query_id
stringlengths
32
32
passage_id
stringlengths
32
32
query
stringlengths
1
300
passage
stringlengths
95
13.7k
category
class label
6 classes
link
stringlengths
28
740
source_dataset
stringclasses
4 values
386ad82c431e47d1cc4af80e9447bab7
71d8919b36b6a438db60caae08d7c1f9
ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን ችግሮች ለመፍታት በህብረት መቆም እንደሚገባ ፖለቲከኞች ገለፁ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 20፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ አሁን የገጠሟትን ችግሮች ለመፍታት እንደ አድዋው ድል በህብረት መቆም እንደሚገባ ፖለቲከኞች ገለፁ።ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የአድዋ ድል በዓልን አስመልክቶ ያነጋገራቸው ፖለቲከኞች በጋራ እውነተኛ ዴሞክራሲ ስርአትን ለመገንባት መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።የአድዋ ድልን ለሀገራዊ መግባባት መጠቀም እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል።ቀድሞ የነበረው የኢትዮጵያውያን ህብረት እና አንድነት አሁን ካጠላው የመገፋፋት ፖለቲካ አንጻር የአድዋ ድልን የማይመጥን እና በድሉ ክብር ልክ ያልተጠቀምንበት ነው ሲሉም ያነሳሉ።ከዚህ ባለፈ ግን የአድዋ ድል ትቶት ያለፈውን እሴት በተጨባጭ ትውልዱ እንዳልተጠቀመበትም አስረድተዋል።ሃገር ፈተና ውስጥ በገባች ጊዜ ህዝቦች በትብብር ቆመዋል የሚሉት ፖለቲከኞቹ፥ ዘንድሮም የህዝቦች አንድነት ሀገሪቱ ለገጠማት ችግር መሹለኪያ ሊሆን ይገባል ብለዋል።ወራሪን ያሳፈረው የአባቶች ታሪክ ዛሬ ላይ ካለው የጥላቻ እና የልዩነት ታሪክ ወጥቶ ለሀገር ሰላም በሚጠቅም መልኩ ሊሰራበት እንደሚገባም አንስተዋል።በጋራ ዴሞክራሲያዊ ስርአት መፍጠር የአሁኑ ትውልድ ሀላፊነት በመሆኑ፥ ሀገርን እና ከአባቶች የተሻገረውን የህብረት አሻራ ጠብቆ ለማቆየት ማስተዋል እንደሚገባም አንስተዋል።የአድዋ ድል ዝክር በተለይም ወጣቱ ሀገራዊ ፍቅር እና ተቆርቋሪነት ውስጥ እንዲገባ ሊነገርና በአግባቡ ጥቅም ላይ መዋል የሚገባው እንደሆነም ገልጸዋል።አሁን እውነተኛ ዴሞክራሲን ለመገንባት የምንሰራበት ወቅት እንደመሆኑ ከአባቶች የቀደመ ታሪክ ልንማር ይገባልም ነው የሚሉት አስተያየት ሰጭዎቹ።አያይዘውም በፖለቲካ ውስጥ ያሉ አካላት የራስን ሀቅ ሸሽቶ ህዝቦችን ለመነጣጠል ትርክትን ከመስበክ ሊቆጠቡ እንደሚገባም አውስተዋል።በሃይለእየሱስ መኮንን
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%8a%a2%e1%89%b5%e1%8b%ae%e1%8c%b5%e1%8b%ab-%e1%8b%ab%e1%8c%8b%e1%8c%a0%e1%88%9f%e1%89%b5%e1%8a%95-%e1%89%bd%e1%8c%8d%e1%88%ae%e1%89%bd-%e1%88%88%e1%88%98%e1%8d%8d%e1%89%b3%e1%89%b5-%e1%89%a0/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
f62dfa9c33dd12c5dfac8049cf7d1af7
0d623dbb5af5a4abac6b37d838c999dd
ኢንጂነር ታከለ በሶማሌና ኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ተፈናቅለው በአዲስ አበባ ከሚገኙ የእስልምና እምነት ተከታዮች ጋር ዒድ አልፈጥርን አከበሩ
 አዲስ አበባ፦ የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ዑማ በሶማሌና ኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች በነበረው ችግር ከመኖሪያቸው ተፈናቅለው በአዲስ አበባ ከሚገኙ የእስልምና እምነት ተከታዮች ጋር የዒድ አልፈጥር በዓልን አከበሩ።በወቅቱም ኢንጂነር ታከለ ለበዓል እንዲሆናቸው ከባለሃብቶች ያሰቧሰቧቸውን የተለያዩ ስጦታዎችን አበርክተውላቸዋል ። ለሁሉም የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። በአካባቢው የሚገኙ መሰረተ ልማቶችን በማሻሻል የመኖሪያ ቤቶችም እንደሚገነቡላቸው ጠቁመዋል።የተፈናቀሉ ዜጎችም በተደረገላቸው ድጋፍ አመስግነዋል።ስጦታው ሰንጋ በሬዎችን ጨምሮ ተለያዩ የምግብ አይነቶች ያካተተ ነው።አዲስ ዘመን ግንቦት 17/2012 በጋዜጣው ሪፖርተር
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=33024
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
f45f85ac702be3d83d125dbe330983ce
91e6970b5e80e4589435ab7e1365d5fd
የጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ ጽህፈት ቤት በአዲስ መልኩ እየተደራጀ መሆኑ ተገለጸ
የጠቅላይ ሚንስትር ልዩ ጽህፈት ቤት በአዲስ መልኩ እየተደራጀ መሆኑን  የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ በመሆን የተሾሙት አቶ ሽመልስ  አብዲሳ ተናገሩ ።       አቶ ሽመልስ አብዲሳ የቀድሞ የጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ ጽህፈት ቤት ሀላፊ የነበሩትን አቶ ፍጹም አረጋን በመተካት መሾማቸው ትናንት ይፋ ተደርጓል ።የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ የሆኑት አቶ ሽመልስ  ከዛሬ  ጀምሮ የጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ ጽህፈት ቤት ኃላፊነት ሥራቸውን በይፋ  እንደሚጀምሩ አስታውቀዋል።አቶ ሽመልስ በመግለጫው ላይ እንደጠቆሙት ፥ በአዲስ መልኩ በመደራጀት ላይ የሚገኘው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ከፍተኛ ኃላፊነት ተሸክሞ የጠቅላይ ሚኒስትሩን የእለት ተዕለት ስራ የመደገፍ፣ ራዕይ የማስፈፀም እንዲሁም የሚኒስትር መስሪያ ቤቶችና ሌሎች ተቋማት ጋር ያለውን ፍላጎት የማሟላት ሥራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል።የፕሬስ ሴክሬተሪ ኃላፊነት የተሾሙት ወይዘሮ ቢልለኔ ትልቅ ሀላፊነት በመውሰድ ከዚህ በፊት በመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ሲሰራ የነበረን ስራ በየእለቱ ከመገናኛ ብዙሃን ጋር ግንኙነት በመፍጠር መረጃዎችን በግልጽነት በጊዜ የመሥጠት ስራን ያከናውናሉ ብለዋል።ቀደም ሲል በጠቅላይ ሚንስትር ጽህፈት ቤት ኃላፊነት ሲያገለግሉ የቆዩት አቶ ፍጹም አረጋም ከፍተኛ ስራን ሲሰሩ መቆየታቸውንም አቶ ሽመልስ በመግለጫቸው  አንስተዋል።በተለይም የኮሙዩኒኬሽን ስራዎች ላይ የጠቅላይ ሚኒስትሩን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴን ለህዝብ ማድረስን ተደራቢ ስራ አድርገው ምሳሌያዊ በሆነ መልኩ ጥሩ ስራ ሲሰሩ ቆይተዋል፤ ለዚህም ጽህፈት ቤቱ  ምስጋና ያቀርባል ብለዋል ።
5ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/30517/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
77c36e74bced4f95b1838f63d8c3e718
d2c93780dc5b73f451f37eb0e8e589ef
ዲየጎ ማራዶና
ዲያጎ አርማንዶ ማራዶና (ስፓኒሽ፡ [ˈdjeɣo maɾaˈðona]፤ ጥቅምት 30 ቀን 1960 - ህዳር 25 ቀን 2020) የአርጀንቲና ፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋች እና አስተዳዳሪ ነበር። በስፖርቱ ታሪክ ውስጥ ከታላላቅ ተጨዋቾች አንዱ ተብሎ በሰፊው የሚነገርለት የ20ኛው ክፍለ ዘመን የፊፋ ተጫዋች ሽልማት ከሁለቱ በጋራ አሸናፊዎች አንዱ ነበር። የማራዶና እይታ፣ ቅብብልብ፣ ኳስን የመቆጣጠር እና የመንጠባጠብ ብቃቱ ከትንሽ ቁመቱ ጋር ተዳምሮ ዝቅተኛ የስበት ኃይል እንዲኖረው እና ከሌሎች ተጫዋቾች በተሻለ እንዲንቀሳቀስ አስችሎታል። የሜዳው መገኘት እና መሪነት በቡድኑ አጠቃላይ ብቃት ላይ ትልቅ ተጽእኖ ያሳደረ ሲሆን ብዙ ጊዜ በተቃዋሚዎች ተለይቶ ይታይ ነበር። ከፈጠራ ችሎታው በተጨማሪ የጎል አይን የነበረው እና የፍፁም ቅጣት ምት ስፔሻሊስት መሆኑ ይታወቃል። ቀደምት ተሰጥኦ የነበረው ማራዶና “ኤል ፒቤ ደ ኦሮ” (“ወርቃማው ልጅ”) የሚል ቅጽል ስም ተሰጥቶት ነበር፣ ይህ ስም በሙያው በሙሉ ከእሱ ጋር ተጣብቋል። እንዲሁም ከሜዳ ውጪ ችግር ያለበት ህይወት ነበረው እና በ1991 እና 1994 እፅ አላግባብ በመጠቀማቸው ታግዶ ነበር።በክላሲክ ቁጥር 10 ቦታ ላይ የተሰማራው የላቀ የጨዋታ ተጫዋች ማራዶና የአለም ሪከርድ የዝውውር ዋጋ ሁለት ጊዜ በማስመዝገብ የመጀመሪያው ተጫዋች ነበር፡ እ.ኤ.አ. በ1982 ወደ ባርሴሎና በ5 ሚሊየን ፓውንድ ሲዘዋወር እና በ1984 ወደ ናፖሊ በገንዘብ ሲዛወር 6.9 ሚሊዮን ፓውንድ። በአርጀንቲኖስ ጁኒየርስ፣ ቦካ ጁኒየርስ፣ ባርሴሎና፣ ናፖሊ፣ ሲቪያ፣ እና ኔዌል ኦልድ ቦይስ በክለብ ህይወቱ የተጫወተ ሲሆን በናፖሊ ብዙ ሽልማቶችን በማግኘቱ በጣም ታዋቂ ነው። በአርጀንቲና ባደረገው ኢንተርናሽናል ህይወቱ 91 ጨዋታዎችን አድርጎ 34 ጎሎችን አስቆጥሯል። ማራዶና በ1986 በሜክሲኮ የተካሄደውን የዓለም ዋንጫን ጨምሮ በአራት የፊፋ የዓለም ዋንጫዎች ተጫውቶ አርጀንቲናን በመምራት ምዕራብ ጀርመንን በፍጻሜው አሸንፋለች እና የውድድሩ ምርጥ ተጫዋች በመሆን የወርቅ ኳስ አሸንፏል። እ.ኤ.አ. በ1986 የአለም ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ በሁለት የተለያዩ ምክንያቶች በእግር ኳስ ታሪክ የገባውን እንግሊዝን 2–1 በማሸነፍ ሁለቱንም ጎሎች አስቆጥሯል። የመጀመርያው ጎል ያልተቆጠበ የአያያዝ ጥፋት ሲሆን “የእግዚአብሔር እጅ” በመባል የሚታወቅ ሲሆን ሁለተኛው ጎል 60 ሜትር (66 yd) አምስት የእንግሊዝ ተጫዋቾችን ያለፈበት ድሪብል ተከትሎ በ2002 በፊፋ ዶትኮም መራጮች “የክፍለ ዘመኑ ጎል” የሚል ድምጽ ሰጠ። ማራዶና በህዳር 2008 የአርጀንቲና ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን አሰልጣኝ ሆነ። በ2010 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው የአለም ዋንጫ ቡድኑን በመምራት በውድድሩ መጨረሻ ላይ ቡድኑን መርቷል። በመቀጠልም መቀመጫውን በዱባይ ያደረገውን ክለብ አል ዋስልን በ UAE Pro-League ለ2011–12 የውድድር ዘመን አሰልጥኗል። በ2017 ማራዶና በውድድር ዘመኑ መጨረሻ ከመልቀቁ በፊት የፉጃይራህ አሰልጣኝ ሆነ። በግንቦት 2018 ማራዶና አዲሱ የቤላሩስ ክለብ ዳይናሞ ብሬስት ሊቀመንበር ሆኖ ታወቀ። ብሬስት ደረሰ እና በሐምሌ ወር ስራውን እንዲጀምር በክለቡ ቀርቦለታል። ከሴፕቴምበር 2018 እስከ ሰኔ 2019 ማራዶና የሜክሲኮ ክለብ ዶራዶስ አሰልጣኝ ነበር። እ.ኤ.አ. ከሴፕቴምበር 2019 ጀምሮ እስከ ህዳር 2020 ህልፈተ ህይወታቸው ድረስ የአርጀንቲና ፕሪሜራ ዲቪሲዮን ክለብ ጂምናሲያ ዴ ላ ፕላታ አሰልጣኝ ነበሩ። የአርጀንቲና እግር ኳስ ተጫዋቾች
null
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
b3bcc7afca34fc3d6099690b2af211a0
41ece37ace59c76b2f074c35e34c226e
አፍሪቃ በአሜሪካ ጋዜጦች
በቡርኪና ፋሶ መፈንቅለ-መንግስት ከተካሄደ አንድ ሳምንት በኋላ የመፈንቅለ-መንግስቱ ኢላማ የነበሩት ጊዚያዊ ፕረዚዳንት ባለፈው ረቡዕ ወደ ስልጣናቸው እንደተመለሱ ኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ ድረ-ገጽ() ዘግቧል።ጊዜያዊ የቡርኪና ፋሶ ፕረዚዳንት ሚካኣኤል ካፋንዶ(Michel Kafando)ሌሎች ሀገሮች መፈንቅለ-መንግስቱን በማውገዛቸው አመስግነዋቸዋል። መፈንቅለ-መንግስቱን ያካሄዱት ባለፈው ጥቅምት ወር በህዝባዊ መነሳሳት ምክንያት ከስልጣን የተወገዱት ፕረዚዳንት ብሌዝ ካምፓኦሬ አጋሮች እንደሆኑ ዘገባው ገልጿል።“የቡርኪና ፋሶ ህዝብ በተለይም ወጣቱ ክፍል ካለምንም ፍርሀት ቆርጦ በመነሳት መፈንቅለ-መንግስቱን በማክሸፍ ተግባር በመርዳቱ እንኮራበታለን” ሲሉ ፕረዚዳንቱ አሞግሰዋል። --------ታይም መጽሄት() ድረ-ገጽ ላይ የወጣ አንድ ጽሁፍ አፍሪቃ በኢኮኖሚ እድገት እየተራመደች ቢሆንም የእድገትዋ ሂደት አካታች አይደለም። ወጣቶች እየበዙበት በመሄድ ላይ ላለው ህዝቧ በቂና ተገቢ የስራ እድል እየፈጠረች አይደልም ይላል። አፍሪቃ እአአ እስከ 2020 ዓ.ም. ባለው ጊዜ (በአምስት አመታት ጊዜ ውስጥ ማለት ነው) 54 ሚልዮን የሚሆን አዲስ የስራ እድል እንደምትፈጥር የኢኮኖሚ ጠበብት ይገምታሉ።ይሁንና በዛን ወቀት 122 ሚልዮን የሚሆኑ አፍሪቃውያን በስራ ሃይል ቁጥር ውስጥ ይገባሉ። ከነሱም በአስር ሚልዮኖች የሚቆጠሩት የስራ እድል አያገኙም ወይም የሚመጥናቸውን አይነት ስራ አያገኙም። ስለሆነም ለተሻል የስራ እድል ሩቁን ቦታ አሻግረው ማየት ይጀምራሉ ሲል ጽሁፉ ያስገነዝባል።የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ወደ ውጭ እንዳይሰደዱ ለማድረግ የሚቻለው አፍሪቃውያን በሀገሮቻቸው ጥሩ የስራ እድል እንዲያገኙ በማድረግ ነው። በአፍሪቃ ሀገሮች ያሉት በግል ንግድ የተሰማሩት ሰዎችና የንግድ መደብሮቻቸው እንዲያድጉና እንዲበለጽጉ እድል በመስጠት የስራ እድሎች እንዲበራከቱ ማደረግ እንደሚቻል ታይም መጽሄት ድረ-ገጽ ላይ የወጣው ጽሁፍ ያስገነዝባል።ሙሉውን ቅንብር የድምፅ ፋይሉን በመጫን ያድምጡ።
4ዓለም አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/2979242.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
8b2a8b322bd62c5e796483f77ac1da3b
19c77c31a4261faa0a85490380277442
‹‹ህወሓት ትላንት የፈጠረውን ችግር በማረሳሳት እንደገና የአራት ኪሎን ወንበር እያሰበ ነው›› አቶ ትግስቱ አወሉ የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበርና የፌዴራሊስት ሀይሎች ፎረም ምክትል ሰብሳቢ
አዲስ አበባ፡-‹‹የፌዴራሊስት ኃይል›› የሚለው የህወሓት ፕሮፖጋንዳ ትላንትና ራሱ የፈጠረውን ችግር በማረሳሳትና በማዘናጋት እንደገና የአራት ኪሎን ወንበር እያሰበ መሆኑን የሚያሳይ ነው ሲሉ አቶ ትግስቱ አወሉ ገለጹ።ጫፍ ከያዘውና ዋልታ ረገጥ ከሆነው የፌዴራሊስት ሀይሎች ፎረም ምክትል ሰብሳቢነት ራሳቸውን ማግለላቸውንም ተናግረዋል።የአንድነት ለዴሞክራሲና የፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበርና በቅርቡ በመቐለ በተቋቋመው የፌዴራሊስት ኃይሎች ፎረም ምክትል ሰብሳቢ የነበሩት አቶ ትግስቱ አወሉ፤ ወቅታዊውን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ሁኔታ አስመልክተው ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ የገዢው ፓርቲ አባል የነበረው ህወሓት ለፌዴራሊስት ኃይሎች ባዘጋጀው ስብሰባ ጥሪ ሲደርሳቸው ድርጅታቸውን ወክለው መሳተፋቸውንና የፎረሙ ምክትል ሰብሳቢ ተደርገው መመረጣቸውን አስታውሰዋል።ነገር ግን በስብሰባው ሂደት ህወሓት ትላንትና የነበረውን ችግር በማስረሳት፤ አገዛዙን በሌላ የአደረጃጀት መንገድ ለማምጣትና እንደገና የአራት ኪሎን ወንበር በማሰብ እየሰራ መሆኑን በመገንዘብ እንዲሁም የህወሓት ዓላማ ከአገር ሠላም ጋር የማይሄድ በመሆኑ ራሳቸውን ከፎረሙ ማግለላቸውን አስታውቀዋል።እንደ አቶ ትግስቱ ማብራሪያ፤ የፌዴራሊስት ሀይሎች ፎረሙ መድረክ የሚያጠነጥነው ብሄራዊ ፌዴራሊዝምና ህገ መንግስቱን ማዳን የሚል ሀሳብን ሲሆን የአደረጃጀቱ ዓላማም ‹‹በፌዴራሊዝሙ ማንነትህ እየተነጠቀ ነው›› በሚል ሀሳብ በደካማ ጎን ለመግባት የሚደረግ እንቅስቃሴ ነው።ምንም እንኳን ህወሓት የፌዴራሊዝም ጉዳይ አሳስቦኛል ቢልም፤ ከዚህ ቀደም የነበረው የራሱ አካሄድ ጸረ ፌዴራሊዝም የነበረና አሁንም ቢሆን ይህ ፕሮፖጋንዳ የሚጠቀመው ትላንትና የነበረውን ችግርበማረሳሳትና በማዘናጋት እንደገና የአራት ኪሎን ወንበር በማሰብ ነው።በለውጥ ሂደት ውስጥ ህገ መንግስቱና የፌዴራል ሥርዓቱ ተንዷል የሚለው ህወሓት ቀድሞም ቢሆን ህገ መንግስቱን ሲተገብር አልነበረም።አቶ ትግስቱ፤ ‹‹ህወሓት የትላንትና አገዛዙን በሌላ የአደረጃጀት መንገድ ለማምጣት በበረሀ በነበረበት ጊዜ የተለያዩ ድርጅቶችን በመሰብሰብ ግንባር እንደፈጠረ ሁሉ አሁንም ባማረ ከተማ ውስጥ ምልመላ እያደረገ ነው።ይህ የፎረሙ አደረጃጀት ከጥግ ወደ መሀል ለመግባት የቀየሱት ሌላ ስትራቴጂና የትላንቱን አስተሳሰብ መልሶ ለማምጣት የሚጠቀምበት ሥልት ነው። ‹‹መስመራችን ኃይላችን ነው›› ይላሉ።ይህ ማለት የሚከተሉት የአብዮታዊ ዴሞክራሲን መስመር እንደሆነ የሚገልጽ ነው።በመሆኑም ይህንን ሊደግፉ የሚችሉ ሌሎች ሀይሎችን ለመፍጠር ነው እየሰሩ ነው ያሉት›› ሲሉም አክለው ገልጸዋል።‹‹ህገ መንግስቱን እናድን›› የሚለው የስብሰባው መሪ ሀሳብ በህወሓት የተነደፈ እንጂ ሌሎች የፖለቲካ ፓርቲዎች ተስማምተውበት ያወጡት አይደለም ያሉት አቶ ትግስቱ፤ በስብሰባው ህወሓት ሁሉንም አማራጮች እንጠቀማለን ማለቱንና ይህ ማለት ደግሞ ከዴሞክራሲያዊ አማራጭ ውጭ ሌላ የሀይል አማራጭ እንዳለው የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል። አካሄዱ ጫፍ የያዘና ዋልታ ረገጥ በመሆኑ ዴሞክራሲያዊ መንገድን የተከተለ አለመሆኑን አስታውቀዋል።ድርጅቱ አሁንም ቢሆን እኩልነት በሚል ስብስብ ውስጥ የበላይነት አስተሳሰቡን ለመጫን እየሞከረ መሆኑንም አስረድተዋል።አቶ ትግስቱ፤ ስብስቡን በበላይነት የሚመራው ህወሓት የብልጽግና ፓርቲ አሃዳዊ ነው የሚለውም የብሄር ብሄረሰቦችን ቀልብ ለመሳብና የሀሳቡ አጋር ለማድረግ አዋጭ የመታገያ መንገድ ነው ብሎ በማሰብ መሆኑን አስታውቀዋል።የፌዴራሊስት ኃይሉ ‹‹ጋብቻ ለመመስረት›› እየተንደረደረ እንጂ ፎረሙ እስካሁን ህጋዊ መሠረት እንደሌለው የጠቆሙት አቶ ትግስቱ በፎረሙ ውስጥ ያለው ስብስብ የተደበላለቀ አቋም ያለው በመሆኑ ቆም ብሎ ሊታይ እንደሚገባውም አስገንዝበዋል።ህዝቡም ቢሆን ከሚነገረው ትርክት ባሻገር የፖለቲካውን አንድምታ ማወቅ እንደሚያስፈልገው አስረድተዋል።በፌዴራሊስት ሀይሎች ስብስብ ውስጥ የተካተቱት ፓርቲዎች በማንነት ፖለቲካና በመልክዓምድር ላይ የተመሠረተ የፖለቲካ እሳቤ ያላቸው ሲሆኑ፤ አሁንም ቢሆን በብሔር የተደራጁ ድርጅቶችንና ሌሎች አገር አቀፍ ድርጅቶችን ለያይቶ የማየት ሁኔታዎች መኖራቸውን አቶ ትግስቱ ገልጸዋል።በስብሰባዎች ሠላማዊ የሚመስል ነገር እንደማይታይ፤ በተለይ የሚጠቀሙባቸው ኃይለ ቃሎች ዴሞክራሲን የሚገልጹ አለመሆናቸው፤ ለምሳሌ ‹‹ተነስ ዝመት›› የሚል ቃል እንደሚጠቀሙና ይህ ቃል በአብዛኛው የአምባገነኖች ቃል መሆኑንም ጠቁመው፤ ህወሓት የትግራይን ህዝብ ባህሪ የማይወክል ነገር ግን የትግራይ ህዝብ የኢትዮጵያ ህዝብ መሆኑ ተዘንግቶ ሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ የትግራይ ህዝብ ስጋት ነው ብሎ እንዲያስብ እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል። የስብስቡ ዓላማ በምንም መልኩ ተቀባይነት የሌለውና ከርሳቸው ድርጅት ተልዕኮ አንጻር የማይሄድ በመሆኑ የነበራቸውን የምክትል ሰብሳቢነት ኃላፊነትም ሆነ ድርጅታቸው በፎረሙ ውስጥ የነበረውን ተሳትፎ ማቋረጣቸውን ጠቅሰው፤ የፌዴራሊስት ፎረሙ ሀሳብ የሚስተናገድበት አግባብም ድርጅታዊ መስመርም እንደሌለው አጽንኦት ሰጥተዋል።የኢትዮጵያን ሰላም የሚያሳጡ መሰል ድርጊቶችን ከሌሎች ድርጅቶች ጋር በመሆን እንደሚታገሉትም ገልጸዋል።አዲስዘመን ጥር 1/2012አዲሱ ገረመው
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=25399
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
4f7383a0f459a52cdd558fe0b326c196
dbb0e0bc8afb0f0c50282d2eaf9b94bb
መሬት መንሸራተትና ጎርፍ በደቡብ ኢትዮጵያ ጥፋት አደረሰ
"መጀመሪያ ጎርፉን ሰበብ አድርጎ መሬቱ መሰንጠቅ ጀመረ፣ ጎርፉ እና ዝናቡ ካቆመ አንድ ሳምንት ቢሆነውም መሬቱ መሰንጠቁን አላቆመም። መሬቱም ወደታች እየሰመጠ ነው። አንድ ሁለት ቤቶችም ሰምጠዋል" ይህን ምስክርነት የሰጡን ከአዲስ አበባ 130 ኪሎ ሜትር ላይ በምትገኘው፣ መናጋሻዋን ቡታጂራ ባደረገችው የመስቃን ወረዳ ውስጥ የሚኖሩት አቶ ሙኸዲን መሃመድ ናቸው፡፡ በከባድ ዝናብ እና ጎርፍ የታጀበውን ያለፈውን ሳምንት ተፈጥሯዊ አደጋ የሚመስል ክስተት በዚህ አካባቢ መደጋገሙን ነዋሪዎች ይናገራሉ። ቦታው ዛቢዳር ተብሎ ከሚጠራው ተራራ አቅራቢያ፣ በኢትዮጵያ የስምጥ ሸለቆ ምዕራባዊ መንደርደሪ ላይ መገኘቱ በተደጋጋሚ ለደረሰው መሬት መንሸራተትና መሰንጠቅ ተጠቂ ሳያደርገው እንዳልቀረ የከርሰ-ምድር አጥኚው አቶ ሚፍታ ሸምሱ ያምናሉ። ይህ ሰማይ ግም ባለ ቁጥር መሬቱ እየራደ የሚከተለው የመሬት መንሸራተት እና መሰንጠቅ የአሁኑ ለሦስተኛ ጊዜ መሆኑንም ያስታውሳሉ፡፡ ባሳለፍነው ሳምንት ላይ ይሄ ስፍራ የመሬት መሰንጠቅ ክስተትን አስተናግዷል። ክስተቱ የሰው ነፍስ ቀጥፏል፣ ንብረት አውድሟል። የመስቃን ወረዳ የኮሚኒኬሽን ቢሮ ጋዜጠኛ አቶ ሬድዋን ከድር፤ ከሰሞኑ የገጠመውን የጉዳቱን ዝርዝር ሲያስቀምጡ 16 ቀበሌዎች ሰለባ እንደሆኑ ይናገራሉ። የተሰነጠቀው ዋና መንገድ "በዘቢዳር ተራራ አካባቢ በተፈጠረ የመሬት መንሸራተት የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ ሰዎች የገቡበት ጠፍቷል። የተወሰኑት በቁፋሮ ተገኝተዋል። ቡታጂራ ከተማ በሚገኝ ወንዝ አካባቢ ህጻናትን ከደራሽ ውሃ ለማዳን የገባ አንድ ሰውም ህይወቱን አጥቷል" ብለዋል በአጠቃላይ ከ5 ያላነሱ ሰዎች ህይወታቸው መጥፋቱንም ጠቁመዋል። ጎርፍና የመሬት መንሸራተት ያስከተሉት ጥፋት ይሄ ብቻ አይደለም። አቶ ሬድዋን ጨማረው እንደነገሩን በሰብል የተሸፈኑ መሬቶችና የመኖሪያ ቤቶች ወድመዋል እንዲሁም ነዋሪዎች ተፈናቅለዋል። ተፈጥሯዊው አደጋ ከአዲስ አበባ ተነስቶ አርባምንጭ የሚያደርሰውን አውራ መንገድ ለሁለት መሰንጠቁን፣ በዚህም ወረዳውን አልፈው የሚሄዱ ተጓዦች በሌላ ቅያሪ መንገድ እንዲያልፉ እየተደረገ መሆኑን ቢቢሲ ከነዋሪዎች ሰምቷል። የመስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን አየለ ደግሞ ለቢቢሲእንደተናገሩት 476 ሰወዎች በጎርፍ ምክንያት የተፈናቀሉ ሲሆን፤ በአሁኑ ሰዓት ወደ መኖሪያቸው እንዲመለሱ ጥረት እየተደረገ እንደሆነ ተናግረዋል። በተጨማሪም በመሬት መሰንጠቅ አደጋ የተፈናቀሉ 145 ሰዎችአሁንም ስጋት ላይ ስለመሆናቸው ጠቁመው፤ በአጠቃላይ የደረሰው የንብረት ውድመት ግምት 2 ሚሊዮን ብር ይደርሳል ብለዋል። የተወሰኑ በአደጋው የተፈናቀሉ አባወራዎችን እና ቤተሰቦቻቸውን የወረዳው አስተዳደር እና የቀይ መስቀል ማህበር ባዘጋጇቸው የድንኳን መጠለያ ውስጥ ለጊዜው እንዲርፉ እንደተደረገ የሚያነሱት አቶ ሬድዋን፤ የሚያዛልቀው መፍትሄ ግን በዚያ ስፍራ የሚኖሩ ሰዎችን ወደ ሌላ ቦታ ማስፈር እንደሆነ ያስረዳሉ። ከጎርፉ ጋር ተያይዞ ተጨማሪ የመሬት መንሸራተት ሊከሰት ይችላሉ የሚል ከፍተኛ ስጋት ያላቸው አቶ ሚፍታ ሸምሱ መወሰድ ባለበት የቅድመ ጥንቃቄ እርምጃም ይስማማሉ። "በስፍራው የሚኖሩ ሰዎች ካለቅድመ ሁኔታ ከአከባቢው እንዲለቁ መደረግ አለበት። ነዋሪዎች በተሻለ ቦታ እንዲጠለሉ ተደርጎ ዘላቂ መላ ማበጀት ያስፈልጋል" ሲሉ የሚመለከታቸው የክልልና የፌዴራል ተቋማት አደጋውን ለመቆጣጠር የበኩላቸውን እንዲያደርጉ ጠይቀዋል። ሆኖም ግን በአካባቢው የሚኖሩ አርሶ አደሮች ቦታቸውን ለቀው ወደ ሌላ ቦታ የመስፈር ፍላጎት እንሌላቸው ተጠቁሟል።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
513ba078122519b3b4e9f951b72c1f37
579b533d7346198ab6ce5cea590e443d
ካለሁበት 34፡ በአሜሪካ የህግ አስከባሪዎች ከማንም ሰው በበለጠ ህግን ይጠብቃሉ፤ ያከብራሉ።
የከፍተኛ ትምህርቴን ለመከታተል ደግሞ ወደ ጅማ ዩኒቨርሲቲ ሄድኩ። የመጀመሪያ ዲግሪዬን እዛው አገኘሁ። ትምህርቴን ጨርሼ ከተመረቅኩኝ በኋላ በተለያዩ የመንግሥት እና የግል ድርጅቶች ውስጥ በሂሳብ ሰራተኝንት ስሰራ ቆየሁ። ከዚም ዲቪ ደርሶኝ ወደ አሜሪካ መጣሁ። አሁን የምኖረው በሳውዝ ዳኮታ ግዛት ሲ ፎልስ በምትባል ከተማ ነው። ይቺ ከተማ በጣም የተዋበች እና ዘመናዊ ናት። ከፍ ካለ ስፍራ የሚፈሰውና ከተማዋን አቋርጦ የሚሄደው ወንዝ ደግሞ ልዩ ውበት ሰጥቷታል። ሃገሬን እና አሜሪካን ማወዳደር ይከብደኛል። አሜሪካ በቴክኖሎጂ የመጠቀች ናት፤ ኢትዮጵያ ግን ገና በማደግ ላይ ያለች ሃገር ነች። እዚህ አገር ሁሉም ነገር በተግባር ነው የሚገለጸው። ህጎች እንኳን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ይደረጋሉ። ኢትዮጵያን ከአሜሪካ የሚለያት ዋናው ነገር ብዬ የማስበው የህግ አተገባበር ሥርዓቱ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ ትልልቅ ህጎች አሉ፤ ነገር ግን ልዩነቱ ወደ ተግባር መቀየሩ ላይ ነው። እዚህ አገር ህጎች ተግባራዊ የሚደረጉት በሰዎች ብቻ ሳይሆን በቴክኖሎጂም ጭምር ታግዘው ነው። የተለያዩ ካሜራዎች እና የቴክኖሎጂ ውጤቶች ህግን ለማስከበር ጥቅም ላይ ይውላሉ። ህግ አስከባሪዎቹም ቢሆኑ ለህጉ ተገዢዎች ናቸው። የእኛን ሃገር ስንመለከት ግን ከታች ካለው የህግ አስከባሪ ጀምሮ እስከ ትልቅ ባለስልጣን ድረስ ሁሉም ከህግ በላይ እንደሆኑ ነው የሚያስቡት። እዚህ አገር ግን ከኢትዮጵያ ተቃራኒ ነው። ህግ አስከባሪዎቹ በግንባር ቀደምነት ለህግ ተገዢ ናቸው። ይሄ ለኔ በጣም ልዩ ነው። ወደ አሜሪካ በመምጣቴ አተረፍኩ ብዬ የማስበው ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ብቻ አይደለም፤ ተግባራዊ እና መፍትሄ ላይ ያተከረ የትምህርት ማግኘቴም ጭምር ነው። የተለየ ስልጣን ወይም ችሎታ ቢኖረኝ በምኖርባት ከተማ ያለውን ከፍተኛ የጤና አገልግሎት እና ለትምህርት የሚደረግ ክፍያ መለወጥ እፈልጋለው። ምክንያቱም ለትምህርት እና ለጤና አገልግሎት የሚከፈለው ክፍያ በጣም የተጋነነ ነው። እኔ የምኖርበት አካባቢ ብዙ የምግብ አይነቶች አሉ፤ እንደ እንጀራ ግን የሚያስደስተኝ የለም። እዚህ ካሉት ምግቦች የምመርጠው ግን ፒዛ ነው። ከሃገሬ ደግሞ ከሚናፍቁኝ ነገሮች መካከል የሰዉ የእርስ በርስ መከባበር እና ባህል አክባሪነት ሁሌም ከልቤ አይጠፉም። የምኖርባት ከተማ ብዙ ተፈጥሮአዊ መስህቦች አሏት፤ ለኔ የተለየ ስሜት የሚሰጠኝና የምወደው በከተማዋ መሃል የሚፈሰው ሲ ፎልስ ወንዝ ነው። ከተማዋ ስሟን ያገነችውም ከዚሁ ወንዝ ነው። አካባቢው ለአይን ስለሚማርክ ብዙ ሰዎች መጥተው ይጎበኙታል። ሁሌም ቢሆን እዚህ ያለውን የተራቀቀ ቴክኖሎጂ እና የተቀናጀ ሥርዓት ስመለከት ሃገሬ ትዝ ትለኛለች። ምናለ ኢትዮጵያም እንደዚህ ብትሆን እላለሁ። እዚህ ሃገር ለመጀመሪያ ጊዜ እንደመጣሁ ያስደነገጠኝ ነገር የሃገሬ ልጆች በተለያዩ ሱሶች እና አደንዛዥ እጾች ተጠምደው ስመለከት ነበር። ያንን ሁሉ ችግር አልፎ እዚህ ደርሶ፤ የመጣበትን ምክንያት ረስቶ ሰው እንዴት ሱስ ውስጥ ይገባል ብዬ በጣም አዘንኩ። እራስን ለማሻሻል ዋናው ነገር የግል ጥረት እና ውሳኔ እንጂ ከሃገር መውጣቱ ብቻ እንዳልሆነ አስተምሮኛል። በሆነ ተአምር አንድ ኃይል ሃገሬ ቢወስደኝ በታላቁ ስምጥ ሸለቆ ውስጥ በሻሸመኔ መንገድ ላይ የምትገኘው የትውልድ ቦታዬ ብሄድ ደስ ይለኛል። ይህች ከተማ በትንንሽ ሃይቆች የተከበበች በመሆኗ ለኑሮ ምቹ እና ተስማሚ መልከዓ-ምድር አላት። የ'ካለሁበት' ቀጣይ ክፍል ለማግኘት ፦ ካለሁበት 35፡ አቧራ እንደ ዝናብ ሲዘንብ አይቼ ስለማላውቅ ሁሌም ያስገርመኛል
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
62c7cd13df2de8dea4a039817ae49df2
55ada02bbcd8f8fc06c1131964938c99
​በኦሮሚያ ክልል አለመረጋጋቱ ቀጥሏል
ባለፈው ሳምንት በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን የተቀሰቀሰው ግጭት በዚህ ሳምንት ቀጥሎ አለመረጋጋቱ በተለያዩ አካባቢዎች ታይቷል፡፡ ግጭቱ በምዕራብ አርሲና በምሥራቅ ሐረርጌ የቀጠለ ሲሆን፣ በሌሎች አካባቢዎችም ተመሳሳይ አለመረጋጋቶች መታየታቸውን ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡በተለይ ባለፈው ሰኞ የካቲት 14 ቀን 2008 ዓ.ም. በምሥራቅ ሐረርጌ ዞን በተቀሰቀሰው ግጭት የሰዎች ሕይወት ማለፉን የጠቆሙት ምንጮች፣ በሐረርና በድሬዳዋ ከተሞች ለተወሰነ ጊዜ የትራንስፖርት አገልግሎት ተቋርጦ እንደነበር  ገልጸዋል፡፡ በዞኑ አለማያ ወረዳ አወዳይ ከተማ በተቀሰቀሰው ግጭት  ሳቢያ በሐረርና በድሬዳዋ ከተሞች መካከል የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተቋርጦ የነበረ ሲሆን፣ በሜታ ወረዳ ጨለንቆ ከተማና በደደር ወረዳ ቆቦ ከተማ በተነሳው ግጭት ከአሰበ ተፈሪ ወደ ሐረርና ድሬዳዋ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተቋርጦ ነበር ተብሏል፡፡ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ለመንግሥት የሚዲያ ተቋማት መግለጫ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ፣ ‹‹መንግሥት በኦሮሚያ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ የጥፋት ኃይሎች ላይ የማያዳግም ዕርምጃ ይወስዳል፤›› ብለዋል፡፡ ‹‹የጥፋት ኃይሎቹ ለዘመናት ከሌሎች ብሔሮች ጋር ተዋህዶ የኖረውን የኦሮሞ ሕዝብ ለማጋጨት በአንዳንድ ቦታዎች በሌሎች ብሔር ተወላጆችና ንብረቶች ላይ ጉዳት አድርሰዋል፤›› ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ‹‹እነዚህ የጥፋት ኃይሎች አገሪቱንና ኢኮኖሚዋን በከፍተኛ ደረጃ ከመጉዳታቸው በፊት የማያዳግም ዕርምጃ ይወሰድባቸዋል፤›› ብለዋል፡፡የጥፋት ኃይሎቹ የተለያዩ የመንግሥት የሕዝብ ንብረቶችን የማፈራረስና የማቃጠል ተግባራት ላይ መሳተፋቸውን ያስረዱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ጥቂት የማይባሉ የፀጥታ ኃይሎች ላይ በሽምቅ ጉዳት ማድረሳቸውን ተናግረዋል፡፡ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ባቀረበው ጥያቄ መሠረትም የፌዴራል መንግሥት በክልሉ የተቀሰቀሰውን ግጭት ለማረጋጋት ጣልቃ መግባቱን ገልጸዋል፡፡በሌላ በኩል የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሙክታር ከድር በሁከቱ ሳቢያ የመንግሥትና የግለሰብ ንብረት እንዳይወድም ኅብረተሰቡ ከፊት በመቆም ሲከላከል ነበር ብለው፣ የአገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች በዚህ ረገድ ከፍተኛ ሚና ነበራቸው ብለዋል፡፡ የጥፋት ኃይሎቹ ያነሱት ሁከት ወደ ከፋ አቅጣጫ ሳያመራ ኅብረተሰቡ በመደራጀት የአካባቢውን ሰላም ቀድሞ ወደነበረበት እንዲመለስ ላደረገው ከፍተኛ ጥረት ሊመሰገን ይገባዋልም ብለዋል፡፡በተያዘው ሳምንት ግን በምሥራቅ ሐረርጌ በተቀሰቀሰው ግጭት የሰዎች ሕይወት ማለፉን የጠቀሱት ምንጮች በምዕራብ አርሲ፣ በምዕራብ ወለጋ፣ በጅማና በአምቦ በነበሩት ግጭቶች ከፍተኛ ንብረት መውደሙ ታውቋል፡፡ከወራት በፊት በኦሮሚያ የተለያዩ አካባቢዎች ተቀስቅሶ የነበረው ተቃውሞ የማገርሸት ባህሪ በማሳየት በተለያዩ አካባቢዎች አለመረጋጋቶች ተስተውለዋል፡፡ ምንም እንኳን የአዲስ አበባና ዙሪያዋ የኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ የጋራ ማስተር ፕላን ተግባራዊ መደረግ የለበትም በሚል በክልሉ ግጭቱ ቢቀሰቀስም፣ ማስተር ፕላኑ እንደማይተገበር ከተገለጸ በኋላም ግጭቱ ቀጥሏል፡፡ የፖለቲካ ተንታኞችም ማስተር ፕላኑ ለግጭቱ መነሻ ሆነ እንጂ፣ በክልሉ በተንሰራፋው የመልካም አስተዳደር ችግር ሕዝቡ መማሩን ይገልጻሉ፡፡ በክልሉ የተቀሰቀሰው ግጭት የበርካቶችን ሕይወት የቀጠፈ ሲሆን፣ ከፍተኛ የሆነ የንብረት ውድመትም አስከትሏል፡፡  ምንም እንኳን ከገለልተኛ ወገኖች ምን ያህል ሰዎች እንደሞቱ መረጃ ማግኘት ባይቻልም፣ በዚህ ሳምንት መግለጫ ያወጣው ሒዩማን ራይትስ ዎች ከ200 በላይ ሰዎች እንደሞቱ እንደሚገመት አስታውቋል፡፡ 
5ፖለቲካ
https://www.ethiopianreporter.com/article/11170
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
bb53122c051e17d054790df0effe98aa
e85b186ade93bd4c814c73b9be2bbd5a
አልጄርያ የምትገኝበት አህጉር የት ነው?
