና 34 ያህል መቁሰላቸውን አስታውቋል፡፡ ከእነዚህ መካከል 17 ያህሉ በቅርቡ በአፋር በታጠቁ ሃይሎች የተገደሉ መሆናቸውም ታውቋል፡፡
0
dd5274dd611b2abe52cc91a5ae753757
af5eaf9e3d5549bb3bfedae24753e2c6
ሕዝበ ሙስሊሙ በጾሙ ወቅት ያሳየውን የመተባበርና የመደጋገፍ መንፈስ አጠናክሮ እንዲቀጥል የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳደሩ አሳሰቡ።
ባሕር ዳር፡ መጋቢት 26/2012 ዓ.ም (አብመድ) የኮሮና ቫይረስ ምርመራ በባሕር እንደሚጀመር የአማራ ክልል የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡ ኢንስቲትዩቱ ይህንን የገለጸው የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ተመሥገን ጥሩነህ ቤተ ሙከራውን በጎበኙበት ወቅት ነው፡፡ኢንስቲትዩቱ ምርመራውን ከመጭው ሰኞ ጀምሮ ለማካሄድ ሙሉ የቤተ ሙከራ ዝግጅት ማጠናቀቁን ነው ያስታወቀው፤ ሁለት ባለሙያዎች ሙሉ ስልጠና ወስደውና ግብዓቶችም ተሟልተው ከነገ በስቲያ ጀምሮ ምርመራ ለማካሄድ ዝግጁ መሆኑን ነው ያመለከተው።በቅርቡም በጎንደርና ደሴ ተመሣሣይ የምርመራ ሥራ እንደሚጀመር የአማራ ክልል የኅብረተሰብ ጤና ኢንስትዩት አመልክቷል፡፡ በደብረ ብርሃንም የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ለማድረግ ቤተ ሙከራውን ለማሟላት እየተሠራ እንደሆነ አስታውቋል፡፡የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳደር ተመሥገን ጥሩነህ ወረርሽኙን ለመከላል እየተደረገ ያለው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በመግለጽ ከመከላከሉ ጎን ለጎን ደግሞ በክልሉ በሚገኙ ሆስፒታሎች ሁሉ ምርመራ ለማድረግ እንዲቻል ጥረቶች መጀመራውን አስታውቀዋል፡፡ የሚያፈልጉ ግብዓቶችን ከፌዴራል መንግሥትና ከውጭ ለማግኘት ጥረት እየተደረገ እንደሆነና በከፊልም በመምጣት ላይ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ርእሰ መሥተዳድሩ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ባለሀብቶች ወረርሽኙን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ እያደረጉት ያለውን ጥረት አመሥግነዋል፤ ሌሎችም የእነሱን አርዓያነት እንዲከተሉ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ ዘጋቢ፡- ስማቸው እሸቴ
0
6dbf14e47046b74aae90a3eb5cf88632
c947a0291dd3a8ad64898c982ffc8774
በካርቱ ግጭት በሰው ላይ ጉዳት ደረሰ
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 23፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በተነሳ የእሳት አደጋ በ48 የንግድ ሱቆች ላይ ጉዳት መድረሱን ፖሊስ አስታወቀ።የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ዋና ኢንስፔክተር አጃናው አዲስ የእሳት አደጋው የደረሰው በጉልት ገበያ አዳራሽ መሆኑን ተናግረዋል።በአደጋው በንግድ ሱቆቹ ውስጥ የነበሩ አልባሳት፣ ሸቀጣሸቀጥ፣ ቅመማቅመም፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶች ሙሉ በሙሉ መውደማቸውን ጠቅሰዋል።የአደጋው መንስኤና የወደመው ንብረት ግምት በፖሊስ እየተጣራ እንደሚገኝ የጠቆሙት ዋና ኢንስፔክተሩ በሰው ህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለ አመልክተዋል።የአካባቢው ማህበረሰብ ባደረገው ተሳትፎ የእሳት አደጋው ወደ ሌሎች ሱቆች ሳይዛመት መቆጠጣር እንደተቻለ መናገራቸውንም ኢዜአ ዘግቧል፡፡ ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
0
1e4587cb9017b5567b571071e6f3ac71
bc6d34f8c1adebc177e4239f75fb4206
የታዳሽ አረንጓዴ ልማት በኢትዮጵያ በሚል ርዕስ በሮም የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስተባባሪነት ዓለም አቀፍ ዌቢናር ተካሄደ
አዲስ አበባ ፣ ህዳር 16 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ”በሴቶች ላይ የሚከሰትን ጥቃት ባለመታዘዝ የብልጽግና ጉዟችንን እናስቀጥል” በሚል መሪ ቃል በኢትዮጵያ ለ15ኛ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ29ኛ ጊዜ የሚከበረው 16 ብርቱካናማ ጸረ ጾታዊ ጥቃት ንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄደ።ዋና ዓላማውም በ2030 የጾታ ጥቃትን ከዓለም ለማጥፋት ነው ተብሏል።መርሃ ግብሩን የአዲስ አበባ ሴቶችና ህጻናት ቢሮ ከኢንጀንደር ኸልዝ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ሲሆን÷ በዚህም ነጭ ሪቫን ለተከታታይ 16 ቀናት በማድረግ ጥቃት ሲፈጸም ዝም አልልም ጥቃትም አልፈጽምም በሚል እንደሚከበር የሴቶችና ህጻናት ቢሮ ሃላፊ ታደስ ግደይ ተናግረዋል።በኢትዮጵያ የኢንጀንደር ኸልዝ ተወካይ ጀማል ጣሰው በበኩላቸው÷ ኮቪድ-19 በዓለም ብሎም በኢትዮጵያ ከተከሰተ ጀምሮ ትምህርት ቤቶች በመዘጋታቸው የጾታ ጥቃት መጨመሩን ተናግረዋል።በፈትያ አብደላ
0
64e693f5be270f8acba4eb1ca0b72e4b
75291c33cf8eb8bac84ece0d84955f44
በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ያተኮረ የፕሬስ መግለጫ በጄነቫ ፕሬስ ክለብ ተዘጋጀ
ከነዓን ማርክነህ በጊኒ የተጫወተ የመጀመርያው ኢትዮጵያዊ በመሆን ቻምፒዮኑ ሆሮያ ክለብን ለመቀላቀል በቅርቡ ወደ ጊኒ ያቀናል።የጊኒው ሆሮያ ክለብ አሰልጣኝ ዲዲዬ ጎሜስ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ከታዩ ጥሩ ክህሎት ካላቸው ተጫዋቾች መካከል አንዱ የሆነው ከነዓንን በጥብቅ ሲከታተሉት ከቆዩ በኋላ በመጨረሻም ለአራት ዓመት የሚያቆየውን የውል ኮንትራት በማስፈረም የግላቸው አድርገውታል። ሆሮያ ከነዓን ለአራት ዓመት የሚቆየውን የረዥም ዓመት ኮንትራት እንዲፈርም መወሰናቸው አሰልጣኝ ዲዲዬ ጎሜስ ከነዓን አሁን ካለበት ወቅታዊ አቋም በተሻለ ሁኔታ ወደ ፊት የሚያድግ አቅም እንዳለው በመተማመን እንደሆነ የከነዓን ወደ ሆሮያ እንዲጓዝ ትልቁን ሚና የተወጣው ቢኒያም ሚዴቅሳ ለሶከር ኢትዮጵያ ተናግሯል።ከዚህ በተጨማሪ ከነዓን አሁን ባቀናበት ሆሮያ ክለብ የተሻለ እንቅስቃሴ ማሳየት ከቻለ ወደ አውሮፓ ወጥቶ እንዲጫወት ዕድል እንደሚያመቻቹለት ሰምተናል። ያለ ሙከራ በቀጥታ ፊርማውን ያኖረው ከነዓን ዛሬ አልያም ነገ የአውሮፕላን ትኬቱ ከተመቻቸ በኃላ ወደ ጊኒ የሚያቀና ይሆናል።በአዳማ ተስፋ ቡድን የእግርኳስ ህይወቱን መነሻው ያደረገው ከነዓን በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እና በአዲስ አበባ ከተማ ክለብ ከመጫወቱ ባሻገር ያለፉትን ሁለት ዓመታት በአዳማ ከተማ ድንቅ የውድድር ጊዜ በማሳለፍ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በወጣት እና በዋናው ቡድን እየተጫወተ ይገኛል።የጊኒ የጥምር ዋንጫ አሸናፊው ሆሮያ ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ከ7 ዓመታት በላይ ቆይታ ያደረገው ዩጋንዳዊው ሮበርት ኦዶንካራን የግሉ ማድረጉ የሚታወስ ነው።
0
12e62db21f6c3dc7c52f9e2aba0b8990
7e0aeaa197b3885c66c64e330d69572c
የአሰልጣኞች አስተያየት ሀድያ ሆሳዕና 1-0 ባህር ዳር ከተማ
ባሳለፍነው የውድድር ዓመት ከወልዋሎ ዓ.ዩኒቨርስቲ ጋር ጥሩ ቆይታ ያደረገው አፈወርቅ ከሳምንታት በፊት ለባህር ዳር ከተማ ለመጫወት መስማማቱን ክለቡን (ባህር ዳር ከተማ) ዋቢ አድርገን መዘገባችን ይታወሳል። ይሁንና የተጨዋቹ ፊርማ በፌደሬሽኑ የፀና ባለመሆኑ ተጨዋቹ የተሻለ ውል ወዳቀረበለት ሀዲያ ሆሳዕና ማምራቱ ታውቋል። በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ቡድን ጥሪ ቀርቦለት መጫወት የቻለው ተጨዋቹ ለአንድ ዓመት በሀዲያ ሆሳህና ቤት ለመቆየት መስማማቱ ታውቋል።በአሰልጣኝ ግርማ ታደሰ የሚመሩት ሀዲያ ሆሳናዎች ከዚህ ቀደም ይሁን እንዳሻው፣ ሄኖክ አርፊጮ፣ ደስታ ጊቻሞ፣ አብዱሰመድ ዓሊ፣ ሱራፌል ዳንኤል፣ በረከት ወልደዮሀንስ እና መስቀሉ ለቴቦን ወደ ቡድናቸው ሲቀላቅሉ ለማስፈረም ተስማምቶ የነበረው ብሩክ ኤልያስ በደቡብ ፖሊስ ቀሪ ውል ያለው በመሆኑ ወደ ክለቡ መመለሱ ተሰምቷል።።
0
5717b0cfb4c429af2a641d8a55536df4
965e21370cbb92b20f76bacba222da23
በቀዶ ህክምና 120 ሚስማሮች የወጣለት ታካሚ ህክምናውን አጠናቀቀ
አዲስ አበባ፡- ለፓርኪንሰን ሁሙማን የሚሰጠው የህክምና አገልግሎት ውስን መሆኑን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡በጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ቡድን መሪ አቶ አበባው አየለ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለፁት ፤የፓርኪንሰን ህሙማን ህክምና የሚያገኙት በሆስፒታሎች ውስጥ ቢሆንም፣ አገልግሎት አሰጣጡ ግን ውስን ሆኗል፡፡የፓርኪንሰን ህመም ህክምና በባህሪው አስቸጋሪ መሆኑን አቶ አበባው ጠቅሰው፣ የበሽታውን ምልክቶች በማየት ካልሆነ በስተቀር በህክምና መሳሪያዎች ብቻ በመመርመርና ውጤቱን በማወቅ ህክምና መስጠት እንደማይቻል ተናግረዋል፡፡ ይህም የህክምና አገልግሎት አሰጣጡን ውስን እንዳደረገው ጠቁመዋል፡፡በዘርፉ የሰለጠኑ ባለሙያዎች ቁጥር አነስተኛ መሆንና በተለይም የነርቭ ህክምና ባለሙያዎች ቁጥር በዝቅተኛ ደረጃ ላይ መገኘት በሆስፒታል ደረጃ ህክምናውን በተሟላ መልኩ ለመስጠት ችግር መፍጠሩን ቡድን መሪው ገልፀው፤ ህክምናው በሚሰጥባቸው ሆስፒታሎች ውስጥ ለሚገኙ ሃኪሞች በህመሙ ዙሪያ አጫጭር ስልጠናዎች አለማግኘታቸውና የግብአት አቅርቦት እጥረት መኖር አገልግሎት አሰጣጡን እንደገደበው አስታውቀዋል፡፡ቡድን መሪው ህመሙ በጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም፣ በትምህርት ቤት ጤናና ስርአተ ምግብ ፕሮግራምና በአእምሮ ጤና ስትራቴጂ እቅድ ውስጥ ተካቶ እየተሰራበት እንደሆነ ጠቅሰው፣አገልግሎቱን ለማስፋት መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሁለንተናዊ እገዛ ሊያደርጉ እንደሚገባ አሳስባዋል፡፡ ከህክምና አገልግሎቱ ባሻገር ታማሚዎች በማህበረሰቡ የሚደርስባቸውን አድሎና መገለል ብሎም ኢኮኖሚያዊ ችግር ለመፍታትም በአጋርነት መስራት እንደሚጠበቅ ገልፀዋል፡፡ከህሙማን ማህበሩ ጋር በመተባበር አጫጭር ስልጠናዎችን ለሃኪሞች በመስጠት የህክምና አገልግሎቱን ለህሙማን የበለጠ ተደራሽ ማድረግ እንደሚቻልም ቡድን መሪው ተናግረው፣ በሃገር አቀፍ ደረጃ ያሉ ጤና ነክ ዩኒቨርሲቲዎች ህመሙን በስርአተ ትምህርታቸው ውስጥ በማካተት የሚያስተምሩበት ከሆነ በዘርፉ የሚታየውን የባለሙያዎች እጥረት መፍታት እንደሚቻል ጠቁመዋል፡፡ፓርኪንሰን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየባሰ የሚሄድ እንቅስቃሴን የሚያውክና በአእምሮ ህመም ስር የሚካተት የስነ ነርቭ ህመም መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይጠቁማሉ፡፡ በጥናት የተረጋገጠ መረጃ ባይኖርም በኢትዮጵያ የፓርኪንሰን ህሙማን ቁጥር ከ200 እስከ 300 ሺ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 30/2011በአስናቀ ፀጋዬ
0
28abe404e2fd5fc12c209dac8ef61647
14a6021ff412973f5982493a5bb4d577
ከስጋና ወተት ምርት 68 ሚሊየን ዶላር ገቢ ተገኘ
-ኢትዮጵያ ባለፉት አስራ አንድ ወራት ወደ ውጭ ከላከቻቸው የተለያዩ ምርቶች 2 ነጥብ 8 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ማግኘቷን የንግድ ሚኒስቴር አስታወቀ።በሚኒስቴሩ የኮርፖሬት ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አማከለ ይማም ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለፁት፤ የተገኘው 2 ነጥብ 8 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር 37 ሺ 358 ቶን የግብርና ምርቶች፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ የማዕድን ዘርፎችና ሌሎች ምርትችን ወደ ተለያዩ የዓለም ሀገራት በመላክ ነው።በአስራ አንድ ወራቱ ውስጥ ለተገኘው ገቢ ከፍተኛውን ድርሻ ያበረከቱት ቡና 653 ሚሊየን 833 ሺ ዶላር በመሆን ቀዳሚውን ስፍራ ሲይዝ ማዕድንና ወርቅ 1 ቢሊየን 55 ሚሊየን 139 ሺ ዶላር፣ የቅባት እህል 404 ሚሊየን 143 ሺ ዶላር በመሆን ቀዳሚውን ስፍራ ሲይዙ ጥራጥሬ፣ አበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬና እና ሌሎች ምርቶችም በቅደም ተከተል እንዳሉ ተናግረዋል።ገቢው ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በተወሰነ ደረጃ ዝቅ ማለቱን ጠቁመው፤ በምርት መጠን ግን ጭማሪ ማሳየቱን አቶ አማከለ ገልፀዋል።የምርት በመጠን ጥርጥሬ፣ የቅባት እህል ቡና፣ ማዕድን፣ አትክልትና ፍራፍሬና እንዲሁም የአበባ ምርት በቅደም ተከተል ከፍተኛውን ድርሻ መያዛቸውን ተናግረዋል። በዘንድሮው የበጀት ዓመት ከውጭ ንግድ አምስት ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ለማግኘት መታቀዱ የሚታወስ መሆኑን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።
0
e313254e656a71c99b8486b31c96d94c
bad40edb3be294b5d7f9c008709733ac
በደቡብ ክልል አሌ ልዩ ወረዳ በደረሰ የመሬት ናዳ የ12 ሰዎች ህይወት አለፈ
በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ዛሬ እኩለ ቀን ገደማ በደረሰ የተሽከርካሪ አደጋ የ18 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በ33 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድና ቀላል የመቁሰል አደጋ መድረሱን ፖሊስ አስታወቀ።የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የትራፊክ ደህንነት ዲቪዥን ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ቱሩምሳ ሰለሞን ለኢዜአ እንደገለጹት አደጋው የደረሰው ከነቀምቴ ከተማ 51 መንገደኞችን አሳፍሮ ወደ ኤቤንቱ ወረዳ ሲጓዝ የነበረ አውቶብስ በዞኑ ጊዳ አያና ወረዳ ለቡ ቀበሌ ሲደርስ ዛሬ ከቀኑ 5፡00 ሰዓት ገደማ በመገልበጡ ነው።የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-29296 ኦሮ የሆነው ቅጥቅጥ ኤፍ ኤስ አር አውቶብስ አደጋው ሊደርስበት የቻለው በአደገኛ ቁልቁለት ላይ ሲጓዝ በመሪው ላይ ባጋጠመው የቴክኒክ ችግር መሆኑንም ኃላፊው አስረድተዋል።አሽከርካሪውንና ረዳቱን ጨምሮ ከሞቱት 18 ሰዎች በተጨማሪ በ10 ሰዎች ላይ ከባድ ፣በ23 ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል የመቁሰል አደጋ የደረሰባቸው ሲሆን የሟቾቹ አስከሬን ለቤተሰቦቻቸው መላኩንም ተናግረዋል።የአካል ጉዳት የደረሰባቸው መንገደኞችም በዞኑ ጊዳ አያና ወረዳ ሆስፒታል በህክምና ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል።(ኢዜአ)
0
b48e9aca82f7aa1b6442b78e9fb4bea5
fa3175082f950b13530244ab3e69e897
በሳልቫኪርና በተቀናቃኛቸው ሪያክ ማቻር መካከል ተፈርሞ የነበረው ተኩስ ማቆም
የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር እና ተቃዋሚ መሪ ሪያክ ማቻር ትናንት ሃገሪቱ መዲና ጁባ ላይ በነገ ቅዳሜ የጊዜ ገደብ አዲሱን የሽግግር መንግሥት ለማቋቋም መስማማታቸውን ይፋ አደረጉ። ሁለቱ የሽግግር መንግሥቱ ለማቋቋም ከአሁን ቀደም ያደረጉዋቸው ሙከራዎች አልተሳኩም፣ በርካታ የጊዜ ገደቦችም አሳልፈዋል።አሁን ያለውን የሽግግር መንግሥት እንደሚበትኑ ትናንት ለጋዜጠኞች የገለጹት በስምምነቱ መሰረት አምስት ምክትል ፕሬዚዳንቶች ዛሬ እንደሚሾሙ አስታውቀዋል።“ዛሬ ተቀምጠን መንግሥታቱን ለማቋቋም ተስማምተናል። በዚህ የመንግስት ምስረታ ውስጥ እንደ የብሄራዊ አንድነት የሽግግር መንግሥት እየተነጋገርን የምንቀጥልባቸው ጉዳዮች አሉ ። ለምሳሌ የጁባ የጸጥታ አጠባበቅ እና ለዋናው ተቃዋሚ ፓርቲ /SPLM / የሚሰጠው ጥበቃ ላይ እንነጋገራለን የተዋሃዱት ኃይሎቻችን ሥልጠን እስከሚጠናቀቅ ድረስ የኛ ወታደሮች አጠቃላዩን የጁባን ጥበቃ እንደሚይዙ ኃላፊነት ወስጃለሁ ሲሉ ኪር አክለው አስረድተዋል።ከፕሬዚዳንት ኪር ጎን የቆሙት ማቻር የቀሩት ችግሮች ባፋጣኝ ይፈታሉ በሚል እሳቤ በዚህ ሳምንት በሚከናወነው የአንድነት መንግስት ምስረት ላይ እንደሚሳተፉ አረጋግጠዋል።
0
0fd7c5e6d1982b59d77063fd0162d6a9
a03eb59951a5e314b16ad0c9938660ac
ጠ/ሚ ዐብይ በዓሉ በሰላም እንዲጠናቀቅ አስተዋጽዖ ላደረጉ ተቋማት እና ግለሰቦች ምስጋና አቀረቡ
አዲስ አበባ ፣ታህሳስ 30 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በመጪው ዕሁድ በአዲስ አበባ የሚካሄደው ታላቁ ሩጫን ጨምሮ የከተራ እና የጥምቀት በዓላት በስኬት እንዲጠናቀቁ የከተማው ነዋሪዎች የተለመደ ድጋፉቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጠይቋል፡፡የገና በዓል በሰላም እንዲከበር ህብረተሰቡ የጥንቃቄ እርምጃዎችን በመተግበር እና የፀጥታ አካላትን በመደገፍ ላበረከተው አስተዋፅኦ ኮሚሽኑ ምስጋና አቅርቧል፡፡የገና በዓል በአዲስ አበባ ያለ ምንም የፀጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ ቅድመ ዝግጅት ተደርጎበት የተለያዩ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸውን ያስታወሰው ኮሚሽኑ የፀጥታ ሃይሉ ከሃይማኖት አባቶች እና ከከተማዋ ነዋሪዎች እንዲሁም ከአስተዳደር አካላት ጋር ተቀናጅቶ በመስራቱ በዓሉ በሰላም ሊከበር መቻሉን ገልጿል፡፡በመጪው ዕሁድ ደግሞ በአዲስ አበባ የሚካሄደው ታላቁ ሩጫን ጨምሮ የከተራ እና የጥምቀት በዓላት በስኬት እንዲጠናቀቁ የከተማው ነዋሪዎች የተለመደ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉም ማሳሰቡን ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