አልጄሪያ አልጄሪያ (አረብኛ፦ الجزائر‎ አል ጃዝኤር; በርበርኛ፦ ድዜየር) በይፋ የአልጄሪያ ሕዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በሰሜን አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። ከቆሳ ስፋት አኳያ በሜዲቴራንያን ባህር ዙሪያ ትልቋ ስትሆን፣ ከአፍሪካ ደግሞ ከሱዳን በኋላ ሁለተኛ ናት። አልጄሪያ ከሰሜን ምሥራቅ በቱኒዚያ፣ ከምሥራቅ በሊቢያ፣ ከምዕራብ በሞሮኮ፣ ከደቡብ ምዕራብ በምዕራባዊ ሣህራ፣ ሞሪታኒያና ማሊ፣ ከደቡብ ምሥራቅ በኒጄር፣ ከሰሜን በሜዲቴራንያን ባህር ትዋሰናለች። ዋና ከተማዋ አልጂርዝ ሲሆን የ፳፻፫ ዓ.ም. ሕዝብ ብዛቷ ወደ 35.7 ሚሊዮን ይገመታል። አልጄሪያ የተባበሩት መንግሥታት፣ የአፍሪካ ሕብረት፣ ኦፔክ እና ሌሎችም ዓለም አቀፍ ድርጅቶች አባል ሀገር ናት። የሀገሯ ስም የመጣው ከአልጂርዝ ከተማ ሲሆን በድሮ ጊዜ ከዛሬዎቹ ምዕራብ ቱኒዚያና ምሥራቅ ሞርኮ አብራ ኑሚዲያ ትባል ነበር። በጥንት ጊዜ አልጄሪያ የኑሚዲያ መንግሥት ትባል የነበረ ሲሆን ነዋሪዎቿ ደግሞ ኑሚዲያውያን ይባሉ ነበር። የኑሚዲያ መንግሥት ከካርታጎ፣ ሮማና ጥንታዊ ግሪክ ጋር ግንኙነት ነበራት። አካባቢው ለምለም እንደነበረ ሲነገር ኑሚዲያውያን ደግሞ ለኃይለኛ ፈረሰኛ ጦራቸው ይታወቁ ነበር።
null
null
https://huggingface.co/datasets/israel/AmharicQA
e4ca21e61b5727b8153bde900d0b32d7
1c9e0ae704800369871f2f2016da466a
አየር መንገዶች "ከምድራችን ይልቅ ጥቅማቸውን ያስቀድማሉ" የሚል ክስ ቀረበባቸው
ይህም አውሮፕላኑ በሚይዘው ክብደት ልክ ብዙ ነዳጅ ተቃጥሎ አየር እንዲበከል እየተደረገ ነው ተብሏል። አየር መንገዶች አውሮፕላኖቻቸው ከመነሻቸው ብዙ ነዳጅ ጭነው የሚነሱት በመዳረሻ አየር መንገዶች ለነዳጅ የሚጠየቁትን ብዙ የነዳጅ ገንዘብ ለማስቀረት ነው። ብሪቲሽ አየር መንገድ "ለደህንነት እና ከዋጋ ጋር በተያያዙ ምክንያቶች" ተጨማሪ ነዳጅ ይዞ መብረር የተለመደ ነው ብሏል። ቢቢሲ ፓኖራማ የተሰኘው የቢቢሲ የቴሌቪዥን ፕሮግራም ባለፈው ዓመት የብሪቲሽ አየር መንገድ አውሮፕላኖች ተጨማሪ ነዳጅ ይዘው በመብረራቸው ተጨማሪ 18ሺህ ቶን ካርበን ዳይኦክሳይድ አመንጭተዋል ሲል መዘገቡ ይታወሳል። አንድ ጥናት እንዳረጋገጠው ደግሞ አውሮፓ ውስጥ ከሚደረጉ ከአምስት በረራዎች ቢያንስ በአንዱ አውሮፕላኑ ተጨማሪ ነዳጅ ይዞ ወደ መዳረሻው ይበራል። ተቺዎች እንደሚሉት ይህ ተግባር አየር መንገዶች የአየር ብክለትን ለመቀነስ እንሰራለን የሚሉትን ቃል ጥያቄ ውስጥ የሚከት ነው። ከተቺዎቹ መካከል አንዱ የሆኑት ጆህን ሳኡቨን አየር መንገዶች "ከምድራችን ይልቅ ጥቅማቸወን ያስቀድማሉ" ለምንለው ይህ ትክክለኛ ማሳያ ነው ሲሉ ተደምጠዋል።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
795edb881ee4669f743f84255444a455
61d6daab3b4d904cbc24f149f1ccef21
ጲላጦስ
ጴንጤናዊው ጲላጦስ(Pontius Pilate) 5ተኛው የይሁዳ ገዢ ነበር። ጴንጤናዊው ጲላጦስ ግዛቱ ከ26-36 ከ.ል.በ.(እ.ኤ.አ.) ቆይቷል። ቀዳሚው ቫሌሪየስ ግራተስ ሲሆን ተከታዩ ማርሴስ ነው። ዜግነቱ ሮማዊ ሚስቱ ክላውዲያ ናት። ታዋቂነቱ በጲላጦስ አደባባይ ነው። የሚከበረው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን ሲሆን በአለ ንግሱ ሰኔ 25 ነው። ማጣቀሻ
null
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
1a99ec90b5589e3e5a88928006de3a88
656c526b1e01e1478d71c077c3c69247
“ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ ቡና ከሌሎቹ ጨዋታዎች የተለየ ነው” ማርት ኑይ
 ለአራተኛ ተከታታይ ግዜ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አሸናፊ ለመሆን ተስፋን የሰነቀው ቅዱስ ጊዮርጊስ የከተማ ባላንታውን ኢትዮጵያ ቡናን ቅዳሜ ይገጥማል፡፡ ፈረሰኞቹ ባሳለፍነው ሳምንት ከወላይታ ድቻ ጋር ነጥብ መጋራታቸውን ተከትሎ ከተከታዮቻቸው የነበራቸውን የነጥብ ልዩነት ማስፋት የሚችሉበትን እድል አምክነዋል፡፡ከሶዶ መልስ ለተጫዋቾቻቸው በቂ እረፍት ሰጥተው ጠንካራ ዝግጅት እንዳደረጉ የቅዱስ ጊዮርጊስ አሰልጣኝ ማርት ኑይ ለሶከር ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡ “ድቻ በርቀት ተጉዘን ከምንገጥማቸው ክለቦች አንዱ ስለሆነ ከጨዋታ በኃላ ለሁለት ቀናት ለተጫዋቾቼ እረፍት ሰጥቼ ነበር፡፡ ይህንን ተከትሎ ያደረግነው ዝግጅት በጣም ጥሩ ነው፡፡ 24 ጤነኛ የሆኑ ተጫዋቾች አሉን፡፡ ስለዚህም ለጨዋታ ዝግጁ ነን፡፡”ሐሙስ በተደረጉ ጨዋታዎች የሊጉ አናት ላይ ከፈረሰኞቹ ጋር የተቀመጡት ደደቢት፣ ሲዳማ ቡና እና በቅርብ ርቀት የሚገኘው አዳማ ከተማ ወሳኝ ነጥቦችን ጥለዋል፡፡ አሰልጣኝ ኖይ ግን የቡድኖችን ነጥብ መጣል ተከትሎ ስለሚፈጠረው ነገር እምብዛም አስተያየት መስጠት አልፈለጉም፡፡ “እኔ የሌሎቹን ነጥብ መጣል አልመለከትም፡፡ እኔ የራሴን ቡድን ነው የምመከተው፡፡ ገና ረጅም ጉዞ ይቀረናል፡፡ ልጆቼን ከፊታችን የቻምፒየንስ ሊግ ጨዋታም ስለሚጠብቅን ጤነኛ እና የነቁ ማድረግ አለብኝ፡፡ ይህ ነው የእኔ ስራ ፡፡ እኛ ይህ ቡድን ነጥብ እየጣለ ነው ሌላኛው ሶስት ተከታታይ ጨዋታ እያሸነፈ ነው እያልን የሂሳብ ስሌት ውስጥ አንገባም፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ የሚሰራውን ስራ እናያለን ከዛ በተረፈ የቀረውን ጨዋታ የወዳጅነት ጨዋታ ቢሆንም ለማሸነፍ ጥረት እንደርጋለን፡፡ ካሸነፍን ደስተኛ እንሆናለን፡፡ ከተሸነፍን ደግሞ ተጋጣሚያችን ከእኛ ተሸሎ ከነበረ እና አቻ ብንወጣም ጉዟችንን እንቀጥላለን፡፡ ሁሌም ግን ጥሩ ውጤትን ይዞ መምጣት ነው አላማችን፡፡”ሆላንዳዊው አሰልጣኝ አዲስ አበባ ውስጥ ከሚገኙ ክለቦች አንፃር ኢትዮጵያ ቡና ከቅዱስ ጊዮርጊስ የሚያደርጉት ጨዋታ የተለየ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ “እኛ አዲስ አበባ ውስጥ ብቻ ከኢትዮጵያ ቡና፣ ደደቢት፣ ባንክ እና ሌሎቹንም እንጫወታለን፡፡ ቢሆንም ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ ቡና ከሌሎቹ ጨዋታዎች የተለየ ነው፡፡ በድሮው ግዜ እንደነበረው በግላስኮው ሴልቲክ ከሬንጀርስ፣ ሊቨርፑል ከኤቨርተን እንዲሁም ኢንተር ከኤሲ ሚላን ደርቢ ነው ይህም በሁለት የተለያዩ ፅንፍ ያሉ የከተማ ክለቦች የሚያደርጉት የደርቢ ጨዋታ ነው፡፡ እኔ ተስፋ ማድርገው በሁለቱም ክለቦች በኩል ተመልካቹን የሚያዝናና እግርኳስ እንድንመለከት ነው፡፡”
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/27390
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
aa6f58ed473557d7100a5d04c83289fa
ece8b4f980bdbb4d68a4d1f960ea9304
ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል ቅንጅታዊ ስራን ማጠናከር ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ
በሀገር አቀፍ ብሎም በክልል እና በዞን ደረጃ ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውርን በመታደግ ረገድ ውጤታማ ሊያደርጉ የሚችሉ አራት የስራ ቡድኖች ተዋቅረው እየተንቀሳቀሱ ሲሆን ከእነዚህ መካከል በክልል ደረጃ በሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሰብሳቢነት የሚመራው የመከላከል ቡድን የ2ዐ1ዐ በጀት ዓመት ዕቅድ ከክልል እና ከዞን ለተውጣጡ ተሳታፊዎች ቀርቦ ውይይት  እንደተደረገበት የአማራ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለፀ፡፡ ውይይቱን የመሩት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሞላ ጀምበሬ እንደገለፁት ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን መከላከል የአንድ ወገን ስራ ብቻ ባለመሆኑ ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ርብርብ መኖር ወሳኝ ነው፡፡ በቀረበው ዕቅድ መሰረትም በክልሉ ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል ህገ-ወጥ ዝውውርን የሚጠየፍ ማህበረሰብ መፍጠር፣ለችግሩ ተጋላጭ ዜጐች ጥበቃና ከለላ ማድረግ እና ከሚመለከታቸው መንግስታዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ አካላት ጋር የቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር ቅድሚያ የተሰጣቸው ተግባራት እንደሆኑ ተመልክቷል፡፡ የውይይቱ ተሳታፊዎች  ካለፉት ዓመታት አፈፃፀም በመነሳት ለስራው ውጤታማነት እንደ ችግር የሚነሱ በህገ-ወጥ ዝውውር የተያዙ ግለሰቦችን ወደ መጡበት አካባቢ ለመመለስ በሚደረግ ጥረት ያሉ የማቆያ፣የትራንስፖርት እና የበጀት የመሳሰሉ እጥረቶች በቀጣይም ችግር ሆነው እንዳይቀጥሉ መፍትሔ ሊቀመጥላቸው እንደሚገባ አስተያየት መስጠታቸዉም ተጠቁሟል፡፡በኢትዮጵያ ህገ ወጥ የሰዎች ዝዉዉር ከጊዜ ወደጊዜ አሳሳቢ እየሆነ የመጣ ችግር ሲሆን መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችም ተመላሽ ዜጎችን ከመደገፍ ባለፈ ህገ ወጥ ዝውውርን ለመቀነስ በሚደረገው ጥረት ወስጥ የድርሻቸውን እንዲወጡም  ተደጋጋሚ ጥሪ ሲደረግ ቆይቷል፡፡የስደት አስከፊነትን በተመለከተ በትምህርት ቤቶች፣ በሃይማኖት ተቋማት፣ በአደረጃጀቶች ንቅናቄ በመፍጠር ለህብረተሰቡ ግንዛቤ መፍጠር እንደሚገባና የሚዲያና የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎችም በህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና በሀገር ውስጥ ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል የሚያሳዩ ፕሮግራሞችን በመስራት የአመለካከት ለዉጥ ለማምጣት በሚደረገዉ ጥረት የበኩላቸዉን ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ ተላልፏል፡፡
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://waltainfo.com/am/31806/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
7d5afd655f4e197915a8b5db2d92b35b
c986744eab0547f92aaefd74994d9caf
ሰብዓዊ መብት ፡ "የሕግ የበላይነት መሰረቱ የፍርድ ቤት ውሳኔዎችን ማክበር ነው" ኢሰመኮ
የኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) የሰብዓዊ መብቶች መከበር ዋና ዋስትናው የፍርድ ቤት ውሳኔ መከበር መሆኑን በመግለጫው ላይ አመልክተዋል። አክለውም አቶ ልደቱን ጨምሮ በፍርድ ቤት ዋስትና መብት ተፈቅዶላቸው ከእስር እንዲለቀቁ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ የሰጠላቸው ታሳሪዎች "በሙሉ በአስቸኳይ እና ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከእስር ሊፈቱ ይገባል" ማለታቸው በመግለጫው ላይ ተጠቅሷል። ቢቢሲ ይህንንና ተያያዥ ጉዳዮችን በማንሳት የኮሚሽኑ ከፍተኛ አማካሪ ከሆኑት ከአቶ ምስጋናው ሙሉጌታ ጋር ቆይታ አድርጓል። ቢቢሲ፡ የፍርድ ቤት ውሳኔ ካለመፈጸም ጋር በተያያዘ መግለጫ ለማውጣት አልዘገያችሁም? አቶ ምስጋናው፡ መዘግየቱን በሚመለከት ከዚህ ቀደምም ስንከታተል ነበር። በእስር ላይ ያሉ ሰዎችን ሁኔታ ኮሚሽኑ ይከታተላል። ሁሉንም የክትትላችንን ውጤት ለሕዝብ ይፋ እናደርጋለን ማለት አይደለም። ይህንን ችግር [የአቶ ልደቱ ዋስትና መብት አለመከበር] መነሻ ተደርጎ ነው እንጂ፣ የተወሰኑ የተደጋጋሙ ነገሮችም አሉ። እንደዚህ በስም ታዋቂ ያልሆኑ የዋስትና መብት የተፈቀደላቸው ነገር ግን በፖሊስ እስር ስላሉ ሰዎች የደረሱን ጥቆማዎች አሉ። ስለዚህ ይህ በአጠቃላይ አሁን የአቶ ልደቱ ታዋቂም ስለሆኑ፣ ብዙ ሰው ጉዳያቸውንም ስለሚከታተል ጥሩ ማሳያ ይሆናል በሚል ነው እንጂ፤ አሁንም እየተከሰተ ያለ ነገር ስለሆነ ዘግይቷል ብዬ አላስብም። ምን ያህል ውጤታማ ይሆናል የሚለው ግን በእኛ እምነት ሰብዓዊ መብትን ማክበርና ማስከበር በዋነኛነት የመንግሥት ኃላፊነት ነው። የመንግሥት አካላትም እኛ ያወጣነውን መግለጫ መሰረት በማድረግ የማስተካከያ እርምጃ ይወስዳሉ። የሕግ የበላይነት የሚባለው መሰረቱ የፍርድ ቤት ውሳኔዎችን አክብሮ መንቀሳቀስ ስለሆነ ነው። በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚከሰቱ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን የተመለከቱ መግለጫዎችን ታወጣላችሁ። እነዚህን ጉዳዮች በተመለከተ ከመንግሥት አካላት ጋር ትነጋገራላችሁ? አቶ ምስጋናው፡ አዎ እንነጋገራለን። እንዲህ አይነት መግለጫ ማውጣት አንደኛው ፋይዳ የመንግሥት አካላትም ነገሩን እንዲገነዘቡ፣ ሕብረተሰቡም ይህንን እንዲረዳውና ግፊት እንዲያደርግ እድል እፈጥራል ብለን እናስባለን። እንነጋገራለን። መግለጫዎች ከማውጣታችን በፊት ችግሮች ሲደርሱ፣ ከደረሱ በኋላ ምርመራ አድርገን የማስተካካያ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ከተለያዩ የመንግሥት አካላት ጋር ውይይት እናደርጋለን። አንዳንዶቹ ይፈታሉ፤ አንዳንዶቹ ጊዜ የሚወስዱ ናቸው ተብሎ ቃል ይገባልናል። እነርሱንም ግን መተግበራቸውን እንከታተላለን። መግለጫዎቹ በመንግሥት ላይም ሆነ ይህንን ውሳኔ በሚወስኑ አካላት ላይ ጫና ይፈጥራሉ ብለን እናስባለን እና በዚያ መልኩ ነው እየሄድንበት ያለነው። ግን ይህ የሚቆም ነገር ሳይሆን ከአሁን በኋላም የምንቀጥልበት ነው። የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ፈርጀ ብዙ ናቸው። በተለያዩ ስፍራዎች የተለያዩ ሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ይሰማሉ። በአገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች እንዳሉት ጥሰቶች ስፋትና ጥልቀት የእናንተ ሪፖርት ምን ያህል ሁሉንም ይሸፍናል? አቶ ምስጋናው፡ በሚፈለገው መጠን ሁሉም ቦታ ላንደርስ እንችላለን። ሰብዓዊ መብቶች እንደምታውቀው ለሁሉም ነው ተግባራዊ የሚሆኑት። አይበላለጡም፤ የማይነጣጠሉ ናቸው። አንድ ሰብዓዊ መብት ከአንድ መብት አያንስም። አንድ አካባቢ የሚደርስ ነገር ከአንድ ቦታ አይበልጥም። ይህ በመርህ ደረጃ በደንብ መሰመር ያለበት ነው። ኮሚሽኑ ሪፎርም ላይ ነው፤ የአቅም ውሱንነት አለበት። ስለዚህ ሁሉም ቦታ ለመድረስ ላይችል ይችላል። ግን በተቻለ መጠን ዋና ዋና የሚባሉትን ለመመርመር ለመከታተል እየሞከርን ነው። ለምሳሌ በወላይታ ምርመራ አድርገናል። በቅርቡም ኦሮሚያ...
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
b965dc4761f82a8d992852796aaa489e
f53d84dc36d4474331b09ab62dd45668
ሪፖርት | ደቡብ ፖሊስ ሳይጠበቅ ከኢትዮጵያ ቡና ሙሉ ሦስት ነጥብ ወሰዷል
በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 14ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር የመውረድ ስጋት የተጋረጠበት ደቡብ ፖሊስ ከሜዳው ውጪ ኢትዮጵያ ቡናን 2-1 በመርታት የዓመቱ ሁለተኛ ድሉን አሳክቷል።ተከታታይ ሁለት ጨዋታዎችን ሽንፈት ያስተናገዱት ኢትዮጵያ ቡናዎች ባሳለፍነው ሳምንት በጅማ አባ ጅፋር ከተረታው ቡድን በተከላካይ ስፍራ ላይ ጉዳት ባስተናገደው ተመስገን ካስትሮ ምትክ ወንድይፍራው ጌታሁንን እንዲሁም በተካልኝ ደጀኔ ምትክ ኃይሌ ገብረተንሳይን ሲተኩ በተመሳሳይ በአማካዩ ካሉሻ አልሀሰን ምትክ አጥቂው ሱሌይማን ሉክዋን በመቀየር ለዛሬው ጨዋታ ቀርበዋል፡፡ በአንጻሩ በሳምንቱ አጋማሽ የአሰልጣኝ ቅያሬ ያደረጉት ደቡብ ፖሊሶች ባሳለፍነው ሳምንት በመቐለ በሜዳው ከተሸነፈው ቡድን ውስጥ ግብ ጠባቂያቸው ዳዊት አሰፋን በሀብቴ ከድር እንዲሁም ኤርሚያስ በላይ ፣ መስፍን ኪዳኔ እና አዲስዓለም ደበበን አስወጥተው በምትካቸው ዮናስ በርታ ፣ በረከት ይስሀቅ እና ዘላለም ኢሳያስን አስገብተዋል፡፡ በጨዋታው የመጀመሪያ 15 ደቂቃዎች ባለሜዳዎቹ ኢትዮጵያ ቡናዎች ከራሳቸው ሜዳ ክፍል ኳስን መስርተው ለመውጣት ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል ፤ ምንም እንኳን በደቡብ ፖሊስ የፊት መስመር ተሰላፊዎች ጫና እምብዛም ባይደረግባቸውም ኳሶቹ ወደ መሀል ሜዳ ከደረሱ በኃላ ወደ ተቃራኒ የሜዳ ክፍል መድረስ ሳይችሉ ቀርተዋል ፤ በአንጻሩ ደቡብ ፖሊሶች ኳስ በቁጥጥራቸው ስር ስትገባ በፍጥነት ወደ መስመር በማውጣት ከመስመር በሚሻገሩ ኳሶች የግብ እድል ለመፍጠር ሙከራ አድርገዋል፡፡ በ7ኛው ደቂቃ ላይ አማኑኤል ዮሀንስ የተነጠቀውን ኳስ የተሻ ግዛው ከቀኝ መስመር ያሻገረለትን ነፃ አቋቋም ላይ የነበረው ሄኖክ አየለ ያመከናት  የጨዋታው የመጀመሪያ ሙከራ ነበረች፡፡ በ16ኛው ደቂቃ ወንድይፍራው ጌታሁን በቀላሉ ማራቅ የሚችለው ኳስ ወደ ውጪ በመውጣቱ ደቡብ ፖሊሶች ካገኙት የማዕዘን ምት የተሻማውን ኳስ በኢስማኢል ዋቴንጋ ደካማ የጊዜ አጠባበቅ ታግዞ ዘሪሁን አንሼቦ ነጻ አቋቋም ላይ ሆኖ በመግጨት ቡድኑን ቀዳሚ ማድረግ ችሏል፡፡ ከግቧ መቆጠር በኃላ ኢትዮጵያ ቡናዎች ፍፁም የሆነ የጨዋታ በላይነትን ወስደው መጫወት ችለዋል ፤ ነገር ግን በ23ኛው ደቂቃ ላይ የኢትዮጵያ ቡናው ሳምሶን ጥላሁን ባጋጠመው ጉዳት የተነሳ በዳንኤል ደምሴ ተቀይሮ ከሜዳ ሊወጣ ተገዷል፡፡ያልተጠበቀ ግብ በማስተናገዳቸው ጫና ውስጥ የገቡ የሚመስሉት የኢትዮጵያ ቡና ተጫዋቾች ጫናውን በሚያሳብቅ መልኩ በርካታ ግላዊ የሆኑ የቅብብል ስህተቶችን ሲሰሩ ተስተውሏል፡፡ ያም ቢሆን ሙከራዎችን ማድረግ የቻሉት ኢትዮጵያ ቡናዎች በ26ኛው ደቂቃ ኃይሌ ገ/ተንሳይ ከመሀል ያሻማውን የቅጣት  ምት ሱሌይማን ሎክዋ በደረቱ አውርዶ ሊመታ ሲል ወንድይፍራው ቀድሞ ደርሶ ወደ ግብ የላከው ኳስ ተከላካዮች ተደርበው ያወጡበት በኢትዮጵያ ቡና በኩል የተደረገ የመጀመሪያው ሙከራ ነበር፡፡ በ30ኛው ደቂቃ ከሁለቱ አጥቂዎች ሎክዋና የኃላሸት ጀርባ የተሰለፈው አቡበከር ናስር በጥልቀት ወደ ኃላ ተስቦ ያስጀመረውን ኳስ ኃይሌ ከቀኝ መስመር ሲያሻማ  አቡበከር በፍጥነት ደቡብ ፖሊስ ሳጥን ውስጥ ደርሶ በግንባሩ ገጭቶ የሞከራትን ኳስ የግቡ ቋሚ ሊመልስበት ችሏል፡፡ ጫና መፍጠራቸውን አጠናክረው የቀጠሉት ቡናዎች በ32ኛው ደቂቃ ዳንኤል ደምሴ ያሾለከለትን ኳስ አቡበከር በፍጥነት ተከላካዮችን አምልጦ ወደ ግብ የሞከረው እና የደቡብ ፖሊሱ ግብ ጠባቂ ሀብቴ ከድር ያዳነበት እንዲሁም በ36ኛው ደቂቃ ዳንኤል ደምሴ ከግራ ያሻማውን ኳስ አቡበከር በደረቱ ተቆጣሮ ቢያስቆጥርም ከጨዋታ ውጭ ተብሎ የተሻረበት ተጠቃሽ ሙከራዎች ነበሩ፡፡ በ37ኛው ደቂቃ በተመሳሳይ ደቡብ ፖሊሶች ካገኙት የማዕዘን ምት የተገኘውን ኳስ ዮናስ በርታ በግሩም ሁኔታ በግንባሩ በመግጨት ሳይጠበቅ የቡድኑን መሪነት ወደ ሁለት ያሳደገች ግብ ማስቆጠር ችሏል፡፡ በአንድ ደቂቃ ልዩነትም አቡበከር ናስር ከግራ መስመር የተሻገለትን ኳስ በደረቱ ተቆጣጥሮ እጅግ ማራኪ የሆነች የመቀስ ምት ግብ በማስቆጠር በሁለቱ ግቦች የተደናገጡ የሚመስሉትን የቡድኑ አባላት እና ደጋፊዎችን ተስፋ ያለመለመች ግብ ማስቆጠር ችሏል፡፡2ለ1 እየተመሩ ከመልበሻ ቤት የተመለሱት ኢትዮጵያ ቡናዎች ሁለተኛውን አጋማሽ ከመጀመሪያው በተሻለ መነሳሳት ነበር የጀመሩት። በተለይም በ50ኛው ደቂቃ አቡበከር ከመስመር ወደ ኃላ ያቀበለውን ኳስ የኃላሸት ከግቡ የቅርብ ርቀት ወደ ግብ የላከው ቢልከውም በቀላሉ በግብ ጠባቂው የተያዘበት እንዲሁም በ59ኛው ደቂቃ ኃይሌ ከግራ መስመር ያሻማውን የቅጣት ምት ወንድይፍራው አግኝቶ ወደ ግብ አቅጣጫውን ቢያስቀይራትም አቡበከር ለጥቂት ሳይደርስባት የባከነችው ኳስ ለግብ የቀረቡ አጋጣሚዎች ነበሩ፡፡በሁለተኛው አጋማሽ ከጅምሩ አንስቶ ወደ ኃላ ማፈግፈግን ምርጫቸው ያደረጉት ደቡብ ፖሊሶች ለተጋጣሚያቸው ጥቃት ተጋልጠዋል። ነገር ግን በከፍተኛ ጫና ውስጥ ሆነው ሲጫወቱ የነበሩት የኢትዮጵያ ቡና ተጫዋቾች ይህን ጫና ለመቋቋም እንደተቸገሩ በሚያሳብቅ መልኩ በተቃራኒ የግብ ክልል ሲቃረቡ የሚሰጡት ደካማ ውሳኔ አሰጣጥ ጨዋታውን ይበልጥ አክብዶባቸዋል፡ የኃላሸት ፍቃዱ ፣ ቃልኪዳን ዘላለም እና ፍፁም ጥላሁንም ያገኟቸውን የግብ ዕድሎች ሳይጠቀሙባቸው ቀርተዋል፡፡በመጨረሻዎቹ 15 ደቂቃዎች በተለይ የደቡብ ፖሊስ ተጫዋቾች በተደጋጋሚ እየወደቁ ሰዓት ለማባከን ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል። እስከመጨረሻው ደቂቃ ግብ ለማግኘት ጥረት ያደረጉት ቡናዎች በ91ኛው ደቂቃ ተቀይሮ ወደ ሜዳ የገባው ቃልኪዳን ዘላለም ከደቡብ ፖሊስ የግብ ክልል ጠርዝ ላይ በቀጥታ ወደ ግብ የላከው ኳስ የግቡ አግዳሚ ሊመልስበት ችሏል፡፡ ጨዋታው በደቡብ ፖሊሶች የ2ለ1 የበላይነት መጠናቀቁን ተከትሎ ኢትዮጵያ ቡና ለሦስተኛ ተከታታይ ጨዋታ ሽንፈት ሲያስተናግድ በአንጻሩ ላለመውረድ እየታገሉ የሚገኙት ደቡብ ፖሊሶች የዓመቱ ሁለተኛ ድላቸውን አስመዝግበዋል፡፡
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/44303
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
be8c5902f5c50a18c5ee17f8ee2d9d23
7190935c7e0be760f062ad31ece27c6d
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ለሌሎች አፍሪካ ሐገራት አስተማሪ ነው ተባለ
በህዝቦች ተሳትፎ እየተገነባ ያለው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ለሌሎች አፍሪካ ሐገራት አስተማሪ መሆኑን ከዙባቤዌ፣ ሞዛምቢክ እና ዴሞክራቲክ ኮንጐ የመጡ ልዑካን ቡድኖች አስታወቁ፡፡ኢትዮጵያ እየገነባች ያለችው ታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ በህዝቦች ተሳትፎ መሆኑ የሚያኮራና የሚያስመሰግን መሆኑን ለልምድ ልውውጥ ከዙምባብዌ፣ ሞዛምቢክ እና ዴሞክራቲክ ኮንጐ የመጡት ልዑካኖች አሳውቀዋል፡፡ከዴሞክራቲክ ኮንጐ የመጡ ሙዙንጉ ዲያከሎ እንዳሉት ከግንባታው ግዙፍነት አንጻር ህዝቡ በዚህ ስራ ግንባታ ድጋፍ ተሳታፊ መሆኑ የባለቤትነት ስሜት የሚፈጥርና አስተማማኝ የፋይናንስ አቅም መሆኑን ተረድቻለሁ፡፡ እዚህ ባየሁት ነገር ለሌሎች አፍሪካ ሃገራት ታላቅ ሃገራዊ ብሮጀክት የህዝቦች ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ማሳያ ነው፡፡የዚምባቤው የሃይልና የልማት ሚኒስቴር የሆኑት ኢ/ር ቤንሰን ኚያራቲ እንዳሉት ይህንን መሰል ታላላቅ ኘሮጀክት በአፍሪካውያን መገንባት እንደማይችል ነበረ የሚታሰበው፡፡ ነገር ግን እዚህ በኢትዮጵያ የተመለከትነው ነገር እጅግ በጣም ተገርሜያለሁ፡፡ አፍሪካውያን ከተባበርን ታላላቅ ኘሮጀክቶችን ለራሳችን አቅም መገንባት እንደምንችል መውሰድ ችያለሁ ብለዋል፡፡የዛምቢያው የሃይል ሚኒስትር በበኩላቸው እዚህ የመጣነው ኢትዮጵያ የሃይል ማመንጫ ግድቧን እንዴት እየገነባች እንዳለ ለማየትና እኛም ለመገንባት ላሰብነው የሃይል ማመንጫ ግድብ ልምድ ለመውሰድ ሲሆን በተለይ የግንባታው ወጪ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ ድጋፍ መሆኑ ለኛ እጅግ በጣም ጠቃሚ ልምድ ነው፡፡ በዚህ ስራ የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ የወሰዱት ቁርጠኛ ተግባር እጅግ በጣም የሚያስደንቅ ነው ብለዋል፡፡የልዑካን ቡድኑ ከኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ ለተደረገላቸው አቀባበል አመስግነው ጉብኝታቸውን አጠናቀው ተመልሰዋል፡፡ መረጃው የታላቁ ህዳሴ ግድብ ህ/ተ/አስተባባሪ ብ/ም/ቤት ፅ/ቤት ነው፡፡
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=578
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
8c77fcfc45f2c1654a28dc0a87987261
e2e12b57187045c7b2e2a772a552e7ca
የጥላቻ ንግግር ረቂቅ ዐዋጅና የመብት ተቋማት ስጋት
የረቂቅ ዐዋጁ አቀራረፅና የቋንቋ አጠቃቀሙ ለትርጉም ክፍት የሆኑ ዓረፍተ ነገሮች በማካተቱ ሐሳብን በመግለፅ ነፃነት ላይ ገደብ ሊጥል ይችላል በማለት በአገር ውስጥ የሚገኙ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶችም ስጋታቸውን አጋርተዋል።የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በበኩሉ ዐዋጁ ዜጎችን ከጥቃት ለመታደግ ታሳቢ ተደርጎ የተረቀቀና አስፈላጊ ነው ብሏል።(ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/5217169.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
69c5046fdd68af3f11696ffc1b918f62
bd4f10c0616685f99b1c9c8bbc5160b4
የካፍ አፍሪካ ዋንጫ ምርጥ 11
ቻምፒዮኗ ካሜሮን ሶስት ተጫዋቾችን በምርፅ 11 ውስጥ ማስመረጥ ስትችል ጋና፣ ግብፅ እና ቡርኪናፋሶ እያንዳንዳቸው ሁለት ሁለት ተጫዋቾችን ማስመረጥ ችለዋል፡፡ ሴኔጋል እና ዲ.ሪ. ኮንጎ አንድ ተጫዋች በምርጥ 11 ውስጥ ማካተት የቻሉ ሃገራት ናቸው፡፡ አፍሪካ ዋንጫው ኮከብ ተጫዋች ተብሎ የተመረጠው የ22 ዓመቱ የካሜሮን አጥቂ ክሪስቲያን ባሶጎግ በፊት መሰምር ተሰላፊነት ተመርጧል፡፡ ባሶጎግ ለሃገሩ ብሄራዊ ቡድን የተጠራው በቅርቡ ነው፡፡ ፈጣኑ አጥቂ ለሃገሩ የዋንጫ የተሳካ ጉዞ ቁልፍ ሚና ነበረው፡፡ ያለው ጉልበት እና ፍጥነት የተጋጣሚ ተከላካዮችን የሚረብሸው ባሶጎግ በፍፃሜው ጨዋታ የግብፁን አንጋፋ የመስመር ተከላካይ አህመድ ፋቲን ሲያስቸግር አምሽቷል፡፡ ምንም እንኳን ያስቆጠረው የግብ መጠን አንድ ብቻ ቢሆንም ያሳየው ድንቅ እንቅስቃሴ የብዙዎችን ቀልብ ስቧል፡፡የማይበገሩት አንበሶቹ የተቆጠረባቸው የግብ መጠን ሶስት ብቻ ነው፡፡ ለዚህም ቁልፍ ሚናን የተወጡት ግብ ጠባቂው ፋብሪስ ኦንዶ እና ሚካኤል ንጋጅዌ ናቸው፡፡ የቡርኪናፋሶዎቹ በርትራንድ ትራኦሬ እና ቻርለስ ካቦሬ በስብስቡ ውስጥ መካተት የቻሉ ሌሎች ተጫዋቾች ናቸው፡፡ ትራኦሬ ፈረሰኞቹ እስከፍፃሜ ግማሽ ባደረጉት ያልተጠበቀ ግስጋሴ ቁልፍ ነበር፡፡ አንጋፋው አማካይ ካቦሬ ለፓውሎ ዱራቴው ቡድን ጥንካሬን ሲፈጥር አስፈላጊ የሆነውን የመሪነት ግዴታውን በብቃት መወጣት ችሏል፡፡ጋና ምንም እንኳን የ35 ዓመት የመታትን አፍሪካ ዋንጫ ድርቅ ባታስቆምም ዳንኤል አማርቴ እና ክሪስቲያን አትሱ በግላቸው መልካም እንቅስቃሴ አሳይተዋል፡፡ አማርቴ ለአቭራም ግራንት ቡድን የተከላካይ ክፍል የተሻለ ግልጋሎትን ሲሰጥ ፈጣኑ አትሱ በመስመር ያደርግ የነበረው እንቅስቃሴ ጥሩ ነበር፡፡ ጋና በመከላከሉ ረገድ እንደጆናታን ሜንሳህ እና ጆን ቦይ ያሉት ተጫዋቾችን ብትይዝም አንዳቸውም የአማርቴ ያህል አልጠቀሟትም፡፡ ጆን ቦይ ይባስ በአፍሪካ ዋንጫው ብቃቱ ከመቼውም ግዜ በላይ ወርዶ ታይቷል፡፡የግብፆቹ አህመድ ሄጋዚ እና መሃመድ ሳላህ ፈርኦኖቹን በሚገባ ያገለገሉ ተጫዋቾች ናቸው፡፡ ሄጋዚ ወደ አል አሃሊ ከተመለሰ ወዲህ በድንቅ አቋሙ ፀንቷል፡፡ ቡድኑ በእዱ ዙሪያ የተገነባ እንደሆነ የሚነገርለት ሳላህ ግብ ከማስቆጠር ባለፈ የግብፅ የመልሶ ማጥቃት ዋነኛ መሳሪያ ነበር፡፡ ሳላህ ግብ የሆኑ ሁለት ኳሶችን አመቻችቶ ማቀበል ችሏል፡፡የዲ.ሪ. ኮንጎው ጁኒየር ካባናንጋ ካሎንጂ የአፍሪካ ዋንጫው ኮከብ ግብ አግቢ ሆኗ ተመርጧል፡፡ ሶስት ግቦችን በአራት ጨዋታዎች ያስቆጠረው ካባናንጋ በምርጥ 11 ውስጥ ሊካተት ችሏል፡፡ የነብሮቹ የአፍሪካ ዋንጫ ጉዞ በጋና ሩብ ፍፃሜ ላይ ቢሰናከልም የካባናንጋን ያህል ግብ ያስቆጠር ተጫዋች በአፍሪካ ዋንጫው የለም፡፡ ካባናንጋ ግብ ማስቆጠሩ በተረፈ ከቡድን አጋሮቹ ጋር ያሳዩት የነበረው የደስታ አገላለፅ ጭፈራ በብዙዎች ተወዷል፡፡ (የኮንጎ ተጫዋቾች ፊምቡ የተባለውን ጭፈራ በተደጋጋሚ በምድብ ጨዋታዎች ላይ አስመልክተውናል፡፡)ብዙዎች ለዋንጫው ገምተዋት ሳይጠበቅ በካሜሮን ተሸንፋ ከውድድር የወጣችው ሴኔጋል ተከላካዩን ሞዶ ካራ ምቦጂ በምርጥ 11 ውስጥ ማካታት ችላለች፡፡ ካራ የተከላካይ ክፍሉን በሚገባ ከመምራቱ ባሻገር ቱኒዚያ ላይ ግብ ማስቆጠር ችሏል፡፡ ኮከብ ተጫዋች፡ ክሪስቲያን ባሶጎግ (ካሜሮን)ኮከብ ግብ አግቢ፡ ጁኒየር ካባናንጋ (ዲ.ሪ. ኮንጎ) በ3 ግቦችየፀባይ ዋንጫ አሸናፊ፡ ግብፅየካፍ የአፍሪካ ዋንጫ ምርጥ 11 ፋብሪስ ኦንዶ (ካሜሮን)ሞዶ ካራ ምቦጂ (ሴኔጋል) አህመድ ሄጋዚ (ግብፅ) ሚካኤል ንጋጅዌ (ካሜሮን) በርትራንድ ትራኦሬ (ቡርኪናፋሶ) ዳንኤል አማርቴ (ጋና) ቻርለስ ካቦሬ (ቡርኪናፋሶ) መሃመድ ሳላህ(ግብፅ) ክሪስቲያን አትሱ (ጋና) ክሪስቲያን ባሶጎግ (ካሜሮን) ጁኒየር ካባናንጋ (ዲ.ሪ. ኮንጎ)
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/25139
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
75483e5ad585d84c5f6091058da73afe
1cb4a0d1cc8fa2111a998e9ec837297a
ሞቃዲሾ በደረሰ የቦምብ ፍንዳታ የሃያ ሰዎች ህይወት አለፈ
ዛሬ የተካሄደው ጥቃት፣ ሕዝብ በሚበዛበት በአንድ የሞቃዲሾ አውራ መንገድ ላይ ሁለት ተሽከርካሪዎች የቦምብ ፍንዳታ ባደረሱ ማግስት ነው።በነውጠኞችና በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች መካከል በተካሄደው ጥቃት፣ ከሞቱት በተጨማሪ፣አርባ ሰዎች መቁሰላቸውም ታውቋል።ከአል ቃዒዳ ጋር የሚሰራው አል ሻባብ ለጥቃቱ ኃላፊነት መውሰዱም ተገልጧል። አንድ የአል ሻባብ ቃል አቀባይ ለሮይተርስ ዜና አውታር በሰጠው ቃል፣ ቡድኑ ማካ አልሙካራማህ ሆቴልን መቆጣጠሩን ገልፃል። ቃል አቀባዩ አበዲሲሲ አቡ ሙሳብ በሰጠው ገለፃ፣ የመንግሥት ኃይሎች ወደ ሆቴሉ ለመግባት ሦስት ጊዜ ሞክረው ተዋጊዎቹ እንዳላስገቧቸውና አሁንም በቡድኑ ቁጥጥር ሥር እንደሚገኝ አመልክቷል።
4ዓለም አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/somalia-attack-3-1-2019/4809444.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
bf24f54863ccbde743bd210d122ea216
84bb04e6392d1b40b1a048d01fc4704e
በመስቀል አደባባይ ፍንዳታ በተጠረጠሩ ታሳሪዎች ላይ የ11 ቀናት ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ ተፈቀደ
ሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም. ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ወደ ሥልጣን በመጡ በአጭር ጊዜ ውስጥ ላስመዘገቡት ለውጥ የምስጋናና የድጋፍ ሰልፍ ለማድረግ መስቀል አደባባይ በወጡ ሰልፈኞች ላይ በተፈጸመ የቦምብ ጥቃት፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ካሳን ጨምሮ ሌሎች ኃላፊነታቸውን ባለመወጣት የተጠረጠሩ ታሳሪዎች ላይ ፍርድ ቤት የ11 ቀን የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ፈቀደ፡፡ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ለፍርድ ቤቱ በሰጡት አስተያየት ‹‹ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ ጥፋተኛ እንዳልሆንኩ ሲያውቁ ይቅርታ ይጠይቁኛል፤›› ሲሉም ተናግረዋል፡፡ፍርድ ቤቱ ለሐምሌ 13 ቀን 2010 ዓ.ም. ቀጥሯል፡፡
5ፖለቲካ
https://www.ethiopianreporter.com/article/11676
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
eacb17973ecf8fabfaad104d80600525
b94eeb5b4bd0702c986d6ed85df02cb6
ኢትዮጵያን ፕሮፌሽናል ፉትቦለርስ አሶሴሽን ጋዜጣዊ መግለጫ ጠርቷል
የፌዴሬሽኑ ቴክኒክ ዲፓርትመት እያዘጋጀው ባለው ስልጠና አስመልክቶ እየቀረቡ ባሉ አቤቱታዎች ዙርያ ፕሮፌሽናል ፉትቦለርስ አሶሴሽን ጋዜጣዊ መግለጫ ጠርቷል።ምስረታውን ካደረገበት ወቅት ጀምሮ ለተጫዋቾች እና አሰልጣኞች መብት ከመታገል በተጓዳኝ የተለያዩ የሙያ ማሻሻያ ስልጠናዎች ከፌዴሬሽኑ ጋር በመተባበር እያዘጋጀ የሚገኘው ማኅበሩ የፌዴሬሽኑ የቴክኒክ ዲፓርትመት በተለያዩ ጊዜያት ተዘጋጅተው እየቀረቡ ባሉ ስልጠናዎች ዙርያ አባላቶቼ ቅሬታዎችን እያቀረቡ ነው በማለት ጋዜጣዊ መግለጫ ጠርቷል።ማክሰኞ የካቲት 24 ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት በዋቢ ሸበሌ ሆቴል በተጠራው በዚህ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ዝርዝር ሀሳቦች ይቀርቡበታል ተብሎ ይጠበቃል።
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/56721
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
7fb12f5cc140e46e8a2370ccf6c78934
3c1c924a8ad874e66e22e7e8e2dcbc35
የናይሮቢው ብሉ ኢኮኖሚ ኮንፍረንስ
በውሃ ሀብት አጠቃቀም ላይ የሚያተኩረውና በናይሮቢ ለአለፉት ሦስት ቀናት ሲደረግ የነበረው ብሉ ኢኮኖሚ ኮንፍረንስ ዛሬ ተጠናቋል። በኮንፍረንሱ ላይ ከ184 ሀገራት የተወጣጡ ዲፕሎማቶችና የመንግሥት ኃላፊዎች እንደተሳተፉበት የዝግጅቱ አስተባባሪርዎች ገልፀዋል።ኢትዮጵያም በኮንፍረንሱ ላይ ያላትን ልምድ ለተሳታፊዎች እንዳጋራች በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ለአሜርካ ድምፅ ገልፀዋል።
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/blue-economy-conf-kenya-11-28-2018/4678614.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
112fd9953aed08767789ca1444e4cda8
a337380c4743026164771268b4ae44e6
የካናዳው ጠቅላይ ሚንስትር ጀስቲን ትሩዶ ወጣት ሳሉ ምን ያህል ጊዜ ፊታቸውን ጥቁር ቀለም እንደተቀቡ እንደማያስታውሱ መግለጻቸው እያነጋገረ ነው።
"ምን ያህል ጊዜ ጥቁር ቀለም እንደተቀባሁ አላስታውስም" የካናዳው ጠቅላይ ሚንስትር ጀስቲን ትሩዶ\nጀስቲን ትሩዶ ፊታቸውን ጥቁር ቀለም ተቀብተው የሚያሳዩ ፎቶግራፎች ጠቅላይ ሚንስትሩ ከዓመታት በፊት በአንድ የግል ትምህርት ቤት ድግስ ላይ ፊታቸውን እና እጃቸውን ጥቁር ቀለም ተቀብተው የሚያሳይ ፎቶግራፍ ይፋ ከተደረገ በኋላ በርካቶች እየወቀሷቸው ይገኛሉ። ይህ ፎቶ ይፋ መደረጉን ተከትሎ፤ ጠቅላይ ሚንስትሩ ጥቁር ቀለም ተቀብተው የሚያሳዩ ሌሎች ፎቶግራፎችም እየወጡ ነው። • የካናዳው ጠቅላይ ሚንስትር ጀስቲን ትሩዶ በዘረኛ ፎቶግራፋቸው እየተተቹ ነው • ሴቶችን እያነቀ የገደለው ኮሪያዊ ከ30 ዓመታት በኋላ ተገኘ • "ዛሚ አልተሸጠም፤ በትብብር እየሠራን ነው" ጋዜጠኛ ሚሚ ስብሃቱ በግል ትምህርት ቤት ድግስ ላይ ጥቁር ቀለም ተቀብተው የተነሱት ፎቶግራፍ ለሕዝብ ይፋ መሆኑን ተከትሎ፤ ጋዜጠኞች ጠቅላይ ሚንስትሩ ሌሎች ተመሳሳይ ፎቶዎች ተነስተው እንደሆነ ጠይቀዋቸው ነበር። ጀስቲን ከዛ ፎቶ ውጪ፤ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሳሉ በተሰጥኦ ውድድር ላይ ጥቁር ቀለም መቀባታቸውን ተናግረው ነበር። ከነዚህ ውጪ በሌላ ወቅት ተመሳሳይ ድርጊት ስለመፈጸማቸው አልተናገሩም ነበር። አሁን ተጨማሪ ቪድዮና ፎቶ ሲወጣ፤ ምን ያህል ጊዜ ጥቁር ቀለም እንደተቀቡ እንደማያስታውሱ ገልጸዋል። የፊታችን ጥቅምት ካናዳ አገራዊ ምርጫ ታካሂዳለች። ለሁለተኛ ጊዜ ጠቅላይ ሚንስትር ለመሆን ቅስቀሳ እያደረጉ ያሉት ጀስቲን በዘረኛ ፎቶዎቻቸው ምክንያት አጣብቂኝ ውስጥ ገብተዋል። ጠቅላይ ሚንስትሩ ራሳቸውን ይሥሉ የነበረው የማኅበራዊ ፍትህ አቀንቃኝ፣ ተራማጅና ልዩነትን የሚያከብሩ እንደሆኑ ነበር። ሆኖም ለሕዝብ ይፋ የተደረጉት ፎቶዎች የጀስቲንን ገጽታ እንዳጠለሹት ተገልጿል። እንደ ጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጠር በ1990ዎቹ፤ ጠቅላይ ሚንስትሩ ነጭ ካናቴራ ለብሰው፣ ፊታቸውን እና ክንዳቸውን ጥቁር ቀለም (ሜክ-አፕ) ተቀብተው የሚያሳይ ቪድዮ ተለቋል። በቪድዮው ላይ ጀስቲን እጃቸውን እያወናጨፉ ምላሳቸውን ሲያወጡ ይታያል። ይህ ቪድዮ የተቀረጸው ጠቅላይ ሚንስትሩ በ20ዎቹ መጀመሪያ ላይ ሳሉ ነበር። የግል ትምህርት ቤት ድግስ ላይ ጥቁር ቀለም ተቀብተው የተነሱት ፎቶ የተወሰደው በ29 ዓመታቸው ነበር። ጠቅላይ ሚንስትሩ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተሰጥኦ ውድድር ላይ ጥቁር ቀለም ተቀብተውም ዘፍነዋል። ጀስቲን፤ "ማድረግ የማይገባኝን አድርጌ ብዙዎችን አስቀይሜያለሁ" ብለው ይቅርታ ጠይቀዋል። የአገሪቱ መከላከያ ሚንስትር ሀሪጂት ሳጃን፤ ጠቅላይ ሚንስትሩ ስህተት መሥራታቸውን ለካናዳ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚንስትሩ ልዩነትን የሚያከብር ፓሊሲ እንዳላቸው ሳይጠቅሱ ግን አላለፉም። የተቀናቃኙ 'ኮንሰርቫቲቭ' (ወግ አጥባቂ) ፓርቲ መሪ አንድሪው ሺር የጠቅላይ ሚንስትሩን 'ይቅርታ' አጣጥለው "ይቅርታው የውሸት ነው" ብለዋል።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
b0467f4efe093aa7aae46d828bbe52b4
ae1203b2ce22e2a7e4179afddea6e0a4
የአፍሪካ ህብረት በናይጄሪያ ተቃዋሚዎች ላይ የደረሰውን ጥቃት አወገዘ
የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ በአገሪቱ ውሰጥ ላሉ የፖለቲካና ማህበራዊ ባለድርሻ አካላት "ሰብዓዊ መብት እንዲጠበቅና ሕግም እንዲከበር" የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። ህጋዊ ባልሆነ መንገድ ሰዎችን በማሰር፣ በማሰቃየትና ግድያም ይፈፅማል በሚል ከፍተኛ ውግዘት እየቀረበበት ያለውና ዘረፋን ለማስቆም የተመሰረተው ልዩ የፌደራል ፖሊስ ኃይል ወይም ሳርስ እንዲበተን ጠይቀዋል ። ከዚህም በተጨማሪ ወንጀል ፈፅመዋል ተብለዋል የሚባሉ የፖሊስ አባላትም ምርመራ እንዲከፈትባቸውና ወደ ፍርድ እንዲቀርቡም አሳሳስበዋል። ናይጄሪያ አባል የሆነችበትና አስራ አምስት አባላት ያሉት የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ማህበረሰብ (ኢኮዋስ) በበኩሉ ተቃዋሚዎችና የናይጄሪያ መንግሥት በውይይት ሊፈቱት ይገባል ብሏል። ኢኮዋስ ተቃውሞው በቀጠለበት በአሁኑ ወቅት ሁለቱም አካላት ኃይል መጠቀም እንደማይገባቸው አሳውቋል። "ተቃዋሚዎቹ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ሰልፋቸውን እንዲያካሂዱና የናይጄሪያም የፀጥታ ኃይሎች ሰልፈኞቹ ላይ ኃይልን ከመጠቀም እንዲታቀቡ ጥሪያችንን እናቀርባለን" ይላል ኢኮዋስ ያወጣው መግለጫ በናይጄሪያ የፖሊስን የጭካኔ በትር ተማርረው የወጡ ተቃዋሚዎች ጎዳና ላይ መውጣታቸውን ተከትሎ በፀጥታ ኃይሎች የተገደሉ ሰዎችን አስመልክቶ የአፍሪካ ህብረትም ሆነ ኢኮዋስ ዝምታን መርጠዋል ተብለው ተተችተዋል። የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት አምነስቲ ማክሰኞ እለት፣ ጥቅምት 10/ 2013 በንግድ ማዕከሏ ሌጎስ በፀጥታ ኃይሎች የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 12 መድረሱን አሳውቋል። የናይጄሪያ ጦር በበኩሉ ሪፖርቱ ሃሰተኛ ዜና ነው በማለት አጣጥሎታል። ከፍተኛ ተቃውሞ የቀረበበት ሳርስ እንዲበተን ቢደረግም የሳርስ አባላት በሌሎች የፖሊስ ክፍሎች እየተሰማሩና እየተመደቡ ነው የሚሉ ጉዳዮች መሰማታቸውን ተከትሎም እንደገና ተቃውሞቹ የቀጠሉት። ሰልፈኞቹ እነዚህ የሳርስ አባላት ለፈፀሙት ወንጀል ህግ ፊት መቅረብ አለባቸውም እያሉ ነው። ከሰሞኑ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት "ስር ነቀል" የፖሊስ ማሻሻያ እንደሚደረግና የሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈፅመዋል የተባሉትም የሳርስ አባላት ወደ ፍርድ ይቀርባሉ ብለው ነበር።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
6acb5f5607df5c9ff2bed8c547ec1678
37f448424f4eae55e0cd5d9d3384f676
የሌ/ጄነራል መሐመድ ሃምዳን ደገሎ የኢትዮጵያ ጉብኝት ምን አንደምታ ይኖረዋል?
የሱዳን ብሔራዊ የሽግግር ም/ቤት ምክትል ፕሬዘዳንቱ ሌተናል ጄነራል መሐመድ ሃምዳን ደገሎ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለመምከር ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡ ብሔራዊ የሽግግር ም/ቤት ምክትል ፕሬዘዳንቱ አዲስ አበባ ሲገቡ በምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ደመቀ መኮንን ፣ በውጭ ጉዳይ ሚንስትር ገዱ አንዳርጋቸውና በጄነራል አደም መሐመድ አቀባበል እንደተደረገላቸው የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል፡፡ ሌተናል ጄነራል መሐመድ ሃምዳን ደገሎ በቆይታቸው ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በሁለቱ ሀገራት ግንኙነትና በወቅተዊ ጉዳዮች ዙሪያ ይመክራሉ። ሌተናል ጄነራል መሐመድ ሃምዳን ደገሎ በሱዳን የፖለቲካ ሽግግር ዉስጥ ከፍተኛ ተጽዕኖ ካላቸው ሰዎች መካከል ይጠቀሳሉ፡፡ በኢትዮጵያ ጉብኝት ሲያደርጉም የአሁኑ የመጀመሪያቸው ነው፡፡ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ በሱዳን አነሳሽነት የሶስትዮሽ ድርድሩ ዳግም ከቀጠለ ከ6ኛ ቀን በኋላ ነው ሌተናል ጄነራል መሐመድ ሃምዳን ደገሎ ወደ ኢትዮጵያ የመጡት፡፡ እስካሁን በኢትዮጵያ ፣ ግብፅ እና ሱዳን መካከል እየተደረገ በለው ድርድር በአንዳንድ ቴክኒካዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግባባት ቢኖርም በህጋዊ ጉዳዮች ዙሪያ ግን አሁንም መግባባት ላይ አልተደረሰም፡፡ ከዚህም ባለፈ ግብፅ እና ኢትዮጵያ ስምምነት ላለመደረሱ አንደኛቸው ሌላኛቸው ተጠያቂ በማድረግ እርስ በእርስ ወነጃጀላቸውን ቀጥለዋል፡፡የግብፅ ዉጭ ጉዳይ ሚኒስትቴር ትናንት ባወጣው መግለጫ “ኢትዮጵያ ግትር አቋም በመያዟ የእስካሁኑ ድርድር ፍሬ አልባ ነው” ያለ ሲሆን ሀገሪቱ ከግድቡ ጋር በተያያዘ ሌሎች አማራጮችን ለመፈልግ መገደዷን አስታውቋል፡፡ ከነዚህም አንዱ ጉዳዩን ወደ ተባበሩት መንግስታት የጸጥታው ምክር ቤት መውሰድ መሆኑን ነው የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሳሚ ሽኩሪ የገለጹት፡፡ የኢትዮጵያ ዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ደግሞ ትናንት በሰጡት መግለጫ ግብፅ የመደራደር ልባዊ ፍላጎት እንደሌላት ገልጸዋል፡፡ ሚኒስትሩ ይሄን ሲያስረዱ “ግብፅ አንድ እግሯን ኒውዮርክ (የተመድ የጸጥታው ም/ቤት) ፣ አንድ እግሯን ደግሞ ድርድሩ ላይ አድርጋ መቀጠሏ በድርድሩ ስምምነት ላይ የመድረስ ፍላጎት የሌላት መሆኑን የሚያሳይ ነው” ብለዋል፡፡ የግብፅ ተደራዳሪዎች ራሳቸው በሚፈልጉት መልኩ ብቻ ስምምነት እንዲደረስ ግትር አቋም እንደያዙም አቶ ገዱ ተናግረዋል፡፡ ድርድሩ እየተካሄደ ባለበት በአሁኑ ጊዜ ዓለም አቀፍ ማህበረሰብን ለማደናገር እና በኢትዮጵያ ላይ ከፍተኛ ጫና ለማሰደር የሚደረግ ማንኛውም ዘመቻ ወይም ኢትዮጵያ ያልተካተተችበትን በቅኝ ግዛት ላይ የተመሰረቱ ስምምነቶችን እንድትቀበል በኢትዮጵያ ላይ ከፍተኛ ጫና ለማሳደር የሚደረግ ሙከራ ተቀባይነት የለውም ሲል የኢፌዴሪ የውሃ ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሰሞኑን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ግብፅ ግድቡ ከአባይ ወንዝ የማገኘውን የዉሃ መጠን ይቀንስብኛል፤ ይሔም ኢኮኖሚያዊ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ቀውስ ያስከትልብኛል የሚል እምነት ሲኖራት ኢትዮጵያ ደግሞ ግብፅና ሱዳን ላይ ጉልህ ጉዳት በማያደርስ መልኩ የተፈጥሮ ሀብቴን እጠቀማለሁ የሚል ጽኑ አቋም ይዛ ግድቡን መገንባቷን ቀጥላለች፡፡ ምንም እንኳን ግብፅ ስምምነት ሳይደረስ የዉሃ ሙሌት መጀመር የለበትም የሚል አቋም ብትይዝም ፣ ከሳምንታት በኋላ ግድቡን ዉሃ ለመሙላት በኢትዮጵያ በኩል ዝግጅት እየተደረገ ነው፡፡ የህዳሴ ግድብ ውሃ የሚያርፍበት ቦታ የደን ምንጣሮ ለማካሔድ በነገው እለት ከ45 ኢንተርፕራይዞች ጋር የቦታ ርክክብ እንደሚፈጸም የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ገልጿል፡፡ የክልሉ የስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ በሽር አብዱራሂም ፣ የህዳሴው ግድብ የመጀመሪያውን ሃይል ማመንጨት የሚያስችለው ውሃ የሚተኛበትን ቦታ ለማመቻቸት የደን ምንጣሮ ለማካሄድ ዝግጅት መጠናቀቁን እና በሚቀጥለው ሳምንት የደን ምንጣሮው እንደሚጀመር ለኢዜአ ተናግረዋል። የምንጣሮ ስራው በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ ሌሎች 25 ኢንተርፕራይዞች በተጠባባቂነት መመዝገባቸውንም ዳይሬክተሩ አብራርተዋል፡፡ ከግድቡ ጋር በተያያዘ በኢትዮጵያ እና በግብፅ መካከል ያለው ፖለቲካዊ ዉጥረት እየተካረረ ባለበት በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ እና ሱዳን ድርድሩ እንዲቀጥል በጠቅላይ ሚኒስትሮቻቸው ዉይይት መስማማታቸውን ተከትሎ ነው ድርድሩ በድጋሚ መካሔድ የጀመረው፡፡ ይሁንና በግብፅ እና በኢትዮጵያ አለመግባባት ምክንያት ድርድሩ ፈተና ላይ እየወደቀ መሆኑ የሱዳን ብሔራዊ የሽግግር ም/ቤት ም/ል ፕሬዘዳንት ሌተናል ጄነራል መሐመድ ሃምዳን ደገሎ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለመምከር ወደ ኢትዮጵያ የመምጣታቸው አንዱ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ይገመታል፡፡ ሌተናል ጄነራል መሐመድ ሃምዳን ደገሎ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ሊወያዩ ከሚችሉባቸው ሌሎች ጉዳዮች መካከል በኢትዮጵያና ሱዳን ድንበር አካባቢ ከሳምንታት በፊት የተፈጠረውን ግጭት የተመለከተ እንደሚሆን ነው የሚጠበቀው፡፡ በወቅቱ የተፈጠረው ግጭት ከዚህ ቀደምም የነበረ እና ሁለቱን ሀገራት ለጦርነት የማይጋብዝ በውይይት የሚፈታ ጉዳይ መሆኑን የሁለቱም ሀገራት ጠቅላይ ሚኒስትሮች መግለጻቸው ይታወቃል፡፡
5ፖለቲካ
https://am.al-ain.com/article/let-gen-mohammed-hamdan-dagalo-deputy-chairman-of-the-transitional-military-council-of-sudan-arrives-in-addis-ababa
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
3bf434019c90ec3c3f7ac22a1ccd83d8
e8ac9dbd0c3104623936794f9161f066
በኮንሶ ጥቃትና ግጭት 66 ሰዎች ተገደሉ
 ከ130 ሺህ በላይ ተፈናቅለዋል በቅርቡ በኮንሶ ዞንና አጎራባቾች በተከሰተው ግጭትና የታጣቂዎች ጥቃት 66 ሰዎች መገደላቸውንና 39 መቁሰላቸውን ያመለከተው የደቡብ ክልል የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሪፖርት፤ ከ130 ሺ በላይ ሰዎች መገደላቸውንም ጠቁሟል።ጥቃቱ በኮንሶ ዞን፣ አማሮ፣ ደራሼና አሌ ወረዳዎችን ያካለለ ሲሆን በድርጊቱ  ተሳታፊ ናቸው የተባሉ 137 ተጠርጣሪዎች በክልሉ የፀጥታ ሃይሎች መያዛቸውም ተመልክቷል።በአካባቢው በሚገኙ 17 ቀበሌዎች የተዳረሰው ይህ ግጭትና ጥቃት በበርካታ ሺህ የሚቆጠሩ መኖሪያ ቤቶችና የመንግስትና ግለሰቦቹ ሃብት የወደመበት መሆኑም ሪፖርቱ ይጠቁማል። በአሁኑ ወቅት የክልሉ መንግስት 4 አባላት ያሉት የህግ ምርመራ ቡድን ወደ አካባቢው አምርቶ ተጨማሪ ምርመራዎችን እያደረገ መሆኑንም አስረድቷል- የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ።በአካባቢው በዋናነት ጥቃቱን እየፈጸመ ያለው በህወሃት ሲደገፍ የቆየው የኦነግ- ሸኔ ታጣቂ ቡድን መሆኑንም ታውቋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የኮንሶ ዞንም ሆነ አጎራባች አካባቢዎች፣ ለሁለት ሳምንታት ከዘለቀው ግጭትና ጥቃት ወጥተው ወደ መደበኛ ሰላማዊ እንቅስቃሴ እየተመለሱ መሆኑንም ቢሮው አስታውቋል። ከየአካባቢዎቹ ለተፈናቀሉት ወገኖች ከረድኤት ተቋማት ጋር በመተባበር አስፈላጊውን ሰብአዊ ድጋፍ ለማድረግ የክልሉ መንግስት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ቢሮው አስታውቋል።
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.addisadmassnews.com/index.php?option=com_k2&view=item&id=26840:%E1%89%A0%E1%8A%AE%E1%8A%95%E1%88%B6-%E1%8C%A5%E1%89%83%E1%89%B5%E1%8A%93-%E1%8C%8D%E1%8C%AD%E1%89%B5-66-%E1%88%B0%E1%8B%8E%E1%89%BD-%E1%89%B0%E1%8C%88%E1%8B%B0%E1%88%89&Itemid=180
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
e0aa7688d5d9dad0851f4b381613a50b
4ffc010731df3da5357ba2ac9c6eb1a7
በመዲናዋ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የንጽህና እቃዎችን ማሰባሰቢያ ማዕከል ተቋቋመ
አዲስ አበባ፣መጋቢት 10፣2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የንጽህና እቃዎችን ማሰባሰቢያ ማዕከል በመስቀል አደባባይ ተቋቁሟል።በከተማዋ ወጣቶችና በጎ ፈቃደኞች የተቋቋመው ኮሚቴ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የንጽህና እቃዎችን የማሰባሰብ ስራ ዛሬ በይፋ መጀመሩን የከንቲባ ጽህፈት ቤት አስታውቋል።ህብረተሰቡም ከነገ ጀምሮ ወደ መስቀል አደባባይ በመሄድ ማንኛውንም የንጽህና እቃ መለገስ እንደሚችል ተገልጿል።የከተማ አስተዳደሩ የንጽህና እቃዎችን መግዛት ለማይችሉ ወገኖች ህብረተሰቡ አቅሙ በፈቀደው ልክ ድጋፍ በማድረግ የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት በሚሰራው ስራ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ጥሪ አቅርቧል።
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%89%a0%e1%88%98%e1%8b%b2%e1%8a%93%e1%8b%8b-%e1%89%a0%e1%8b%9d%e1%89%85%e1%89%b0%e1%8a%9b-%e1%8b%a8%e1%8a%91%e1%88%ae-%e1%8b%b0%e1%88%a8%e1%8c%83-%e1%88%8b%e1%8b%ad-%e1%88%88%e1%88%9a%e1%8c%88/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
c398b4e99353d76910bede3d6493a531
5b69d4622e060a6cdf1b82e44b287cda
ገዳዩ ኮሮና ቫይረስ በ 12 ሀገራት መሥፋፋቱ ሥጋት ፈጥሯል፡፡
ባሕር ዳር፡- ጥር 17/2012ዓ.ም (አብመድ) ኮሮና ቫይረስ በቻይና 56 ሰዎችን ለሞት፣ 2 ሺህ ሰዎችን ደግሞ ለህመም ዳርጓል፡፡የኮሮና ቫይረስ ከቀላል እስከ ከባድ የመተንፈሻ አካል ሕመም የሚያስከትልና ለሞትም ሊዳርግ የሚችል የቫይረስ ዝርያ ነው፡፡ በሽታው በትንፋሽ፣ ባልበሰሉ ምግቦች እና በቫይረሱ ከታመሙ ሰዎች ጋር በሚደረግ ንክኪ ይተላለፋል። ትኩሳት፣ ሳል እና የአተነፋፈስ ችግር ደግሞ ምልክቶቹ ናቸው፡፡ ቫይረሱ ከቻይና ባሻገር በአሜሪካ፣ ፈረንሳይ፣ አውስትራሊያ፣ ታይላንድ፣ ጃፓን፣ ደቡብ ኮሪያ፣ ታይዋን፣ ቬትናም፣ ሲንጋፖር፣ ማሌዥያ እና በኔፓል እንደተከሰተ እየተዘገበ ነው፡፡ በሽታው በሀገራቱ የተከሰተው ደግሞ በሥራ እና በሌሎች ምክንቶች ከቻይናዋ ውሃን ቆይተው ወደ ሀገራቸው በ
4ዓለም አቀፍ ዜና
https://www.amharaweb.com/%e1%8c%88%e1%8b%b3%e1%8b%a9-%e1%8a%ae%e1%88%ae%e1%8a%93-%e1%89%ab%e1%8b%ad%e1%88%a8%e1%88%b5-%e1%89%a0-12-%e1%88%80%e1%8c%88%e1%88%ab%e1%89%b5-%e1%88%98%e1%88%a5%e1%8d%8b%e1%8d%8b%e1%89%b1-%e1%88%a5/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
e0789eecf069dc7612008cc07517b196
83f0ca4f67136ef3bb856e00a0723fcc
ሴካፋ ከ15 ዓመት በታች| ሩዋንዳ ማለፏን ስታረጋግጥ ሁለተኛው ጨዋታ ተቋርጧል
በኤርትራ አዘጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው እና ስምንተኛ ቀኑ የያዘው የሴካፋ ከ15 ዓመት በታች ዋንጫ ዛሬም ሲቀጥል ሩዋንዳ ወደ ቀጣይ ዙር ማለፏን አረጋግጣለች። የደቡብ ሱዳን እና ዩጋንዳ ጨዋታ ደግሞ ተቋርጧል።ስምንት ሰዓት ላይ የጀመረው እና ተመጣጣኝ ፉክክር ታይቶበታል የተባለው የሩዋንዳ እና የታንዛንያ ጨዋታ ሲሆን በጨዋታውም ሩዋንዳ ተጋጣሚዋን 2-1 በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፏን አረጋግጣለች።10:30 የተጀመረው የዩጋንዳ እና ደቡብ ሱዳን ጨዋታ ደግሞ እስከ ዕረፍት ዩጋንዳ አምስት ለ ባዶ እየመራች ወደ ዕረፍት ቢያመሩም ሁለተኛው አጋማሽ ተጀምሮ ብዙይ ሳይሄድ ከጨዋታው በፊት አምስት ተጫዋቾች በጉዳት ምክንያት በማጧቷ በጎዶሎ ቅያሪ ወደ ጨዋታው የገባችው ደቡብ ሱዳን በሁለተኛው አጋማሽ ተጨማሪ አምስት ተጫዋቾች በጉዳት በማጧቷ ጨዋታው በአስገዳጅ ሁኔታ ተቋርጧል፤ ዩጋንዳም የጨዋታው አሸናፊ ሆናለች። ከሩዋንዳ በመቀጠል ወደ ግማሽ ፍፃሜው የተሸጋገረች ሌላዋ ቡድንም ሆናለች።# ቡድን | ተጫ | ልዩነት | ነጥብ 1 ዩጋንዳ 3 (+10) 9 2 ሩዋንዳ 3 (+7) 9 3 ታንዛኒያ 3 (+3) 3 4 ኢትዮጵያ 3 (-6) 1 5 ደ/ሱዳን 4 (-14) 1ቀጣይ ጨዋታዎች ነገ ሲቀጥሉ በምድብ ሀ የመጨረሻ ጨዋታዎች 8:00 ላይ ብሩንዲ ከ ሱዳን፣ 10:30 ላይ ሶማሊያ ከኤርትራ ይጫወታሉ።
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/50131
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
f1f74a528c1f9826c063a8357976fcc4
81837e0413f261a2941141eea91d5038
ሪፖርት | ከጉዞ የተመለሱት ሀዋሳዎች ከቅዱስ ጊዮርጊስ አንድ ነጥብ ወስደዋል
ከትላትናው የደጋፊዎች ግጭት በኃላ ቅዱስ ጊዮርጊሶች የስታዲየሙን ጸጥታ ሁኔታ ከሚያስጠብቀው አካል ጨዋታው መቀጠልና መካሄድ የሚያስችል ማረጋገጫ ስለተሰጠን ጨዋታው መካሄድ አለበት ቢሉም በአንጻሩ ሀዋሳ ከተማዎች በተወሰኑ ደጋፊዎቻችን እንዲሁም በቡድን አባላቶቻችን ላይ ጉዳት ስለደረሰ ጨዋታውን አናካሂድም የሚል አቋም በመያዛቸው ጨዋታው ትላንት መካሄድ ሳይችል ቀርቷል። በዛሬው እለትም ሀዋሳ ከተማዎች በአቋማቸው ፀንተው ወደ ሀዋሳ ጉዞ ከጀመሩ በኃላ ከባቱ (ዝዋይ) ከተማ ዳግም ወደ አዲስ አበባ ተመልሰው ጨዋታውን አድርገዋል፡፡መካሄድ ከነበረበት ጊዜ በ23 ሰዓት ዘግይቶ ዛሬ በከፍተኛ የጸጥታ ኃይል ቁጥጥር ታጅቦ በዝግ ስታዲየም የተካሄደው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ያለግብ በአቻ ውጥት ነው የተጠናቀቀው፡፡ቅዱስ ጊዮርጊሶች በሲዳማ ቡና ከተረታው ቡድን ውስጥ ምንተስኖት አዳነ እና አሜ መሐመድን አስወጥተው በሰልሀዲን በርጌቾና በኃይሉ አሰፋ ሲተኩ በአንጻሩ ሀዋሳ ከተማዎች በሜዳቸው አዳማ ከተማን ከረታው ቡድን በገብረመስቀል ዱባለ ምትክ አክሊሉ ተፈራን ብቻ በመቀየር ጨዋታውን ጀምረዋል፡፡ ለ10 ዓመታት ቅዱስ ጊዮርጊስን ያገለገለውና ባሳለፍነው ክረምት ከክለቡ ተለያይቶ አሳዳጊ ክለቡ ሀዋሳ ከተማን የተቀላቀለው አዳነ ግርማ በቅጣት ምክንያት የቀድሞ ክለቡን መግጠም ባይችልም በስታዲየም ተገኝቶ ጨዋታውን ተከታትሏል፡፡በ4-2-3-1 የሚመስል መነሻ አሰላለፍ ጨዋታውን የጀመሩት ሀዋሳ ከተማዎች ሁለት ተፈጥሮአዊ የሆኑ የመስመር ተከላካዮችን በ10 ቁጥር ሚና ከተሰለፈው ታፈሰ ሰለሞን ግራና ቀኝ ዳንኤል ደርቤ እና ደስታ ዮሀንስን መጠቀማቸው አግራሞትን የጫረ ነበር። ይህም የቅዱስ ጊዮርጊስ ዋነኛ የፈጠራ ምንጭ የሆኑትን ሁለቱ የመስመር ተከላካዮቹ አብዱልከሪም መሐመድ እና ኄኖክ አዱኛን እንቅስቃሴ በመገደቡ ረገድ የተዋጣለት ውሳኔ ሆኖ አልፏል፡፡ሁለቱም ቡድኖች ቀጥተኛ አጨዋወትን ምርጫቸው በሚያደረጉ ሁለት ቡድኖች መካከል እንደመከናወኑ ጨዋታው እምብዛም ማራኪ የሚባል እንቅስቃሴ አልታየበትም፡፡ ቶሎ ቶሎ በሚደረጉ የረጃጅም ኳሶች ልውውጦች ታጅቦ የተካሄደው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ በተለይ በመጀመሪያው አጋማሽ በሁለቱም ቡድኖች ከፍተኛ የሆነ የኃይል አጨዋወት፣ አካላዊ ንኪኪዎችና ጉሽሚያዎች የበዙበት ነበር፡፡ሀዋሳ ከተማዎች በተሻለ የመልሶ ማጥቃት ቁመና ላይ ባይገኙም ኳስ ሲያጡ ከእስራኤል እሸቱ በስተቀር ከኳስ ኃላ በጣም ጠቅጠቅ ብለው ሲከላከሉ ተስውሏል ፤ ነገርግን ኳስ በቁጥጥራቸው ስር ስትገባ ደግሞ በተለይም በዳንኤል ደርቤ በኩል ከሚነሱ ተሻጋሪ ኳሶች አጋጣሚዎችን ለመፍጠር ጥረት አድርገዋል። በአንጻሩ ቅዱስ ጊዮርጊሶች በመጀመሪያው አጋማሽ ከሁለቱ ቡድኖች በተሻለ ምንም እንኳን ኳሶቹ ከጨዋታ ውጪ ቢባሉም በ20ኛውና በ27ኛው ደቂቃ ላይ ከአብዱልከሪም መሀመድና ከሄኖክ አዱኛ በቀጥታ የተሻገሩትን ረጃጅም ኳሶች ተጠቅሞ አቤል ያለው የሞከራቸውን ኳሶች አንዱን ተክለማርያም ሲያድንበት ሌላኛው ደግሞ ግብ ብትቆጠርም ዳኛው ሳያፀድቋት ቀርተዋል፡፡ ከነዚህ ሙከራዎች ውጭ በተለይ በ14ኛው ደቂቃ ላይ በሀይሉ አሰፋ ወደ ቀኝ ያደላውን የቅጣት ምት አሻምቶ የቅዱስ ጊዮርጊሱ ተከላካይ ፍሪምፓንግ ሜንሱ ተንሸራቶ ሳይደርስባት የቀረው ኳስ አስቆጭ አጋጣሚ ነበረች፡፡ ሀዋሳ ከተማዎች ምንም አይነት የግብ ማግባት አጋጣሚን መፍጠር ባልቻሉበት በዚሁ በመጀመሪያ አጋማሽ ከተከላካይ እንዲሁም አማካይ ስፍራ ተጫዋቾች በቀጥታ የሚጣሉ ኳሶችን ከሶስቱ የጊዮርጊስ ተጫዋቾች በማሸነፍ የግብ እድል ለመፍጠር ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል፡፡የሁለተኛው አጋማሽ እንቅስቃሴ እንደመጀመሪያው ሁሉ አሰልቺ እንቅስቃሴ የታየበት ነበር፡፡ በ66ኛው ደቂቃ ላይ አምና በአፍሪካ ቻምፒየንስ ሊግ ቅድመ ማጣሪያ ከዩጋንዳው ኬሲሲኤ ጨዋታ ወዲህ ከሜዳ ርቆ የነበረው ሰልሀዲን ሰዒድ በኃይሉ አሰፋን ተክቶ በመግባት የመጀመሪያ ጨዋታውን ማድረግ የቻለውም በዚሁ አጋማሽ ነበር፡፡ከመጀመሪያው አጋማሽ በተሻለ መሀል ሜዳ ላይ ከሶስቱ የአጥቂ ስፍራ ተጫዋቾች ፊት ላይ ተቆርጠው ከመቅረት ጋር ተዳምሮ የተወሰደባቸውን የመሐል ሜዳ የቁጥር ብልጫ ለመቅረፍ ከአንድ የሀዋሳ ከተማ አጥቂ ጋር በትይዩ ሲቆሙ ከነበሩት ሶስት የመሀል ተከላካዮች ውስጥ በተወሰነ መልኩ በሁለተኛው አጋማሽ አስቻለው ታመነ ተነጥሎ ወደ መሀል ሜዳ እየገባ ለመጫወት ነፃነት ተሰጥቶት ተስተውሏል። በ69ኛው ደቂቃ ላይ ናትናኤል ዘለቀ ከሀዋሳዎች ሳጥን ውጭ በቀጥታ ወደ ግብ የላካት ኳስ ከግቡ አግዳሚ በላይ ለጥቂት ወደ ውጭ የወጣችበት ኳስ በጨዋታው የታየችው የተሻለችው ሙከራ ነበረች፡፡በጨዋታው በግሉ ጥሩ መንቀሳቀስ የቻለው ወጣቱ አጥቂ እስራኤል እሸቱ በቀጥታ ከተከላካዮች የሚላኩለትን ኳሶች ለመጠቀም ከጊዮርጊስ ተከላካዮች ጋር ያደረገው ጥረት የሚደነቅ ነበር። በዚህ መልኩ ያገኛትን ኳስ በ64ኛው ደቂቃ ወደ ግብ የላካትና ፓትሪክ ማታሲ ያዳነበት ኳስ ጥረቱን ማሳያ ነበረች፡፡ጨዋታው 0ለ0 በሆነ ውጤት መጠናቀቁን ተከትሎ ሀዋሳ ከተማ ነጥቡን ወደ 11 በማሳደግ በመሪነቱ ቀጥሏል፡፡
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/42436
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
be385e8d0bce73b4be74e4595b2ca264
dd4b10d8b529e3c48d5322c2c3eb23a4
‹‹ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ›› በሚል ቅፅል ስም የሚታወቁት ማን ናቸው?
ጣይቱ ብጡል «ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ» በሚል ቅፅል ስም የታወቁት እቴጌ ጣይቱ ከአባታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለ ማርያም እና ከእናታቸው ወይዘሮ የውብ ዳር ነሐሴ ፲፪ ቀን ፲፰፻፴፪ዓ/ም በጌምድር ውስጥ ደብረ ታቦር ከተማ ተወለዱ። በየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓት መሠረት በተወለዱ በ ፹ ቀናቸው ጥቅምት ፳፯ ቀን ፲፰፻፴፫ ዓ/ም በደብረ ታቦር ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ክርስትና ተነሡ። እናታቸው ወይዘሮ የውብዳር ከባለቤታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለ ማርያም ከሞቱ በኋላ በጅሮንድ መዩ የተባሉትን የዓፄ ቴዎድሮስን ባለሟል አግብተው ነበር። እሳቸውም ጣይቱ ብጡል ትምህርት እንዲቀስሙ ለማድረግ ልዩ መምህር ቀጥረውላቸው እንደነበር ይታወቃል። እቴጌ ጣይቱ በማኅደረ ማርያም ሆነው ሲማሩና መፃሕፍትን ይቀጽሉ በነበሩበት ጊዜ ለቤተክርስቲያን መጋረጃ መሥሪያ በትርፍ ጊዜያቸው ፈትል እየፈተሉ ያቀርቡ ነበር። በበገና ቅኝትና ድርደራም በኩል የታወቁ ባለሙያ እንደነበሩ ይተረክላቸዋል። የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ በሸዋ የዓፄ ቴዎድሮስ እንደራሴ ከነበሩት አቶ በዛብህ ጋር ነሐሴ ፲፯ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ/ም በጋዲሎ አካባቢ በተደረገው ጦርነት ድል አድርገው ወደ አንኮበር ገብተው በነሐሴ ፳፬ ቀን ነገሡ። በነገሡም በአሥራ ሁለት ዓመታቸው በጣይቱ ብጡል እናት በወይዘሮ የውብዳር ቤት ከጣይቱ ብጡል ጋር ተጫጭተው ስለጋብቻቸው ተነጋገሩ። ከተጫጩ ከሁለት ዓመት በኋላ ወይዘሮ ጣይቱን ለማስመጣት በቤተ መንግሥቱ በተደረገው ምክር መሠረት አለቃ ተክለማርያም ወልደ ሚካኤል ደብዳቤ ተሰጥቷቸው ተላኩ። በዚያም አስፈላጊው ሁሉ በተፋጠነ ሁኔታ ተሟልቶ በጐጃም በኩል ደንገጡሮችና አሽከሮች አስከትለው ጉዞውን ጀመሩ። ደብረ ብርሃንም በገቡ ጊዜ ንጉሡ /ምኒልክ/ ታላቅ አቀባበል አደረጉላቸው። ከዚያም ጣይቱ ወንድማቸው ራስ ወሌ ብጡል ዘንድ ለጥቂት ዓመታት ተቀምጠው ከቆዩ በኋላ የጋብቻቸው ስነ-ሥርዓት የፋሲካ ዕለት ሚያዝያ ፳፭ ቀን ፲፰፻፸፭ ዓ/ም በአንኮበር መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ቁርባን ተቀብለው ተጋቡ።
null
null
https://huggingface.co/datasets/israel/AmharicQA
431cb9914aa9a4c2e7ce6c8af9d04822
e4a9823a45e498bbdb3fe2ef36d0e99a
በመጪው መስከረም ወር እምቦጭ አረምን ለማስወገድ የሚያስችል የዘመቻ ሥራ ይከናወናል – ም/ ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ
አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 9፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በመጪው መስከረም ወር እምቦጭ አረምን ለማስወገድ የሚያስችል የዘመቻ ሥራ እንደሚከናወን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ገለጹ።የእምቦጭ አረምን በዘላቂነት ለመከላከልና ለመቆጣጠር ያስችላል ተብሎ በተዘጋጀው ስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በተገኙበት ውይይት ተደርጓበታል።ስትራቴጂክ ዕቅዱ አረሙን ማስወገድ፣ በዘላቂነት የውኃና አካባቢ ጥበቃ መሥራትና ነፃ የሀይቅ ዳርቻ መሥራት እንዲሁም በሀይቁ ዙሪያ የሚኖሩ አርሶ አደሮችን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።ዕቅዱ ላይ ገለጻ ያደረጉት የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ በበኩላቸው የእምቦጭ አረም በ1956 ዓ.ም በአባ ሣሙዔል ግድብ ለመጀመሪያ ጊዜ የታየ መጤ ወራሪ አረም መሆኑን ይገልጻሉ።ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ በጣና ሀይቅ ላይ አረሙ በፍጥነት እየተስፋፋ መሆኑን በአማራ ክልል በሚገኙ ሰባት ወረዳዎችና 35 ቀበሌዎች መዳረሱን ተናግረዋል።እምቦጭ አረም በብዝሃ ሕይወት አንዲሁም በማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስኮች ላይ የደቀነው ሥጋት ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።በጣና ሀይቅና በአጠቃላይ በጣና ተፋፈስ ዙሪያ የእርሻ መስፋፋት፣ የውኃ አካላት ላይ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎች፣ ከከተማና ከኢንዱስትሪ ወደ ጣና ሀይቅ የሚገቡ ፍሳሾች አረሙ እንዲስፋፋ አስተዋጽኦ እያደረጉ መሆኑን አብራርተዋል።ይሁንና አረሙን ማስወገድ የሚቻለው ልማዳዊ ከሆነ አሰራር ወጥቶ ስትራቴጂውን ተግባራዊ በማድረግ መሆኑን በመግለፅ ለዚህም በጋራ መሥራት እንደሚገባ አሳስበዋል።በተጨማሪም የተለያዩ አገሮችን ተሞክሮች በማየት እምቦጭ አረምን ለኃይል አማራጭነት መጠቀም እንደሚቻል መግለፃቸውን ኢዜዘ ዘግቧል።የእምቦጭ አረምን ለመከላከል በጣና ተፋፈስ ዙሪያ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት እየተከናወነ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ በተለይም የተለያዩ ፈሳሾችና ንጥረ ነገሮች ወደ ሀይቁ እንዳይገቡ የማድረግ ተግባር ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%89%a0%e1%88%98%e1%8c%aa%e1%8b%8d-%e1%88%98%e1%88%b5%e1%8a%a8%e1%88%a8%e1%88%9d-%e1%8b%88%e1%88%ad-%e1%8a%a5%e1%88%9d%e1%89%a6%e1%8c%ad-%e1%8a%a0%e1%88%a8%e1%88%9d%e1%8a%95-%e1%88%88%e1%88%9b/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
92bc9e2f0a6912000dcbb4ddacafc5a0
3462d90e533c023dccdb09afb7150260
ኢትዮጵያ በናይል ተፋሰስ ፍትሃዊ የውኃ ኃብት አጠቃቀም ላይ የያዘችውን አቋም አጠናክራለች
-ኢትዮጵያ በናይል ተፋሰስ ፍትሃዊ የውኃ ኃብት አጠቃቀም ላይ የያዘችውን አቋም አጠናክራ እንደምትቀጥል ገለጸች።የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ አቶ ሞቱማ መቃሳ በቅርቡ በኡጋንዳ ኢንቴቤ የተካሄደውን 24ኛው የተፋሰሱ አገሮች የሚኒስትሮች ስብሰባን አስመልከተው በሠጡት መግለጫ በስብሰባው ከትብብሩ ራሷን አግልላ የቆየችው ግብጽ ለመመለስ ጥያቄ ማቅረቧን ገልጸዋል።በዓለም ረጅሙ ወንዝ የሆነው ናይል 10 አገራትን በተፋሰሱ ያቀፈ ሲሆን፤ አገሮቹም በወንዙ አጠቃቀም በጋራ ለመሥራት የናይል ተፋሰስ ኢኒሼቲቭን አቋቁመው በትብብር እየሰሩ ናቸው ብለዋል ።የኢኒሼቲቩ ዋና ዓላማም በተፋሰሱ አገሮች ፍትሃዊ የውኃ ኃብት አጠቃቀም እንዲኖር ለማስቻል እንደሆነ ነው በትብብር ማዕቀፉ ሰነድ የተቀመጠው።ይህን መርህ መሠረት በማድረግ የላይኛው የተፋሰሱ አገራት የውኃ ኃብቱን በፍትሃዊነት የሚጠቀሙበት የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ2012 መፈረማቸውን ጠቅሰዋል ።ሚኒስትሩ እንዳሉት ስምምነቱ የተፋሰሱ አገሮች በመተማመን በጋራ ኃብታቸው እንዲጠቀሙ ዕድል ይፈጥራል።ፍትሃዊ የውኃ አጠቃቀም መርሆውን አብዛኛዎቹ የተፋሰሱ አገሮች ስለተቀበሉት ይህን አጠናክሮ መቀጠል ያስፈልጋል ነው ያሉት።በናይል ተፋስስ ፍትሃዊ የውኃ ኃብት አጠቃቀም ረገድ ኢትዮጵያ የያዘችው አቋም እንደሚጠናከርም ነው ያረጋገጡት።ግብጽ በኢንቴቤው የውኃ የሚኒስትሮች ስብሰባ ወደ ናይል ተፋሰስ ኢኒሼቲቭ ለመመለስ ጥያቄ አቅርባለች ብለዋል ።በዚህ ዙሪያ አስተያየታቸውን የሠጡት አቶ ሞቱማ ግብጽን ጨምሮ የተፋሰሱ አገሮች በውኃ ኃብት ዙሪያ ተባብረው ቢሠሩ ሁሉም ተጠቃሚ ይሆናሉ የሚል እምነት በኢትየጵያና በሌሎችም አገሮች መኖሩን አንስተዋል።  እናም የተፋሰሱ አገራት በጋራ የመሥራት አስፈላጊነትን ተገንዝበው በዚህ ማዕቀፍ እየሰሩ ሲሆን ግብጽ ወደ ትብብሩ ብትመለስ የሚጠቅም እንጂ የሚጎዳ አይሆንም ብለዋል።የግብጽ መመለስ ከትብብር ስምምነት ማዕቀፉ ጋር የተዛመደ መሆን እንደሌለበትም ነው ሚኒስትሩ ያሰመሩበት።ግብጽ የትብብሩ አባል ለመሆን መመለስ እንደምትችል አስረድተው ስምምነቱን በሚቀይር መልኩ የምትስተናገድበት ሁኔታ አይኖርም ብለዋል።በኢንቴቤው የሚኒስትሮች ስብሰባም የግብጽ ጥያቄ ተቀባይነት ያገኘ ቢሆንም፤ በአባልነት ትቀጥል አትቀጥል የሚለው ግን ወደፊት በውይይት እንደሚወሰን ነው የጋራ መግባባት ላይ የተደረሰው።ኢትዮጵያ የትብብር ስምምነት ማዕቀፉ ፍጹም ለድርድር የሚቀርብ ጉዳይ አለመሆኑን በግልጽ አቋም የተያዘበት ነው ብለዋል።ስብሰባው ካሳለፋቸው ውሳኔዎች አንዱ የግብጽ ወደ ትብብሩ ዳግም መመለስ በአዎንታ ተመልክቶ ዝርዝር አፈፃጸሙ ወደፊት ይታያል የሚል ነው።ግብጽ ወደ ትብብሩ ብትመለስ የምታነሳቸው ጥያቄዎች አይኖሩም ማለት ባይቻልም የኢትዮጵያ አቋም ግን ከፍትሃዊ የውኃ አጠቃቀም ውጭ ሊሆን እንደማይችል ሚኒስትሩ አስምረውበታል።በስምምነቱ ዙሪያ ጥያቄ ብታነሳም ያለቀለት ጉዳይ በመሆኑ የተፋሰሱ አባል አገሮች ዳግም ወደኋላ ተመልሰው የሚያዩበት ጉዳይ አይኖርም ነው ያሉት።"አገራት ፈርመው የተቀበሉትን ስምምነት ተመልሶ ወደኋላ ማየት ማለት ፍትሃዊ የውኃ አጠቃቀም እንዳይኖር መፍቀድ ማለት ነው፤ ይህ ደግሞ በአሁኑ ዘመን ሊሰራ አይችልም" ብለዋል አቶ ሞቱማ።ኢትዮጵያ የላይኛውም ሆነ የታችኛው የተፋሰሱ አገሮች እንዲጎዱ ሳይሆን፤ ሁሉም አገሮች ፍትሃዊ የሆነ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ነው የምትሻው ሲሉም አክለዋል ።ይህን አቋም የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የብዙዎቹ የተፋሰሱ አገሮች ጭምር እንደሆነ ጠቅሰው በግብጽ የሚነሳው "ታሪካዊ የውኃ አጠቃቀም መብት" በአሁኑ ደረጃ መስተናገድ አይችልም ብለዋል።በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የድንበርና ድንበር ተሻጋሪ ኃብቶች ጉዳዮች ጄኔራል ዳይሬክተር አምባሳደር ሸምሱዲን አህመድም እንዳሉት የግብጽ ወደ ትብብሩ መመለስ ጠቃሚ ቢሆንም ስትመለስ ግን ቀደም ሲል የተደረሰበት ስምምነት ወደኋላ የሚመለስ መሆን የለበትም።በመስኩ ሰፊ ምርምር ያካሄዱት ዶክተር ያዕቆብ አርሳኖ በበኩላቸው የግብጽ ወደ ትብብሩ መመለስ ሁሉንም አገሮች የሚጠቅም መሆኑን ነው ያስረዱት ።ግብጽ ወደ ትብብር ለመመለስ ቁርጠኛ ከሆነች ሌሎች የተፋሰሱ አገሮች የፈረሙትን የትብብር ስምምነት ማዕቀፍ ተቀብላ ማጽደቅ ይጠበቅባታል ብለዋል ።ግብጽ ከትብብር ማዕቀፉ ሯሳን ያገለለችው እንደ አውሮፓውያን የጊዜ ቀመር በ2012 ሲሆን በስምምነቱ አንቀጽ 14 ንዑስ አንቀጽ ለ "አንድ አገር ውኃውን ሲጠቀም ጉልህ ጉዳት በማያደርስ ሁኔታ" የሚለውን በመቃወም ነበር።የናይል ተፋሰስ ኢኒሼቲቭ የተፋሰሱ አገሮች በወንዙ ውኃ ዘላቂና ፍትሃዊ የሆነ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማትን ማረጋገጥን ታሳቢ አድርጎ ዘጠኝ አገራትን አካቶ እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር በ1999 የተቋቋመ መሆኑ ይታወቃል ። (ኤፍ.ቢ.ሲ) 
5ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/24029/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
dbb3ac7dd7272922ba0ce98fedeeb0f9
0bb49014b45e618ffe7b49c5d1d490fa
የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ ከግድያ ሙከራ ተረፉ
የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅህፈት ቤት ዳይሬክተር አሊ ባክሂት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ተሸከርካሪ መንገድ ላይ በነበረበት ወቅት ሙከራው እንደተረገበት በመግለፅ፤ ሆኖም ምንም አይነት ጉዳት እንዳላጋጠመ ገልፀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃመዶክ ወደ ቢሮዋቸው እያቀኑ በነበረበት ወቅት የግድያ ሙከራው እንደተረገባቸው አልጀዚራ ዘግቧል። ሆኖም እስከአሁን በጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ ለተደረገው የግድያ መከራ ሃላፊነቱን የወሰደ አካል የለም። በማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን የወጡ ተንቀሳቃሽ ምስሎች የሱዳን ባለስልጣናት የሚጠቀሟቸው ሁለት ነጭ ተሸከርካሪዎች በጎዳና ላይ ቆመው የሚታዩ ሲሆን፥ አንደኛው በመስኮት በኩል ጉዳት አጋጥሞታል ፣ ሌላኛው ተሸከርካሪም በጥቃቱ ከፍተኛ ጉዳት አጋጥሞት እንደሚታይ ተጠቁሟል።
4ዓለም አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%8b%a8%e1%88%b1%e1%8b%b3%e1%8a%91-%e1%8c%a0%e1%89%85%e1%88%8b%e1%8b%ad-%e1%88%9a%e1%8a%92%e1%88%b5%e1%89%b5%e1%88%ad-%e1%8a%a0%e1%89%a5%e1%8b%b0%e1%88%8b-%e1%88%83%e1%88%9d%e1%8b%b6%e1%8a%ad/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
a729bd58875122351114ee7d11f1209b
791e315e0adc7fb5e2c6909aa6efcccf
በዊስኮንሲን ግዛት፣ ኬኖሻ ከተማ ውስጥ ፖሊስ ሦስት ልጆቹ ፊት በጥይት ደብድቦት በተአምር የተረፈው ጄኮብ ብሌክ በጠበቃው በኩል የፍትሕ ያለህ እያለ ነው።
ጥቁር አሜሪካዊውን በ7 ጥይት የመታው ነጭ ፖሊስ 'ክስ አይመሰረትበትም'\nጄኮብ ብሌክ የአካባቢው ዐቃቤ ሕግ ድርጊቱን በፈጸመው ፖሊስ ላይ የወንጀል ክስ አይመሰረትም ማለቱን ተከትሎ የጄኮብ ጠበቃ አሜሪካ ሦስት የፍትሕ ሥርዓት ነው ያላት ሲሉ ለሚዲያ ተናግረዋል። አንዱ ለነጭ ፖሊሶች፣ ሌላው ለተራው ሕዝብ እና የመጨረሸው ደግሞ ለጥቁሮች ነው ሲሉ ቁጣቸውን ገልጠዋል። ጄኮብ ደጅ ቆማ ወደነበረችው መኪናው ሲራመድ ሁለት ፖሊሶች በቅርብ ርቀት እየተከተሉት ነበር። የመኪናውን በር እንደከፈተ ግን 3 ሕጻናት ልጆቹ ከኋላ ወንበር ተቀምጠው ድርጊቱን እየተመለከቱ 7 ጥይቶች ከጀርባው ሲተኮሱበት ይታያል። ይህ በተንቀሳቃሽ ምሥል ዓለም የተመለከተው ቪዲዮ እያለ እስከአሁን በጉዳዩ ተጠያቂ የሚሆን አንድም ፖሊስ እንዳልተከሰሰ ተዘግቧል። ወደፊትም በወንጀል የሚጠየቅ የፖሊስ መኮንንም አይኖርም ተብሏል። የጄኮብ ጠበቃ ውሳኔውን ተከትሎ እንደተናገሩት፣ ዘረኛ በሆነው የፍትሕ ሥርዓት ውስጥ የ20 ሰከንድ ግልጽ የቪዲዮ ማስረጃን ውድቅ ለማድረግ ዐቃቢ ሕግ 4 ወራት ፈጅቶበታል ብለዋል። "ፍትሕ ቢኖር፤ ዓይናችን ለተመለከተው ነገር የሁለት ሰዓት ማብራሪያ አስፈላጊ አልነበረም" ሲሉም ተናግረዋል። ጥቁር አሜሪካዊው ጄኮብ ብሌክ 7 ጥይት በቅርብ ርቀት ተርፈከፍክፎበት በሕይወት ቢተርፍም ከወገብ በታች ሙሉ በሙሉ መንቀሳቀስ አይችልም። ጄኮብ ብሌክ ከኋላው በተደጋጋሚ በፖሊስ የተተኮሰበት ወደ መኪናው እያመራ በነበረ ቅጽበት የመኪናው በር እንደከፈተ ነበር። ይህ ሁሉ ሲሆን መኪናው ውስጥ ኋላ ወንበር ተቀምጠው የነበሩ ሦስት ሕጻናት ልጆቹ ድርጊቱን ተመልክተዋል። በጥቁር አሜሪካዊው ጄኮብ ብሌክ ላይ ነጭ ፖሊሶች ያደረሱት ጥቃት በዊስኮንሲንና በሌሎች የአሜሪካ ግዛቶች ከፍተኛ ቁጣን መቀስቀስ ይታወሳል። ድርጊቱን በነሐሴ 23/2020 (እአአ) የፈጸመው ፖሊስ ረስተን ሼስኪይ ይባላል። እስከአሁንም የወንጀል ክስ አልተመሰረተበትም። ይህን ድርጊት ተከትሎ በተነሳ ተቃውሞ ሁለት ሰዎች ተገድለው አንድ ሌላ ሰው በኬኖሻ ከተማ መቁሰሉ አይዘነጋም። ፖሊስ እንዴት ላይከሰስ ቻለ? የኬኖሻ ከተማ ዐቃቤ ሕግ ማይክል ግራቭሊ ድርጊቱን በፈጸመው የፖሊስ መኮንን ላይ እንድም የወንጀል ክስ አልተከፈተም፣ አይከፈትምም ብለዋል። የፖሊስ መኮንኑ ሼስኪ በጄኮብ ላይ በቅርብ ርቀት ጥይት አከታትሎ ሲተኩስበት አንድ መንገደኛ ነው ቅጽበቱን በቪዲዯ አስቀርቶ በመላው አሜሪካ ቁጣ እንዲቀሰቀስ ምክንያት የሆነው። ድርጊቱ የተፈጸመበት ክፍለ ከተማ ዐቃቤ ሕግ እንደሚሉት ክሱን መመሥረት አስፈላጊ የማይሆነው ፖሊስ መኮንኑ ድርጊቱን የፈጸምኩት ራሴን ለመከላከል ነው የሚለውን የክርክር ነጥብ መምዘዙ አይቀሬ ስለሚሆን ነው። የኬኖሻ የፖሊስ መኮንኖች ማኅበር እንደሚለው ጄኮብ በጊዜው ቢላ ይዞ የነበረ ሲሆን ያን እንዲጥል በፖሊስ መኮንኑ በሚስተር ሼስኪ በተደጋጋሚ ቢነገረውም ሊሰማ አልቻለም። የፖሊስ መኮንኑ ጠበቃ ብሬንዳን ማቲው እንዳሉት ደግሞ ጄኮብ ስለት ያለው መሳሪያ ይዞ ወደተኮሰበት ፖሊስ ዞሮ ጥቃት ለመፈጸም አስቦ ነበር። መርማሪዎች በበኩላቸው እንደሚሉት ፖሊሱ በመኪናው ወለል ላይ ስለት ያለው ነገር እንደተመለከተ ብቻ ጠቅሰዋል፣ ጄኮብ ብሌክ ስለቱን ለመጠቀም ሙከራ ስለማድረጉ ያሉት ነገር የለም። ቅጽበቱን የቀረጸው መንገደኛ በበኩሉ ለሲኤንኤን ቴሌቪዥን ሲናገር መቅረጽ ከመጀመሩ በፊት ፖሊስ ከጄኮብ ጋር ሲታገል፣ በጡጫ ሲመታውና በጨረር ማደንዘዣ መሳሪያ ሊያጠቃው ሲሞክር ነበር። እሱ ቪዲዮ መቅረጽ የጀመረው ከዚህ በኋላ ነበር። 20 ሰከንዶች በሚረዝመው በዚህ ቪዲዮ ላይ ጄኮብ ወደ ግል መኪናው ተራምዶ የፊት በሩን ሲከፍት በቅርብ ርቀት ደግሞ 2 ፖሊሶች ሲከተሉት ከዚያ ደግሞ የመኪናው በር...