0
55871fa572103592e06ea9e809fa135f
7ed7157573f3e4a3705efdfbebc0e289
” ዕቅዴ ጠንካራ ቡድን መገንባት ነው” አብርሀም መብራቱ
በአሰልጣኝ አብራሃም መብራቱ የሚመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በመጪው እሁድ በባህርዳር ዓለምአቀፍ ስታዲየም ከዩጋንዳ ጋር የወዳጅነት ጨዋታ ሊያደርግ ነው፡፡በካሜሩን አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የቻን ውድድር በመጪው ጥቅምት 8 ከሩዋንዳ ጋር ላለባቸው የመልስ ጨዋታ 24 ተጫዋቾችን በመያዝ ዝግጅታቸውን በአዳማ የጀመሩት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት ለመልሱ ጨዋታ ወደ ሩዋንዳዋ ርዕሰ መዲና ኪጋሊ ከማምራታቸው በፊት በመጪው ሳምንት እሁድ በባህር ዳር ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በቀጠናው ጠንካራ ብሔራዊ ቡድንን መገንባት ከቻሉት “ክሬኖቹ” ጋር የወዳጅነት ጨዋታ የሚያደርጉ ይሆናል፡፡ለቻን ለማለፍ ከመጨረሻው እና ፈታኙ ምዕራፍ ላይ የሚገኙት ዋሊያዎቹ በሁለተኛው ዙር የመጀመሪያ ጨዋታ በትግራይ ዓለምአቀፍ ስታዲየም በሩዋንዳ 1-0 በሆነ ጠባብ ውጤት መረታታቸው ይታወሳል፡፡ዩንዳዎች ለዚህ ጨዋታ ይረዳቸው ዘንድ በቅርቡ ሴባስትያን ዴሳብሬን በመተካት የብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ተደርገው የተሾሙት ጆናታን ሚክንስትሪ ለ21 በውጪ ሀገራት ለሚጫወቱ ተጫዋቾች ጥሪ አድርገዋል፡፡ በዚህ የቡድን ስብስብ ውስጥ በቅርቡ ለጊኒው ኤሲ ሆሮያ ፊርማውን ያኖረው ሮበርት ኦዶንካራን ጨምሮ የቀድሞው ሌላኛው የፈረሰኞቹ የቀድሞ ጎል ዘብ ዴኒስ ኦንያንጎም ተካቷል፡፡ከቀናት በፊት በይፋ የተሾሙት የሰሜን አይርላንዳዊዉ ጆናታን ከዚህ ቀደም በሴራሊዮን ፣ ሩዋንዳ ብሔራዊ ቡድን የሰሩ ሲሆን በ27 አመታቸው የሴራሊዮን ብሔራዊ ቡድንን በአሰልጣኝነት ሲረከቡ የዓለማችን ወጣቱ የብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ በመሆን ባለታሪክ መሆናቸው አይዘነጋም፡፡የቡድኑ ተጫዋቾች ከጨዋታው ሁለት ቀን በፊት በአዲስ አበባ ተሰባስበው ወደ ባህርዳር የሚያቀኑ ይሆናል፡፡
0
c66fd29b61a0a551d71c73e7a3e33dbe
a9570acdb90e5ea78af8589dbca50c64
ባለፉት 24 ሰዓታት 1 ሺህ 733 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው የ13 ሰዎች ህይወት አልፏል
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት ለ7 ሺህ 9 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርምራ ተደርጎ 579 ሰዎች ቫይረሱ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ።በዚህም በኢትዮጵያ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 14 ሺህ 547 ሰዎች የደረሰ ሲሆን ከእነዚህ መካከል ቫይረሱ ያለባቸው 7 ሺህ 931 ሰዎች የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል ብለዋል።በአሁኑ ወቅት 66 ፅኑ ታማሚዎች የሚገኙ ሲሆን 170 ሰዎች ደግሞ ከቫይረሱ አገግመዋል።ይህን ተከትሎም ከቫይረሱ ያገገሙት ሰዎች ቁጥር 6 ሺህ 386 እንደደረሰም ነው ሚኒስትሯ በትዊተር ገፃቸው ላይ ያሰፈሩት።ሚኒስትሯ እንደገለፁት በ24 ሰዓታቱ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የ5 ሰዎች ህይወት አልፏል፡፡በኢትዮጵያ እስካሁን በቫይረሱ ምክንያት 228 ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል።በአጠቃላይ ለ389 ሺህ 348 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ መደረጉንም አስታውቀዋል፡፡
0
90c92a99dcb33ccd32c201d019f3d59f
e993317336f269789c45b1826e977caa
በኦሮሚያ 18 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ አዳዲስ ባለሃብቶች ስራ ጀመሩ
-በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 6ሺ863 አዳዲስ መሠረታዊ የሕብረት ሥራ ማህበራት በመላው አገሪቱ መቋቋማቸውን የፌደራል ሕብረት ሥራ ኤጀንሲ አስታወቀ። በኤጀንሲው የሕዝብ ግንኙነት ዳይሮክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ይግዛው ዳኘው ለዋልታ እንደገለጹት በተለያዩ ክልሎች የሕብረት ሥራ ማህበራትን ለማስፋፋት በተደረገ እንቅስቃሴ በ2005 የበጀት ዓመት 245 ሚሊዮን ብር ካፒታል ያፈሩ 6ሺ863 ማህበራት ተቋቁመዋል፡፡ ከሕብረት ሥራ ማህበራቱ በተጨማሪም 49 ሚሊዮን ብር መቆጠብ የቻሉ 28 የሕብረት ሥራ ዩኒየኖች መቋቋማቸውን አቶ ይግዛው አስረድተዋል። በአምስት አመቱ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ መሰረት 59ሺ የመሠረታዊ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ለማደራጀት መታቀዱን ያስታወሱት አቶ ይግዛው እስካሁን በተደረገው እንቅስቃሴ 6 ነጥብ 6 ሚሊዮን አባላትን ያቀፉና ከ3 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 48 ሺ 124 ማህበራት መቋቋማቸውን ተናግረዋል፡፡በተመሳሳይ በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ 511 የሕብረት ሥራ ዩኒየኖችን ለማደራጀት መታቀዱን የተናገሩት ዳይሬክተሩ እስካ 2005 በጀት ዓመት ድረስ 8ሺ431 አባላትን ያቀፉና ከ1ነጥብ5 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ማስመዝገብ የቻሉ 293 ዩኒየኖች እንዲደራጁ መደረጉን ዳይሬክተሩ አስረደተዋል፡፡ በእስካሁኑ እንቅስቃሴ የተገኘው ውጤት ኤጀንሲው በዕቅዱ መሠረት እየተጓዘ ሞኑን አመላካች መሆኑን አቶ ይግዛው ገልጸዋል። የሕብረት ሥራ ማህበራት እንዲጠናከሩ ለማስቻል ኤጀንሲው የተለያዩ የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎችን፤ የፋይናንስ ድጋፍና የመጋዘን አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረጉን የጠቆሙት አቶ ይግዛው ልዩ ድጋፍ የሚሹ ክልሎችን የመደገፍ ሥራዎች ላይ አተኩሮ እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል ።የግብርና የሕብረት ሥራ ማህበራትን ለማጠናከር የግብርና ሕብረት ሥራ ልማት ስትራቴጂ በመንግሥት እንዲፀድቅ መደረጉን የገለጹት አቶ ይግዛው የአርዳይታ የግብርና ቴክኒክ ኮሌጅን የግብርና ሕብረት ሥራ የልቀት ማዕከል በማድረግ በ2006 ዓ.ም ሥልጠና መሥጠት እንደሚጀምር አያይዘው ገልጸዋል ። በተጨማሪም በአጠቃላይ 5ሺ ቶን የመያዝ አቅም ያላቸውን አራት መጋዘኖች በመንግሥትና በታላላቅ የሕብረት ሥራ ዩኒየኖች ትብብር በ37 ሚሊዮን ብር ወጪ በአማራና በትግራይ ክልሎች በመገንባት ላይ እንደሚገኙ አቶ ይግዛው መናገራቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።
0
6240127f66a87e3047bfb623f4b975f0
2c13701337655bd36bfd507d83dbbaa3
በስዊዘርላንድ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ተከበረ
11ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ቅድመ ዝግጅት በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ተመለከተ፡፡የበዓሉ አስተናጋጅ የሆነችው ሐረር ከተማ በዓሉን በድምቀት ለማክበር የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን እያከናወነች መሆኑን ፌዴሬሽን ምክር ቤት ገልጿል፡፡የሐረሪ ክልላዊ መንግስት ለበዓሉ ዝግጅት ተገቢውን ትኩረት በመስጠት አዳራሾችና የእንግዶች ማረፊያ የመሳሳሉ ቤቶችን የማዘጋጀት ሥራ እያከናወነ እንደሆነ የምክር ቤቱ አፈ ጉባዔ አቶ ያለው አባተ ለዋልታ ገልፀዋል፡፡በተለይም ከተማዋ ብዙ ሰው ማስተናገድ የሚችል አዳራሽ እንዳልነበራት አስታውሰው አሁን በዓሉን ምክንያት በማድረግ ትልቅ አዳራሽ እየተገነባ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡በከተማዋ የሚገኙ ሆቴሎች ውስን መሆናቸውን አፈ ጉባዔው ጠቁመው አሁን ላይ በርካታ ሆቴሎች መገንባታቸውን ጨምረው ገልፀዋል፡፡ የበዓሉ ሥነ ሥርዓት የሚከበርበት ስታዲየምም እየተዘጋጀ ነው፡፡የከተማዋ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ግንባታ፤ የፅዳትና የውበት ሥራዎችም በስፋት መከናወናቸውን አቶ ያለው ተናግረዋል፡፡ በዚህ በኩል ህብረተሰቡም በስፋት መሳተፉ ነው የተመለከተው፡፡ክልሉ በዓሉን በተለያዩ የልማት ሥራዎች ለማክበር የጀመራቸው ሥራዎችም በተያዘላቸው ዕቅድ መሰረት እየተከናወኑ ናቸው ብለዋል- አፈ ጉባዔው፡፡በ2010 ዓ.ም ግንባታውን ለማጠናቀቅ እየተገነባ የሚገኘው ትልቅ ሪፈራል ሆስፒታል ቀደም ብሎ በማጠናቀቅ ከተቻለም በበዓሉ ቀን ለማስመረቅ ግንባታው እየተፋጠነ ይገኛል፡፡የወጣት ማዕከላትና የፖሊስ ጣቢያዎችን የመሳሰሉ የተለያዩ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ግንባታም ተከናውኗል፡፡በክልሉ በዓሉን ምክንያት በማድረግ የተገነቡትና የተከናወኑት የልማት ሥራዎች ከ10 ዓመት በኋላ ሊከናወኑ የሚችሉ እንደነበር አቶ ያለው ይናገራሉ፡፡ በመሆኑም በዓሉ ልማትን ለማፋጠንም ጉልህ ሚና እንደሚያበረክት አስረድተዋል፡፡ቀደም ሲል በዓሉን ያስተናገዱ ክልሎችም ከፍተኛ የልማት ሥራዎችን በስፋት ማከናወናቸውን አስታውሰዋል፡፡የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔን ጨምሮ የተለያዩ አካላት የክልሉን የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በቅርቡ መጎብኘታቸው ይታወሳል፡፡
0
1bc5213c58df20a19e51412532e9c6a9
f7b37ccae61d078b36ce2b6c401dab47
ምዕራብ ጃፓን ከባድ የመሬት መናወጥ ቢያንስ ሦስት ሰዎች ሞቱ
ትናንት ሰኞ መስከረም 5/2012 ምሽት አራት ሰዓት ላይ ከሐረር ወደ አዲስ አበባ ሲያቀና የነበረ ከባድ መኪና ምዕራብ ሐረርጌ ቆቦ አካባቢ በሰርግ ስነ ስርዓት ላይ በነበሩ ሰዎች ላይ አደጋ በማድረሱ መንገዱ ዝግ ሆኖ እንዲያድርና እንዲውል እንደተደረገ የአዲስ ማለዳ ምንጮች ከስፍራው አረጋግጠዋል።ምንጮች እንደተናገሩት እንደተናገሩት በአካባቢ የሕግ አካላት ባለመምጣታቸው መንገዱ ምፍትሔ ሊበጅለት እንዳልቻለና ከ1 ሽሕ በላይ መኪኖች በመንገዱ ዳር ላይ ቆመው የመንገዱን መከፈት እየተጠባበቁ እንደሆነም ጠቁመዋል። መንገዱ አደጋው ከደረሰበት እስከ ሰባት ኪሎ ሜትር ድረስ ዝግ እንደሆነም አዲስ ማለዳ ከስፍራው ያገኘችው መረጃ ያመላክታል።ከባድ መኪናው ባደረሰው አደጋ እስካሁን የሟቾች ቁጥር በውል እንደማይታወቅ የተገለጸ ሲሆን በአካባቢ የአዲስ ማለዳ ምንጮች ግን ዐስር ያህል ሰዎች ሕይወታቸውን እንዳጡ ተናግረዋል። አሽከርካሪው በአካባቢው ሕብረተሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉንም ምንጮች ከስፍራው ገልጸዋል።
0
e53dadb21bc4b3803f0bb8c17b61f054
e53dadb21bc4b3803f0bb8c17b61f054
ቻን 2020| ዋልያዎቹ የማጣርያ ዝግጅታቸውን ዛሬ ጀመሩ
የአፍሪካ ሀገራት ዋንጫ (ቻን) በ2020 ካሜሩን ላይ ይስተናገዳል፡፡ ለዚሁ ውድድር በቅድመ ማጣሪያው ከጅቡቲ ጋር የተደለደለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዛሬ በአዳማ ከተማ ዝግጅቱን ጀምሯል።አሰልጣኝ አብርሃም መብራቱ እና ረዳቶቻቸው ጥሪ ካደረጉላቸው 23 ተጫዋቾች መካከል ሙጂብ ቃሲም በፓስፖርት ጉዳይ በዛሬው ልምምድ ላይ ካለመገኘቱ በቀር የተቀሩት 22 ተጫዋቾች ተገኝተዋል። ከ10:30 የጀመረው የዛሬው ልምምዳቸው ለ45 ደቂቃ የቆየ ሲሆን ቀለል ያለ ከኳስ ጋር ያተኮረ ልምምድ ሰርተዋል።ብሔራዊ ቡድኑ ለአንድ ሳምንት በአዳማ በሚኖረው ቆይታ የተለያዩ የልምምድ መርሐ ግብሮችን በማውጣት ዝግጅቱን እየሰራ የሚቆይ ሲሆን ምናልባትም በኢትዮጵያ ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ የፊታችን እሁድ ተፋላሚ የሚሆኑት ፋሲል ከነማ እና ሀዋሳ ከተማ ከብሔራዊ ቡድን ጋር በዝግጅት ላይ የሚገኙ ተጫዋቾቻቸውን የጨዋታው ቀን ሲቃረብ ሊወስዷቸው እንደሚችሉ ሰምተናል።ብሔራዊ ቡድኑ ሐምሌ 19 የመጀመርያ ጨዋታውን ወደ ጁቡቲ በማቅናት ከተጫወተ በኋላ በሳምንቱ የመልሱን ጨዋታ ድሬዳዋ ላይ እንደሚያደርግ ሲታወቅ የመጀመርያ የማጣርያ ጨዋታውን በድል የሚያጠናቅቅ ከሆነ መስከረም ወር ላይ ከሩዋንዳ ጋር የሚጫወት ይሆናል።
1
0aed9fedc4fd3cc916702d11ed5f48cd
2796a51eed552456f22d40058c597c4f
የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን የምክክር መድረክ በኦስትሪያ በመካሄድ ላይ ነው
የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች የምክክር መድረክ በኢንተር ኮንቲነታል ሆቴል እየተካሄደ ነው።የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምክክር መድረክ ፥ ባለፈው ጊዜ በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ተዘጋጅቶ የነበረው ውይይት 2ኛ ምዕራፍ ነው ተብሏል።የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ እንደተናገሩት ነጻ፣ ፍታዊና ታመዓኒ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችሉ የፖለቲካና የህግ ለውጦች ተከናውነዋል ብለዋል።እንደ ወይዘሪት ብርቱካን ገለጻ የዴሞከራሲ ተቋማትን ለመገንባት፣ በተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል ሊኖር የሚገባውን ትብብር ለማጠናከርና ተፎካካሪ ፓርቲዎች በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይተው የጋራ ምላሽ ለመሥጠት የሚያስችሉ ሓሳቦችን ለማዳበር ምክክሩ አስፈላጊ ነው ብለዋል ።ፓርቲዎቹ በጽሑፍ ለምርጫ ቦርድ ያቀረቧቸውንና ወደፊትም የሚያቀርቧቸው አጀንዳዎችን የቦርዱ ሰብሳቢና ቦርዱ በሚያቋቁመው የድጋፍ ኮሚቴ አማካኝነት በቅደም ተከተል ለውይይት አቅርበው ያፀድቃሉ ተብሎ ይጠበቃል። (ኤፍቢሲ)
0
330d2263158fc8d66386ccadeed97a9d
eae6ea34388ae10680ac5c76d5cee18d
ለአራት የህክምና ላቦራቶሪዎች የአክሪዲቴሽን አገልግሎት ተሰጠ
አዲስ አበባ ፣ ህዳር 12 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) መዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በህክምና ዶክትሬት የትምህርት ዘርፍ ያሰለጠናቸው 19 ተማሪዎችን ዛሬ አስመረቀ፡፡ዩኒቨርሲቲው የዛሬ ተመራቂዎችን ጨምሮ 99 የህክምና ዶክተሮችን አሰልጥኖ አስመርቋል።በዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዝዳንት ማዕረግ የጎባ ሪፈራል ሆስፒታል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጄይላን ቃሲም ሆስፒታሉ ለአካባቢው ማህበረሰብ ከሚሰጠው የህክምና አገልግሎት በተጓዳኝ በተለያዩ የህክምና ሙያዎች ስልጠና እየሰጠ እንዳለ መግለጻቸውን ኢዜአ ዘግቧል።በ1999 ዓ.ም 742 ተማሪዎች ተቀብሎ ስራ የጀመረው መዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ አሁን ላይ ከ24 ሺህ የሚበልጡ ተማሪዎች አሉት።
0
3a35a0517f18524fd0e64462ae36906c
3a35a0517f18524fd0e64462ae36906c
አቶ አብነት ገ/መስቀል በፊፋ ግብዣ ወደ ሩሲያ አቅንተዋል
የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማኅበር ሊቀመንበር አቶ አብነት ገ/መስቀል በፊፋ በቀረበላቸው ግብዣ መሰረት የ2018 የሩሲያ ዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍፃሜ እና የፍፃሜ ጨዋታዎችን ለመታደም ትላንት ወደ ሩሲያ አቅንተዋል። ትላንት ምሽትም በሴይንት ፒተርስበርግ ስታድየም በመገኝት ፈረንሳይ ከቤልጅየም ያደረጉትን ጨዋታ የተከታተሉ ሲሆን ከዚህ በኋላም ቀሪ ጨዋታዎችን እስከ ፍፃሜው ድረስ በተመሳሳይ መልኩ ጨዋታዎችን ይከታተላሉ ተብሎ ይጠበቃል ።ቅዱስ ጊዮርጊስን በሊቀ መንበርነት የሚመሩት አቶ አብነት ገ/መስቀል በአፍሪካ እግርኳስ ኮንፌድሬሽን (ካፍ) ውስጥ የክለብ ውድድሮች ኮሚቴ አባል መሆናቸው ይታወቃል።
1
4c69b2bd3dfa71985fdcd83371291018
68bc41459c5b47786acc96d3b1aa4a0a
ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ የኢጋድ አባል አገራት የመሪዎች የምክክር ስብሰባ ላይ ለመካፈል ጁባ ገቡ
ደቡብ ሱዳን በኃይልና በመሠረተ ልማት ላይ ትኩረቱን ያደረገ የምክክር መድረክ ልታስተናግድ ነው ።የምክክር መድረኩ ጁባ በመሰረተ ልማት ነዳጅ እና ዘይት ምርቷ ላይ ዘላቂ አሰራር እንድትተገብር የሚያስችላት ነውም ተብሏል፡፡በ2011 ከሱዳን ነፃነቷን አግኝታ የደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ መንግስትን የመሰረተችው አገር በአገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የተባለውን ጉባኤ ልታስተናግድ እንደሆነ ሱዳን ትሪቡን እያስነበበ ይገኛል፡፡አገሪቱ በመጪው ጥቅምት ወር ላይ ታካሂዳለች የተባለው በኃይል እና መሠረተ ልማት ላይ ትኩረቱን ያደረገው ጉባኤ ለጁባ የልማት ጉዞ እንቅስቃሴ እና በአገሪቱ ፖለቲካ ላይም አዎንታዊ ተጽእኖይኖረዋል እየተባለ ይገኛል፡፡ከአፍሪካ ቀንድ አገራት በከርሰ ምድር ነዳጅና ዘይት የበለፀገች እንደሆነች የሚነገርላት ደቡብ ሱዳን፤ ባለፉት ዓመታት በገጠማት የእርስ በእርስ ጦርነት ሳቢያ ተፈጥሮዋ ኢኮኖሚዋን ሳይጠቅም እንደቆየ ይነገራል፡፡የአሁኑ ጉባኤም በዚሁ ጉዳይ ላይ መፍትሔን የሚያስቀምጥ ነው፡፡ አለማቀፍ የተፈጥሮ ማዕድን አበልፃጊ ኩባንያዎች እና አገራት ጋር በጥምረት ለመስራት የምትችልበት አቅጣጫ ይዘረጋል ተብሏል፡፡አፍሪካን በመሰረተ ልማት ለማስተሳሰር በሚደረገው ጥረትም አገሪቱ ከጎረቤቿ እኩል እንድትሆንም የፕሬዝደንት ሳልቫ ኪር መንግስት የሚያቀርበው ምክረ ሀሳብ ላይ ይመከርበታል፡፡ጉባኤው በአፍሪካ ህብረት የነዳጅ እና ኃይል ጉዳዮች ኮሚሽን የተዘጋጀ ሲሆን አህጉራዊ ይዘት ያለው ነው፡፡የጥቅምቱን ጉባኤ ርዕሰ መዲናዋ ጁባ ታስተናግዳለች፡፡ ፕሬዝደንት ኪርን ጨምሮ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች የኢንዱስትሪ ተመራማሪዎች፣ የምጣኔ ሃብት ባለሙያዎች እና ባለሃብቶች ይታደሙበታልም እየተባለ ይገኛል፡፡የአፍሪካ አገራት የተፈጥሮ ሃብት አጠቃቀም በተመለከተ በደህንነት፣ ቴክኖሎጂ እና የመሰረተ ልማት ላይ ያተኮሩ ጥናቶች ቀርበው አገራቱ እንደሚመካከሩባቸው እና ወጥ አቅጣጫም እንደሚይዙ ይጠበቃል ሲል የዘገበው ሱዳን ትሪቡን ነው፡፡
0
6734971b411906794d4cf98de2cc96c8
54999b275e831da48098313e526cb9df
የሱዳኑ መሪ ታሪካዊ የሆነ ሲሲና አውሮፕላን ለህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ በመታሰቢያነት አስረከቡ
ኢትዮጵያ ባጋጠማት የአየር ጸባይ ለውጥ ምክንያት በሃገሪቱ ድርቅ ቢያጋጥማጥም ይህንን አስቸጋሪ ሁኔታ በመቋቋም ከአፍሪካ ቀዳሚ የሆነ የምጣኔ ሃብት እንደምታዝመዘግብ ነው ተቋሙ የገለጸው፡፡እንደ አይቬሪኮስት፤ ሴኔጋል፤ ታንዛኒያ እና ሩዋንዳ ያሉ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት እ.አ.አ በ2017 የምጣኔ ሃብት እድገታቸው ከ6 በመቶ በላይ እንደሚሆን ነው ፋይናንሻል ታይምስ አይ ኤም ኤፍን ዋቢ አድርጎ የዘገበው፡፡ከሰሃራ በታች ያሉ የአፍሪካ ሀገራት የምጣኔ ሃብት ዕድገታቸው በአማካይ 2.5 በመቶ እንደሚሆን አይ ኤም ኤፍ ይፋ አድርጓል፡፡በተለይም ደግሞ መንግስታት ለህዝባዊ አገልግሎቶች የሚመድቡት ወጪ መጨመር፤ የነዳጅና የማዕድናት ዋጋ በተወሰነ መልኩ ዋጋቸው ከፍ ማለቱ የምጣኔ ሃብት እድገታቸው እንዲነቃቃ ማድረጉን አብራርቷል፡፡ይሁንና በበርካታ የአፍሪካ መንግስታት ዘንድ እየተበራከተ የመጣው የውጪ እዳ በወደፊቱ የእድገት መሰረታቸው ላይ ትልቅ እንቅፋት ሊሆን እንደሚችል አሳስቧል (ኢብኮ) ፡፡
0
c27c0b7c68b457e7149a70891869ee85
c27c0b7c68b457e7149a70891869ee85
ህወሃት ከፌዴራሊስት ሀይሎች ጋር እየሰራሁ ነው በማለት ህብረተሰቡን እያወናበደ ይገኛል- የኢትዮጵያ ፌዴራሊስ ሀይሎች ጥምረት
አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ህወሃት ከፌዴራሊስት ሀይሎች ጋር እየሰራሁ ነው በማለት ህብረተሰቡን እያወናበደ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ፌዴራሊስ ሀይሎች ጥምረት አስታወቀ።በፌዴራሊስ ሀይሎች ጥላ ስር የተሰባሰብን አካላት የህወሃት አካሄድ ስላልተመቸን እንዲታገድ በማድረግ ውይይታችንን በአዲስ አበባ እያካሄድን እንገኛለን ብሏል ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በላከው መግለጫ።ህወሃት የፌዴራሊስት ሀይሎችን በመጠቀም የስልጣን ጥማቱን ለማሳከት ሲንቀሳቀስ ተመልክተነዋል ያለው ጥምረቱ አሁንም ከፌዴራል ሀይሎች ጋር እየሰራሁ ነው በማለት የትግራይን ህዝብ ለማሳሳት ሲሞክር እየተመለከትን ነው ብሏል።የኢትዮጵያ ፌዴራሊስት ሀይሎች ጥምረት በመግለጫው ሀገር በታኝ የሆነ አጀንዳ ካላቸው ቡድኖች ጋር አንዳችም ዓይነት ህብረት እንደሌለን የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲያውቅ እንፈልጋለን ነው ያለው።የፌዴራሊስት ሀይል ሆኖ ለመቀጠል በሀሳብም ይሆን በኢኮኖሚ አሃዳዊ ቁመና ይዞ መቀጠል ተገቢ አይደለም ብሏል ጥምረቱ።የህወሃት እውነተኛ ማንነት ደግሞ ሀገርን በፌዴራል እሳቤ አስተዳድራለሁ በሚል የይስሙላ የክልል አስተዳደር ዘርግቶ የእርሱን ሀሳብ ብቻ ሲያስፈፅም የነበረ ፤ ሀገር ያመነጭቸውን ሀብት በኢ ፍትሃዊነት ሲያባክን የነበረ መሆኑን አንስቷል።መሻሻል የማያሳይ እና ወቅታዊውን የሀገሪቱን ፓለቲካ የማይዋጅ ሆኖ በመገኘቱ ህዋሃትና ኢዲህንን በይፋ ከጥምረቱ መሰናበታቸውን ህዝቡ ተረድቶ በስማችን እየነገደ ያለውን የህወሃት ቡድን ህዝብ ከጥምረቱ ጋር በጋራ በመሆን እንዲታገል ጥሪ አቅርቧል።ህወሃት እያራመደ የሚገኘው አቋም ኢትዮጵያ በፌዴራላዊ አስተዳደር እንዲሁም ፍትሃዊነት እና እኩልነት ባረጋገጠ እና ባጣጣመ መልኩ እድትመራ የመፈለግ አይደለም ብሏል።ከዚያ ይልቅ እኔ ከሞትኩ ……. በሚል አመለካከት ˝እኔ ካልመራኋት ትበታተን ˝ የሚል አደጋ ከፊት የደቀነ በመሆኑ እና ኢትዮጵያን ለውጭ ጠላቶች አሳልፎ ለመስጠት የማያመነታ በመሆኑ በህግ አግባብ እንዲጠየቅ እና እንዲታረም እየተሰራ መሆኑን ጥምረቱ አስታውቋል።
1
ccfe41b589d8a15efce1b2fa47543669
ccfe41b589d8a15efce1b2fa47543669
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በጅማና ዳውሮ ጉብኝት አድርገዋል
አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በጅማ እና ዳውሮ ጉብኝት አድርገዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጅማ አባ ጅፋር አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም በአባ ገዳዎች፣ በሀይማኖት አባቶች የሀገር ሽማግሌዎች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ተወካዮች አቀባበል አድርገውላቸዋል።በአቀባበሉ ላይም ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና ለሌሎችም እንግዶች የተለያዩ ስጦታዎች እንደተበረከቱም ከጅማ ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከውጭ ሀገራት ባለሀብቶች ጋር በመሆን በደቡብ ክልል ዳውሮ ዞንም ጉብኝት አድርገዋል።
1
f27b9b0c8c9b08c4cd5edbe771f5e4a2
c58c92441c052920025abea8c6011642
ኳታር 2022| ስለ ነገው የዋልያዎቹ ጨዋታ አጫጭር መረጃዎች
ወልቂጤ ከተማበምድብ ለ ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ወልቂጤ ከተማ ከሜዳው ውጪ በኦሜድላ ሜዳ ከየካ ክ/ከተማ ጋር ባደረገው ጨዋታ ለተነሳው ግርግር ምክንያት ሆኗል በሚች ሶስት የሜዳው ጨዋታዎችን በገለልተኛ ሜዳ እንዲያከናውን እና የ100 ሺ ብር ቅጣት እንደተጣለበት ይታወሳል። ክለቡ ቅጣቱን ይግባኝ በማለቱ ጉዳዩ እስኪታይ ድረስ ተፈፃሚ ሳይሆን የቆየ ሲሆን ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ በወሰነው መሰረት የጨዋታ ቅጣቱ ወደ አንድ ዝቅ እንዲል ሲደረግ የገንዘብ ቅጣቱም ወደ 10 ሺሀ ብር እንዲቀንስ መወሰኑ ታውቋል።ካፋ ቡናበምድብ ሐ 14ኛ ሳምንት ካፋ ቡና ከ ሻሸመኔ ከተማ ያደረጉት ጨዋታ 1-1 ዘልቆ ወደ መጠናቀቂያው ሲቃረብ የተሰጠ ፍፁም ቅጣት ምት ሳይመታ የሻሸመኔ ቡድን ሜዳውን ለቆ በመውጣቱ ሳይጠናቀቅ መቅረቱ ይታወሳል። ይህን ተከትሎም የዲሲፕሊን ኮሚቴ ካፋ ቡና በፎርፌ አሸናፊ እንዲሆን ወስኗል።በሌላ በከል ደግሞ በጨዋታው ላይ ለታየው የስፖርታዊ ጨዋነት ጥሰት ባለሜዳው ካፋ ቡና ቀጣይ ሁለት የሜዳው ጨዋታዎችን በገለልተኛ ሜዳ እንዲያደርግ ከውሳኔ ደርሷል። ካፋ በውሳኔው ቅሬታውን በመግለፅ ይግባኝ መጠየቁም ታውቋል።የምድብ ሀ ተስተካካይ ጨዋታዎችበተለያዩ ምክንያቶች ሳይደረጉ የቆዩ የምድብ ሀ ጨዋታዎች ነገ ይደረጋሉ ተብሎ ይጠበቃል። ለገጣፎ ከደሴ የሚደርገው ጨዋታ ባለው ነባራዊ የአየር ሁኔታ የሜዳ ወይም የሰዓት ለውጥ ሊደረግብት እንደሚችል የተሰማ ቢሆንም አሁን ባለው መረጀ ሁሉም ጨዋታዎች ነገ 9:00 እንደሚደረጉ ይጠበቃል።አውስኮድከ ፌዴራል ፖሊስ ለገጣፎ ለገዳዲ ከ ደሴ ከተማ ወሎ ኮምቦልቻ ከ ገላን ከተማ ወልዲያ ከ ቡራዩ ከተማየሳምንቱ መጨረሻበሊጉ በዚህ ሳምንት ቅዳሜ እና እሁድ ሊደረጉ የነበሩ ጨዋታዎች ወደ ቀጣዩ ሳምንት ተሸጋግረዋል። ነገ የተስተካካይ ጨዋታዎቹ የሚካሄዱ በመሆናቸውም ሚያዚያ 26 እና 27 ሁሉም ቡድኖች በተመሳሳይ የጨዋታ ቁጥር ላይ በመገኘት የ16ኛ ሳምንት መርሐ ግብራቸውን እንደሚያከናውኑ ይጠበቃል።
0
f3cb12f41ae3856b66bcf889988eb04a
853020a3a0d3be121d496db3ad5c84a2
የተጫዋቾች ችግር ገፍቶ እየወጣ ነው
የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አክሲዮን ማኅበር ገደብ ተጥሎበት የነበረውን የተጫዋቾች ደሞዝ አከፋፈል በተመለከተ ውሳኔ አስተላልፏል።ትናንት እና ዛሬ አንደኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን በኢንተር ኮንትኔንታል አዲስ ሆቴል ያደረገው ይህ አክሲዮን ማኅበር የተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውይይት አከናውኖ ውሳኔ አስተላልፏል። በጉባዔው ላይም ከተነሱት አጀንዳዎች መካከል የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተጫዋቾች የደሞዝ ጣሪያን የሚመለከት ይገኝበታል።እንደሚታወሰው 2010 ላይ ኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ባልተገኙበት ስብሰባ ላይ የኢትዮጵያ ስፖርት ኮሚሽን እና የኢትዮጵያ እግርኳክ ፌዴሬሽን የክለብ ተወካዮቸን ሰብስበው የተጫዋቾች ደሞዝ ላይ ምክክር አድርገው ነበር። በዚህ ውይይት ላይም ክለቦች ‘ለተጫዋች የምንከፍለው ወርሃዊ ክፍያ ገደብ ይኑረው’ በማለት የተጫዋቾች ደሞዝ ከ50 ሺ እንዳይበልጥ ወስነው ወጥተዋል። ይህንን ተከትሎ የተለያዩ ጥያቄዎች ከጉዳዩ አፈፃፀም ጋር በተገናኘ ሲነሱ ቆይተው በዛሬው ዕለት አክሲዮን ማኅበሩ ጉዳዩ ላይ አዲስ ውሳኔ አስተላልፏል።በዚህም መሰረት በርካታ ክለቦች ‘ከጠረጴዛ ሥር’ የሚባል አከፋፈል በማምጣታቸው እና መንግሥት ማግኘት የሚገባውን የታክስ ክፍያ በአግባቡ ባለማግኘቱ አከፋፈሉ ከ2014 ጀምሮ እንዲቀር ተወስኗል። ይህ በገደብ የነበረው አከፋፈል ቀርቶም ክለቦቹ በአቅማቸው እንዲከፍኩ መብት ይሰጣል ተብሏል። በዘንድሮ የውድድር ዘመን ግን ክለቦች 2010 ክረምት ወር የተላለፈውን ውሳኔ አክብረው እንዲከፍሉ እና ለ2014 አከፋፈል ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ተጠቁሟል።
0
3c6540334e91c5cf080596fc879cb106
e70aa1fd2a7d76327ba06952f44a4e07
በዓለም የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር ከ27 ሚሊየን አለፈ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 3ሺህ 895 የላብራቶሪ ምርመራ 119 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።ይህንን ተከትሎም በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 5 ሺህ 689 መድረሱን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ዛሬ ባወጡት ሪፖርት አመላክተዋል።ከጠቅላላው የላብራቶሪ ምርምራ ውስጥ 87 ናሙናዎች በአስክሬን ላይ የተደረገ የላብራቶሪ ምርምራ ሲሆን 4 ናሙናዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል።በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ የተገኘባቸው እና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር 98 መድረሱን ገልፀዋል።በሌላ መልኩ በትላንትናው ዕለት 117 ሰዎች (78 ከአዲስ አበባ፣ 35 ከትግራይ ክልል እና 4 ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ) ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 2 ሺህ 132 ደርሷልም ብለዋል።
0
49756d547e38813b199710b56c150cac
c2bf7889a823357edd8b1fbdf0c877d1
​ወልዋሎ ሶስት ተጫዋቾችን አስፈረመ
በርከት ያሉ ተጫዋቾችን ከሳምንታት በፊት አስፈርሞ የነበረው ኢኮሥኮ ተጨማሪ አራት ተጫዋቾችን አስፈርሟል፡፡አሰልጣኝ ዳንኤል ገብረማርያምን በዋና አሰልጣኝነት የሾመው የምድብ ለ ተወዳዳሪዌ ኢኮሥኮ ከሳምንት በፊት በርካታ አዳዲስ እና ነባር ተጫዋቾችን ያስፈረመ ሲሆን አሁንም ተጨማሪ አራት ተጫዋቾች ከተለያዩ ክለቦች ወደ ስብስቡ ቀላቅሏል፡፡ የራስወርቅ ተረፈ (ግብ ጠባቂ ከአክሱም)፣ ይገርማል መኳንንት (ግብ ጠባቂ ከአውስኮድ)፣ መላኩ ተፈራ (ተከላካይ ከአውስኮድ) እና ፍፁም ግርማ (አማካይ ከወልቂጤ) አዲሶቹ ፈራሚዎች ናቸው፡፡© ሶከር ኢትዮጵያ
0
74a3b434441c94e5dc99a901e6bdcd12
74a3b434441c94e5dc99a901e6bdcd12
በሶሪያ ጉዳይ የቪየናው ምክክር አልያዘም
በዩናይትድ ስቴትስ እና በሩሲያ የተመራውና 17 አገሮች ያሉበት ዓለም አቀፉ የሶሪያ ድጋፍ ሰጪ ቡድን ለተቋረጠው የጄኔቫው የተፋላሚ ወገኖች ንግግር ማንሰራራት መንገድ ይጠርጋል የሚል ተሥፋ ቢያሳድርም ስምምነት ላይ ሳይደርስ ቀርቷል።ይሁንና ደራሽ እርዳታ በውጊያው ወደተጠመዱት አካባቢዎች ለማድረስ የሚያስችል መንገድ በአፋጣኝ ለመክፈትና ግጭቶቹሙሉ በሙሉ እንዲቆም የሚጠይቅ የጋራ መግለጫ አውጥተዋል።የዩናይትድ ስቴትሱ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ጆን ኬሪ የቪየናው ጉባኤ ሲጠናቀቅ ባሰሙት ንግግር ሁለት ወራት በሞላው የተኩስ አቁም ላይ አደጋ ስላጠላውና እየጨመረ ስለመጣው ቀውስ ተናግረዋል።አምስት ዓመት ያስቆጠረውን የሶሪያው ቀውስ ተፋላሚ ወገኖች ያስጠነቀቁት የጉባኤው ተሳታፊዎች፤ የተኩስ አቁሙን ደጋግሞ መጣስ ስምምነቱ የሚሰጠውን ጥበቃ ጨርሶ እንዳያሳጣ ያላቸውን ሥጋት ገልጠዋል።የተባበሩት መንግስታት የሶሪያ ልዩ መልዕክተኛ ስተፋን ደ ሚስቱራ በበኩላቸው ሲያስረዱ ደራሽ እርዳታ ወደ ሁሉምበውጊያው ወደተጠመዱ አካባቢዎች ለማድረስ ለግንቦት 24 ቀነ ገደብ ተይዟል፤ ብለዋል።የአሜሪካ ድምጹ ቪክተር ቢቲ (Victor Beattie) ያጠናቀረውን ዘገባ፣ አሉላ ከበደ አቅርቦታል ከድምጽ ፋይሉ ያድምጡ።
1
33fcfb5ff057d837e12287dc0d999b2d
33fcfb5ff057d837e12287dc0d999b2d
“ለሀገርና ለሕዝብ ጥቅም ሲባል ልናሰምረው እና ልናከብረው የሚገባን ቀይ መስመር ተጥሷል” የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳኅለወርቅ ዘውዴ
ፕሬዝዳንቷ ጥቅምት 22/2013 ዓ/ም በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ ነዋሪ አማራዎች ላይ በተፈጸመው የግፍ ጭፍጨፋ የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገልጸዋል፡፡በጽሕፈት ቤቱ የፌስ ቡክ ገጽ ይፋ የሆነው የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳኅለወርቅ ዘውዴ ሙሉ መልእክት፡-የሰማሁት ዜና ልቤን ሰብሮታል ብል ማጋነን አይሆንም፡፡ የዛሬ ዓመት የተናገርኩትን ከመድገም ዉጪ ሌላ ቃላት የለኝም፡፡ ዘርና ሐይማኖት ለፖለቲካ ጥቅም እንዲውሉ ሲደረግ፣ ንጹሀን ዜጎቻችን በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደሉ፣ ሲፈናቀሉና ሲንከራተቱ ስናይ ስሜትን ለመግለጽ ቃላት ያጥራል፤ ለቅሶ፣ ድንጋጤና ሥጋት የብዙዎችን በር አንኳኩቷል፤ ሃዘናቸው ሃዘኔ/ሃዘናችን ነው፤ ለሀገርና ለሕዝብ ጥቅም ሲባል ልናሰምረው እና ልናከብረው የሚገባን ቀይ መስመር ተጥሷል፤ ሀገራችንን ካንዣበበባት ክፉ አዳጋ ለማዳን ሁላችንም ሚና አለን፤ የሚመለከታቸው ሁሉ የበኩላቸውን መወጣት አለባቸው፤ ቀይ መስመር መጣስ የለበትም እንበል::
1
1865accc9e7de2422e81f4d50c650d17
d0d1985786dd5a72fbfb01224f78bda2
የውጪ ሃገራት ገንዘቦችን በህገ ወጥ መንገድ ሲመነዝሩ የነበሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
ባሕር ዳር፡ መስከረም 06/2013ዓ.ም (አብመድ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ድንበር አካባቢ 600 ሺህ ብር በህገ-ወጥ መንገድ ሲያዘዋውር የተገኘ ተጠርጣሪ ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን የክልሉ ሠላም ግንባታ እና ጸጥታ ቢሮ አስታወቀ።የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ሙሳ ሃሚድ እንደገለጹት ግለሰቡ ገንዘቡን ሲያዘዋወር የተገኘው ትናንት በአሶሳ ዞን ሱዳን ጠረፍ በሆነችው ኩርሙክ ከተማ ውስጥ ነው፡፡በቁጥጥር ስር የዋለው ተጠርጣሪው ለፖሊስ በሰጠው ቃል ገንዘቡን ለወርቅ ግዥ እያንቀሳቀስኩ ነው ማለቱን አቶ ሙሳ ማስረዳታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።“በክልሉ የህገ-ወጥ ገንዘብ ዝውውር በስፋት ሊኖር እንደሚችል ይገመታል “ያሉት አቶ ሙሳ ችግሩን ለማቆም ህብረተሰቡን ያሳተፈ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል፡፡
0
dbee8c089416fcd43518bccd8cf6babc
7cb0a8e0fe3aca9c7fac294a28a36648
አርቴታ አርሰናልን በአሰልጣኝነት ተረከበ
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የተቋቋመው ግብረ ኃይል የመተከል ዞንን የፀጥታ ማስከበር ስራ መረከቡን ሜጀር ጄኔራል አስራት ዴኔሮ አስታወቁ።በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተቋቋመውና ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና የመከላከያ ሠራዊት አመራሮች የተካተቱበት ግብረ ኃይል በዞኑ የሕግ የበላይነትን የማረጋገጥ ስራውን ሙሉ በሙሉ ጀምሯል።የፀጥታ ኃይሉን የሚመሩት ሜጀር ጄኔራል አስራት ዴኔሮ እንደገለጹት፤ የንፁሃንን ሕይወት በማጥፋት ወንጀል የተሳተፉ ተጠርጣሪዎችን የማደን ስራው ቀጥሏል።“በወንጀሉ የተሳተፉ ተጠርጣሪዎች በአጭር ጊዜ የሕግ ተጠያቂ ይሆናሉ” ሲሉም ተናግረዋል።ችግሩን ከመሰረቱ ለመፍታት በአሁኑ ወቅት በየደረጃው ከሚገኙ የማኅበረሰብ አባላትና አመራሮች ጋር ውይይት እየተካሄደ ሲሆን ወንጀለኞቹን በመለየት ለሕግ የማቅረቡ ስራም እንደሚቀጥል ሜጀር ጄኔራሉ ተናግረዋል።ከዚህ ጎን ለጎን የተፈናቀሉትን መልሶ የማቋቋምና የሕዝቡን የዕለት ተዕለት ኑሮ ቀድሞ ወደነበረበት የመመለስ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።ሜጀር ጄኔራል አስራት ዴኔሮ “በመተከል ዞን የተጀመረው የሕግ የበላይነትን የማረጋገጥ ተልዕኮ በአጭር ጊዜ ይጠናቀቃል” ብለዋል ሲል የዘገበው ኢዜአ ነው።