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
3cb0d7756ccd847b030f7a5f6e15a408
502ddc8d9c406bf73699c1eabd0f2c89
የአውስትራሊያ ሳይንቲስቶች ከቻይና ውጭ ለመጀመርያ ጊዜ የኮሮና ቫይረስን ቅጂ ለማባዛት ጫፍ ደርሰዋል። ይህ ከተሳካ ቫይረሱን ለመቆጣጠር ይበል የሚያሰኝ ተስፋ ይሰጣል ተብሏል።
የአውስትራሊያ ሳይንቲስቶች ኮሮና ቫይረስን 'ሊያመርቱ' ነው\nውጤቱም የዓለም ጤና ድርጅት እንዲያውቀው ይደረጋል። በሂደትም የቫይረሱን ባህሪ ለማወቅና ብሎም ለማከም ተስፋ ሰጪ ሙከራዎች ይኖራሉ። የቻይና ሳይንቲስቶችም የቫይረሱን ቅጂና ዘረመላዊ ሂደቱን ማወቅ የቻሉ ሲሆን ቫይረሱን ራሱን ግን መፍጠር አልቻሉም። እስከዛሬ ኮሮና ቫይረሱ 132 ሰዎችን የገደለ ሲሆን 6ሺ ሰዎች በቫይረሱ መጠቃታቸው ታውቋል። ከቻይና ውጭ ደግሞ በትንሹ በ16 አገሮች 47 ሰዎች ቫይረሱን እንደተሸከሙ ተረጋግጧል። ከነዚህ አገሮች መሀል አሜሪካ፣ ፈረንሳይና አውስትራሊያ ይገኙበታል። በሜልበርን፣ የሚገኙት ሳይንቲስቶች እንደሚሉት ቫይረሱን የቀዱት አንድ በቫይረሱ ከተጠቃ ግለሰብ ነው። ናሙናው የተላከላቸውም ባለፈው አርብ ነበር። 'ለእንዲህ አይነት የቫይረስ ክስተት ለረዥም ዘመን ስንዘጋጅበት ነበር። ለዚህም ነው በፍጥነት ቫይረሱን ቅጂ ማምረት የቻልነው' ብለዋል የጥናት ቡድኑ ኃላፊ። • በአዲሱ ቫይረስ የሟቾች ቁጥር አሻቀበ • ኮሮናቫይረስ አሜሪካ፣ ታይዋን፣ ጃፓን፣ ቬትናም ጨምሮ በሌሎች አገራት ተሰራጭቷል • ቻይና በ 6 ቀናት ውስጥ ደረጃውን የጠበቀ ሆስፒታል ልትገነባ ነው የቫይረሱ ቅጂ መገኘቱ ምን ፋይዳ ይዞ ይመጣል? ሐኪሞች እንደሚሉት ቫይረሱ ቅጂ መመረቱ በሙከራ ጥናት ውስጥ የቁጥጥር ናሙና (ኮንትሮል ማቴሪያል) ሆኖ ያገለግላል። ይህም ማለት በሽታን ለማከም ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል። በተለይ የበሽታውን ምልክቶች ማሳየት ያልጀመሩና ነገር ግን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ለመለየት አጋዥ ነው። የቻይና ባለሥልጣናት እንዳረጋገጡት ቫይረሱን አስቸጋሪ ያደረገው ልክ እንደ ጉንፋን ከሰው ወደ ሰው በቀላሉ መተላለፉና ገና ወደ ሙሉ በሽታ ሳያድግ መሠራጨቱ ነው። የቫይረሱ ቅጂ መመረት መቻሉ በተለይ የሙከራ ክትባትን ለመፍጠር እጅግ ወሳኝ እርምጃ ነው እየተባለ ነው። የዓለም አቀፉ ጤና ድርጅት እንደሚለው ኮሮና ቫይረስ ራሱን እስኪያጎለብት ከ2 እስከ 10 ቀናት ይፈጅበታል። በዚህ ጊዜ ወደ ሌላ ሰው መሰራጨት መቻሉ ነው አሁን ችግር እየፈጠረ ያለው። አውስትራሊያ ዛሬ እንዳስታወቀችው 600 ዜጎቿን ከዉሃን ግዛት በማውጣት በክሪስማስ ደሴት ለብቻቸው ለማስቀመጥ ተዘጋጅታለች። ክሪስማስ ደሴት ከአውስትራሊያ በ2ሺ ኪሎ ሜትር ርቃ የምትገኝ ናት።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
e32c51eadcc9e4a1622af7ee3e0988f5
f229301db2c237f27f11945a1d43c1ee
ዓባይ ባንክ አክሲዮን ማኅበር ለደንበኞቹ የወለድ ቅናሽ አደረገ፡፡
ባሕር ዳር፡ ግንቦት 07/2012 ዓ.ም (አብመድ) የዓባይ ባንክ አክሲዮን ማኅበር ዘርፈ ብዙ ዓለም አቀፍ ቀውስ የፈጠረውን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መቋቋም ያስችላቸው ዘንድ ለደንበኞቹ የወለድ ቅናሽ ማድረጉን አስታውቋል፡፡ የብድሩን የክፍያ ጊዜ፣ ወረርሽኙ ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳት እና የባንኩን አቅም ታሳቢ በማድረግ ከ0 ነጥብ 5 እስከ 3 በመቶ ድረስ የወለድ ምጣኔ ቅናሽ ማድረጉን የዓባይ ባንክ አክስዮን ማኅበር የኮርፖሬት አገልግሎት ምክትል ፕሬዘዳንት በለጠ ዳኛው መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ባንኩ በወረርሽኙ በተለየ ሁኔታ ተጠቂ ይሆናሉ ተብለው የሚታሰቡ የሆቴል፣ አስጎብኚ፣ የአበባ ምርት ላኪ እና አቅራቢ የንግድ ዘርፎች ላይ ከፍ ያለ የወለድ ቅናሽ አድርጓል፡፡ ዓባይ ባንክ ይህንን የወለበተጠቀሱት ዘርፎቶ ላይ ከግንቦት ጀምሮ በቀጣይ ሦስት ወራት ውስጥ ተበዳሪዎች እንዲከፍሉ የሚጠበቅባቸውን የዋና ብድር እና የወለድ ክፍያ ማስተላለፉንም በመግለጫው ጠቅሷል፡፡የብድር ማራዘሚያ ጥያቄ ለሚያቀርቡ ደንበኞቹ እንደየሁኔታው እየታየ እንዲፈቀድ ይደረጋልም ተብሏል፡፡ የብድር ማራዘሚያ ጥያቄ በነጻ እንዲሆን እና የቅድሚያ ብድር ክፍያ ቅጣት እንደተነሳም ተገልጿል፡፡ ኤ ቲ ኤም ለሚጠቀሙ ደንበኞቹ የአገልግሎት ክፍያ ነጻ እንዲሆንና ደንበኞቹ በአንድ ጊዜ እስከ 10 ሺህ ብር ድረስ በኤ ቲ ኤም ማውጣት እንዲችሉ መደረጉንም ምክትል ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል።ባንኩ ቫይረሱን ለመከላከል እና በተለያየ ሁኔታ ተጎጂ ለሚሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ለማድረግ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለተቋቋመዉ ዕርዳታ አሰባሳቢ ኮሚቴ የ3 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉም ተገልጿል፡፡የዓባይ ባንክ አክሲዮን ማኅበር ሠራተኞችን ከወረርሽኙ ለመከላከል እየወሰደ ያለውን ርምጃም አቶ በለጠ በመግለጫቸው አብራርተዋል፡፡ “ይህንን አስቸጋሪ ወቅት በኢትዮጵያዊ አንድነት፣ በመተባበር እና በጽናት እንደምንሻገረው ባለ ሙሉ ተስፋ ነን” ብለዋል ምክትል ፕሬዝዳንቱ፡፡
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.amharaweb.com/%e1%8b%93%e1%89%a3%e1%8b%ad-%e1%89%a3%e1%8a%95%e1%8a%ad-%e1%8a%a0%e1%8a%ad%e1%88%b2%e1%8b%ae%e1%8a%95-%e1%88%9b%e1%8a%85%e1%89%a0%e1%88%ad-%e1%88%88%e1%8b%b0%e1%8a%95%e1%89%a0%e1%8a%9e%e1%89%b9/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
485783423b675757a2a947659bc9545c
e2574137f5177d5eab5fa725d36c0c21
“አረጋውያን እናቶቻችን እና አባቶቻችን ከመሆናቸው ባሻገር የአንድ ሀገር ሀብት እና የዕውቀት ምንጭ፣ ታሪክ እና ጥበብ ስለሆኑ ልንከባከባቸው እና ልንደግፋቸው ይገባል፡፡” ዶክተር ሙሉነሽ አበበ
ባሕር ዳር፡ መስከረም 20/213ዓ.ም (አብመድ) ነገ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ30ኛ በሀገራችን ለ29ኛ ጊዜ የሚከበረውን የአረጋውያን ቀን አስመልክቶ የአማራ ክልል ሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ የአረጋውያን በዓል በሚከበርበት ወቅት ጧሪ እና ደጋፊ የሌላቸውን አረጋውያን ቋሚ በሆነ መልኩ የሚደገፉበት ሥርዓት መፍጠር እንደሚገባ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የማኅበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ እና የአማራ ክልል ሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ሙሉነሽ አበበ (ዶክተር) አሳስበዋል፡፡በአማራ ክልል 1 ነጥብ 4 ሚሊዮን አረጋውያን እንዳሉ ኃላፊዋ የክልሉ መንግሥት ለአረጋውያን የገቢ ምንጭ ማስገኛ በማሰብ በሁሉም ዞኖች የአረጋውያን መርጃ ማዕከላት እንዲገነቡ በመወሰኑ እስካሁን ዘጠኝ ዞኖች ቦታ ተረክበው እንቅስቃሴ መጀመራቸውን አብራርተዋል፡፡ የኮሮናቫይረስን ከመከላከል አንፃር በክልሉ በበጎ አድራጎት ድርጅቶች የታቀፉ አረጋውያንን የመደገፍ ሥራ ሲሠራ መቆየቱንም ዶክተር ሙሉነሽ አበበ ጠቅሰዋል፤ ከችግሩ ስፋት እና ጥልቀት አንፃር ግን በቂ አለመሆኑን አስረድተዋል፡፡
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.amharaweb.com/%e1%8a%a0%e1%88%a8%e1%8c%8b%e1%8b%8d%e1%8b%ab%e1%8a%95-%e1%8a%a5%e1%8a%93%e1%89%b6%e1%89%bb%e1%89%bd%e1%8a%95-%e1%8a%a5%e1%8a%93-%e1%8a%a0%e1%89%a3%e1%89%b6%e1%89%bb%e1%89%bd%e1%8a%95/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
7a29475785950ea33bf6f26681fb354b
594605369bc7117e3fb11bc23539c518
በማርገዛቸው ከትምህርት ቤት የተባረሩት ተማሪዎች ተመረቁ
ከሁለት ዓመት በፊት የታንዛኒያው ፕሬዝዳንት ጆን ማጉፉሊ ያረገዙ ተማሪዎች ከትምህርት ቤት መባረር አለባቸው ብለው ከተናገሩ በኋላ በአገሪቱ እየተበራከተ የመጣው የታዳጊዎች እርግዝና ጉዳይ በዓለም አቀፍ ደረጃ የውዝግብ ርዕስ ሆኖ ነበር። ማርቲና ሳይመን ሲያራ የተባሉት የ72 ዓመት ጡረተኛ መምህር በሰሜናዊ ታንዛኒያ በምትገኘው የአሩሳ ከተማ ውስጥ ለእናቶቹ በከፈቱት ትምህርት ቤት ውስጥ ለተባረሩት ተማሪዎች የመማር ዕድልን ፈጥረውላቸዋል። ፋራጃ በተባለው ማዕከል ውስጥ ሴቶቹ የምግብ ዝግጅትና የልብስ ስፌት ሥልጠናዎችን የሚያገኙ ሲሆን ከሁሉ የበለጠው ደግሞ ትምህርታቸውን ሳያቋርጡ በትኩረት እንዲከታተሉ ሥራዎቻቸውን የሚያሳዩበትና የሚሸጡበት ቦታም ተዘጋጅቶላቸዋል። • በታንዛንያ አርግዘው የተገኙ ተማሪዎችና ወላጆቻቸው ታሰሩ • ታንዛኒያ ያጋጠማትን የኮንዶም እጥረት ለመቅረፍ 30 ሚሊዮን ኮንዶሞች ከውጭ አስገባች • ታንዛኒያ በዊግና ሰው ሰራሽ ጸጉር ላይ ከፍተኛ ቀረጥ ጣለች ከተማሪዎቹ መካከል አንዷ የሆነችውና የመንታ ልጆች እናት የሆነችው የ23 ዓመቷ ዴብራ ኢማኑኤል በ17 ዓመቷ በማርገዟ ቤተሰቦቿ ያባረሯት ሲሆን ከትምህርት ቤትም ተባራ ነበር። "ልጆቼን ለማሳደግና ለማስተማር ገንዘብ የሚያስገኝልኝ የራሴ የሆነ ሥራ እጀምራለሁ" ስትል በምግብ ዝግጅት የተከታተለችውን ሥልጠና ጨርሳ ስትመረቅ ለቢቢሲ ተናግራለች። የታንዛኒያው ፕሬዝዳንት ከሁለት ዓመት በፊት በተካሄደ አንድ ሥነ ሥርዓት ላይ "ካረገዛችሁ፤ አለቀላችሁ" በማለት ተማሪ ልጃገረዶችን ካስጠነቀቁ በኋላ ከፍተኛ ወቀሳና ትችት ቀርቦባቸው ነበር። በወቅቱ ፕሬዝዳንቱ አጽንኦት ሰጥተው የተናገሩት ያለውን የአገሪቱን ሕግ ጠቅሰው ነበር። እንደ አውሮፓዊያኑ በ2002 የጸደቀው ሕግ ተማሪ ልጃገረዶች አርግዘው ከተገኙ ከትምህርት ቤት ማባረርን ይፈቅዳል።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
76a86fb894c48bb09c8af0aa968156a1
ad2d5450cb91a4b2a5879584b7435b44
‹‹ለትግራይም ሆነ ለፌዴራል መንግሥት ዕውቅና እንሰጣለን›› የዕርቀ ሰላም ኮሚሽን
‹‹በመንግሥታቱ መካከል ለውይይት ፈቃደኝነት ቢኖርም ቅድመ ሁኔታዎች  ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነየሱስ ሱራፌልበትግራይ ክልልና በፌዴራል መንግሥት መካከል የሕጋዊነት መካሰስ ቢቀጥልም፣ የኢትዮጵያ ዕርቀ ሰላም ኮሚሽን ሁለቱም ሕጋዊና ቅቡልነት ያላቸው መሆኑን የኮሚሽኑ ኃላፊዎች ገለጹ፡፡በተለያዩ ምክንያቶች ተከስተው ለዓመታት የቆዩ የቂምና ቁርሾ ችግሮችን በዕርቅ ዕልባት ሰጥቶ፣ ሰላምና ፍቅርን እንዲያሰፍን የተቋቋመው የኢትዮጵያ ዕርቀ ሰላም ኮሚሽን፣ የዕርቀ ሰላሙን የማስፈን ሥራውን ለመጀመር በቅርቡ በተለያዩ የአገሪቱ ሥፍራዎች እየጨመሩ የመጡ ግጭቶችና በማቋቋሚያ አዋጁ ውስጥ ያልተካተቱ የሕግ ማዕቀፎች እንቅፋት እየሆኑበት መምጣታቸውን ኃላፊዎቹ አስታውቀዋል፡፡በበጀት ዓመቱ የመጀመርያ ሩብ ዓመት የሥራ እንቅስቃሴውና ያከናወናቸውን ተግባራት አስመልክቶ፣ የኮሚሽኑ ሰብሳቢ ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ እየሱስ  ሱራፌል፣ ከምክትላቸው ወ/ሮ የትነበርሽ ንጉሤና ከአርቲስት ደበበ እሸቱ ጋር በመሆን ኮሚሽኑ ለምን ወደ ሥራ ለመግባት እንደዘገየና አገሪቱ ካለችበት ነባራዊ የፀጥታ መደፍረስ ጋር ተያይዞ የገጠሟቸውን ችግሮች፣ ጥቅምት 12 ቀን 2013 ዓ.ም. በጠሩት ጋዜጣዊ መግለጫ ሥነ ሥርዓት ላይ አብራርተዋል፡፡በፌዴራልና በትግራይ ክልላዊ መንግሥታት መካከል ለተነሱት አለመግባባቶችን በተመለከተ ከሁለቱም ወገኖች ጋር ተገናኝተን ተወያይተናል፡፡ እንደሚታወቀው እኛ የተቋቋምንበትን ዋነኛ ዓላማው በሕዝቦች መካከል ግጭት ሲኖር፣ ቁርሾ ሲኖርና አለመግባባት ሲፈጠር ያለውን ችግር በማጥናትና በመለየት፣ በሕዝቦች መካከል መግባባት እንዲፈጠር በማገዝ ሰላምንና መግባባትን ማምጣት ነው፡፡ነገር ግን መንግሥት ለመንግሥት አለመግባባት ሲኖር የራሱ የሆነ ችግር መፍቻ መንግሥታዊ መስመር አለ፡፡ በቀጥታ የሚመለከተን ሥራችን ነው ባንልም፣ በመንግሥታት መካከል ያሉትን አለመግባባቶች በውይይትና በመግባባት እንዲፈቱ የራሳችን አገራዊ ኃላፊነት እንወጣለን፡፡ለዚህም ደግሞ ባለፉት ጥቂት ወራት ብቻ ትግራይን ጨምሮ በሁሉም ክልሎች በመዘዋወር ውይይት አድርገናል፡፡ የፌዴራል መንግሥቱን ጨምሮ ሁሉም የክልል መንግሥታት ጥረታችንን የሚጋሩትና ሰላም ለማምጣት ያላቸውን ተነሳሽነት አስተውለናል ያሉት ሰብሳቢው፣ በትግራይ መንግሥት በኩልም ያለው የሰላም ፍላጎት ከተጠቀበው በላይ እንዳገኙት ገልጸዋል፡፡ይህንኑ የሰብሳቢውን ሐሳብ የሚጋሩት ምክትል ሰብሳቢዋ ወ/ሪት የትነበርሽ በበኩላቸው፣ ‹‹ወደ ትግራይ በሄድንበት ወቅት ከክልሉ ፕሬዚዳንት ደብረ ጽዮን (ዶ/ር) በኩል ያየነው ዝግጁነት ከገመትነው በላይ ያስደሰተንና ጥረታችን የበለጠ ለማጠናከር ያነሳሳን ሆኖ አግኝተነዋል፤›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡በትግራይ ክልልና በፌዴራል መንግሥታት በኩል የሕጋዊ ተቀባይነት ጉዳይን በተመለከተ ስለሚካሰሱበት ጉዳይ ለኮሚሽኑ ኃላፊዎች አስተያየታቸውን እንዲሰጡ ሪፖርተር ጥያቄ አንስቶላቸው ነበር፡፡ ለዚሁ ጥያቄ ምላሽ የሰጡት ካርዲናል ብርሃነ የሱስ፣ ከክልል መንግሥታቶችም ሆነ ከፌዴራል መንግሥት በጎ ምላሽ ቢያገኙም ወደ ውይይት መድረክ ለመምጣት ግን ከሁለቱም በኩል ችግሮች መስተዋላቸውን አመልክተዋል፡፡ ወደ ክልሎች በተጓዝንበት ወቀት ክልሎች ውይይት እንዲያደርጉ በጠየቅናቸው ጊዜ ለውይይት ዝግጁ መሆናቸውንና ፍቃደኝነቱ እንዳላቸው ገልጸዋልና ያሉት ካርዲናል ብርሃነ የሱስ፣ ችግሩ ለመወያየት ቅደመ ሁኔታ ማስቀመጣቸው መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡‹‹ወደ ክልሉ በሄድንበት ጊዜ የክልል አመራሮች ከዝግጁነታቸው ባለፈ ለውይይቱ እንደ ቅድመ ሁኔታ የሚያስቀምጧቸው ጉዳዮች እንዳሏቸው መግለጻቸው ፈታኝ ሁኔታ እየፈጠረብን ነው፡፡ እንግዲህ የሠለጠነ መንገድ የሚባለው ችግር መፍቻ በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጦ መወያየት ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ መደማመጥን ይጠይቃል፡፡ መደማመጥ በሌለበትና የእኔ ብቻ ይደመጥ የሚል አስተሳሰብ ካለ ደግሞ ወደምንፈልገው ውይይት ወይም መቀራረብ ያደርሳል ብዬ አልገምትም፤›› ሲሉ ሰብሳቢው ምላሽ ሰጥተዋል፡፡‹‹እኛ ውይይት እናዘጋጅና ተወያዩ ብለን ለአንዳንድ ክልሎች ስንገልጽላቸው፣ ያነሷቸው ቅድመ ሁኔታ አሉ፡፡ ያ ደግሞ ለማቀራረብ ለምናደርገው ጥረታችን መሰናክል ሆኗል፤›› ሲሉ ጨምረው ገልጸዋል፡፡ነገር ግን እንዲወያዩ በተጠየቁት ወገኖች በኩል ስለተነሱት የቅድመ ሁኔታዎች ጥያቄን በተመለከተ ዝርዝር ማብራርያ አልሰጡም፡፡ ይሁን እንጂ በአገሪቱ የችግር አፈታትን ለመተግበር በውይይት ችግርን የመፍታት ልማዳችን ውስጥ ያለብን ችግር መሆኑን አክለዋል፡፡የሁለቱን መንግሥታት ወቅታዊ ውዝግቦችና የፈጠረውን ውጥረት በተመለከተ ተጨማሪ ምላሽ የሰጡት ምክትል ሰብሳቢውም ‹‹ከትግራይና ከፌዴራል መንግሥታት ጋር የተፈጠረውን ዓይነት ችግር ለመፍታት ለኮሚሽኑ የተሰጠው የሕግ አካሄድ ባይኖርም፣ ጉዳዩን በተለየ ሁኔታ በማየት ሁለቱ መንግሥታት ቁርlቸውን በውይይት እንዲፈቱ የኮሚሽኑ ጥረት መቀጠሉን ገልጸዋል፡፡››‹‹ምንም እንኳን ያለፉን በደሎችንና ግጭቶችን ተከትሎ በሕዝቦች መካከል የተስተዋሉ ቁርሾዎችንና ቂሞችን በዕርቅ እንዲዘጉ ለማድረግ ብቻ የተቋቋምን ቢሆንም፣ የትግራይ ጉዳይ ግን ካለው ነባራዊ ሁኔታ አንፃር በአገር ሰላም ላይ ሊኖር የሚችለውን ተፅዕኖ በማየት፣ በተለየ ሁኔታ እኛም ገብተንበታል፤›› ብለዋል፡፡ ወ/ሮ የትነበርሽ ምንም እንኳን የፌዴራሉም መንግሥትም ሆነ የክልሉ መንግሥት አንዱ ለአንዱ ዕውቅና በመንፈግ ቢካሰሱም፣ ኮሚሽኙ ግን ለሁለቱም መንግሥታት ዕውቅና እንደሚሰጥ ምክትል ሰብሳቢዋ ለሪፖተር በሰጡት ምላሽ ገልጸዋል፡፡‹‹ለእኛ ሁለቱም መንግሥታት ተቀባይነት ያላቸውና ዕውቅና የምንሰጣቸው ናቸው፡፡ ሁለቱም ቅቡልነት ያላቸው መንግሥታት ናቸው፤›› ያሉት ኃለፊዋ፣ ‹‹እንዲህ ያሉ በመንግሥታት መካከል አለመግባባት ሲፈጠሩ ችግሩን የመፍታት ሚና በሕግ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት የተሰጠን ነገር ባይኖርም እንደ ዜጋና ኃላፊነት እንደሚሰማው አካል፣ የሁለቱ መንግሥታት አለመግባባት ከሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቶች ሰላም አንፃር የሚኖረውን ተፅዕኖ በማየት የተለየ አድርገን ነው የገባንበት፤›› ሲሉ አክለዋል፡፡ ‹‹በእኛ በኩል እንደ ገለልተኛ ኮሚሽን ማድረግ የምንችለው፣ በክልሎችና በፌዴራል መንግሥት መካከል ሰክነው እንዲነጋገሩ መጠየቅ ነው፡፡ ለመነጋገርና ለመወያየት ገለልተኛ አወያይ አስፈልጓቸው እኛ ራሳችን ዝግጁ መሆናችንን፣ ሌላም አወያይ ካስፈለጋቸው ኮሚሽኑ እንደሚያቀርብላቸው ለሁለቱም አካላት ገልጸንላቸው ነበር፤›› ሲሉም ጨምረው አክለዋል፡፡ ኮሚሽኑ ዝግጁነትን በመደበኛ መንገድ ለሚመለከታቸው አካላት ያሳወቀ መሆኑን የገለጹት ወ/ሮ የትነበርሽ፣ ይህን መሰሉ አለመግባት በመንግሥታትና በመንግሥት መዋቅሮች መካከል የሚፈጠሩ ችግሮች ለመፍታት በግልጽ በሕግ ባለመቀመጡ ምክንያት፣ የዕርቀ ሰላም ሥራ ላይ ሥጋት ሆኖ የሚቀጥል ከሆነ ለወደፊት ማስተካከል የሚችልበት ሁኔታ ወደፊት ኮሚሽኑ በሪፖርቱ እንደሚያካትተውና ለሚመለከተው አካል እንደሚያሳውቅ አስረድተዋል፡፡ ነገር ግን አሁን ያለው በትግራይና በፌዴራል መንግሥታት መካከል የተፈጠረው ውዝግብ በሁለት መንግሥታት መካከል ያለ የሥልጣን ጉዳይ ሲሆን፣ በኢመደበኛ ልውውጦች እንደምንሰማው ፖለቲካ ሲሆን በትግል ሊፈቱን እንደሚፈልጉ የምንረዳው ነው ብለዋል፡፡ ነገር ግን በሁለቱም በኩል ስምምነት ለማምጣት ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ያሉበት ሰብስብ እንደመሆኑ መጠን የሚደረጉ የሰላም ውይቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥረታቸውን እንደሚቀጥሉም ገልጸዋል፡፡ ይሁን እንጂ በዋነኝነት በሕግ ደረጃ ይህ ዓይነቱ የማስታረቅ ሥራ ለኮሚሽናችን በአዋጅ ደረጃ ያልተሰጠ ኃላፊነት መሆኑን ሕዝብ እንዲገነዘብላቸው አስምረዋል፡፡ ከዚሁ ከግጭትና ቁርሾ አፈታት ጋር በተያያዘ አዋጁ በበርካታ ጉዳዮች መስተካከል የሚፈልግ መሆኑን የጠቆሙት ወ/ሮ የትነበርሽ፣ አዋጁን ለማሻሻል ከጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ጋር እየተወያዩ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በተጨማሪም ኮሚሽኑ ባለፈው ሦስት ወራት ከ370 በላይ የሚሆኑ ባህላዊ ግጭት የመፍቻ ዘዴዎችን መሰነዱን ጠቅሰው ለቀጣይም በዋነኝነት ሊፈታቸው ቅድሚያ ያሰባቸውን ከ21 በላይ የተለያዩ ችግሮችን መለየቱን ኃላፊዎቹ አስታውቀዋል፡፡ እነዚህ ለዕርቅ ፈታኝ ናቸው የተባሉት 21 ግጭቶች፣ በአገሪቱ ሁሉም ክልሎች ከበርካታ ዓመታት በፊት ጀምሮ የነበሩ መሆናቸውን ኮሚሽኑ አመልክቷል፡፡ ከእነዚህም ግጭቶች የተወሰኑት ጥለው ያለፏቸው ጠባሳዎች ዛሬም ድረስ ለግጭት መነሻ እንዲሆኑ መሆናቸውንና ተመልሰው በሚፈጠሩ ተያያዥ ግጭቶች የሰው ሕይወት መጥፊያ ምክንያት እየሆኑ መቀጠላቸው ተገልጿል፡፡ ለእነዚህም ችግሮች ዕልባት ለመስጠት ኮሚሽኑ በአንድ ወር ውስጥ ከኢትዮጵያ ተሰባስበው ለሚመጡ የአገር ሽማግሌዎች፣ ወጣትቶችና ለሴቶች ተከታታይ የውይይት መድረክ እያዘጋጀ መሆኑን ኃላፊዎቹ ገልጸዋል፡፡ 
5ፖለቲካ
https://www.ethiopianreporter.com/article/20255
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
773fae6cd4164b959145aa1b8ef09bb2
b50fbf4ca7ac5200961fb9d29c313634
ጠ/ሚ ዐቢይ የገናን በዓል ከአረጋውያን፣ ህጻናት እና አካል ጉዳተኞች ጋር በአንድነት ፓርክ አከበሩ
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 28፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ዛሬ ጠዋት የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልን ከአረጋውያን፣ ህጻናት እና አካል ጉዳተኞች ጋር በአንድነት ፓርክ አክብረዋል።በዚህ ወቅትም ቁሳዊ ሃብት ብቻውን ባለጸጋ አያደርግም፤ብልጽግና መስጠት እና መካፈልን የሚጨምር መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ተናግረዋል።መረጃው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ነው፣
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%8c%a0-%e1%88%9a-%e1%8b%90%e1%89%a2%e1%8b%ad-%e1%8b%a8%e1%8c%88%e1%8a%93%e1%8a%95-%e1%89%a0%e1%8b%93%e1%88%8d-%e1%8a%a8%e1%8a%a0%e1%88%a8%e1%8c%8b%e1%8b%8d%e1%8b%ab%e1%8a%95%e1%8d%a3-%e1%88%85/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
497b3bb41a041504124a025de3134999
41ae9afaf495833ba01123ff11d6461b
የሐዋርያት ሥራ ፳፰
ቁጥር ፳፰ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ የመጨረሻው ምዕራፍ ሲሆን ይዘቱ የጳውሎስን ጉዞ በተለይ ከማልታ ወደ ጣልያን ከዞም በሮም መርጋቱን የሚገልጽ ነው ። የጻፈውም ቅዱስ ሉቃስ እንደሆነ በማስረጃ ሙሉበሙሉ ቤተክርስቲያን የምታምነው ነው ። ስለ ፅሑፉ የመጀመሪያው ፅሑፍ በኮይን ግሪክ ሲፃፍ በ፴፩ ንዑስ ክፍል የተከፈለ ነው ። በጣም ጥንት ከሚባሉ እነዚህን ክፍሎች የሚይዙ ፅሑፎች የሚከተሉት ናቸው ፡ ወደ ግዕዝ የተተረጎመው ማለትም መጸሐፍ ቅዱስ ከዕብራይስጥ ወደ ግዕዝ ሲተረጎም የነበረው ፅሑፍ Codex Vaticanus 325-350 ዓ.ም.እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር Codex Sinaiticus 330-360 ዓ.ም. እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር Codex Bezae 400 ዓ.ም. እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር Codex Alexandrinus 400-440 ዓ.ም. እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር Codex Ephraemi Rescriptus 450 ዓ.ም. እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር (ቁጥር ፩-፬) Codex Laudianus 550 ዓ.ም.(ቁጥር ፳፯-፴፩) የተጠቀሱ ቦታዎች ተግባራቱ የተፈፀሙበት ቦታዎችን በቅደምተከተል እንደሚከተለው ይነበባሉ መላጥያ እስክንድሪያ ሳይራኪዩዝ ሬጂየም ፑቼዮሊ ሮም አፒዪ ፎረም ስሪ ኢንስ ቁጥር ፰ በዚህ ምዕራፍ የግዕዝ ጽሑፉ የሚጨምረው አለ ይህም ምንድንነው "ጳውሎስም ወደ እርሱ ገብቶ ጸለየለት እጁንም በላዩ ጭኖ ፈወሰው።" የሚለው ነው ። በዚህም ምክኒያት ፑፕልዮስም ልጁም በጳውሎስ ላይ ልዩ የአምላክ ኃይል እንዳለበት እንዲያምኑ አረጋቸው ።  የሐዋርያት ሥራ ፳፰ ቁጥር ፩ - ፲ 1 በደኅና ከደረስን በኋላ በዚያን ጊዜ ደሴቲቱ መላጥያ እንድትባል አወቅን። 2 አረማውያንም የሚያስገርም ቸርነት አደረጉልን፤ ዝናብ ስለ ሆነም ስለ ብርዱም እሳት አንድደው ሁላችንን ተቀበሉን። 3 ጳውሎስ ግን ብዙ ጭራሮ አከማችቶ ወደ እሳት ሲጨምር እፉኝት ከሙቀት የተነሣ ወጥታ እጁን ነደፈችው። 4 አረማውያንም እባብ በእጁ ተንጠልጥላ ባዩ ጊዜ፥ እርስ በርሳቸው፦ ይህ ሰው በእርግጥ ነፍሰ ገዳይ ነው፥ ከባሕርም ስንኳ በደኅና ቢወጣ የእግዚአብሔር ፍርድ በሕይወት ይኖር ዘንድ አልተወውም አሉ። 5 እርሱ ግን እባቢቱን ወደ እሳት አራገፋት አንዳችም አልጐዳችውም፤ 6 እነርሱም፦ ሊያብጥ ወይም ወዲያው ሞቶ ሊወድቅ ነው ብለው ይጠባበቁት ነበር ብዙ ጊዜ ግን ሲጠባበቁ በእርሱ ላይ የሚያስገርም ነገር ምንም ባላዩ ጊዜ፦ ይህስ አምላክ ነው ብለው አሳባቸውን ለወጡ። 7 በዚያም ስፍራ አጠገብ ፑፕልዮስ የሚሉት የደሴት አለቃ መሬት ነበረ፥ እርሱም እንግድነት ተቀብሎን ሦስት ቀን በፍቅር አሳደረን። 8 የፑፕልዮስም አባት በንዳድና በተቅማጥ ታሞ ተኝቶ ነበር፤ ጳውሎስም ወደ እርሱ ገብቶ ጸለየለት እጁንም በላዩ ጭኖ ፈወሰው። 9 ይህም በሆነ ጊዜ የቀሩት ደግሞ በደሴቲቱ ደዌ የነበረባቸው እየመጡ ተፈወሱ፤ 10 በብዙ ክብርም ደግሞ አከበሩን፥ በተነሣንም ጊዜ በመርከብ ላይ የሚያስፈልገንን ነገር አኖሩልን። ቁጥር ፲፩ - ፳ 11 ከሦስት ወርም በኋላ በደሴቲቱ ከርሞ በነበረው በእስክንድርያው መርከብ ተነሣን፥ በእርሱምየዲዮስቆሮስ አላማ ነበረበት። 12 ወደ ሰራኩስም በገባን ጊዜ ሦስት ቀን ተቀመጥን፤13 ከዚያም እየተዛወርን ወደ ሬጊዩም ደረስን። ከአንድ ቀን በኋላም የደቡብ ነፋስ በነፈሰ ጊዜ በሁለተኛው ቀን ወደ ፑቲዮሉስ መጣን። 14 በዚያም ወንድሞችን አግኝተን በእነርሱ ዘንድ ሰባት ቀን እንድንቀመጥ ለመኑን፤ እንዲሁም ወደ ሮሜ መጣን። 15 ከዚያም ወንድሞች ስለ እኛ ሰምተው እስከ አፍዩስ ፋሩስና ሦስት ማደሪያ እስከሚባለው ሊቀበሉን ወጡ፥ ጳውሎስም ባያቸው ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገነ ልቡም ተጽናና። 16 ወደ ሮሜም በገባን ጊዜ ጳውሎስ ከሚጠብቀው ወታደር ጋር ለብቻው ይቀመጥ ዘንድ ተፈቀደለት። 17 ከሦስት ቀንም በኋላ ጳውሎስ የአይሁድን ታላላቆች ወደ እርሱ ጠራ፤ በተሰበሰቡም ጊዜ እንዲህ አላቸው፦ ወንድሞች ሆይ፥ እኔ ሕዝቡን ወይም የአባቶችን ሥርዓት የሚቃወም አንዳች ሳላደርግ፥ ከኢየሩሳሌም እንደ ታሰርሁ በሮማውያን እጅ አሳልፈው ሰጡኝ። 18 እነርሱም መርምረው ለሞት የሚገባ ምክንያት ስላልነበረብኝ ሊፈቱኝ አሰቡ፤ 19 አይሁድ ግን በተቃወሙ ጊዜ፥ ወደ ቄሣር ይግባኝ እንድል ግድ ሆነብኝ እንጂ ሕዝቤን የምከስበት ነገር ኖሮኝ አይደለም። 20 ስለዚህም ምክንያት አያችሁና እነግራችሁ ዘንድ ጠራኋችሁ፤ ስለ እስራኤል ተስፋ ይህን ሰንሰለት ለብሻለሁና። ቁጥር ፳፩ - ፴፩ 21 እነርሱም፦ እኛ ከይሁዳ ስለ አንተ ደብዳቤ አልተቀበልንም፥ ከወንድሞችም አንድ ስንኳ መጥቶ ስለ አንተ ክፉ ነገር አላወራልንም ወይም አልተናገረብህም። 22 ነገር ግን ስለዚህ ወገን በየስፍራው ሁሉ እንዲቃወሙ በእኛ ዘንድ ታውቆአልና የምታስበውን ከአንተ እንሰማ ዘንድ እንፈቅዳለን አሉት። 23 ቀንም ቀጥረውለት ብዙ ሆነው ወደ መኖሪያው ወደ እርሱ መጡ፤ ስለ እግዚአብሔር መንግሥትም እየመሰከረ ስለ ኢየሱስም ከሙሴ ሕግና ከነቢያት ጠቅሶ እያስረዳቸው፥ ከጥዋት ጀምሮ እስከ ማታ ድረስ ይገልጥላቸው ነበር። 24 እኵሌቶቹም የተናገረውን አመኑ፥ እኵሌቶቹ ግን አላመኑም፤ 25 እርስ በርሳቸውም ባልተስማሙ ጊዜ፥ ጳውሎስ አንዲት ቃል ከተናገረ በኋላ ሄዱ፤ እንዲህም አለ፦ መንፈስ ቅዱስ በነቢዩ በኢሳይያስ ለአባቶቻችን፦ 26 ወደዚህ ሕዝብ ሂድና፦ መስማትን ትሰማላችሁና አታስተውሉም፥ ማየትንም ታያላችሁና አትመለከቱም፤ 27 በዓይናቸው እንዳያዩ በጆሮአቸው እንዳይሰሙ በልባቸውም እንዳያስተውሉ ተመልሰውም እንዳልፈውሳቸው፥ የዚህ ሕዝብ ልብ ደንድኖአል ጆሮአቸውም ደንቁሮአል ዓይናቸውንም ጨፍነዋል በላቸው ሲል መልካም ተናገረ። 28 እንግዲህ ይህ የእግዚአብሔር ድኅነት ለአሕዛብ እንደ ተላከ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን፤ እነርሱ ደግሞ ይሰሙታል። 29 ይህንም በተናገረ ጊዜ አይሁድ እርስ በርሳቸው እጅግ እየተከራከሩ ሄዱ። 30 ጳውሎስም በተከራየው ቤት ሁለት ዓመት ሙሉ ተቀመጠ፥ ወደ እርሱም የሚመጡትን ሁሉ ይቀበል ነበር፤ 31 ማንም ሳይከለክለው የእግዚአብሔርን መንግሥት እየሰበከ ስለ ጌታ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እጅግ ገልጦ ያስተምር ነበር። ክርስትና ሃይማኖት ነክ መዋቅሮች መጽሐፍ ቅዱስ ተዋህዶ
null
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
c7931a45b4812e75bc8d70ba97ecab0a
01a55ac8addd7e5be7c858c13c650d09
እንዳለ ከበደ ስድስተኛ የድሬዳዋ ከተማ ፈራሚ ሆኗል
የመስመር ተጫዋቹ እንዳለ ከበደ ማረፊያው የምስራቁ ክለብ ሆኗል፡፡ከቀናት በፊት የስድስት ወራት ውል እየቀረው ከመቐለ 70 እንደርታ ጋር በስምምነት የተለያየው እንዳለ ከበደ ከዚህ ቀደም ወደ ድሬዳዋ ለማምራት ጫፍ መድረሱን ዘግበን እንደነበር የሚታወስ ሲሆን አሁን ዝውውሩን በማጠናቀቅ ስድስተኛ አዲስ ፈራሚ ሆኖ ብርቱካናማዎቹን ተቀላቅሏል።ከዚህ ቀደም በአርባምንጭ ከተማ፣ ሲዳማ ቡና እና መቐለ የተጫወተው እንዳለ በጉዳት እየተቸገረ በሚገኘው የድሬዳዋ ስብስብ ጥሩ የመስመር አማራጭ እንደሚሆን ይጠበቃል።ድሬዳዋ በዚህ የዝውውር መስኮት ከእንዳለ ቀደም ብሎ ሄኖክ ኢሳይያስ፣ ክዌክ አንዶህ፣ ኑሁ ፉሴይኒ፣ ምንያምር ጴጥሮስ እና ይስሀቅ መኩርያን አስፈርሟል።© ሶከር ኢትዮጵያ
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/57149
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
1f31d99ff37ee37445c8865567983c90
0bb37dab165b47265eff6aa2e9aa2247
ከጄሰን ድሩሎ ጀርባ ያሉት ኢትዯጵያውያን ተወዛዋዦች
የኢትዮጵያዊነት ቡድን አባላት "ሌትስ ሸት አፕ ኤንድ ዳንስ" የሙዚቃው መጠሪያ ነው። "እስኪ ሌላ ሌላውን ትተን፣ ዝም ብለን እንደንስ" እንደማለት ነው። • በአማርኛ የሚያንጎራጉረው ፈረንሳያዊ የሙዚቃው ቪድዮ ላይ በዳንስ ብቃቱ የገነነው ጄሰን ድሩሎ ሲወዛወዝ ይታያል። ጃፓናዊያኑ ኤንሲቲ 127ቶችም ይውረገረጋሉ። የበርካታ ኢትዮጵያዊያንን ቀልብ የሳቡት ግን በቪድዮው ላይ ያሉት ኢትዮጵያዊያን ተወዛዋዦች ናቸው። የሙዚቃ ቪድዮው ሲጀምር የፑል መጫወቻ ጠረጴዛ ላይ የሚደንስ ኢትዮጵያዊ ህጻን ይታያል። ከዚያም በስኬት ቦርድ የሚንቀሳቀሱ ወጣቶች። ጄሰን ድሩሎ በሙዚቃው እኩሌታ ላይ "ኢትዮጵያውያን ሴቶች እስኪ ትከሻችሁን አሳዩኝ?" በሚል መልክ ኢትዮጵያዊያን እንዲወዛወዙ የሚጠይቅ ስንኝ አለው። • ተፈራ ነጋሽ፡ "በነገራችን ላይ ሙዚቃ አልተውኩም" ኢትዮጵያውያኑ ተወዛዋዦችም እስክስታውን ይወርዱታል። ለንደን፣ ሎስ አንጀለስ፣ ጃማይካ፣ እስያ. . . ሙዚቃው የተለያዩ የዓለም ክፍሎችን ውዝዋዜ ያሳያል። "ኢትዮጵያዊነት" "ኢትዮጵያዊነት" በወጣት ተወዛዋዦች የተመሰረተ የባህላዊ ውዝዋዜ ቡድን ነው። የቡድኑ አባላት ባህላዊ ውዝዋዜን ከዘመነኛ ዳንስ ጋር በማዋሀድ ይታወቃሉ። በርካታ የሙዚቃ ቪድዮዎች ላይ የሚወዛወዙት ወጣቶች፣ በጄሰን ድሩሎ የሙዚቃ ቪድዮ ላይም ተሳትፈዋል። ከዘጠኝ ዓመት በፊት "ኢትዮጵያዊነት"ን የመሰረቱት ስድስት ወጣቶች ዛሬ ዓለም አቀፍ እውቅና ያለው ቪድዮ ላይ ችሎታቸውን ማሳየት ችለዋል። • የሙዚቃ ሕክምና በኢትዮጵያ • የፕሮፌሰሩ ዳንስ ሕንዶችን አስደንቋል ተወዛዋዦቹ 'ባላገሩ አይዶል' የተሰኘውን ውድድር በውዝዋዜ ዘርፍ ማሸነፋቸው ይታወሳል። ኢትዮጵያዊነቶች በጄሰን ድሩሎ የሙዚቃ ቪድዮ ላይ የተሳተፉት የቪድዮው አዘጋጆችን ጥሪ ተከትለው እንደሆነ ከቡድኑ አባላት አንዱ የሆነው ፍቅረማርያም በቀለ ይናገራል። ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገሮች የተውጣጡ ዳንሰኞች ሥራቸውን የሚያሳይ ቪድዮ ለአዘጋጆቹ ካሳዩ በኋላ "ኢትዮጵያዊነት" ተመርጧል። "ልምምድ የምናደርግበት ቦታ መጥተው ቪድዮ ሲቀርጹን በጣም ወደውን ነበር። ይህን ቪድዮ ዓለም ነው የሚያየው። ድሮ የምንሰራው ቪድዮ ግን ሀገር ውስጥ የተገደበ ነበር። እኛ ከምንም በላይ የምንፈልገው ኢትዮጵያዊ ባህላችን ዓለም ላይ ከፍ እንዲል ነው።" ተወዛዋዦቹ ከዚህ ቀደም ከሠሩባቸው የሙዚቃ ቪድዮዎች የቤቲ ጂ፣ የፍቅረአዲስ ነቃጥበብና የዮሴፍ ገብሬን መጥቀስ ይቻላል። • ባህልን በኤሌክትሮኒክ ሙዚቃ የቀመመው ሮፍናን • ዳንስን በሁለተኛ ዲግሪ ኢትዮጵያዊነቶች በውዝዋዜ መላው ሀገሪቱን እንደሚወክሉ ለማሳየት የቡድናቸውን መጠሪያ መምረጣቸውን ፍቅረማሪያም ይናገራል። ፍቅረማሪያም የሙዚቃ ቪድዮው ኢትዮጵያን እንዲሁም ባህሏን እንደሚያስተዋውቅ ያስረዳል። "ውዝዋዜ ቋንቋ ነው" የሚለው ፍቅረማሪያም ተወዛዋዦችን እንደ ባህል አምባሳደር ያያቸዋል። እንደ ጄሰን ድሩሎ ባሉ እውቅ ሙዚቀኞች ቪድዮ ክሊፕ ላይ መታየት የተወዛዋዦቹን እውቅና እንደሚያሳድገው ያምናል። የሙዚቃ ቪድዮው አዘጋጆች የቡድኑን ስድስት አባላትና ኬንያዊያን ተወዛዋዦችን ይዘው ወደ ሐረር ካቀኑ በኋላ ነበር ቪድዮው የተቀረጸው። ቪድዮውን ቀርጾ ለማጠናቀቅ አራት ቀን ወስዶባቸዋል። ቪድዮው ኢትዮጵያ ውስጥ ብዙም ያልታወቁ ባህሎችን ቀንጭቦም ቢሆን እንደሚያሳይ ተወዛዋዡ ያስረዳል። • ሙዚቃ ሳይሰሙ መወዛዋዝ ይችላሉ? ኢትዮጵያ ውስጥ ውዝዋዜ ከማጀቢያነት ባለፈ ራሱን እንደቻለ ጥበብ እንደማይታይ የሚናገረው ፍቅረማሪያም፤ ተወዛዋዦቹ ዓለም አቀፍ መድረክ ላይ መታየታቸው የተዛባውን አመለካካት በመጠኑም ቢሆን እንደሚቀርፈው ተስፋ ያደርጋል።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
3e6770957a146725a353036577e437c2
85ea8fff3017a844da228a3e83d218cb
በትናንትናው ዕለት በአማራ ክልል ከተደረገው የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራና ግድያ ጀርባ አሉ ተብለው የተጠረጠሩት ብርጋዲየር ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ያሉበት እንደማይታወቅ የክልሉ የሰላም ግንባታና ህዝብ ደኅንነት ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ገደቤ ኃይሉ ለቢቢሲ ገልፀዋል።
ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ያሉበት እንደማይታወቅ የአማራ ክልል ገለፀ\nበትናንትናው ዕለት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድርን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮች ግምገማ እያካሄዱ ባሉበት ወቅት ብርጋዲየር ጄኔራሉ በልዩ ኃይሎች ታጅበው እንደመጡና በመጀመሪያም የርዕሰ መስተዳደሩ አጃቢዎች ላይ ተኩስ እንደከፈቱ፤ ቀጥለውም የክልሉ አመራሮች ላይ የተኮሱ ሲሆን በዚህም ሦስቱ እንደተመቱ አቶ ገደቤ ይናገራሉ። • ስለመፈንቅለ መንግሥት ሙከራውና ስለግድያው እስካሁን የምናውቀው •ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል ሰዓረ መኮንን መገደላቸው ተነገረ •መፈንቅለ መንግሥቱና የግድያ ሙከራዎች "ጥቃቱ በከፍተኛ ደረጃ የተቀነባበረ ነው" ያሉት አቶ ገደቤ የፀጥታ ቢሮ፣ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የርዕሰ መስተዳድሩ ቢሮና የአዴፓ ጽህፈት ቤት ላይም ጥቃት እንደደረሰ ገልፀዋል። "ጥቃቱ ያልተጠበቀ ነው" የሚሉት አቶ ገደቤ በወቅቱም የክልሉ ፀጥታ ኃይል አካባቢውን ለመቆጣጠር ጥረት ባደረገበት ወቅት ብርጋዲየር ጄኔራሉ እንዳመለጡ ገልፀው፤ ከርዕሰ መስተዳድሩና ከአማካሪያቸው በተጨማሪ አጃቢዎቻቸው የተገደሉ ሲሆን እስካሁን ባለው ሁኔታ የሟቾች ቁጥር እንደማይታወቅ ገልፀዋል። በባህርዳር ሁኔታዎች ቢረጋጉም የርዕሰ መስተዳድሩን ሞት ተከትሎ ከተማዋ በድንጋጤ መዋጧን አቶ ገደቤ ተናግረዋል። "ርዕሰ መስተዳድሩ ለክልሉ ህዝብ ሌት ተቀን የሚሰራ ሰው ነበር፤ እንዲህ ባለ ሁኔታ መሰዋቱ በጣም አስደንጋጭና አሳዛኝ ነው" በማለት አቶ ገደቤ ለቢቢሲ ገልፀዋል።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
feaafa2567d9b138522345ec3a0f92f2
fea03ce6e5594c362bf8c0d02ccdaa6a
የውድድር ዘመኑ ምርጥ 11
ወርሃ ነሐሴ ላይ የጀመረው የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ በማንችስተር ሲቲ አሸናፊነት ተጠናቋል። ዌስትብሮም፣ ስቶክና ስዋንሲ ደግሞ ከሊጉ ሲወርዱ፤ አርሴናል ደግሞ ከዌንገር ጋር የነበረው የ22 ዓመታት ቁርኝት ቋጭቷል። እነዚህ ሁሉ እንዳሉ ሆነው የውድድር ዘመኑ ምርጥ አስራ አንድ ውስጥ መካተት የቻሉት ምርጥ 11 ተጫዋቾች እነማን ናቸው? ግብ ጠባቂ ዳቪድ ዴ ሂያ (ማንቸስተር ዩናይትድ) ሆዜ ሞሪኖ ዴ ሂያ ወደ ሪያል ማድሪድ ከመሄድ ይልቅ ዩናይትድ እንዲቆይ ያሳመኑት ጊዜ ትልቅ ነገር እንደሰሩ እሙን ነበር። ዴ ሂያ በዚህ የውድድር ዘመን ያሳየው ብቃት እጅግ ማራኪ ነበር። ምንም እንኳ ሞሪኖ ለዚህ ድንቅ በረኛ የሚመጥን ተከላካይ መስመር ሊሰሩ ባይችሉም። ትዝ የሚላችሁ ከሆነ ሞሪኖ ከቼልሲ ጋር ዋንጫ ሲያነሱ ፒተር ቼክ በረኛ ነበር፤ ዊሊያም ጋላስ፣ ጆን ቴሪና ሪካርዶ ካርቫልሆ ደግሞ ተከላካዮች። ዴ ሂያ እነዚህን የመሳሰሉ ተከላካዮች ቢኖሩት ኖሮ ዩናይትድ ዋንጫ የማንሳት አቅም ነበረው። ያም ሆነ ይህ ዴ ሂያ በ18 ጨዋታዎች ምንም ጎል ያልተቆጠረበት ግብ ጠባቂ ሆኖ የወርቅ ጓንቱን መውሰድ ችሏል። ተከላካይ መስመር ዎከር፣ ዳንክ፣ ኦታሜንዲ እና ያንግ ካይል ዋከር (ማንቸስተር ሲቲ) - ፔፕ ጋርዲዮላ ዎከርን ከቶተንሃም በ50 ሚሊየን ዩሮ ሲገዛው ጥርጣሬ ገብቶኝ ነበር። ነገር ግን በመጀመሪያ ጨዋታው ያሳየውን ብቃት ስመለከት ሲቲዎች ለተጫዋቹ ያወጡት ወጭ የማያስቆጭ እንደሆነ ገባኝ። በምርጥ የመከላከል አቋም ላይ በመገኘት ቡድኑ ዋንጫ እንዲያነሳ ከማገዙም በላይ ለጎል የሚሆኑ ኳሶችንም ሲያቀብል ነበር። ሊዊ ዳንክ (ብራይተን) - ይህ ተጫዋች በቻምፒንሺፕ ደረጃ ሲጫወት ተመልክቸዋለሁ፤ በፕሪሚዬር ሊጉ ያየሁት ግን ፍፁም ሌላ ሆኖ ነው። የቶተንሃሙ ጆን ቬርቶኸንን መርጬ መገላገል እችል ነበር፤ ነገር ግን ብራይተብ ጥሩ ይሁንም አይሁን ዳንክ በዚህ ዓመታ ያሳየው ብቃት ያለምንም ጥርጥር ሊያስመርጠው ይገባል። 56 ጎል ሊሆኑ የሚችሉ ኳሶችን ጠራርጎ በማስወጣትም ከሁሉም የላቀ መሆኑን አሳይቷል። ኒኮላስ ኦታሜንዲ (ማንቸስተር ሲቲ) - ይህ ልጅ አቋሙ የሚዋዥቅ ነበር፤ ነገር ግም በዚህ ዓመት ዘላቂ የሆነ ብቃት አሳይቶናል። ቨንሴንት ኮማፓኒ በተጎዳብት ሰዓትም እጅግ ወሳኝ ተጫዋች ሆኖ መገኘት ችሏል። አልፎም ከማንኛውም የሊጉ ተጫዋች በበለጠ ስኬታማ ኳሶችን ለቡድን አጋሮቹ ማቀበል ችሏል። አሽሊ ያንግ (ማንቸስተር ዩናይትድ) - ያንግ በዩናይትድ ያበቃለት ተጫዋች መስሎኝ ነበር። ከአንቶኒዮ ቫልንሲያ በመቀጠል ከክንፍ ተጫዋችነት ወደ ተመላላሽ ተከላካይነት የተቀየረ መሆንም ችሏል። በዚህ የወድድር ዘመን ባሳየው ብቃትም በ32 ዓመቱ ለእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን እንዲጠራ ሆኗል። አማካዮች ደ ብረይን፣ ፈርናንዲኖ እና ሲልቫ ኬቭን ዴ ብረይን (ማንቸስተር ሲቲ) - በዚህ የውድድር ዘመን ካየኋቸው ተጫዋቾች ሁላ እንደ ኬቭን አንጀቴን ያራሰው የለም። እንደው ሞሃመድ ሳላህ የሚገርም ብቃት ላይ መገኘቱ እንጂ የውድድር ዘመኑ ምርጥ መሆን ይገባው የነበረ ልጅ ነው። እንግዲህ እግር ኳስ እንዲህ ነው። ይህን ተጫዋች የውድድር ዘመኑ ምርጥ ተጫዋቾች መሃል ከማካተት ያለፈ ነገር ማድረግ ብችል አደርግ ነበር። ፈርናንዲንሆ (ማንቸስተር ሲቲ) - ክሎውድ ማኬሌሌ ከሪያል ማድሪድ፤ ጋርካምቢያሶ ደግሞ ከኢንተር ጋር መሰል ድል መጋራት ችለዋል። ፈርናንዲኖ ደግሞ ከሲቲ ጋር ስኬትን ማጣጣም ችሏል። እኒህ ተጫዋቾች ራሳቸውን ከእነ ዚነዲን ዚዳን እኩል ባይመድቡም ለቡድናቸው ድል የማይቆፍሩት ድንጋይ የለም። ዳቪድ ሲልቫ (ማንቸስተር ሲቲ) - ሲልቫ ለሲቲ በጣም ለየት ያለ ግልጋሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ ተጫዋች...