0
9ec08d08fce97f0e9743b4252d4dc151
9ec08d08fce97f0e9743b4252d4dc151
አርባምንጭ ከተማ እና ላኪ ሰኒ ተለያይተዋል
አርባምንጭ ከተማ በክረምቱ ሲዳማ ቡናን በመልቀቅ ክለቡን ከተቀላቀለው ናይጄርያዊ አጥቂ ላኪ ሳኒ ጋር መለያየቱ ታውቋል።በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አስከፊ አጀማመርን ያደረገው አርባምንጭ ከተማ በክረምቱ በዝውውር መስኮቱ ባልተለመደ ሁኔታ ሶስት የውጭ ተጫዋቾች ያስፈረመ ቢሆንም የውድድር አመቱ ከመጀመሩ በፊት ከጋናዊው አጥቂ ሰይዱ ባንሴ ጋር መለያየቱ ይታወሳል። አሁን ደግሞ ሌላኛውን ናይጄሪያዊ አጥቂ ላኪ ሳኒን አሰናብቷል። ክለቡ ለሶከር ኢትዮጵያ እንደገለፀው ከሆነ ተጫዋቹ በክለቡ እያሳየ ባለው አቋም ደስተኛ ካለመሆናቸው በተጨማሪ አሞኛል በሚል ሰበብ በልምምድ ላይ በተደጋጋሚ ባለመገኘቱ ምክንያት ከተጫዋቹ ጋር ለመለያየት ተገደዋል።አሁን አሁን ወደ ሀገራችን የሚመጡ የውጭ ተጫዋቾች ከክለቦች ጋር በተለያዩ ምክንያቶች እምብዛም አገልግሎት ሳይሰጡ ወደ ሀገራተው ሲመለሱ ይስተዋላል። በዚህ አመት ብቻ ከውጭ ከመጡ ተጫዋቾች መካከል ፒተር ዱስማን (ደቡብ ሱዳን/አዳማ) ፣ ሂላሪ ኢኬና (ናይጄሪያ/ወላይታ ድቻ) ፣ ሰይዱ ባንሴ (ጋና/አርባምንጭ) ፣ ሮበርት ሴንቴንጎ (ዮጋንዳ/ፋሲል – በድጋሚ ተመልሷል) ፣ ክርስቶፎር አሞስ ኦቢ (ናይጄርያ/ፋሲል) ይጠቀሳሉ።
1
b5bc54d10e8893643d0c8170d6806de8
b5bc54d10e8893643d0c8170d6806de8
የአማራ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝና የጋምቤላ ክልሎች ከ3 ሺህ 550 በላይ ለሚሆኑ የህግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረጉ
የአማራ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና የጋምቤላ ክልሎች ከ3 ሺህ 550 በላይ ለሚሆኑ የህግ ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጋቸውን አስታወቁ።የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ሀላፊ አቶ ፍርዴ ቸሩ እንደተናገሩት፥ የክልሉ መንግስት ለህግ ታራሚዎቹ ይቅርታውን ያደረገው የ2011 አዲስ ዓመትን አስመልክቶ ነው።ለህግ ታራሚዎቹ ይቅርታ የተደረገውም የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ የይቅርታ ቦርድ ከ3 ሺህ በላይ ታራሚዎቹ ይቅርታ ተደርጎላቸው እንዲፈቱ ያቀረበውን ጥያቄ ተከትሎ መሆኑንም አስታውቀዋል።ይቅርታ የተደረገላቸው የሀግ ታራሚዎችም ከዛሬ ማለዳ ጀምሮ ከማረሚያ ቤቶች እየወጡ ቤተሰቦቻቸውን መቀላቀል መጀመራቸውንም አቶ ፍርዴ አስረድተዋል።በተመሳሳይ የጋምቤላ ክልል የማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ሀላፊ ኮሚሽነር ቲቶ ሀዋርያ እንደተናገሩት፥ በክልሉ የተለያዩ ወንጀሎችን በመስራት ተፈርዶባቸው የነበሩ ከ370 በላይ ታራሚዎች ከእስር እንዲፈቱ ተደርጓል።የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ሀላፊ ኮሚሽነር አዲሱ ሀተሴም በክልሉ የተለያዩ ወንጀሎችን ሰርተው ተፈርዶባቸው የነበሩ 188 ታራሚዎች በይቅርታ መፈታታቸውን አስታውቀዋል።ከእነዚህ ውስጥም ዘጠኙ ሴት ታራሚዎች መሆናቸውን ኮሚሽነር አዲሱ ተናግረዋል።(ኤፍ.ቢ.ሲ)
1
3c455a3fc935cfeef1a781f3584092c4
3c455a3fc935cfeef1a781f3584092c4
እንጂነር ስመኘው በቀለ እራሳቸውን ማጥፋታቸውን ፌደራል ፖሊስ አስታወቀ
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ እንጂነር ስመኘው በቀለ እራሳቸውን ማጥፋታቸውን ፖሊስ ባደረገው ምርመራ ማረጋገጡን አስታወቀ ።የፌደራል ፖሊስ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጋር በመተባበር በዛሬው ዕለት ይፋ ባደረገው መግለጫው እንደገለጸው በሐምሌ 19 ፣ 2010 ዓም ጥዋት 2:30 ሰዓት ላይ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት እንጂነር ስመኘው በቀለ በራሳቸው ሽጉጥ እራሳቸውን ማጥፋታቸውን የፎረንሲክ ምርመራ ውጤቱ እንደሚያሳይ ተገልጿል ።እንጂነሩ የተኮሱት ጥይት በግራ ጆሯቸው ገብቶ በቀኝ ጆሮ አካባቢ የወጣ መሆኑን የገለጸው ፖሊስ አደጋው ኢንጂነሩ ከሞቱ በኋላ በመኪናቸው ውስጥ ሁለት ፖስታዎች መገኘታቸው ተመልክቷል ።የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ዘይኑ ጀማል በመግለጫው ወቅት እንደተናገሩት እንጂነር ስመኘው ከመሞታቸው አንድ ቀን ቀደም ብለው ትልቅ ልጃቸው ማጥናት እንዳለበትና መረጃ መገኘቱን ገልጸዋል ።በተጨማሪም ስመኘው ጠዋት ላይ ቢሮ መገኘታቸውና ለሁለት ሹፎሮቻቸውና ለጸሓፊያቸው ስልክ ጭምር በመደወል በፖስታ የታሸገ ማስታወሻ እንዲሰጥላቸው ማድረጋቸውን ያነሱት ኮሚሽነሩ ኢንጂነሩ በምን ምክንያት እንደሞቱ በትክክል የሚያስቀምጡ አለመሆናቸው ግን አያይዘው ገልጸዋል ። እንጂነሩ በምን ምክንያት ሞቱ የሚለውን ለወደፊቱ ይበልጥ በዝርዝር ምርመራ የሚደረግበት መሆኑ የጠቆሙት ኮሚሽነሩ የግድቡ ግንባታ በተፈለገው ደረጃ አለመድረስና እስካሁን የወጣው ወጪ ከፍተኛ መሆን እራሳቸውን ለማጥፋት ምክንያት እንደሆነ በጥርጣሬ አስቀምጠዋል ።
1
7229c58fb0bb02a8d7953da4d95472e7
7229c58fb0bb02a8d7953da4d95472e7
የተጓተተው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ህንፃ ግንባታ ሊጀመር ነው
አዲስ አበባ፡- ለ10 ዓመታት ይጀመራል እየተባለ በተለያዩ ምክንያቶች ሲጓተት የነበረው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ህንፃ ግንባታ ጥር 15 ቀን 2011 ዓ.ም ከተቋራጩ ጋር ውል ታስሮ ወደ ሥራ ሊገባ መሆኑን ቴአትር ቤቱ አስታወቀ፡፡የቴአትር ቤቱ የግዥ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ እዮብ ታምሩ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ ዘመናዊው ባለአራት ፎቅ የቴአትር ቤት ህንጻ ግንባታ ጨረታውን ካሸነፈው አፍሮ ጽዮን ኮንስትራክሽን ድርጅት ጋር ውል በመግባት ግንባታው እንደሚጀመር አስታውቀዋል፡፡የሚገነባው ህንፃ ዘመናዊ ቴአትር ቤት የሚያሟላውን ሁሉንም ነገር የያዘ ሲሆን፤ በምሥራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ይሆናል፡፡ የቴአትር መመልከቻ አዳራሹ ዘመናዊ የድምጽና የመብራት ሥርዓት ይኖረዋል፡፡ ከወጥ ቤት እስከ ዘመናዊ የስፖርት ማዘውተሪያ ድረስ እንደሚይዝም ዳይሬክተሩ አመላክተዋል፡፡እንደ አቶ እዮብ ገለጻ፤ ግንባታው የሚካሄደው በአሁኑ ወቅት እንደ ቢሮ በሚጠቀሙበት ቦታ ላይ ስለሆነ ሌላ ቢሮ ተከራይተው ለግንባታው ለቀዋል፡፡ የኮንትራክተር መረጣና የግንባታ ፈቃድ ቀደም ሲል ተጠናቅቋል፡፡ ከበጀት ጋር ተያይዞ ለሚቀጥለው ዓመት ይተላለፍ አይተላለፍ የሚባለው ታይቶ በዘንድሮ ዓመት ግንባታው እንዲካሄድም የገንዘብ ሚኒስቴር ፈቅዷል፡፡ግንባታውን በበላይነት የሚቆጣጠረው የቤቶችና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር መረጃ እንደሚያመለክተው፤ ግንባታው 1.4 ቢሊዮን ብር የሚፈጅ ሲሆን፤ በሦስት ዓመት ጊዜ ውስጥም ይጠናቀቃል፡፡ ህንፃው ዘመናዊ ቴአትር ቤት የሚያስፈልገውን ሁኔታዎች ሁሉ የያዘ መሆኑን ያረጋግጣል፡፡የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ቤት የተገነባው ከ64 ዓመት በፊት ሲሆን፤ 1ሺ200 አካባቢ ተመልካች የመያዝ አቅምም አለው፡፡ በአሁኑ ወቅት ግን ጣራው የማፍሰስ ችግር ስላለበት ዝግጅቶችን በአግባቡ ለማካሄድ እያስቸገረ ነው፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 24/20111በአጎናፍር ገዛኽኝ
1
6cb725a7543bd577dac231b581aad341
3960a7f080031ac61c069f42c281f61e
የሐምሌ 22 አጫጭር ዜናዎች
ሥመ ጥሩዋ ጋዜጠኛ ግዌን አይፊል የዜና ረፍትን ተከትሎ የሲ ኤን ኤን የምሽት ዜናዎች ጋዜጠኛ ዶን ሌመን“ወንዶች በበዙበት የሙያ ስምሪትሽ ዘመን ፆታና ቀለም ሳይበግርሽ በችሎታሽና በማይናወጥ ትኩረትሽ ለሃያልነት የበቃሽ” ሲል አድንቁዋታል።ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ“ለዴሞክራሲያችን ስምረት ዋስትና ለሆነው ለነፃና ጠንካራ ፕሬስ የቆመች” ሲሉ አክብረዋታል። ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
0
e341e94be794c479436cc1675de644e7
3fbcd0ab80719b665a48f66d9de4c509
ዓብይ አህመድ ከፔንስ ጋር ተነጋገሩ
እሁድ ነሐሴ 20 ቀን 2010 ዓ.ም. ያለመከሰስ መብታቸው በሶማሌ ክልል ምክር ቤት የተነሳባቸው የቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ ሙሐመድ ዑመር (አብዲ ኢሌ)፣ ዛሬ ሰኞ ነሐሴ 21 ቀን 2010 ዓ.ም. በቁጥጥር ሥር ዋሉ፡፡ከአቶ አብዲ ጋር ያለመከሰስ መብታቸው የተነሳባቸው የክልሉ የሴቶችና ሕፃናት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ራህማ ሐይባ፣ የክልሉ የፍትሕ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዲ ጀማል አህመድ፣ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም አድን ሳባ፣ የጅግጅጋ ከተማ ከንቲባ አቶ ኢብራሂም መሐመድ ሙባረክ፣ የክልሉ ምክር አባላት አቶ ዴክ አህመድ ቡራሌና አቶ ዑመር መሐመድ ናቸው፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ለመጀመርያ ጊዜ ቅዳሜ ነሐሴ 19 ቀን 2010 ዓ.ም. በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የፕሬዚዳንቱ ጉዳይ በሕግ የሚታይ እንደሆነ አስታውቀ ነበር፡፡ በሶማሌ ክልል ይፈጸም የነበረው የሰብዓዊ መብት ጥሰት በፊልም የሚታይ ልብ ወለድ እንጂ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚደረግ አይመስልም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ታሳሪዎች የሚጠበቅባቸውን ብቻ ሳይሆን ከሚጠበቅባቸው በላይ እንዲናዘዙ ከአንበሳ፣ ከጅብና ከነብር ጋር እንደሚታሰሩ ገልጸዋል፡፡ ይህ ድርጊት በታሳሪዎቹ ላይ ይፈጽም የነበረው ለማስፈራራት እንደነበረም ተናግረዋል፡፡
0
2ada5e33fc4ca213ad785edb962ecca3
2c4c29da909e10735b690c35d9a5b6b3
ኢትዮጵያ በ2003 በግብፅ የተከሰተውን የፖለቲካ ትኩሳት ተጠቅማበታለች ስትል ግብጽ አስታወቀች
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 12፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙርያ በግብፅ የሚደረገውን የዲፕሎማሲ ጫናና የሴራ ፖለቲካ እስከ መጨረሻው ለማክሰም የግድቡን ግንባታ በፍጥነት ማጠናቅቅ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን የፖለቲካ እና የታሪክ ምሁራን ተናገሩ።ምሁራኑ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ባደረጉት ቆይታ የግድቡ ግንባታ በተፋጠነ ቁጥር ከካይሮ ሊሰነዘሩ የሚችሉ የአጅ አዙር የደህንነት ስጋቶችን ለመቀልበስ ሁለም ኢትዮጵያዊ በንቃት መጠበቅ ይገባዋል ብለዋል።በአዲስ አበባ ዩኒቨረሲቲ የታሪክ ትምህርት ተመራማሪ ተባባሪ ፕሮፌሰር ተፈሪ መኮንን፥ ኢትዮጵያ በዓባይ ጉዳይ ባጎረስኩ ተነከስኩ ብሂል እየተጓዘች ያለች ሀገር ናት ብለዋል።ዶክተር ተፈሪ፥ የእስካሁኑን የዓባይ ወንዝ ፖለቲካ ኢፍትሃዊ አካሄድ መቀልበስ የሚቻለው ግድቡን በማጠናቀቅ ነው ይላሉ።ኢትዮጵያ የካይሮን የዘመናት የናይል ወንዝ ለብቻዬ ልጠቀም የጥቅላላ ውሃ ፖለቲካ ለማስተካከል የዓባይ ወንዝ ተፋሰስ የትብብር ማዕቅፍ እንዲመሰረት አድርጋለች ነው ያሉት።ይህ ማዕቀፍ ግን በካይሮ ሰዎች አሳሳች ዲፕሎማሲ እና ኢትዮጵያን አግላይ ስልት ከተገቢው ደረጃ አልደረሰም።የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህሩ እና በብሉ ናይል የውሃ ምርምር ማዕከል የውሃ ጉዳይ ተመራማሪ ውብእግዜር ፈረደ፥ የግብፅ አካሄድ የመስኖ ስራዬ ይጎዳል አልያም ግድቡ የከፋ ተፅእኖ ያደርሳል ከሚል አመክንዮ የመጣ አይደለም ነው የሚሉት።አቶ ውብ እግዜር ፈረደ እንደሚሉት፥ የዓባይ ወንዝን የፖለቲካ ካርድ መምዘዣ ማድረግን ማስቆም ይገባናል ባይ ናቸው።ዶክተር ተፈሪ መኮንን ደግሞ፥ በህብረተሰቡ ዘንድ በህዳሴው ግድብ ዙርያ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ግንዛቤ እንዲፈጠር መሰራት ያለበት ጉዳይ አለ ባይ ናቸው።በስላባት ማናዬ
0
04f30d32c73ba3e6a5a5e0b7d1c86c15
e1044bb4428a9fed92e3bac31d525346
ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮጵያ ቡና ከአሞሌ ጋር ስምምነት ፈፀሙ
11፡30 በተደረገው ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ በአዳነ ግርማ የ27ኛ ደቂቃ ግብ የመጀመርያውን አጋማሽ 1-0 እየመራ አጠናቋል፡፡ ዩጋንዳዊው ብሪያን ኡሞኒ በጨዋታው የመጨረሻ ደቂቃ የቅዱስ ጊዮርጊስን መሪነት አስተማማኝ ያደረገች ግብ አስቆጥሮ ጨዋታው በቅዱስ ጊዮርጊስ 2-0 አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡ድሉን ተከትሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ16 ነጥብ ከአዳማ ከነማ በ3 ነጥቦች አንሶ ሁለተኛ ደረጃን ሲይዝ ደደቢት 3ኛ ደረጃውን ለሲዳማ ቡና አስረክቦ ወደ 4ና ደረጃ ወርዷል፡፡የ7ኛ ሳምንት ጨዋታ ውጤቶችሀዋሳ ከነማ 1-2 አዳማ ከነማቅዱስ ጊዮርጊስ 2-0 ደደቢትሀዲያ ሆሳእና 5-1 ወላይታ ድቻአርባምንጭ ከነማ 2-0 ኢትዮጵያ ቡናሲዳማ ቡና 1-0 መከላከያድሬዳዋ ከነማ ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክዳሽን ቢራ ከ ኤሌክትሪክየሊጉ ውድድር በቻን ምክንያት ለመጪዎቹ 45 ቀናት የሚቋረጥ ሲሆን የ8ኛ ሳምንት ጨዋታዎች የካቲት 5 ይደረጋሉ፡፡
0
a1d6a480419922ad7e1a9bd85ada2752
6881460c6cc918b0bf84a341ff6c2277
የህብረቱ መሪ ሀሳብ የአፍሪካን ወቅታዊ ሁኔታ ያገናዘበ ነው – አቶ ነቢያት ጌታቸው
የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ኢንዱስትሪ ቀን በየዓመቱ ህዳር 20 ቀን እንዲከበር በወሰነው መሰረት የዘንድሮ በዓል ትናንት በኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል ተከብሯል፡፡የአፍሪካን ልማትና ዕድገት ለማፋጠን ኢንዱስትሪ ወሳኝ በመሆኑ አፍሪካውያን ለኢንዱስትሪ ልማት ትኩረት መስጠት እንዳለባቸው በዕለቱ ተገልጿል፡፡የዘንድሮ የአፍሪካ ኢንዱስትሪ ቀን ከተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት 50ኛ ዓመት በዓል ጋር መከበሩ የተለየ ያርገዋል ተብሏል፡፡የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የንግድና ኢንዱስትሪ ተወካይ የአፍሪካን የኢንዱስትሪ ጉዞ ለማቀጣጠል የግልና መንግስታዊ የገንዘብ ተቋማት ድጋፍ ማድረግ እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡የገንዘብ ፍሰት፣ ምቹና አስተማማኝ ፖሊሲ፣የመንግስታት ቁርጠኝነት የአፍሪካን ኢንዱስትሪ ለማፋጠን ወሳኝ መሆናቸውንም አስረድተዋል፡፡በጉባዔው እንደተመለከተው ከሰሀራ በታች በሚገኙ አገራት የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት እያደገ ነው፡፡ እአአ በ2010 ዓ.ም 28 ቢሊዮን ዶላር የነበረው የውጭ ኢንቨስትመንት ፍሰት በ2015 ዓ.ም 40 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል፡፡ቀኑ ‹‹የአፍሪካን ኢንዱስትሪ በገንዘብ ለመደገፍ ያሉ ተግዳሮቶችና ምቹ ሁኔታዎች›› በሚል መሪ ቃል ተከብሯል፡፡እአአ በ2063 የበለፀገች አፍሪካን ዕውን ለማድረግ የኢንዱስትሪ ዘርፉን ማጠናከር እንደሚገባ መመልከቱን ዋልታ ዘግቧል፡፡
0
e39aeb3a5a8aa32a4a17a18f4e945b85
bdafbb6781fd7931d933993b548c65b1
የመከላከያ ሰራዊት መቐለ ከተማን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሯል- ጄኔራል ብርሀኑ ጁላ
አዲስ አበባ፣ ህዳር 13፣ 2013 (ኤፍቢሲ) የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት በአድዋ ተምቤን መሥመር ማይቅናጥል በተባለውና ልዩ ስሙ ሰላስል በተሰኘው የሐውዜን ተምቤን መገንጥያ መንገድ የገጠመውን የጁንታውን ኃይል ድል አድርጓል።በዚሁ መገንጠያ ላይ የሠራዊቱን ግሥጋሴ ለመግታት በኮሎኔል ጸጋዬ ማርክስና በኮሎኔል ሸሪፎ የሚመራው የጁንታው አንድ ክፍለ ጦር ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል፡፡የመከላከያ ዘመቻ ዋና መመሪያ ማምሻውን እንዳስታወቀው የመከላከያ ሠራዊት ክፍለ ጦሩን ሙሉ በሙሉ ከደመሰሰ በኋላ ወደ መቀሌ የሚያደርገውን ጉዞ አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡
0
00af6d7dc283f189c1abb61b51423528
6ed45a15b13c7e7bc5345719c6a0084a
በጎንደር ግጭት ወደ ሱዳን የተሰደዱ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ
በማላዊ እስር ቤት ውስጥ የነበሩ 34 ኢትዮጵያውያን ዜጎች በዛሬው ዕለት ወደ ሀገራቸው እንደሚመለሱ በኬንያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታወቀ።ኢትዮጵያውያኑ ወደ ሀገራቸው የሚመለሱትም ኤምባሲው ከሚመለከታቸው የማላዊ መንግሥት ባለሥልጣናት ጋር ባደረገው ውይይትና በተደረሰው ስምምነት መሠረት ነው።በተያያዘ ዜና በህገ ወጥ መንገድ ወደ ኬንያ ለመግባት ሲሞክሩ በኬንያ የፀጥታና ደህንነት አካላት በቁጥጥር ሥር ውለው በኬንያ እስር ቤት ውስጥ የሚገኙ 42 ኢትዮጵያውያን በናይሮቢ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባደረገው ጥረት በቅርቡ ወደ ሀገራቸው የሚመለሱ መሆኑ ነው የተገለፀው።በኬንያ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ማላዊ የሚከናወነውን የዲፕሎማሲ ስራ የሚሸፍን መሆኑ ይታወቃል።ኤምባሲው በያዝነው መጋቢት ወር መጀመሪያ ላይም በህገ ወጥ መንገድ ወደ ኬንያ በመግባታቸው በሀገሪቱ የፀጥታ አካላት በቁጥጥር ስር የነበሩ 103 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ማድረጉ ይታወሳል።ምንጭ፡- በኬንያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ
0
6d6875f5756769592dc7214742d817ec
e03f426c21f8a00753dc2adbecfb530a
አፈ ጉባኤው 9ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን በመጪው ሰኞ እንደሚከበር አስታወቁ
ባሕር ዳር፡ መስከረም 20/2012 ዓ/ም (አብመድ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ2ዐ12 ጥራትን፣ ተናባቢነትንና ተፈፃሚነትን በማረጋገጥ ሀገራዊ ለዉጡን ሊደግፉ የሚችሉ የሕግ ማዕቀፎችን በማዘጋጀት የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማፋጠን አንደሚሠራ አፈ-ጉባኤ ታገሠ ጫፎ አስታወቁ፡፡ለፓርላማ ተጠሪ የሆኑ ተቋማት አሠራራቸውንና አደረጀጀታቸውን ፈትሾ በማስተካከል የኅብረተሰቡን የመልካም አስተዳደርና የልማት ችግሮችን በመፍታት የተጀመረውን ለውጥ ማስቀጠል እንደሚገባም አፈ-ጉባኤ ታገሠ ጫፎ ተናግረዋል፡፡ምክር ቤቱ በዘንድሮው ዓመት በ2ዐ11 ለምክር ቤቱ በዋና ኦዴተር ከቀረበው ሪፖርት ግኝት በመነሳት የተጓደሉ የአሠራር ሥርዓቶችን ፈትሾ በማስተካከልና የሀብት አስተዳደር ሥርዓትን በመዘርጋት የሀገሪቱ ሀብት በአግባቡ ጥቅም ላይ መዋሉን ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሠራ አፈ ጉባኤ ተናግረዋል፡፡በምክር ቤቱ በአምስተኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ የሀገራዊ ምርጫ እና የሕዝብና ቤቶች ቆጠራ በተሳካ ሁኔታ እንዲከናወን፣ በምክር ቤቱ የጸደቁ አዋጆችን ከባለድርሻ አካላት ጋር ተፈፃሚነታቸውን በመከታተል ግልፅና ተዓማኒነት እንዲኖረው በማድረግ ረገድ ትልቅ ሥራ እንደሚጠብቅም አስረድተዋል፡፡ምክር ቤቱ በ4ኛ ዓመት የምርጫ ዘመኑ የምክር ቤት አባላት ከወትሮው በተለየ መልኩ በሚወጡ ሕጎች ዙሪያ ሰፊ ውይይትና ክርክር አንዲሁም ባለተለመደ መልኩ በተቃውሞና በድምፀ ተዓቅቦ፣ በአብላጫ ድምጽ ሕጐች መጽደቃቸውን አፈ ጉባኤው አስታውሰው ይህም በምክር ቤቱ ዴሞክራሲ እየጎለበተ መምጣቱን አመላካች በመሆኑ ዘንድሮም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ምክር ቤቱ በዋናነት ሕግ የማውጣት ተግባርን የሚያከናውን ሲሆን በ2ዐ11 ዓ.ም የወጡ ሕጎች በሀገሪቱ ከተጀመረው ለውጥ ጋር የሚጣጣምና አጋዥ የሆኑ ሕጐች ጸድቀው ወደ ተግባር መገባቱንም ገልፀዋል፡፡ምክር ቤቱ በ2ዐ11 ዓ.ም ባደረገው የክትትልና የቁጥጥር ሥራ አንዳንድ ተቋማት ላይ የሚስተዋሉ የአሰራር ክፍተቶችን በመለየት ችግሩን በዘላቂነት ለመፈታት የሚያስችሉ የአሠራር ሥርዓቶች የመዘርጋትና የመቋቋሚያ አዋጆችንም ጭምር እንዲሻሻሉ የማድረግ ሠራ መሠራቱን አፈ ጉባኤው አስታውሰዋል፡፡
0
2692d071dd951702c61d35ae480a51d9
38a79e0a96653e3c4bbf79922acef079
የሎጅስቲክስ ስትራቴጂ መተግበር የዘርፉን ችግሮች በመፍታት ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ የእንግሊዝ ጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ሰር ኒኮላስ ሆይተን የተመራውን የልኡካን ቡድንን ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።በውይይቱ ላይ ሁለቱ ሀገራት በአፍሪካ ቀንድ ጸጥታ ዙርያ ተባብረው መስራት የሚችሉበትን መንገድ መክረዋል።ኢትዮጵያ በተለይም የሶማልያንና ደቡብ ሱዳንን ጸጥታ ለማረጋገጥ እያበረከተች ያለችውን አስተዋጽኦ የሚደነቅ ነው ሲሉም ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ገልጸውላቸዋል።ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ እንግሊዝ ለአካባቢው ጸጥታ ከፍተኛ ትኩረት መስጠቷን አስታውሰው ውይይቱ የአካባቢውን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ለሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚያቀርቡት ሪፖርት አካል መሆኑን ገልጸዋል።አያይዘውም ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ በተለይም በሶማሊያ ጉዳይ ከሰላም አስከባሪው አሚሶም ጋር በመተባበር በአልሸባብ የሚሰነዘረውን ጥቃት ለማስወገድ እያደረገች ያለችውን አስተዋጽኦ አድንቀዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በበኩላቸው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድን በተለይም የሶማሊያንና ደቡብ ሱዳንን ጸጥታ ለማረጋገጥ እያበረከተች ያለችውን አስተዋጽኦ መግለፃቸውን ውይይቱን የተከታተሉት አንድ የወጭ ጉዳይ ከፍተኛ የስራ ሃላፊ ገልፀዋል፡፡ሁለቱ ሃገራት የሶማሊያን ብሄራዊ መከላከያ ሃይል ዓቅም በመገንባት ረገድ እና የደቡብ ሱዳንን ጸጥታ ለማረጋገጥ ከኢጋድ ጋር እየተደረገ ያለውን ጥረት በመደገፍ ረገድ አብረው መስራት የሚችሉበት መልካም እድል እንዳለ አብራርተውላቸዋል።በኤታማዦር ሹሙ የሚመራው ልኡካን ቡድን በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ ለመገምገም ቀጣይ ጉብኝቶችን ያካሂዳል ተብሎ ይጠበቃል።(ኢዜአ)
0
915c787d1c635287fc64f398da990e93
67f1bc88fa7d68b15fec1848158fc5cd
የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የተሻሻለ መርሐ ግብር
የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 13ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከቅዳሜ ጀምረው ሲከናወኑ የመርሐ ግብሩ አካል የሆኑ አራት ጨዋታዎች የቀን ለውጥ ተደርጎባቸዋል። ለውጥ ከተደረገባቸው ጨዋታዎች መካከል የሀዲያ ሆሳዕና እና ወላይታ ድቻ ጨዋታ አንዱ ነው። ጨዋታው እሁድ አቢዮ ኤርሳሞ ላይ እንዲከናወን ቢወሰንም ሀዲያ ሆሳዕና ሁለት የሜዳው ጨዋታዎችን በገለልተኛ ሜዳ እንዲያደርግ በመቀጣቱ ምክንያት ወደ ሀዋሳ ተዘዋውሯል። በዚህም ማክሰኞ የካቲት 3 የሚከናወን ይሆናል። በሀዋሳ ቅዳሜ እና እሁድ ሊደረጉ የነበሩት ሁለት ጨዋታዎች በአንድ ቀን ተገፍተው እሁድ እና ሰኞ ይከናወናሉ። ቅዳሜ የነበረው የሀዋሳ ከተማ እና ጅማ አባ ጅፋር ጨዋታ እሁድ ሲወናወን እሁድ የነበረው የሲዳማ ቡና እና አዳማ ከተማ ጨዋታ ወደ ሰኞ ተሸጋሽጓል። የእነዚህ ጨዋታዎች የቀን መሸጋሸግ ምክንያት ግን አልታወቀም። ሌላው በዚህ ሳምንት የቀን ሽግሽግ የተደረገበት ጨዋታ የኢትዮጵያ ቡና እና ወልቂጤ ከተማ ጨዋታ ነው። እሁድ ሊደረግ የነበረው ይህ መርሐ ግብር በአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ምክንያት ወደ ሐሙስ የካቲት 5 (10:00) ሊሸጋገር ችሏል። የተሻሻለው የ13ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ይህንን ይመስላል©ሶከር ኢትዮጵያ
0
c2b8a0d97416926ab9090d4c696b1df9
23fe4cb6707c18f0a36a8a470f089722
“ሁኔታው እንደ መሪም እንደ ዜጋም ልብ ይሰብራል” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ከደቡብ ብሔሮች፣ ብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልል የዞን አመራሮች ጋር ተወያይተዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ ውይይቱን አስመልክተው በፌስቡክ ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት “የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልል በብዙ የተፈጥሮ እና የባህል መስህቦች የታደለ ነው”። እነዚህን መልካም ጎኖች ለመጠቀም በጋራ ከሠራን፣ ክልሉ ለሌሎች የሚተርፍ የልማት ማዕከል እንደሚሆን ለበርካታ ጊዜያት መናገራቸውንም አስታውሰዋል።“ባለፉት ሁለት ዓመታት፣ ወደ ክልሉ በተደጋጋሚ በመጓዝ ለማኅበረሰብ ልማት በእጅጉ ስለሚያስፈልጉ ጉዳዮች ከአንደበታቸው አድምጫለሁ፤ ሁሉንም መሠረታዊ ፍላጎቶች በአንድ ጊዜ ለማሟላት የሚቻል ባይሆንም፣ በዚህ ወቅት ዐበይት የመሠረተ ልማት፣ የኢንቨስትመንት እና ተያያዥ ሥራዎች ተከናውነዋል” ሲሉም ገልፀዋል።በዛሬው እለትም ከክልሉ የዞን አመራሮች ጋር በነበራቸው ውይይት፣ በደቡብ ክልል ባለ ብዙ ገጽ ዕድገት እና ዘላቂ ሰላም እንዲኖር የአስተዳደራዊ መዋቅር መርኆውን ቅድሚያ ሰጥቶ መመልከት አስፈላጊ እንደ ሆነ መስማማታቸውንም አስታውቅዋል።በዚህ ውይይት፣ በዝርዝር ሊታዩ የሚገባቸው ሌሎች ጉዳዮችም ተነሥተዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ፥ “ጉዳዮቹ የበለጠ ዳብረው ተመልሰን እንድንወያይባቸው ስምምነት ላይ ደርሰናል” ብለዋል።
0
2a24c4ca5affae0e8bd0b0baeed8cdb8
2a24c4ca5affae0e8bd0b0baeed8cdb8
ሁከቱ በቱሪስቶች ምንም ጉዳት እንዳላደረሰ ሚንስቴሩ አስታወቀ
በኢትዮጵያ ተከሰቶ በነበረው ሁከትና አለመረጋጋት በቱሪስቶች ላይ አንዳችም ጉዳት እንዳልደረሰ የባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር አስታወቀ፡፡የሚኒስቴሩ የቱሪዝም ልማት ዘርፍ ሚንስቴር ዴኤታ ወይዘሮ ታደለች ዳልቾ ትናንት ከሆቴል ባለሐብቶችና ሥራ አስኪያጆች ጋር ባደረጉት የምክክር መድረክ በቅርቡ በሀገሪቱ የነበረውን ሁከትና ግጭት ተከትሎ በቱሪስቶች ላይ የንብረት፣ አካል ወይም የሕይወት ጉዳት እንዳልደረሰ ገልጸዋል፡፡ይሁንና ወይዘሮ ታደለች እንደገለጹት፤ በሆቴሎችና ሎጆች ላይ ከፍተኛ የንብረት መውደም ከመድረሱም ባሻገር በቱሪዝም ኢንዱስትሪው መቀዛቀዝ መታየቱን ገልጸዋል፡፡የተቀዛቀዘውን የቱሪዝም ኢንደስትሪ ለማነቃቃት እንዲቻል ከአስጎብኝዎች፣ የሆቴሎች ማሕበርና የኢትዮጵያ አየር መንገድ የተውጣጣ ንዑስ ኮማንድ ፖስት ተቋቁሞ ወደ ሥራ መግባቱን ጠቁመዋል፡፡በሆቴሎች፣ ሪዞርቶችና ሎጆች ላይ የደረሰውን ጉዳት በተመለከተ ባለሐብቶቹ የደረሰባቸውን ጉዳት በተደራጀ መልኩ መረጃው ለኮማንድ ፖስቱ ቢያቀርቡ መረጃዎቹ ተለይተውና ተተንትነው ከሚመለከተው አካል ጋር በመሆን መፍትሄ ለመሻት ጥረት እንሚደርግም አስታውቀዋል፡፡የቱሪዝም ኢንደስትሪውን ወደነበረበት ለመመለስ እንዲቻል ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍል ሰላምን በማስከበር በኩል የድርሻውን እንዲወጣ ሚንስቴሩ ጥሪውን አቅርቧል፡፡፡የውይይቱ ተሳፊዎች በሁከትና ግርግሩ ሳቢያ የቱሪዝም ፍሰቱ በመቀነሱ ከፍተኛ የሆነ ገቢ እጥረት እንዳጋጠማቸው አመልክተዋል፡፡ስለሆነም ባንኮች የብድር እፎይታ ጊዜ እንዲሰጧቸው መንግስት ሁኔታዎቹን እንዲያመቻችላቸው ጠይቀዋል፡፡አሁን በሀገሪቱ የተፈጠረውን ሰላምና መረጋጋት ቱሪስቶች እንዲያውቁት የመገናኛ ብዙኃንና የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች ከፍተኛ ሥራዎችን ማከናወን እንዳለባቸው አመልክተዋል ፡፡የአዲስ አበባ ሆቴሎችና ሪዞርቶች ከ20 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ነው በውይይቱ የተመለከተው ፡፡አዲስ አበባ ከጄኔቫና ኒውዮርክ በመቀጠል ከፍተኛ የቱሪዝም የኮንፍረንስ መዳረሻ እንደሆነች የሚታወቅ መሆኑን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል፡፡
1
8d073283a566178b382ee3b7c6ec55c4
8d073283a566178b382ee3b7c6ec55c4
“የኢትዮጵያ ተጫዋቾች ፍጥነት ሊያስቸግረን ይችላል” – ዋሊድ መስሉብ
ለፈረንሳዩ ሎርዮ ክለብ የሚሰለፈው አልጄሪያዊ ዋሊድ መስሉብ የአልጄሪያ ብሔራዊ ቡድን ከኢትዮጵያ ጋር በሚያደርገው ጨዋታ ለተጋጣሚው ዝቅተኛ ግምት ሰጥቶ መግባት እንደሌለበት ተናግሯል። ዋሊያዎቹ ፈጣን እና ጥሩ የእግርኳስ ክህሎት ያላቸው በመሆኑ አልጄሪያውያኑ ጥንቃቄ የተሞላበት ጨዋታ መከተል እንዳለባቸው ነው ተጫዋቹ የገለፀው።“ከኢትዮጵያ ጋር የምናደርጋቸው ሁለቱ ጨዋታዎች ለእኛ እጅግ አስፈላጊ እና ለአፍሪካ ዋንጫው የማለፍ ዕድላችንን የሚወስኑ መሆናቸው ግልፅ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ፈጣን እና ጥሩ የቴክኒክ ችሎታ ያላቸው ተጫዋቾች የሚገኙበት ቡድን ነው። ስለዚህ ለተጋጣሚያችን ተገቢውን ክብር ሰጥተን በጥንቃቄ መጫወት ይኖርብናል፤” ሲል ያለውን አስተያየት ሰጥቷል።የ30 ዓመቱ የአማካይ ሀገሩ ለመጨረሻ ጊዜ ባደረገችው ጨዋታ በዓለም ዋንጫ ማጣሪያው ታንዛኒያን 7-0 ያሸነፈች መሆኑ ወደዛሬው ጨዋታ በልበ ሙሉነት እንዲገቡ ያስቻላቸው መሆኑን የተናገረ ሲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንም ከብሊዳው ጨዋታ ይልቅ አዲስ አበባ ላይ ፈታኝ ሊሆን እንደሚችል ያለውን ግምት ሰንዝሯል።“ምድቡን እየመራን መሆናችን እና የመጀመሪያውን ጨዋታ በሃገራችን መጫወታችን የአዲስ አበባውን የመልስ ጨዋታ የሚያቀልልን ይሆናል። ነገር ግን ከ2000 ሜትር በላይ በሆነ ከፍታ ላይ ባለችው አዲስ አበባ የሚኖረን ጨዋታ ፈታኝ መሆኑ አይቀርም። በፍጥነት አየር ንብረቱን በመላመድ ሁለቱንም ጨዋታዎች ለማሸነፍ መስራት ይኖርብናል። ለጊዜው ግን ሙሉ ትኩረታችን በብሊዳ በሚደረገው ጨዋታ ላይ ነው።”የአልጄሪያ ብሔራዊ ቡድን የኢትዮጵያ አቻውን ዛሬ ከምሽቱ 4፡30 ላይ ቢልዳ በሚገኘው ሙስታፋ ቻከር ስታዲየም የሚያስተናግድ ይሆናል።
1
cd30332a35e570fa3d610d3f58461c06
418b78d29e82e16e44e069407e585e36
የጋሞ ዞን ነዋሪዎች ለመከላከያ ሠራዊት 6 ሚሊየን ብር እና 77 ሠንጋዎችን ለሃገር መከላከያ ሰራዊት አበረከቱ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 10፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የምዕራብ አርሲ ዞን ነዋሪዎች ከ900 በላይ የእርድ ከብቶችንና ከ700 ኩንታል በላይ የምግብ እህል ለኢፌዴሪ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ድጋፍ አድርገዋል፡፡የዞኑ ነዋሪዎች በአጠቃላይ 520 ሰንጋዎች፣ 350 በጎች፣ 60 ፍየሎች፣ 520 ኩንታል ስንዴ፣ 110 ኩንታል በቆሎ እና 100 ኩንታል ቡና በድጋፍ አሰባስበዋል፡፡ድጋፉንም ዛሬ የኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ ከዞኑ አመራር ተረክበዋል፡፡አቶ ፍቃዱ ድጋፉን ከዞኑ አመራር ሲረከቡ ለተደረገው ትብብር ሁሉ አመስግነዋል፡፡ሃላፊው የህወሓት ጁንታ ቡድን የሀገር ኩራትና መከታ በሆነው የሰሜን እዝ ላይ የሽብር ጥቃት መፈፀሙን አንስተው፥ ድጋፉ የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ለሚደረገው ዘመቻ ታላቅ አቅም መሆኑን ተናግረዋል፡፡የምዕራብ አርሲ ዞን አስተዳዳሪ አቶ አበራ ቡኖ በበኩላቸው ዞኑ ከነበረበት የፀጥታ ችግር ወጥቶ ወደ ልማት ስራዎችን መዞሩን እና ለሀገር ደህንነትና ሰላምም የድርሻውን እያበረከተ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡
0
3dadf9126be858fa06c65b8d34a9159d
3dadf9126be858fa06c65b8d34a9159d
ባህር ዳር ከተማ የአሰልጣኙን ውል አራዘመ
አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ በባህር ዳር ከተማ ለተጨማሪ ጊዜ ለመቆየት ውላቸውን አራዝመዋል።ባለፈው ክረምት ባህር ዳር ከተማን ለማሰልጠን የተረከቡት የቀድሞው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና ብሔራዊ ቡድን ረዳት አሰልጣኝ በጣና ሞገዶቹ ቤት መልካም የውድድር ዓመት ያሳለፉ ሲሆን ሊጉ በኮቪድ-19 ምክንያት እስከተሰረዘበት ወቅት ድረስ በተለይ በሜዳው የማይበገር ቡድን በመስራት አራተኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችለው ነበር። ይህን ተከትሎም በክለቡ ለተጨማሪ ሁለት ዓመታት ለመቆየት የሚያስችላቸውን የውል ማራዘምያ በዛሬው ዕለት በተደረገ መርሐ ግብር ተፈራርመዋል።አሰልጣኝ ፋሲል በመርሐ ግብሩ ላይ ባደረጉት ገለፃ በከተማው ያለውን የእግርኳስ መነቃቃት እና በቡድኑ ላይ የታየውን እድገት ለማስቀጠል በማሰብ ውል ማራዘማቸውን የተናገሩ ሲሆን ወደፊት ሊጉ መካሄድ ሲጀምር በተለይ ከሜዳ ውጪ የተመዘገበውን ደካማ ውጤት ለማሻሻል እንደሚሰሩ ገልፀዋል።አሰልጣኙ የሚፈልጓቸውን አዳዲስ እና ውል የሚራዘሙላቸው ተጫዋቾችን በቀጣይ ሁለት ቀናት እንደሚያሳውቁ ሲጠበቅ ክለቡም ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ ወደ እንቅስቃሴ እንደሚገባ ተነግሯል።
1
2842bc61593de9f5ac56b7073049721a
364c0a3a8c8928005c849bf88c86fbb1
የዋልያዎቹ አሰልጣኝ ቅጥር ነገ አቅጣጫ ይሰጥበታል