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
e6dbe55c6979cb6139f3b124c835dc0c
50d6a49946ed7430d5f3cfb75f52bf1b
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማትን በዘላቂነት መምራት የሚያስችል መሪ ዕቅድ ይፋ ሆነ
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማትን በዘላቂነት መምራት የሚያስችል መሪ ዕቅድ ይፋ ሆነ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማትን በዘላቂነት መምራት የሚያስችል ስፓሻል መሪ ዕቅድ ይፋ ተደረገ።የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሸን የኢንዱስትሪውን ዘርፍ ዕድገት ለማሳካትና ለመምራት የሚያስችል ሀገራዊ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ስፓሻል ጥናት ረቂቅ ሪፓርት ላይ የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል።በመድረኩ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ሃላፊዎች እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።በዚህ ወቅት ንግግር ያደረጉት የኢንዱስትሪ ፓርኮች ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሳንዶካን ደበበ ለሚቀጥሉት 20 ዓመታት የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ዘለቄታዊ ልማት የሚመራ ስፓሻል ጥናት መዘጋጀቱን ተናግረዋል።ጥናቱ እንደ አገር የመጀመሪያ መሆኑንና ኢትዮጵያ ያላትን ሀብት የመሬት ሁኔታ በማየት የተዘጋጀ ነው ብለዋል።አሁን ያሉትን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ከመምራት ባለፈ ወደ ፊት የሚመሰረቱ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን ከምስረታቸው ጀምሮ በማገዝና በመምራት ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል።የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ፣ የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችን ለመመለስና በየትኛው አካባቢ ምን አይነት ኢንደስትሪ ፓርክ መገንባት አለበት የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችል መሆኑንም ገልጸዋል።የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማትን በዘላቂነት ለመምራት ይፋ በሆነው ስፓሻል መሪ ዕቅድ ላይ የመድረኩ ተሳታፊዎች እየተወያዮበት ሲሆን በዕቅዱ ላይ መሻሻል ያለባቸውን ነገሮች እንደሚያነሱ ይጠበቃል።(ምንጭ፡- ኢዜአ)  
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://waltainfo.com/am/%e1%8b%a8%e1%8a%a2%e1%8a%95%e1%8b%b1%e1%88%b5%e1%89%b5%e1%88%aa-%e1%8d%93%e1%88%ad%e1%8a%ae%e1%89%bd-%e1%88%8d%e1%88%9b%e1%89%b5%e1%8a%95-%e1%89%a0%e1%8b%98%e1%88%8b%e1%89%82%e1%8a%90%e1%89%b5/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
38a4692faa7ec0cae4ffadc1d2b664a7
1fa894b235351a4c78e766f62d8a0d19
ማራዶና የተሳካ የአንጎል ቀዶ ህክምና ተደረገለት
  የቀድሞው የአለማችን የእግር ኳስ ኮከብ አርጀንቲናዊው ዲያጎ አረማንዶ ማራዶና፣ ባለፈው ሳምንት የተሳካ የአንጎል ቀዶ ህክምና እንደተደረገለት መነገሩን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡በደም ማነስ ሲሰቃይ የቆየው የ60 አመቱ ማራዶና ባለፈው ሰኞ ቦነስ አይረስ ውስጥ ወደሚገኝ አንድ ክሊኒክ መወሰዱን ያስታወሰው ዘገባው፤ በአንጎሉ ውስጥ የደም መርጋት ችግር በመገኘቱ 80 ደቂቃ የፈጀ የተሳካ ቀዶ ህክምና እንደተደረገለት የግል ሃኪሙ መናገራቸውን አመልክቷል፡፡ማራዶና ከቀዶ ህክምናው በኋላ በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኝና እንዳገገመ የጠቆመው ዘገባው፤ በርካታ አድናቂዎቹና ደጋፊዎቹ ከሆስፒታል ሲወጣ ጠብቀው ስሙን እየጠሩ ደስታቸውን እንደገለጹለትም አስረድቷል፡፡
4ዓለም አቀፍ ዜና
https://www.addisadmassnews.com/index.php?option=com_k2&view=item&id=26713:%E1%88%9B%E1%88%AB%E1%8B%B6%E1%8A%93-%E1%8B%A8%E1%89%B0%E1%88%B3%E1%8A%AB-%E1%8B%A8%E1%8A%A0%E1%8A%95%E1%8C%8E%E1%88%8D-%E1%89%80%E1%8B%B6-%E1%88%85%E1%8A%AD%E1%88%9D%E1%8A%93-%E1%89%B0%E1%8B%B0%E1%88%A8%E1%8C%88%E1%88%88%E1%89%B5&Itemid=212
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
d633217e2c670b5057d561975d7d1fae
434b92078b4ab7fdca743f72229cdd24
በአማራ ክልል ተጨማሪ ሁለት ሰዎች ላይ የኮሮናቫይረስ ተገኘባቸው።
ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 20/2012 ዓ.ም (አብመድ) በአማራ ክልል በ24 ሰዓታት ውስጥ በ796 ሰዎች ናሙና ላይ በተደረገ ምርመራ ሁለት ሰዎች የኮሮናቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ ቫይረሱ የተገኘባቸው  አንድ የ25 ዓመት ወንድ እና አንዲት የ35 ዓመት ሴት ናቸው፡፡
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.amharaweb.com/%e1%89%a0%e1%8a%a0%e1%88%9b%e1%88%ab-%e1%8a%ad%e1%88%8d%e1%88%8d-%e1%89%b0%e1%8c%a8%e1%88%9b%e1%88%aa-%e1%88%81%e1%88%88%e1%89%b5-%e1%88%b0%e1%8b%8e%e1%89%bd-%e1%88%8b%e1%8b%ad-%e1%8b%a8%e1%8a%ae/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
376346d2e47b88e3226ce0df21f87382
75135bd5a22fd749c65f81b0faee473b
የውጭ አገር ስደተኞች የሥራ ዕድል እንዲያገኙ ሊፈቀድ ነው
ኢትዮጵያ ይኼንን በመፍቀዷ ለ200 ሺሕ ሥራ አጦች ዕርዳታ ታገኛለችኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ የውጭ አገሮች ስደተኞች ከመጠለያ ካምፖች ወጥተው መኖር፣ መዘዋወርና ተለይተው በሚፈቀዱ የሥራና የንግድ እንቅስቃሴዎች እንዲሳተፉ የሚፈቅድ ረቂቅ የሕግ ሰነድ ለፓርላማ ቀረበ፡፡ረቂቅ ሰነዱ በሥራ ላይ የሚገኘውን የስደተኞች ጉዳይ አዋጅ አሻሽሎ እንደ አዲስ የሚደነግግ ሲሆን፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም ሐሙስ ሰኔ 21 ቀን 2010 ዓ.ም. በረቂቁ ላይ ተወያይቶ ለዝርዝር ዕይታ ለቋሚ ኮሚቴ መርቶታል፡፡ረቂቁ በኢትዮጵያ የሚገኙ ስደተኞች ከመጠለያ ካምፖች ውጪ ለመኖር እንዲችሉ፣ በየትኛውም የአገሪቱ ክፍል የመዘዋወር ነፃነትን የሚያጎናፅፍ ድንጋጌ ይዟል፡፡ከዚህ በተጨማሪም የባንክ ሒሳብ የመክፈት፣ መንጃ ፈቃድና መታወቂያ ማውጣት እንዲችሉ መብት የሚሰጥ ድንጋጌ የያዘ ሲሆን፣ ከ20 ዓመት በላይ በኢትዮጵያ የኖሩ ስደተኞች አግባብ ባለው ሕግ የኢትዮጵያ ዜግነትን እንዲያገኙም በሰነዱ ተካቷል፡፡የሥራ ዕድልን በተመለከተም ለውጭ አገር ዜጎች ከተሰጡ መብቶች እጅግ የተሻለውን ያህል ተጠቃሚ እንዲሆኑ መብት የሚሰጥ ድንጋጌ በረቂቁ ተካቷል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ በተለየ ሁኔታ ለስደተኞች የሚፈቀዱ የሥራ ዘርፎች ተለይተዋል፡፡ እርሻ፣ ኢንዱስትሪ፣ አነስተኛና ጥቃቅን የዕደ ጥበባትና የንግድ ዘርፎች ተዘርዝረዋል፡፡ንብረት የማፍራትና የማስተላለፍ፣ የአዕምሮ ውጤቶች ጥበቃ እንዲያገኙ፣ እንዲሁም በኢትዮጵያውያንና በስደተኞች መካከል መድልኦ እንደማይደረግ የሕግ ሰነዱ ይዘረዝራል፡፡መንግሥት ይኼንን የሚፈቅድ ከሆነ ለኢትዮጵያውያን ሥራ አጦች የጋራ ተጠቃሚነትን የሚውል የሥራ ዕድል መፍጠሪያ ዕርዳታ እንደሚገኝ የሰነዱ ማብራርያ ይገልጻል፡፡ከእነዚህም መካከል ለ100 ሺሕ ሰዎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር የሚያስችሉ ኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ በተመሳሳይ 100 ሺሕ ሰዎችን በመስኖ የታገዘ የእርሻ ልማት እንዲያለሙ እንደሚያስችል እንደሆነ ይገልጻል፡፡ ለዚህም ሲባል የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ የዓለም ባንክ፣ የአውሮፓ ኅብረትና ሌሎች አገሮች የኢንቨስትመንት ካፒታል በዕርዳታ ለመስጠት ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ስምምነት ማድረጋቸውን ያስረዳል፡፡የኢንዱስትሪ ፓርኮቹ ሲጠናቀቁ ከሚፈጠረው ለ100 ሺሕ ሰዎች የሚሆን የሥራ ዕድል ውስጥ 70 በመቶ (70 ሺሕ) ለኢትዮጵያውያን የሚደለደል ሲሆን፣ ቀሪው 30 በመቶ (30 ሺሕ) ለስደተኞች እንደሚሆን ማብራርያው ይገልጻል፡፡በተመሳሳይ በእርሻ ልማት የሥራ ዕድል ለመፍጠር 10 ሺሕ ሔክታር መሬት የተዘጋጀ መሆኑን፣ በዚህም ከሚፈጠረው 100 ሺሕ የሥራ ዕድል 70 በመቶ ለኢትዮጵያውያን ቀሪውን 30 በመቶ ደግሞ ለስደተኞች እንደሚደለድል ይገልጻል፡፡በመሆኑም በሁለቱ የሥራ ዘርፍች ከሚፈጠረው የሥራ ዕድል ውስጥ 60 ሺሕ ስደተኞች ተጠቃሚ ይሆናሉ፡፡
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.ethiopianreporter.com/article/11583
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
bac7233d9fae7a26cbdc4bb47c06f6f7
0ecf387836bdb6bf469520ba514733ce
የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን እና የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ለመጀመሪያ ጊዜ ተገናኝተዋል።
የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪምና የሩስያው ፑቲን ተገናኙ\nሁለቱ መሪዎች በሩስያ ምስራቃዊት ከተማ ቭላዲቮስቶክ አቅራቢያ በሚገኝ ረስኪ የተባለ ቦታ ነበር የተገናኙት። ኪም እና ፑቲን የኮርያ ሰርጥን ከኒውክሌር ነጻ ስለማድርግ ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል። • የሰሜን ኮርያ የኒዩክሌር ሚሳየል ሙከራ ደቡብ ኮርያንም ልምምድ እንድታካሂድ አስገድዷል በተጨማሪም ኪም ጆንግ ኡን ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ያደረጉት ውይይት መክሸፉን ተከትሎ፤ ኪም ከሩስያው ፕሬዘዳንት ድጋፍ ሊጠይቁ ይችላሉ። ኪም ትላንት ሩስያ ሲገቡ የሀገሪቱ ባለስላጣኖች ሞቅ ያለ አቀባባል አድርገውላቸዋል። በወታደራዊ ባንድ ሙዚቃ ዘና እንዲሉ ከተደረገ በኋላ ዘወትር ከመኪናቸው ጎን ለጎን በሚሮጡ ጠባቂዎቻቸው ታጅበው ተወስደዋል። "ጉብኝቴ ውጤታማ እና ጠቃሚም ይሆናል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ" ሲሉ ኪም ለሩስያ የቴሌቭዥን ጣቢያ ተናግረዋል። • ኪም ጆንግ ኡን የጦርነት ልመና ጥሪ በማድረግ ተወቀሱ የሰሜን ኮርያና የሩስያን የሁለትዮሽ ግንኙነትን ከማጠናከር ባለፈ ከፕሬዝዳንት ፑቲን ጋር ስለ ኮርያ ሰርጥ ጉዳይ ለመወያየት እቅድ እንደያዙም ኪም ተናግረዋል። የሩስያ መንግሥት ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ የኮርያ ሰርጥ የኒውክሌር ጉዳይን በተመለከተ አሁን ላይ ውጤታማ ሊሆን የሚችል ዓለም አቀፍ ጥረት እምብዛም አለመኖሩን ተናግረዋል። እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2003 ተጀምሮ የቆመው የሰሜን ኮርያ፣ ደቡብ ኮርያ፣ ቻይና፣ ጃፓን፣ ሩስያና አሜሪካ ውይይትን ቃል አቀባዩ ጠቅሰዋል። ሰሜን ኮርያና ሩስያ ምን ይፈልጋሉ? ተንታኞች እንደሚሉት፤ የኪም እና ዶናልድ ትራምፕ ውይይት ፍሬ ስላላፈራ ሰሜን ኮርያ እንደ ሩስያ ያሉ ወዳጆች ከጎኗ ማሰለፍ ግድ ይላታል። ሰሜን ኮርያ በምጣኔ ሀብት ረገድም ብቸኛ አጋሯ አሜሪካ አንዳልሆነች ማሳየት ትፈልጋለች። • ሰሜን ኮርያ የአሜሪካውያንን አጽም መለሰች ሩስያ በበኩሏ በኮርያ ሰርጥ ጉዳይ ቀንደኛ ተዋናይ መሆን ትፈልጋለች። ፑቲን ከኪም ጋር ለመገናኘት በጉጉት ሲጠብቁ ነበርም ተብሏል። እንደ አሜሪካና ቻይና ሁሉ ሩስያም የሰሜን ኮርያ ኒውክሌር ክምችት እንቅልፍ ይነሳታል።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
8da5a086dd0f4e306b3af80473996a6a
cff6585f313050c248aa0f04144e334a
አርባምንጭ ከተከታታይ ሽንፈት በኋላ ድል ሲቀናው ድቻ እና ድሬዳዋ ነጥብ ተጋርተዋል
በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 5ኛ ሳምንት ጨዋታ አርባምንጭ የውድድር አመቱን የመጀመርያ ሶሰት ነጥብ ሲያስመዘግብ ወላይታ ድቻ ከ ድሬዳዋ ከተማ አቻ ተለያይቷል። የወልዲያ እና መቐለ ከተማ ጨዋታ ደግሞ ሳይደረግ ቀርቷል።በተከታታይ ጨዋታዎች ሙሉ ሶስት ነጥብ ማግኝት ተስኖት የነበረው አርባምንጭ ከተማ መከላከያን አስተናግዶ 2-0 አሸንፏል። የመጀመርያው አጋማሽ ያለ ግብ የተጠናቀቀ ሲሆን 62ኛው ደቂቃ ላይ ወንድሜነህ ዘሪሁን ከረጅም ርቀት የመታት ኳስ የግቡን ብረት ገጭታ ስትመለስ ከተስፋ ቡድን ያደገው አጥቂው ብርሀኑ አዳሙ አዞዎቹን ቀዳሚ አድርገዋል፡፡ የጨዋታው መደበኛ ክፍለ ጊዜ ተጠናቆ በጭማሪ ደቂቃ ላይ በግምት 35 ሜትር ርቀት ላይ ፀጋዬ አበራ አክርሮ የመታት ኳስ ከመረብ አርፋ ጨዋታው በአርባምንጭ 2-0 አሸናፊነት ተጠናቋል።ከጨዋታው በኃላ አሰልጣኝ ፀጋዬ ኪ/ማርያም ለሶከር ኢትዮጵያ በሰጡት አስተያየት “ውጤቱ ይገባን ነበር። በሚያስፈልገን ሰአተ አግኝተናል።” ሲሉ የመከላከያው ምንያምር በበኩላቸው ” እድል ከኛ ጋር አልነበረችም ማሸነፍ ይገባን ነበር” ብለዋል፡፡ሶዶ ላይ የተገናኙት ወላይታ ድቻ እና ድሬዳዋ ከተማ በአቻ ውጤት ጨዋታቸውን አጠናቀዋል። በመጀመሪያው አጋማሽ ድሬዳወች ገና ጨዋታው እንደተጀመረ ሄይቲያዊው አማካይ ሳውሬል ኦልሪሽ የግብ ጠባቂውን አቋቀም ተመልክቶ ከመሀለኛው የሜዳ ክፍል የላካት ኳስ ከመረብ አርፋ ድሬዎች መሪ መሆን የቻሉ ሲሆን 43ኛ ደቂቃ ላይ ቶጎዊው አጥቂ ጃኮ አራፋት የጦና ንቦችን አቻ አድርጎ ተጨማሪ ጎል ሳይቆጠር በዚሁ ውጤት ተጠናቋል።ወልዲያ ላይ ዛሬ ሊደረግ የነበረው የወልዲያ እና መቐለ ከተማ ጨዋታ ከስታድም ውጪ በከተማው መንገዶች በተነሳ ግጭት ምክንያት ሳይደረግ ቀርቷል።
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/31647
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
9e716769cbc740c67d615a6bb1fa78f4
8b67c44e95bf2df05a78e736e824340f
ጠ/ሚኒስትሩ በሰ.አሜሪካ የስፖርት ፌስቲቫል ላይ እንዳይገኙ ተወሠነ
  ከአንድ ወር በኋላ በሰሜን አሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ፣ ለ35ኛ ጊዜ በሚካሄደው በአሜሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የስፖርት ፌስቲቫል ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ለመገኘት ያቀረቡት ጥያቄ ተቀባይነት አላገኘም ተባለ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሣምንት በፊት ለስፖርት ፌስቲቫል አዘጋጁ ፌዴሬሽን፤ “በፕሮግራማችሁ ላይ ከኢትዮጵያውያን ጋር ልገናኝ” የሚል ደብዳቤ መፃፋቸው የታወቀ ሲሆን ፌዴሬሽኑም ይገኙ አይገኙ የሚለውን የወሠነው በአባላቱ ድምፅ ነው ተብሏል፡፡ 14 የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት “ዶ/ር አብይ መገኘት የለባቸውም” የሚል ድምፅ ሲሠጡ፣ “11 ደግሞ ይገኙ” ብለዋል፡፡ 8 ድምፀ ተአቅቦ ማድረጋቸው ታውቋል፡፡ ፌዴሬሽኑ በድረ ገፁ በሠጠው መግለጫ፤ “አብዛኛው አመራር አይገኙ የሚል ውሣኔ ያሣለፉት እንዳይገኙ ከመፈለግ ሣይሆን ጥያቄው የቀረበበት ጊዜ አጭር በመሆኑ፣ ሁኔታዎች አገናዝቦ ለመወሰን አመቺ ባለመሆኑ ነው” ብሏል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ፤ በቀጣይ በሚደረገው ተመሣሣይ የስፖርት ፌስቲቫል ላይ የመገኘት እድል እንዲሰጣቸው መመቻቸቱንና ጥያቄያቸው ለቀጣይ መሸጋገሩንም ፌደሬሽኑ አስታውቋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ፣ በሠሜን አሜሪካና ካናዳ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሚሰባሰቡበት የስፖርት መድረክ ላይ ልገኝ ብለው የጠየቁ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ መሪ ናቸው ያለው ፌዴሬሽኑ፤ ይህን ጥያቄያቸውንም በከፍተኛ ሁኔታ እናከብራለን፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩም የኢትዮጵያን የፖለቲካ ችግር ለመፍታት እያደረጉ ያለውን ጥረት እናበረታታለን ብሏል፡፡ በሐምሌ ወር በዳላስ- ቴክሳስ በሚካሄደው የኢትዮጵያና ትውልደ ኢትዮጵያኑ የስፖርት ፌስቲቫል ላይ ዶ/ር አብይ ይገኙ አይገኙ የሚለው ጉዳይ የፌደሬሽኑን አባላትና በውጪ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሲያወያይ መሠንበቱ ታውቋል፡፡
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.addisadmassnews.com/index.php?option=com_k2&view=item&id=21894:%E1%8C%A0-%E1%88%9A%E1%8A%92%E1%88%B5%E1%89%B5%E1%88%A9-%E1%89%A0%E1%88%B0%E1%8A%A0%E1%88%9C%E1%88%AA%E1%8A%AB-%E1%8B%A8%E1%88%B5%E1%8D%96%E1%88%AD%E1%89%B5-%E1%8D%8C%E1%88%B5%E1%89%B2%E1%89%AB%E1%88%8D-%E1%88%8B%E1%8B%AD-%E1%8A%A5%E1%8A%95%E1%8B%B3%E1%8B%AD%E1%8C%88%E1%8A%99-%E1%89%B0%E1%8B%88%E1%88%A0%E1%8A%90&Itemid=180
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
8218379495565ae5c785f25e03936b20
c5cf58fb7aa081bd7e0ea630c4a5e527
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን የ2012 ዓ.ም ሁሉም የሊግ ውድድሮች መሰረዙን ትላንት አስታውቋል። ውድድሩ በመሰረዙም አሸናፊ እና ወራጅ ቡድን አለመኖሩን አስታውቆ፤ ኢትዮጵያ በሚቀጥለው ዓመት የአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ እና የኮንፌደሬሽን ካፕ ላይ እንደማትሳተፍ ገልጿል።
በእግር ኳስ በፌዴሬሽኑ ውሳኔ ላይ የክለብ አመራሮች ምን ይላሉ?\nየ17ኛ ሳምንት ጨዋታዎችን በተከናወነበት ሊግ ቀሪ 13 መርሃ ግብሮች መካሄድ ይጠበቅባቸው ነበር። ይህም 45 በመቶ የሚሆነውን ውድድር ይሸፍናል። የኮሮናቫይረስ ወረርሽኘን ምክንያት በማድረግ የተላለፈውን ውሳኔ በተመለከተ የሊጉ ክለቦች ምን ይላሉ? የባህር ዳር ከነማ ስፖርት ክለብ ሥራ አስኪያጅ አቶ ልዑል ፍቃዱ፤ የፌደሬሽኑን ውሳኔ የሰሙት ከመገናኛ ብዙሃን መሆኑን ጠቅሰው "የተወሰደው እርምጃ ጥሩ እና ወቅታዊ ነው" ሲሉ ይገልጻሉ። በዚህ ሃሳብ የሚስማሙት የፋሲል ከነማ ክለብ ሥራ አስኪያጅ አቶ አብዮት ብርሃኑ ናቸው። እንደ አቶ አብዮት ከሆነ "ከየትኛውም ነገር በላይ የሰው ልጅ ህይወት ስለሚበልጥ" ውድድሩ በመቋረጡ ላይ ቅሬታ የላቸውም። የመቀሌ 70 አንድርታ ክለብ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሽፈራው ተክለሃይማኖት ግን "የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ውሳኔ ወቅታዊ ነው። ቢሆንም እንደግለሰብ የውሳኔው ሂደት ላይ ቅሬታ አለኝ። አሰልጣኞችን በማነጋገር ብቻ ነው ጥናት ያደረጉት። የክለብ ኃላፊዎችን አላነጋገሩም። ከባለቤቱ መረጃ ማግኘት ነበረባቸው። ውሳኔው ላይ ቁንጽል መረጃ ነው የወሰዱት" ይላሉ። የባህር ዳር ከነማ ስፖርት ክለብ ሥራ አስኪያጅ አቶ ልዑልም በዚህ ሃሳብ ይስማማሉ። "ክለቦች የራሳቸውን ሃሳብ ያቀረቡበት ነገር ያለ አይመስለኝም፤ እንደክለብ ምንም አስተያት አላችሁ በሚል የቀረበ ነገር የለም። እንዲህ ቢሆን? ያለው ነገር የለም" ብለዋል። "የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር ተነጋግረዋል" የሚሉት የፌደሬሽኑ ጊዜያዊ ዋና ጸሐፊ የሆኑት አቶ ባህሩ ጥላሁን ናቸው። "የሊጉ አብይ ኮሚቴ ወይም ሼር ካምፓኒ ከሚመለከታቸው ክለቦች እና ከውድድርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ጋር እንዲወያይ አቅጣጫ ተሰጥቶት ነበር" ይላሉ። "እነዚህን ሂደቶች ተከትለናል። ሼር ካምፓኒው ከአብይ ኮሚቴ እና ከውድድርና ስነ-ርዓት ኮሚቴ ጋር በመሆን ምክረ ሃሳብ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አቀረበ። ፌደሬሽኑ ደግሞ ከመንግስትም የተቀመጠውን አቅጣጫ በመመልከት ውሳኔ አስተላለፈ" ባይ ናቸው። "ከሊጉ ጋር የተያያዘውን ሼር ካምፓኒው ኃላፊነት እንዲወስድ የተደረገ ሲሆን አብይ ኮሚቴው ደግሞ ከክልቦች የተወጣጡ ስለሆኑ ተሳትፈዋል" ብለዋል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ክለቦቹን የሚወክለውን ሼር ካምፓኒ አናግሬያለሁ ቢልም ክለቦቹ ግን በዚህ ተቃራኒ ቆመዋል። "ሼር ካምፓኒ ተቋቁሟል እኛም አባል ነን። ካምፓኒው እና ፌደሬሽኑ ተነጋግረው ሊሆን ይችላል። ካምፓኒው ግን ክለቦቹን አላናገረም" ያሉት አቶ ልዑል ናቸው። አቶ ሽፈራውም ተመሳሳይ አቋም አላቸው። "ለግብር ይውጣ ሼር ካምፓኒ ቢያናግሩም እኛን ካማፓኒው ማናገሩን ማወቅ ነበረባቸው። ዓለም አቀፉ የእግርኳስ አስተዳዳሪ /ፊፋ/ ፍኖተ ካርታ ክለቦችን አናግራችሁ ለሃገር ተስማሚ የሆነ ውሳኔ ላይ እንድትደርሱ ብሏል። እኛ አስተዳዳሪ አካላችን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ነው። አወዳዳሪ አካላችን ደግሞ ሼር ካምፓኒው ነው። በቴክኖሎጂም ቢሆን ሃሰባችንን ማድመጥ ነበረበት" ብለዋል። ሌላው የውሳኔው ወቅታዊነት ላይ የሚቀርብ ጥያቄ ነው። የስፖርት ጋዜጠኛው መኳንንነት በርሄ እንደሚለው ያነጋገራቸው አብዛኛዎቹ ክለቦች በጉዳዩ ላይ ውይይት እንዳላደረጉ እንደገለጹለት አስታውቋል። ለዚህም "ክለቦችን ያላማከለ የሊግ ካምፓኒውንም የፈጠነ ይመስለኛል። አንዳንድ ክለቦችን ሳነጋግር የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽንም ሆነ ሊግ ካምፓኒው አላነጋገረንም የሚል ሃሳብ አንስተዋል። ክለቦች ሊግ መስርተዋል። ሊጉ ያለ ክለቦች ምንም ነው። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ውሳኔው ትንሽ የፈጠነ ይመስለኛል።" የፌደሬሽኑ ጊዜያዊ...
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
5853d3044f071ede7343f66e0462f5c3
dea498baf41a827a47bd7a8f44a6c2b2
በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ 100 ቀናት ውስጥ ዶላር በጥቁር ገበያ ለምን ቀነሰ?
የውጭ ምንዛሬ ወትሮም የአንድን አገር ኢኮኖሚያዊ ጤና የሚያሳብቅ የትኩሳት መለኪያ ብልቃጥ 'ቴርሞሜትር' ነው። በተለይም ጥቁር ገበያ ከመንግሥት ቁጥጥር ያፈነገጠ፣ በገበያ ፍላጎት የሚመራ በመሆኑ የተሻለውና የሚታመነው የትኩሳት መለኪያ ተደርጎ ይወሰዳል። ታዲያ የታመመው ምጣኔ ሐብታችን ትኩሳቱ እየበረደለት ይሆን? ቢቢሲ በዚህ ድንገተኛ የጥቁር ገበያ ዶላር ተመን ማሽቆልቆል ዙርያ የምጣኔ ሃብት ባለሞያዎችን አወያይቷል። • የብር የመግዛት አቅም መቀነስ አንድምታዎች • ዓለም አቀፍ የንግድ ተቋማትና ኢትዮጵያ - 'ፒዛ ሃት' "የድንበር ቁጥጥሩ ይመስለኛል..." ዶክተር ቆስጠንጢኖስ የዋጋ ከፍና ዝቅ መሬት ላይ ባለ ነገር ብቻ አይከሰትም። በተለይም የምንዛሬ ምጣኔ አንዳች ኮሽታ በተሰማ ቁጥር ሊናጥ የሚችል ድንጉጥ ገበያ ነው። ዶክተር ቆስጠንጢኖስ ከዚሁ ጋር የሚያያዝ ምሳሌን ያነሳሉ። "የአሜሪካ "ትሬዠሪው" በሚሰበሰብበት ጊዜ ማርኬቱ ገና ስብሰባው ሊካሄድ ነው ሲባል ነው መናወጥ የሚጀምረው" በተመሳሳይ ከሰሞኑ በድኀረ ዐብይ የተሰሙ፣ የታዩ፣ የተገመቱና የተከሰቱ ዐበይት ክንውኖች የጥቁር ገበያውን ዶላር አደብ ሳያስገዙት አልቀሩም። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ የውጭ ምንዛሬ ጥሪ ለዳያስፖራው በይፋ ማቅረባቸው፣ በሶማሌ ክልል ነዳጅ የማውጣቱ ዜና፣ በአገሪቱ አንጻራዊ ሰላም እየሰፈነ መምጣቱ ከሚጠቀሱት ክስተቶች መካከል ጥቂቶቹ ናቸው። • የኢትዮጵያ የዕዳ መጠን እየጨመረ ነው • ወሳኝ ምጣኔ ሃብታዊ እርምጃዎች በ100 ቀናት አፍሪካ በየዓመቱ ከምታገኘው ሁሉን አቀፍ እርዳታ 10 እጥፍ የሚበልጠው በኀቡእ የሚሸሽ ነው። ኢትዮጵያም የዚሁ አካል ናት። ቢሊየን ዶላሮች በሕገ ወጥ መንገድ በየዓመቱ ያፈተልካሉ። በተለይም ኢትዮጵያ ውስጥ በነበረው አለመረጋጋት ብዙ ዜጎች ገንዘባቸውን በዶላር ቀይረው ወደ ውጭ ያሸሹ እንደነበር መረጃዎች ይጠቁማሉ። በመንግሥት ሹሞች የሚፈጸም ሌብነትና ዝርፍያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ 'ሌቦች' የሚሏቸውን ጨምሮ ጥቁር ገበያውን ሲያንሩት እንደነበር ዶክተር ቆስጠንጢኖስ ይገምታሉ። እነዚህ ዘራፊዎች የአገሬውን ገንዘብ ወደ ባንክ ወስደው ለማስቀመጥ አይችሉም። ጥያቄ ስለሚፈጥርባቸው። ስለዚህ የዘረፉትን ወደ ዶላር በመቀየር ማሸሽን ይመርጣሉ። አገር በስፋት ስትዘረፍና ብራቸውን ወደ ዶላር መቀየር የሚፈልጉ ዘራፊዎች ቁጥር ሲጨምር የጥቁር ገበያ የምንዛሬ ዋጋ በዚያው መጠን ይመነደጋል። • የኢትዮጵያና ኤርትራ ግንኙነት ኢኮኖሚያዊ ትርፍ? • የጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ እርምጃዎች የት ድረስ? በብር የሚከፈላቸው የውጭ ተቋራጮች ዶክተር ቆስጠንጢኖስ ለጥቁር ገበያ ዋጋ መናር ሌላ ምክንያት ይመስለኛል የሚሉት አገር ውስጥ ትልልቅ ግንባታ ለማካሄድ የሚጫረቱ የቻይና ኩባንያዎችን ነው። እነዚህ ኩባንያዎች ጨረታ የሚገቡት በብር እንዲከፈላቸው በመዋዋል ነው። ነገር ግን በቢሊዮን ብር ከተከፈላቸው በኋላ ብሩን ወደ ዶላር ቀይረው ከአገር ያስወጡታል። ይህን ግብይት የሚያደርጉት ደግሞ በጥቁሩ የዶላር ጉሊት ነው። ዶክተር ቆስጠንጢኖስ እንደምሳሌ የሚያነሱት ሰሞኑን ድንበር አካባቢ አንድ ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ዶላር በትራክ ተጭኖ ሊወጣ ሲል መያዙን ነው። ይህ ዓይነቱ የድንበር ቁጥጥር የጥቁር ገበያ የዶላር ግዢ ፍላጎቱን የቀነሰ ይመስለኛል ይላሉ። ምክንያቱም ኩባንያዎቹ የሕግ ተጠያቂነት ስለሚያስፈራቸው። የቀድሞው የንግድ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ክቡር ገና ግን በዶክተር ቆስጠንጢኖስ ሃሳብ የሚስማሙት በግማሹ ነው። "የጠረፍ ቁጥጥር ሲኖር (የዶላር) ገበያውን ቀነስ አያደርገውም አልልም። ተጽእኖ ይኖረዋል። ሆኖም የጠረፍ መዘጋት በዚህ ዓይነት ዶላሩን በአንድ ጊዜ ዝቅ...