ለአፍሪካ ሕዳሴ እውን መሆን አባል አገራቱ ሙስናን ለማስቆም በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋቂ መሐማት ገለጹ።30ኛው የሕብረቱ ጉባዔ ከዛሬ ጀምሮ ለሰባት ተከታታይ ቀናት በአዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን፤ በሚል መሪ ሃሳብ ውይይት ከማድረግም ባለፈ አቅጣጫም ይሰጥበታል ተብሎ ይጠበቃል።የሕብረቱ ሊቀ መንበር ሙሳ ፋቂ መሐማት በጉባኤው መክፈቻ ላይ እንዳሉት፤ አፍሪካዊያን እንደ ግብርና፣ ትራንስፖርት፣ ሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ ኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ፣ ፋይናንስ፣ አመራርነት እና የመሳሰሉ በርካታ የሚወያዩባቸው አጀንዳዎች አሏቸው።ይሁን እንጂ ከሁሉም በላይ አፍሪካዊያን ሊመክሩበት የሚገባው ጉዳይ ሙስና መሆን አለበት ብለዋል። "ሙስና ደረጃው ይለያይ እንጂ በአፍሪካ ውስጥ ስር በመስደድ ዕድገቷን እየገታና በሕዝቦች እኩል ተጠቃሚነት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደረ በመሆኑ የዘንድሮው የሕብረቱ ጉባዔ አቅጣጫ እንደሚሰጥበት ይታመናል" ብለዋል።በመሆኑም እኤአ የ2018ቱ ጉባዔ ቀዳሚ አጀንዳ ሙስናን መዋጋት ሲሆን፤ ይህም በአህጉሪቱ ኢኮኖሚና ዕድገት ላይ ከሚያሳድረው ተፅዕኖ አኳያ በአጽንኦት ከመምከርም ባለፈ አቅጣጫ ይሰጥበታል።በአፍሪካ በየዓመቱ ከ143 ቢሊዮን በላይ ዶላር በሙስና እንደሚመዘበር የአፍሪካ ህብረት ከሁለት ዓመት በፊት ይፋ ያደረገው ጥናት ያስረዳል።ይህ ኃብት 25 በመቶ ከሚሆነው የአህጉሪቷ ዓመታዊ ጥቅል ምርት ጋር እኩል ነው።በዚህም አፍሪካዊያን ይህን በመመከቱ ረገድ የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ሙሳ ፋቂ መሐማት አሳስበዋል።ሕብረቱም በዚህ ረገድ የተቻለውን እንደሚያደርግ የገለጹት ሊቀ መንበሩ፤ አባል አገራት በትኩረት ሊሰሩበት እንደሚገባ አሳስበዋል። በባለፈው ዓመት የሕብረቱ ጉባዔ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራና የወጣቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተቀመጠው አቅጣጫና መሪዎች ለተግባራዊነቱ ባደረጉት ያላሰለሰ ጥረት ለውጥ መታየት ጀምሯል ነው ያሉት።የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልንድ ትራምፕ በአፍሪካውያን ላይ ያስተላለፉት የጥላቻ ንግግርን የሚቃወም የአቋም መግለጫ የሕብረቱ መሪዎቹ እንዲነጋገሩበት ሐሳብ ተነስቷል።ጉዳዩም ለሚኒስትሮች እንዲቀርብ ከተሳታፊዎች ጥያቄ የቀረበ ሲሆን፤ ሊቀ መንበሩ ሐሳቡ ለውይይት እንዲቀርብ አጽድቀውታል። (ኢዜአ)
0
123795dc4f1a8e416e38e2e84ed7a317
5591a6185f401b144914cfac08321718
የሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ሚኒስቴር ቤት ኤኒይ ከተባለ ምግባረ ሰናይ ድርጅት ጋር ስምምነት ተፈራረመ
አዲስ አበባ ፣ ጥር 16 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የሱዳን መንግስት ከተቃዋሚዎች ጋር የሰላም ስምምነት ተፈራረመ።ስምምነቱ ከሰሜኑ የሱዳን ህዝቦች ነፃ አውጭ ንቅናቄ (ኤስ ፒ ኤል ኤም፤ ኤን) ጋር የተፈረመ ነው ተብሏል።የአሁኑ ስምምነት በቀጠናው የተያዘው የሰላም እቅድ አካል መሆኑም ነው የተነገረው።ቡድኑ ከፈረንጆቹ 2011 ጀምሮ በትጥቅ ትግል ላይ ቆይቷል።ኤስ ፒ ኤል ኤም፤ ኤን የብሉ ናይል እና ደቡብ ኮርዶፋ አካባቢዎችን የማስተዳደር እቅድ እንዳለው ይነገራል።ምንጭ ፡- አልጀዚራ
0
80a39e85b0af8b1551fa86b8eee04549
4a48e442576a9b88a16f08c6183c7d4c
የ8100 A 3ኛ ዙር ዕጣ ወጣ
አዲስ ዕጣ ስለሚወጣባቸው ቤቶች በቅርቡ ይፋ እንደሚደረግ ተጠቆመባለፈው ዓመት የካቲት 27 ቀን 2011 ዓ.ም. በኢንተርኮንቲኔንታል አዲስ ሆቴል በቀድሞ የከተማ ልማት ሚኒስትር አቶ ጃንጥራር ዓባይና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ (ኢንጂነር)፣ ዕጣ የወጣባቸው የ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ለዕድለኞች ለማስተላለፍ የፌዴራል መንግሥት ውሳኔ እየተጠበቀ መሆኑ ተገለጸ፡፡ ዕጣው በወጣበት ማግሥት በተለይ በርካታ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በተገነቡበት ኮዬ ፈጬ ሳይት፣ ‹ቤቶቹ የተገነቡት በኦሮሚያ ክልልና በይዞታችን ላይ በመሆኑ ተላልፈው ሊሰጡ አይገባም› በማለት በአካባቢው ነዋሪዎች ተቃውሞ መነሳቱ ይታወሳል፡፡ ተቃውሞው ከተሰማ በኋላ ከከተማ አስተዳደሩና ከኦሮሚያ ክልል የተውጣጡ የኮሚቴ አባላት የድንበሩን ሁኔታ አጣርተው እንዲያቀርቡ ውሳኔ መተላለፉም አይዘነጋም፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ቤቶች ልማት ቢሮ ኃላፊ ሰናይት ዳምጠው (ኢንጂነር) የ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ለማስተላለፍ የፌዴራል መንግሥት ውሳኔ እየተጠበቀ መሆኑን ለሪፖርተር የገለጹ ቢሆንም፣ ከተቃውሞው ጋር በተያያዘ በተቋቋመው ኮሚቴ የውሳኔ ሐሳብ ወይም በሌላ አካል ውሳኔ ግልጽ አላደረጉትም፡፡ ቢጠየቁም ‹‹በወቅቱ የተነገረውን እናንተም ታውቃላችሁ፤›› በማለት አልፈውታል፡፡ ጉዳዩ በፌዴራል መንግሥት መያዙ ብቻ ሳይሆን ዕጣ በወጣባቸው ወቅት ግንባታቸው ተጠናቆ የነበረው 80 በመቶ ብቻ እንደነበሩ የገለጹት የቢሮ ኃላፊዋ፣ ቀሪ ግንባታዎች እየተደረጉና መሟላት ያለባቸው መሠረተ ልማቶች እየተከናወኑ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡ ዕጣ የወጣባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች ቁልፍ እንደሚሰጥና እንደሚተላፉም አረጋግጠዋል፡፡ ዕጣ የወጣባቸው የ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶችና አዲስ ዕጣ የሚወጣባቸውን የጋራ መኖሪያ ቤቶች በሚመለከት፣ ‹‹ለሕዝብ ይፋ በምናደርግበት ሚዲያ እናሳውቃለን፤›› ብለዋል፡፡ እስካሁንም አስተዳደሩ የቤቶችን ግንባታ በሚመለከት ለሕዝቡ በተለያዩ ማስታወቂያዎች ሲያስረዳና ሲያስተዋውቅ እንደነበርም አስታውሰዋል፡፡ ከዓመት በፊት ዕጣ የወጣላቸው የ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕድለኞች ከነገ ዛሬ ቤቱን ተረከቡ እንባላለን ብለው ቢጠባበቁም፣ ምንም ዓይነት ጥሪም ሆነ ሌላ መግለጫ ባለማግኘታቸው አቤቱታ ተፈራርመው ለቤቶች ልማት ቢሮ ስለማስገባታቸው የተጠየቁት ቢሮ ኃላፊዋ፣ ‹‹እኔ ቢሮ የደረሰ አቤቱታ የለም፡፡ ምናልባት ለቤቶች ኮርፖሬሽን ደርሶ ከሆነ እጠይቃለሁ፤›› በማለት ስለአቤቱታው የሚያውቁት እንደሌለ ተናግረዋል፡፡
0
10466187c31fdc0e05e9d8234d1b5e3e
dee7d7d799c8ba8a1b2024c05cda5e69
በአዲስ አበባ ባለፉት ሁለት ቀናት ሁለት ፖሊሶችን ጨምሮ የ10 ሰዎች ህይወት አለፈ
አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 19 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በምሥራቅ ጎጃም ዞን ከሞጣ ወደ አዲስ አበባ ይጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ከከባድ ገልባጭ መኪና ጋር ተጋጭቶ የ10 ሰዎች ሕይወት አልፏል። አደጋው ከንጋቱ 11 ሰዓት ከ30 ከሞጣ ወደ አዲስ አበባ ይጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ለመንገድ ሥራ ጌጠኛ ድንጋይ ጭኖ ወደ ተቃራኒ አቅጣጫ ይጓዝ ከነበረ ከባድ ገልባጭ መኪና ጋር ተጋጭቶ የደረሰ ነው።በአደጋው የአውቶብሱን ሾፌር ጨምሮ የ10 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ተመስገን ይበልጤ ተናግረዋል።የገልባጭ መኪናው ሾፌርና ረዳት አለመገኘታቸውንም ዋና አስተዳዳሪው ገልጸዋል።ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በሞጣ እና ግንደወይን ከተማ ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል።በአደጋው ሳቢያ አምስቱ ቀላል ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን፥ የከፋ ጉዳት የደረሰበት አንድ መንገደኛ ባሕር ዳር ጥበበ ግዮን ሆስፒታል ለተሻለ ሕክምና መላኩም ታውቋል።በሰላም አሰፋየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
0
6b5c3aa5aca76cbcac1c74e36886ee53
64588a54b4be93837ab4e53a43059d44
ከውጪ ለገቡ ሰዎች የሚደረገው ጥበቃ የፌደራል ፖሊስን ማቋቋሚያ አዋጅ የሚጣረስ እንደሆነ ተገለጸ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 9፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) አቶ ጃዋር መሃመድ እና በቀለ ገርባን ጨምሮ በ24 ሰዎች ላይ ክስ ተከፍቷል፡፡ጠቅላይ አቃቤ ህግ ጃዋር ሲራጅ መሀመድ፣ በቀለ ገርባ፣ ሀምዛ አድናን፣ እንዲሁም በሌሉበት የተከሰሱትን የኦሮሚያ ሜዲያ ኔትወርክ (OMN)፤ ደጀኔ ጉተማ፣ ዶ/ር ብርሃነመስቀል አበበ እና ፀጋዬ ረጋሳን ጨምሮ በአጠቃላይ በ24 ሰዎች ላይ እንደየተሳትፏቸው በ1996 የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀፅ 240 በመተላለፍ ብሔርን እና ሐይማኖትን መሰረት ያደረገ የእርስ በርስ ግጭት በመቀስቀስ አንዱ ወገን በሌላው ወገን ላይ እንዲነሳሳ በማድረግ ፣ የሽብር ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1176/2012፣ የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀል አዋጅ ቁጥር 761/2004 እና የጦር መሳሪያ አስተዳደርና ቁጥጥር አዋጅ ቁጥር 1177/2012 በመተላለፍ በፈፀሙት ወንጀል የፌደራል ጠቅላይ ዐ/ሕግ መስከረም 6 ቀን 2013 ዓ.ም በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት በመዝገብ ቁጥር 260215 አስር ተደራራቢ ክሶች አስከፍቷል፡፡ተከሳሾቹም መስከረም 11 ቀን 2013 ዓ.ም ፍ/ቤት ቀርበው ክሱ ይደርሳቸዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ የኢፌዲሪ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
0
e1e9e13a88006c4c301bbaa54940bc1c
6afbc607aa720f4f4368c7a8eb9beddb
የዲሞክራሲያዊት ኮንጎ ሪፐብሊክ ተቃዋሚዎች ሰልፍ ለማካሄድ ቆርጠዋል
የዲሞክራሲያዊት ኮንጎ ሪፖብሊክ ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ካቢላ እንደገና ለመመረጥ ላለመወዳደር መወሰናቸውን ዩናይትድ ስቴትስ በደስታ ተቀብላለች፡፡ገዢው ፓርቲ አለች ዩናይትድ ስቴትስ የኮንጎ ገዢ ፓርቲ ካቢላን ሳይሆን ሌላ ሰው በዕጩነት ለማቅረብ መወሰኑ የሃገሪቱን ዲሞክራሲ ወደፊት የሚያራምድ ትልቅ ውሳኔ ነው።የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ሂዘር ኖወርት ባወጡት መግለጫ ሚስተር ካቢላ የኮንጎን ህገ መንግሥት እና እኤአ በ2016 የተደረሰውን ሥምምነት ለማክበር ዝግጁ መሆናቸውን የሚያሳይ ርምጃ በመሆኑ አበረታች ሆኖ አግኝተነዋል ብለዋል፡፡አክለውም የኮንጎ ሕዝብ ጥቃት ይደርስብናል ብሎ ሳይሸማቀቅ ሃሳቡን በነፃነት መግለጽ አለበት ብለዋል። የኮንጎ የምርጫ ኮሚሽን እና ባለሥልጣናቱ በመጪው ታኅሳስ ሃያ ሦስት የሚካሄደው ምርጫ ተዓማኒ እንዲሆን አስፈላጊውን ዕርምጃ ሁሉ እንዲወስዱ እናሳስባለን ብለዋል።ጆሴፍ ካቢላ የቀድሞ የሀገር ግዛት ሚኒስትር ኢማኑኤል ራማዛኒ ሻዳሪ እንዲወዳደሩ ድጋፍ እሰጣለሁ ሲሉ አስታውቀዋል።ሰማኒያ ሚሊዮን ህዝብ ያላት ያቺ ሃገር ከእውሮፓውያን ቅኝ ገዢዎች ነጻ ከወጣችበት እኤአ ከ1960 ሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር ኖሯት አታውቅም።
0
989c99a4710ce105716e16f7084e47e1
377c70c719117558d987fa6e6c8cb4ad
በአማራ ክልል 27 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተይዘዋል፤ ከእነዚህ መካከል 7 ሰዎች አገግመዋል፡፡
አዲስ አበባ፣ታህሳስ 27፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ ለ3 ሺህ 934 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ 322 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ።ዶክተር ሊያ በፌስቡክ ገጻቸው እንደገለጹት 203 ሰዎች ደግሞ ከቫይረሱ አገግመዋል፡፡እንዲሁም ባለፉት 24 ሰዓታት በቫይረሱ ምክንያት 13 ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡እስካሁን ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች 112 ሺህ 813 ሲደርስ 1 ሺህ 963 ሰዎች ደግሞ ለህልፈት ተዳርገዋል፡፡በአሁኑ ጊዜ ቫይረሱ ያለባቸው 11 ሺህ 463 ሲሆኑ ከእነዚህ ውስጥ 245 ሰዎች ደግሞ በጽኑ የታመሙ መሆናቸውን ነው የገለጹት፡፡ወረርሽኙ ኢትዮጵያ ከገባ ጀምሮ ለ1 ሚሊየን 826 ሺህ 56 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጓል፡፡ከእነዚህም መካከልም 126 ሺህ 241 በወረርሽኙ የተያዙ ሲሆን አሁን ላይ 11 ሺህ 463 ሰዎች ቫይረሱ እንዳለባቸው ተገልጿል፡፡ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
0
49cde769ea0182fafeb4f48a760a5dbf
49cde769ea0182fafeb4f48a760a5dbf
ወልድያ ዩኒቨርሲቲ ለአካል ጉዳተኞች የመጓጓዣ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።
ባሕር ዳር፡ መስከረም 24/2013ዓ.ም (አብመድ) የወልድያ ዩኒቨርሲቲ በሰሜን ወሎ ዞን ለሚገኙ የእንቅስቃሴ ችግር ያለባቸው አካል ጉዳተኞች አጋዥ የቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል፡፡ ድጋፉ በዞኑ ለሚገኙ ሆስፒታሎች እና በእግር ለመንቀሳቀስ ለሚቸገሩ የአካል ጉዳተኞች የሚያግዝ ነው፡፡የዩንቨርሲቲው መምህር ፋሲል ንጉሴ (ዶክተር) ተነሳሽነትና ፕሮጀክት አዘጋጅነት አሜሪካን ከሚገኝ የክርስቲያን በጎ አድራጎት ድርጅት የተገኘው የመጓጓዣና የአካል ድጋፍ ቁሳቁስ 240 መሄጃ ወንበር (ዊልቼር)፣ 25 ምርኩዞች (ክራንች) እና 100 የእርምጃ ድጋፎች(ወከር) ሲሆኑ ግምታቸው 1 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር እንደሆነ ተናግረዋል፡፡‘‘እንደ አንድ መምህር የማኅበረሰብ አገልግሎት ሥራን መሥራት ስለሚጠበቅብኝ የአካል ጉዳተኞችን ችግር መፍታት አንድ የማኅበረሰብ ችግር መፍታት ስለሆነ በዚያ መነሻ ይህ ሐሳብ መጣልኝ” ያሉት ዶክተር ፋሲል ንጉሴ አካል ጉዳተኞችን ከመርዳት በላይ ለኅሊናን የሚያስደስት ነገር አለመኖሩን ገልጸዋል፤ ዩኒቨርሲቲዎችና መምህራን ከመማር ማስተማሩ ጎን ለጎን የማኅበረሰቡን ችግር አጥንቶ የመፍታት ኃላፊነትም ግዴታም እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡የወልድያ ዩኒቨርሲቲ የጥናትና ምርምር እና ማኅበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ሰሎሞን አበጋዝ (ዶክተር) ዩኒቨርሲቲው አስፈላጊውን የውጪ ግንኙነት በማድረግና ንብረቶቹ ከወደብ ጀምረው የሚጓጓዙበትን ወጪ በመሸፈን እገዛ ማድረጉንም ጠቁመዋል፡ ከዚህ በፊትም በተለያዩ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች የማኅበረሰብ አገልግሎት ሲሰጥ እንደቆየና ይህንኑ አገልግሎቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል፡፡የመንቀሳቀሻ ተሽከርካሪ (ዊልቼር) ድጋፍ ከተደረገላቸው ውስጥ ወይዘሮ ፀሐይነሽ ደምሴ አስተያዬታቸውን ለአብመድ ሰጥተዋል፡፡ ወይዘሮ ፀሐይነሽ በምርኩዝ (ክራንች) ይጓዙ በነበረበት ጊዜ ይወድቁ፣ ይደክማቸውና በጡታቸው አካባቢ የሕመም ስሜት ይፈጥርባቸው እንደነበር ጠቅሰው የተሰጣቸው ዊልቼር ምቾት ስላለው እንደልብ እንደሚያንቀሳቅሳቸው ገልጸዋል ለተደረገላቸው ድጋፍም አመሥግነዋል፡፡ዘጋቢ፡- ዋሴ ባየ – ከወልድያ
1
9ff53af9922a4491f91488633d7f8876
6f9d94476f32f55c6963b75b6797e9f2
ለሠራተኞች በሚከፈል ደመወዝና ጥቅማ ጥቅም ማነስ ምክንያት የኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ልማት ፓርክ ሊዘጋ እንደሚችል ተገለጸ፡፡
የመቐለና ኮምቦልቻ ኢንዱስትሪፓርኮች ሙሉ በሙሉ በባለሃብቶች መያዛቸውን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታወቀ ። የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሲሳይ ገመቹ ከዋልታ ቴሌቭዥን ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት የመቐለና የኮምቦልቻ ኢንደስትሪ ፓርኮች የመሥሪያና የማምረቻ ቦታዎች ሙሉ በሙሉ በባለሃብቶች የተያዙ መሆናቸውን ገልጸዋል ።በሁለቱም የኢንዱስትሪ ፓርኮች ባለሃብቶቹ ተጨማሪ የመሥሪያ ቦታ እየጠየቁ እና እየተመቻቸላቸው እንደሆነ ሥራ አስፈጻሚው ጠቁመዋል ፡፡መንግሥት ሼዶችን ከመገንባት ውጪ የለማ መሬት በማዘጋጀት በመቐለና ኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ለባለሃብቶች እያቀረበ መሆኑንና ባለሃብቶችም በተሠጣቸው የለማ መሬት የራሳቸውን የማምረቻ ቦታ ግንባታ እንዲከናውኑ ምቹ ሁኔታዎች እየተፈጠሩላቸው መሆኑን አያይዘው ገልጸዋል ። በተጨማሪም ግንባታቸው በመጠናቀቅ ላይ የሚገኙት የድሬዳዋ ፣የአዳማ ፣የጅማ ፣የቦሌ ለሚ ሁለትና የቂሊንጦ ኢንደስትሪ ፓርኮች በቀጣይ ሶስት ወራት ተጠናቀው ወደ ስራ እንዲገቡ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ እንደሆነም ሥራ አስፈጻሚው ገልፀዋል፡፡
0
7201d88c1422187354715bf18a5f50b5
3ed90d01ebc605c7384e7df17a68da8e
የሮሒንግያ ሙስሊሞች የጥቃት ዘመቻ ሸሽተው ከተሰደዱ አንድ ዓመት ሆናቸው
“አማራዊ ማንነታችን የጥቃት ምንጭ መሆኑ ሊቆም ይገባል” ሲሉ የንግድ ሚኒስትሩ አሳሰቡ፡፡ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 23 /2013 ዓ.ም (አብመድ) የንግድ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል በወለጋ የደረሰውን ጥቃት አስመልክቶ በቲውተር ገፃቸው መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው “ ከወንድም ህዝቦች ጋር በአንድነት ስጋና ደም ገብረን ባቆምናት ኢትዮጵያ አማራዊ ማንነታችን የጥቃት ምንጭ መሆኑ ሊቆም ይገባል፤ መከራ ያጠነክረናል እንጂ አያጠፋንም፤ ኢትዮጵያም ትቀጥላለች” ብለዋል፡፡ሚኒስትሩ እንዳሉት “ሁሉም ትውልድ የራሱ የቤት ስራ አለበት፤ በመስዋዕትነታችን ከሌሎች ወንድም ህዝቦች ጋር በነጻነት፣ በእኩልነት እና በፍትሃዊ ተጠቃሚነት የምንስተናግድባት ኢትዮጵያን እናፀናለን ” ነው ያሉት፡፡