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
fc8aab3d236d3886b0ff23007661767d
0aed9fedc4fd3cc916702d11ed5f48cd
የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን የምክክር መድረክ በኦስትሪያ በመካሄድ ላይ ነው
አዲስ አበባ ፣ ጥር 25፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ሚና ለዘላቂ የልማት ግቦች በሚል የምክክር መድረክ በኦስትሪያ ቬና ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።የምክክር መድረኩ ለዘላቂ የልማት ግቦች መሳካት የአባል ሀገራት ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ነባራዊ ሁኔታ ላይ በጥልቀት ለመወያየት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የተዘጋጀ  ነው።እንዲሁም በሀገር በቀል እውቀት እና በማደግ ላይ ያሉ ቴክኖሎጂ ጠቀሜታና ተግዳሮቶች ዙሪያ ተወያይቶ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ እና የአባል ሀገራት አቅም ግንባታ ፍላጎትን በመለየት የተጠናከረ ድጋፍ ለማድረግ ያለመም ነው።በምክክር መድረኩ በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የሳይንስና ምርምር ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄኔራል ዶክተር ሰለሞን ቢኖርን ጨምሮ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ አውሮፓ ህብረት አባላት እና ከ30 ሀገራት የተወከሉ ተጋባዥ የመንግስት ኃላፊዎች ተገኝተዋል።የምክክር መድረኩ ለቀጣይ ሁለት ቀናት እንደሚቀጥልም ከሣይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%8b%a8%e1%88%b3%e1%8b%ad%e1%8a%95%e1%88%b5%e1%8d%a3-%e1%89%b4%e1%8a%ad%e1%8a%96%e1%88%8e%e1%8c%82%e1%8a%93-%e1%8a%a2%e1%8a%96%e1%89%ac%e1%88%bd%e1%8a%95-%e1%8b%a8%e1%88%9d%e1%8a%ad%e1%8a%ad/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
d8b9f1b180720a98123b5efc56384115
e424921b6aeea956755a5769eb0fa75a
ኦሮሚያ፡ የኦሮሚያ አስተዳደርና ፀጥታ ቢሮ "የተወሰደው እርምጃ ተመጣጣኝ ነው" አለ
ከሰሞኑ በኦሮሚያ ክልል የተከሰተው አለመረጋጋት ለመቆጣጠር የተወሰደው እርምጃ ተመጣጣኝ መሆኑን የኦሮሚያ ክልል አስተዳደር እና ጸጥታ ቢሮ አስታወቀ።በኦሮሚያ ለተቃውሞ በተጠሩ ሰልፎች ምክንያት የሰዎች ህይወት መጥፋቱን ተከትሎ የፀጥታ ኃይሎች "ተመጣጣኝ ያልሆነ ኃይል" ከመጠቀም እንዲቆጠቡ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ጥሪ ማቅረቡ ይታወሳል። በክልሉ በአሳሳ፣ አሰቦት፣ አወዳይ፣ ባሌ ሮቤ፣ ጭሮ፣ ደንገጎ፣ ድሬ ጠያራ፣ ዶዶላ፣ ገለምሶ፣ ጊኒር፣ ሀሮማያ፣ ሂርና እና ሻሸመኔ ባሉ ከተሞች የሰዎች ህይወት ማለፉን ኮሚሽኑ ከተለያዩ ምንጮች መረጃ እንደደረሰውም በትናንትናው ዕለት ባወጣው መግለጫ አስፍሯል። የሰዎች ህይወት ያለፈውም የኦሮሞ ተቃዋሚ ፓርቲ ፖለቲከኞች እንዲለቀቁ በተጠራ የተቃውሞ ሰልፍ መሆኑንም ጠቅሷል።በኦሮሚያ ክልል የአስተዳርና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ጂብሪል መሐመድን ስለተፈጠረው አለመረጋጋትና በጸጥታ ኃይሎች ተመጣጣኝ ያልሆነ እርምጃ ተወስዷል መባሉን አስተባብለዋል።"ኮሚሸኑ ያወጣው መግለጫ ብዙ ስህትት አለው" ያሉት አቶ ጂብሪል መግለጫው "ሰላማዊ ሰልፍ በወጡ ሰዎች ላይ" ማለቱን በማንሳት ሰላማዊ ሰልፍ የሚባል ነገር እንደማያውቁ ገልፀዋል።እንደ አስተዳደርና ጸጥታ ኃላፊው የተካሄደው "ሁከት" ነው። ሁለተኛው ስህተት ይላሉ አቶ ጂብሪል፣ "ሰልፍ የወጡ ሰዎች የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ይፈቱ ይላሉ። የፓርቲ አመራር ስለሆነ የታሰረ የለም። በወንጀል ስለተጠረጠሩ ነው የታሰሩት" ሲሉ ያስረዳሉ።በሶስተኝነትም መግለጫውን ለማስተባበል የጠቀሱት "ምንጫቸው ፌስቡክ ነው። ጉዳዩ ከሚመለከተው አካል ምላሽ አልጠየቁም" የሚል ነው።የተወሰደው እርምጃ ተመጣጣኝ አይደለም የሚለውን ክስ ሲመልሱ "ተመጣጣኝ ያልሆነ እርምጃ ከተወሰደ ማየት ይቻላል። እስካሁን ባለው የተወሰደው እርምጃ ተመጣጣኝ ነው።" ብለዋል።አቶ ጂብሪል የተደረገው ነገር ሰላማዊ ሰልፍ ሳይሆን ሁከት ነው ካሉ በኋላ፣ የመንገድ የመዝጋት ሙከራ፣ ንብረት ለመዝረፍ፣ የትራንስፖርት መስጫ ተሽከርካሪዎችን ለመሰባበር፣ መንገደኞች ላይ ጠርሙስ ውስጥ ቤንዚን ጨምሮ ክብሪት ለኩሶ ለማቃጠል መሞከሩን እና ባንክ ለመዝረፍ የተሞከረበት ቦታም መኖሩን ገልፀዋል።በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ይላሉ የኦሮሚያ አስተዳደርና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊው፣ "መኪና ሁሉ ተጓዥ 30 ሰው ከሚሞት አንድ ሰው መሞቱ ግድ ይላል። እንደዚህ አይነት እርምጃ ነው የተወሰደው። ይህም ይቀጥላል።"ዶዶላ የቆሰለ ፖሊስ፣ የሞተ የመንግሥት ካቢኔ አባል አለ ያሉት አቶ ጂብሪል፣ የገደለው ሰውዬ እንዲቆም ተነግሮት እምቢ በማለቱ ፀጥታ ኃይሎች እርምጃ መውሰዳቸውን ለቢቢሲ ተናግረዋል። አክለውም "ይህ ሲሆን እንደዚህ አይነት እርምጃዎች የማይወሰዱ ከሆነ የሕግ የበላይነት የሚባለው የት አለ ታዲያ?" ሲሉ ጥያቄ ያቀርባሉ።"ሐረር ላይ ከወታደር መሣሪያ ቀምቶ ከሌላው ሊቀማ ሲል ነው እርምጃ የተወሰደው። . . . በአጠቃላይ የሚጣራ ነገር ሊኖር ይችላል። አልፎ አልፎ ስህተት የተፈጸመባቸው ቦታዎች ሊኖሩ ይችላሉ። በመቶኛ ግን ስናየው አብዛኛው ቦታ የተወሰዱት እርምጃዎች ተመጣጣኝ ናቸው።" የሞቱና የቆሰሉ ሰዎች ቁጥርን ተጠይቀውም፣ "መረጃ እየተጠናቀረ ነው። ሲያልቅ እንናገራለን" ብለዋል።በክልሉ በተለያዩ ከተሞች ከሰኞ ጀምሮ አለመረጋጋት መኖሩን መዘገባችን ይታወሳል። ሰኞ እለት በድሬ ጥያራ ከተማ የባለቤቷ ወንድም እንደተገደለ እና ትናንት ሥርዓተ ቀብሩ እንደተፈጸመ ለደህንነቷ ሲባል ስሟ ያልተገለፀ ወጣት ለቢቢሲ ተናግራናለች። የሞተው ወጣት 30 ዓመቱ መሆኑን ገልፃ፣ በቅርቡ ያገባ ሙሽራ እንደነበር ነግራናለች። እርሱና ሶስት ጓደኞቹ በፀጥታ ኃይሎች በጥይት የተመታን ግለሰብ፣ በባጃጅ ወደ ሆስፒታል በመውሰድ ላይ ሳሉ፣ ሌሎች የፀጥታ ኃይሎች በማስቆም እንደ ደበደቧቸውና የአጎቷ ልጅም በጥይት ተመትቶ መሞቱን ትናገራለች።በድሬ ጥያራ የሚሠሩ የጤና ባለሙያ ደግሞ "በ12 በነበረው ሰልፍ ላይ ከባድ ተኩስ ነበር። ሲተኮስ እኛ ጤና ጣቢያ ነበርን። ከዛ መከላከያዎች ወደ እኛ መጡና አስክሬን የምትሰበስቡበት አምቡላንስ ይዛችሁ ኑ አሉን" በማለት የተፈጠረውን ሁናቴ ያስታውሳሉ።በቦታው በተገኙበት ወቅትም በርካታ ሰዎች በጥይት ተመትተው፣ ሌሎች ተደብድበው፣ ሌሎች ደግሞ ሕይወታቸው አልፎ ሜዳ ላይ መመልከታቸውን ለቢቢሲ ተናግረዋል። "በሕይወት ለነበሩት እርዳታ ሰጥተን ወደ ሆስፒታል ሪፈር አደረግን። የሞቱትን ወደ ጤና ጣቢያው ወሰድን። ሁለት ልጆች ሞተዋል። አንደኛው ማዲ ኡመር ሁለተኛው ደግሞ ፈሪድ አብዲ ይባላል። በወቅቱ ተደብድበው የነበሩትን መቁጠር አልቻልኩም። በጥይት የተመቱት ግን ወደ 12 የሚሆኑ ሰዎች ናቸው" ሲሉ የተመለከቱትን ለቢቢሲ አስረድተዋል።በጭሮ ሆስፒታል የጤና ባለሙያም ስላለው ሁኔታ ሲናገሩ "በቀደም [ሰኞ] 24 ሰዎች ተመትተው ነበር እኛጋ የመጡት። ከዛ በኋላ ቁጥሩ 30 ደርሷል" ካሉ በኋላ ሰኞ እለት ተመትቶ ወደ ጭሮ ሆስፒታል ህክምና ሲደረግለት የነበረ ጉማ የሚባል የ19 ዓመት ወጣት ሐሙስ እለት ሕይወቱ ማለፉን ተናግረዋል። ". . .ሌላ ወጣት ዶባ ከሚባል ወረዳ በጥይት ተመትቶ መጥቶ ነበር። ትናንት ወደ ቀዶ ሕክምና ክፍል እየወሰድነው ሳለ ሞተ። በአጠቃላይ በኛ ሆስፒታል አራት ሰዎች ሞተዋል። አራቱም በጥይት ነው የተመቱት።"በሐረር ሕይወት ፋና ሆስፒታል የሚሠሩ ባለሙያ እንደነገሩን ከሆነ ደግሞ፣ ከአወዳይና ከሌሎችም ከተሞች 23 ሰዎች ተመትተው ሆስፒታል ገብተዋል። ሦስት ሰዎች ሆስፒታል ከደረሱ በኋላ እንደሞቱም ነግረውናል። ባለሙያው እንዳሉት አብዛኞቹ በሆስፒታላቸው የሚገኙት ሰዎች ጭንቅላታቸው እና ከጀርባቸው የተመቱ ናቸው። አብዛኞቹ በአስጊ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙም አክለዋል።
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.bbc.com/amharic/53852371
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
bab53a49eba17fc115904816c4d7df9a
118ebf7802d3bf2a127054fa395f81da
በሁመራ ከተማ የኢትዮጵያና ኤርትራ ህዝቦች የህዝብ ለህዝብ መድረክ ስነ ስርዓት እየተካሄደ ነው
የኢትዮጵያና ኤርትራ ህዝቦች በሁመራ ከተማ የህዝብ ለህዝብ መድረክ ስነ ስርዓት እየተካሄደ ይገኛል፡፡በመድረኩ ላይ በሺህዎች የሚቆጠሩ የኦምሓጀርን ነዋሪዎች ጨምሮ የሁለቱ ሀገራት የመካላከያ ኃይል አባላት፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ተገኝተዋል፡፡በዚሁ መድረክ ላይ የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል ተገኝተዋል፡፡የህዝብ ለህዝብ መድረኩ በኢትጵያና ኤርትራ ህዝቦች መካከል የተጀመረውን ሰላማዊ ግንኙነት የበለጠ እንደሚያጠናክረው ተግልጿል፡፡ከሦስት ቀናት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድና ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በተገኙበት ሁለቱን ሀገራት የሚያገናኘውን የሁመራ-ኦምሓጀርን መንገድ መክፈታቸው ይታወሳል፡፡ (ኤፍ.ቢ.ሲ)
5ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/30811/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
7c734f6a0ed7b2ce3c30e7a2ff3b2702
4b99d331df9da3670ea39379424ffa49
ለኢንተርፕራይዞች 4 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ብድር ተሰጥቷል
አዲስ አበባ፡- የፌዴራል ሥራ ዕድል ፈጠራና ምግብ ዋስትና ኤጀንሲ በ2012 በጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት ከሩብ ሚሊየን ለሚበልጡ አንቀሳቃሾች 4ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር የብድር አገልግሎት መሰጠቱን አስታወቀ፡፡በኤጀንሲው የኮሙዩኒኬሽን ባለሙያ አቶ በኃይሉ ንጉሤ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለፁት፤ ኤጀንሲው ለአንቀሳቃሾቹ 4ነጥብ5 ቢሊየን ብር ብድር ለመስጠት ታቅዶ፣ በ44ሺ551 ኢንተርፕራይዞች ሥር ለታቀፉ 106ሺ569 አንቀሳቃሾች ብድር ተሰጥቷቸዋል፡፡ብድሩን የወሰዱት በአገልግሎት፣ ንግድ፣ ኮንስትራክሽን፣ ከተማ ግብርና ፣ በጥቃቅንና ማኑፋክቸሪንግ የተደራጁ መሆናቸውን አቶ በኃይሉ ጠቅሰው፣ በዚህም ለ406ሺ453 ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩም ጠቁመዋል፡፡አቶ በኃይሉ ለኢንተርፕራይዞች ከሚሰጠው ብድር 3ቢሊየን ብር ለማስመለስ ታቅዶ ከዘመኑ ብር 1ነጥብ6 ቢሊየን ብር ማስመለስ መቻሉንም አመልክተዋል፡፡ከውዝፍ ዕዳም 282 ሚሊየን ብር እንዲመልሱ መደረጉን ጠቅሰው፣በአጠቃላይ 2ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ማስመለስ መቻሉን ጠቁመዋል፡፡የብድር አመላለሱ ከ2011 ተመሳሳይ ስድስት ወራት 1ነጥብ 7ቢሊየን ብር ጋር ሲነፃፀር በ23 በመቶ መሻሻል አሳይቷል፡፡በብድር ስርጭት አጠቃቀም በኦሮሚያና ሱማሌ ክልሎችና በአዲስ አበባ ከተማ የተሻለ አፈፃፀም መታየቱን ገልጸው፣ በብድር አመላለስ በኩል ሶማሌ ክልል ከዕቅድ በላይ ማከናወኑን አስታውቀዋል፡፡ ደቡብና ትግራይ ክልሎችና ድሬዳዋ ከተማ መስተዳድር መካከለኛ መሆናቸውን ጠቅሰው፣ ሌሎች ክልሎች አፈፃፀማቸው በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡የብድር አመላለስ ለአዳዲስ ሥራ ፈላጊዎች ብድር ከማሠራጨት አንፃር የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ከግምት በማስገባት በንቅናቄና በቅንጅት መሥራት ይገባል ሲሉም አቶ በኃይሉ አስገንዝበዋል፡፡በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት ለ177ሺ 189 ኢንተርፕራይዞች 9ነጥብ9 ቢሊዮን ብር የገበያ ትስስር ለመፍጠር ታቅዶ 58ሺ 5 ኢንተርፕራይዞች 8ነጥብ5 ቢሊዮን ብር የገበያ ትስስር መፈጠሩን የጠቀሱት የኮሙዩኒኬሽን ባለሙያው፤ የገበያ ትስስሩ በአብዛኛው በመንግሥት በሚወጡ ጨረታዎች እና በኮንስትራክሽን ዘርፍ ላይ የተንጠለጠለ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ኤጀንሲው ሀገር አቀፍ ንቅናቄ በማካሄድ በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት በተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የተሻለ የቁጠባ ባህል እንዲኖር በማድረግም 4ነጥብ 9 ቢሊየን ብር በማስቆጠብ የዕቅዱን 94 በመቶ ማሳካት መቻሉን አመልክተው፣ ከዚህ ውስጥ በተማሪዎች የተቆጠበው 13ነጥብ 7 ሚሊየን ብር እንደሚሆን አስረድተዋል፡፡አዲስ ዘመን ጥር 26/2012
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=26621
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
dc2adffb9ca0ada136e42ffbd0f82be9
754451769659e049da58e4e40d55aee9
በሀሰተኛ ደረሰኝ ግብይት የፈፀሙ 130 ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ
– ገቢዎች ሚኒስቴር የዕቅዱን 101 በመቶ አሳክቷልአዲስ አበባ፡- በስድስት ወራት ውስጥ ብቻ ሀሰተኛ ደረሰኝ በሚጠቀሙና በግብይት ወቅት ደረሰኝ በማይቆርጡ 130 ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ። ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያላቸው 191 ተጠርጣሪዎች በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ የተደረገ ሲሆን በታክስ አስተዳደር አዋጅ መሰረትም ድርጅቶቹ 8 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር እንዲቀጡ መደረጉን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ።የገቢዎች ሚንስትር ወ/ሮ አዳነች አቤቤ እንደገለጹት፤ በግብይት ወቅት ደረሰኝ የማይቆርጡ ድርጅቶችን የኢንተለጀንስ ጥናት በመጠቀም ለማወቅ የተቻለ ሲሆን፤ በዚህም ሀሰተኛ ደረሰኝ ሲጠቀሙ በተገኙና በግብይት ወቅት ደረሰኝ በማይቆርጡ 130 ድርጅቶች ተደርሶባቸው በህግ እንዲጠየቁ ተደርጓል። ከዚሁ ጋር በተያያዘም ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያላቸው 191 ተጠርጣሪዎች በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ የተደረገ መሆኑን ሚኒስትሯ የተናገሩ ሲሆን፤ በታክስ አስተዳደር አዋጅ መሰረትም ድርጅቶቹ 8 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር እንዲቀጡ መደረጉን አስታውቀዋል።ሚኒስትሯ አክለው እንደገለጹትም፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በ2012 በጀት ዓመት ስድስት ወራት 125 ነጥብ ሰባት ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ 127 ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር በመሰብሰብ የዕቅዱን 101 በመቶ አሳክቷል። የዕቅድ አፈፃፀሙ  ከባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ28 ነጥብ ዘጠኝ ቢሊዮን ብር ብልጫ ያለው ሲሆን የ29 በመቶ ዕድገትም አሳይቷል። በስድስት ወራት ከተሰበሰበው ገቢ ውስጥ 58 በመቶ ከሀገር ውስጥ ገቢ ሲሆን ቀሪው 42 በመቶ የሚሆነው ከጉምሩክ ገቢ የተሰበሰበ ነው። ለዕቅዱ መሳካት ከፍተኛ ሚና የተጫወቱት ሠራተኞችና ታማኝ ግብር ከፋዮች እንደሆነ ተገልጿል። ግብር ከፋዮች ሳይገደዱ በፍላጎታቸው እየከፈሉ መሆናቸውን ወ/ሮ አዳነች አስታ ውሰው፤ ለህግ ተገዢ ያልሆኑትን ግብር ከፋዮች ወደ ትክክለኛ መስመር ለማምጣት ጠንካራ የህግ ማስከበር ሥራ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።አዲስ ዘመን ጥር 16/2012ዋለልኝ አየለ
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=26113
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
1ce5463e105bc186d6d63c4714152011
2cce7fc8ce715a1ecac2f4d38b1a969c
የተባበሩት ምንግሥታት በየመን የዓለማችን አስከፊው ረሃብ ሊከሰት ይችላል ሲሉ አስጠነቀቁ
ማርክ ሎወኮክ በሳውዲ የሚመራው ጥምር ኃይል የእርዳታ ቁሶች ወደ የመን እንዲገቡ መተባበር አለበት ብለዋል። ባለፈው ሰኞ የሁቲ አማጺያን ወደ ሳዑዲ ሚሳዬል ከተኮሱ በኋላ ጥምር ኃይሉ ወደ የመን የሚደረጉ የአየር፣ የየብስ እና የምድር መጓጓዣ ዘዴዎችን በሙሉ ዝግ አድርጓል። ሳውዲ አረቢያ ወደ የመን የሚደረጉ የመጓጓዣ ዘዴዎችን በሙሉ ዝግ ማድረጉ ያስፈለገው ኢራን የመን ውስጥ ለሚገኙ የሁቲ አማጺያን የጦር መሳሪያ ድጋፍ እንዳታደርግ ነው ብላለች። እአአ ከ2015 ጀርምሮ የሳውዲ መራሽ ኃይልን ስትዋጋ የቆየችው ኢራን፤ ለአማጺያኑ ምንም አይነት ድጋፍ አለደረኩም ትላለች። በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ የተባበሩት ምንግሥታት እና የቀይ መስቀል ማህበር በየመን አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ለሚሹ ሚሊዮኖች እርዳታ ማቅረብ አለመቻሉን ተናግረዋል። በጦርነት እየታመሰች ያለቸው የመን የዜጎቿን ፍላጎት የምታሟለው ሁሉንም አይነት ሸቀጦች ከውጪ ሃገር በማስገባት አው። አሁን ላይ ግን ምግብም ሆነ፣ ነዳጅ አልያም መድሃኒት ወደ ሃገሪቱ ማስገባት አልተቻለም።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
af3303f852abeccd793068486a391626
397c8ce03b87ca93242e335bbfee8671
1897
ታኅሣሥ 24 ቀን - የጃፓን-ሩስያ ጦርነት፡ ጃፓን ፖርት አርሰር ከሩስያ ማረከ። ጥር 14 ቀን - ብዙ ሰላማዊ ሰልፈኞች በሰይንት ፒተርስቡርግ ሩስያ በፖሊስ ተገደሉ። የካቲት 26 ቀን - የሩስያ ሠራዊት በሙክደን ውግያ በጃፓን ተሸነፈ። መጋቢት 26 ቀን - በምድር መንቀጥቀጥ በህንድ 20,000 ሰዎች ሞቱ። ግንቦት 20 ቀን - ጃፓን የሩስያን መርከብ ኃይል አጠፋ። ግንቦት 30 ቀን - የኖርዌይ ምክር ቤት ነጻነት ከስዊድን አዋጀ። ነሐሴ 26 ቀን - በካናዳ ውስጥ አልቤርታና ሳስካቸዋን አዳዲስ ግዝቶች ሆኑ። ነሐሴ 30 ቀን - ጃፓን በሩሲያ ላይ አሸንፎ በፖርትስመስ ኒው ሃምፕሽር ውል ተፈራረሙ። ያልተወሰነ ቀን፦ ጣልያኖች ተከራይተው የነበረውን ሞቃዲሾን በዋጋ ገዙትና የጣልያ ሶማሊያ መቀመጫ ሆነ። ፈረንሳይ ከተደገፉት ሃይማኖቶች ተለየ። በኬንያ ዋና ከተማ ከሞምባሳ ወደ ናይሮቢ ተዛወረ። ልደቶች ዮፍታሄ ንጉሴ አመታት
null
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
68d6d56157ac1f7b3ddafd54c466d72f
915aff7de6bda21bb2f66083aec5022e
ጥቅምት ፳፪
ጥቅምት ፳፪ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፶፪ኛው እና የመፀው ፳፯ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፫፻፲፬ ቀናት ሲቀሩ፣ በዘመነ ዮሐንስ፤ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፫፻፲፫ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፭፻፭ ዓ.ም. - በቫቲካን ውስጥ የሚገኘው የቅዱስ ጴጥሮስ ካቴድራል፣ በልዩ ሲስቲን ጸሎት ቤት ጣሪያ ላይ በሚካኤል አንጀሎ የተሳለው ታሪካዊ ስዕል ለመጀመሪያ ጊዜ ለሕዝብ ታየ። ፲፱፻፳፫ ዓ/ም - በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የንግሥ በዓል ዋዜማ፤ የታላቁ ንጉሠ ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አጠገብ፤ ለበዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ። ፲፱፻፵፭ ዓ.ም. - አሜሪካ በዓለም የመጀመሪያውን የሃይድሮጅን ቦምብ በማፈንዳት ማርሻል ደሴቶች (Marshall Islands) ላይ ፈተነች። ፲፱፻፶፫ ዓ.ም. - በአሜሪካ የፕሬዚደንትነት ምርጫ ዘመቻቸው ላይ ለዕጩነት የቀረቡት ጆን ኤፍ ኬኔዲ፣ የሰላማዊ ተልእኮ ወይም (Peace Corps) በሚል ያቀዱትን ኃሣብ ይፋ አደረጉ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የጀርመን ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ (ምሥራቅ ጀርመን) አዲስ አበባ ላይ ቤተ-ልዑካን (ኤምባሲ) ከፈተ። - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ ቤጂንግ የበረራ መሥመር ጀመረ። - የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በጎ አድራጎት ድርጅት የዓመቱ ሽሽልማት ተቀባይ፣ የሴኔጋል ፕሬዚደንት ሊዮፖልድ ሴዳር ሴንግሆር አዲስ አበባ ገቡ። - የቆጵሮስ ደሴት ፕሬዚደንት አቡነ መቃሪዮስ የንጉሠ ነገሥቱን ፵፫ኛ የዘውድ በዐል ያካተተ የአምስት ቀን ጉብኝት ለማድረግ አዲስ አበባ ገቡ። ፲፱፻፸፬ ዓ.ም. - በካሪቢያ ባሕር ላይ የሚገኙት የአንቲጋ እና ባርቡዳ ደሴቶች ነጻነታቸውን ከብሪታንያ ተቀዳጁ። ፲፱፻፹፮ ዓ.ም. - በአውሮፓ፣ የማስትሪክት ውል የሚባለው ስምምነት የአውሮፓ ሕብረትን በመመሥረት ሥራ ላይ ዋለ። ልደት ዕለተ ሞት ፲፱፻፸፪ ዓ.ም. - የሠላሳ አራተኛው የአሜሪካ ፕሬዚደንት የድዋይት ዴቪድ አይዘንሃወር ባለቤት ሜሚ አይዘንሃወር በተወለዱ በ ሰማንያ ሁለት ዓመታቸው አረፉ። ፳፻ ዓ.ም - በሁለተኛው የዓለም ጦርነት መደምደሚያ ላይ ሂሮሺማ ላይ የአቶም ቦምብ የጣለውን የአሜሪካ አየር ኃይል ዠበብ ያበረሩት ብርጋዴር ጄኔራል ፖል ቲቤትስ (Brigadier Gen. Paul Tibbets) በተወለዱ በዘጠና ሁለት ዓመታቸው አረፉ። ዕለታት ዋቢ ምንጮች P.R.O., FCO 371/1660 - ANNUAL REVIEW FOR ETHIOPIA FOR 1973
null
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
0b5d94ecd81d97ffd14451a120902901
52f8c25279876ec6e0da5cf45f995f01
አርቲስት ፍቃዱ ተክለማርያም ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ
ላለፉት 42 ዓመታት በመድረክ፣ በራድዮ፣ በቴሌቭዥን፣ በፊልም በርካታ የመድረክ የጥበብ ሥራዎች የሚታወቀው ተዋናይ ፍቃዱ ተክለማርያም ትላንት ምሽት ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱ ተገለፀ፡፡ከወራት በፊት ሁለቱም ኩላሊቶቹ ከጥቅም ውጪ በመሆናቸው ንቅለ ተከላ እንደሚያስፈልገው መገለፁ ይታወሳል። የአርቲስቱ አስክሬን ከነበረበት የፀበል ቦታ ተነስቶ ወልዲያ ከደረሰ በኋላ አሸኛኘት ተደርጎለታል፡፡በኦቴሎ፣ ኤዲፐስ ንጉሥ፣ ሐምሌት፣ ቴዎድሮስ፣ ንጉሥ ኦርማህ፣ የሰርጉ ዋዜማ፣ አቡጊዳ ቀይሶ፣ ባለካባ ባለዳባ፣ መልዕክተ ወዛደር የመድረክ ሥራዎቹ፤ በቴሌቪዥን ባለጉዳይ ፣ ገመና፣ መለከት እና በመሳሰሉት ሥራዎቹ ይታወቃል።በኢትዮጵያ ራድዮ “ከመጽሃፍት ዓለም” በተሰኘው የራድዮ ፕሮግራም “ሞገደኛው ነውጤ፣ ጥቁር ደም፣ ሳቤላ፣ የነበረው እንዳልነበር” በተሰኙ አጫጭርና ረጅም ልቦለዶች ሥራዎቹ ይታወቃል፡፡
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/fikadu-te/4509092.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
4e4a3c03e5bf6ca833640d33f0fce28e
a026f0d9b7c65d4d3fb1f3886cfeea56
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ 2ኛ ዙር የካቲት 11 ይጀመራል
የሊጉ 2ኛ ዙር መርሃ ግብር የካቲት 6 እንዲጀመር ፕሮግራም የወጣ ቢሆንም ለሁሉም ክለቦች ተመጣጣኝ የእረፍት ጊዜ ለመስጠት በሚል የሁለተኛው ዙር የመጀመርያ ሳምንት (10ኛ ሳምንት) ወደ ሌላ ጊዜ ተሸጋግሮ የካቲት 11 ላይ በሚደረጉ የ11ኛ ሳምንት ጨዋታዎች የ2ኛው ዙር ይደረጋል፡፡ የ11ኛ ሳምንት ፕሮግራምምድብ ሀቅዳሜ የካቲት 11 ቀን 200909:00 ጥረት ኮርፖሬት ከ ኢትዮጵያ ቡና (ባህርዳር)09:00 አዳማ ከተማ ከ ኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ (አዳማ አበበ ቢቂላ) እሁድ የካቲት 12 ቀን 200910:00 ድሬዳዋ ከተማ ከ ቦሌ ክፍለከተማ (ድሬዳዋ) ሰኞ የካቲት 13 ቀን 200909:00 ኤሌክትሪክ ከ ደደቢት (አአ ስታድየም)11:30 መከላከያ ከ ንፋስ ስልክ (አአ ስታድየም) ምድብ ለቅዳሜ የካቲት 11 ቀን 200909:00 ሀዋሳ ከተማ ከ ልደታ ክፍለከተማ (ሀዋሳ)09:00 ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅድስት ማርያም (አአ ስታድየም)እሁድ የካቲት 12 ቀን 200909:00 ሲዳማ ቡና ከ አቃቂ (ይርጋለም)09:00 ጌዲኦ ዲላ ከ አአ ከተማ (ዲላ)09:00 አርባምንጭ ከተማ ከ ንግድ ባንክ (አርባምንጭ)
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/25290
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
8f19815a04729574de3e616ea7750722
002b4fe9c1b4d144a2cb13bfc872944f
በኢትዮጵያ ባለፉት ሶስት ዓመታት 51 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ የውጭ ባላሃብቶች ፈቃድ ወስደዋል
– በኢትዮጵያ ባለፉት ሶስት ዓመታት 51 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ የውጭ ባለሃብቶች በተለያዩ መሰኮች ለመሰማራት ፈቃድ መውሰዳቸው ተገለጸ፡፡የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኤጀንሲ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ነጋሽ እንዳሉት ባለፉት ሶስት ዓመታት 2 ሺህ 164 የውጭ ባለሃብቶች የፕሮጀክት ፈቃድ ወስደዋል፡፡ፈቃዱን ከወሰዱት ባለሃብቶች መካከል 133 ኘሮጀክቶች ግንባታ የጀመሩ ሲሆን ፣ 637 ኘሮጀክቶች ደግሞ ወደ ማምረት የተሸጋገሩ ናቸው፡፡ሥራ የጀመሩት የውጭ ኘሮጀክቶች ለ26 ሺህ ዜጐች ቋሚና ለ35 ሺህ ዜጎች ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ፈጥሯዋል፡፡ፈቃድ ከተሰጣቸው የውጭ ፕሮጀክቶች ውስጥ 423 በግብርና፣ 888 ፕሮጀክቶች በማኑፋክቸሪንግ እና 855 ደግሞ በአገልግሎት ዘርፍ የተሰማሩ ናቸው፡፡አብዛኛውን ደረጃ ከያዙት ባለሃብቶች ውስጥም የቻይና፣ የሱዳን፣ የሕንድ፣ የቱርክ፣ እና የአሜሪካ ዜግነት የያዙ ኢትዮጵያውያን ዳያስፖራ ሲሆኑ ባስመዘገቡት ካፒታል ደግሞ የቱርክ ፣ የሕንድ ባለሃብቶች የመጀመሪያዎችን ደረጃ መያዛቸውን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ያለው ምቹ የኢንቨስትመንት ፖሊሲና ሰላምና መረጋጋት በሀገሪቱ መወለ ነዋያቸውን ለማፍሰስ የሚጠይቁ የውጭ ባለሃብቶችን ቁጥር እንዳሳደገውም ዳይሬክተሩ መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
5ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/28469/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
e073959e149ff8386ebe1baefe176260
e9c476d506dbb819417eaf0db87275f9
የኢትዮጵያ የውጭ አጋሮች የመብት መርማሪዎችና ሚዲያዎች ያለ ምንም እክል በመላው ትግራይ ክልል እንዲንቀሳቀሱ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ጫና እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቦላቸዋል።
በትግራይ ክልል አጣሪዎችና ሚዲያዎች እንዲገቡ በመንግሥት ላይ ጫና እንዲደረግ ጥሪ ቀረበ\nበተለያዩ የዓለማችን አገራት ውስጥ ግጭቶችን የሚከታተለው አለም አቀፉ ክራይሲስ ግሩፕ ነው ይኼንን ጥሪ ያቀረበው። ቡድኑ "Finding a Path to Peace in Ethiopia's Tigray Region" በሚል ርዕስ ባወጣው የ19 ገፅ ሪፖርት አገሪቷ ወደ ሰላም በዘላቂነት የምትመለስበትን፣ ከትግራይ ክልል ጋር ያለው ግጭት በቋሚነት የሚፈታበትን ጨምሮ ሌሎች ጉዳዮችን አካቷል። ቡድኑ ለአሜሪካ መንግሥት፣ ለአውሮፓ ህብረትና ለአፍሪካ ህብረት እንዲሁም ሌሎች አጋሮች የመብት ተመራማሪዎችና ሚዲያዎች ያለምንም እክል ገብተው ስራቸውን እንዲያከናውኑ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት እንዲፈቅዱ ጫና እንዲያደርጉ ጠይቋል። ተፈፀሙ የሚባሉ ጥሰቶች በሙሉ በገለልተኛ አካል እንዲጣራ እነዚሁ አካላት ጫና ሊያደርጉ ይገባል ብሏል። የተረጋጋ ፖለቲካ ለመፍጠር ባለስልጣናቱ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርን ጨምሮ አለም አቀፉ ማህበረሰብ ለሚጠይቀው የህይወት አድን እርዳታ ሙሉ በሙሉ የኢትዮጵያ መንግሥት በሩን ሊከፍት እንደሚገባም በሪፖርቱ አካቷል። በክልሉ ውስጥ በፌደራል መንግሥት የተቋቋመው የአዲሱን ጊዜያዊ አስተዳደር ባለስልጣናት ጨምሮ፣ የተለያዩ የረድዔት ድርጅቶች እያስጠነቀቁ ያለው የሰብዓዊ ቀውስ ከዚህ እንዳይከፋ እንዲሁም በርካቶችን ከሞት ለመታደግ የተለያዩ የረድዔት ድርጅቶች ያለ ምንም እክል ሊንቀሳቀሱና እርዳታቸውን ሊለግሱ እንደሚገባም አስምሯል። ለሳምንታት ያህል የዘለቀውን ውጊያ ተከትሎ የፌደራል መንግሥቱ የክልሉን አስተዳዳሪ ህወሃት ከስልጣን በማስወገድ የክልሉን መዲና እንደተቆጣጠረና ድል እንደተቀናጀ አሳውቋል። ምንም እንኳን የፌደራል መንግሥቱ ጦርነት እንዳለቀ ቢያውጅም የተባበሩት መንግሥታትን ጨምሮ ሌሎች ሪፖርቶች እንደሚያሳዩት ውጊያው መቀጠሉን ነው። በዚህ ውጊያ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች እንዳለቁ፣ በትግራይ 1/3ኛ የሚሆነውን ነዋሪ አፈናቅሏል፣ በርካታ ጥሰቶችም በሁሉም ወገኖች ተፈፅመዋል ያለው ሪፖርቱ እንዲሁም 4.5 ሚሊዮን የሚሆኑ የክልሉ ነዋሪዎች አስቸኳይ ጊዜ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል። የፌደራል መንግሥቱ፣ ከስልጣን የተወገዱት የትግራይ አመራሮች፣ ሰብዓዊ እርዳታ ድርጅቶች፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችና አቀንቃኞች መሬት ላይ ስላለው ነገር የተለያየ እውነታን መናገራቸውን ተከትሎ ልዩነቶች እየሰፉ ነው፤ ለሚያስፈልገው እርዳታም እንቅፋት ሆኗል ይላል ሪፖርቱ። ይህንንም ለማስተካከል መደረግ ያለበት ብሎ ሪፖርቱ ያሰፈረው የፌደራል መንግሥቱ ጋዜጠኞች ሪፖርት እንዲያደርጉ እንዲሁም ሪፖርት የተደረጉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ተጨማሪ ምርመራ እንዲያደርግ መሆን አለበት። ከዚህም በተጨማሪ የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች ከፍተኛ ኮሚሽነር እንዲሁ የራሱን ምርመራ እንዲያከናውን መፈቀድ እንዳለበትና መንግሥት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ጉባኤን ጨምሮ በአገሪቷ ላሉት የሲቪል ሶሳይቲ ድርጅቶች፣ እንዲሁም ሂውማን ራይትስ ዋች፣ አምነስቲ ኢንተርናሽናል ለመሳሰሉ አለም አቀፍ ድርጅቶች በሩን ሊከፍት ይገባል ብሏል። በተለያዩ ሪፖርቶች የኤርትራ ወታደሮች መሳተፋቸው የተጠቀሰ ሲሆን በቅርቡ የኤርትራ ወታደሮች ከትግራይ ክልል በአስቸኳይ እንዲወጡ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት (ስቴት ዲፓርትመንት) የአውሮፓ ህብረት መጠየቃቸው ይታወሳል። የኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ በተደጋጋሚ ይህ ህግ የማስከበር ዘመቻ እንደሆነና በትግራዩ ግጭት የኤርትራ ጦር አለመሳተፉን ማሳወቁ የሚታወስ ነው። የአውሮፓ ህብረትን ተከትሎ አሜሪካም ሆነ ሌሎች ተባብረው የሰብዓዊ ረድዔት ድርጅቶች ሙሉ በሙሉ እርዳታ እንዲደርስ እንዲያደርጉም ካስፈለገም ከትግራይ ኃይሎች ጋር እንዲደራደሩ መሆን እንዳለበት ሪፖርቱ...
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
36a46ca4931fe94231d1fae9a72f29b5
259e5d501f6d0480f026c18508bdbab2
ጅማ አባ ጅፋር የሦስት ተጫዋቾችን ዝውውር አጠናቋል
በዝውውር መስኮቱ በርካታ ተጫዋቾችን እያስፈረመ የሚገኘው ጅማ አባ ጅፋር ሦስት ተጫዋቾችን በዛሬው እለት በይፋ ማስፈረሙን አስታውቋል። ከቅዱስ ጊዮርጊስ የረጅም ዓመታት ቆይታ በኋላ ክለቡን የለቀቁት አሉላ ግርማ እና ዘሪሁን ታደለ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ቡና የለቀቀው አስቻለው ግርማ ጅማ አባጅፋርን የተቀላቀሉ ተጫዋቾች ናቸው።በ2001 ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዋናው ቡድን በማደግ በፍጥነት የመጀመርያ ተሰላፊ መሆን ችሎ የነበረው አሉላ ግርማ በቀጣይ ዓመታት በብሔራዊ ቡድን እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ውጤታማ ጊዜን ማሳለፍ ችሎ ነበር። ሆኖም ያለፉትን ሁለት ዓመታት ከጉዳት ጋር በተያያዘ ሲቸገር ተስተውሏል። ከፈረሰኞቹ ጋር መለያየቱን ተከትሎም በሁለት ዓመት ውል ጅማን ተቀላቅሏል። በተከላካይ እና አማካይ ስፍራ ላይ መጫወት የሚችለው አሉላ በኄኖክ አዱኛ መልቀቅ የተፈጠረውን ክፍተት እንደሚሸፍን ታምኖበታል።እንደ አሉላ ሁሉ በሚሌንየሙ መጀመርያ ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዋናው ቡድን ማደግ የቻለው ዘሪሁን ታደለ ሌላው በሀለት ዓመት ውል ጅማን የተቀላቀለ ተጫዋች ነው። ዘሪሁን በመጀመርያዎቹ ጊዜያት ብዙዎች ተስፋ ጥለውበት የነበረ ግብ ጠባቂ ቢሆንም በውሰት በመድን ካሳለፈው ጊዜ ውጪ በቅዱስ ጊዮርጊስ በመደበኛነት የውጪ ዜጋ ግብ ጠባቂዎች ተጠባባቂ ሆኖ ቆይቷል።አስቻለው ግርማ ሶስት የቡና ቡድን ጓደኞቹን ተከትሎ ወደ ጅማ አምርቷል። አስቻለው በ2005 አጋማሽ ሱሉልታ ከተማን ለቆ ወደ ቡና ካመራ በኋላ ድንቅ ጊዜን አሳልፎ በ2008 ወደ ሀዋሳ ከተማ አምርቶ በ2009 በድጋሚ ወደ ቡና በመመለስ ያለፉት ሁለት የውድድር ዘመናትን ማሳለፍ ችሏል። የመስመር አጥቂው በጅማ የአንድ ዓመት ውል የፈረመ ሲሆን ውሉን ወደ ሁለት ዓመት ከፍ ለማድረግ ድርድር መሆኑ ተገልጿል።ጅማ አባ ጅፋር የሶስቱ ተጫዋቾችን ዝውውር ጨምሮ እስካሁን በዝውውር መስኮቱ 11 ተጫዋቾችን ማስፈረም ችሏል።
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/39077
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
8b799f1a5e620403ab9f2e8afbf3d97e
08bda5e2e969b34dfd2655ed01efe820
ወንጀለኛ አካላት ዕርቅና ድርድር ፈላጊ በመምሰል ከሕግ የበላይነት ሊያመልጡ አይችሉም- ጠ/ሚ ዐቢይ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 28፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ወንጀለኛ አካላት ዕርቅ እና ድርድር ፈላጊ በመምሰል ከሕግ የበላይነት ሊያመልጡ እንደማይችሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አስታወቁ።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት ነው ይህንን ያሉት።በመልእክታቸው አክለውም፥ የሚከናወነው ኦፕሬሽን ዓላማው፣ የሚገባቸውን ቅጣት ሳያገኙ ከገደብ አልፈው የቆዩትን አጥፊ ግለሰቦች እና ቡድኖች በሀገራችን ሕግጋት መሠረት ተጠያቂ ማድረግ ነው ብለዋል።
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%8b%88%e1%8a%95%e1%8c%80%e1%88%88%e1%8a%9b-%e1%8a%a0%e1%8a%ab%e1%88%8b%e1%89%b5-%e1%8b%95%e1%88%ad%e1%89%85%e1%8a%93-%e1%8b%b5%e1%88%ad%e1%8b%b5%e1%88%ad-%e1%8d%88%e1%88%8b%e1%8c%8a-%e1%89%a0/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
d70ff96ea3ecd1a601514e7a56ea5a2d
41c40d601fc0b6a7da9c3a405c2b6464
ፌዴሬሽኑ ለብሄራዊ ቡድኑ ተጫዋቾች የ20ሺህ ብር ማበረታቻ አበርክቷል
ብሄራዊ ቡድኑ በአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣርያ ካደረጋቸው ሁለት ጨዋታዎች በኋላ ዛሬ ለተጫዋቾቹ የማበረታቻ ገንዘብ አበርክቷል፡፡ ከቡድኑ አባላት ጋርም በወቅታዊ ጉዳዮች ዙርያ ውይይት ተደርጓል፡፡የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ጁነይዲ ባሻ እና የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት እና የፅህፈት ቤት ሃላፊው ዛሬ ጠዋት ቡድኑ ባረፈበት ካፒታል ሆቴል በመገኘት ከተጫዋቾቹ ጋር የተወያዩ ሲሆን ከጉዞ እና ከመሳሰሉት ጋር የተያያዙ ችግሮች በተጫዋቾች ተነስተዋል፡፡ ፌዴሬሽኑም በብሄራዊ ቡድኑ የሚፈጠሩትን ችግሮች ለመቅረፍ እንደሚሰራና እንደ አልጄርያው አይነት በረጅም ጉዞዎች የሚፈጠሩ መጉላላቶችን ለማስወገድ ከሚመለከተው አካል ጋር እንደሚሰራ የፌዴሬሽኑ ሃላፊዎች ከተጫዋቾቹ ጋር ባደረጉት ውይይት ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም ፌዴሬሽኑ ከተጫዋቾች እና የብሄራዊ ቡድን አባላት ጋር በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች ቶሎ ቶሎ በመገናኘት ችግሮች እንዳይፈጠሩ ጥረት እንደሚያደርግ ቃል ገብቷል፡፡የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለብሄራዊ ቡድን አባላት የማበረታቻ ገንዘብ ሲያበረክት ለሁሉም ተጫዋቾች እያንዳንዳቸው 20ሺህ ብር ተበርክቶላቸዋል፡፡ፌዴሬሽኑ ከትላንትናው ጨዋታ በፊት የትኛውም ውጤት ቢመዘገብ 10ሺህ ብር ለማበርከት ወስኖ የነበረ ቢሆንም ተጫዋቾቹ በትላንትናው ጨዋታ ያሳዩት እንቅስቃሴ ፌዴሬሽኑን በማስደሰቱ ማበረታቻው ወደ 20ሺህ ብር እንዲያድግ መወሰኑ ተነግሯል፡፡
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/8205
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
87b43cd15c788582cc1f4a4894416027
01781913886167401a56ed5a1ee1e039
ሪሃና “ያለ አግባብ በስሜ ነግዷል” በሚል ወላጅ አባቷን ከሰሰች
ታዋቂዋ አሜሪካዊት የፖፕ ሙዚቃ አቀንቃኝ ሪሃና የቤተሰቡ ስያሜ የሆነውን ፌንቲ የሚል ቃል ለኩባንያው ስያሜነት በመጠቀምና የኩባንያው ባለድርሻ ወይም የስራ አጋር እንደሆንኩ በማስመሰል ዝናዬን ተጠቅሞ በስሜ በመነገድ ያልተገባ ጥቅም አግኝቷል በማለት በወላጅ አባቷ ሮቢን ፌንቲ ላይ ክስ መመስረቷ ተነግሯል፡፡ፌንቲ የሚለውን ቃል ለንግድ ምልክትነት ወይም ለኩባንያ መጠሪያነት የመጠቀም የባለቤትነት መብቱ የሪሃና እንደሆነ የዘገበው ቢቢሲ፤ ወላጅ አባቷ ግን በ2017 ፌንቲ ኢንተርቴይንመንት የተባለ የመዝናኛው መስክ ኩባንያ ከማቋቋም አልፎ እሷ በማታውቀው መልኩ በስሟ የሙዚቃ ጉዞ ለማዘጋጀት ከሌሎች ኩባንያዎች ጋር ከ15 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሚገመት የድብቅ ድርድር እስከማድረግ መድረሱንና ድምጻዊቷም በዚህ ድርጊቱ አባቷን መክሰሷን አመልክቷል፡፡አባትዬው የድምጻዊቷን የንግድ ምልክት ከመጠቀም ባለፈ ታዋቂነቷን ተጠቅሞ እሷ በማታውቀው ሁኔታ በስሟ የንግድ ድርድር ማድረጉ ህገወጥ ድርጊት እንደሆነ በግለሰቡ ላይ የተመሰረተው ክስ ያስረዳል፡፡አለማቀፍ ዝናን ያተረፈቺው ድምጻዊቷ ሪሃና “ፌንቲ ቢዩቲ” እና “ሳቬጅ ኤክስ ፌንቲ”ን ጨምሮ በፌንቲ የንግድ ምልክት ስር ባቋቋመቻቸው የተለያዩ የንግድ ኩባንያዎች ትርፋማ ስራዎችን ስታከናውን እንደቆየችም ዘገባው አስታውሷል፡፡
4ዓለም አቀፍ ዜና
https://www.addisadmassnews.com/index.php?option=com_k2&view=item&id=23008:%E1%88%AA%E1%88%83%E1%8A%93-%E2%80%9C%E1%8B%AB%E1%88%88-%E1%8A%A0%E1%8C%8D%E1%89%A3%E1%89%A5-%E1%89%A0%E1%88%B5%E1%88%9C-%E1%8A%90%E1%8C%8D%E1%8B%B7%E1%88%8D%E2%80%9D-%E1%89%A0%E1%88%9A%E1%88%8D-%E1%8B%88%E1%88%8B%E1%8C%85-%E1%8A%A0%E1%89%A3%E1%89%B7%E1%8A%95-%E1%8A%A8%E1%88%B0%E1%88%B0%E1%89%BD&Itemid=212
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
50baf8aa9ecca1e50227d3547d8f18c2
5d00420fb6039235afb68372ccdbcbd2
የከተማ አስተዳደሩ በመጠናቀቅ ላይ ያለ ባለዘጠኝ ፎቅ ሕንፃ ካርታ ማምከኑ ተቃውሞ አስነሳ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ በልደታ ክፍለ ከተማ ልደታ መልሶ ማልማት ቦታ ላይ፣ ዊዝደም የገበያ ማዕከል አክሲዮን ማኅበር የሚያስገነባውን በመጠናቀቅ ላይ የሚገኝ ባለዘጠኝ ፎቅ ሕንፃ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ እንዲመክን ማድረጉ ተቃውሞ አስነሳ፡፡የሊዝ ውሉን በማቋረጥ የይዞታ ማረጋገጫው ካርታ እንዲፈርስ የተደረገው በልደታ ክፍለ ከተማ በቀድሞ ቀበሌ 07/14 የሚገኘውና በመልሶ ማልማት ተነሺ የነበሩ የቀበሌና የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲና የንግድ ቤቶችን ተከራይተው ይሠሩ የነበሩ 55 ግለሰቦች፣ በአክሲዮን ማኅበር ተደራጅተው በሊዝ ውል በወሰዱት 1,425 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ እየተገነባ ያለ ሕንፃ መሆኑን የማኅበሩ አባላት ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡የአስተዳደሩ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ዊዝደም የገበያ ማዕከል እያስገነባው የሚገኘው ሕንፃ እንዲመክን ያደረገው በካቢኔ ውሳኔ፣ በአስተዳደሩ ፍትሕ ቢሮ አስተያየትና በከንቲባው ጽሕፈት ቤት ውሳኔ አራት ግለሰቦች (በመልሶ ማልማት ተነሺ ናቸው የተባሉ) በአክሲዮን ማኅበሩ እንዲካተቱ ያስተላለፉትን ውሳኔ፣ አክሲዮን ማኅበሩ ተግባራዊ ባለማድረጉ መሆኑን በተለያዩ ጊዜያት ገልጿል፡፡ቢሮው የገለጸውን ወይም አስተላልፌያለሁ የሚለውን ‹‹አራቱ ግለሰቦች በአክሲዮን ማኅበሩ ውስጥ መካተት አለባቸው የሚል ውሳኔ›› የሚቃወሙት የአክሲዮን ማኅበሩ ባለድርሻዎች ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ከአስተዳደሩ የመሬት አስተዳደርና ግንባታ ፈቃድ ባለሥልጣን ጋር ሚያዝያ 1 ቀን 2004 ዓ.ም. ለ50 ዓመታት የሚቆይ የሊዝ ውል ፈጽመዋል፡፡ ቅድሚያ የሊዝ ግምት በመክፈል ቀሪ የሊዝ ዋጋ በ20 ዓመታት ለመክፈልም ተስማምተዋል፡፡ በወቅቱ የማኅበሩ አባላት 54 የነበሩ ሲሆን፣ በአክሲዮን ማኅበሩ መካተት እንዳለባቸው በመግለጽ ከአስተዳደሩ ጋር የሚከራከሩ አንድ አባል ስለነበሩ፣ አስተዳደሩ የጠየቃቸውን መሥፈርት የሚያሟሉ ከሆነ በማኅበሩ እንዲካተቱ የሚል በውሉ ላይ ተጠቅሶ ስለነበር ተከራካሪው ግለሰብ አሟልተው በመቅረባቸው መካተታቸውን አስረድተዋል፡፡ ቁጥራቸውም 55 መድረሱን አክለዋል፡፡አክሲዮን ማኅበሩ ውሉን ፈጽሞና ቦታውን ተረክቦ ወደ ግንባታ መግባቱን የሚናገሩት የማኅበሩ አባላት፣ ሕንፃው መሠረቱ ወጥቶና የፎቆች ግንባታ በመካሄድ ላይ እያለ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽሕፈት ቤት ጥር 26 ቀን 2005 ዓ.ም. አራት ግለሰቦች በመልሶ ማልማቱ የተነሱ መሆናቸውን ጠቅሶ፣ በአክሲዮን ማኅበሩ ውስጥ እንዲካተቱ ለልደታ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽሕፈት ቤት ማሳወቁን ተናግረዋል፡፡የክፍለ ከተማው መሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽሕፈት ቤት ለከንቲባው ጽሕፈት ቤት የሰጠውን ምላሽ የማኅበሩ አባላት ለሪፖርተር እንዳስረዱት፣ በአክሲዮን ሊካተቱ የሚችሉት ግለሰቦች የተከራዩትን የመንግሥት ቤት በሕጋዊ መንገድ በስማቸው የተዋዋሉና የተከራዩ መሆን አለባቸው፡፡ ግለሰቦቹ ከቀበሌውም ሆነ ከመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲ በቂ ማስረጃ (ኦርጂናልና ኮፒ) ባይኖራቸውም እንኳን፣ በአክሲዮኑ ይካተቱ የሚለው ከመመርያ አንፃር ሲታይ ለአሠራር ክፍተት የሚፈጥር ነው በማለት ካቢኔው ውሳኔውን በድጋሚ እንዲመለከተው ጽሕፈት ቤቱ ምላሽ መስጠቱን አስረድተዋል፡፡የክፍለ ከተማው መሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽሕፈት ቤት የካቢኔው ውሳኔ ከመመርያ ውጪ መሆኑንና ምንም ሕጋዊ ማስረጃ የሌላቸውን ግለሰቦች እንደማያካትት ገልጾ ለቢሮው ምላሽ የሰጠ ቢሆንም፣ የአስተዳደሩ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰለሞን ኃይለ፣ የክፍለ ከተማው ጽሕፈት ቤት የታዘዘውን እንዲፈጽም የማሳሰቢያ ደብዳቤ መጻፋቸውን ሰነዶች ያስረዳሉ፡፡የቢሮ ኃላፊው ጽሕፈት ቤቱ አራቱን ግለሰቦች በአክሲዮኑ ውስጥ እንዲያካትት የትዕዛዝ ደብዳቤ የጻፉት፣ የከንቲባ ጽሕፈት ቤትና የካቢኔ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ አሰግድ ጌታቸው፣ የፍትሕ ቢሮው በካቢኔው ውሳኔ ላይ የሰጠውን አስተያየት መሠረት አድርጐ ቢሮው እንዲያስፈጽም የትዕዛዝ ደብዳቤ ከጻፉ በኋላ መሆኑን፣ የተጻጻፏቸው ደብዳቤዎች ይገልጻሉ፡፡ የፍትሕ ቢሮው በሰጠው የሕግ አስተያየት፣ በማኅበሩና በአስተዳደሩ መካከል የተፈጸመው ውል ሕግ መሆኑን ጠቅሶ፣ ማኅበሩ ግዴታውን በውሉ መሠረት የማይፈጽም ከሆነ የሊዝ ውሉ ሊቋረጥና የይዞታ ማረጋገጫ ካርታው መክኖ የመንግሥት መሬት እንዲመለስ ማድረግ የሚችል መሆኑን ለካቢኔው አስተያየቱን መግለጹን ሰነዶች ያስረዳሉ፡፡የፍትሕ ቢሮው የሰጠውን አስተያየት ተከትሎ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ የማኅበሩ የሊዝ ውልና የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ከኅዳር 28 ቀን 2008 ዓ.ም. ጀምሮ እንዲቋረጥና እንዲመክን ያደረገ ቢሆንም፣ የአስተዳደሩ የመሬት ባንክና ማስተላለፍ ጽሕፈት ቤት ድርጊቱን ተቃውሟል፡፡የመሬት ባንክና ማስተላለፍ ጽሕፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ጀማል አልይ በጻፉት የመቃወሚያ ደብዳቤ ሰፋ ያለ ማብራሪያ አቅርበዋል፡፡ አክሲዮን ማኅበሩ ተጨማሪ ሰዎችን ባለማካተቱ በተፈጠረ አለመግባባት፣ በውል ተቀባይ (ማኅበሩ) እና በውል ሰጪ (ልደታ ክፍለ ከተማ የመሬት ባንክና ማስተላለፍ ጽሕፈት ቤት)፣ እንዲሁም ሥልጣን ባላቸው በየደረጃው በሚገኙ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ክርክር ተደርጐበት ፍርድ አለመሰጠቱን ሥራ አስኪያጁ በደብዳቤያቸው ገልጸዋል፡፡ መሠረታዊ ክፍተት እያለ የሕግ አስተያየትን (ፍትሕ ቢሮ በሰጠው) ብቻ መነሻ በማድረግ የሊዝ ውልን ማቋረጥና የይዞታ ባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታን ማምከን ተገቢ አለመሆኑንም አክለዋል፡፡ የፌዴራል ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጣቸውን አስገዳጅ ውሳኔዎችንም ያለመመልከት ችግር መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 78(1) እና 79 (1 እና 4) ሥር የተረጋገጠውን ነፃ ፍርድ ቤት መኖርንና የዳኝነትን ሥልጣን ትርጉም አልባ የሚያደርግ ዕርምጃ በቢሮው መወሰዱንም ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል፡፡ውሳኔው በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 37 የተረጋገጠውን የዜጐችን ፍትሕ የማግኘት መብት፣ እንዲሁም በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 40 (1 እና 2) መሠረት የንብረት ባለቤት የመሆንን ዋጋ የሚያሳጣ መሆኑን አስረድተው፣ ቢሮው የሊዝ ውል ለማቋረጥም ሆነ የይዞታ ማረጋገጫን ካርታ ለማምከን ሕጋዊም ሆነ የአሠራር መሠረት እንደሌለው አስረድተዋል፡፡ ድርጊቱ የማይተካ ከፍተኛ የፍትሐ ብሔር ኃላፊነትና በግለሰብ ደረጃም ተጠያቂነትን የሚያስከትል መሆኑን አቶ ጀማል አስገንዝበዋል፡፡የማኅበሩ አባላት እንደሚናገሩት፣ ቅድሚያ የሊዝ ክፍያ የፈጸሙት ልጆቻቸውን ዓረብ አገር ልከው ነው፡፡ ሕንፃው ተጠናቆ ወደ ሥራ ለመግባት የቻሉትን ሁሉ እያደረጉ የቀጠሉ ቢሆንም፣ ሕንፃው ሰባተኛ ፎቅ ላይ ሲደርስ ግንባታው ታግዶ ካርታው እንዲመክን መደረጉ እንዳስደነገጣቸውና እንዳሳዘናቸው ተናግረዋል፡፡ በሕጋዊ መንገድ የተደራጀና አስፈላጊውን መሥፈርት አሟልቶ ወደ ሥራ የገባን ማኅበር፣ ያለምንም ምክንያት በሕገወጥ መንገድ ግለሰቦችን በግድ ካላካተታችሁ ተብሎ ሕጋዊ ሰነድ ማምከን ሕገወጥነት መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ በነጋ በጠባ ልማትን የሚሰብክ መንግሥት እንደዚህ ያለ ሕዝብንና አገርን የሚጐዳ ተግባር ይፈጽማል የሚል እምነት እንደሌላቸው የሚናገሩት የማኅበሩ አባላት፣ ድርጊቱን እየፈጸሙ የሚገኙት ሕዝብን በአግባቡና በሕጉ መሠረት ያገለግላሉ ተብሎ ሥልጣን ላይ የተቀመጡ ግለሰቦች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ግንባታው ሰባተኛ ፎቅ ላይ ሲደርስ ውል በማቋረጥና ካርታ በማምከን የሕንፃው መሠረት በውኃ እንዲሞላ በመደረጉ፣ በአጭር ጊዜ ሕንፃውን ሊያፈርሰው እንደሚችል ጠቁመው፣ መንግሥት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥቶ እንዲያስተካክልላቸውና ችግሩን በፈጠሩትም ላይ ዕርምጃ ወስዶ ወደ ግንባታቸው እንዲመልሳቸው ጠይቀዋል፡፡           
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.ethiopianreporter.com/content/%E1%8B%A8%E1%8A%A8%E1%89%B0%E1%88%9B-%E1%8A%A0%E1%88%B5%E1%89%B0%E1%8B%B3%E1%8B%B0%E1%88%A9-%E1%89%A0%E1%88%98%E1%8C%A0%E1%8A%93%E1%89%80%E1%89%85-%E1%88%8B%E1%8B%AD-%E1%8B%AB%E1%88%88-%E1%89%A3%E1%88%88%E1%8B%98%E1%8C%A0%E1%8A%9D-%E1%8D%8E%E1%89%85-%E1%88%95%E1%8A%95%E1%8D%83-%E1%8A%AB%E1%88%AD%E1%89%B3-%E1%88%9B%E1%88%9D%E1%8A%A8%E1%8A%91-%E1%89%B0%E1%89%83%E1%8B%8D%E1%88%9E-%E1%8A%A0%E1%88%B5%E1%8A%90%E1%88%B3
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
9bf34d84299d13f338bc06e8e8094a0c
aa081fd691dab784a476f04df11dd9f1
‹‹ለቲፒ ማዜምቤ የተጋነነ አክብሮት አይኖረንም ፤ ምክንያቱም እኛ ቅዱስ ጊዮርጊሶች ነን›› ሮበርት ኦዶንካራ
በካፍ ቻምፒዮንስ ሊግ 1ኛ ዙር ጨዋታ ቲፒ ማዜምቤን ነገ ባህርዳር ስታድየም ላይ የሚያስተናገድው ቅዱስ ጊዮርጊስን ጎል የሚጠብቀው ሮበርት ኦዶንካራ ክለቡ ከነገው ጨዋታ በፊት ካደረገው የመጨረሻ ልምምድ በኋላ ለሶከር ኢትዮጵያ አስተያየቱን ሰጥቷል፡፡ዩጋንዳዊው ኢንተርናሽናል ሮበርት ኦዶንካራ ቅዱስ ጊዮርጊስ ለነገው ጨዋታ ጥሩ ዝግጅት እንዳደረገ እና በአእምረው ረገድም እንደተዘጋጁ ገልጧል፡፡ ‹‹ለቲፒ ማዜምቤው ጨዋታ ስናደርገው የነበረው ዝግጅታት ጥሩ ነበር፡፡ አሁን የቡድናችን ቅርጽ እና ተነሳሽነት በመልካም ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ ማን በጨዋታው ላይ እንደሚሰለፍ ስለማናውቅ ቦታችንን ለማስከበር ጠንክር እየሰራን እንገኛለን፡፡ ሁሉም የቡድን አባላት ከጉዳት ነፃ በመሆናችን ጨዋታውን ለማሸነፍ ተዘጋጅተናል፡፡ በአእምሮው ረገድም ጥሩ ተዘጋጅተናል፡፡ አሁን በሁላችንም አእምሮ ውስጥ ያለው ጨዋታውን ማሸነፍ ነው፡፡ ›› ብሏል፡፡ ሮበርት አክሎም ለቲፒ ማዜምቤ የተጋነነ ክብር እንደማይሰጡ ተናግሯል፡፡‹‹ ቲፒ ማዜምቤን ጥለን ለማለፍ የምንችለውን ያህል እናደርጋለን፡፡ በነገው ጨዋታ የሜዳ እና የደጋፊ አድቫንቴጅ ይኖረናል፡፡ ይህንንም መጠቀም ይኖርብናል፡፡ ቲፒ ማዜምቤ ጠንካራ ክለብ በመሆኑ ብናከብራቸውም ከሚገባው በላይ የተጋነነ አክብሮት አይኖረንም፡፡ ምክንያቱም እኛ ቅዱስ ጊዮርጊሶች ነን፡፡ የነገው ጨዋታ ጥካራ ቢሆንም የሜዳችንን አድቫንቴጅ በሚገባ ተጠቅመን ወደ ሉሙምባሺ ለመጓዝ ተዘጋጅተናል፡፡‹‹ በተለያዩ አጋጣሚዎች ቲፒ ማዜምቤን የመከታተል እድል አጋጥሞኛል፡፡ ምርጥ ተጫዋቾችን ያሰባሰበ ጠንካራ ቡድን ነው፡፡ ነገር ግን ይህንን እንደ ትልቅ ነገር አንመለከተውም፡፡ ሜዳ ላይ የምንገባው 11ለ11 ሆነን ነው፡፡ ጨዋታውን አቅልለን እንጫወታለን፡፡ ጥቃቅን ስህተቶች ላለመስራት ተጠንቅቀን እንጫወታለን፡፡ የሜዳችንን እና የደጋፊያችንን አድቫንቴጅ ተጠቅመንም እናሸንፋለን፡፡››በ2003 አጋማሽ ፈረሰኞቹን ከተቀላቀለ በኋላ አስተማማኝ ግብ ጠባቂነቱን በማስመስከር በቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች ከሚዘመርላቸው ተጫዋቾች አንዱ ሆኗል፡፡ በነገው እለትም ደጋፊዎቹ የቡድኑ የጅርባ አጥንት እንደመሆኑ እምነቱን ገልጧል፡፡‹‹ በማንኛውም ጨዋታ የሜዳን አድቫንቴጅ መጠቀም አስፈላጊ ነው፡፡ እግርኳስን ስትጫወት ከጀርባህ ደጋፊዎችን ማግኘት ሁልጊዜም የበለጠ እንድትጫወት ያነሳሳሃል፡፡ ብትደክም እንኳን ተነቃቅተህ እንደገና ወደ ጨዋታው እንድትመለስ ይረዳሃል፡፡ እናም በደጋፊዎቻችን ታግዘን ቲፒ ማዜምቤዎችን ከመጀመርያው እስከ መጨረሻው በማጥቃት ላይ የተመሰረተ እንቅስቃሴ አድርገን እናሸንፋለን፡፡›› ሲል ሀሳቡን አጠቃሏል፡፡
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/7058
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
b55d71a718b6077f91b809fe5c02c0ea
dba1848e08d3a8e939be6073b7ea9b73
ኢትዮጵያና ፈረንሳይ በትምህርት ዘርፍ ያላቸውን የቆየ ግንኙነት አጠናክረው ለመቀጠል ተስማሙ
አዲስ አበባ ፣ ጥር 4 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የትምህርት ሚኒስትሩ ዶክተር ኢጅነር ጌታሁን መኩሪያ አዲሱን በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር ረሚ ማርቹክስን ተቀብለው አነጋግረዋል።በዚህ ወቅትም ኢትዮጵያና ፈረንሳይ በትምህርት መስክ በጋራ መስራት በሚችሉበት ጉዳይ ላይ መክረዋል።ሁለቱ ሀገራት በትምህርት ዘርፍ ያላቸውን የቆየ ግንኙነት አጠናክረው ለመቀጠል መስማማታቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። 
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%8a%a2%e1%89%b5%e1%8b%ae%e1%8c%b5%e1%8b%ab%e1%8a%93-%e1%8d%88%e1%88%a8%e1%8a%95%e1%88%b3%e1%8b%ad-%e1%89%a0%e1%89%b5%e1%88%9d%e1%88%85%e1%88%ad%e1%89%b5-%e1%8b%98%e1%88%ad%e1%8d%8d-%e1%8b%ab/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
658d256f656fa08bdc4edd4f711500bb
f52ac6d4a3ce869935560b9398e389a0
​ሀድያ ሆሳዕና የቀድሞ ተጫዋቹን  አስፈረመ
ዱላ ሙላቱ ሀድያ ሆሳዕናን ተቀላቀለ። ከዚህ ቀደም በሀዲያ ሆሳዕና መጫወት የቻለው. ፈጣኑ የመስመር ተጫዋች ቡድኑ በ2008 መጨረሻ ክለቡን ከለቀቀ በኃላ በደቡብ ፖሊስ፣ መቐለ 70 እንደርታ እና ያለፉትን ሁለት ዓመታት ደግሞ በአዳማ ከተማ ሲጫወት ቆይቷል፡፡ ከወራት በፊት በአዳማ ከተማ ለመቀጠል ቅድመ ስምምነት የፈፀመ ቢሆንም የቀድሞው አሰልጣኙ አሸናፊ በቀለን ተከትሎ ሀድያ ሆሳዕናን ተቀላቅሏል፡፡ ወደ ቀድሞ ክለቡ በመመለሴ ደስተኛ መሆኑን እና ጥሩ ጊዜ ለማሳለፍ እንደተዘጋጀም ለሶከር ኢትዮጵያ ተናግሯል፡፡© ሶከር ኢትዮጵያ
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/61995
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
b49cf11bdaefb0777b1fc0c8bbba869c
6e54af1fa8367015a9bd1463aeb7efab
የኢትዮጵያ ዋንጫ | ፋሲል ከነማ ወደ ሩብ ፍፃሜው ተቀላቅሏል
በኢትዮጵያ ዋንጫ አንደኛ ዙር በዛሬው ዕለት አንድ ጨዋታ መቐለ ላይ ተከናውኖ ፋሲል ከነማ ከሜዳው ውጪ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን 1-0 በማሸነፍ ሩብ ፍፃሜውን ተቀላቅሏል።በጉዳት በርካታ ተጫዋቾቻቸው ያጡት ባለሜዳዎቹ ወልዋሎዎች ከእሁዱ የፕሪምየር ሊግ ጨዋታ አብዱልዓዚዝ ኬይታ፣ ቢንያም ሲራጅ፣ እንየው ካሳሁን፣ ሪችሞንድ አዶንጎ፣ አፈወርርቅ ኃይሉ እና ብርሃኑ ቦጋለን አሳርፈው በበረከት አማረ፣ በረከት ተሰማ፣ ሮቤል አስራት፣ ሳምሶን ተካ፣ ዳዊት ፍቃዱ እና አብዱልራህማን ፉሴይኒ ተክተው ወደ ሜዳ ገብተዋል። ዐፄዎቹ በበኩላቸው ጀማል ጣሰው፣ ሰለሞን ሐብቴ፣ ሐብታሙ ተከስተ፣ አብዱልራህማን ሙባረክን በማሳረፍ በምትካቸው ሳማኬ ሚኬል፣ ፍፁም ከበደ፣ በዛብህ መለዮ እና ኤፍሬም ዓለሙ አካተው ጨዋታውን ጀምረዋል።በጨዋታው ከኳስ ቁጥጥር ብልጫ በተጨማሪ የተሳካ የማጥቃት ሽግግር ያደረጉት ዐፄዎቹ በተጠቀሰው አጨዋወት እጅግ ለጎል የቀረበ ሙከራ አድርገው ነበር፤ ሰዒድ ሀሰን ከመስመር በጥሩ ሁኔታ ያሻማትን ኳስ ከግቡ ቅርብ ርቀት ነፃ አቋቋም የነበረው በዛብህ መለዮ በግንባሩ ገጭቶ አልተጥቀመባትም እንጂ። ከዚ ውጭ በጨዋታው  ከቆሙ ኳሶች ጥሩ የግብ ዕድሎች ሲፈጥሩ የታዩት ፋሲሎች በመጀመርያው አጋማሽ ማለቅያ ላይ ጥሩ የግብ ዕድል አግኝተው ነበር ሽመክት ጉግሳ ከማዕዘን ምት የተሻማን ኳስ በግንባሩ ገጭቶ ኤፍሬም አሻሞ ከግቡ መስመር የመለሳት ኳስም ከቆሙ ኳሶች ከተፈጠሩት ዕድሎች ትጠቀሳለች። በመጀመርያው አጋማሽ በርካታ ተጫዋቾች ያለ ተፈጥሮአዊ ቦታቸው ያጫወቱት ቢጫ ለባሾቹ በሁለተኛው አጋማሽ የተጫዋቾች ለውጥ በማድረግ ወደ ሜዳ ገብተው ከመጀመሪያው አጋማሽ የተሻለ ቢንቀሳቀሱም ንፁህ የግብ ዕድል መፍጠር አልቻሉም ፤ በአንፃሩ ፋሲሎች በመጀመርያው ደቂቃ መሪ ለመሆን ተቃርበው ነበር። ኢዙ ኢዙካ ከግቡ ፊት ለፊት ያገኛትን ኳስ ተጠቅሞ መቶ በረከት አማረ ሲተፋት የተመለሰችው ኳስ ሽመክት ጉግሳ ቢመታትም በረከት አማረ በድጋሚ እጅግ በሚያስደንቅ ብቃት አድኗታል። በ52ኛው ደቂቃ ደግሞ ሱራፍኤል ዳኛቸው ከመዓዘን ያሻማውን ኳስ ያሬድ ባየህ በግንባር ገጭቶ ቡድኑን መሪ ማድረግ ችሏል።ግብ ከተቆጠረባቸው በኋላ የተሻለ መነቃቃት ያሳዩት ወልዋሎዎች በሁለት አጋጣሚዎች አቻ ለመሆን ተቃርበው ነበር። በተለይም አብዱልራህማን ያሻማውን ኳስ ባልተለመደ ቦታ መሃል ላይ የተሰለፈው ተስፋየ ዲባባ በግንባር ገጭቶ ለጥቂት የወጣችበት ሙከራ ወልዋሎን አቻ ለማድረግ ከተቃረቡት ሙከራዎች የተሻለች ነበረች። ብርሃኑ አሻሞ ከቅጣት ምት መቷት ሙጂብ ቃሲም በግንባር ገጭቶ ያወጣት እና በግሉ ጥሩ ሲንቀሳቀስ የነበረው ኤፍሬም አሻሞ እና ደስታ ደሙ በጥሩ ቅብብል ገብተው ያልተጠቀሙባት ኳሶችም ይጠቀሳሉ። ግብ ካስቆጠሩ በኋላ ቶሎ ቶሎ ወደ ተቃራኒ ግብ ክልል ከመሄድ የጎንዮሽ ቅብብል የመረጡት ፋሲሎች በኤፍሬም ዓለሙ እና በዓለምብርሃን ይግዛው ለግብ የቀረቡ ሙከራዎች አድርገው በዕለቱ ኮከብ ሆኖ የዋለው በረከት አማረ ግብ በመሆን ተርፈዋል። በተለይም የዓለምብርሃን ይግዛው ሙከራ የፋሲልን መሪነት ወደ ሁለት ከፍ ለማድረግ የተቃረበች ነበረች።ጨዋታው በፋሲል ከነማ 1-0 አሸናፊነት መጠናቀቁን ተከትሎ ዐፄዎቹ ወደ ሩብ ፍፃሜ መሸጋገር የቻሉ ሲሆን የአዳማ ከተማ እና ባህር ዳር ከተማ አሸናፊንም በቀጣይ የሚገጥሙ ይሆናል። 
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/43301
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
d02033dfdaa2b9a5b52ffb0ff94336d9
fcb0e17bb46a995f7e61d5c13468d615
አዋሬ አካባቢ ለአደጋ ተጋላጭነቱ እየታወቀ ዕርምጃ ባለመወሰዱ   በተደጋጋሚ ጉዳት እየደረሰበት መሆኑ ተነገረ
የአዲስ አበባ ከተማ የእሳትና አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን፣ በየካ ክፍለ ከተማ ከሚገኙ አካባቢዎች የአዋሬ አካባቢ ቁጥር አንድ የአደጋ ተጋላጭ መሆኑን አጥንቶ፣ ለሚመለከታቸው አካላት የመፍትሔ ዕርምጃ እንዲወስዱ ምክረ ሐሳብ ቢያቀርብም፣ ተግባራዊ ባለመደረጉ በተደጋጋሚ አደጋ እያጋጠመው መሆኑን  አስታውቀዋል፡፡የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ቡድን መሪ አቶ ጉልላት ጌታነህ ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም. በአዋሬ አካባቢ የደረሰውን የእሳት አደጋ አስመልክቶ ከሪፖርተር ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ የአካባቢው የአደጋ ተጋላጭነቱ በኮሚሽኑ በኩል ተጠንቶ ነበር ብለዋል፡፡ ከጥናት ባለፈም ከየካ ክፍለ ከተማ፣ ከወረዳውና ከኅብረተሰቡ ጋር ውይይት መደረጉንም አስረድተዋል፡፡ አካባቢው በጣም ለአደጋ የተጋለጠ ስለሆነ ነዋሪዎች ወደ ሌላ ሥፍራ የሚዘዋወሩበትን ምክረ ሐሳብ ኮሚሽኑ አቅርቦ የነበረ ቢሆንም፣ ይህ በሚመለከታቸው አካላት ተግባራዊ አለመደረጉን ገልጸወዋል፡፡ እሳቸው በወቅቱ የኮሚሽኑ ባልደረባ ባይሆኑም ያገኙትን መረጃ ጠቅሰው እንዳስታወሱት፣ በሥፍራው በ2004 ዓ.ም. ከፍተኛ የእሳት አደጋ ተከስቶ ነበር፡፡ አካባቢው ለአደጋ ተጋላጭ በመሆኑ በኮሚሽኑ በኩል ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ መሰጠቱን፣ ሆኖም ይህ ተግባራዊ ባለመሆኑ በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 አዋሬ ገበያ ማዕከል ላይ ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም. ከሌሊቱ 10፡54 ሰዓት ላይ መንስዔው ባልታወቀው የእሳት አደጋ፣ አንድ ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን ገልጸዋል፡፡ ኮሚሽኑ ከኅብረተሰቡ፣ ከአዲስ አበባና ከፌዴራል ፖሊስ ጋር በመተባበር 130 ሺሕ ሊትር ውኃ ተጠቅሞ አደጋውን ከማለዳው በ1፡50 ሰዓት ላይ በመቆጣጠሩ አራት ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት ማትረፉንም አክለዋል፡፡ በአደጋው የሞትም ሆነ የአካል ጉዳት አልደረሰም ብለዋል፡፡ በማግሥቱ ጥቅምት 25 ቀን ደግሞ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 15 ቦሌ አራብሳ በሚገኝ የብሎኬት ሼድ ውስጥ አደጋ ያጋጠመ ሲሆን፣ በዚህም ሳቢያ የ200 ሺሕ ብር ንብረት ጉዳት ደርሶበታል፡፡ 400 ሺሕ ብር ያህል ደግሞ ለማትረፍ መቻሉን አቶ ጉልላት ገልጸዋል፡፡የኮሚሽኑን የሩብ ዓመት አስመልክቶ አቶ ጉልላት እንደገለጹት፣ ከሐምሌ 1 እስከ መስከረም 30 ቀን 2013 ዓ.ም. በአዲስ አበባና በዙሪያዋ 96 አደጋዎች ተከስተዋል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 45 የእሳት ሲሆኑ፣ 51 የተለያዩ ድንገተኛ አደጋዎች ናቸው፡፡ አጠቃላይ ከተመዘገቡት አደጋዎች 87 በአዲስ አበባ የቀሩት ደግሞ በኦሮሚያ ልዩ ዞን ውስጥ ናቸው፡፡ በአደጋዎቹ 23 ሰዎች መሞታቸውን፣ 37 ሰዎች መጎዳታቸውን፣ 44 ሰዎችን ደግሞ ማትረፍ መቻሉ ተገልጿል፡፡ በንብረት ላይ በደረሰ ጉዳት 46,318,120 ብር የሚገመት ንብረት የወደመ ሲሆን፣ 511,000,505 ብር የሚገመት ንብረት ለማዳን መቻሉንም አክለዋል፡፡ ወቅቱ ፀሐይና ንፋስ የበዛበት መሆኑን በማስታወስም፣ ኅብረተሰቡ እሳት ሊያስነሱ የሚችሉ ቁሳቁሶችን በጥንቃቄ እንዲይዝ አሳስበዋል፡፡
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.ethiopianreporter.com/article/20393
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
9eaa363b180b572ff626a1022e65a126
3967758a4649b241b61035d92daf0b9c
በእሳት አደጋ የሰው ህይወት ሲያልፍ ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ ንብረት ወደመ
በአዲስ አበባ ከተማ ባለፈው ቅዳሜ በደረሱ ሁለት የእሳት አደጋዎች የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ ንብረት ወደመ።የከተማው እሳትና ድንገተኛ አደጋ መከላከልና መቆጣጠር ባለስልጣን አደጋውን ለመቆጣጠር ባከናወነው ተግባር 25 ሚሊዮን ብር የሚገመት ኃብት ማዳን ችሏል።አደጋዎቹ የደረሱት በቦሌና በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተሞች መሆኑን የባለስልጣኑ ህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ስለሺ ተስፋዬ ለኢዜአ ተናግረዋል።በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተክርስቲያን አጠገብ የሚገኝ መኖሪያ ቤት ላይ በደረሰው አደጋ የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ ሁለት ሰዎች ደግሞ ከባድ የአካል ጉዳት ገጥሟቸዋል።በዚሁ አደጋ 300 ሺህ ብር የሚገመት ንብረት የወደመ ሲሆን 10 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ንብረትን ግን ማዳን ተችሏል ብለዋል።የቤተክርስቲያኑ የምዕመናን መቀመጫዎች በአደጋው መቃጠላቸውም ነው የተናገሩት።አደጋውን ለመቆጣጠር 51 ሺህ ሊትር ውሃ፣ 10 ከባድና ቀላል የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪዎች እንዲሁም 50 የአደጋ መቆጣጠር ሰራተኞች ተሳትፈዋል፤ በ45 ደቂቃ ውስጥም እሳቱን ማጥፋት ተችሏል ሲሉም ገልፀዋል።በቦሌ ክፍለከተማ ወረዳ 4 ልዩ ቦታው በፀጋ ሆስፒታል አካባቢ የተነሳው ሁለተኛው የእሳት አደጋ በ29 ቤቶች ላይ ጉዳት አድርሷል፤ 5 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረትም አውድሟል።ከዚህም ሌላ በአደጋው 63 ሺህ 500 ብር በጥሬ ገንዘብ የወደመ ሲሆን 33 ሺህ ብር በጥሬ ገንዘብ ለማዳን እንደተቻለም አብራርተዋል።እሳቱን ለማጥፋት በተደረገው ርብርብ በአጠቃላይ 15 ሚሊዮን ብር የሚገመት ኃብት ማዳን መቻሉንም ነው የህዝብ ግንኙነት ባለሙያው የተናገሩት።በዚህ አካባቢ የተነሳውን እሳት ለማጥፋት 76 ሺህ ሊትር ውሃ፣ ስምንት ከባድና ቀላል የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪዎችና 53 የአደጋ መቆጣጠር ሰራተኞች ተሰማርተዋል። አደጋውን መቆጣጠር የተቻለው በአራት ሰዓት ውስጥ ነው ተብሏል። (ኢዜአ)
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://waltainfo.com/am/32245/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
3ae814c5a76409f782309a06208509c8
d0cf5e0583326ac9689dc326c9272f78
ወደ ውጭ ከተላኩ ምርቶች ከአንድ ቢሊዮን 300 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኘ፡፡
ወደ ውጭ ከተላኩ ምርቶች ከአንድ ቢሊዮን 300 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኘ፡፡ባሕር ዳር፡ ጥር 04/2013 ዓ.ም (አብመድ) ባለፉት ስድስት ወራት ወደ ውጪ ከተላኩ የተለያዩ ምርቶች ከአንድ ቢሊዮን 300 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ገለጸ። ሚኒስቴሩ የዘርፉን የግማሽ ዓመት አፈፃፀም ከባለድርሻ አካላት ጋር በአዳማ ከተማ እየገመገመ ነው።የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋናው አረጋ በግምገማው መድረክ እንዳሉት ገቢው ከተገኘባቸው ምርቶች መካከል ወደ ውጭ የተላኩ ቡና፣ ቅመማ ቅመም፣ ጥራጥሬ፣ የቅባት እህሎች ይገኙበታል።ከማዕድንና ኢንዱስትሪ ምርቶች የተገኘው የውጪ ምንዛሬ የተሻለ መሆኑም ተገልጿል።የተገኘው ገቢ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀርም ከ224 ሚሊዮን በላይ የአሜሪካን ዶላር ብልጫ መገኘቱን አመልክተዋል።እንደ ሚኒስትር ዴኤታው ገለጻ የተሻለ አፈፃፀም ያለ ቢሆንም ሀገሪቱ ከውጪ ለምታስገባው የተለያዩ ምርቶች በዓመት ከ19 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ እያወጣች ነው። ሀገሪቱ ወደ ውጭ ከምትልካቸው ምርቶች በዓመት የሚገኘው ከ3 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር መዝለል አልቻለም ፤ አሁን ያለውን አቅምና አፈጻጸም ይዘን ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ማሳካት አንችልም ብለዋል።በተለይም በአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና ተወዳዳሪ ለመሆንና የሀገሪቱን ጥቅም ለማስጠበቅ በወጭ ምርቶች ጥራትና ብዛት ላይ መስራት እንደሚገባ አምባሳደር ምስጋናው ተናግረዋል።የግብርናና ማኑፋክቸሪንግ የኢንዱስትሪ ምርቶችን የእሴት ሰንሰለት ውስጥ ማሳለፍ፣ የንግድና ግብይት ሥርዓትን ማዘመን፣ የተቋማት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም አቅም ማጎልበት፣ ድጋፍና ክትትል ላይ በሙሉ አቅም መስራት ግብ ለማሳካት እንደሚረዳ ጠቅሰዋል።በዚህም የመንግስትን እጅ መጠበቅ ብቻ ሳይሆን ባለሃብቶች የሚያጋጥማቸውን ችግር በማቃለል በተለይም የአቅርቦት፣ መሬትና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ በትብብር ለመስራት መሰል መድረኮች ጠቃሚ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.amharaweb.com/%e1%8b%88%e1%8b%b0-%e1%8b%8d%e1%8c%ad-%e1%8a%a8%e1%89%b0%e1%88%8b%e1%8a%a9-%e1%88%9d%e1%88%ad%e1%89%b6%e1%89%bd-%e1%8a%a8%e1%8a%a0%e1%8a%95%e1%8b%b5-%e1%89%a2%e1%88%8a%e1%8b%ae%e1%8a%95-300-%e1%88%9a/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
feec7251d0dece056b8fdfc071e738b9
59fdb42fb79bec3a85c23f1d2b2376fe
ባራክ ኦባማ "የፅናት ተምሳሌት" ሽልማት ተቀበሉ
የቀድሞው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ትላንት ዕሁድ ባደረጉት ንግግር የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አባላት ከፓርቲያቸው አቋም ጋር ቢጣረስም ዕውነቱን መርምረው ሃቅ እንደሚናገሩ ጥልቅ ምኜቴ ነው ብለዋል፡፡የዩናይትድ ስቴትስ የመጀመሪያው ጥቁር ፕሬዚዳንት ትላንት ይህን አስተያየት የሰጡት ቦስተን ከተማ ውስጥ የጆን ኤፍ ኬኔዲን ተቋም "የፅናት ተምሳሌት" በሚል ርዕስ የሚጠራውን ሽልማት በተቀበሉበት ወቅት ነው፡፡የኦባማ አስተያየት የተሰማው የዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ምክር ቤት ከክንዋኔዎቻቸው በዓይነተኛነቱ ተልይቶ የሚታወቀውን የሀገሪቱን የጤና ምርሃ ግብር የሚተካ አዲስ ፖሊሲ ባፀደቀ ከጥቂት ቀናት በኋላ መሆኑ ነው፡፡ኦባማ በርሳቸው አስተዳደር የፀደቀና በስማቸው የሚጠራ የጤና ፖሊሲ ለመሻርና ለመተካት ግፊት በማድረግ ላይ የሚገኙትን ተተኪያቸውን ዶናልድ ትራምፕን በስም ከመጥራትም ሆነ እርሳቸውን ከማመላከት ተቆጥበዋል፡፡ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
4ዓለም አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/us-obama-award-5-8-2017/3843158.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
c627abc618388ebbe14ff820e0ac4828
37109d21b9ff22cb6a1fa9675b28dd48
የተፈጥሮ ሕግጋት ጥናት
ፊዚክስ (ከግሪክ φυσικη /ፊውሲኬ/ በቃሉ አመጣጥ) የተፈጥሮ ጥናት ወይም የተፈጥሮ ሳይንስ ማለት ነው። የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈጥሮአዊ በሆነ አቀራረብ ጠፈር የተገነባባችውን መሰረታዊ ቁሳቁሶችን፥ በነሱ ላይ የሚከሰቱን የሃይሎችና ውጤቶቻቸውን ያጥናል። ይህም የተፈጥሮን ህጎች ማክበር ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። በዚህ ሳይንስ የሚገነቡ ቴኦሪዮች ስነ ሒሳብን እንደ መሳሪያ በመጠቀም ያንድ ሥርአትን እንቅስቃሴ ለማስረዳትና ለመተንበይ የሚያልሙ ናቸው። ይህ ሳይንስ የሚቀበለው ሊለኩና ተመልሰው ሊሞከሩ የሚችሉን ውጤቶች ብቻ ነው። ሳይንሳዊ ዘዴ የሳይንስና ቴክኖሎጂ መዝገበ ቃላት -- የቃላት ትርጓሜ፣ ከእንግሊዝኛ ወደ አማርኛ ይህ የውቀት ዘርፍ ከሞላ ጎደል የሚከተሉትን ያጠናል፦ ሥነ-እንቅስቃሴ ቅጥ ኅዋ ጊዜ ጉልበት አዙሪት ጉልበት ግስበት የመሬት ስበት ስራ አቅም ሃይል ልዩ አንጻራዊነት አጠቃላይ አንጻራዊነት ብርሃን ቀለም ኮረንቲ መብረቅ ድምጽ ሙቀት ሞገድ
null
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
b4c3b34c7893724bf0a7699812225e8d
3ccf1a829fcd1b4cca3167e8f1a7c1d0
ምርጫ ቦርድ የተራዘመ ቀን ቆርጦ እንዳላቀረበ አሳወቀ
ከኮሮና ቫይረስ ስጋት ጋር በተያያዘ ምርጫው በተያዘበት ቀን ነሐሴ 23፣ 2012 ማካሄድ እንደማይችል ያሳወቀው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ውሳኔውን ለተወካዮች ምክር ቤት ማሳወቅ እንጂ የተራዘመ ቀን ቆርጦ እንዳላቀረበ አስታውቋል።ቦርዱ ተጠሪነቱ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደመሆኑ መጠን በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ምክንያት ተይዘው የነበሩ ተግባራት ማከናወን እንደማይችል ጠቅሶ ወሳኔውን ለምክር ቤቱ ማሳወቁን ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስፍሯል።••በዚህም መሰረት በጊዜ ሰሌዳው ሲከናወኑ የነበሩ ተግባራት እንዲቆሙ፣ የወረርሽኙ ስጋት ሲወገድ እንደገና ተገምግሞ እንቅስቃሴ እንዲያስጀምር የሚሉ ውሳኔዎች ማስተላለፉንም ለምክር ቤቱ ሪፖርት አድርጓል።ቦርዱ በተሰጠው ሃላፊነት መሰረት ችግሩን ለተወካዮች ምክር ቤት ከማቅረብ እና በጥናት ላይ የተመሰረተ ውሳኔ ከማድረግ ውጨ ከስልጣኑ ውጪ የሰራው ወይም ስልጣኑ ኖሮት ሳይወጣ የቀረው ሃላፊነት የለምም ብሏል። በህገ መንግስቱ በተቀመጠው መሰረት በስራ ላይ የሚገኘው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የስልጣን ጊዜው ከሚያበቃበት አንድ ወር አስቀድሞ ቦርዱ አጠቃላይ ምርጫውን ማድረግ የማይችል መሆኑን ምክር ቤቱ ተገንዝቦ፣ ከዚህ አንጻር የሚሰጠው ውሳኔ ቢኖር ለመነሻነት ያገለግለው ዘንድ ይህ ውሳኔ እንዲሁም ቦርዱ ያደረገው የዳሰሳ ጥናት ሰነድ ለህዝብ ተወካዮች እንዲተላለፍለት ማድረጉን ጠቅሷል።ከዚህም በተጨማሪ እንዲህ አይነት ውሳኔዎች ላይ ሲደረስ ከተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በሁለት ዙር ውይይት መደረጉን ጠቅሶ በመግባባትም ተጠናቋል ብሏል። የፖለቲካ ፓርቲዎቹም የወረርሽኙ አሳሳቢነት በተለይም እንደ ኢትዮጵያ አይነት ላለ አገር ሊያስከትል የሚችለውን ቀውስ ጠቅሰው ከተለያዩ የመንግሥት አካላትም ጋር በመመካከር እንዲሰራ ጠይቀዋል።
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.bbc.com/amharic/52196304
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
21fc34c697dc323143073e31762e47d8
6d1d08e9ac81693af5063102b7d12832
ህዝቡ አንድነቱን በማጠናከር ለየትኛውም ፈተና ሳይንበረከክ ለስኬት ሊሰራ ይገባል – አቶ ሽመልስ አብዲሳ
ህዝቡ አንድነቱን በማጠናከር ለየትኛውም ፈተና ሳይንበረከክ ለስኬት ሊሰራ እንደሚገባ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ተናገሩ።አቶ ሽመልስ ዛሬ በሰጡት መግለጫ አዲሱን አመት በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን፥ በ2012 ዓ.ም ለተሻለ ተጠቃሚነት ይሰራል ብለዋል።በ2011 ዓ.ም የተገኙ ስኬቶችን በማጠናከርም ለ2012 ዓ.ም እቅድ አፈጻጸም ህብረተሰቡ የድርሻውን ሊወጣ ይገባልም ነው ያሉት።በቀጣዩ በጀት አመትም መንግስት ህዝቡን የተሻለ ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚሰራም አንስተዋል።አዲሱ አመት ስኬታማ ስራዎች የሚሰሩበት፣ ሰላም የሚረጋገጥበት፣ የህግ የበላይነት ለማስከበር የሚሰራበት፣ ህዝቡን ከድህነት ለማውጣት የተጀመሩ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን የምናስቀጥልበት እና ስራ አጥ ዜጎች የተሻለ ስራ የሚያገኙበት እንደሚሆንም ተናግረዋል።በፖለቲካው ዘርፍም በ2011 ዓ.ም የታዩ መልካም ስራዎችን በማስቀጠል ስኬታማ ስራዎች እንደሚሰሩም ገልጸዋል።እንደ ኤፍ ቢ ሲ ዘገባ የህብረተሰቡ ኑሮ እንዲሻሻልም በኢኮኖሚው ዘርፍ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉም ነው ያሉት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ።በየደረጃው ያለ የመንግስት አመራር የተያዙ እቅዶችን ለማስፈጸም በተጠያቂነት እንዲሰራም አሳስበዋል።ባለፉት ሁለት የክረምት ወራት በዜግነት አገልግሎት የችግኝ ተከላን ሳይጨምር ከ1 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት ስራ መሰራቱንም አስረድተዋል።በዚህም የህብረተሰቡ ተሳትፎ ከፍተኛ እንደነበር ጠቅሰው፥ ህብረተሰቡ ላደረገው ተሳትፎም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።ይህ የህብረተሰቡ ተሳትፎ በ2012 በጀት አመት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ጠቅሰዋል።
5ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/31335/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
45fb70d4733f8e8ea0d1093595ec17e4
1b9064fb9a353d8e66463652a0b3fb45
የሴቶች ጥሎ ማለፍ | ሀዋሳ ከተማ ጥረትን በመርታት ወደ ቀጣዩ ዙር አልፏል
በኢትዮጵያ ሴቶች ዋንጫ (ጥሎ ማለፍ) ሀዋሳ ከተማ ጥረት ኮርፖሬትን አስተናግዶ 1-0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ቀጣዩን ዙር መቀላቀል ችሏል።በመጀመሪያው አጋማሽ ኳስን ተቆጣጥረው ቶሎ ቶሎ ወደ ግብ በመድረስ በኩል ጥሩ ሲንቀሳቀሱ የነበሩት ሀዋሳዎች ደቂቃዎች አየገፉ በሄዱ ቁጥር ግን በተለይ ሳራ ኪዲ መዳከሟን ተከትሎ አስፈሪነታቸው ቢቀንስም የተጋጣሚያቸው ጥረት ኮርፖሬት ያልተቀናጀ አጨዋወት ግን ጫና እንዳይፈጠርባቸው አስተዋፅኦ አድርጓል። በ3ኛው ደቂቃ ነፃነት መና ሞክራ ታሪኳ በርገና መልሳው በጥረት ኮርፖሬት ተከላካዮች ርብርብ ግብ ከመሆን በዳነው ኳስ ወደ ግብ መድረስ በቻሉት ባለሜዳዎቹ በኩል 8ኛው ደቂቃ ላይ ቅድስት ቴቃ በተከላካዮች መሀል ሰንጥቃ የሰጠቻትን ኳስ በመጠቀም ነፃነት መና በጥሩ አጨራረስ ሀዋሳን ቀዳሚ አድርጋለች። 28ኛው ደቂቃ ላይ ትመር ጠንክር ከቀኝ መስመር ያሻማችው ኳስ መሬት ላይ ሳያርፍ ሊድያ ጌትነት በቀጥታ ወደ ግብ ሞክራ በአግዳሚው ለጥቂት የወጣችው በመጀመሪያው አጋማሽ በጥረት በኩል የምትጠቀስ ብቸኛዋ ሙከራ ነበረች። 31ኛው ደቂቃ ላይ የግብ ጠባቂዋ ተሪኳ በርገና ድንቅ ብቃት ባይታከልበት ኖሮ መሳይ ተመስገን ከነፃነት መና ያገኘችውን ኳስ ወደ ግብ በመቀየር የሀዋሳን መሪነት የምታሰፋበት አጋጣሚ ነበራት። ምርቃት ፈለቀም ከሳጥን ውጪ የሞከረችው ኳስ አግዳሚውን ለትሞ ሊመለስ ችሏል። ጨዋታውም በሀዋሳ ከተማ 1-0 መሪነት ወደ ዕረፍት አምርቷል።በሁለተኛው አጋማሽ እጅግ ተሻሽለው የመጡት ጥረት ኮርፖሬቶች ጫና ፈጥረው መጫወት ችለዋል። ሆኖም ግብ ለማግባት ካላቸው ፍላጎት የተነሳ ኳስ ባገኙ ቁጥር በፍጥነት ተቀባብለው ወደ ግብ ለመድረስ ሲሞክሩ የሚሰሯቸው የቅብብል ስህተቶች እና ወደ ሳጥን የሚጥሏቸው ረጃጅም ኳሶች በቀላሉ በሀዋሳ ከተማ ተከላካዮች እንዲመለስባቸው ሆኗል። ባለሜዳዎቹም ከተከላካዮቻቸው ጥንካሬ እና ንቃት ውጪ ጥሩ ባልነበረው የመሀል እና የአጥቂ ስፍራቸው አልፎ አልፎም ቢሆን ሙከራዎችን ከማድረግ አልተቆጠቡም። በ50ኛው ደቂቃ ወርቅነሽ መሰለ በግራ መስመር ተነጥላ ወጥታ ለነበረችው ምርቃት ፈለቀ አመቻችታ ሰጥታት የጥረቷ ተከላካይ ቃልኪዳን ተስፋዬን አልፋ ወደ ጎል ብትሞክርም ታሪኳ በርገና አድናባታለች። ድንቅ ብታቷን ስታሳይ የነበረችው እና አንድ ለአንድ ከተጫዋቾች ጋር ስትገናኝ የግል ብቃቷን ተጠቅማ ኳሶችን ስታስጥል የነበረችው ሀሳቤ ሞሶ ከሳጥን ውጪ የተገኘውን የቀጣት ምት በቀጥታ ወደ ጎል ሞክራ ግብ ጠባቂዋ አባይነሽ ኤርቀሎ ኳሱን ሳትቆጣጠረው ቀርታ ትመር ጠንክር ብታገኘውም አባይነሽ ቀድማ የያዘችባት በጥረት ኮርፖሬቶችን አቻ ልታደርግ የምታስችል ሙከራ ነበረች። ከማዕዘን መሳይ ተፈሪ ያሻማችውን ቅድስት ቴቃ በግንባር ገጭታ ለጥቂት የሳተችው ኳስ ደግሞ በሀዋሳ በኩል የምትጠቀስ ሙከራ ነበረች። ሆኖም ጨዋታው ተጨማሪ ግቦች ሳያስተናግድ በሀዋሳ ከተማ 1-0 አሸናፊነት መጠናቀቁን ተከትሎ ባለሜዳዎቹ ወደ ቀጣዩ ዙር መቀላቀላቸውን አረጋግጠዋል።
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/48539
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
681b773d9ecf02978e0b745adde832a7
2442489553cfe6ba22dc55a08e9ea37d
በኤክሳይስ ታክስ አዋጅ አተገባበር ዙሪያ ከቢራ አምራቾች ጋር ውይይት ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 24፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዲሱ ኤክሳይስ ታክስ አዋጅ አተገባበር ዙሪያ እየተፈጠሩ ያሉ ብዥታዎችን ሊያጠራ የሚችል ውይይት ከቢራ አምራቾች ጋር ተካሄደ።ውይይቱን የገቢዎች ሚኒስትር ወይዘሮ አዳነች አቤቤ እና የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሺዴ መምራታቸውን ከገቢዎች ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።የዋጋ ጭማሪ እና የሰራተኛ መቀነስ የውይይቱ አጀንዳዎች ሲሆኑ፥ በመድረኩ ከቢራ አምራቾች ለተነሱት ጥያቄና አስተያየት መልስና ማብራሪያ ተሰጥቷል።ከተነሱት ጥያቄዎችና አስተያየቶች መካከል የገብስ ዋጋ መጨመር በቢራ ዋጋ ላይ ጭማሪ ለመደረጉ ምክንያት መሆኑን አምራቾች ገልጸዋል።ከመድረክ በተሰጠው ምላሽ አዋጁ ከመጽደቁ በፊት የተፈጠረ በመሆኑ ከአዋጁ ጋር ግንኙት እንደሌለው ተገልጿል።ከዚህ በተጨማሪም የተለያዩ ሚዲያዎች የዋጋ ንረት ሊያስከትል የሚችል የታክስ አዋጅ እንደሆነ አድርገው ቀድመው ዜና በመስራታቸው ለዋጋ መጨመር መንስኤ እንደሆነና ከአምራቾች በኩል የቢራ ማስታወቂያ መከልከልና የተጠቃሚው ቁጥር መቀነስ ጋር ተያይዞ ለዋጋ መጨመሩ እንደምክንያት አቅርበዋል።ይህም ከአዋጁ ጋር እንደማይገናኝና በመንግስት በኩል የህብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅ የተወሰደ እርምጃ መሆኑን ነው የተገለጸው።የገቢዎች ሚኒስትር ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በውይይቱ ወቅት፥ የኢትዮጵያ የታክስ ምጣኔ ከአፍሪካም ሆነ ከዓለም ሀገራት ጋር ሲነፃፀር ዝቅተኛ መሆኑን ተናግረዋል።ሆኖም የኤክሳይስ ታክስ ማሻሻያው በምርቶች ላይ ከሚያስከትለው የዋጋ ለውጥ አንጻር ነጋዴው እያደረገው ያለው የዋጋ ጭማሪ የተጋነነ በመሆኑ ለፋብሪካዎችም ሆነ ለማህበረሰቡ ስለማይበጅ ሁሉም ሀላፊነት ተሰምቶት በጋራ መስራት ይገባዋል ብለዋል።በተለይም በገበያ ውስጥ የዋጋ ጭማሪ የሚስተዋልበት የቢራ ምርት አምራቾች ከቸርቻሪዎች ጋር በጋራ በመስራት የማስተካከል ሃላፊነት እንዳለባቸው ጠቅሰው፥ ኃላፊነታቸውን በማይወጡ አካላት ላይ መንግስት ክትትልና ቁጥጥር እንደሚያደርግም ነው ያነሱት።የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሺዴ በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ የቢዝነስ አመችነትን እየተገበረች በመሆኗ አሁን እየተተገበረ ያለው የኤክሳይስ ታክስ አዋጅ ኢንቨስትመንትን የሚያበረታታ በመሆኑ አምራቾች ለሚያጋጥሟቸው ችግር በጋራ በመወያየት መፍትሄ እየሰጡ መሄድ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።አሁን እየታየ ላለው የዋጋ ንረትም ፋብሪካዎች ሀላፊነት ወስደው መስራት እንደሚጠበቅባቸው ጠቅሰዋል።የንግድ ሚኒስትር ዲኤታ አቶ እሸቴ አስፋው አዲስ የተተገበረው የኤክሳይስ ታክስ በሌሎች ሀገራት በተለያዩ ምርቶች ላይ የተጣለውን የታክስ ምጣኔ ከፍተኛ ነው ወይ የሚለውን በሚዛናዊነት መመልክት እንደሚገባ አንስተዋል።በአዋጁ አተገባበር ዙሪያ ግልጽነት ለመፍጠር ከሌሎች አምራቾች ጋር የሚደረጉ ውይይቶች ቀጣይነት እንደሚኖራቸው በውይይቱ ወቅት ተነስቷል።በመጨረሻም ለአዋጁ አተገባበር ክትትል፣ ድጋፍና ቁጥጥር ለማድረግ ከሶስቱም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችና ከአምራቾች የጋራ ኮሚቴ ተቋቁሟል።ለሚያጋጥሙ ችግሮች በየደረጃው የተቋቋመው ኮሚቴ በየሳምንቱና በየወሩ ተገናኝቶ መፍትሄ እንዲያስቀምጥም መግባባት ላይ ተደርሷል።
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%89%a0%e1%8a%a4%e1%8a%ad%e1%88%b3%e1%8b%ad%e1%88%b5-%e1%89%b3%e1%8a%ad%e1%88%b5-%e1%8a%a0%e1%8b%8b%e1%8c%85-%e1%8a%a0%e1%89%b0%e1%8c%88%e1%89%a3%e1%89%a0%e1%88%ad-%e1%8b%99%e1%88%aa%e1%8b%ab/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
0d0b4c9e47ff9dc5682a316c1b3aebbb
2cfa48815c09076edc72a12a4f55fb17
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንትነት እስከ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚኒስቴርነት ድረስ ያገለገሉት ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደ ማሪያም በአፍሪካ ሕብረት የትምህርት እና የሳይንስ ጉዳዮችን ለመሚመለከተው ኮሚሽን ኮሚሽነርነት ሳይመረጡ ቀርተዋል።
ፕሮፌሰር ሂሩት ለአፍሪካ ሕብረት የኮሚሽነርነት ቦታ ለምን ሳይመረጡ ቀሩ?\nለዚህም እንደ ምክንያት ከተቀመጡት ጉዳዮች መካከል በያዝነው ዓመት መተግበር የጀመረው እና በየሩዋንዳው ፕሬዘዳንት ፖል ካጋሜ መሪነት ሲዘጋጅ የነበረው የኮሚሽኑ አዲስ መዋቅር መፅደቁ ነው። ካጋሜ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀ መንበር ሆነው ባገለገሉበት አንድ ዓመት ማለትም ከፈረንጆቹ 2018 እስከ 2019 ባሉት ዓመታት ሕብረቱ ውጤታማ አልነበረም በሚል አዳዲስ የለውጥ ሃሳቦችን አቅርበው ነበር። ይህንን ተከትሎም ባዋቀሩት ኮሚቴ በኩል ሕብረቱን ሙሉ ለሙሉ ኦዲት ያስረደረጉ ሲሆን የሥራ ድግግሞሽን ማስቀረት ብሎም የፋይናንስ ጥገኝነትን ማስቀረት የዚሁ ለውጥ ዋና አላማዎች ነበሩ። በፖል ካጋሜ የተመራው ይህ የለውጥ ሃሳብ ካነገባቸው አራት አላማዎች አንዱ የነበረው የሕብረቱን መዋቅር በሰብሰብ እና ውጤታማነቱን መጨመር ይገኝበታል። በዚህ መሰረትም ሲጠና የቆየው አዲሱ መዋቅር ከዚህ ቀደም ስምንት የነበረውን የኮሚሽነሮች ቁጥር ወደ ስድስት ቀንሷል። በ34ኛው መደበኛ የመሪዎች ጉባኤው ላይም በመጀመሪያው ቀን ምርጫ ዋና ኮሚሽነር፣ ምክትል ኮሚሽነር እና ስድስት የዘርፍ ኮሚሽነሮችን ለመምረጥ ነበር እቅድ የተያዘው። በሕብረቱ ታሪክ የመጀመሪያ በተባለለት ኮሚሽነር ሙሳ ፋኪን ለሁለተኛ ግዜ የመረጠው ጉባኤው ከሩዋንዳ የመጡትን የ ዶ/ር ሞኒክ ንሳንዛባጋንዋ ደግሞ የመጀመሪያዋ ሴት ምክትል ኮሚሽነር አድርጎ መርጧል። የሩዋንዳዋ ተወካይ የመጀመሪያዋ የኮሚሽኑ ሴት ምክትል ኮሚሽነር ሆነው የተመረጡ ሲሆን ይህም ፕሮፌሰር ሂሩትን በተዘዋዋሪ ከውድድር ውጪ አደርጓቸዋል። ከፕሮ. ሂሩት ጋር እነማን ተወዳደሩ በየአራት ዓመቱ የሚካሄደው ይህ የኮሚሸነሮች ምርጫ በኮሮናቫይረስ ምክንያት በተያዘው ዓመት ሊስተጓጎል ይችላል የሚሉ ስጋቶች ቢኖሩም ከስድስቱ ኮሚሽነሮች አራቱን በመምረጥ ተገባዷል። ዓመቱ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ዕጩ የቀረበበትም ነበር። የኮሚሽነሮች ምርጫ በአህጉሩ ካሉ አምስት ቀጠናዎች ተመጣጥኖ እንዲመረጥ ይደረጋል። ስለዚህም ተመራጭ ኮሚሽነሮቹ ካላቸው ብቃት በሻገር የቀጠና ምጣኔም ዋና ግብአት ነው። የሕብረቱ አምስቱ ቀጠናዎች የምሥራቅ፣ የምዕራብ፣ የደቡብ፣ የሰሜን እና የማዕከላዊ ናቸው። ፕሮፌሰር ሂሩትን ጨምሮ አምስት ተፎካካሪዎ የቀረቡበት የትምህርት፣ የሳይንስ እና የኢኖቬሽን ኮሚሽነርነት ዘርፍ ከፍተኛ ዕጩ የቀረበበት ነበር። ከምሥራቅ አፍሪካ ቀጠና ብቻ ሦስት ተፎካካሪዎችን ይዞ የመጣ ሲሆን ከኡጋንዳ እና ሞሪሺየስም ተወዳዳሪዎች የነበሩበት ነው። ሪታ ታግዊራ ሞርሺየስን ወክለው የቀረቡ ሲሆን ጆን ፓትሪክ ካባዮ ደግሞ ከኡጋንዳ ከፕሮ. ሂሩት ጋር ተፎካካረዋል። በተጨማሪም ደቡብ አፍሪካ እና ዚምቧብዌ ተፎካካሪዎችን አቅርበዋል። ከአፍሪካ ሕብረት ጋር የተገናኘ ሰፊ የሥራ ልምድ ያላቸው አንድ የቢቢሲ ምንጭ እንደሚገልጹት አንድ ቀጠና ሦስት ሰው ማቅረቡ በራሱ በአገራቱ መካከል ያለውን ከፍተኛ ያለመናበብ የሚያሳይ ነው ይላሉ። የምሥራቅ አፍሪካ ቀጠና የሩዋንዳዋ የምጣኔ ሃብት ባለሙያ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው መመረጥ ከውድድር ውጪ ሊያደርጋቸው እንደሚችል ፍርሃት እንዳላቸው ፕሮ. ሂሩት ከኢትዮጵያ ቴሌቪሽን ጋር ጥር 22/2013 ባካሄዱት ቃለ ምልልስ ገልፀው ነበር። "ስለቀጣዩ የምርጫ ደረጃ የሰማሁት ነገር ትንሽ ግራ አጋቢ ነው ነው። የኮሚሽኑ ሰብሳቢ ወይም ምክትል ከምሥራቅ አፍሪካ የሚመጣ ከሆነ ሌላ ኮሚሸነር ከቀጠናው እንደማይቀበሉ ነው። ይህ ከእኛ ቁጥጥር ውጪ ነው። ግን ያው በተስፋ እጠብቃለሁ" ሲሉ ሂሩት ገልፀው ነበር። የዶክተር ሞኒክ ንሳንዛባጋንዋ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው መመረጣቸው "ሳይታለም የተፈታ" እንደነበረ የምርጫ ሂደቱን በቅርበት የተከታተሉት ምንጫችን...