0
476d36c2f15175890200e6b050fdc988
8c2ca6a9082db0dce97383c0d7701dc8
ተመድ እየሩሳሌምን በእሥራኤል ዋና ከተማነት ዕውቅና ረቂቅ ውሣኔ ላይ ድምፅ ይሰጣል
ተሻሽሎ የቀረበውን የኢትዮጰያ የምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ስነ ምግባር ረቂቅ አዋጅን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሙሉ ድምፅ አፀደቀው፡፡ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ በረቂቅ አዋጁ ላይ ሰፊ ክርክር ካደረገ በኋላ ነው በሙሉ ድምፅ ያፀደቀው፡፡ይሁን እንጂ ወንድ እና ሴት ተወዳዳሪዎች እኩል ድምጽ ቢያገኙ ሴት ተወዳዳሪዋ እንደምታሸንፍ በረቂቅ አዋጁ ላይ ቢቀመጥም ም/ቤቱ በአብላጫ ድምጽ ውድቅ አድርጎታል።ምክንያቱ ደግሞ የፆታ እኩልነትን መርህ የሚፃረር የሚል ነው፡፡ዛሬ በፀደቀው ረቂቅ አዋጅ የመንግስት ሰራተኛ የፖለቲካ ፓርቲ አባል ሆኖ በምርጫ ቅስቀሳና በውድድር ቢሳተፍ ያለ ደመወዝ ፈቃድ ማግኘት እንደሚችል ይደነግጋል፡፡የፖለቲካ ፓርቲዎች አባሎቻቸውን በተለያዩ ምክንያቶች ከአባልነት ለመሰረዝ ቢፈልጉም ያለ ፍርድ ቤት ፈቃድ ማሰናበት እንዲችሉም ፈቃድ የሚሰጥ ተብሏል፡፡በፀደቀው ረቂቅ አዋጅ መሰረት ለግል ለተወዳዳሪዎች መንግስት ድጋፍ እንደሚሰጥም ተደንግጓል፡፡ምንጭ ፡ ኢቢሲ
0
ff8d0f88e7e9504dd3daa141a7ed8b9c
d80fe55af59750cb52367578db89fad6
በመዲናዋ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ክልከላዎችን በተላለፉ 268 አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በመደበኛ ስብሰባው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም መርማሪ ቦርድ አባላትን በአብላጫ ድምፅ አፀደቀ።ምክር ቤቱ በመደበኛ ስብሰባው የሚኒስትሮች ምክር በትግራይ ክልል ያወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማጽደቁን ተከትሎ ነው የመርማሪ ቦርድ አባላትን የሰየመው።መርማሪ ቦርዱ 7 አባላት ያሉት ሲሆን፥ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ከህግ ባለሙያዎች የተውጣጡ መሆናቸውም ታውቋል።በዚህም መሰረት፦የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም መርማሪ ቦርድ አባላቱን በ6 ተቃውሞ እና በአብላጫ ድምጽ አጽድቆታል።የመርማሪ ቦርዱ ስልጣን እና ተግባርም፦ በሀይለኢየሱስ ስዩም
0
3726fbeff94957f667a4c2f5db931a12
ec11fd807830e49968fa210d478aaf9c
ባለፉት 24 ሰዓታት 730 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው 7 ሰዎች ህይወት አልፏል
አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 20 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰአታት ለ18 ሺህ 724 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 1 ሺህ 533 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ፡፡ ከዚህ ባለፈም ባለፉት 24 ሰአታት የ16 ሰዎች ህይወት ማለፉን የገለፁት ሚኒስትሯ በቫይረሱ ሳቢያ ለህልፈት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር 725 ደርሷል፡፡ በተጨማሪም ባለፉት 24 ሰአታት 515 ሰዎች ሲያገግሙ ይህን ተከትሎም ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 16 ሺህ 311 ደርሷል፡፡ አሁን ላይ 327 ሰዎች ደግሞ በፅኑ ህክምና ክፍል ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛሉም ነው የተባለው፡፡ በኢትዮጵያ እስካሁን ለ813 ሺህ 410 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 45 ሺህ 221 ሰዎች ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል፡፡ ከዚህ ውስጥ 16 ሺህ 311ዱ ሲያገግሙ 28 ሺህ 181 ሰዎች ደግሞ የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል፡፡
0
65d11b4f2fcb9ba536351cbc4da5caf5
2ea111c580c4797b545312be50235a95
በሶማሌ ክልል የተፈጠረውን ሰላም በመጠቀም በንግድና ኢንዱስትሪ ዘርፍ ውጤታማ ሥራዎችን መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
የባህል ዘርፉን በመጠቀም ለሀገር ሰላም እና ልማት ሊሰራ እንደሚገባ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር አሳሰበ፡፡ሶስተኛው ዓመታዊ የጥናትና ምርምር ጉባዔ "ባህላዊ እሴቶቻችን ለሃገራዊ አንድነታችን እና ለዘላቂ ቱሪዝም ልማት" በሚል መሪ ቃል በመቐለ ተካሂዷል።በጉባኤው ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው በሶስቱ ዘርፎች ላይ ለተሳታፊዎቹ ገለፃ ያደረጉ ሲሆን፤ በገለጻቸውም ባህልን ማወቅ የህይወት እሳቤ መነሻ ነው፣ ግለሰብም ሆነ ማህበረሰብ ያለ ባህል ህልውናቸው ይወድቃል ብለዋል።ከውጭ የሚገቡ የጎብኚዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን የገለፁት ሚኒስትሯ፤ ዓመታዊ የጎብኚ ቁጥር በምን ያህል መጠን እንደጨመረ ግን ያሉት ነገር የለም።ዶክተር ሂሩት አክለውም ኢትዮጵያ ያላትን ሃብት ያክል አለመጠቀሟን እና በቀጣይ በስፋት እና በትጋት ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል።የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በርካታ ቅርሶች ቢኖራትም ከዘርፉ የሚገባትን ያህል አልተጠቀመችም ብለዋል።በጉባኤው ባህል፣ ቱሪዝም እና ስፖርትን በተመለከተ ጥናቶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
0
53f5d76d6781c9ec34e26efd6c943b1c
fb5a8152d4cee5c81033b451f79dc4e2
በኮንጎ የ’ሕገወጥ’ የማዕድን ፈላጊዎች ላይ ጉድጓድ ተደርምሶ በርካቶች ሞቱ
በኮንጎ ሪፑብሊክ መዲና ብራዛቪል ትላንት በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ሶስት ፖሊሶችና ሁለት ታጣቂዎች እንደተገደሉ ተዘግቧል።ውጊያው የተከፈተው የሀገሪቱ ፕረዚዳንት ዴኒስ ሳስዋ ንጉዌሶ በአጨቃጫቂ ምርጫ ለሶስተኛ ጊዜ ካሸነፉ ባኋላ ነው።ፖሊሶች እንደሚሉት “ኒንጃዎች” የተባለው ጸረ ንጉሶ ሚልሻ የቀድሞ አባላት በአከባቢው የፖሊስ ጣብያ፣ በወታደራዊና በመንግስት መስሪያ ቤቶች ላይ ወረራ አካሄደው በእሳት አጋይተዋቸዋል።
0
43c364baa7dd8fa11c46221be2922cc0
866d10b39ae2a24c0e77eae44d5bfa4d
ውይይት በወቅታዊ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ቁመና
አዲስ አበባ፣ የካቲት 12፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሰላም ሚኒስቴር ከፓስቶራሊስት ፎረም ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር የአርብቶ አደሩን አካባቢና የልዩ ድጋፍ ክልሎችን ልማት በሚመለከት የፓናል ውይይት አካሄደ።የዘርፉ ምሁራን የተሳተፉበት ይህ ውይይት “አርብቶ አደርነት፣ የለውጥ ሂደትና የወደፊት አቅጣጫ በኢትዮጵያ” በሚል ርዕስ የአርብቶ አደሩን የኑሮ ዘይቤ መለወጥ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው ተብሏል።በመድረኩ አርብቶ አደሩ በሃገሪቱ ኢኮኖሚ ያለው ድርሻ ከፍተኛ መሆኑ ተመላክቷል።በአርብቶ አደር አካባቢዎች የሚሰሩ የልማት ስራዎች የማህበረሰቡን ችግር በሚፈታና እምቅ የተፈጥሮ ሃብቶችን መሠረት ባደረገ መልኩ መሰራት እንዳለባቸው ተነስቷል።አርብቶ አደሩ ወደ ዘመናዊ የእንስሳት ሃብት ልማት ገብቶ ተጠቃሚ እንዲሆንም ተገቢ የአቅም ግንባታ ሥራዎችን መሥራት ያስፈልጋልም ነው የተባለው።አርብቶ አደሩ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት የሚያበረክተው አስተዋፅኦ ከፍ እንዲል በጥናት የተደገፈ እገዛ ማድረግ የሃገሪቱ የኢኮኖሚ ዕቅድ አካል መደረግ አለበት መባሉን ከሰላም ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል ።
0
55f7af16ca3f5b85b2cbad2bf546935d
03759ff6ccb95b322590c47b1ccd20a3
የኢዴፓ አመራሮች ፓርቲውን ለማክሰም ፈተና ገጥሟቸዋል
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ሦስተኛ ፍትሐ ብሔር ችሎት፣ ላለፉት ዘጠኝ ወራት የቤት ኪራይ መክፈል ያልቻለው አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ማተሚያ ማሽኑን እንዳይሸጥ፣ እንዳይለውጥና ለሦስተኛ ወገን እንዳያሳልፍ እንዲሁም አሁን ከሚገኝበት ቦታ እንዳይወጣ አገደ፡፡ፍርድ ቤቱ ይህን የዕግድ ትዕዛዝ ያስተላለፈው በቤቱ አከራይ አቶ ዘካሪያስ ብርሃኑ አማካይነት በቀረበ ክስ ነው፡፡ ፍርድ ቤቱ ታኅሳስ 4 ቀን 2008 ዓ.ም. በአራዳ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 16 የቤት ቁጥር አዲስ በካርታ ቁጥር አ/13/14/0564 ተመዝግቦ የሚገኘውን ቤት ፓርቲው ለአቶ ዘካሪያስ እንዲያስረክብ ወስኗል፡፡በዚህም መሠረት አቶ ዘካርያስ ብርሃኑ 33,494 ብር የወጪ ኪሳራ ጠይቀዋል፡፡ የፓርቲው ማተሚያ ማሽን እስከ 33,494 ብር የሚያወጣ መሆን አለመሆኑን በባለሙያ ግምት ከተረጋገጠ በኋላ እንዳይሸጥ እንዳይለወጥ፣ ለሦስተኛ ወገንም እንዳይተላለፍና ከከሳሽ ቤት እንዳይወጣ ታግዶ እንዲቆይ መታዘዙን የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ያስረዳል፡፡ከሳሽ አቶ ዘካርያስ ብርሃኑ ለበርካታ ወራት ሲንከባለል በቆየው ውዝግብ የተነሳ ማግኘት የሚገባቸውን ጥቅም እንዳጡ ለሪፖርተር የገለጹ ሲሆን፣ ‹‹ለፍትሕና ለዴሞክራሲ እታገላለሁ የሚል ፓርቲ እንዲህ የአንድን ግለሰብ መኖሪያ ቤት ይዞ አልለቅም ማለቱ እጅግ ግራ የሚያጋባና ቆሜለታለሁ ከሚለው መርህ ጋር የሚጋጭ ነው፤›› በማለት አስረድተዋል፡፡የአከራይና የተከራይ ወገኖች ውዝግብ የተጀመረው በምርጫ ቦርድ ዕውቅና የተነፈገው የፓርቲው የቀድሞ አመራር ፓርቲውን ለቅቆ ከወጣ በኋላ፣ በምርጫ ቦርድ ዕውቅና የተሰጠው የእነ አቶ ትዕግሥቱ አወሉ አመራር ፓርቲውን ከተረከበ ጀምሮ ነው፡፡የቤቱ አከራይ የሆኑት አቶ ዘካርያስ የቤት ኪራይ ዋጋ እንደሚጨምሩ በመግለጽ ለፓርቲው አመራሮች ማሳወቃቸውን፣ ፓርቲው ግን በጭማሪው ያልተስማማ መሆኑን መግለጹና ክፍያ እንደማይፈጽም ማስታወቁን መዘገባችን የሚታወስ ነው፡፡ የፓርቲውን በአሁኑ ወቅት አንድነት ፓርቲን የሚመሩትን አቶ ትዕግሥቱ አወሉን ለማግኘት የተደረገው ተደጋጋሚ ሙከራ አልተሳካም፡፡
0
04ca4810aa70626a033b2a8f4ac79adc
04ca4810aa70626a033b2a8f4ac79adc
በልደታ ክፍለ ከተማ ከ35 ሺህ ብር በላይ ነባሩ ባለሃምሳ ሐሰተኛ የብር ኖት ከነተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡
ባሕር ዳር፡ መስከረም 21/2013ዓ.ም (አብመድ) በአዲስ አበባ ልደታ ክፍለ ከተማ ከ35 ሺህ ብር በላይ ነባሩ ባለሃምሳ ሐሰተኛ የብር ኖት ከነተጠርጣሪው ተይዞ ምርመራ እየተጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ገለፀ፡፡ የአዲስ አበባ እና የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አባላት ከጥርጣሬ በመነሳት በአንድ ግለሰብ ላይ ባደረጉት ድንገተኛ ፍተሻ በእጅ ቦርሳው ውስጥ 35 ሺህ 50 የቀድሞውን ባለሃምሳ ሐሰተኛ የብር ኖት ከአንድ የንግድ ባንክ ቅርንጫፍ ቲተር ጋር ከእነተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር አውለዋል ብሏል ኮሚሽኑ፡፡የልደታ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የልዩ ልዩ ወንጀሎች መርማሪ ምክትል ሳጅን ንጉሴ ማናዬ ኅብረተሰቡ ግብይት በሚፈጽምበት ወቅት በሐሰተኛ የብር ኖቶች የማታለል ወንጀል እንዳይፈጸምበት መለያዎቹን በጥንቃቄ በመመልከት እንዲገበያይ እና አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙ ለፖሊስ ጥቆማ እንዲሰጥ ማሳሰባቸውን ኢብኮ ዘግቧል፡፡
1
5eb1e1bfdbcd7ecb7efa86e854f3e452
5eb1e1bfdbcd7ecb7efa86e854f3e452
ኢትዮጵያ 10ኛውን የዓለም አቀፍ ቀን የዴሞክራሲ ቀን አከበረች
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የዴሞክራሲና የግጭት መከላከል ቀንን ለ10ኛ ጊዜ አከበረች ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባዘጋጀው የዓለም የዴሞክራሲና ግጭት መከላከል ቀን በዓል በአገሪቱ የሚገኙ የሲቪክ ማህበራት እንዲሁም የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንን ጨምሮ የተለያዩ የዴሞክራሲ ተቋማት ተገኝተዋል ። በበዓሉ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የመንግሥት ተጠሪ ሚንስትር ዲኤታ አቶ መለስ ጥላሁን በሥነ ሥርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት ዴሞክራሲ ለአገሪቱ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት ዴሞክራሲ እጅግ ወሳኝ በመሆኑ ምክንያት መንግሥት ልዩ ትኩረት እንደሚሠጠው ተናግረዋል ። በአገሪቱ የዴሞክራሲያዊ ተቋማት መጎልበት ለዴሞክራሲ መጠናከር አስፈላጊ መሆኑን የጠቆሙት ሚንሰትር ዲኤታው የሴቶችን ንቃተ ህልና ማሳደግ ፣ የህግ የበላይነትን ማረጋገጥና እኩል የሆነ የኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ማስፈን ለዴሞክራሲ ዕድገት ጉልህ ሚና ይጫወታል ብለዋል ። ዴሞክራሲ በአንድ አገር ውስጥ በሚኖሩ የተለያዩ ብሔሮች ፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መካከል እኩልነትና መቻቻል እንዲኖር የሚያደርገው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን ሚንስትር ዲኤታው ተናግረዋል ። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ኡባህ ሞሃመድ በበኩላቸው ግጭት ተፈጥሯዊና በየትኛውም የዓለም ክፍል የሚነሳ ሁኔታ እንደሆነ ገልጸው የሚያጋጥሙ ግጭቶችን በተገቢው ሁኔታ ለመፍታት የግጭት መከላከል ስትራቴጂን መንደፍ እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል ። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶክተር አዲሱ ገብረእግዛብሔር በአገሪቱ ለሚደርሱ ግጭቶች ቅድመ ማስጠንቀቂያ ትንተና የሚሠራ ተቋም አለመኖሩ እጅግ አሳዛኝ መሆኑን ተናግረዋል ።የአገሪቱ ህገ መንግሥት ህዝቦች በሚያደርጉት ተሳትፎ ዴሞክራሲን፣ ሰላምንና ልማትን በማረጋጋጥ አንድ የፖለቲካ ማህበረሰብን መፍጠር እንደሚገባቸው መደንገጉን ዶክተር አዲሱ አመልክተዋል ።የዓለም አቀፉ የዴሞክራሲና የግጭት መከላከል ቀን በዓል በዓለም ደረጃ ለ11ኛ ጊዜ እየተከበረ ነው ።
1
4bbd800e718f9adfed916cb21c1657f3
4bbd800e718f9adfed916cb21c1657f3
የብአዴን ጉባዔ
የብአዴን ጉባዔ ሁለተኛ ቀኑን ይዟል፡፡ ጉባዔው በዛሬው ውሎው በክልሉ ልማት በዴሞክራሲና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ባሉ ችግሮች ላይ መወያየቱ ተገልጿል፡፡ ድርጅቱ ከማዕከላዊ ጉባዔ ገዳቸው አቶ በረከት ስምኦንና አቶ ታደሰ ካሣ እንዲሁም የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል እንዲሁም ነባር አመራር ሆነው ያልተገኙ እንዳሉ ታውቋል፡፡
1
4208eccbc9f1b0d18c583a798447f5a2
06eafb68bf2e2832340d0ccf7ede2a47
የሚገነቡ ህንፃዎች የጥራት ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ ሚኒስቴሩ የተጠናከረ ቁጥጥር ሊያደርግ ይገባል-ምክር ቤቱ
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ባለፉት 6 ወራት 210 ፋብሪካዎች ላይ ቁጥጥር ለማድረግ አቅዶ በ185 ድርጅቶች ላይ ቁጥጥርና ክትትል ማድረጉን ገልጿል፡፡ቁጥጥር ከተደረገባቸው 185 ፋብሪካዎች ከ47 ፋብሪካዎች ወካይ ናሙናዎችን በመውሰድ የፊዚካል እና የላብራቶሪ ምርመራ አድርጓል።በተካሄደው የላብራቶሪ ምርመራ ውጤት መሰረትም የ9 ፋብሪካዎች ምርት ከደረጃ በታች በመሆኑ ከማስጠንቀቂያ እስከ ማሸግ የሚደርስ እርምጃ ተወስዶባቸዋል፡፡እርምጃ የተወሰደባቸው የሳሙና፣ የሲሚንቶ፣የውሃ እና የወይን ፋብሪካዎች ሲሆኑ÷ የ14 ፋብሪካዎች ናሙና የላብራቶሪ ውጤት እስከሚደርስ እየተጠበቀ መሆኑም ተገልጿል፡፡162ቱ ፋብሪካዎች ደግሞ የኢትዮጵያን የጥራት ደረጃ መስፈርት ያሟሉ ሆነው መገኘታቸውን ከንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡በተጨማሪም ከ90 ሺህ በላይ የንግድ ተቋማት ላይ አስተዳደራዊና ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን ሚኒስቴሩ አስታውቋል ገለጸ፡፡የዋጋ ንረትና የኑሮ ውድነት ለመከላከል በንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የሚመራ ግብረ-ሀይል ከፌዴራል እስከ ወረዳ ድረስ ተዋቅሮ ሰፊ ስራ መሰራቴ ተጠቁሟል።በዚህም በህገ-ወጥ መንገድ ግብይቱን ሲሳተፉ የነበሩ 91 ሺህ 602 ህገ-ወጥ ደላላዎችና ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል ነው የተባለው።ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይ ያድርጉ!
0
253aafb218612e7320e72fa5f74e9e7c
78bba6fdbc06c8a0caf360420c31e0bc
የግድቡ አጠቃላይ ግንባታ 76.35 በመቶ መድረሱ ከቀናት በፊት ተገልጿል
አዲስ አበባ፤ የህዳሴው ግድብ የሲቪል ኢንጂነሪንግ፣ የዋናው ግደብ እንዲሁም የኤሌክትሮ መካኒካል ግንባታ በጥሩ ሂደት ላይ እንደሚገኝና በቅርቡ እንደሚጠናቀቅ ተገለጸ። የህዳሴው ግድብ ፕሮጀክት ማናጀር ኢንጅነር ክፍሌ ሄሮ ለኢትዮጵያ ሄራልድ ጋዜጣ እንደተናገሩት በአሁኑ ወቅት የዋናው የሳድል የኮርቻ ግድብና ማስተንፈሻው እንዲሁም የሀይል ማስተላለፊያው ግንባታ በአማካይ 84 ነጥብ አምስት በመቶ ተጠናቋል። የዋናው ግድብ ግንባታ 80 ነጥብ ሁለትበመቶ፤ የሳድል (ኮርቻ) ግድቡ ግንባታ ደግሞ 96 በመቶ መድረሱንም ጠቁመዋል። በአሁኑ ወቅት በሁለቱም በኩል እየተካሄደ ያለው የግንባታ ፍጥነት ሀገሪቱ ያለችበትን የእድገት ጉዞ የሚያመላክትም ነው ብለዋል። ኢንጅነር ክፍሌ ጨምረው እንደተናገሩት ከሲቪል ምህንድስናው የማስተንፈሻ ቦይ ግንባታው 96 በመቶ የደረሰ ሲሆን የሀይል ማመንጫ ጣቢያውና መቆጣጠሪያውን የሚያካትተው የኤሌክትሮ መካኒካል ግንባታው 69 በመቶ እንዲሁም ሌሎቹ ስራዎች 57 በመቶ መጠናቀቃቸውንም ገልጸዋል። አጠቃላይ የግድቡ ግንባታ የሲቪል ምህንድስናውን፤ ኤሌክትሮ መካኒካል፤ የሀይል ማመንጫ ሞተር ግንባታውንና የብረታብረት ስራውን ጨምሮ በዓማካይ 68 ነጥብ አምስት በመቶ ደርሷል። ሁሉም ኮንትራክተሮች በቅንጅት የሚሰሩ ከሆነ እ አ አ በ2022 ፕሮጀክቱ የሚጠናቀቅ ይሆናል ሲሉም የፕሮጀክት ማናጀሩ አስረድተዋል። ከዚህ ቀደም ግንባታው በአንድና በሁለት ኮንትራክተሮች ይከናወን እንደነበር ያስታወሱት ኢንጅነሩ በአሁኑ ወቅት እየሰሩ ያሉት ግን በርካታ ኮንትራክተሮች በመሆናቸውና ስራው በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው የኮንትራክተሮቹ በህብረት መስራት የግድቡን ግንባታ በተቀመጠለት የግዜ ገደብ ለማጠናቀቅ እንደሚያግዝ አስገንዝበዋል።አዲስ ዘመን መስከረም 12 ቀን 2012 ዓ ምራስወርቅ ሙሉጌታ
0
d1040e98536be6c3ed4db8a6ae960a1c
83a691f6bef338204ca65f5e011cfdbb
ፕሮፌሰር መረራ ስለፓርቲዎቹ ስምምነት
ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለማስወገድ በዋና ወንጀል ላይ ተካፋይ በመሆን፣ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር የተያያዙ ግዴታዎችን በመተላለፍና የሐሰት ወሬዎችን በማውራት ወንጀሎች ክስ የተመሠረተባቸው ዶ/ር መረራ ጉዲና፣ ባቀረቡት የክስ መቃወሚያ መሠረት ክሱ እንዲሻሻል ፍርድ ቤት ዓርብ ግንቦት 25 ቀን 2009 ዓ.ም. ብይን ሰጠ፡፡ዶ/ር መረራ የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ያቀረበውን ክስ በመቃወም ያቀረቡትን አቤቱታና ዓቃቤ ሕግ የሰጠውን ምላሽ የሚመረምረው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት፣ ከተከሳሽ ጋር ክስ የቀረበባቸውን የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን (ኢሳት) እና የኦሮሞ ሚዲያ ኔትወርክ (ኦኤምኤን) ክሶችን ዓቃቤ ሕግ እንዲያሻሽል ብይን ሰጥቷል፡፡ፍርድ ቤቱ በሰጠው ብይን እንደገለጸው፣ ኢሳትና ኦኤምኤን ሕጋዊ ድርጅቶች መሆን አለመሆናቸው ተገልጾ መቅረብ አለበት፡፡ ድርጅቶቹ ሕጋዊ ከሆኑ በየትኛው አገር እንደሚገኙ፣ መቼና እንዴት እንደተቋቋሙ ተገልጾ መቅረብ አለበት፡፡ በመሆኑም ክሱ ተሻሽሎ እንዲቀርብ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ዶ/ር መረራ በዕለቱ ማለትም ግንቦት 25 ቀን 2009 ዓ.ም. በጠበቆቻቸው አማካይነት አቤቱታ አቅርበዋል፡፡ ተከሳሹ ባቀረቡት አቤቱታ ከቀረቡባቸው ክሶች ጋር የደረሱዋቸው ማስረጃዎች፣ የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕጉን የተከተሉ አለመሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ ባልተከሰሱበት በሽብርተኝነት አዋጁ መሠረት የቀረቡ በመሆናቸው፣ ተስተካክለው እንዲደርሱዋቸው እንዲታዘዝላቸው ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡ፍርድ ቤቱ በሰጠው ምላሽ አቤቱታው መቅረብ የነበረበት ቀደም ብለው ካቀረቡት የክስ መቃወሚያ ጋር መሆን አስታውቆ ተቀብሏቸዋል፡፡ ዓቃቤ ሕግ አሻሽሎ የሚያቀርበውን ክስ ለመቀበልና ተከሳሹ ባቀረቡት አቤቱታ ላይ ብይን ለመስጠት ለሰኔ 13 ቀን 2009 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
0
455e6992f757f17bafaa7b3e20bf30ab
54a1c43d33ea7b760209a6b638028d3d
“ሻዛ”፤ የሰሊጥ ቅቤ ማምረት ጀመረ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 25፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) 8 ሚሊየን ብር የሚገመት የምግብ እና የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ድጋፍ መደረጉን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ፅህፈት ቤት አስታወቀ።የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል በተደረገው የድጋፍ ጥሪ መሰረት ዛሬ አልሳም ግሩፕ፣ አምደሁን ጀኔራል ትሬዲንግ እና አቶ ጀማል አህመድ ከ8 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የምግብ እና የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን በጋራ ድጋፍ አድርገዋል።ድርጅቶቹ በመስቀል አደባባይ በመገኘት ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ፅህፈት ቤት ሃላፊ እና የድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ አባል ወይዘሮ አለምጸሀይ ጳውሎስ አስረክበዋል።4 ሺህ ኩንታል ስንዴ እና በቆሎ፣ 900 ካርቶን የአትክልት ቅቤ እና 2 ሺህ ካርቶን የገላ ሳሙና እንደሚገኙበት ከአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
0
b39254a2787137503b8cc68bc2b014a8
1a58719a79c5ff811c959248b05cd1da
124ኛውን የአድዋ ድል በዓል ለመዘከር የተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች የሚሳተፉበት የአድዋ ጉዞ ተጀመረ
በአዲስ አበባ ሌላ የአድዋ ድል መዘከሪያ ሀውልት ሊቆም እንደሆነ የአስተዳድሩ ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ ኡማ ገለፁ፡፡ ምክትል ከንቲባው ይህንን ያሉት ዛሬ ለ123ኛ ጊዜ በዳግማዊ ሚኒሊክ አደባባይ እየተከበረ ያለውን የአድዋ ድል በአል አከባበር በማስመልከት በአዲስ አበባ ምኒሊክ አደባባይ ባደረጉት ንግግር ላይ ነው፡፡ድል ከነፃነት በላይ ነው ያሉት ምክትል ከንቲባው የድል መንፈስ የሰው ልጅ ከማሸነፍ በፊት ቀድሞ የሚያሸንፍበት መሳርያ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ምክትል ከንቲባው አክለውም የአድዋ ድል በአል አያቶቻችን እና እናት አባቶቻችን ፅናትን በመታጠቅ አሁን ያለችዋን ኢትዮጵያን ከጠላት መንጋጋ በመቀማት እንዳስቀሩልንና በመስዋዕትነት የተገኘች ሀገር ላይ እንዳለን ተናግረዋል፡፡እንደ ኢንጂነር ታከለ ገለፃ አሁን ያለው ትውልድ ከአሉባልታ ወሬ ይልቅ የአገር ግንባታን ማስቀደም አለበት ያሉ ሲሆን መንግስታት ቢያልፉም አገርና ትውልድ ግን ይቀጥላልም ብለዋል፡፡ምክትል ከንቲባው በመጪው አመት 124ተኛውን የአድዋ ድል መዘከሪያ በአል ሲከበር የመታሰቢያ ሀውልቱ ቆሞ ይሆናል የሚል እምነትን እንደሰነቁም ተናግረዋል፡፡ በዳግማዊት ግርማ ፎቶ፡- በገባቦ ገብሬ
0
bc6f9f63709dcc979f9591bac4cfc1ff
e04bf1f142c0aaf06c04fae9717226f5
ጀርመን ለኢትዮጵያ የ4 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የድጋፍ ማዕቀፍ ይፋ አደረገች
በአዲስ አበባ የተካሄደውን ሦስተኛውን ፋይናንስ ለልማት ጉባዔ ሲታደሙ የሰነበቱት የአውሮፓ ኅብረት ከፍተኛ ኃላፊዎች፣ ለኢትዮጵያ የሴፍቲኔት ፕሮግራምና ለመንገድ ዘርፍ ልማት የሚውል የ4.4 ቢሊዮን ብር ወይም፣ የ190 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ ኅብረቱ መስጠቱን በማስመልከት ከመንግሥት ጋር ስምምነት ፈረሙ፡፡ሐምሌ 10 ቀን 2007 ዓ.ም. በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ዋና መሥሪያ ቤት በተካሄዴው ስምምነት ወቅት እንደተገለጸው፣ ለውጤት ተኮር ሴፍቲኔት ፕሮግራሞች ማስፈጸሚያ 1.1 ቢሊዮን ብር ወይም የ50 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ ሲደረግ፣ ለመንገድ ኔትወርክ ማስፋፊያ እንዲውል የተሰጠው ደግሞ 3.3 ቢሊዮን ብር ወይም 140 ሚሊዮን ዩሮ ነው፡፡በአውሮፓ ኅብረት ኮሚሽን የዓለም አቀፍ ትብብርና ልማት ኮሚሽነር ኔቨን ሚሚካ ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትሩ አቶ ሱፊያን አህመድ ጋር ዕርዳታ ስምምነቱን ተፈራርመዋል፡፡የአውሮፓ ኅብረት በሴፍቲኔት በኩል የሰጠው ድጋፍ በኢትዮጵያ ተጨማሪ 4.7 ሚሊዮን የምግብ ዋስትና ችግር ላለባቸው ዜጎች የሚውል ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም ድጋፍ ሲያገኙ የነበሩ 3.6 ሚሊዮን ዜጎችን እንደሚያካትትም ሚሚካ አስታውቀዋል፡፡ አቶ ሱፊያን በሰጡት መግለጫ፣ የአውሮፓ ኅብረት እ.ኤ.አ. ከ2005 ጀምሮ 1.1 ቢሊዮን ዩሮ ለኢትዮጵያ የልማት ሥራዎች የፋይናንስ ድጋፍ መስጠቱን ተናግረዋል፡፡ከዚህ ጋር በተያያዘ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ 40 ሚሊዮን ዩሮ ብድር መስጠቱን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል፡፡ የባንኩ ኃላፊዎች በሰጡት መግለጫ መሠረት፣ ለኢትዮጵያ መንግሥት የተሰጠው ብድር በሃያ ዓመታት ወስጥ የሚከፈል ነው፡፡ ከዚህ ጎን ለጎንም የፈረንሳይና የጣልያን መንግሥታት በጋራ 40 ሚሊዮን ዩሮ በማቅረብ፣ በጠቅላላው የ80 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ ከአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክና ከአባል አገሮቹ የተገኘው ገንዘብ ለመካከለኛና አነስተኛ ከተሞች የመጠጥ ውኃ አቅርቦትና የሳኒታሪ ሥራዎች ማስፋፊያ ይውላል፡፡
0
85be24d2fe91e52e973d1a1766dd73b8
82f2a2996454a34e27cd830cbd01e7dc
ቻይና ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ በሁለት ከተሞች የጉዞ ክልከላ ጣለች
ባሕር ዳር፡ ሚያዝያ 25/2012 ዓ.ም (አብመድ) ባለፉት 24 ሰዓታት ለ1 ሺህ 560 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎ በሁለት ሰዎች ላይ የኮሮና ቫይረስ መገኘቱን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ሚኒስቴሩ በማኅበራዊ ገጹ እንዳስታወቀው ሁለቱም የጉዞ ታሪክ የሌላቸው ኢትዮጵያውያን ናቸው፡፡ አንደኛው ታማሚ ከባቱ (ዝዋይ) አዲስ አበባ ሄደው በሕክምና ተቋም ተኝተው ሕክምና ሲከታተሉ ናሙና ተወስዶላቸው የተመረመሩ የ49 ዓመት ወንድ ናቸው፡፡ ሁለተኛዋ ደግሞ በቤት ለቤት ቅኝትና አሰሳ የተገኙ የደቡብ ክልል ስልጤ ወረዳ ነዋሪ የ45 ዓመት ሴት ናቸው፡፡የጤና ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ስድስት ተጨማሪ ሰዎች ደግሞ ከቫይረሱ አገግመዋል፤ ሁሉም ከድሬዳዋ መሆናቸውም ተመላክቷል፡፡ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ከኮሮና ቫይረስ ያገገሙ ሰዎች ቁጥርም 75 ደርሷል፤ በሕክምና ክትትል ላይ የሚገኙት ደግሞ 55 ናቸው፡፡በኢትዮጵያ ከመጋቢት 4/2012ዓ.ም ጀምሮ 135 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው በምርመራ ተረጋግጧል፤ የሦስት ታካሚዎች ሕይወት አልፏል፤ ሁለት የውጭ ዜጎች ደግሞ ወደ ሀገራቸው ተልከዋል፡፡ አጠቃላይ የተመረመሩት ሰዎች ብዛት ደግሞ 22 ሺህ 330 ደርሷል፡፡
0
a075848a470f4b574c80910c4c4eac96
ce05f4bcd7335d5b9ac3b57d4ec82cbf
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኮሮና ቫይረስ ስጋት በምርጫ ኦፕሬሽን ላይ ስለሚኖረው ተጽእኖ ከፖለቲካ ፓርዎች ጋር ተወያየ
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 1፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቦርድ አመራር አባል እና ሰራተኞች የጋና ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ሂደትን ተከታተሉ።የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቦርድ አመራር ፍቅሬ ገብረህይወት የተመራው የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰራተኞች ቡድን ነው የጋና ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ሂደትን የተከታተለው።በቆይታቸውም የጋራና ፕሬዘዳንታዊ ምርጫ ሂደትን፣ የድምጽ መስጫ ቀን የተደረጉ ተግባራትን፣ የኮቪድ ወረርሽን በመከላከል የተከናወነውን የድምጽ መስጠት ሂደት ተመልክተዋል።እንዲሁም ምርጫን የኮቪድ ወረርሽኝ ጥንቃቄ በማድረግ ለማከናወን የተደረጉ ተግባራትን፣ የምርጫ አስፈጻሚው ተቋምን አሰራር፣ የምርጫ ክልል ደረጃ ውጤት ቆጠራ፣ ድመራ እና ይፋ የማድረግን ሂደቱንም ተመልክተዋል።ከጋና ምርጫ ኮሚሽን አመራር አካላትም ጋር ተገናኝተው መወያየታቸውነም ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ልኡካን ምርጫውን ከመታዘብም በተጨማሪ በተለይ በኮቪድ ወረርሽኝ ስጋት ውስጥ ሆኖ ምርጫ ማከናወን የሚያስፈልጉትን የበጀት እና የሎጄስቲክስ ዝግጅቶችን ከጋና ምርጫ ልምድ መቅሰም መቻላቸውንም ቦርዱ አስታውቋል።የጋራ ፕሬዘዳንታዊ ምርጫ ሰኞ ህዳር 28 ቀን 2013 መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን፥ በፕሬዚዳንታዊ ምርጫውም የ 76 ዓመቱ ናና አኩፎ አዶ 51 ነጥብ 6 በመቶ ድምጽ በማግኘት ማሸነፋቸውም ታውቋል።ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የፋና ድረ ገጽ ይጎብኙ፤ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን ይወዳጁንዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
0
87a7118e409516dcbebae45d4ff28477
87a7118e409516dcbebae45d4ff28477
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ ባን ኪ ሙን በኢትዮጵያ በድርቅ የተጎዱ አከባቢዎችን ሊጎበኙ ነው
-የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ፀሀፊ ባን ኪ ሙን የፊታችን እሁድ ኢትዮጵያ ኤል ኒኖ ያደረሰባትን አሉታዊ ተፅእኖ ለመቋቋም እያደረገች ያለችውን ጥረት ለመመልከት የመስክ ጉብኝት ሊያደርጉ ነው።ባን የመስክ ጉብኝታቸውን የሚያደርጉት በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን በድርቁ በተጎዱ አከባቢዎች ነው ተብሏል።ከመስክ ጉብኝቱ አስቀድሞም ባን ከኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጋር በጉዳዩ ላይ በአዲስ አበባ ውይይት ያደርጋሉ ተብሏል።ዋና ፀሀፊው ቅዳሜ በሚጀመረው 26ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች መደበኛ ጉባኤ ላይ ይገኛሉ።በጉባኤው ላይ ከ40 የሚበልጡ የህብረቱ አባል አገራት መሪዎች እና በርከት የሚሉ የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።(ኤፍ.ቢ.ሲ)የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ ባን ኪ ሙን በኢትዮጵያ በድርቅ የተጎዱ አከባቢዎችን ሊጎበኙ ነውአዲስ አበባ ፣ ጥር 20/2008(ዋኢማ)-የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ፀሀፊ ባን ኪ ሙን የፊታችን እሁድ ኢትዮጵያ ኤል ኒኖ ያደረሰባትን አሉታዊ ተፅእኖ ለመቋቋም እያደረገች ያለችውን ጥረት ለመመልከት የመስክ ጉብኝት ሊያደርጉ ነው።ባን የመስክ ጉብኝታቸውን የሚያደርጉት በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን በድርቁ በተጎዱ አከባቢዎች ነው ተብሏል።ከመስክ ጉብኝቱ አስቀድሞም ባን ከኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጋር በጉዳዩ ላይ በአዲስ አበባ ውይይት ያደርጋሉ ተብሏል።ዋና ፀሀፊው ቅዳሜ በሚጀመረው 26ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች መደበኛ ጉባኤ ላይ ይገኛሉ።በጉባኤው ላይ ከ40 የሚበልጡ የህብረቱ አባል አገራት መሪዎች እና በርከት የሚሉ የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።(ኤፍ.ቢ.ሲ)
1