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
a7cc35d2ef334674219edd675b530e65
3d1165803f2ff3e4c9b593ea91a03323
በአፍጋኒስታን የዩናይትድ ስቴትስ ወታደራዊ ሰፈር ጉዳት ደረሰ
አፍጋኒስታን በሚገኘው ትልቁ የዩናይትድ ስቴትስ ወታደራዊ ሰፈር ላይ ዛሬ በፈነዳው ከባድ ቦምብና በተከፈተው የተኩስ ጥቃት ጉዳት የደረሰባቸው አብዛኞቹ ሲቪሎች መሆናቸው ታውቋል።የሀገሪቱ ወታደራዊ ባለሥልጣኖች በገልጹት መሰረት፣ አንድ አጥፍቶ ጠፊ፣ ፓርዋን በተባለው ክፍለ-ሀገር በሚገኘው፣ ባግራም የአውሮፕላን ማረፍያ አጠገብ ባለ፣ የማይሰራ ሆስፒታል በር ላይ፣ በፈንጂ የተሞላ መኪናን አፈነዳ። ታሊባን ለጥቃቱ ሃላፊነት ወስዷል።
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/afghanistan-attack-12-11-2019/5201877.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
d90703674dc5c3386c967d775db99d10
b91b352edf5bd425d4303733cd2901c6
የአንበጣ መንጋ የከፋ ጉዳት እንዳያስከትል የመከላከል ሥራ እየተካሄደ መሆኑን ክልሉ አስታወቀ
አዲስ አበባ፡- የአንበጣ መንጋ በሰብል ላይ የከፋ ጉዳት እንዳያስከትል ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት እያደረገ እና የመከላከል ስራ እየተካሄደ መሆኑን የጋምቤላ ክልል አስታውቋል፡፡ የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ ሃላፊ ዶከተር ሉ ኦቡፕ ከአዲስ ዘመን ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለፁት፤ የአንበጣ መንጋው በግንቦት ወር መጀመሪያ በዲማ ወረዳ የተከሰተ ሲሆን በመቀጠልም በመዥንግ ዞን ላይ በሁለት ቀን ልዩነት ተከስቷል፡፡ ሃላፊው በአሁኑ ወቅት መንጋው በመዠንግ ዞን ከፍተኛ ስጋት እየሆነ መምጣቱን ጠቅሰው፤ በዲማ ወረዳ የተከሰተው የአንበጣ መንጋ ግን ገበሬው ድምፅ በማስማት ከቦታው እንዲሽ መደረጉን ገልፀዋል፡፡ በመዠንግ ዞን መንጋው መጠነኛ ጉዳት በሰብል ላይ አድርሶ የነበረ መሆኑንም የገለፁት ሃላፊው፤ በቀጣይም በዚሁ ዞንና በሌሎች አካባቢዎች ላይ በመዛመት የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ ለመከላከል የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ ከፌዴራል ግብርና ሚኒስቴር ጋር በመሆን ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ የአንበጣ መንጋ በሶስት የአርሶ አደርና በአንድ ሞዴል አርሶ አደር የበቆሎ ማሳዎች ላይ ጉዳት ያደረሰ መሆኑን የገለፁት ሃላፊው፤ የአንበጣ መንጋው በሌሎች አካባቢዎች ላይ ተጨማሪ ጉዳት እንዳይስከትል ለመከላከል በዞንና በወረዳ ደረጃዎች ባሉ የቢሮው መዋቅር ለአርሶ አደሮች ግንዛቤ እንዲፈጠር መልእክት መተላለፉን አስታውቀዋል:: መንጋውን በክልል አቅም ብቻ መቆጣጠር የማይቻል በመሆኑ መልእክቱን ለፌዴራል ግብርና ሚኒስቴር በማስተላለፍ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ውይይቶች መደረጋቸውንም ሃላፊው አመልክተዋል፡፡ ይህንንም ተከትሎ በፌዴራል ግብርና ሚኒስቴር በኩል የአንበጣውን መንጋ በአውሮፕላንና በሂሊኮፕተር ለመከላከል የሚያስችሉ ስራዎች መጀመራቸውን ተናግረዋል፡፡ የአንበጣ መንጋው በተከሰተባቸው ዲማ ወረዳና እና መዠንግ ዞን በአካባቢው ያሉ ባለሙያዎች ለአርሶ አደሮች ድጋፍ እያደረጉ እንደሚገኙና አንበጣው በተከሰተባቸው ቦታዎች ላይ ጥናት በማድረግ የፌዴራል ግብርና ሚኒስቴር ባለሙያዎችም በተመሳሳይ የቴክኒክ፣ የሎጀስቲክ፣ የበጀትና የመኪና ድጋፎችን እንዲያደርግ ጥያቄ መቅረቡንም ሃላፊው ገልፀዋል፡፡ በተመሳሳይ ባለሙያዎቹ የአንበጣ መንጋው በተከሰተባቸው ቦታዎች ላይ በመውረድ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን እንዲሰሩ መወሰኑንና ከፍተኛ አመራሩም ከክልሉ ፕሬዚዳንትና ምክትል ፕሬዚዳንት ጋር በመሆን ወደ ስፍራዎቹ በመሄድ ጉብኝት የሚያደርጉበት ሁኔታም እንዳለ ጠቁመዋል፡፡ ከግብርና ባለሙያዎች ጋር በተደረገ ንግግር በአሁኑ ወቅት የአንበጣው መንጋ በተበታተነ መልኩ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝና ዋናው መንጋ ገና ያለተከሰተ እንደሆነ የተረጋገጠ መሆኑንም ሃላፊው አያይዘው የጠቀሱ ሲሆን፤ በቀጣይ ዋናው የአንበጣ መንጋ ተከስቶ ከዚህ የበለጠ ጉዳት በሰብል ላይ እንዳያስከትል በክልሉ በኩል አስፈላጊው ዝግጅት እየተደገ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡ በዋናነትም በተለይ በአሁኑ ወቅት አንበጣው የሚከሰትባቸው ቦታዎች ተለይተው ከቀበሌ አስከ ዞን ድረስ የተጠናከረ የኮሙዩኒኬሽን ሥርዓት እንዲኖር እና ሲከሰትም በቶሎ ስራዎችን ለመስራት አስፈላጊው ዝግጅት ሁሉ መደረጉንም አመልክተዋል፡፡አዲስ ዘመን ግንቦት 11/2012
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=32633
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
289342872db34ecbfbec72bb70d267e2
648a3395b206d14d17bdd1aaaf2a00a9
ኢትዮጵያ ጂቡቲንና ኤርትራን ለማደራደር እንደምትፈልግ ለጂቡቲ መንግሥት አስታወቀች
ኢትዮጵያ ጂቡቲና ኤርትራ ድንበርን በተመለከተ አለመግባባታቸውን እንዲፈቱ፣ በአደራዳሪነት መሥራት እንደምትፈልግ ለጂቡቲ መንግሥት አስታወቀች፡፡ ይህ የተገለጸው ዓርብ ሐምሌ 27 ቀን 2010 ዓ.ም. ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክተው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ መለስ ዓለም መግለጫ በሰጡበት ወቅት ነው፡፡ሁለቱ አገሮች ድንበር የሚገኘውን ራስ ዱሜራ ተራራና ደሴት ይገባኛል በማለት ግጭት የቀሰቀሰ ውዝግብ ውስጥ መቆየታቸው ይታወሳል፡፡ በተለይ በሥፍራው የነበረው የኳታር የሰላም አስከባሪ ጦር ከለቀቀ በኋላ፣ ኤርትራ በመቆጣጠሯ ችግሩ ተካሮ ቆይቷል፡፡የኢትዮጵያ አደራዳሪነት ከኤርትራ ጋር በተፈጸመው ዕርቅና የኢትዮጵያ መንግሥት በኤርትራ ላይ ከዘጠኝ ዓመታት በፊት የተጣለው ማዕቀብ እንዲነሳ በመጠየቁ ምክንያት፣ ፍሬያማ ላይሆን ይችላል የሚሉ አካላት አሉ፡፡ ከኤርትራ ጋር ሰላም ለማውረድና የጦርነቱን ምዕራፍ ለመዝጋት በማለም ሐምሌ 1 እና 2 ቀን 2010 ዓ.ም. በአስመራ ጉብኝት ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር)፣ ከአስመራ ጉብኝታቸው መልስ አዲስ አበባ የመጡትን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝን በማግኘት በይፋ ኤርትራ ላይ የተጣለው ማዕቀብ እንዲነሳ ጥያቄ አቅርበው ነበር፡፡ ይህም ጂቡቲን ያላማከለ ዕርምጃ በመሆኑ ተቀይማለች የሚሉ መረጃዎች ሲወጡም ነበር፡፡ከዚህ በተጨማሪም ለ15 ዓመታት ከኤርትራ ጋር የነበረውን ሰላም አልባ ግንኙነት ለመቀየር፣ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት መሐመድ አብዱላሂ መሐመድ (ፎርማጆ) በአስመራ ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት፣ ኤርትራ ላይ የተጣለው ማዕቀብ መነሳቱ በአካባቢው ኢኮኖሚያዊ ትስስርን ለማምጣት ይረዳል ሲሉ ተናግረው ነበር፡፡ነገር ግን በዚህ የጂቡቲ መንግሥት ደስተኛ እንዳልሆነ አስታውቋል፡፡ በሶማሊያ የጂቡቲ ኤምባሲ ባወጣው መግለጫ ፕሬዚዳንት አብዱላሂ ፎርማጆ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኤርትራ ማዕቀብ እንዲነሳ ጥሪ በማቅረባቸው፣ የጂቡቲ መንግሥትና ሕዝብ ማዘኑን አስታውቋል፡፡ ማዕቀቡ ኤርትራ አካባቢውን በማተራመስ፣ በተለይም አሸባሪውን አልሸባብ በመርዳትና ከጂቡቲ ጋር ያለውን የድንበር ውዝግብ በተመለከተ የተጣለ ሆኖ ሳለ፣ ፕሬዚዳንቱ በጉብኝታቸው ይኼንን ማድረጋቸው አግባብ አይደለም ብሏል፡፡ኢትዮጵያም ማዕቀቡ ከመኖሩ ይልቅ መነሳቱ ጠቃሚ ነው ብላ እንደምታምን በመግለጽ እንዲነሳ መጠየቋን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ፣ ካሁን ቀደም በሰጡት መግለጫ ማስታወቃቸው ይታወሳል፡፡ይሁንና ኤርትራ ለማዕቀቡ መጣል ምክንያት በሆኑ ጉዳዮች ላይ ተጨባጭ ዕርምጃ ባለማሳየቷ፣ የማዕቀቡ መነሳት ፍላጎት መነሻን የሚጠይቁ አሉ፡፡በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢትዮጵያ መልዕክተኛ ተቀዳ ዓለሙ (አምባሳደር)  ለፀጥታው ምክር ቤት፣ ‹‹ባለፈው ሳምንት የጂቡቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አዲስ አበባ በመምጣት የፕሬዚዳንት ጉሌን መልዕክት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) አድርሰው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ጋር ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል፡፡ ኢትዮጵያ በኤርትራና በጂቡቲ መካከል ሰላም ለማውረድ አስፈላጊውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁነቷን ትገልጻለች፡፡ ይህም ለአካባቢው ሰላምና ደኅንነት ሚናው ከፍተኛ በመሆኑ ቁርጠኝነታችንም የላቀ ነው፤›› ብለዋል፡፡
5ፖለቲካ
https://www.ethiopianreporter.com/article/12307
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
65901b647f4e3dbc12946953323201d8
51a23d9c828c290bb6bd92bb1c059c1e
አራት ኢትዮጵያውያን ሴት ዳኛች ወደ ታንዛንያ ያመራሉ
ከኅዳር 3 እስከ 13 በታንዛንያ በሚካሄደው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ላይ ለመዳኘት ከኢትዮጵያ ሁለት ዋና እና ሁለት ረዳት ዳኞች ተመርጠዋል።ወደ ስፍራው የሚያመሩት ዋና ዳኞች ፀሐይነሽ አበበ እና አስናቀች ገብሬ (ፎቶ ከላይ) እና ረዳት ዳኞች ወይንሸት አበራ እና ወጋየሁ ዘውዴ (ፎቶ ከታች) ናቸው።ረዳት ዳኞች የሆኑት ወይንሸት አበራ እና ወጋየሁ ዘውዴ ከዚህ በፊት በተካሄዱ የሴካፋ ዋንጫ ጨዋታዎች ላይ የተሳተፉ ሲሆን ወይንሸት ከሁለት ዓመት በፊት በተደረገው፤ ወጋየሁ ደግሞ ባለፈው ዓመት በተካሄደው ውድድር ላይ መሳተፋቸው ይታወሳል። ወደ ውድድሩ በዋና ዳኝነት የሚያመሩት ፀሐይነሽ አበበ እና አስናቀች ገብሬ ደግሞ የመጀመሪያ ኢንተርናሽናል ውድድራቸው የሚመሩ ይሆናል።
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/51394
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
85cdd5e782e1b11911affcfdba134e49
62080aaafee7190a22cfe0c3f412a7b0
በ2006 ዓ.ም በመጋቢት መገባደጃ ምሽት ሁለት ሰዓት አካባቢ 13 ሰዎችን ጭኖ ከአዲስ አበባ የተነሳው በተለምዶ 'ዶልፊን' የሚባለው ሚኒባስ ወደ አዳማ እየበረረ ነው።
''እግሬን ባጣም ትልቁን ነገር አትርፌ ለትንሹ አልጨነቅም''\nበዛኑ ቀን ማለዳ ለሥራ ከአዳማ ወደ አዲስ አበባ የሄዱት የፊልም ቀረጻ ቡድን አባላትም ስለቀን ውሏቸው እየተጨዋወቱ የመልስ ጉዞ ላይ ናቸው። እንደሌሎቹ ሁሉ ፍሬሕይወት ታምሩም ከመሃል መቀመጫ ከመስታወቱ በታቃራኒ ባለው ወንበር ላይ ተቀምጣ አጠገቧ ካለችው የስምንት ወር ነፍሰጡር ጋር እያወራች ነው። ግን እነዚህ ሁሉ ጨዋታዎች ከሞጆ ከተማ ብዙም አልዘለቁም፤ በቅጽበት ወደለየለት እሪታ ተቀየሩ። የሚጓዙበት መኪና ወደ አዳማ የሚወስደውን መንገድ ስቶ ከጥቂት ሜትሮች በኋላ ገደል ወዳለበት ቦታ መንደርደር ጀመረ። በፍጥነት ይጓዝ ስለነበር አሽከርካሪው መኪናውን መቆጣጣር አልቻለም፤ ከጥቂት ጉዞ በኋላ ተገለበጠ። በእርግጥ ትላለች ከአደጋው ተርፋ ለነጋሪነት የበቃችው ፍሬሕይወት "በአደጋው ብዙዎቹ የደረሰባቸው አደጋ የመፈነካከት፣የመጋጋጥ፤ የመጫጫርና የአጥንት መቀጥቀጥ ጉዳት ነበር።'' እርሷ ግን ከቁርጭምጭሚቷ በታች የደረሰባት አደገኛ ስብራት ከፍተኛ ህመም ፈጥሮባት እንደነበረ ታስታውሳለች። የተባበሩት መንግሥታት የለፈውን እሁድ የዓለም የትራፊክ ተጎጂዎች ቀን በሚል አስቦት አልፏል። በአጋጣሚ አደጋው ሲከሰት ከኋላቸው በነበረ መኪና ውስጥ ያሉ ሰዎች ወደ አደጋው ቦታ ቶሎ በመድረሳቸው ተጎጂዎችን ይዘው ወደ አዳማ ሆስፒታል ነጎዱ። ያኔ ነበር ገና በድንጋጤ ስሜት ላይ እያለች አስደንጋጩን ዜና የሰማችው። "አዳማ ሆስፒታል እንደደረስኩኝ ሃኪሞቹ ጉዳቴን ከመረመሩ በኋላ አደጋው መጠገን የሚችል ስላልሆነ ከቁርጭምጭሚቴ በታች ያለው የእግሬ ክፍል መቆረጥ እንዳለበት ነገሩኝ ፤እኔ ደግሞ ያኔ አይደለም ስለእግር መቆረጥ ስለህክምናው በትክክል ማሰብ አልቻልኩም ፤ ምክንያቱም በሕይወት መትረፌን አላመንኩም ነበር፤ ካሁን ካሁን የምሞት እየመሰለኝ፣ ሌላ ቦታም ተጎድቼ ይሆን እያልኩ ሰውነቴን ነበር የምፈትሸው'' ትላለች ። ፍሬሕይወት ከአደጋው በኋላ በህክምና ላይ እያለች ከጠያቂዎቿ ጋር ፍሬሕይወት በወቅቱ የቀድሞው የኦሮሚያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የአሁኑ የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ በአማርኛ ለሚያስተላልፈው ዘገባ በሪፖርተርነትና በዜና አንባቢነት ትሰራ ነበር፤ የተለያዩ መድረኮችንም ታዘጋጃለች። '' የባሰ ከባድ ጉዳት እንደደረሰበኝ ነው ያሰብኩት ፤እግሬ ብቻ አልመሰለኝም ነበር፤ ከዚያ ሃኪሙን 'እግሬ ብቻ ነው 'አልኩት 'አዎ' ሲለኝ በቃ 'እግሬ ካልጠቀመኝ ቆርጠህ ከላዬ ላይ ጣለው መትረፌ ትልቅ ነገር ነው አልኩት'።'' በእርግጥ ውሳኔው ለፍሬሕይወት ቀላል አልነበረም። ነገር ግን በዛች ቅጽበት እግሯን ለማጣት ከመቃረቧ በላይ 'እኖርላቸዋለሁ' ለምትላቸው ልጆቿ ስትል በሕይወት መትረፏን ነበር እንደተዓምር ያየችው። "እግዚአበሔር ጠብቆን ነው እንጂ ጥቂት ሸርተት ቢል ቀጥታ ወደገደሉ ነበር የሚገባው፤ የሚገርመው ከጎኔ የነበረችው የስምንት ወር ነፍሰጡር ከእግር መጫጫር የዘለለ አደጋ አልገጠማትም፤ ልጇ ላይ ምንም ጉዳት ሳይደርስበት ከወር በኋላ በሰላም ተገላግላለች።'' ያኔ አደጋው ሲደርስባት የመጀመሪያ ልጇየ6 ፣ሁለተኛው ደግሞ ገና የአንድ ዓመት ህጻን ነበሩ። '' ለልጆቼ ጉዳቱን ማስረዳት ከብዶኝ ነበር'' የእርሷ ጉዳት ከሌሎች የባሰበት ምክንያት ከአቀማመጧ ምናልባትም ካደረገችው ጫማ ጋር ሊያያዝ እንደሚችል ታስባለች። ''ረጅም ታኮ ጫማ ነበር ያደረግኩት፤እግሬንም በደንብ ዘርግቼው ከፊት ለፊት ባለው ወንበር ሥር ከትቼው ነበር ፤ ያ ይመስለኛል መኪናው ሲገለባበጥ ቁርጭምጭሚቴ አካባቢ ወንበሩ ይዞኝ የተሰበረው'' እርሷ ከኋላ ስለነበረች አታስተውለው እንጂ ጋቢና የተቀመጡት ተሳፋሪዎች ሹፌሩ ፍጥነቱን እንዲቀንስ ሲነግሩት እንዳንዴም እንቅልፍ ወሰድ ሲያደርገው በጩኸት እየተናገሩ...
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
67fd1bbf24744916a8504b9e44e49c80
11174ecbfcccb44fb3f067e3bfdc8268
ኤጀንሲው የማለዳና ሌሊት ቀዝቃዛ የአየር ሁኔታ እንደሚቀንስ አስታወቀ
በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ጥዋትና  ማታ ላይ የሚስተዋለው ቀዝቃዛማና ደረቃማ የአየር ሁኔታ እየቀነሰ እንደሚመጣ የብሔራዊ ሚቲዎሮሊጂ ኤጀንሲ አስታወቀ ። በኤጀንሲው  የአየር ትንበያና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ጊዚያዊ ዳይሬክተር ወይዘሮ ጫሊ ደበሌ ለዋልታ እንደገለጹት ሰሞኑን በላሊና ክስተት ምክንያት በአብዛኛው የአገሪቱ  አካባቢዎች የተፈጠረው ቀዝቃዛና ደረቃማ የአየር ሁኔታ በጥር ወር እንደሚቀንስና ወደ መደበኛ ሁኔታ እንደሚመለስ  የትንበያ መረጃዎች ያመለክታሉ ።በአሁኑ ወቅት የተከሰተው ቀዝቃዛና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ በተለይ በማለዳና በለሊት የሚስተዋል  መሆኑን  የጠቆሙት ወይዘሮ ጫሊ ክስተቱ በአገሪቱ ሰሜናዊ ምስራቅ፣ መካከለኛ ምስራቅና ደቡብ ደጋማ አከባቢዎች ላይ አይሏል ብለዋል ።በበጋ ወቅት ፀኃይ በደቡባዊ ንፍቀ ክበብ አካባቢ የምትገኝ በመሆኑ የሙቀት መጠን አነስተኛ እንደሚሆንና  በኤዢያ ሳይቤሪያ አካባቢ የተነሳው የተጠናከረ ከፍተኛ የአየር ግፊት የአረብ ባህረ ሰላጤን በማቋረጥ በኢትዮጵያ ላይ ደረቅና ቀዝቃዛማ የአየር ሁኔታ እንዲፈጠር አድርጓል ።እንደ ወይዘሮ ጫሊ ገለጻ የላሊና የአየር ሁኔታ ክስተት በበጋ ወቅት ደረቅና ቀዝቃዛማ ሁኔታን የሚፈጥርና  በክረምት ወቅት  ግን እርጥበትን የሚጨምር ነው ብለዋል ።ወቅቱ የመኸር የሰብል ምርት የሚሰበሰብበት እንደመሆኑ መጠን ቀዝቃዛ የአየር ሁኔታው አሉታዊ ተጽዕኖ እንዳያሳደር በባህላዊ  መንገድ የሙቀት መፍጠሪያ ዘዴዎች ጥቅም ላይ እንዲውሉ ጥሪ አቅርበዋል ። 
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://waltainfo.com/am/31534/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
fb777b0548362c6a8cc4a80f9070b685
861ca081b80bcb72e8e5bce6513093f0
ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ደደቢት | ቀጥታ የፅሁፍ ስርጭት
​​15′ 50′ ሳላዲን ሰይድ 31′ ምንተስኖት አዳነ | 71′ ጌታነህ ከበደ 72′ አበባውቡጣቆ (OG) ጨዋታው ተጠናቀቀ ! 90+1 ደደቢቶች በአጭር ቅብብል ወደተጋጣሚያቸው የግብ ክልል ለመድረስ በመቸገራቸው ከኋላ መስመር ረጅም ኳሶችን ወደ አጥቂዎቹ ለመላክ እየሞከሩ ይገኛሉ ።90′ ጭማሪ ደቂቃ 5 !89′ ቅዱስ ጊዮርጊሶች ከራሳቸው ግብ በረጃጅም ኳሶች በመጠቀም ለመውጣት እየሞከሩ ነው ።87′ ደደቢቶች በሽመክት በቀኝ በሽመክት ጉግሳ በኩል አድልተው እያጠቁ ይገኛሉ ። የቅዱስ ጊዮርጊስ ተጨዋቾች ሙሉ ለሙሉ በራሳቸው ሜዳ ላይ ሆነው እየተከላከሉ ነው ።85′ የተጨዋች ለውጥ ቅዱስ ጊዮርጊስአንዳርጋቸው ይላቅ በፕሪንስ ሴቭሪን ተተክቷል82′ ደደቢቶች የአቻነት ግብ ለማግኘት ወደፊት ገፍተው እየተጫወቱ ነው ። አብዛኛው የጨዋታ እንቅስቃሴ በቅዱስ ጊዮርጊስ ሜዳ ላይ ሆኗል ።80′ የተጨዋች ለውጥ ደደቢትአቤል እንዳለ ገብቶ ዳዊት ፍቃዱ ወጥቷል76 ‘ ቀይ ካርድ ደደቢት ብርሀኑ ቦጋለብርሀኑ ቦጋለ ያስር ሙገርዋን አላግባብ በመናገሩ በሁለተኛ ቢጫ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል ።74′ የተጨዋች ቅያሪ ቅዱስ ጊዮርጊስበሀይሉ አሰፋ በብሩኖ ኮኔ ተለውጦ ወጥቷል ።72 ጎል !  ደደቢት አበባው ቡጣቆ (OG)ከግራ መስመር ሰለሞን ሀብቴ ያሻገረውን ኳስ ሽመክት ሲሞክር በአበባው ቡጣቆ ተጨርፋ ለደደቢት ሁለተኛ ግብ ሆናለች ። 71 ጎል ! ደደቢት ጌታነህ ከበደበሳጥኑ ጠርዝ ላይ አስቻለው በጌታነህ ላይ በሰራው ጥፋት የተሰጠውን ቅጣት ምት ራሱ ጌታነህ በቀጥታ አስቆጥሮታል ። 65′ የተጨዋች ቅያሪ ቅዱስ ጊዮርጊስያስር ሙገርዋ አዳነ ግርማን ተክቶ ወደሜዳ ገብቷል ።65 ‘ ቢጫ ካርድ ቅዱስ ጊዮርጊስፍሬዘር ካሳ ኤፍሬም አሻሞ ላይ ጥፋት በመስራቱ የማስጠንቀቂያ ካርድ ተመልክቷል 64 ‘ ጌታነህ ከነደ ከረጅም ርቀት ከዳዊት የተቀበለውን ኳስ ሞክሩ በግብ ቋሚ ለጥቂት ወጥቶበታል ።62′ ቢጫ ካርድ ቅዱስ ጊዮርጊስ !አበባው ቡጣቆ በግራ መስመር በሽመክት ጉግሳ ላይ በሰራው ጥፋት የቢጫ ካርድ ተመክቷል ።57′ ሰለሞን  ከቀኝ መስመር ያሻማውን የማዕዘን ምት አክሊሉ በግንባሩ በመግጨት ቢሞክርም ኳስ በጎን ወጥታለች ። ደደቢት እስካሁን ከፈጠራቸው ይግብ ዕድሎች የተሻለ አጋጣሚ ነበር ።53 ‘ ቢጫ ካርዶች ደደቢት !የደደቢት ተጨዋቾች የተረበሹ ይመስላሉ ። ጌታነህ ከበደ በሀይሉን በክርን በመማታቱ ፣ ሽመክት ጉግሳ አስቻለው ላይ በሰረው ጥፋት እንዲሁም ብርሀኑ ቦጋለ ከዳኛ ጋር በመከራከሩ የቢጫ ካርድ ተመልክተዋል 50 ጎል ቅዱስ ጊዮርጊስ ሳላዲን ሰይድከግራ መስመር በሀይሉ ያሻማው ቅጣት ምት ክሌመንት በአግባቡ ማውጣት ተስኖት ሳላዲን ባርጌቾ በግንባሩ ሞክሯ ኳሷ የግቡን አግዳሚ ገጭታ ስትመለስ ሳላዲን ሰይድ አግኝቶ ለራሱ ሁለተኛ ለቡድኑ ሶስተኛ ጎል አድርጎታል ። 47′ ከሉውጡ በኋላ ደደቢት ከሶስቱ ተከላካዮች አንዱ የነበረውን ኩዌኩን በስዩም ቦታ ላይ በመቀየር የኋላመስመር ተሰላፊዎቹን ወደ አራት ከፍ አድርጓል ። የቡድኑ ቅርፅ አሁን ላይ ወደ 4 4 2 ቅርፅ የመጣ ይመስላል ። 46′ የተጨዋች ቅያሪ ደደቢት ኤፍሬም አሻሞ ገብቶ ስዩም ተስፋዬ ወጥቷል ።46′ ሁለተኛው የጨዋታ አጋማሽ በጌታነህ ከበደ አማካይነት ተጀምሯል ።የመጀመሪያው አጋማሽ ተጠናቀቀ ! 45′ ጭማሪ ደቂቃ 1 !42′ ደደቢቶች ለፊት መስመር ተሰላፊዎቻቸው የመጨረሻ ኳስ ማድረስ ተስኗቸዋል ። በተጋጣሚያቸው ሜዳ ላይ የሚነጠቋቸው ኳሶችም ለመልሶ መጠቃት እያጋለጣቸው ነው ። 39′ ፕሪንስ በግራ መስመር ያሻገረለትን ኳስ ሳላዲን በቀጥታ ሞክሮ በግቡ አናት ወጥቶበታል ።33′ ደደቢቶች ብርሀኑ ቦጋለን ወደመሀል በማስገባት ኤሪክ በነበረበት ቦታ ላይ ከሳምሶን ጥላሁን ጎን እንዲሆን በማድረግ ሰለሞን ሀብቴን የግራ መስመር ተመላላሽነት ቦታ ሰጥተውታል ።32′ የተጨዋች ለውጥ ደደቢት ኤሪክ ኦፖኩ በሰለሞን ሀብቴ ተተክቷል ። 31 ‘ ጎል ቅዱስ ጊዮርጊስ ምንተስኖት አዳነበሀይሉ አሰፋ ከቀኝ መስመር ያሻማውን ኳስ ምንተስኖት በግንባሩ አስቆጥሯል ። እንደመጀመሪያው ጎል ሁሉ አሁንም ግብ አግቢው ያለምንም ጫና ብቻውን ነበር ።29′ የደደቢት የመስመር ተመላላሾች በተሻለ ወደፊት ገፍተው ለመጨጫወት እየሞከሩ ነው ። ያም ሆኖ ቡድኑ እስካሁን ጠንካራ ሙከራ ማድረግ አልቻለም ።26′ ቢጫ ካርድአስቻለው ታመነ በጌታነህ ላይ ከሜዳው አጋማሽ የተወሰኑ ሜትሮች ጠጋ ብሎ በሰራው ጥፋት የጨዋታውን የመጀመሪያ የማስጠንቀቂያ ካርድ ተመልክቷል ።20′ ደደቢቶች የሚሰነዝሩት ጥቃት በ ጊዮርጊስ ሜዳ ላይ በቂ ተጨዋቾችን ያሳተፈ ባለመሆኑ በቀላሉ እየተቋረጠ ይገኛል ።18′ በሜዳው ቁመት በጊዮርጊስ ግብ ትይዩ በግምት ከ 20 ሜትር ጌታነህ የመታውን ቅጣት ምት የጊዮርጊስ ተከላካዮች ተደርበው አውጥተውታል ። በማዕዘን ምት ጨዋታው ቀጥሏል ።15 ‘ ጎል ቅዱስ ጊዮርጊስ ሳልሀዲን ሰይድ ፕሪንስ ከግራ መስመር ያሻገረለትን ኳስ በነፃ አቋቋም ላይ የነበረው ሳላዲን በቀጥታ በመምታት ግብ አድርጎታል ።10′ ደደቢት በመጀመሪያው ዙር ተደርጎ እንደነበረው ጨዋታ ሁሉ ዛሬም የመሀል ሜዳ የበላይነት ተወስዶበታል ።8′ በጨዋታው ቅዱስ ጊዮርጊሶች የበላይነቱን ወስደዋል ። በተደጋጋሚ ወደጎል እየደረሱ ከጨዋታ ውጪ እየሆኑ ነው ።4′ አዳነ ግርማ ከሳጥን ውጪ አክርሮ የሞከረውን ኳስ ዐይናለም ተደርቦ ሲያወጣበት ፕሪንስ አግኝቶ በድጋሜ ቢሞክርም ወደላይ ወጥቶበታል ።3′ ጌታነህ ከበደ በግምት ከ 25 ሜትር የተገኘውን ቅጣት ምት ሞክሮ ወደላይ ተነስቶበታል ።1′ ጨዋታው በቅዱስ ጊዮርጊሱ ሳላዲን ሰይድ አማካይነት ተጀመረ ።ተጨዋቾች እና ዳኞች ወደሜዳ ገብተዋል ከደቂቃዎች በኋላ ጨዋታው ይጀምራል ።የቅዱስ ጊዮርጊስ አሰላለፍ30 ሮበርት ኦዶንካራ2 ፍሬዘር ካሳ – 13 ሳላዲን በርጊቾ – 15 አስቻለው ታመነ – 4 አበባው ቡታቆ19 አዳነ ግርማ – 21 ተስፋዬ አለባቸው – 23 ምንተስኖት አዳነ11 ፕሪንስ ሰቭሬን – 7 ሳላዲን ሰይድ – 16 በሃይሉ አሰፋ ተጠባባቂዎች1 ፍሬው ጌታሁን12 ደጉ ደበበ25 አንዳርጋቸው ይላቅ3 መሀሪ መና18 አቡበከር ሳኒ24 ያስር ሙገርዋ17 ብሩኖ ኮኔየደደቢት አሰላለፍ33 ክሌመንት አዞንቶ 5 ኩዌኩ አንዶህ – 14 አክሊሉ አየነው – 6 አይናለም ኃይለ7 ስዩም ተስፋዬ – 8 ሳምሶን ጥላሁን – 29  ኤሪክ ኦፖኩ – 10 ብርሃኑ ቦጋለ 19 ሽመክት ጉግሳ9 ጌታነህ ከበደ – 17 ዳዊት ፍቃዱተጠባባቂዎች22 ታሪክ ጌትነት16 ሰለሞን ሐብቴ27 እያሱ ተስፋዬ15 ደስታ ደሙ18 አቤል እንዳለ21 ኤፍሬም አሻሞ12 ሮበን ኦባማ09፡54 አሁን የሁለቱ ቡድኖች ተጨዋቾች ወደመልበሻ ክፍል ገብተዋል ። በመቀጠል አሰላለፋቸውን ይዘን እንመለሳለን ።09፡30 ተጨዋቾች እና ዳኞች ወደሜዳ ገብተው ማሟሟቅ ጀምረዋል ።ዳኛየእለቱን ጨዋታ ኢንተርናሽናል አልቢትር በአምላክ ተሳማ የሚመራው ይሆናል ።ያለፉት 3 ጨዋታዎች ውጤትቅዱስ ጊዮርጊስ   | አቻ | አሸነፈ | አሸንፈደደቢት  | ተሸነፈ | አሸነፈ | አቻግንኙነትደደቢት በ 2002 ዓ.ም ወደሊጉ ከመጣ ጅምሮ ሁለቱ ቡድኖች 15 ጊዜ ተገናኝተዋል ። ከእነዚህ ጨዋታዎች ውስጥ ቅዱስ ጊዮርጊስ 10 ጊዜ ማሸነፍ ሲችል 25 ግቦችንም አስቆጥሯል ። ደደቢት በበኩሉ 15 ግቦችን አስቆጥሮ ሶስት ጨዋታዎችን በድል አጠናቋል ። የተቀሩት ሁለት ጨዋታዎች ደግሞ በአቻ ውጤት የተጠናቀቁ ነበሩ ። በዘንድሮው የውድድር አመት ሁለተኛው ሳምንት ላይ ባደረጉት ጨዋታም ቅዱስ ጊዮርጊስ 2 ለ 0 አሸንፎ ነበር ።ደረጃቅዱስ ጊዮርጊስ 32 ነጥቦችን በመሰብሰብ ሊጉን እየመራ ሲሆን ደደቢት በ4 ነጥቦች ዝቅ ብሎ በ 28 ነጥቦች በሁለተኛነት እየተከተለው ይገኛል ። ጤና ይስጥልኝ ክቡራት እና ክቡራን !በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 17ተኛ ሳምንት በሰንጠረዡ አናት ላይ የሚገኙት ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ደደቢት የሚፋለሙ ይሆናል ። ዛሬ የካቲት 25 2009 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታድየም ከቀኑ 10 ሰዐት ላይ የሚጀምረውን የዚህን አጓጊ ጨዋታ ዋና ዋና እንቅስቃሴዎች በቀጥታ የፅሁፍ ስርጭት ወደ እናንተ እናደርሳለን !መልካም ቆይታ ከሶከር ኢትዮጵያ ጋር !
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/26112
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
f56b6427c554d6bfeef866096834d5b5
10d0172aae00e91ea51bdad72b8fe11e
ታላቁ ቲግራኔስ
ታላቁ ቲግራኔስ (ሮማይስጥ፦ Tigranes፤ 148 ዓክልበ. - 63 ዓክልበ. የኖረ) ከ103 ዓክልበ. እስከ 55 ዓክልበ. ድረስ የአርመኒያ መንግሥት ንጉሥ ነበር። የአርመኒያ ሰዎች የአውሮፓ ታሪክ
null
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
f6a5259502673a17eb63388ef2310733
dd0bfb88e9e0eff444a3787385d62671
"ቤቶች ከመፍረሳቸው በፊት ዜጎች መጠለያ የማግኘት መብታቸው መከበር አለበት" ባለአደራ ምክር ቤት
ከ30 ሺ በላይ ቤተሰቦች የሚኖሩባቸው ቤቶች በምን ሁኔታ እንደተገነቡ፤ መቼ እንደተገነቡና በወቅቱ የከተማው አስተዳደር ለምን ኃላፊነታቸውን እንዳልተወጡ ለህዝብ መረጃ ሳይቀርብ ማፍረሱ ዜጎችን ከሰላማዊ ኑሯቸው ማፈናቀል፣ የዘፈቀደ አካሄድና በአስተዳደሩም ላይ ጥያቄ የሚያስከትል ነው ብሏል። "በምርጫ እሸነፋለሁ" በሚል ስጋት ውስጥ ያለ ጊዜያዊ አስተዳደር መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት ፣ ይህ እንቅስቃሴ ሕጋዊ ሽፋንን የተላበሰ መንግስታዊ የመሬት ወረራ ሆኖ አግኝተነዋል" በሚል መግለጫው አትቷል። • "በሰላማዊ ትግል እስከመጨረሻው በፅናት እንታገላለን" እስክንድር ነጋ • ''አዲስ አበባ የሁላችንም ከተማ ናት'' ከንቲባ ታከለ ኡማ ባለአደራ ምክር ቤቱ ከተማዋ ውስጥ ህገወጥነት መስፋፋት እንደሌለበት ቢያምንም ነዋሪዎች የመኖሪያ ቤት የማግኘት ፍላጎታቸው ሊሟላ ይገባል በሚለው መግለጫው ቤቶቹ የሚፈርስበት ወቅቱ ክረምት መሆኑም ተቀባይነት እንደሌለው ገልጿል። "ጊዜያዊ አስተዳደሩ እንደሚለው ቤቶቹ ሕገ ወጥ ናቸው ቢባል እንኳን፣ ዓመቱን ሙሉ ጠብቆ የክረምት ወቅት መባቻ ላይ ስናስገባ"አፈርሳለሁ" ብሎ መነሳቱ ፍጽሞ ሰብአዊነት እና ኃላፊነት የጎደለው አፈጻጸም ሆኖ አግኝተነዋል፡፡" ብሏል። አስተዳደሩ በጊዜያዊነትና እና በቋሚነት የመፍትሄ አቅጣጫዎች ባለማስቀመጡ ዜጎች ተፈናቅለው በየጎዳናው ላይ የሚጥላቸው ሁኔታም እንደሚፈጠርም አሳስቧል። በተጨማሪም ምክር ቤቱ በመግለጫው አስተዳደሩ ሊያደርጋቸው ይገባል የሚላቸውን የመፍትሄ ሃሳቦች ጠቁሟል። • ጠበቃ ሔኖክ አክሊሉና ሚካኤል መላክ እንዲለቀቁ አምነስቲ ጠየቀ የኃገሪቱ ህገመንግሥትም ሆነ ኢትዮጵያ የፈረመቻቸው አለም አቀፍ ህግጋት እንዲከበሩ በሚደነግገው መሰረት ቤቶች ከመፍረሳቸው በፊት ዜጎች መጠለያ የማግኘት መብታቸው እንዲከበርና፤ አስተዳደሩ አዳዲስ ህገወጥ ቤቶች እንዳይሰሩ በመከላከልና ህግጋቱን እያከበሩ እስከቀጣዩ ምርጫ ባለበት እንዲቆዩ የሚል ምክረ ኃሳብ ይዟል። እነዚህ ምክረ ኃሳቦች ተግባራዊ ካልሆኑ ግን ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንደሚገባ አስታውቋል።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
cf6e5ff7fbf51e71d671fd3942ee3050
a6543bf127167aa9d1c8d7519c1ce364
ማ ራዎ ከጠዋቱ 3 ሰዓት እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት፤ በሳምንት ለስድስት ቀናት ትሠራ ነበር።
እንቅልፍ በመቀነስ የሥራ ጫናን ‘የመበቀል’ ልማድ\nቻይና፣ ሻንጋይ ውስጥ ለሚገኝ መድኃኒት አምራች ትሠራ የነበረው ማ፤ በአጭር ጊዜ ነበር ሕይወቷ በሥራ የተዋጠው። ለመመገብ አጭር ሰዓት ብቻ ነበራት። ለመተኛትም እንዲሁ። "ከሥራ ውጪ ምንም የግል ሕይወት አልነበረኝም። ድብርት ይዞኝ ነበር" ትላለች። ሥራዋ ለግል ሕይወት ጊዜ ስላሳጥት እንቅልፏን መስዋዕት እያደረገች ለራሷ ጊዜ ለመስጠት ትሞክር ነበር። ካላት አጭር የመኝታ ጊዜ ቀንሳ ዜና ማንበብ፣ ቪድዮ ማየት ጀመረች። ብዙዎች እንደ ማ እንቅልፍ ትተው የተለያየ ተግባር ያከናውናሉ። ቀናቸው በሥራ ስለሚዋጥ ከምሽት ውጪ ክፍተት አያገኙም። ምሽት ላይ ከመተኛት ይልቅ ጊዜ በማጣት ሳቢያ ያልሠሩትን ነገር ያገባድዳሉ። ጋዜጠኛዋ ዳፊን ኪ ሊ "ቀናቸውን ባሻቸው መንገድ ማሳለፍ ያልቻሉ ሰዎች ማታ ከመጠን በላይ በማምሸት ለማካካስ ይሞክራሉ" ስትል ትዊተር ላይ ጽፋ ነበር። ጽሑፉን ከ4,500 በላይ ሰዎች ወደውታል። አንድ ሌላ ሰው ደግሞ "ቀኖቼ በኔ ሳይሆን በሌሎች ቁጥጥር ሥር ናቸው። ምሽቱ ግን የእኔ ነው" ሲል ጽፏል። በእንግሊዘኛ 'revenge bedtime procrastination' ይባላል። የሥራ ጫና የሚበዛባቸው ሰዎች ለእንቅልፍ ጊዜ ሲያገኙ ከመተኛት ይልቅ የተለያየ ሥራ ይሠራሉ። መጽሐፍ ያነባሉ፣ ቲቪ ያያሉ፣ ከሰዎች ጋር ያወራሉ ወዘተ. . . እንቅልፍን መበቀል እንደማለት ነው። እንቅልፍ ለምን እምቢ ይለናል? በቂ እንቅልፍ አለማግኘት የጤና ቀውስ ነው። እአአ 2019 ላይ በ12 አገሮች የተሠራ ጥናት እንደሚያሳየው ከ11,000 በላይ ሰዎች መተኛት ከሚገባቸው ሰዓት ባነሰ 6.8 ሰዓት ብቻ ይተኛሉ። በየቀኑ በአማካይ ስምንት ሰዓት መተኛት ይመከራል። አንዳንዶች መተኛት የማይችሉት ስለሚጨነቁ ወይም በዙሪያቸው ያሉ ነገሮች ስለሚረብሿቸው ነው። አብላጫውን ቁጥር የሚይዙ ሰዎች የማይተኙት ግን በሥራ ጫና ወይም በትምህርት ምክንያት ነው። ቻይና የተሠራ ጥናት ከ1990ዎቹ ወዲህ የተወለዱ ሰዎች በአግባቡ እንደማይተኙ ያሳያል። በተለይም በግዙፍ የቴክኖሎጂ ተቋሞች የሚሠሩ እምብዛም አይተኙም። የ33 ዓመቷ ጉ ቢንግ የምትሠራው ዲጂታል ኤጀንሲ ውስጥ ነው። ከሌሊት ስምንት ሰዓት በፊት አትተኛም። እሷ ብቻ ሳትሆንም ጓደኞቿም ከእኩለ ሌሊት በኋላ ነው የሚተኙት። ጉ ልተኛ ብትል እንኳን አምሽታ መሥራት ስላለባት መተኛት አትችልም። ለእንቅልፍ ጊዜ ስታገኝ ደግሞ የራሷን ሥራ መሥራት ስለምትጀምር ሳትተኛ ትቀራለች። "ጊዜዬን መሥሪያ ቤቱ ቀምቶኛል። ያለኝ ጊዜ ከሥራ ውጪ ያለው ሰዓት ብቻ ነው። ስለዚህ እንቅልፍ ትቼ የተሰረቅኩትን ሰዓት አካክሳለሁ" ትላለች። በሥራና በግል ሕይወት መካከል መስመር ጠፍቷል በሼፈልድ ዩኒቨርስቲ የሥነ ልቦና መምህርቷ ሲያራ ኬሊ፤ በሥራ እና በግል ሕይወት መካከል ያለው መስመር እየጠፋ ነው ይላሉ። አንድ ሰው ከሥራ ባልደረባው ጋር በማንኛውም ጊዜ ይነጋገራል። ይህ ግንኙነት ደግሞ ሥራና የግል ሕይወትን እያደበላለቀ ነው። ሥራ ሲበዛ የመዝናኛ ጊዜን እንደሚቀንስ እሙን ነው። መዝናኛ ጊዜ ለማግኘት ብሎ እንቅልፍን መስዋዕት ማድረግ ግን ጤናማ እንዳልሆነ ባለሙያዎች ይናገራሉ። ዘለግ ላለ ጊዜ እንቅልፍ ማጣት ለተለያየ የአዕምሮ ህመም ያጋልጣል። የሥነ ልቦና መምህርቷ ሲያራ ሰዎች መዝናኛ ሰዓት የግድ ማግኘት አለባቸው። የሥራ ጫና መዝናኛ ሰዓት ሲያሳጣቸው እንቅልፍ ትተው የሚዝናኑትም ለዚያ ነው። "ሠራተኞች መንፈሳቸውን የሚያዝናኑበት መንገድ ሊያገኙ ይገባል" ሲሉ አሠሪዎች ጉዳዩን እንዲያስቡበት ይመክራሉ። የሠራተኞች መብት ላይ የሚሠሩት የማኅበረሰብ ባለሙያ ሂውንግ ቹንግ፤ ሠራተኞች የእንቅልፍ እንዲሁም የመዝናኛ ሰዓት በሚያሳጣቸው መንገድ ሥራ ሊደራረብባቸው...
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
32a68fcc0a60df11a130e9c029604a32
40a27a9d76ec350c40c9046477506467
አዲሱ የብር ለውጥ ከተጀመረ ወዲህ 14 ቢሊየን ብር ወደ ባንክ ገቢ መደረጉ ተገለጸ
አዲስ አበባ ፣መስከረም 23 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ አዲሱ የብር ለውጥ ከተጀመረ ወዲህ 14 ቢሊየን ብር ወደ ባንክ ገቢ መደረጉን ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ።አዲሱ የብር ለውጥ ከተጀመረ ባሉት 14 ቀናት ውስጥ ብቻ 580 ሺህ ዜጎች አዲስ የሂሳብ አካውንት ሲከፍቱ ÷ ከባንክ ውጭ የነበረ 14 ቢሊዮን ብርም ወደ ባንክ መግባቱን ብሔራዊ ባንክ ገልጿል።67 ቢሊየን አዲሱን ብር በመላ አገሪቱ ባሉ 99 ነጥብ 9 በመቶ የባንክ ቅርንጫፎች ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲዳደረስ መደረጉን የብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶክተር ይናገር ደሴ ገልፀዋል።የብር ለውጡ ያስፈለገበት አንዱ ዓላማ ከባንክ ውጭ ያለን ገንዘብ ወደባንክ የማስመለስ ጉዳይ እንደነበር ያስታወሱት የባንኩ ገዥ ÷ ከዚህ አንጻር በአጭር ጊዜ ውስጥ ይሄንን ያህል ገንዘብ ወደ ባንክ ስርዓቱ መመለሱ የዓላማውን መሳካት ያሳያል ብለዋል።የብር ለውጡ ሌላኛው ዓለማ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነትን ማሳደግ እንደሆነ የገለጹት ዶክተር ይናገር÷ አዲስ የባንክ ሂሳብ ከተከፈቱት 580 ሺህ ዜጎች በተጨማሪ በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎች አካውንት ይከፍታሉ ተብሎ ይጠበቃል።ህብረተሰቡ በተያዘው የጊዜ ገደብ ውስጥ በእጁ ያለውን አሮጌ የብር ኖት በአዲሱ መቀየር እንዳለበትም ዶክተር ይናገር ማሳሰባቸውን ኢቢሲ ዘግቧል።የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%8a%a0%e1%8b%b2%e1%88%b1-%e1%8b%a8%e1%89%a5%e1%88%ad-%e1%88%88%e1%8b%8d%e1%8c%a5-%e1%8a%a8%e1%89%b0%e1%8c%80%e1%88%98%e1%88%a8-%e1%8b%88%e1%8b%b2%e1%88%85-14-%e1%89%a2%e1%88%8a%e1%8b%a8%e1%8a%95/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
ccde672ae98d7f69cdb8eeb49e97a3d8
8b3040f7efe1db2f25af333adb11a3cd
የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገንቢ ያልሆኑ አስተያየቶችን እየሰጡ ነው ሲሉ የውጭ ጉዳይ ቃል አቀባይ ወቀሱ
የውጭ ጉዳይ  ቃል አቀባይ አቶ መለስ ዓለም የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሜህ ሽኩሪ ከስምምነት ውጭ የሆኑና ገንቢ ያልሆኑ አስተያየቶችን እየሰጡ ነው ሲሉ ወቀሱ፡፡ ቃል አቀባዩ ይኼንን ያሉት ዛሬ ግንቦት 2 ቀን 2010 ዓ.ም. በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው፡፡ካርቱም ሱዳን መጋቢት 28 ቀን 2010 ዓ.ም. የተካሄደው ድርድር ውጤታማ ሳይሆን ከቀረ በኋላ፣ ሚኒስቴሩ ለሌላ ውይይት ካይሮ ላይ ሚያዝያ 12 ቀን 2010 ዓ.ም. ሚኒስትሮቹ እንዲሰበሰቡ አሳስበው ነበር፡፡ይሁንና፣ የተለያዩ ሚዲያዎች ኢትዮጵያና ሱዳን ለሚኒስትሩ ጥሪ መልስ ሳይሰጡ እንደቀሩ ተዘግቧል፡፡ ሆኖም የሦስቱ አገሮች የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ግንቦት 7 ቀን 2010 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ተገናኝተው ለመወያየት ቀጠሮ ይዘዋል ሲሉ ቃል አቀባዩ ተናግረዋል፡፡
5ፖለቲካ
https://www.ethiopianreporter.com/article/10283
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
64f073229f78a83d15ddc431db9c87f4
9d93c1460fdfa053ba2a8bed406e28ea
አንተነህ ተስፋዬ ወደ ሰበታ ከተማ አምርቷል
ሰበታ ከተማ ወደ መከላከያ አምርቶ የነበረው የመሀል ተከላካይ ስፍራ ተጫዋቹ አንተነህ ተስፋዬን በእጁ አስገብቷል፡፡ከወራት በፊት ለመከላከያ ለመጫወት ፈርሞ የነበረው ተጫዋቹ ቡድኑ በከፍተኛ ሊጉ እንዲጫወት በመወሰኑ ክለቡን በስምምነት ከለቀቀ በኋላ ነው ወደ ሰበታ ሊያመራ የቻለው። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ስብስብ ውስጥ ተካቶ የሚገኘው የቀድሞው የአርባምንጭ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ተጫዋች አንተነህ በድሬዳዋ ከተማ ሁለት ድንቅ ዓመታትን ማሳለፉ ይታወሳል፡፡በአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ የሚሳተፈው ሰበታ ከተማ በነገው ዕለትም ሁለት የውጪ ሀገር የአጥቂ ስፍራ ተጫዋቾችን ሊያስፈርም እንደሚችል የክለቡ ስራ አስኪያጅ አቶ ዓለማየሁ ምንዳ ለሶከር ኢትዮጵያ ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/51260
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification