query_id
stringlengths
32
32
passage_id
stringlengths
32
32
query
stringlengths
1
300
passage
stringlengths
95
13.7k
category
class label
6 classes
link
stringlengths
28
740
source_dataset
stringclasses
4 values
cb1046254be35c0da1666fb012884928
b080930c1c35070fe71498a332442fd6
ኮቪድ-19 በት/ቤቶች ላይ የፈጠረው ጫና
በዓለም ዙሪያ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ትምህርት ቤቶች እንዲዘጉ በማስገደዱ ዓለማችን በህፃናትትምህርት ላይ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚዘልቅ የከበደ አደጋ ተደቅኖበታል ሲሉ የተመድ ዋና ፀኃፊ አንቶንዮ ጉቴሬዥ አሳሰቡ።ዋና ፀኃፊው ይህን ያሳሰቡት "መፃኢ ተስፋችንን እንታደግ" በሚል ርዕስ የመንግሥታቱ ድርጅት የጀመረውን አዲስ ዘመቻ ትናንት ባስተዋወቁበት ንግግራቸው ነው።የዘመቻው ዓላማ በድህረ ኮቪድ-19 መደበኛ ትምህርትን መመለስና ማጠናከር ላይ ትኩረት መስጠት መሆኑ ተገልጿል።እኤአ ሃምሌ አጋማሽ ድረስ በ106 ሃገሮች ከ1ቢሊዮን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸውና 40ሺህ ህፃናት ደግሞ ከመዋዕለ ህጻናት ውጪ ሆነዋል ብለዋል።ወረርሽኙን ከተቆጣጠርን በኋላ ቅድሚያ ትኩረታችን ህፃናትን ወደትምህርት ገበታቸው መመለስ መሆን ይኖርበታል ሲሉ አሳስበው በተለይም አካል ጉዳተኞች፣ ልጃገረዶች፣ ስደተኞችና ተፈናቃዮች የተለየ ትኩረት ሊሰጣቸው እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
4ዓለም አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/generational-catastrophe-possible-as-pandemic-creates-education-crisis-8-4-2020/5530199.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
a95ba189bc4a079346e5fe9c97b4661c
97d0dbd8ea8cf7287934d354be5a6ed6
ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ከጃፓንና ደቡብ ኮሪያ መሪዎች ጋር ሊወያዩ ነው
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 9፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ በሚቀጥለው ሳምንት ከጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤ እና ከደቡብ ኮሪያው ፕሬዚዳንት ሙን ጃ ኢን ጋር ሊወያዩ ነው።መሪዎቹ የሚያካሂዱት የሶስትዮሽ ውይይይት በፈረንጆቹ  የፊታችን ታህሳስ 24 ቀን በደቡብ ምዕራብ ቻይና ቸንግዱ ከተማ የሚያካሄድ መሆኑን የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።ከሶስትዮሽ ውይይቱ በፊትም ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ከሀገራቱ መሪዎች ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ የተናጠል ውይይት የሚያድርጉ መሆኑ ተመላክቷል።የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉዳዩን አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ፥መሪዎቹ በሶስትዮሽ ውይይታቸው  በተለያዩ ቀጠናዊና እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ የሚመክሩ መሆኑን አስታውቋልበተለይም በሰሜን ኮሪየ የኒውክሌር ጦር መሳሪያ መርሃ ግብር ዙሪያ በጥልቀት የሚመክሩ መሆኑ ነው የተገለጸው።በቅርቡ ሩሲያ እና ቻይና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰሜን ኮሪያ ላይ ከጣላቸው ማዕቀቦች ውስጥ የተወሰኑት እንዲነሱ ሃሳብ ማቅረባቸው ይታወሳል።ይህም ሰሜን ኮሪያ በኒውክሌር የጦር መሳሪያ ዙሪያ ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን ድርድር እንደ አዲስ በመጀመር አጠናክራ እንድትቀጥል የሚያበረታታ መሆኑ ተገልጿል።አሜሪካ በበኩሏ በሩሲያ እና ቻይና የቀረበው ረቂቅ ሃሳብ በትክክለኛው ጊዜ ያልቀረበ ከመሆኑ ባሻር የወቅቱን ነባራዊ ሁኔታ ያላገናዘበ ስትል አጣጥላዋለች።ምንጭ፦  ሲ ጂ ቲ ኤን
4ዓለም አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%8d%95%e1%88%ac%e1%8b%9a%e1%8b%b3%e1%8a%95%e1%89%b5-%e1%88%ba-%e1%8c%82%e1%8a%95%e1%8d%92%e1%8a%95%e1%8c%8d-%e1%8a%a8%e1%8c%83%e1%8d%93%e1%8a%95%e1%8a%93-%e1%8b%b0%e1%89%a1%e1%89%a5-%e1%8a%ae/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
39dba64ac8cfa971ce8fcb2e4a4941df
222a07c9df164055eeffc35d004c33b4
የከፍተኛ ሊግ ወሳኝ ጨዋታዎች እና ሌሎች መረጃዎች
የምድብ ሐ ሁለት ጨዋታዎች አይከናወኑምየከፍተኛ ሊግ ምድብ ሐ 20ኛ ሳምንት አራት ጨዋታዎች ነገ ሲደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ግን ወደ ሌላ ጊዜ መሸጋገራቸውን የከፍተኛ ሊግ ኮሚቴ አስታውቋል። በነቀምት ከተማው ተጫዋች ወንድወሰን ዮሐንስ ድንገተኛ ህልፈት ምክንያት ነቀምት ከተማ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ከሚገኘው አርባምንጭ ከተማ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ የማይኖር በመሆኑ የመሪው ሀዲያ ሆሳዕና እና ከምባታ ሺንሺቾ ጨዋታ መራዘሙን አቶ ኢብራሂም አህመድ ለሶከር ኢትዮጵያ ተናግረዋል። ” ሊጉ ውበቱን ጠብቆ እንዲጓዝ የሁለቱ ጨዋታን በይደር አቆይተነዋል። ሌሎቹ ጨዋታዎች ግን ይደረጋሉ፤ በተመረጡ ጨዋታዎች ላይም ተጨማሪ ተቆጣጣሪዎች ተልከዋል። ” ያሉት አቶ ኢብራሂም በነቀምቱ ተጫዋች ወንድወሰን ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘንም በኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ስም ገልፀዋል።ሁለት ተፎካካሪዎች የቀሩበት የምድብ ሀ ትንቅንቅበምድብ ሀ ባለፈው ሳምንት ደሴ ከተማ ተስተካካይ ጨዋታውን ከወሎ ኮምቦልቻ ጋር አድርጎ አቻ በመለያየቱ ከምድቡ ወደ ፕሪምየር ሊግ ለማለፍ የሚደረገው ፉክክር በሰበታ ከተማ እና ለገጣፎ ለገዳዲ መካከል ሆኗል። በ20ኛው ሳምንት ሁለቱም ቡድኖች ጠንካራ ጨዋታ የሚጠብቃቸው ሲሆን ሰበታ ከተማ ከ ደሴ ከተማ፤ ለገጣፎ ለገዳዲ ከ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ይጫወታሉ።የአራት ነጥብ ልዩነት ይዞ ምድቡን እየመራ የሚገኘው ሰበታ ከተማ አንድ እግሩን ወደ ፕሪምየር ሊጉ የማስገባት አላማን አንግቦ ደሴ ከተማን በሜዳው ያስተናግዳል። ሰበታ ይህን ጨዋታ አሸንፎ ለገጣፎ የሚሸነፍ ከሆነም ከ2003 በኋላ ዳግም ወደ ሊጉ መመለሱን የሚያረጋግጥ ይሆናል።በአሰልጣኝ ክፍሌ ቦልተና እየሰለጠነ የሚገኘው ሰበታ ከተማ በውድድር ዓመቱ እስካሁን ሽንፈት ያላስተናገደ ብቸኛው የከፍተኛ ሊግ ቡድን ሲሆን ደሴ በአንፃሩ በሁለተኛው ዙር ከየትኛውም ቡድን በተሻለ ከፍተኛ ማንሰራራት አሳይቶ ሦስተኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል።በጨዋታው ዙርያ የሰበታ ከተማው አሰልጣኝ ክፍሌ ቦልተና ለሶከር ኢትዮጵያ ይህን ብለዋል። ” ጨዋታው ከበድ ይላል። ምክንያቱም ደሴ ከተማ በሁለተኛው ውድድር አጋማሽ ተጠናክሮ የቀረበ ቡድን ነው። ሆኖም ቡድኔ ከመቼውም ጊዜ በላይ በሥነ ልቦናም ሆነ በአካል ብቃት እንዲሁም በሜዳ ላይ እንቅስቃሴ የተሻለ ደረጃ ላይ ይገኛል። በልምምድ ሜዳ ሳለን ከንቲባው ሜዳ ድረስ በመምጣት ተጫዋቾቼንም ሆነ የአሰልጣኙን አባላት አበረታተዋል። አሁን ደጋፊው ላይ ትልቅ መነቃቃት ተፈጥሯል። ይህም ለኛ ሌላ ኃይል ነው። በሜዳችን ያለመሸነፍ ጉዛችንን አስጠብቀን እንጓዛለን። ” ብለዋል።ሁለቱ ቡድኖች በመጀመርያው ዙር ደሴ ላይ ባደረጉት ጨዋታ ሰበታ 2-1 አሸንፎ ተመልሷል።ለገጣፎ ለገዳዲ የሰበታን ነጥብ መጣል ተስፋ በማድረግ ከሜዳው ኢትዮ ኤሌክትሪክን ይገጥማል። በወጣቱ አሰልጣኝ ዳዊት የሚመራው ለገጣፎ በአራት ነጥብ የራቀው ሰበታ ከተማን በ21ኛ ሳምንት በሜዳው የሚያስተናግድ እንደመሆኑ ከዚህ ጨዋታ ሙሉ ሦስት ነጥብ ማግኘት ለመጀመርያ ጊዜ ወደ ፕሪምየር ሊግ ለመግባት ለሚያደርገው ጉዞ ስንቅ ይሆነዋል።የለገጣፎው አሰልጣኝ ዳዊት ሐብታሙ ለሶከር ኢትዮጵያ በሰጡት አስተያየት ተጋጣሚያቸው ተቀራራቢ አጨዋወት ያለው መሆኑ እንደሚያመቻቸው ተናግረዋል። ” ተጋጣሚያችን ኳስን መሰረት አድርጎ የሚጫወት ቡድን ነው። በመጀመሪያው ዙር ባደረግነው ጨዋታ በደንብ አይተናቸዋል። አጨዋወታቸው ከእኛ ጋር ተቀራራቢ እንደመሆኑ የስፖርት ቤተሰብ ጥሩ ጨዋታ የሚያይ ይመስለኛል። ቡድናችን አሁን ላይ አንድ ተጫዋች በቅጣት ከማጣቱ ውጪ ሁሉም በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛሉ። ይህን ጨዋታ በማሸነፍ ወደ ፕሪምየር ሊግ ለማደግ የምናደርገውን የትንቅንቅ አጠናክረን እንቀጥላለን። ተጫዋቾቼም ይህን ያደርጉታል። ” ብለዋል።በመጀመሪያው ዙር መርሀ ግብር ለገጣፎ ላይ ባደረጉት ጨዋታ ለገጣፎ ለገዳዲ 1-0 ማሸነፉ ይታወሳል።የሜዳ ለውጥ መድን ሜዳ ላይ ጨዋታውን ሲከናውን የቆየው ኢኮስኮ በዚህ ሳምንት የሜዳ ለውጥ አድርጓል። ምክንያት ተብሎ የቀረበው የኢትዮጵያ መድን ሜዳውን ለጤና ቡድን በመሰጠቱ ሲሆን ከአዲስ አበባ ከተማ ጋር የሚያደርገውን ጨዋታም በአዲስ አበባ ስታዲየም እንደሚያደርግ የቡድን መሪው ሙሉጌታ አሰፋ ለሶከር ኢትዮጵያ ገልፀዋል። የአቃቂ ቃሊቲ እና ቡራዩ ከተማ ጨዋታም በተመሳሳይ አዲስ አበባ ስታድየም ላይ በ4:00 ይካሄዳል።የሳምንቱ ጨዋታዎች (20ኛ ሳምንት)ምድብ ሀ እሁድ ሰኔ 2 ቀን 2011አቃቂ ቃሊቲ (9:00) ቡራዩ ከተማ ፌዴራል ፖሊስ (9:00) ወልዲያ አክሱም ከተማ (9:00) ወሎ ኮምበልቻ አውስኮድ (9:00) ገላን ከተማ ኢትዮ ኤሌክትሪክ (9:00) ለገጣፎ ለገዳዲ ሰበታ ከተማ (9:00) ደሴ ከተማምድብ ለ እሁድ ሰኔ 2 ቀን 2011ሀላባ ከተማ (9:00) ሶዶ ከተማ ናሽናል ሴሜንት (9:00) የካ ክ/ከተማ ድሬዳዎ ፖሊስ (9:00) ነገሌ አርሲ ኢኮስኮ (9:00) አዲስ አበባ ከተማ ዲላ ከተማ (9:00) ኢትዮጵያ መድን ሀምበሪቾ (9:00) ወልቂጤ ከተማምድብ ሐ እሁድ ሰኔ 2 ቀን 2011ቡታጅራ ከተማ (9:00) ቤንች ማጂ ቡና ነገሌ ቦረና (9:00) ጅማ አባቡና ሻሸመኔ ከተማ (9:00) ስልጤ ወራቤ ካፋ ቡና (9:00) ቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/48814
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
1b499a6548c059ea4b3aac1273f51116
461eb83b299aa3d15d343b6005f22663
በኦሮሚያ ክልል ግጭት ለተፈናቀሉ ወገኖች ከአምስት ሺሕ በላይ ሰዎች ዕርዳታ ለገሱ
ሰሞኑን በኦሮሚያ ክልል ውስጥ ተከስቶ በነበረው ግጭት ሳቢያ ከመኖሪያ ቤታቸው ለተፈናቀሉና በአብያተ ክርስቲያናትና በሌሎች ሥፍራዎች ተጠልለው ለሚገኙ ወገኖች፣ በአዲስ አበባ ሰብዓዊ ዕርዳታ እየተሰበሰበ ነው፡፡ ከአምስት ሺሕ በላይ ሰዎች ዕርዳታ መለገሳቸው ታውቋል፡፡ከረቡዕ ጥቅምት 12 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ በክልሉ የተጀመረው ተቃውሞ ወደ ግጭት ተለውጦ በተፈጸሙ ጥቃቶች 78 ሰዎች ሕይወታቸው ሲያልፍ፣ በርካቶች ከመኖሪያቸው ተፈናቅለው በተለያዩ ሥፍራዎች ተጠልለዋል፡፡ በአገር ፍቅር ቴአትር ቤት ለእነዚህ ወገኖች እየተሰበሰበ በሚገኘው ዕርዳታ ከልጅ እስከ አዋቂ የሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎች ዕርዳታቸውን እየለገሱ መሆናቸውን፣ እስከ ዓርብ ጥቅምት 21 ቀን 2012 በተደረገው ዕርዳታም ከአምስት ሺሕ በላይ ግለሰቦች ደረቅ ምግቦች፣ ዘይት፣ አልባሳት፣ ውኃና የቤት ቁሳቁሶች ማበርከታቸውን የዕርዳታ አስተባባሪዎች አስረድተዋል፡፡ ሰብዓዊ ዕርዳታውን በበጎ ፈቃደኝነት ከሚያስተባብሩት አንዱ አቶ መሐመድ ካሳ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ሰሞኑን በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የተከሰቱት ችግሮች እርስ በርስ አለመደማመጥ፣ በዕርጋታ አለመነጋገርና የጥሞና መጉደል የፈጠረው መሆኑንና ይህም በርካታ ንፁኃን ዜጎች ከቀያቸው እንዲፈናቀሉና ዕርዳታ እንዲሹ ምክንያት ሆኗል፡፡ አንድ ሰው ሠርቶ ብዙ ቤተሰቡን በሚያስተዳድርበት፣ ታላላቆች ታናናሾቻቸውን በሚንከባከቡበት የኢትዮጵያ የአኗኗር ዘይቤ እንዲህ ዓይነቱ ችግር ሲከሰት ጉዳቱ እንደሚከብድ ያስታወሱት አቶ መሐመድ፣ ለእነዚህ ወገኖች ሰብዓዊ ዕርዳታውን አጠናክሮ ቶሎ መድረሱ ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡ በግጭት ምክንያት ነዋሪዎች ከቤታቸው ሲፈናቀሉ ሕፃናት፣ ሴቶች፣ አረጋውያንና የመንቀሳቀስ ችግር ያለባቸው እንደሚጎዱና ለእነዚህ ወገኖች ሰብዓዊ ዕርዳታ ማድረግ፣ አለሁ ማለትና ከጎን መቆም አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከዚህ ቀደም ቅድሚያ ለሰብዓዊነት በሚል ዕርዳታዎችን ሲያሰባስቡ እንደነበር፣ አሁን ‹‹ኬር ኤንድ ሼር›› በሚል በማኅበራዊ የትስስር ገጾች ዕርዳታ ከሚያደርግ ቡድን ጋር ተባብረው እየሠሩ መሆኑን፣ በዚህም አልሚ ምግቦችንና የሕክምና ቁሳቁስን ጨምሮ የተለያዩ ሰብዓዊ ድጋፎች መገኘታቸውን ገልጸዋል፡፡ ሰኞ ጥቅምት 17 ቀን 2012 ዓ.ም. የተጀመረው ሰብዓዊ ዕርዳታ የማሰባሰብ ሥራ እስከ ማክሰኞ ጥቅምት 25 ቀን ድረስ የሚዘልቅ መሆኑንና አርቲስቶች፣ የጉዞ ዓድዋ ተጓዦች፣ የእምነት አባቶችና ሌሎችም በጎ ፈቃደኞች በዓይነት ብቻ የሚሰጠውን ዕርዳታ እያስተባበሩ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡ በሥፍራው ሲያስተባብር የነበረው አቶ ያሬድ ሹመቴ ዕርዳታ የማሰባሰቡን ሥራ እነሱ ሲያከናውኑ፣ ዕርዳታውን ተፈናቃዮች ወዳሉባቸው አካባቢዎች በመውሰድ የሚተባበሩት ቀይ መስቀል ማኅበርና ብሔራዊ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን መሆናቸውን አስረድቷል፡፡ እስካሁን ወደ አርሲ ዶዶላ ከሕፃናት እስከ አዋቂ ሊያገለግሉ የሚችሉ ምግብና አልባሳት በአንድ መኪና ተጭነው የተላኩ ሲሆን፣ በቀጣይ ችግሩ ባሉባቸው አካባቢዎች ለማድረስ እየተሠራ መሆኑን አክሏል፡፡ ድሬዳዋ፣ ምሥራቅ ሐረርጌ፣ ባሌ ሮቤ፣ አርሲ ዶዶላና ኮፈሌ በአስቸኳይ የሚላኩባቸው ቦታዎች እንደሆኑና ከዚህ በኋላም በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች እንደሚላክ ጠቁመዋል፡፡ ኅብረተሰቡ እስከ ቀነ ገደቡ በዓይነት ብቻ ዕርዳታ እንዲያደርግም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ እስከ ሐሙስ ጥቅምት 20 ቀን 2011 ዓ.ም. ከለጋሾች ከስምንት እስከ አሥር ሚሊዮን ብር የሚገመቱ የተለያዩ የዕርዳታ ቁሳቁሶች መገኘታቸውን፣ አስተባባሪዎቹ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
5ፖለቲካ
https://www.ethiopianreporter.com/article/17188
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
3626bd3990fdb3859df7fe8b210253f3
87e85991a86d359f5e1ff57c187d8e35
​”የተሰጠኝን ሚና በትጋት መወጣት ነው የምፈልገው” ሱሌይማን ሰሚድ
ሱሌማን ሰሚድ ይባላል። ለአዳማ ከተማ በቀኝ መስመር ተከላካይነት አመዛኙን የፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች በመጀመርያ ተሰላፊነት እየተጫወተ ይገኛል። ከተለመደ ቦታው ውጪ እየተጫወተ የሚገኘው የአዳማው 24 ቁጥር ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ እያሳየ ይገኛል። ሱሌይማን በእግርኳስ ህይወቱ፣ በሚና ለውጡ እና በወደፊት እቅዶቹ ዙርያ ከሶከር ኢትዮጵያ ጋር ያደረገውን ቆይታ እነሆ። የሱሌይማን ትውልድ እና እድገት በቅርብ አመታት ኮከቦችን ለኢትዮጵያ እግርኳስ እያበረከተች በምትገኘው አሶሳ ከተማ ነው። የወጣቱ የእግርኳስ ህይወት የተጀመረውም በዚሁ ከተማ መንደሮች በመጫወት ነው። ” ከመኖርያ ቤቴ አካባቢ 50 ሜትር ርቆ ትልቅ ስታድየም አለ። ከትምህርት ቤት ስመለስ የእኔ ታላላቆች ኳስ ሲጫወቱ ከጎል ጀርባ በመሆን የሚጫወቱበትን ኳስ እያቀበልኩ ሰው ሲጎድልባቸው ደግሞ አብሬ እየተጫወትኩ የእግርኳስ ተጨዋች የመሆን ፍላጎቴ እየጨመረ መጣ። በኋላም ለትምህርት ቤት ውድድር መጫወት ጀምሬ ባለበት አጋጣሚ በፍቃዱ የተባለ አሰልጣኝ የሚመራው ሲት ቦይስ የሚባል ፕሮጀክት ነበር። አሰልጣኙ የማደርገውን ጥሩ እንቅስቃሴ በመመልከት ‘ ና እዚህ ፕሮጀክት ስራ። እኔ እፈልግሀለው። ‘ ብሎ ሲጠራኝ በሙሉ ፍቃደኝነት ወደ ፕሮጀክት በመቀላቀል እግርኳስን ህይወቴን በአሰልጣኝ የመሰልጠን ጅማሮዬን አደረኩ” ይላል። ሱሌማን በዚህ ፕሮጀክት በቆየባቸው የሁለት አመታት ብዙ የእግርኳስ መሰረታዊ ስልጠናዎችን እንዳገኘ ይገልፃል። በትልቅ ደረጃ እግርኳስ ተጨዋች ለመሆን የሚያስችለውን ህልሙን ሊያሳካ የሚችልበት መንገድ የተጠረገለት ግን በ2006 ሻሸመኔ ላይ በተደረገ ውድድር ነበር።” በ2006 ሻሸመኔ ከተማ ላይ በተካሄደው ሀገር አቀፍ የፕሮጀክት ምዘና ውድድር ላይ አሶሳን በመወከል ተሳትፌ ባሳየሁት ጥሩ እንቅስቃሴ ተመርጬ ከቤተሰብ ከትውልድ ስፍራዬ ርቄ ወደ አአ በመምጣት የኢትዮዽያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚን ተቀላቀልኩ። ለሦስት ተከታታይ አመታት በጣም ጠቃሚ የሆኑ ስልጠናዎችን አግኝቻለሁ። አሁን ላለው የእግርኳስ ህይወቴ መሰረት የጣልኩበት ቆይታም አድርጌያለው። በአካዳሚ ቆይታዬ አበበ በቂላ ስታድየም ላይ በአአ እግርኳስ ፌዴሬሽን በሚዘጋጀው የተስፋ ቡድኖች ጨዋታዎች ላይም ተሰላፊ ነበርኩ። ” እውነት ለመናገር በአካዳሚ ውስጥ ገብቶ እግርኳስን መሰልጠን ብዙ ጠቀሜታ ቢኖረውም ዋናው ነገር ከቤተሰብ ከትውልድ መንደርህ ተለይተህ አካዳሚ ስትገባ የሆነ አላማ እንዳለህ ታስባለህ። ይህን አላማ ለማሳካት ደግሞ አሰልጣኞች ከሚሰጡኝ ስልጠና ባሻገር በግል የተለያዩ ልምምዶችን ጠንክረህ እንድሰራ አድርጎኛል። ስለዚህ አካዳሚ ገብቼ ያገኘሁት ጠቀሜታ በአላማ እንድትኖር ለአላማ እንድትሰራ ፣ ፕሮፌሽናል የመሆን ህልም እንዲኖርህ አንተን ብቁ ሊያደርግ የሚያስችል የስልጠና ማዕከል ነው ” ተስፈኛው ወጣት በአካዳሚ በነበረው ቆይታ ቡድኑ በተስፋ ውድድር ላይ በሚያሳየው ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ ጎልቶ መውጣት ችሏል። በአካዳሚው ለነበረው ቆይታ እና ለነበረው ጥሩ ጊዜ እንዲሁም ድጋፍ ላደረጉለት አካላት በሙሉ ምስጋናውን ያቀርባል። የሱሌይማን ቀጣይ ማረፍያ እና የመጀመርያ ክለቡ አዳማ ከተማ ነው። ተጫዋቹ በ2008 ክረምት አካዳሚን ለቆ በአሸናፊ በቀለ የሚሰለጥነውን ቡድን የተቀላቀለበትን መንገድ እንዲህ ያስረዳል። ” በአአ የተስፋ ቡድኖች ጨዋታ ላይ በነበረኝ አቋም ከሁለትም ሦስት ቡድን ፈልገውኝ ነበር። ሆኖም እኔ የመጀመርያ ምርጫዬ አዳማ ከተማ ስለነበር ከ2009 ጀምሮ በአዳማ ከተማ በአሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ ስብስብ ውስጥ ተካትቼ በመስራት የመጀመርያ ጨዋታዬንም በአአ ሲቲ ካፕ ላይ የአዳማ ማልያ በመልበስ መጫወት ጀመርኩ። በመቀጠል በፕሪምየር ሊጉ አንደኛ ዙር ላይ ሙሉ ለሙሉ የመጫወት እድል አላገኘሁም ነበር። በኋላ በሁለተኛው ዙር ላይ አልፎ አልፎ ቢሆንም ተቀይሮ በመግባት የመጫወት እድል አግኝቻለሁ። የበለጠ ግን ዘንድሮ በአአ ሲቲ ካፕ ላይ ባሳየሁት መልካም እንቅስቃሴ በፕሪምየር ሊጉ ከ10 ጨዋታ በ8ቱ የቋሚ ተሰላፊነት እድል አግኝቼ በመጫወት ላይ እገኛለው። ” ሱሌይማን ከተወለደበት መንደር በመውጣት የኢትዮጵያ ኮከብ የሆነው ሳላዲን ሰዒድን ምሳሌ ያደርጋል። የእርሱን ዱካ ተከትሎ የሀገሪቱ ምርጥ ተጫዋች መሆንም ይፈልጋል። በተስፋ ውድድር ላይ በአካዳሚ ማልያ ሲያደርገው የነበረው እንቅስቃሴም የሳላዲንን ፈለግ ተከትሎ ምርጥ አጥቂ እንደሚሆን ፍንጭ ሰጥቶ ነበር። ሆኖም አዳማ ከተማን ከተቀላቀለ ወዲህ በቀኝ መስመር ተከላካይነት እየተሰለፈ ይገኛል። ሱሌይማን ፍላጎቱ በአጥቂነት የመጫወት ቢሆንም በሚሰጠው ሚና ለመጫወት ዝግጁ እንደሆነ ይገልፃል። ” በአካዳሚ በነበረኝ ቆይታ የአጥቂ መስመር ተጨዋች ነበርኩ። ሆኖም ግን በአሁኑ ሰአት የተከላካይነት ስፍራ እንድጫወት ተደርጓል። ወጣት እንደመሆኔ መጠን ምንም እንኳን እግርኳስ መጫወት ስጀምር አጥቂ የመሆን ትልቅ ፍላጎት ቢኖረኝም ስራ እስከሆነ ድረስ አሰልጣኞች የሚሰጡኝ ሚና ሁሉ በትጋት በሚገባ መወጣት አለብኝ። ይህን ስታደርግ ደግሞ የፕሮፌሽናልነት አዕምሮ እንዲኖርህ ያደርገሀል።” በአዳማ ከተማ ዘንድሮ በ8 ጨዋታዎች ላይ የተሰለፈው ሱሌይማን ቡድኑ በተጫዋች ስብስብ ጠንካራ እንደሆነ ገልጾ ካለው የነጥብ መቀራረብ አንፃር ካለፉት አመታት የተሻለ ደረጃ ላይ ተቀምጠው ለማጠናቀቅ እንደሚተጉ ተናግሯል። በግሉም ራሱን በማሻሻል ትልቅ ተጫዋች የመሆን ህልሙን ገልጿል። ” ትልቅ ተጫዋች የመሆን አላማ አለኝ። ጠንክሬ በመስራት በውጪ ሀገራት ክለቦች የመጫወት እና ለብሔራዊ ቡድን ከወጣት ቡድን ጀምሮ እስከ ዋናው ብሔራዊ ቡድን ድረስ መጫወት እፈልጋለው። ትልቅ ተጨዋች ለመሆን ካሰብክ እና አላማ ካለህ አዕምሮህን የፕሮፌሽናል አስተሳሰብ እንዲኖረው ማድረግ አለብህ። በትንሽ አድናቆት እና ሙገሳ አላማህን የምትስት ከሆነ ወደዚህ ህይወት የገባህው ለአላማ ሳይሆን በአጋጣሚ እንጂ ፈልገህ አይደለም ማለት ነው። ስለዚህ አሁን ባለኝ አቋም ተዘናግቼ አልቀመጥም። በዚህ እድሜ ይህን መስራት ከቻልኩ ነገ ከነገህ ወድያ ደግሞ የተሻለ ነገር መስራት እንደምችል ስለማስብ ጠንክሬ ስራዬን በመስራት አላማዬን ለማሳካት እጥራለው ። “
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/32852
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
32bf7f749e17c5a796cd6750249ea6d3
45c4e4d56e1e76b62129d9bf91423810
ቅድመ ዳሰሳ | ወልዋሎ ከ ወላይታ ድቻ
በመጀመርያው ሳምንት ሙሉ ሶስት ነጥብ አግኝተው በሊጉ አናት የሚገኙት ክለቦች የሚያገናኘውን ጨዋታ እንደሚከተለው ዳሰነዋል።በመጀመርያው ሳምንት ከሜዳቸው ውጭ ሰበታ ከተማን አሸንፈው የተመለሱት ቢጫ ለባሾቹ በነገው የሜዳቸው ጨዋታ ትልቅ ግምት ይሰጣቸዋል።በአዲስ አበባ ዋንጫ ላይ ጥሩ የውድድር ግዜ ያላሰለፉት ወልዋሎዎች በመጀመርያው ሳምንት ወሳኝ ድል አስመዝግበው በጥሩ የአሸናፊነት መንፈስ ላይ ይገኛሉ። በቅድመ ውድድር ላይ ከተጠቀሟቸው ተጫዋቾች ብዙም ለውጥ ሳያደርጉ የአጨዋወት እና የቅርፅ ለውጥ ብቻ አድርገው የሜዳ ውጭ ጨዋታቸውን ያካሄዱት ወልዋሎዎች የነገው ጨዋታ በሜዳቸው እና በደጋፊያቸው ፊት እንደመሆኑ የማሸነፍ ጫናው የሚኖረው በእነሱ ላይ ነው። በዚህም ከመጀመርያው ሳምንት በተለየ አጨዋወት ማጥቃት ላይ መሠረት አድርገው እንደሚገቡ ይጠበቃል።ቢጫ ለባሾቹ በነገው ጨዋታ ባልታወቀ ምክንያት ከቡድኑ ጋር ከሌለው ጁንያስ ናንጋጁቦ ውጭ በጉዳት እና በቅጣት የሚያጡት ተጫዋች የለም።በመጀመርያው የሊጉ መርሃ ግብር የቅርብ ተቃናቃኛቸው ሲዳማ ቡናን አሸንፈው ከተጋጣሚያቸው ወልዋሎ በእኩል ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ የሚገኙት ወላይታ ድቻዎች ምንም እንኳ ጨዋታው ከሜዳቸው ውጭ ቢሆንም ቀላል ግምት አይሰጣቸውም። የጦና ንቦች የቅድመ ውድድር ጊዜያቸው ባሳለፉበት እና በመጠኑ በተላመዱት የመጫወቻ ሜዳ መጫወታቸው ለቡድኑ ጥሩ ዕድል እንደሆነ ቢታሰብም ወሳኝ አጥቂያቸው ባዬ ገዛኸኝ በጉዳት ማጣታቸው ለቡድኑ ጥሩ ዜና አይደለም።አንዳንዴ በኳስ ቁጥጥር ብልጫ ተመስርተው ሲያስፈልግም በረጃጅም ኳሶች ወደ ተጋጣሚ ግብ ክልል ለመጠጋት የሚሞክሩት ወላይታ ድቻዎች በነገው ጨዋታ የመሃል ሜዳ የኳስ ቁጥጥር ብልጫ ለመውሰድ ይቸገራሉ ተብሎ ባይጠበቅም ጠጣሩ የወልዋሎ የመከላከል ክፍል ለማለፍ ግን ይቸገራሉ ተብሎ ይገመታል። በተለይም ቡድኑ ፈጣኑ አጥቂ ባዬ ገዛኸኝ እና በትግራይ ዋንጫ ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ ያሳየው በረከት ወልዴን በጉዳት ማጣቱ በአጨዋወቱ ላይ ለውጥ ለማድረግ ይገደዳል።የጦና ንቦች በጉዳት ምክንያት የበረከት ወልዴ እና ባዬ ገዛኸኝ አገልግሎት የማያገኙ ሲሆን የተስፋዬ አለባቸው መሰለፍም አጠራጣሪ ነው።የእርስ በርስ ግነኙነት– ቡድኖቹ በሊጉ አራት ጊዜ ተገናኝተው በአስገራሚ ሁኔታ አራቱንም በአቻ ውጤት አጠናቀዋል።– ስድስት ጎሎች በተቆጠሩበት የሁለቱ ግንኙነት ሁለቱም ቡድኖች ሦስት ሦስት ጎሎችን አስቆጥረዋል።ግምታዊ አሰላለፍወልዋሎ (4-2-3-1)ዓብዱልዓዚዝ ኬይታገናናው ረጋሳ – ፍቃዱ ደነቀ – ዓይናለም ኃይለ – ሳሙኤል ዮሐንስክብሮም ዘርዑ – አቼምፖንግ አሞስሰመረ ሃፍታይ – ካርሎስ ዳምጠው – ምስጋናው ወልደዮሐንስኢታሙና ኬይሙኔወላይታ ድቻ (4-1-4-1)መክብብ ደገፉያሬድ ዳዊት – ደጉ ደበበ – አንተነህ ጉግሳ – እዮብ ዓለማየሁተስፋዬ አለባቸውዘላለም ኢያሱ – ኢድሪስ ሰዒድ – ነጋሽ ታደሰ – ቸርነት ጉግሳዳንኤል ዳዊት
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/52431
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
1f2e0b86fc0e737fdb5b9007c457bdc7
8d91c4f21dd720951ca100b9044c57e5
ቻይና የኢንተርኔት ነጻነትን በማፈን ዘንድሮም ከአለም አንደኛ ናት
ሁዋዌ በ5ጂ ኢንተርኔት ፍጥነት አዲስ ክብረ ወሰን አስመዘገበ የኢንተርኔት አገልግሎትን በማቋረጥና ስለላን ጨምሮ ሌሎች ነጻነትን የሚጋፉ እርምጃዎችን በመውሰድ የዜጎችን የኢንተርኔት ነጻነት በማፈን ላለፉት ሶስት ተከታታይ አመታት ከአለም አገራት ቀዳሚነቱን ይዛ የዘለቀችው ቻይና፣ ዘንድሮም በአንደኛ ደረጃ ላይ መቀመጧ ተዘግቧል፡፡ፍሪደም ሃውስ የተባለው አለማቀፍ ተቋም በ56 የአለም አገራት ያካሄደውን ጥናት መሰረት በማድረግ ሰሞኑን ያወጣውን አለማቀፍ የኢንተርኔት ሁኔታ አመላካች ሪፖርት ጠቅሶ ዴይሊ ሜይል እንደዘገበው፣ ቻይና በአመቱ እጅግ የከፋውን የኢንተርኔት ነጻነት አፈና በመፈጸም ቀዳሚነቱን ስትይዝ፣ ኢራንና ሶርያ በሁለተኛና በሶስተኛ ደረጃ ይከተላሉ፡፡በሪፖርቱ የዜጎችን የኢንተርኔት አገልግሎት ነጻነት በማክበር ከአለማችን ቀዳሚዋ አገር ተብላ የተጠቀሰችው አይስላንድ ስትሆን፣ ኢስቶኒያና ካናዳ በሁለተኛና በሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡በሌላ ዜና ደግሞ፣ የቻይናው የቴሌኮም ኩባንያ ሁዋዌ፣ በ5ጂ የሞባይል ኢንተርኔት ፍጥነት አዲስ ክብረ ወሰን ያስመዘገበበትንና በሰከንድ ከ2.92 ጊጋ ባይት በላይ ፍጥነት ያለውን አዲስ ኔትወርክ በስራ ላይ ማዋሉን ዘ ጋርዲያን ዘግቧል፡፡ሁዋዌ ከቱርክ ቴሎኮም ኩባንያ ጋር በመተባበር በኢስታምቡል ይፋ ያደረገው ይህ እጅግ ፈጣን የሞባይል ኔትወርክ፣ በሁዋዌ ሜት ኤክስ ስማርት ፎን አማካይነት ተሞክሮ በፍጥነት አዲስ የአለም ክብረወሰን ማስመዝገቡ ታውቋል፡፡ ኩባንያው ይህንን እጅግ ፈጣን ኔትወርክ በስራ ላይ ለማዋል የረቀቁ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀሙን ማስታወቁን የዘገበው ዘ ጋርዲያን፤ ይህ አዲስ እምርታ ኩባንያው ከአሜሪካ መንግስት እየተደረገበት ያለውን ጫና ተቋቁሞ በአለማቀፉ የሞባይል ስልኮች ገበያ ያለውን ድርሻ ለማሳደግ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ ለመቀጠል ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑንም አመልክቷል፡፡
4ዓለም አቀፍ ዜና
https://www.addisadmassnews.com/index.php?option=com_k2&view=item&id=24492:%E1%89%BB%E1%8B%AD%E1%8A%93-%E1%8B%A8%E1%8A%A2%E1%8A%95%E1%89%B0%E1%88%AD%E1%8A%94%E1%89%B5-%E1%8A%90%E1%8C%BB%E1%8A%90%E1%89%B5%E1%8A%95-%E1%89%A0%E1%88%9B%E1%8D%88%E1%8A%95-%E1%8B%98%E1%8A%95%E1%8B%B5%E1%88%AE%E1%88%9D-%E1%8A%A8%E1%8A%A0%E1%88%88%E1%88%9D-%E1%8A%A0%E1%8A%95%E1%8B%B0%E1%8A%9B-%E1%8A%93%E1%89%B5&Itemid=212
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
9f0127d47b0d527380a787edc7d55729
d7bbbd82a635b0c8f7f1eeaceeb99b00
የህግ ማስከበር ዘመቻውን የተሳሳተ ትርጓሜ የመስጠት ዝንባሌ እንዳለ ተገለፀ
የአዲስ አበባ፣ ህዳር 19፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)  በኢትዮጵያ የሚካሄደውን የህግ ማስከበር ዘመቻ የተሳሳተ ትርጓሜ የመስጠት ዝንባሌ እንዳለ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ አስታውቋል።የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ በትግራይ ክልል እየተካሄደ ያለውን ህግን የማስከበር ዘመቻን አስመልክቶ በሚተላለፉ የተሳሳቱ መልእክቶች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥቷል።የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ ማብራሪያ ከሰጠባቸው ጉዳዮች ውስጥም “ኢትዮጵያ ወደ እርስ በርስ ጦርነት እየገባች ነው” የሚለው አንዱ ነው።የህግ ማስከበር ዘመቻው ግልፅ እና የተወሰነ ግብ ያለው ነው ያለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ ፥ ዋናው አላማውም የፅንፈኛው ህወሓት አባላትን ለህግ ማቅረብ ነው፤  ዘመቻውም በቅርቡ ይጠናቀቃል ብሏል።“የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የትግራይ ከተሞችን እየደበደበ ነው እና ሰራዊቱ መቀሌን በአየር እየደበደበ ነው የሚለው ሌላኛው የተሳሳተ መሆኑን በመጥቀስ ማብራሪያ የሰጠበት ነው።እንዲሁም “በመቀሌ ከተማ በሚካሄደው ዘመቻ ምህረት የለም” ተብሏል በሚል የሚሉ የተሳሳቱ ትርጓሜ የተሰጠባቸው መረጃዎች መሰራጨታቸውንም አስታውቋል።
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%8b%a8%e1%88%85%e1%8c%8d-%e1%88%9b%e1%88%b5%e1%8a%a8%e1%89%a0%e1%88%ad-%e1%8b%98%e1%88%98%e1%89%bb%e1%8b%8d%e1%8a%95-%e1%8b%a8%e1%89%b0%e1%88%b3%e1%88%b3%e1%89%b0-%e1%89%b5%e1%88%ad%e1%8c%93/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
bcbeb7053ea48465d2e89a4e0dd93ff0
b96c0fdb0395033fd4afbbb55c746e59
ወልዋሎ ከሦስት ተጫዋቾች ጋር ለመለያየት ተስማማ
በጥር ዝውውር መስኮት በርካታ ተጫዋቾች ያስፈረሙት ወልዋሎዎች ከፍቃዱ ደነቀ፣ ካርሎስ ዳምጠው እና ምስጋናው ወልደዮሐንስ ጋር ለመለያየት በቃል ደረጃ ተስማምተዋል። በቀጣይ ቀናትም ሒደቱ ሙሉ ለሙሉ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።ባለፈው የክረምት ዝውውር መስኮት ቡድኑን ተቀላቅለው ላለፉት ስድስት ወራት ክለቡን ያገለገሉት እነዚህ ሦስት ተጫዋቾች በቀድሞ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ቡድን ውስጥ ወሳኝ ሚና ከነበራቸው ተጫዋቾች እንደነበሩ ይታወሳል።በክረምቱ ከመጀመርያ ፈራሚዎች አንዱ የነበረው ምስጋናው በመጀመርያው ዙር በቀኝ ተከላካይ መስመር ተቀዳሚ ተመራጭ ሆኖ በሁሉም ጨዋታዎች ተሰልፎ ተጫውቷል። ሁለተኛው በስምምነት የተለያየው ተከላካዩ ፍቃዱ ደነቀ በጉዳት ከሜዳ እስከራቀበት ግዜ ድረስ የተከላካይ ክፍሉን በቋሚነት የመራ ሲሆን በተወሰኑ ጨዋታዎችም በአማካይነት ተሰልፎ ቡድኑ ማገልገሉ ይታወሳል። ሶስተኛ ከቡድኑ ጋር በስምምነት የሚለያየው ካርሎስ ዳምጠው ቡድኑ በሊጉ ጅማሬ ላይ ላሳየው ወጥነት ያለው ብቃት ጥሩ አበርክቶ የነበረው ሲሆን በግማሽ ዓመት የቡድኑ ቆይታው ሁለት ጎሎች በማስቆጠር እና ሁለት በማመቻቸት በአራት ግቦች ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ አድርጓል።© ሶከር ኢትዮጵያ
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/56946
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
7eda1e6602019899691812e71a17598b
2e4de83a6859c4342ceaa557e5a33f0c
ንጹሐን ዜጎች ዒላማ ሳይሆኑ፣ ከተሞችንና ቅርሶች ሳይጎዱ መቀሌ ለመግባት ተችሏል- ጠ/ሚ ዐቢይ  
አዲስ አበባ፣ ህዳር 19፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ንጹሐን ዜጎች ዒላማ ሳይሆኑ፣ ከተሞችንና ቅርሶች ሳይጎዱ መቀሌ ለመግባት መግባት መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለፁ።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በፌስቡክ ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት፥ የትግራይ ሕዝብ ከስግብግቡ ጁንታ ጋር እንዳልሆነ በተግባር ማስመስከሩን ገልፀዋል።የመከላከያ ሠራዊት በድል በገሠገሠባቸው የትግራይ አካባቢዎች ሁሉ የትግራይ ሕዝብ ለሀገሩ ያለውን ፍቅርና ለመከላከያ ሠራዊቱ ያለውን ክብር አሳይቷል ብለዋል።ጁንታው ካስታጠቃቸው ጥቂት የክፋት ኃይሎች ውጭ ያለው የትግራይ ሕዝብ መቀሌ እስኪገባ ድረስ ለመከላከያ ሠራዊቱ የሚጠበቅበትን ድጋፍ ሁሉ አድርጓል፤ ይህም የሠራዊቱን ድልና የጁንታውን ሽንፈት አፋጥኖታል ሲሉም ገልፀዋል።ስግብግቡ ጁንታ በየትኛውም መመዘኛ ለትግራይ ሕዝብ አይመጥነውም፤ የትግራይ ሕዝብ ከእውነት ጋር በመቆምና የጁንታውን እኩይ ዓላማ በመፃረር ከቀበሌ ቀበሌ፣ ከዞን ዞን መቀሌ እስኪገባ ድረስ ተመሳሳይ ድጋፍ ለሠራዊቱ ሰጥቷል።“ለዚህም ከፍ ያለ ምስጋናዬን አቀርባለሁ” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፥ ጁንታው በሸሸበት ከተማና አካባቢ ሁሉ የጤና ተቋማትን፣ ትምህርት ቤቶችን፣ ድልድዮችን፣ መንገዶችን፣ መሥሪያ ቤቶችን እያወደመ ሄዷል፤ በዚህም የገዛ ወገኑ  ጠላት መሆኑን አሳይቷል ብለዋል።“ጁንታው እኔ ከሞትኩ ብሎ ያፈረሳቸውን መሠረተ ልማቶች በፍጥነት በመገንባት የትግራይ ሕዝብ ወደ ሰላማዊ ኑሮው እንዲመለስ ለማድረግ የቻልነውን ሁሉ እንደምናደርግ ቃል እገባለሁ” ሲሉም ገልፀዋል።“በዚህ ዘመቻችን ንጹሐን ዜጎች ዒላማ ሳይሆኑ፣ ከተሞቻችንና ቅርሶቻችን ሳይጎዱ መቀሌ ለመግባት ተችሏል” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ።
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%8b%a8%e1%89%b5%e1%8c%8d%e1%88%ab%e1%8b%ad-%e1%88%95%e1%8b%9d%e1%89%a5-%e1%8a%a8%e1%88%b5%e1%8c%8d%e1%89%a5%e1%8c%8d%e1%89%a1-%e1%8c%81%e1%8a%95%e1%89%b3-%e1%8c%8b%e1%88%ad-%e1%8a%a5%e1%8a%95/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
7954b9dd4aea0c9ef39c5deb692cc041
643fdde2d514254785da049a8cce4ee4
አዴፓ የከሸፈውን መፈንቅለ መንግሥት ያቀነባበሩትና የመሩት "የእናት ጡት ነካሾች" ናቸው አለ
በመግለጫው ላይ ሰኔ 15/2011 ዓ.ም የተካሄደውን የከፍተኛ አመራሮች ግድያና መፈንቅለ መንግሥቱን ያቀነባበሩና በድርጊቱ የተሳተፉ አካላትንም አውግዟል። የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ፓርቲ ከታገለባቸው ጉዳዮች መካከል "የዜጎች ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብት እንዲከበር" መሆኑን አስታውሶ ብርጋዴር ጄኔራል አሳምነው ፅጌን ጨምሮ ሌሎች ግለሰቦች ከታሰሩበት ነፃ እንዲወጡ በግምባር ቀደምትነት የታገሉትን አመራሮች "በግፍና በጭካኔ መግደል የእናት ጡት ነካሽነት እና ክህደት" ነው በማለት ድርጊቱን አውግዟል። • "ብ/ጄነራል አሳምነው በባጃጅ ለማምለጥ ሲሞክሩ ነው የተገደሉት'' • በኢትዮጵያ የኤሊ አደን ለምን አየተበራከተ መጣ? • በፌስታል ተጥላ ለተገኘችው ልጅ የጉዲፈቻ ጥያቄዎች ጎረፉላት አክሎም "በከሸፈው መፈንቅለ-መንግሥት የተፈፀመው ጥቃትና ወንጀል እንዲሁም የአመራሮቻችን የግፍ አገዳደል የአማራን ሕዝብ ያሳፈረና ያዋረደ ሆኖ ሳለ ወንጀሉን ለመሸፋፈን እና ለማሳነስ ሆነ ተብሎ አሉቧልታ በመንዛት ህዝባችንን ለማደናገር እና አቅጣጫ ለማሳት የምትሰሩ አካላት ከዚህ ዕኩይ ድርጊታችሁ ተቆጠቡ" ሲል አሳስቧል። የማዕከላዊ ኮሚቴው መግለጫ በከሸፈው መፈንቅለ-መንግሥት እጃቸው ያለበትን ግለሰቦችና ቡድኖች በህግ ቁጥጥር ስር የማዋል ሥራው በሁሉም አካላት ርብርብ "በአጠረ ጊዜና በተሳካ ሁኔታ የተፈፀመ መሆኑን" ጠቅሶ "አሁንም ወንጀለኞችን ሙሉ በሙሉ በህግ ቁጥጥር ስር የማዋልና ህጋዊ እርምጃ የመውሰድ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል" ሲል አስታውቋል። በክልሉ በተደጋጋሚ የታዩ የሰላም መደፍረሶችን በማንሳትም የፀጥታ መዋቅሩን መልሶ ለማጠናከርና በክልሉ አስተማማኝ ሰላምና ደህንነት እንዲረጋገጥ "በልዩ ሁኔታ ተግባራዊ እንቅስቃሴ በማድረግ አስፈላጊው ሁሉ ህጋዊ እርምጃ ይወሰዳል" ብሏል። ድርጅቱ ውስጣዊ አንድነቱ የሚያስፈልግበት ጊዜ ላይ እንደሚገኝ አስታውሶ የድርጅቱን አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች እንዲሁም የክልሉንና የኢትዮጵያን ሕዝቦች፤ "ከመቼውም ጊዜ በላይ በአንድነት በመቆም የተፈጠረውን ፈተና" በብቃት ለማለፍና አገራችንን ለመታደግ በፅናት እንድትቆሙ" በማለት ጥሪውን አቅርቧል። አክሎም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የተለያዩ አካላት መረጋጋትን፣ ሠላምና አንድነትን የሚያጠናክሩ ሥራዎች ላይ በማተኮር በኃላፊነት ስሜት መንቀሳቀስ እንደሚጠበቅባቸው አስታውሷል። በመጨረሻም የከሸፈው መፈንቅለ መንግሥት በአማራ ክልልና ሕዝብ ላይ ብቻ የተፈፀመ ሳይሆን በመላው ኢትዮጵያዊያን ላይ የተፈፀመ ጥቃት መሆኑን በመግለፅ በዚህ ወቅት ከጎኑ የነበሩትን በአጠቃላይ አመስግኗል።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
11b2c9a4ae24fe495ca1eb3ce6c3d962
7fd45e870d50fd356cdf0e54a44b5675
ደኢህዴን በሁሉም የልማት መስኮች አበረታች ውጤት መመዝገቡን ገለጸ
ባለፈው ዓመት የተካሔደውን የጥልቅ ተሀድሶ ንቅናቄ ተከትሎ በክልሉ በሁሉም የልማት መስኮች አበረታች ውጤት መመዝገቡን የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ደኢህዴን/ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽ/ቤት ገለጸ፡፡ማዕከላዊ ኮሚቴው ሰሞኑን ባካሔደው መደበኛ ስብሰባ በልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ ማስተላለፉም ተመልክቷል፡፡የደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ በልጅጌ በጽ/ቤታቸው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደተናገሩት ባላፈው ዓመት የተካሔደውን የጥልቅ ተሀድሶ ንቅናቄ ተከትሎ በክልሉ በልዩ ልዩ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ዘርፎች አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡ማዕከላዊ ኮሚቴው ሰሞኑን ባካሄደው ስብሰባ የህዝቦችን አንድነት የሚጻረሩ እና ለሰላም እጦት ምክንያት የሚሆኑ አመለካከቶች እና ተግባራትን በዝርዝር ፈትሿል፡፡ በዚህም በአንዳንድ አካባቢዎች ተስተውለው የነበሩ የጠባብ ብሔርተኝነት አመለካከቶች እና ተግባራት እልባት እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡ ይህም የጥልቅ ተሀድሶው ውጤት መሆኑን አቶ ተስፋዬ ጠቁመዋል፡፡ሙስናና ብልሹ አሰራርን በመዋጋት ረገድ የተጀመሩ ስራዎች አበረታች መሆናቸውንም ማዕከላዊ ኮሚቴው ለይቷል፡፡ ከጥልቅ ተሀድሶው ወዲህ በሙስናና ብልሹ አሰራር ውስጥ ተሳታፊ ሆነዋል የተባሉ 672 አመራሮች እና ባለሙያዎችን መለየት የተቻለ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 8ቱ ከፍተኛ አመራሮች፣ 17ቱ ደግሞ በመካከለኛ ደረጃ የሚገኙ አመራሮች መሆናቸውን አቶ ተስፋዬ ጠቁመዋል፡፡52 ሚሊየን የባከነ የህዝብና የመንግስት ገንዘብም ተመላሽ የተደረገ ሲሆን በገጠር እና በከተማ አለአግባብ ሊባክን የነበሩ በርካታ መሬቶችንም ማስመለስ ተችሏል ብለዋል፡፡በክልሉ የሚገኙ ወጣቶች በእውቀት እና በምክንያት ላይ ተመስርተው ሀሳቦቻቸውን እና አመለካከቶቻቸውን በጉልህ ማንፀባረቅ እንዲችሉ ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ማሳተፍ መቻሉንም ማዕከላዊ ኮሚቴው በበጎ ጎኑ ገምግሟል፡፡የክልሉን ወጣቶች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከማሳደግ አንፃርም 6 መቶ ሺ ወጣቶችን በቋሚና በጊዜያዊ የስራ እድል ለማሳተፍ ታቅዶ 520 ሺህ ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ የተቻለ ሲሆን ከነዚህ መካከል 386 ሺ ወጣቶች በተመረጡ ፓኬጆች በቋሚ የሥራ እድል የተሳተፉ መሆናቸውን አቶ ተስፋዬ ገልጸዋል፡፡በተለያዩ ተቋማት በሚሰጡ አገልግሎቶች ተሃድሶው ያመጣቸው ለውጦች ቢኖሩም የህዝቡን እርካታ በሚያረጋግጡበት ደረጃ ላይ ባለመሆናቸው ተሃድሶው የበለጠ ግለቱን ጠብቆ መሄድ እንዳለበት አቅጣጫ መቀመጡንም ጠቁመዋል፡፡በተያዘውም በጀት ዓመት በመልካም አስተዳደር ዘርፍ የተጀመሩ ሥራዎች ይበልጥ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የሚደረግ መሆኑን የገለጹት አቶ ተስፋዬ የክልሉ ህዝቦች በየደረጃው የጀመሯቸውን ትግሎች አጠናክረው እንዲቀጥሉ ማዕከላዊ ኮሚቴው ጥሪ ማቅረቡንም ከክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት  የተገኘዉ መረጃ ያመለክታል፡፡ 
5ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/29374/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
e2a0a1833ef44918be871051a7ba36c6
fd77c9e3808683d3833bd3218848e35c
“ዝክረ መለስ” የውይይት መድረክ ተካሄደ
– የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስቴር አቶ መለስ ዜናዊ በገንዘብና ኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ የነበራቸው የአመራር ሚና፣ ለብሔራዊ ክልል መንግስታት የነበራቸው ትኩረት እንዲሁም ማህበራዊና ፖለቲካዊ ሰብዕናቸው ላይ ያተኮረ አገር አቀፍ የምክክር መድረክ ተካሄደ፡፡“ዝክረ መለስ” በሚል ርዕስ ዛሬ በሸራተን አዲስ በተካሄደው ውይይት ላይ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር አቶ ሱፍያን አህመድ፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አያሌው ጎበዜ እና የመለስ ፋውንዴሽን ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ አዜብ መስፍን  የመወያያ ፅሁፎቹን አቅርበዋል፡፡የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር በገንዘብና ኢኮኖሚ ጉዳዮች ዙሪያ የነበራቸውን የአመራር ሚና በተመለከተ በሽግግር ዘመን (1984 – 1987) ፣በተሃድሶ ዘመን (1988 – 1993) እና የፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ትግበራ ዘመን (1994 ወዲህ) በሚል በሶስት ዘመናት የተከፋፈለ የመወያያ ፅሁፍ አቶ ሱፍያን አቅርበዋል፡፡    በሽግግር ዘመን በአገሪቱ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ስርዐት ያልነበረትና ምርትና አግልግሎት ሰጪ ተቋማት እጥረት ይታዩ የነበረበት ወቅት መሆኑን ያስታወሱት አቶ ሱፍያን እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ አቶ መለስ ሳይንሳዊና ምክንያታዊ በሆነ መንገድ አዳዲስ ፕሮግራሞችንና የመዋቅር ዝርጋታዎችን ለማምጣት የተንቀሳቀሱበት ጊዜ ነበር ብለዋል፡፡በተሃድሶ ዘመን መለስ በዋናነት ትኩረቱን አገሪቱ አሁን የምትመራባቸውን ዝርዝር ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎችን ያዘጋጁበት ወቅት ነበር ያሉት አቶ ሱፍያን በተጨማሪም በዚህ ወቅት አጋጥመው የነበሩ የኢህአዴግ የውስጥ ችግሮችንና የኤርትራን ወረራ በበሳል አመራር የተወጡበት ጊዜ ነበር ብለዋል፡፡           ከዚህ በኋላ ባሉት ጊዜያት የአቶ መለስ ትኩረት ሶስት የአምስት ዓመት እቅዶች በመንደፍና የፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ትግበራን በቅርበት በመከታተል አገሪቱ ፈጣንና ተከታታይ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ የቻለችበት ወቅት ላይ መድረስ ተችሏል በማለት ፁሁፋቸውን አጠቃለዋል፡፡አቶ መለስ ለብሔራዊ ክልል መንግስታት የነበራቸው ትኩረት በተመለከተ የመወያያ ጽሁፍ ያቀረቡት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አያሌው ጎበዜ በበኩላቸው የፌዴራል ስርዓት እንዲተገበር የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ትልቅ ሚና ተጫውተዋል ብለዋል፡፡ በተለይም የክልሎችን አቅም በመገንባትና ፍትሃዊ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች በሁሉም ክልሎች እንዲዳረስ አቶ መለስ ሰፊ ስራ ሰርተዋል ሲሉ አቶ አያለው ተናግረዋል፡፡የአቶ መለስን ማህበራዊና ፖለቲካዊ ሰብዕና በተመለከተ ባለቤታቸው ወ/ሮ አዜብ ባቀረቡት ፅሁፍ መለስ በዓላማ የሚያምን፣ ለስኬቱም በማይሰስት ቸርነት ሙሉ ጊዜውን፣ እውቀቱንና ሁለንተናዊ እሱነቱን ሰጥቶ ከራስ በላይ ለሆነ አላማ እስከ ህልፈቱ ታምኖ የኖረ ሰው ነው ብለዋል፡፡ወ/ሮ አዜብ አክለውም መለስ የህዝቦችን ሰብአዊና ዜግነታዊ የማይገሰስ ክቡርነት ብሎም ምትክየለሽ ወሳኝነት መቆምያው ያደረገ ህዝባዊና ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ የተላበሰ መሪ ነበር ሲሉ አጠቃለዋል፡፡ድምፂ ወያነ ትግራይ ሬዲዮ ያዘጋጀው ይህ “ዝክረ መለስ” የተሰኘው የውይይት መድረክ ላይ ከፍተኛ ባለስልጣናትና ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍል የተውጣጡ እንግዶች የተገኙበት ሲሆን በቀረቡት ፅሁፎች ላይም ውይይት ተደርጓል፡፡
5ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/24717/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
eb19f1f66a68b5f478ab5365d427dd42
b3cad7fd9301c06780d61e8df8e410db
አለም ዓቀፉ የህፃናት አድን ድርጀት ለባህርዳር ከተማ የ42 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ
አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 10፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) አለም ዓቀፍ የህፃናት አድን ድርጅት ለባህርዳር ከተማ የኮሮና ቫይረስ ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚውል 42 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ።በተደረገው ድጋፍ ዙሪያ የክልሉ የኮሮና ቫይረስ መከላከል እና መቆጣጠር ግብረ ሀይል አስተባባሪ ዶክተር ሙሉነሽ አበበ፣ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ እና የባህርዳር ከተማ ክፍለ ከተሞች ኃላፊዎች በተገኙበት ወይይት ተደርጓል።የምዕራብ አማራ የህጻናት አድን ድርጀት ስራ አስኪያጅ ሙሉቀን እማኙ ድርጀቱ በሀገሪቱ ስድስት ከተሞች ማለትም አዲስ አበባ፣ ባህርዳር፣ ሀዋሳ፣ ድሬዳዋ፣ አዳማ እና ጅግጀጋ ለተጎጂዎች በምግብ፣ ውሃ እና ጤና ዘርፎች እርዳታ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።በዛሬው ዕለትም በባህርዳር ከተማ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ለችግር የበለጠ ተጋላጭ ለሆኑ የህበረተሰብ ከፍሎች የ42 ሚሊየን ብር ድጋፍ መደረጉን ገልጸዋል።ከ42 ሚሊየን ብር ድጋፍ ውስጥ 36 ሚሊየን በቀጥታ ልዩ ድጋፍ ለሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሰጥ እና ቀሪው ለጤና እና ለውሃ አገልግሎት እንደሚውል ነው የተናገሩት።በድጋፋ 5 ሺህ 536 አባወራዎች እና እማወራዎች እንዲሁም 22 ሺህ 144 የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ እንደሚሆኑም ነው ስራ አስኪያጁ የገለፁት።የክልሉ የኮሮና ቫይረስ መከላከል እና መቆጣጠር ግብረ ሀይል አስተባባሪ ዶክተር ሙሉነሽ አበበ በበኩላቸው፥ አለም ዓቀፉ የህፃናት አድን ድርጅት በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ላደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።በቀጣይም በትክክል መረዳት የሚገባቸውን ሰዎች መመልመቻቸውን የሚያረጋግጥ ግብረ ሀይል ከሰራተኛ ና ማህበራዊ ጉዳይ፣ ከጤና፣ ከገንዘብ እና ኢኮኖሚ እና ከውሃ ተቋማት መቋቋም አለበት ብለዋል።በናትናኤል ጥጋቡየዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%8a%a0%e1%88%88%e1%88%9d-%e1%8b%93%e1%89%80%e1%8d%89-%e1%8b%a8%e1%88%85%e1%8d%83%e1%8a%93%e1%89%b5-%e1%8a%a0%e1%8b%b5%e1%8a%95-%e1%8b%b5%e1%88%ad%e1%8c%80%e1%89%b5-%e1%88%88%e1%89%a3%e1%88%85/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
9605fc7f4dea7087a6be5eb3d7133333
6256645ebd1558725e419af20bc76cf7
በአዲስ አበባ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ ለማስቀረት አንድ ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋል
በአዲስ አበባና በዙሪያዋ የሚገኙ 12 የኦሮሚያ ክልል ልዩ ዞን ከተሞች በየጊዜው የሚገጥማቸውን የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ ለማስቀረት ማስተር ፕላን ተነደፈ፡፡ አዲሱን ማስተር ፕላን ተግባራዊ ለማድረግ አንድ ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋል፡፡‹‹አዲስ አበባና ዙሪያዋ የኤሌክትሪክ ዲስትሪቢውሽን ማስተር ፕላን ጥናት ፕሮጀክት›› በሚል ስያሜ የተነደፈው ማስተር ፕላን፣ በሚቀጥሉት 20 ዓመታት በአጭር፣ በመካከለኛና በረዥም ጊዜ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል፡፡ባለፈው ሐሙስ ሰኔ 4 ቀን 2007 ዓ.ም. በማስተር ፕላኑ ላይ ውይይት በተደረገበት ወቅት፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አዜብ አስናቀ እንደተናገሩት፣ እ.ኤ.አ. እስከ 2017 ድረስ ተግባራዊ በሚደረገው የአጭር ጊዜ ዕቅድ አሮጌ ኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ይለወጣሉ፡፡በአጠቃላይ ፕሮጀክት ተግባራዊ ለማድረግ አንድ ቢሊዮን ዶላር በጀት መያዙ ተገልጿል፡፡ ከዚህ ውስጥ እ.ኤ.አ. እስከ 2017 ለሚተገበረው የአጭር ጊዜ ዕቅድ ማስፈጸሚያ 285 ሚሊዮን ዶላር፣ እ.ኤ.አ. ከ2018 እስከ 2022 ተግባራዊ ለሚሆነው መካከለኛ ዘመን ዕቅድ ማስፈጸሚያ 37 ሚሊዮን ዶላር፣ ለረዥም ጊዜ ዕቅድ ማስፈጸሚያ (እ.ኤ.አ. ከ2023 እስከ 2034) 745 ሚሊዮን ዶላር መበጀቱ ተገልጿል፡፡በአጠቃላይ በአዲስ አበባና አካባቢው የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎትና ዕድገት ለማጣጣም የተያዘውን ዕቅድ ለማስፈጸም፣ 1,067 ቢሊዮን ዶላር ይፈጃል ተብሎ ተገምቷል፡፡ፕሮጀክቱ ተግባራዊ የሚደረገው በአዲስ አበባ በሚገኙት አሥር ክፍላተ ከተሞችና በኦሮሚያ ልዩ ዞን በሚገኙት አዲስ ዓለም፣ ኢሉ፣ ወልመራ፣ ሙሎ፣ ሱሉልታ፣ በረህ፣ አሌልቱ፣ ጊምቢቹ፣ አደአ፣ አቃቂ፣ ዓለም ገና፣ ቀርሳና ማሊሞ ወረዳዎች ናቸው፡፡አዲስ አበባና ዙሪያዋ አገሪቱ ከምታመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል ውስጥ 60 በመቶውን እንደሚጠቀሙ ኢንጂነር አዜብ ገልጸው፣ አካባቢዎቹ የሚያጋጥማቸውን የኤሌክትሪክ ኃይል ሥርጭት መቆራረጥ ለማስቀረት የፕሮጀክቱ ተግባራዊ መሆን ወሳኝ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡ይህንን ማስተር ፕላን ከአፍሪካ ልማት ባንክ በተገኘ 3.5 ሚሊዮን ዶላር ያጠናው የእንግሊዝ ኩባንያ የሆነው ፓርሳን ብሪንኤርሆፍ ሊሚትድ ነው፡፡ የኩባንያው ተወካይ ናንካ ብሩስ በውይይቱ ላይ እንደተናገሩት፣ አዲስ አበባ በፍጥነት እያደገች በመሆኑ እያጋጠማት ካለው የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ ወጥታ፣ ለዕድገቷ የሚያስፈልጋትን ኃይል ለማግኘት ማስተር ፕላኑ ጠቀሜታው የጎላ ነው፡፡ይህ ፕሮጀክት ተግባራዊ ሲሆን፣ በከተማው የሚገኙ አሮጌ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያዎች በአዲስ ይተካሉ፡፡ መሻሻል ያለባቸውም እንዲሻሻሉ ይደረጋል በማለት ኢንጂነር አዜብ ተናግረዋል፡፡በቀጣይነት ይህ ፕሮጀክት በሐዋሳ፣ በመቐለ፣ በባህር ዳርና በሌሎች ትልልቅ የክልል ከተሞች ተግባራዊ እንደሚሆን ኢንጂነር አዜብ አስረድተዋል፡፡በአዲስ አበባና በአካባቢው ለረጅም ጊዜ እያጋጠመ ያለው የኃይል መቆራረጥ፣ በዋናነት በኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያና ማሠራጫ ጣቢያዎች እርጅና ምክንያት ነው ሲባል ቆይቷል፡፡ ነገር ግን ከቅርብ ወራት ወዲህ ለኃይል መቆራረጡ የበልግ ዝናብ በተፈለገው መጠን ባለመዝነቡ ምክንያት፣ ግድቦች በቂ ውኃ ባለመያዛቸው እንደሆነ ባለሙያዎች እየተናገሩ ነው፡፡
3ቢዝነስ
https://www.ethiopianreporter.com/article/7635
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
07d7420f8082204cbd7cc08e9f0ae06e
ea706fc728a8d5ede01d08d68898d155
ሄርበርት ሁቨር ምን ያህል አሜሪካውያን ቱሪስቶችና ሠራተኞች ከአውሮፓ ወደ አገራቸው መልሰዋል?
ሄርበርት ሁቨር (1866 - 1957 ዓ.ም.) ከ1921 እስከ 1925 ዓ.ም. ድረስ 31ኛ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ነበሩ። የሁቨር ቤተሠብ ከስዊስና ጀርመን ትውልድ ሲሆን ሃይማኖቱ የክዌከር ('የሚንቀጠቀጡ' ማለት ነው) ቤተ ክርስቲያን ነበረ። ወላጆቹ በልጅነቱ ጊዜ ካረፉ አንስቶ ድሃ አደግ ሆነና ከአጎቱ ጋር አደገ። በስታንፎርድ ዩኒቨርሲቴ መጀመርያ ክፍል በመሆኑ ትምህርቱ በነጻ ተቀበለ። ከዚያ በላይ የዩኒቬርሲቴው የቤስባልና የፉትቦል ቡድኖች አለቃ ሆነ። በ1887 ዓ.ም. የጂዮሎጂ ዲግሪ ይዘው ተመረቁ። ለ20 ዓመት የማዕደን ሊቅ ሲሆኑ እንኳን በአውስትራልያና በእንግሊዝ በማዕደን ዘርፍ የሠሩት ሥራ ስመ ጥሩ ሆነ። መጀመርያው ታላቅ አለማዊ ጦርነት በ1906 ዓ.ም. በጀመረበት ወቅት ሁቨር ከራሳቸው ኪስ ለጋሥነት አውጥተው 120,000 አሜሪካውያን ቱሪስቶችና ሠራተኞችን ከአውሮፓ ወደ አገራቸው አስመለሷቸው። ከዚያ በጀርመኖች በተወረረው በቤልጅግ ውስጥ የኖሩት ረሃብተኞች ምግብ እንዲደርሳቸው ብዙ አደረጉ። በዚህ አይነት ሥራ በጦርነት ጊዜ የሁቨር ስም ጀግና እንዳለው ሁኔታ በመገኘት ላይ ሄዶ ነበር። ጦርነቱም ከተጨረሰ በኋላ ለምሥራቅ አውሮጳ ድሃ ሕዝብ እስከ ሩስያም ድረስ በረሃብ ላሉት ሰዎች ምግብ አደረሷቸው።
null
null
https://huggingface.co/datasets/israel/AmharicQA
ef2e15a52b923d94ee0bd883df396196
6c1067716ca66e9f00b6687e6b6d8061
ባዶ ሆድና ትምህርት
«ምግብ ሳይመገቡ መማር ይከብዳል፤ መምህሩ  የሚለውን  በደንብ አንከታተለውም» ይላል   የአስራ ሁለት መቱ ታዳጊ ዮሐንስ ሙለታ።  ታዳጊው  በኮከበ ጽባህ አጸደ ህጻናትና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት  የስድስተኛ ክፍል  ተማሪ ነው። የቤተሰቦቹ የኑሮ ደረጃ ዝቅተኛ በመሆኑ ባለፉት ዓመታት ቁርስና ምሳውን ይመገብ የነበረው በትምህርት ቤቱ ነበር። ዘንድሮ ግን እሱ ምክንያቱን ባያውቀውም በጣም ለባሰባቸው የደሃ ልጆች ብቻ የምግብ አገልግሎት ስለሚሰጥ እሱ ከሳምንቱ አብዛኛውን ቀን በባዶ ሆዱ ለማሳለፍ መገደዱን ይናገራል። እሱ ባይናገርም ነጭ ሆነው የደረቁት ከንፈሮቹ የሆዱን ባዶነት ያሳብቁበታል።በተመሳሳይ በወጣቶች ገነት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት የስድስተኛ ክፍል ተማሪ የሆነችው የአስራ ሁለት ዓመቷ አበባ «ምሳ ይዤ አልመጣም፤ ብዙ ጊዜ የምበላው  ከጓደኞቼ ጋር ነው፤ አንዳንድ ጓደኞቻችን ብዙ ቀን ጾማቸውን ይውላሉ፤ የሚያፍሩት ደግሞ ባዶ ምሳ እቃ ይዘው መጥተው ይመለሳሉ።» የምትለው ተማሪ ሀና ትምህርት ሲጀመር ምገባው  በጥቅምት ይጀመራል ቢባልም እስካሁን  ግን ምንም  ነገር የለም።  መምህራኖቻችንን ስንጠይቃቸው በቅርቡ ይጀመራል ይሉናል ትላላች።የትምህርት ቤቱ  የአደረጃጀት ምክትል ርዕሰ መምህር የሆኑት አቶ ዘነበ ወርቁ  ከዚህ ቀደም በእናት ወግ በጎ አድራጎት 107 እንዲሁም  በፍቅር ወንድማማቾች የጤና ስፖርት ማህበር 18  ተማሪዎች የምገባ ፕሮግራሙ ተጠቃሚ እንደነበሩ በማስታወስ ዘንድሮ  ፍቅር ወንድማማቾች የስፖርት ማህበር ብቻ 3 ሺ ብር በመመደብ 25 ተማሪዎችን  እየመገበ መሆኑን ይናገራሉ። በትምህርት ቤቱ አብዛኛው ተማሪ  ከደሀ ቤተሰብ የመጡ፣ ዘመድ ጋር ተጠግተው የሚኖሩና በትርፍ ሰዓታቸው ሥራ እየሠሩ ራሳቸውን የሚደጉሙ ናቸው። ከልዩ ፍላጎትና ከአጸደ ህጻናት ውጪ ካሉት 1ሺ200 ተማሪዎች አራት መቶ የሚደርሱት የምግብ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው እንደሆኑ ይናገራሉ።  አዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ተለይተው እንዲቀርቡለት በጠየቀው መሰረት ከፍተኛ ችግር ያለባቸው 270 ተለይተው የተላኩ ቢሆንም እስካሁን በቅርቡ ይጀመራል ከሚል ምላሽ ውጪ ጠብ ያለ ነገር እንደሌለ ይናገራሉ።የወጣቶች ገነት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር  የሆኑት አቶ ታገል መንግስቱ በበኩላቸው የምገባ ፕሮግራሙ መጀመሪያ ቀን እነሱንም እንደናፈቃቸው ይገልጻሉ። ባለፈው ዓመት  የእናት ወግ በጎ አድራጎት 85 ተማሪዎችን ይዞልን ነበር ዘንድሮ ከመቶ በላይ ምገባ የሚያስፈልጋቸውን ለይተናል።   አዲስ አበባ ትምህርት ቢሮን ባለፈው ሳምንት ጠይቀን  ይጀመራል ብንባልም የመጣ ነገር የለም። በመሆኑም ብዙ ተማሪዎች በችግር ውስጥ ናቸው። በአሁኑ ወቅት በጣም የባሰባቸውን እስካሁንም ሲደግፍልን የነበረው ሙላት የበጎ አድራጎት ድርጅት ለ27 ተማሪዎች የምሳና ቅዳሜ ደግሞ የጥናትና የምሳ ድጋፍ እያደረግልን ይገኛል።ብዙ ቤተሰብ  እንደ አምናው የምገባ ፕሮግራሙ ይኖራል ብሎ ስላልተዘጋጀ ቅሬታ ፈጥሮበታል ይላሉ።«ምገባው በጥቂት ቀናቶች ውስጥ ይጀመራል» የሚሉት ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የህጻናት ጤናና ምገባ ቢሮ አስተባባሪ የሆኑት ወይዘሪት ሜቲ ታምራት ናቸው። ወይዘሪት ሜቲ እንደተናገሩት  ፕሮግራሙ እስካሁን ሲካሄድ የነበረው በተለያዩ አካላት  ድጋፍ ነበር።  በዋናነትም የእናት ወግ በጎ አድራጎት  ማህበር እስከ ባለፈው ዓመት 22 ሺ ተማሪዎችን  በአስሩም ክፍለ ከተማ በሚገኙ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ሲመግብ ነበር። ሌሎች የተለያዩ ተቋማት፣ መምህራን፣ ማህበረሰቡና ባለሀብቶች ደግሞ ወጥነት ባይኖረውም አስር ሺ  ለሚደርሱ ተማሪዎች አገልግሎት ሲሰጡ ነበር።  የእናት ወግ የበጀት እጥረት ስለገጠመው በዚህ ዓመት እየመገበ ያለው ዘጠኝ ሺ ብቻ ሲሆን፣ እነዚህም በተለይ ችግሩ በሰፋባቸው አራዳ፣ ቂርቆስና ጉለሌ እንዲሆም በሌሎቹ ክፍለ ከተሞች በተወሰኑ ትምህርች ቤቶች ብቻ ነው።ፕሮግራሙ ውጤታማና አስፈላጊ መሆኑ ስለታመነበት ከተማ አስተዳደሩ ለመደገፍና ለሚያስፈልጋቸው ሁሉ ተደራሽ ለማድረግ መስራት ጀምሯል። በዚህም በ2011 ከተማ መስተዳድሩ በፈቀደው በጀት ፕሮግራሙ 51 ሺ የሚደርሱ ተማሪዎችን የቁርስና ምሳ ተጠቃሚ ለማድረግ ወስኗል። ለዚህም የመጀመሪያ ዙር  66ነጥብ 9 ሚሊየን ብር የተፈቀደ ቢሆንም ፋይናንስና ኢኮኖሚ ብሩን ለክፍለ ከተሞች የለቀቀው  ታህሳስ  አምስት ዘግይቶ ነው።ሆኖም በአሁኑ ወቅት ወደ የትምህርት ቤቱ አካውንት እንዲገባ ተደርጓል።    በሴቶችና ህጻናት ጉዳይ በኩልም ምግብ የሚያዘጋጁት እናቶች እንዲደራጁ ተደርገው ወደ ስራ እየገቡ ነው። አንዳንድ ትምህርት ቤቶች  በፍጥነት ጀምረዋል በቅርብ ጊዜ  ደግሞ ሁሉም ትምህርት ቤቶች የሚጀምሩ ይሆናል ።ፕሮግራሙ የሚካሄደው ተማሪዎችን ለመርዳት ሳይሆን ህጻናቱ በቂ ምግብ የማግኘት መብት ስላላቸው ነው የሚሉት ወይዘሪት ሜቲ ከዚህ ቀደም  ትምህርት የሚያቋርጡ ክፍል ውስጥ የሚወድቁ እንደነበሩ በማስታወስ  ልጆቹ ተምረው ቢጨርሱም ውጤታማ፣ ጤናማ ብቁ ዜጋም እንደማይሆኑ ይናገራሉ።   በመንግስት የሚደረገው ድጋፍ የማይቆራረጥ በመሆኑ ጥቅሙ ከፍተኛ  ነው የሚሉት ወይዘሪት ሜቲ በተደረገው የዳሰሳ ጥናት ዘንድሮ በከተማዋ ሰባ ሺ የሚደርሱ ተማሪዎች ድጋፉ እንደሚያስፈልጋቸው ተረጋግጧል ብለዋል።አዲስ ዘመን ታህሳስ 20/2011በራስወርቅ ሙሉጌታ
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=2170
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
fc8338220645c8156a8ffcd7db92bf9a
66eee7c3a354b9a7a46f761213d1ad84
የሶስትዮሽ ስብሰባው ነገ ይካሄዳል ተብሎ ነበር
ኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብን አስመልክቶ ከሱዳን እና ግብጽ ጋር በአሜሪካ ሊካሂድ የታሰበው ስብሰባ ላይ እንደማትገኝ አስታወቀች ፡፡ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን አስመልክቶ በኢትዮጵያ፣ በግብጽ እና በሱዳን መካከል በአሜሪካ የትሬዠሪ ቢሮ ሴክሬተሪ እና የዓለም ባንክ ፕሪዝዳንት በታዛቢነት የተገኙበት የሶስትዮሽ ድርድር በአሜሪካ ሲካሂድ የቆየ መሆኑ ይታወቃል፡፡ አሁንም በአሜሪካ የትሬዠሪ ቢሮ ሴክሬተሪ የተጠራው እና በዋሺንግተን ዲሲ የካቲት 19 እና 20 ቀን 2012 ዓ.ም ሊካሂድ በታሰበው የሶስትዮሽ የድርድር መድረክ፣ የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን በአገር ውስጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር የሚያደርገውን ውይይት ባላማጠናቀቁ፣ ኢትዮጵያ አልሳተፍም ብላለች፡፡ በተጠቀሰው ጊዜ በአሜሪካ በመገኘት ውይይቱን ማድረግ እንዳልተቻለ ጥሪውን ላደረገው የአሜሪካ የትሬዠሪ ቢሮ የኢትዮጵያ መንግስት ማስታወቁን የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚ/ር ገልጿል፡፡ በሌላ በኩል የግብጹ አህራም ኦንላይን እንደዘገበው የግብጽ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሚ ሹክሪ በስብሰባው ለመታደም ወደ አሜሪካ አቅንተዋል፡፡ በአሁኑ ስብሰባ የመጨረሻ ስምምነት ላይ ይደርሳሉ ተብሎ ይጠበቅ እንደነበረም ነው አህራም በዘገባው የጠቆመው፡፡ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ትናንት የካቲት 17 ማምሻውን ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ወደ ጣሊያን ማምራታቸው ይታወቃል፡፡ በነገው እለት በዋሺንግተን ዲ.ሲ. ይካሄዳል በተባለው የሶስትዮሽ ስብሰባ ላይ አቶ ገዱን ጨምሮ የሶስቱ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እንደሚሳተፉ ይጠበቅ ነበር፡፡
5ፖለቲካ
https://am.al-ain.com/article/ethiopia-will-not-participate-on-washington-s-meeting-over-the-gerd
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
c3d3265681d42aa7dd68661d5cfac2e0
32729c489b66f00b9e69535adbc688ae
የጃክ ማ ፋውንዴሽን የኮሮና ቫይረስ ለመከላከል ለሶስተኛ ጊዜ ግብዓት መላኩ ተገለጸ
አዲስ አበባ፡- ለሶስተኛ ጊዜ ከጃክ ማ ፋውንዴሽን ለአፍሪካ አገራት የተላከው የኮሮና ቫይረስ መከላከያ ግብአት ኢትዮጵያ ገብቷል፡፡ ትናንት ወደ ኢትዮጵያ የገባው ወደ 61 ሺህ ቶን የሚጠጋ ይህ ቁሳቁስ ለ54 የአፍሪካ ሀገራት የሚከፋፈል እንደሆነ ተነግሯል፡፡ በውስጡም 199 ሺህ 300 ከንክኪ መከላከያ ልብሶች፣ 300 የመተንፈሻ ቬንትሌተሮች፣ 708 የሙቀት መለኪያዎች፣ 28 ሺህ 500 የሕክምና ጓንቶች እና 3 ሺህ 800 የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብሎች ይገኙበታል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በፌስቡክ ገፃቸው፤ የጃክ ማ ፋውንዴሽን ከአፍሪካ ጎን በአጋርነት በመቆሙ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ ጃክ ማ በመጀመሪያው ዙር ለእያንዳንዱ የአፍሪካ አገር ቫይረሱን ለመለየት የሚረዱ 20 ሺህ መመርመሪያዎች፣ 100 ሺህ የፊት ጭምብል፣ የህክምና ባለሙያዎች የሚለብሷቸው አንድ ሺህ መከላከያ ልብሶች በሁለተኛው ዙር ደግሞ 500 የመተንፈሻ መሳሪያዎች (ቬንትሌተር)፣ 200 ሺህ የፊት መሸፈኛዎችና የህክምና ሙሉ ልብሶች፣ አንድ ሚሊዮን ናሙና መውሰጃ ፣ ሁለት ሺህ የሰውነት ሙቀት መለኪያ እና 500 ሺህ ጓንቶች ለአፍሪካ አገራት ልከው መከፋፈላቸው ይታወሳል። አዲስ ዘመን ሚያዝያ 20/2012በጋዜጣው ሪፖርተ
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=31250
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
e5f7a855126e7da0f97f4b902ab2a72e
9b412ec74dcdd37ad659ccebc4887e4e
'አስጸያፊ' ከመባል ኦስካር ወደማሸነፍ
የንጽህና መጠበቂያው ሞዴስ ሲሠራ ትላንት ባልተለመደ ሁኔታ ያለ አስተዋዋቂ የተካሄደው የኦስካር የሽልማት ሥነ ሥርዐት በርካታ ጥቁር ፊልም ሠሪዎች ጎልተው የወጡበት ነበር። 'ብላክ ፓንተር' በምርጥ ኦሪጅናል ስኮር፣ በፕሮዳክሽን ዲዛይንና በኮስቲውም ዲዛይን ሦስት ሽልማቶች አግኝቷል። በተጨማሪም ዛንዚባር የተወለደው የሮክ ኤንድ ሮል ሙዚቀኛ ህይወትና ሥራ የሚዳስሰው ፊልም እንዲሁም፣ ለበርካታ ዓመታት ሽልማት ሳይገኝ የቆየው ስፓይክ ሊ ተሸልሟል። ሌላው ተሸላሚ የጽህና መጠበቂያ ሞዴስ ላይ የሚያተኩረው ዘጋቢ ፊልም ነው። በሥራው ከተሳተፉት አንዷ ደግሞ ስኔህ ትባላለች። ስኔህ የወር አበባ ያየችው በ15 አመቷ ነበር። ለመጀመሪያ ጊዜ የወር አበባዋ ሲመጣ ምን እየተፈጠረ እንደሆነ አላወቀችም ነበር። "በጣም ደንግጬ ነበር። ከባድ በሽታ የያዘኝ መስሎኝ ማልቀስ ጀመርኩ" በማለት ትናገራለች። • "በወንድሜ ለአምስት ዓመታት ተደፍሬአለሁ" • በፍቅረኞች ቀን የፍቅር ስጦታ ለሴት ተማሪዎች "ለእናቴ ለመናገር ስለፈራሁ ለአክስቴ ነበር የነገርኳት። አክስቴ 'አሁን አድገሻል ማለት ነው። አታልቅሺ፤ ተፈጥሯዊ ነው።' በማለት አስረዳቺኝ። ለእናቴ የነገረቻት እሷ ናት" ስኔህ አሁን 22 አመቷ ነው። በመንደሯ በሚገኝ የንፅህና መጠበቂያ (ሞዴስ) በሚያመርት አነስተኛ ድርጅት ውስጥ ትሠራች። ስለ ወር አበባ ለህብረተሰቡ ታስተምራለች። ስኔህ ስለ ወር አበባ የተዛባ አመለካከት እንዳለ ትናገራለች 'ኢንድ ኦፍ ሴንቴንስ' (የአረፍተ ነገር መጨረሻ) የተባለው ዘጋቢ ፊልም ኦስካር ሲያሸንፍ፤ ስኔህ የኦስካር ዝግጅትን ለመታደም ወደ ሎስ አንጀለስ አቅንታለች። ዘጋቢ ፊልሙ የተሠራው በሰሜን ሆሊውድ አንድ የተማሪዎች ቡድን ባሰባሰበው ገንዘብ ንፅህና መጠበቂያ (ሞዴስ) የሚሰራ ማሽን እና ኢራናዊ አሜሪካዊ ፊልም ሠሪ ራይካ ዜህታብቺን ወደ ስኔህ መንደር በመላክ ነው። ፊልሙ የተቀረፀው በካቲክሄታ መንደር ባሉ የእርሻ ቦታዎች፣ ሜዳዎች እና የትምህርት ክፍሎች ነው። እንደ ሌሎቹ የሕንድ አካባቢዎች ሁሉ በካቲክሄራ መንደርም የወር አበባ የመነጋገሪያ ርዕስ አይደለም። • ሴቶች የተቆጣጠሩት የስፔን ካቢኔ • ታሪክ እየቀየሩ ያሉት ሴቶች ሴቶች በወር አበባ ወቅት እንደቆሸሹ ስለሚታሰብ ከሀይማኖት ቦታዎች እና ሌሎች ማኅበራው ክንውኖችም ይታገዳሉ። ስለ ወር አበባ ብዙ የተዛቡ አመለካከቶች ስላሉም ሰኔህ የወር አበባ ከማየቷ በፊት ስለ ወር አበባ ምንነት አለማወቋ አይገርምም። "የወር አበባ የመነጋገሪያ ነጥብ አልነበረም፤ በሴቶች መካከልም መወያያ ርዕስ አልነበረም" ትላለች። እንደ አውሮፓውያኑ በ2017 'አክሽን ኢንዲ' ውስጥ የሚሠራ ሱማን የተባለ ጎረቤቷ ንፅህና መጠበቂያ (ሞዴስ) የሚሠራ አነስተኛ ድርጅት ውስጥ ለመሥራት ፈቃደኛ እንደሆነች ጠየቃት። የኮሌጅ ተመራቂ የሆነችው እና አንድ ቀን ለደልሂ ፖሊስ መሥራትን የምታልመው ሰኔህ ጥያቄውን በደስታ ተቀበለች። በመንደሩም "ሌላ ምንም አይነት የሥራ እድል" አልነበረም። 'ፍላይ' የተባለው ንጽህና መጠበቂያ ሞዴስ "እናቴን ፍቃድ ስጠይቃት 'አባትሽን ጠይቂ አለችኝ'። በቤታችን ሁሉም ከባድ ውሳኔዎች በወንዶች ነው የሚወሰኑት" ስኔህ ለአባቷ ስለ ሥራው ለመናገር በጣም አፍራ ስለነበረ የህፃናት መፀዳጃ እንደምትሰራ ነበር የነገረችው። "ሥራውን ከጀመርኩ ሁለት ወር በኋላ ነው እናቴ ለአባቴ የሴቶች መፀዳጃ (ሞዴስ) እንደምሠራ የነገረችው" ትላለች ሰኔህ። እድለኛ ሆና አባቷ " ችግር የለውም፤ ሥራ ሥራ ነው" አለ። • ሴቶች በሰሜን ኮሪያ ሠራዊት ውስጥ • መጠጥ የ130 ሰው ህይወት ቀጠፈ ዛሬ አነስተኛ ድርጅታቸው ከ18 እስከ 31 ዓመት የሆኑ ሰባት ሴት ሠራተኞች...
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
faa284db65971f6ae60229a731d7e75d
12971878e68d0213c0485c7b729803c2
የጀርመን ሮማን ካቶሊክ ቤተክርስትያን ቀሳውስት ከፈረንጆቹ 1946-2014 ባለው ጊዜ 3600 ገደማ ሕፃናት ላይ ፈፅመውታል የተባለው ጭቆና ይፋ ሆኗል።
የጀርመን ቄሶች ሕፃናት ላይ የፈፀሙት በደል ይፋ ሆነ\nጥናቱን ያካሄደው የጀርመን ሮማን ካቶሊክ ቤተክርስትያን ኦፊሴላዊ ውጤቱን መስከረም 25 ለሕዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል። ዘገባው እንደሚጠቁመው 1670 ገደማ የቤተክርስቲያኒቱ ሰዎች 3677 ሕፃናት ላይ ፆታዊ ጥቃት አድርሰዋል። • የ80 ሚሊየን ዶላር የሙስና ቅሌት ተጋለጠ የቤተክርስትያኒቱ ቃል አቀባይ የሆኑ ግለሰብ በውጤት 'እጅግ ማፈራቸውን እና ጭንቀት ውስጥ መግባታቸውን' ተናግረዋል። ጥናቱ 'ግፍ ፈፃሚ ቀሳውስት አሏት' እየተባለች ለምትታማው የሮማን ካቶሊክ ቤተክርስትያን ሌላ መዘዝ ይዞ ብቅ ብሏል። ከጥቃት አድራሽ ቀሳውስት መካከል 38 በመቶ ያህሉ ብቻ ናቸው ቅጣት የተጣለባቸው የሚል ዘገባም ብቅ ብሏል፤ ከስድስት አንድ ብቻ ናቸው ለፍርድ የሚቀርቡት። ጥቃት ከደረሰባቸው ሕፃናት መካከል በርካቶቹ ወንዶች እንደሆኑ ሲነገር ዕድሜያቸው ደግሞ ከ13 ዓመት በታች ነው ተብሏል። • የአፍሪካ እግር ኳስ ቅሌት ጥናቱን ያካሄዱት ሦስት የጀርመን ዩኒቨርሲቲዎች ሲሆኑ 38 ሺህ ያህል መዝገቦች አገላብጠዋል፤ በርካታ መዝገቦች እንደተደመሰሰ ቢጠረጠርም። የቤተክርስቲያኒቱ ቃል አቀባይ የሆኑት ቢሾፕ ስቴፋን አከርማን «የጥናቱ ዓላማ በቤትክርስትያናችን እየተፈፀመ ያለውን ግፍ ማስቆም ነው» ብለዋል። የሮማን ካቶሊክ ቤ/ክ ዋና መቀመጫ የሆነችው ቫቲካን ስለጉዳዩ እስካሁን ምንም ባትልም ሊቃ ጳጳሳት ፖፕ ፍራንሲስ ግን ስለጉዳዩ ለመምከር ለወርሃ የካቲት ቀጠሮ መያዛቸው እየተነገረ ነው። • በሄይቲ የኦክስፋም ቅሌት፡ ተጠርጣሪዎች የአይን እማኞችን አስፈራርተዋቸዋል
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
f87dbaa84e56327601a5cb04071df48c
ed2a6583cd32aef33563b2a748f5adce
የአሜሪካ ዶላር ቅቡልነት ማክተሚያ እየተቃረበ መሆኑን ብሎምበርግ ዘገበ፡፡
ባሕር ዳር፡ ሰኔ 07/2012 ዓ.ም (አብመድ) ለ60 ዓመታት የአብዛኞቹ ሀገራት የመጠባበቂያ የባንክ ክምችት መለኪያ ሆኖ የዘለቀው የአሜሪካ ዶላር ቅቡልነት እያከተመ እንደሆነ ብሉምበርግ ዘግቧል፡፡ የአሜሪካውያን የኑሮ ሁኔታ ለዓለም ሚዛን ሆኖ መቆየቱ የዶላርን ቅቡልነት ማስቀጠሉን ያመለከተው ዘገባው በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት የተደቆሰው የሀገሪቱ ምጣኔ ሀብት የኑሮ ሚዛንነቷን ማሳጣቱን ገልጧል፡፡ከአሜሪካ ምጣኔ ሀብት መዳከም በተጨማሪ ሀገሪቱ እንደ ልዩ አድራጊ ፈጣሪ የመቆጠሯ ጉዳይም አጣብቂኝ ውስጥ መግባቱን ብሉምበርግ አመላክቷል፡፡ የሀገራት ውስጣዊ የምጣኔ ሀብት መሠረትና በውጭ ሀገራት የአሜሪካ የጥንካሬና ድክመት ሁኔታ ምዘና የዶላርን ቅቡልነት ማብቂያ የሚያመለክቱ እንከኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ተፅዕኖ አስቀድሞም የአሜሪካ ምጣኔ ሀብት ማሽቆልቆል እንደጀመረ ያስታወሰው ዘገባው በዚህ የአውሮፓውያን የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ሀገራዊ የቁጠባ መጠን 1 ነጥብ 4 ከመቶ እንደነበርና ይህም በሀገሪቱ ታሪክ 5ኛው ዝቅተኛ የቁጠባ መጠን የተመዘገበበት እንደሆነ አብራርቷል፡፡የሀገራት ባንኮች በዶላር መጠባበቂያ ገንዘባቸውን ስለሚያስቀምጡ ግን ሳያውቁት አሜሪካን ይደጉማሉ፤ በዚህም በቂ ቁጠባ ከውጭ ታገኛለች፡፡ የውጭ ኢንቨስትመንት ስበቷ ግን ከ1982 (እ.አ.አ) ጀምሮ እየቀነሰ እንደሆነ ነው የተመላከተው፡፡የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትና የቁጠባ መውረድ ከኮሮናቫይረስ የምጣኔ ሀብት ቀውስ ጋር ተዳምረው የአሜሪካን ዶላር የበላይነት እንደቀነሱት ታውቋል፡፡ የዚህ ዓመት የበጀት ጉድለት እስከ 19 ነጥብ 9 በመቶ እንደሚሆንም ተገምቷል፤ በእርግጥ በቀጣዩ የአውሮፓውያን በጀት ዓመት ወደ 9 ነጥብ 8 በመቶ እንደሚወርድ ተስፋ ተደርጓል፡፡በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ሚሊዮኖች ሥራ ማጣታቸው ደግሞ የበለጠ የበጀት ጉድለት መንስኤ እንደሚሆን ተመላክቷል፤ የሥራ ማጣቱ የቁጠባ መጠንን በእጅጉ ይቀንሰዋልና፡፡ የቁጠባ መጠን በሂደት ከዜሮ በታች 10 ሊደርስ እንደሚችልም ተሰግቷል፡፡ ይህ ደግሞ በአሜሪካ የምጣኔ ሀብት ታሪክ ታይቶ የማያውቅ አደጋ ያስከትላል፡፡በዚህም ቀውስ ውስጥ ሆኖ የአሜሪካ ዶላር በጥር ከነበረበት የመግዛት አቅም ሚያዝያ ላይ ሰባት ከመቶ ጨምሮ መገኘቱን ያመለከተው መረጃው ዕድገቱ ግን በሌሎች ሀገራት ፍላጎት የተነሳ እንጂ በአሜሪካና በንግድ ሸሪኮቿ ምጣኔ ሀብት መጎልበት የመጣ አለመሆኑን አመላክቷል፡፡በዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር የአሜሪካ ምጣኔ ሀብት ዓለማቀፋዊ ተጽእኖ ፈጣሪነት እንደሚያከትምም እየተገለጸ ነው፡፡ አሜሪካ ተጽእኖ የምትፈጥርባቸው ዓለማቀፍ ተቋማትንና ስምምነቶችን አለማክበርና ራስን ማግለል እንደሚያዳክማትም ነው የተገለጸው፡፡ ከ “ፓሪስ” የአየር ንብረት ለውጥ ስምምነት ማፈንገጥ፣ ከፓስፊክ ተሻጋሪ አጋርነት (ትራንስ-ፓስፊክ ፓርትነርሺፕ)፣ ከዓለም ጤና ድርጅትና ከነባሩ የአትላንቲክ ጥምረት ራሷን ማግለሏ በአብነት ተጠቅሰዋል፡፡ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን በአግባቡ መቆጣጠር አለመቻልና በቅርቡ የተከሰተው ማኅበራዊ ቀውስ ከ1960ዎቹ (እ.አ.አ) ወዲህ ሀገሪቱ ዓይታ የማታውቃቸው ችግሮች ናቸው፡፡ እነዚህ ሁሉ ቀውሶች ደግሞ ከዓለማቀፋዊ መሪነቷ ለመውረዱ ማሳያ ሆነዋል፡፡ምንም እንኳ ምጣኔ ሀብቷ ከመጪው ጥር አካባቢ ጀምሮ ሊያንሰራራ እንደሚችል ቢጠበቅም የቁጠባ አቅሟ በቀላሉ ይጠገናል ተብሎ አልተገመተም፡፡ የዶላር የመግዛት አቅም ከውጭ ንግድ አንጻር በመጪው ሐምሌ እስከ 35 በመቶ እንደሚወርድ መገመቱ ደግሞ ግሽበቱን ለመመከት ፈተና እንደሚሆንባት አስግቷል፡፡የአሜሪካ ዶላር የመግዛት አቅም እንደተተነበየው ከወረደ ደግሞ ሦስት አንኳር ጉዳዮችን ያስከትላል፤ ግሽበት፣ ለተወሰነ ጊዜ በግሽበት ውስጥ መቆየት እና ከቀውሱ ለማገገም ጊዜ መውሰድ፡፡ የእነዚህ ሁሉ ድምር ደግሞ የፋይናንስ ገበያውን በአዙሪት ውስጥ ሊያቆየው ይችላል፡፡ ይህም የአሜሪካን የንግድ ጉድለት ያሰፋዋል፡፡ የንግድ ድጎማ ሥርዓቷ፣ በተለይም ከቻይና ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነት ባላቸው 102 ሀገራት ላይ የምትከተለው አሠራር መልሶ ራሷን እንዳያዳክማትም ተሰግቷል፡፡የዋሽንግተን ጊዜንና ሁኔታን ያላጤነ ከቻይና የሚጋፈፍ የፋይናንስ ጉድለት አሞላልም መጨረሻው የማገገሚያ ጊዜዋን ሊያራዝመው እንደሚችል ዘገባው ያስረዳል፡፡ብሉምበርግ ዘገባውን ሲቋጭም የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝንና የዘረኝነት ቀውሱ የዓለም ምጣኔ ሀብት አድራጊ ፈጣሪውን የአሜሪካ ዶላር መሪነት ያሳጣዋል፤ የአሜሪካንም ምጣኔ ሀብት የከፋ ቀውስ ውስጥ ያስገባዋል ብሏል፡፡ዘገባው የአሜሪካ ዶላር ጥገኛ በሆኑ ሌሎች ሀገራት ላይ ምን ሊከሰት እንደሚችልና ቀጣዩ የአሜሪካ ዶላርን የሚተካ መገበያያ ምን እንደሆነ አላመለከተም፡፡
4ዓለም አቀፍ ዜና
https://www.amharaweb.com/%e1%8b%a8%e1%8a%a0%e1%88%9c%e1%88%aa%e1%8a%ab-%e1%8b%b6%e1%88%8b%e1%88%ad-%e1%89%85%e1%89%a1%e1%88%8d%e1%8a%90%e1%89%b5-%e1%88%9b%e1%8a%ad%e1%89%b0%e1%88%9a%e1%8b%ab-%e1%8a%a5%e1%8b%a8%e1%89%b0/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
6ef6aa0ca3e1ce3f3007d42657c5ace9
25a7c27f8b01f1e3f55ba0d590e970e3
በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት ያገኙት ነጂብ ማኅፉዝ የምን ሀገር ዜጋ ናቸው?
አብዱልራዛቅ እ.ኤ.አ. በ1994 ላይ ያሳተሙት ‹ፓራዳይዝ› የተሰኘው ልብ ወለድ ታንዛኒያ ውስጥ በ20ኛው ምዕት ዓመት የልጅ አስተዳደግ ምን እንደሚመስል ፍንትው አድርገው ያሳዩበት ነው። በዚህ ልብ ወለድም ዓለም አቀፉን የ‹ቡከር› ሽልማት ለማግኘት መቻላቸውን ቢቢሲ ዘግቦታል፡፡ እንደ የኖቤል ኮሚቴ የሥነ ጽሑፍ ክፍል አገላለጽም፣ ‹‹[የእሳቸው] ገጸ ባህርያት ሁሌም ቢሆን በባህልና አኅጉራት መካከል የሚሽከረከሩ፣ በአሁን ሕይወትና በመጪው ሕይወት መካከል የሚመላለሱ ናቸው። በቀላሉ ሊያልፉት የማይችሉት ከባድ እውነታ ውስጥ ናቸው፡፡›› እ.ኤ.አ. በ1948 በዛንዚባር የተወለዱት አብዱልራዛቅ፣ እ.ኤ.አ. በ1960ዎቹ መገባደጃ አገረ እንግሊዝ የገቡት ስደተኛ ሆነው ነው። በቅርቡ ጡረታ እስከወጡበት ዕለት ድረስ በካንተርበሪው የኬንት ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዝኛና የድኅረ ቅኝ ግዛት ሥነ ጽሑፎች ፕሮፌሰር ነበሩ። ሽልማቱ፣ ደራሲው ያለፉበትን የስደተኞች ቀውስንና ቅኝ አገዛዝን በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ውይይት እንዲደረግባቸው ያስችላል ብለዋል፡፡ ‹‹እነዚህ በየዕለቱ ከእኛ ዘንድ ያሉ ነገሮች ናቸው። ሰዎች እየሞቱ ነው፣ ሰዎች በዓለም ዙርያ አሁንም እየተጎዱ ነው፡፡ በእነዚህን ጉዳዮች ላይ በፍፁም ቀናነትና አስተውሎት መንገድ መነጋገር መላ መምታት አለብን፤›› ብለዋል የኖቤል ተሸላሚው አብዱልራዛቅ። ዓምና በሥነ ጽሑፍ ያሸነፉት አሜሪካዊው ገጣሚ ሊዊስ ግሉክ መሆናቸው ይታወሳል። የስዊድኑ አካዴሚ በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት ከሸለማቸው ታላላቅ ደራስያን መካከል ከአፍሪካ አኅጉር ስድስት ደራስያን ይገኙበታል፡፡ እነርሱም ዎሌ ሾንካ (ናይጀሪያ)፣ ነጂብ ማኅፉዝ (ግብፅ)፣ ናዲን ጎርዲመር (ደቡብ አፍሪካ)፣ ጄ.ኤም ኮትዚ (ደቡብ አፍሪካ)፣ እና ዶሪስ ሌሲንግ (ዚምባቡዌ -እንግሊዝ) ይገኙበታል፡፡
null
null
https://huggingface.co/datasets/israel/AmharicQA
7b8d6ea4eeeb51c6616c2860df2417d2
c4be84dbb4897b2b4d19f91885494e20
7 ኤርትራዊያን ተጫዋቾች ካምፓላ አየር ማረፊያ ላይ ተሰወሩ
በዘንድሮ የሴካፋ ውድድር ላይ በኡጋንዳ የተሳተፈው የኤርትራ ብሔራዊ ቡደን አባላት የሴካፋ ቃል አቀባይ ሮጀርስ ሙሊንደዋ ተጫዋቾቹ የጠፉት ውድድራቸውን አጠናቀው ወደ ሃገራቸው ለመመለስ ኢንቴቤ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ከደረሱ በኋላ መሆኑን ለቢቢሲ ተናግረዋል። ቃል አቀባዩ ጨምረውም "ከዚህ ቀደም የሚጠፉት ከሆቴላቸው ነበር። አሁን ግን አየር ማረፊያ ደርሰው 'ቼክኢን'እንደማድረግ፤ መኪና ተከራይተው ከሚጠብቋቸው ጓደኞቻቸው ጋር በመሆን ተሰውረዋል" ብለዋል። ኤርትራውያን እግር ኳስ ተጫዋቾች ለውድድር ከሃገራቸው ከወጡ በኋላ የመጥፋታቸው ዜና ይህ የመጀመሪያው አይደለም። ባሳለፍነው ጥቅምት ወር ላይም ከ20 ዓመት በታች የሴካፋ ውድድር ላይ ለመሳተፍ ከሃገራቸው የወጡ አራት ኤርትራውያን ካረፉበት ሆቴል መጥፋታቸው ይታወሳል። የሴካፋው ቃል አቀባይ ሮጀርስ ሙሊንድዋ ጥቅምት ወር ላይ አራቱ ኤርትራውያን እግር ኳሰኞች የጠፉበትን ሁኔታ ሲያስታውሱ፤ "በካምፓላ በርካታ ኤርትራውያን አሉ። ኤርትራውያኑ ካሸነፉበት ውድድር በኋላ ሆቴል ድረስ አብሮ በመሄድ ብዙዎች ድጋፋቸውን ሲሰጡ ነበር። ከዛ ተጫዋቾቹ ከደጋፊዎቻቸው ጋር ተቀላቅለው ነው ከሆቴል የወጡት። እኛ የትኛው ተጫዋች የትኛው ደጋፊ መሆኑን መለየት አልቻልንም ነበር" ይላሉ። የተጫዋቾቹን መጥፋት ሴካፋ ለኡጋንዳ መንግሥት፣ ለኡጋንዳ ስፖርት ፌዴሬሽን እና በኡጋንዳ ለኤርትራ ኤምባሲ ማሳወቁን ቃል አቀባዩ ተናግረዋል። 7ቱ ተጫዋቾች ከሆቴል ሳይሆን አየር ማረፊያ ደርሰው ለምን እንደተሰወሩ ሲያስረዱ፤ "ከየሃገራቱ ጋብዘን የሴካፋ አዘጋጅ ኮሚቴ አባላት ያደረግናቸው ሰዎች።" አሉ የሚሉት ቃል አቀባዩ፤ በስም የሚጠቅሷቸው እና ከኤርትራ የመጡት ልዑክ የእግር ኳስ ባለሙያ ሳይሆኑ "የኤርትራ ከፍተኛ ፖሊስ አባል መሆናቸውን ተረዳን" ይላሉ። እኚህ በስም የተጠቀሱት ግለሰብ ተጫዋቾቹ በሚያርፉበት ሆቴል አብረዋቸው ስለነበሩ ተጫዋቾቹ ከሆቴል መሰወር አለመቻላቸውን ተናግረዋል። "ውድድሩ እስኪያበቃ ድረስ ከሆቴሉ መውጣት ያልቻሉት ሲከታተላቸው ስለነበረ ነው" በማለት ይናገራሉ። ኤርትራውያን ተጫዋቾች ለስፖርታዊ ውድድር ከሃገራቸው በወጡ ቁጥር የመጥፋታቸው ነገር እጅጉን እያሳሰበን ነው የሚሉት ሮጀር ሙሊንድዋ፤ "ይህ ከኤርትራም አልፎ ለቀጠናው እግር ኳስ አደጋ ነው" ይላሉ። "እንደ ሴካፋ በኤርትራ እግር ኳስ ላይ ከፍተኛ ፍላጎት አለን። የኤርትራ እግር ኳስ በፍጥነት እያደገ ነው። ከ20 ዓመት የሴካፋ ውድድር ላይ የግማሽ ፍጻሜ ውድድር ሊደረግ በዋዜማ ዕለት ነው 4ቱ ተጫዋቾች የጠፉት። ከዚያም በኬንያ 1 ለ 0 ኤርትራ ተሸነፈች። ልጆቹ ባይጠፉ ኖሮ ውጤቱ ሌላ ሊሆን ይችል ነበር። በአሁኑም የሴካፋ ውድድር የፍጻሜ ተፋላሚዎች ነበሩ። በየግዜው መጥፋታቸው የኤርትራ መንግሥት ከሃገር እንዳይወጡ ያደርጋቸዋል። ይህ ደግሞ የእግር ኳስ ችሎታቸውን እንዳያሳድጉ ያደርጋል" በማለት ስጋታቸውን ይገልጻሉ። በየዓመቱ በርካታ ኤርትራውያን ወጣቶች የተሻለ ኑሮን ፍለጋ ከኤርትራ ወጥተው ይሰደዳሉ። 2016 ላይ የወጣ አንድ ሪፖርት እንደሚጠቁመው ከአፍሪካ ሃገራቸውን ጥለው ከሚወጡ ወጣት አፍሪካውያኖች አብዛኛዎቹ ኤርትራውያን ናቸው። በኤርትራ ውስን የፖለቲካ ነጻነት እና ማብቂያ የሌለው ብሔራዊ አገልግሎት ከሌሎች ምክንያቶች ጋር ተደማምሮ ወጣቶች ሃገራቸውን ጥለው እንዲሰደዱ እንደሚያደርጋቸው ይነገራል። በጉዳዩ ላይ የኤርትራ የእግር ኳስ ፌደሬሽን አባላት ምላሽ እንዲሰጡን ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
937f288e7c5bd900a0cbd36fe502237d
c528e86b384ef5042150115d145befa7
ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የኢቦላን ወረርሽኝ ለመግታት ከ60 ሺህ በላይ ለሚሆኑና በመደበኛነት ወደ ሩዋንዳና ኡጋንዳ ለሚገቡ ድንበር ተሻጋሪ ነጋዴዎች የኢቦላ ክትባት ልትሰጥ እንደሆነ አስታወቀች።
ኮንጎ ለድንበር ተሻጋሪ ነጋዴዎች የኢቦላ ክትባት ልትሰጥ ነው\n• በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የጤና ባለሙያዎች ጥቃት ደረሰባቸው • የኢቦላ መከላከያ ክትባት በኮንጎ ሊሰጥ ነው በሩዋንዳ ድንበር ላይ በሚገኘው የኮንጎያዊያን የንግድ ማዕከል' ጎማ' የኢቦላ ኬዝ መገኘቱን በቅርቡ አንድ ሪፖርት ይፋ ማድረጉን ተከትሎ ነበር ለድንበር ተሻጋሪ ነጋዴዎች ትኩረት መሰጠት የተጀመረው። ባለፈው ዓመት ብቻ በኢቦላ ምክንያት በትንሹ 1900 ሰዎች ሕይወት ያለፈባት ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የኢቦላ ወረርሽኝ መከላከል አስተባባሪ የሆኑት ጂን ጃኪዩስ ሙየምቤ ከሆነ፤ በሩዋንዳ የሚገኙ የጤና ባለሥልጣናትም ድንበር ተሻጋሪ ነጋዴዎችን በተመለከተ ለሚደረገው የክትባት ዘመቻ 100 ሺህ ክትባቶችን ጠይቀዋል። ይሁን እንጂ የክትባት ዘመቻው መቼ እንደሚጀመር አልታወቀም። • ኢቦላ ወደ ኡጋንዳ እየተዛመተ ነው ዶ/ር ሙየምብ እንዳሉት ለድንበር ተሻጋሪ ነጋዴዎቹ ክትባት ከተሰጠ በኋላ የኢቦላ ታማሚ በተገኘባቸው አካባቢዎች ክትባቱን መስጠት እንደሚጀምሩ የህክምና ቡድኑ አስታውቋል። ዓለም አቀፉን የጤና ድርጅት ጨምሮ ዓለም አቀፍ የጤና ባለሙያዎች የተሳተፉበት ክትባት አገልግሎት ላይ መዋል የጀመረ ሲሆን ክትባቱ በዲሞክራቲክ ኮንጎ ግርታን ፈጥሮ ነበር። ክትባቱ በጆንሰን እና ጆንሰን የተሰራ ሲሆን በዲሞክራቲክ ኮንጎ ባለፈው ዓመት ሲሰጥ ከነበረው ከአንድ የሜርክ ክትባት መጠን የተለየ ነው ተብሏል። በምስራቃዊ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በሚዛመቱ ሀሰተኛ መረጃዎችና እምነት ማጣት ሳቢያ የኢቦላ ወረርሽኝን ለመቆጣጠር የሚደረገውን ጥረት ገትቶታል።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
7bf733113d3392dc2d8fe31bce5ba306
d50e2fec85d16fd05efbaa74cfe9a15f
ምዕራባዊያኑ በትግራይ ጉዳይ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጋር ምን መከሩ?
ከእነዚህ መሪዎች መካከል የጀርመኗ መራሂተ-መንግሥት አንግላ ሜርክልና የፈረንሳዩ ፕሬዝደንት ኢማኑዔል ማኽሮ ይጠቀሳሉ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ ጠዋት ደግሞ ከአዲሱ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከን ጋር ውይይት ማድረጋቸውን አሳውቀዋል። የዩናይትድ ስቴትስ አዲሱ የጆ ባይደን አስተዳደር አባል የሆኑት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩም ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጋር መምከራቸውን ገልፀዋል። ሚኒስትር ብሊንከን በትዊተር ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት ከጠ/ሚ ዐቢይ ጋር መነጋገራቸውን አስታውቀው በትግራይ ክልል ያለውን ቀውስ እንዳሳሰባቸው ተናግረዋል። ጨምረውም በትግራይ ክልል ምንም ዕክል የሌለው የሰብዓዊ እርዳታ ፍሰት እንዲኖር ጥሩ አቅርበዋል። 'ነገር ግን ተግዳሮቶች ቢኖሩም ዩናይትድ ስቴትስ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ለውጥ እንዲቀጥልና ሰላማዊ ለውጥ እንዲኖር ድጋፍ እንደምታደርግ' ገልፀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይም ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያን ለውጥ ለመደገፍ ላላቸው ቁርጠኝነት አመስግነዋል። አክለው በዩኤስ እና ኢትዮጵያ መካከል የሚኖር ጠንካራ ግንኙነት ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ግንባታ አስፈላጊ እንደሆነ አስምረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትዊተር ገፃቸው በፃፉት መልዕክት ትግራይ ክልል ስላለው ሁኔታ ምንም ያሉት ነገር የለም። በተመሳሳይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከጀርመኗ መራሂተ መንግሥት ጋር ባደረጉት የስልክ ልውውጥ ስለሃገራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮች እንዲሁም ስለ ኮቪድ-19 እና ምጣኔ ሃብታዊ ግንኙነቶች ማውራታቸውን በትዊተር ገፃቸው አሳውቀዋል። በኢትዮጵያ የጀመርን ኤምባሲ የትዊተር ገፅ በበኩሉ መራሂተ-መንግሥት ሜርክል ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር በነበራቸው ቆይታ ሰብዓዊ እርዳታ አቅራቢ ድርጅቶቸና መገናኛ ብዙሃን በትግራይ ክልል በነፃ እንዲንቀሳቀሱ ጥሪ ማቅረባቸውን አስታውቋል። በሌላ በኩል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከፈረንሳዩ ፕሬዝደንት ጋር በሁለቱ ሃገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ስለማጠናከር እንዲሁም ሃገራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮችን በተመለከተ መምከራቸውን አስታውቀዋል። የፈረንሳዩ ፕሬዝደንት ኢማኑዔል ማኽሮ ስለዚህ ጉዳይ በማሕበራዊ ድር አምባዎቻቸው ያሉት ነገር ባይኖርም የፈረንሳይ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ባወጣው መግለጫ ፈረንሳይ በትግራይ ክልል ያለው ሁኔታ እንዳሳሰባትና የኢትዮጵያ መንግሥት ለሰብዓዊ እርዳታ ድርጅቶች ፈቃድ እንዲሰጥ መጠየቋን አስታውቋል። በሌላ በኩል በአስመራ የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ የኤርትራ መንግሥት ወታደሮቹን ከትግራይ ክልል በአስቸኳይ እንዲያስወጣ አሜሪካ ጥሪ አቅርባለች ብሏል። ኤምባሲው በፌስቡክ ገፁ የአሶሺዬትድ ፕሬስ ዘገባን አጋርቷል። በዘገባው የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ 'የኤርትራ ወታደሮች በትግራይ ክልል የሰብዓዊ መብት ጥሰት እየፈፀሙ እንደሆነ የሚጠቁም መረጃ አሜሪካ እንዳላት' ተናግረዋል ብሏል። የኤርትራ መንግሥት በትግራይ ክልል ስላለው ጦርነት ብዙም ያለው ነገር ባይኖርም ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ የኤርትራ ወታደሮች በትግራይ ጦርነት አልተሳተፉም ሲል በተደጋጋሚ አስተባብሏል። በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ሆነው ያገለገሉ አምባሳደሮች በቅርቡ ትግራይ ክልል ያለው ሁኔታ አሳስቦናል ብለው ግልፅ ደብዳቤ ፅፈው ነበር። የኤርትራ መንግሥት ማስታወቂያ ሚኒስትር ለዚህ ግልፅ ደብዳቤ ምላሽ መስጠቱ አይዘነጋም።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
6ec4c83bb69f8f0712490f5baddb59c1
7459f6a60cfc5ecec3142605e99a67ab
‹‹የግጭት አዘጋገብ ጥንቃቄ የተሞላበት ሊሆን ይገባል›› የኢትዮጵያ ብሮድካስት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጌታቸው ድንቁ
አዲስ አበባ፡- የቃላት አመራረጥ፣ አገላለፅና በአጠ ቃላይ የሚተላለፉ የግጭት ዘገባዎች ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊደረግቸው እንደሚገባ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጌታቸው ድንቁ ገለፁ፡፡ ዋና ዳይሬክተሩ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እናደተናገሩት፤ እንደ ኢትዮጵያ ባለች ለግጭት መነሳት ብዙ ምክንያቶች ባሉባት አገር የግጭት አዘጋገብ ከፍተኛ ጥንቃቄ የተሞላበት መሆን አለበት። ‹‹መገናኛ ብዙሃን በባህሪያቸው ግጭትን የማምጣት አቅም አላቸው፡፡ ይህ በተለያዩ አገራት ታይቷል፤ ታሪክም መዝግቦታል፡ ፡›› ብለዋል፡፡ እንደዶክተር ጌታቸው ገለፃ፤ አሁን ያለው ግጭት ሁሉም መነሻቸው መገናኛ ብዙሃን ናቸው በሚል በዋነኛ መንስኤነት መጥቀስ ባይቻልም፤ ግጭቶችን ለማብረድ ቀድሞ መንስኤዎችን አጥንቶ ለህብረተሰቡ በማሳወቅ ችግሩን ማስቀረት እንዲቻል ያለውን አቅም ሙሉ ለሙሉ ተጠቅሞ አለመስራት ታይቷል፡፡ አዘጋገብ ላይም ጋዜጠኞቹ ከአገሪቷ የፖለቲካ ኢኮኖሚ እሳቤ ነፃ ባለመሆናቸው የራሳቸው ሃይማኖት፣ ብሔርና ፍላጎት ያላቸው በመሆኑ የኔ ከሚሉት አንፃር እየተነሱ የሚዘግቡበት ሁኔታም መኖሩን አመልክተው፤ ነገር ግን በጥንቃቄ መዘገብ እንዳለበት ጠቁመዋል፡፡አዲስ ዘመን ሚያዝያ 25/2011
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=10012
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
4af965aa8aba187ff3a1592a5c84cc8e
e87dc704cbd322622be13b09f1d2fa9b
አንደኛው ክንፉ በአየር ላይ የተቦደሰው አውሮፕላን በሰላም አረፈ
ቦይንግ 777 የሆነው አውሮፕላን 231 መንገደኞች ያሳፈረ ሲሆን በተጨማሪ 10 የአየር መንገዱ ሠራተኞች ነበሩ። ምንም እንኳ አውሮፕላኑ በደረሰበት እክል ምክንያት አካላቱ እየተቦዳደሱ ዴንቨር አካባቢ ያሉ መኖሪያ ቤቶች ላይ ቢያርፉም ተመልሶ በሰላም ማረፍ ችሏል። አውሮፕላኑ በደረሰበት አደጋ ምክንያት ምንም ዓይነት ጉዳት ሰው ላይ አለመድረሱ ተዘግቧል። የብሩምፊልድ ፖሊስ ከአውሮፕላኑ የወዳደቁ ናቸው የተባሉ የአንደኛው ሞተር ስብርባሪዎች ከመኖሪያ ቤቶች አቅራቢያ ማግኘቱን በፎቶ ማስረጃ አረጋግጧል። ተሳፋሪዎች ልክ አውሮፕላኑ እንደተነሳ 'ከባድ ፍንዳታ' መስማታቸውን ተናግረዋል። የበረራ ቁጥሩ 328 የሆነው ይህ አውሮፕላን የዩናይትድ ኤርላይንስ ንብረት ነው። አውሮፕላኑ ከዴንቨር አውሮፕላኑ ማረፊያ ወደ ሆኖሉሉ [ሁዋይ] እየበረረ ሳለ ነው የቀኝ ክንፍ ሞተሩ ላይ አደጋ ያጋጠመው ሲል የፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር አሳውቋል። ኤፒ የዜና ወኪል ያነጋገረው አንድ ተሳፋሪ ከባድ ፍንዳታ የተሰማው የአውሮፕላኑ ዋና አብራሪ መልዕክት እያስተላለፈ ሳለ ነው ብሏል። "አውሮፕላኑ በጣም መንቀጥቀጥ ጀመረ፤ ከዚያ የምንበርበት ከፍታ ትተን ወደታች መምዘግዘግ ጀመርን" ሲል ነው ተሳፋሪው ሁኔታውን የገለፀው። ተሳፋሪው አክሎ ምናልባት አደጋ ቢከሰት መለየት እንዲችሉ እሱና ባለቤቱ መታወቂያ ወረቀታቸውን በኪሳቸው እንዳኖሩ ተናግሯል። በይነ መረብ ላይ የተለጠፉ ፎቶዎች እንደሚያሳዩት እክል ከገጠመበት ክንፍ ላይ ጭስ ሲወጣ ነበር። አንድ አውሮፕላኑ ውስጥ የነበረ ተሳፋሪ የቀረፀው ተንቀሳቃሽ ምስል እንደሚያሳየው አንደኛው ሞተር በእሳት ከተያያዘ በኋላ ተሰብሮ ወደታች ተምዘግዝጓል። ሲኤንኤን ያናገረው አንድ የአካባቢው ነዋሪ የአውሮፕላኑ ስባሪ ከሰማይ ወደታች ሲወድቅ አይቶ ልጆቹን ከለላ ፍለጋ ሲሯሯጥ እንደነበር ተናግሯል። አደጋው የተከሰተው በሃገሪቱ ሰዓት አቆጣጠር ቅዳሜ ከሰዓት 7 ሰዓት አካባቢ ነው። የብሉምፊልድ ፖሊስ ነዋሪዎች የአውሮፕላኑን ስብርባሪ ከቦታው እንዳያነሱ አሳስቧል። የፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደርና ብሔራዊው የትራንስፖርቴሽን ሴፍቲ ቦርድ አደጋውን እንደሚያጣሩ ተነግሯል።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
afcb678b3e812428026a89371eff7b66
ae4ecaeb4f65c09159403682a76761a5
ከእሁድ ዕለት መስከረም 18፣2012 ጀምሮ በጎንደር አካባቢ፣ አዘዞና ማራኪ [ቀበሌ 18] አካባቢ፣ በነበረው አለመረጋጋት በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን ቢቢሲ ያነጋገራቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ገልፀዋል።
"የሰለጠነና በሙሉ አቅም የሚዋጋ ኃይል ነው ችግሩን የሚፈጥረው" የማዕከላዊ ጎንደር ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ\nባለፈው ሳምንት መጨረሻ በማዕከላዊ ጎንደር ጭልጋ አካባቢ በተከሰተ ግጭት ሕይወታቸው ያለፈ ሰዎችን አስከሬን ወደ ጎንደር በሚመጣበት ወቅት፣ ወጣቶች በሁኔታው ተቆጥተው በከተማዋ አንጻራዊ አለመረጋጋት እንዲፈጠር ምክንያት መሆኑን ለቢቢሲ አስተያየታቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ተናግረዋል። በጎንደር ነዋሪ የሆኑት አቶ ዘነበ ለቢቢሲ እንደተናገሩት ከእሁድ ጀምሮ ወጣቱ በአዘዞና ቀበሌ 18 ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኙ የቅማንት ተወላጆች ላይ ጉዳት የማድረስና ቤታቸውን የማቃጠል እርምጃዎች ተፈፅሟል ይላሉ። • ለ21 ዓመታት የኢትዮጵያን ቅርስ ደብቀው ያቆዩት ኢትዮጵያዊ • የአማራ ክልል ፖሊስ ረዳት ኮሚሽነር በቁጥጥር ስር ዋሉ • "ለስልጣን ተብሎ የሚፈጠር ውህደትን ህወሓት ፈጽሞ አይቀበለውም" አቶ ጌታቸው ረዳ ይህም የሆነው ጭልጋ የሞቱ ሰዎች አስከሬን ጎንደር ሲገባ "በግጭቱ ተሳትፎ በሌላቸው የቅማንት ተወላጆች ላይ ወጣቱ የበቀል እርምጃ በመውሰዱ ነው" በማለት ይከስሳሉ። ሌላኛው ስሙን መጥቀስ ያልፈለገው የጎንደር ከተማ ነዋሪ ደግሞ "ወጣቱ በጭልጋ የተገደሉትን ተከትሎ በከተማዋ የሚኖሩ ነገር ግን ይህ ችግር እንዲፈጠር አስተዋፅኦ የሚያደርጉ ሰዎች ይያዙልን በማለት ወደ ቤታቸው ሲያመራ ቤታቸው ውስጥ ሆነው ተኩስ ከፍተዋል" ይላል። በዚህም ምክንያት አንድ የልዩ ሃይል አባል እና አንድ ሰላማዊ ግለሰብ ግርግሩን በማረጋጋት ላይ እያሉ በተተኮሰ ጥይት መገደላቸውን ይናገራል። "ሰዎቹም ሙሉቀን ሲተኩሱ ውለዋል፤ በቂ ትጥቅ የነበራቸውና በኋላም ቤታቸው ሲፈተሽ የተለያዩ ከባድ መሳሪያዎች ተገኝተውባቸዋል" በማለት በቅማንት ተወላጆች ላይ "አንድ ወገን ላይ ያነጣጠረ ጥቃት አልደረሰም" ይላሉ። አቶ ዘነበ እንደሚሉት ግን በተነሳው ግርግር ብዙ ሰዎች ተጎድተዋል፤ ንብረት ተዘርፏል፤ ቤቶችም ተቃጥለዋል፤ ይህ ጥቃትም "አንድ ወገን ላይ ያነጣጠረ ነው" ብለዋል። ለዚህ ደግሞ "የመንግሥት እጅ አለበት" ባይ ናቸው። ከጎንደር ከተማ ትንሽ ወጣ ብላ በምትገኘው ቁስቋም አካባቢ ከፍተኛ ቦታ ላይ ሆነው የተኩሱም ድምፁም ጎንደር ስለሚሰማ ሽብር ለመፍጠር እንጂ የተደራጀ ጥቃት አልተሰነዘረም የሚሉት ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉት ግለሰብ አሁንም በተለያዩ የጎንደር ከተማና ዙሪያዋ አልፎ አልፎ በየግቢያቸው ሆነው የሚተኩሱ አሉ፤ በተወሰነ መልኩ የንግድ እንቅስቃሴዎች ተገድበዋል፣ የትራንስፖርት አገልግሎትም በአንጻሩ ቀንሷል በማለት የዛሬውን የጎንደር ውሎ ይናገራሉ። በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡን የጠየቅናቸው የጎንደር ከተማ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ አሁን ላይ ዝርዝር መረጃ ለመስጠት እንደሚቸገሩ ገልጸው በአጠቃላይ በከተማዋ ውስጥ የተቃጠለ ቤት አለመኖሩንና አልፎ አልፎ ግን መስኮታቸው የተሰባበሩ ቤቶች እንዳሉ ገልጸዋል። የማዕከላዊ ጎንደር ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር እንየው በአካባቢው (በማዕከላዊ ዞን) አሁን አንጻራዊ መረጋጋት መኖሩን ገልጸዋል። "በሎጂስቲክስም በአካልም ድጋፍ የሚደረግለት 'ጽንፈኛው ኮሚቴ' ግድያዎችን በመፈጸም ግጭቶችን ወደ ጎንደር ከተማ የማስገባት እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል" ብለዋል። ይህንንም ለመከላከል ከተለያዩ የጸጥታ መዋቅሮች ጋር እየሰሩ መሆናቸውን ኃላፊው ገልጸው "በተደራጀ፤ በሰለጠነ እና በሙሉ አቅም የሚዋጋ ኃይል ነው ችግሩን የሚፈጥረው" በማለት በህዝብ ላይ ትንኮሳ በመፍጠር ችግሩን በህዝቦች መካከል ለማድረግ እየሰራ ነው ብለዋል። "የውክልና ጦርነት አለ የምንለው ዝም ብለን አይደለም" የሚሉት ኮማንደሩ ሌሎች ያሰማሯቸው ኃይሎች ናቸው ያሏቸውን በቀጣዮቹ ጊዜያት "አንድ ሁለት ተብለው በሚቆጠሩ ማስረጃዎች ይፋ እናደርጋለን" ብለዋል።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
0b9ce89d2afa19e3052f8bd9663973ac
91b6fcb2746bcf75e7708044021338e1
በ33 ሚሊዮን ዶላር የብረት ፋብሪካ ተገንብቶ ተመረቀ
በደቡብ ኮሪያ ባለሀብቶች የተቋቋመው ኢኮስ የብረታ ብረት ማምረቻ ኃላፊነቱ የግል ማኅበር፣ በ33 ሚሊዮን ዶላር ያስገነባው ፋብሪካ በይፋ ተመርቆ ተከፈተ፡፡ኩባንያው በዱከም ከተማ ያስገነባውን ፋብሪካ ማክሰኞ ጥቅምት 6 ቀን 2011 ዓ.ም. ሲያስመርቅ፣ ፕሬዚዳንት ሙላቱ ተሾመ (ዶ/ር) ጨምሮ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል የተለያዩ የመንግሥት ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡ኩባንያው የኢትዮጵያ መንግሥትን በመወከል ከዓመታት በፊት በራሳቸው አማካይነት በተደረገለት ግብዣ ወደ ኢትዮጵያ መምጣቱን ያስታወሱት ፕሬዚዳንቱ፣ ፋብሪካው ተጠናቆ በማየታቸው ደስተኛ እንደሆኑና በመንግሥትም በኩል አስፈላጊው እገዛ እንደሚደረግለት አስታውቀዋል፡፡ኢኮስ ከአራት ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስዶ መንቀሳቀስ የጀመረ ሲሆን፣ የፋብሪካውን ግንባታ በማጠናቀቅ ሥራ ጀምሯል፡፡ ኩባንያው በመጀመሪያው የፕሮጀክት ምዕራፍ በዓመት 210 ሺሕ ቶን የግንባታ ብረቶችንና ገመድ ተሸካሚ ምሰሶዎችን የማምረት አቅም እንዳለው ታውቋል፡፡ነገር ግን ኩባንያው አሁን ባለው የውጭ ምንዛሪ እጥረት ምክንያት ከውጭ ጥሬ ዕቃዎችን ማስገባት ስለማይችል፣ በቀጣዮቹ ጥቂት ወራት እስከ 15 ሺሕ ቶን ብቻ ለማምረት እንደሚገደድ አስታውቋል፡፡ የውጭ ምንዛሪ እጥረት ችግሩ እንደሚፈታ ተስፋ እንዳላቸው የተናገሩት የኩባንያው ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሼል ሲ.ቾ፣ ችግሩን ለመፍታት ከፋይናንስ ተቋማት ጋር እየሠሩ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡በዋናነት የሚያስፈልጉትን የጥሬ ዕቃዎች ከደቡብ ኮሪያ፣ ከዩክሬንና ከቱርክ ኩባንያዎች እየተረከበ የሚገኘው ኩባንያው፣ በሙሉ አቅም ማምረት ሲጀምር የምርቱን መጠን እንደሚጨምር ተገልጿል፡፡ በሁለተኛ ምዕራፍ የግንባታ ፕሮጀክቱ በዓመት 500 ሺሕ ቶን የአርማታ ብረትና የተለያዩ የብረታ ብረት ምርቶችን ለማምረት የሚያገለግለውን የቢሌት ጥሬ ዕቃ የሚያመርት ፋብሪካ የመክፈት ዕቅድ እንዳለውም ተጠቁሟል፡፡በዓመት እስከ 200 ሺሕ ቶን የሚሆኑ ውድቅዳቂ ብረቶችን ከአገር ውስጥ በመሰብሰብ እንደ ጥሬ ዕቃ ለመጠቀም ኩባንያቸው ዕቅድ እንዳለው፣ የኩባንያው ዋና ሥራ አስፈጻሚ ተናግረዋል፡፡ይህ ፕሮጀክት እንደ ዕቅዱ ስኬታማ ከሆነ መንግሥት በዓመት ለብረታ ብረት ጥሬ ዕቃዎች ከሚያወጣው ከፍተኛ ወጪ እስከ 50 ሚሊዮን ዶላር ያድናል ተብሏል፡፡በአሁኑ ወቅት 14 ያህል የአርማታ ብረት አምራቾች በሥራ ያሉ ሲሆን፣ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ መንግሥት የአገር ውስጥ አምራቾችን ለማበረታታት የተለያዩ የቀረጥና የታክስ እገዛዎች ሲያደርግ መቆየቱ ይታወቃል፡፡ከዚህ ጋር በተያያዘ አምራቾቹ ያላቸውን አቅም ገንብተው የአገር ውስጥ ገበያውን እንዲቆጣጠሩና ከውጭ የሚመጣውን ብረት እንዲተኩ ቢጠበቅም፣ አሁንም ከፍተኛ መጠን ያለው የብረት ጥሬ ዕቃ በውጭ ምንዛሪ እየተገዛ ወደ አገር ውስጥ እየገባ ነው፡፡የብረት አምራቾቹም የሚያስፈልጉዋቸውን ጥሬ ዕቃዎች ማለትም የወዳደቁ ብረቶችን ከአገር ውስጥ ተጠቅመው እንዲያመርቱ ቢጠበቅም፣ አሁንም በተለያዩ ምክንያቶች የወዳደቁ ብረቶችን በብዛትና በጥራት ማግኘት አዳጋች መሆኑ ይነገራል፡፡በዚህም ምክንያት የአገሪቱ ከፍተኛ መጠን ያለው የውጭ ምንዛሪ ለብረታ ብረት  ጥሬ ዕቃዎች ግዥ እየወጣ ነው፡፡
3ቢዝነስ
https://www.ethiopianreporter.com/article/13393
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
ffd5a8859660a63db430b144d52f64c0
335209812e84462c654dd09a883cf25c
ካሜሩን ጋናን 2 ለ 0 አሸንፈች
በጋቦን አስተናጋጅነት ሲካሄድ በቆየው 31ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር የፊታችን እሁድ ለፍፃሜ የሚጋጠሙት ሁለት ብሔራዊ ቡድኖች ዛሬ ታውቀዋል፡፡ካሜሩን ጋናን 2 ለ 0 አሸንፋ ትናንት ቡሩኪና ፋሶን 4 ለ 3 ከሸኘው የግብፅ ቡድን ጋር ለዋንጫው ፍፃሜ ትጋጠማለች፡፡ለደረጃ ቅዳሜ ቡሩኪናና ጋና ይጫወታሉ፡፡በዛሬው ጨዋታ ሙሉ በሙሉ ብልጫ ያሳየውና ሁለት ድንቅ ጎሎችን ያስቆጠረው የካሜሩን ቡድን ነው፡፡የፍፃሜ ግጥሚያዎች የሚካሄዱት በዋናዋ ከታማ ስቴዲየም ይሆናል፡፡
4ዓለም አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/african-cup-of-nations-2-2-2017/3703910.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
3268bec5eaf42514edc851784e0ed557
5711e5df462c89a86f60459214293a46
ጥራቱን ያልጠበቀ የጨው ምርት ገበያውን ማጥለቅለቁ ጥያቄ አስነስቷል
የምርት ጥራት ደረጃውን ያልጠበቀ፣ የአዮዲን ይዘቱ አነስተኛ የሆነና ከነአካቴው አዮዲን የሌለው የጨው ምርት ከአፋር ክልል አፍዴራ ወደ መሀል አገር ገበያ በብዛት እየባ እንደሆነ ተገለጸ፡፡ ይህም ድርጊት ጥያቄ አስነስቷል፡፡ለአገሪቱ ለምግብ ፍጆታ የሚውለው ጨው በአብዛኛው የሚመረተው በአፋር ክልላዊ መንግሥት አፍዴራ ሐይቅ በባህላዊ ጨው አምራቾች ማኅበር ነው፡፡ የአገሪቱ ወርኃዊ የጨው ፍጆታ 360,000 ኩንታል ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 310,000 ኩንታል የሚሆነው በአፍዴራ በባህላዊ መንገድ እየተመረተ በጨው ነጋዴዎች አማካይነት ለማዕከላዊ ገበያ ብሎም በመላ አገሪቱ ይከፋፈላል፡፡ ጨው ለሰው ልጆች ጤና አስፈላጊ የሆነውን አዮዲን የተሰኘውን ንጥረ ነገር ሊኖረው የሚገባ በመሆኑ ለምግብነት የሚውል ጨው ከአዮዲን ጋር እንዲደባለቅ ይደረጋል፡፡ አዮዲን ለሕፃናት አዕምሮ ዕድገት ወሳኝ በመሆኑ የአዮዲን እጥረት የአዕምሮ ዝግመት፣ የእንቅርት በሽታንና ውርጃን እንደሚያስከትል የሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡መንግሥት ለምግብነት የሚውል የጨው ምርት ከአዮዲን ጋር እንዲደባለቅ የሚያስገድድ ሕግ አውጥቷል፡፡ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የሕፃናት መርጃ ድርጅት ጋር በመተባበር ባህላዊ የጨው አምራቾች ማኅበራት አቅማቸውን እንዲገነቡና የአዮዲን ንጥረ ነገር በምርታቸው ውስጥ እንዲጨምሩ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል፡፡መጋቢት 16 ቀን 2003 ዓ.ም. የሚኒስትሮች ምክር ቤት የምግብ ጨው አዮዲን እንዲኖረው የሚያስገድድ ደንብ አውጥቷል፡፡ ደንቡ ማንኛውም ሰው አዮዲን የሌለው ጨው ለሰው ምግብነት አገልግሎት እንዲውል ማዘጋጀት፣ ወደ አገር ውስጥ ማስገባት፣ ማከማቸት፣ ማከፋፈል፣ ማጓጓዝ ወይም መሸጥ እንደማይችል ይደነግጋል፡፡ ማንኛውም ለሰው ምግብነት የሚውል አዮዲን ያለው ጨው አግባብ ባለው አካል በሚያወጣው የጨው ደረጃዎች መሠረት የጥራት ደረጃ መመዘኛ ማሟላት እንዳለበት ይጠቅሳል፡፡ ‹‹ማንኛውም ሰው ይህን ደንብ ወይም ደንቡን ለማስፈጸም የወጡትን መመርያዎች ተላልፎ ቢገኝ አግባብ ባላቸው የአዋጅ ድንጋጌዎች መሠረት ይቀጣል፤›› ይላል የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ፡፡ይህን ደንብ የማስፈጸም ሥልጣን በአዋጅ የተሰጠው የኢትዮጵያ የምግብ፣ የመድኃኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለሥልጣን ነው፡፡ ይሁን እንጂ የአገሪቱን ሕግ በመተላለፍ የጥራት ደረጃውን ያልጠበቀ፣ ዝቅተኛ የአዮዲን ይዘት ያለው ወይም ከነጭራሹ አዮዲን የሌለው የምግብ ጨው ለገበያ እየቀረበ እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ በአፍዴራ የሚገኙ የጨው አምራቾች ማኅበራት የአመራረት ጥራት ብቃት ላይ የሚነሳው ጥያቄ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ከነአካቴው አዮዲን ያልተቀላቀለበት የጨው ምርት በስፋት ወደ ገበያ እየገባ እንደሆነ ምንጮች ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ ‹‹ለኅብረተሰቡ አዮዲን የሌለው ጨው እየቀረበለት ነው፡፡ ልጆቻችንን አዮዲን የሌለው ጨው እየመገብን ሊሆን ይችላል፡፡ ጉዳዩ እንደ አገር አሳሳቢ ነው፤›› ብለዋል ምንጮች፡፡ እንደ ማሳያ የሚጠቅሱት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ጨው የጫኑ ተሽከርካሪዎች በሰመራ ከተማ ኬላ በኢትዮጵያ የምግብ የመድኃኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለሥልጣን መያዛቸውን ነው፡፡ባለፈው ሳምንት ባለሥልጣኑ ደረጃውን ያልጠበቀ የጨው ምርት የጫኑ 40 ተሽከርካሪዎችን በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያካሄደ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ጉዳዩ ያሳሰበው የኢትዮጵያ የምግብ፣ መድኃኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለሥልጣን በአፋር ክልል በሚገኙ መግቢያና መውጫ ኬላዎች ላይ የሚያደርገውን የጨው ምርት ጥራት ቁጥጥር ማጠናከሩን አስታውቋል፡፡ የባለሥልጣኑ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሳምሶን አብረሃም መሥሪያ ቤታቸው በጥራት መቆጣጠሪያ ጣቢያዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር በማድረግ ላይ እንደሆነ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ ባለሥልጣኑ በአፍዴራና በሌሎችም ጣቢያዎች ያሰማራቸው ኢንስፔክተሮች ፈጣን የመመርመሪያ መሣሪያ እንዳላቸውና ጥብቅ ፍተሻ እንደሚያደርጉ አቶ ሳምሶን ለሪፖርተር በሰጡት ማብራሪያ ገልጸዋል፡፡ ‹‹አዮዲን ያልተቀላቀለበት ጨው ለኅብረተሰቡ ፍጆታ እንዲውል ለሽያጭ ሊያቀርቡ ሲሉ እየተያዙ ነው፤›› ብለዋል፡፡ጨው የጫኑ ተሽከርካሪዎች ከላይ የተጫኑት ጆንያዎች አዮዲን ያለው ጨው የያዙ ሆነው ከታች ግን አዮዲን ያልተቀላቀለበት ጨው የያዙ ጆንያዎች ተጭነው እንደተገኙ አስረድተዋል፡፡ ለፋብሪካዎች በግብዓትነት የሚቀርበው ጨው አዮዲን ያልተደባለቀ እንደሆነ፣ አምራቾችና ነጋዴዎች ለፋብሪካዎች አዮዲን የሌለው ጨው ማቅረብ እንደሚችሉ የገለጹት አቶ ሳምሶን፣ ይህን ለማድረግ ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የድጋፍ ደብዳቤ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡ የድጋፍ ደብዳቤውን በፍተሻ ኬላዎች ላይ እያሳዩ ለፋብሪካዎች ምርታቸውን ማቅረብ እንደሚችሉ ገልጸዋል፡፡ይሁን እንጂ ለፋብሪካ በጥሬ ዕቃነት የሚቀርብ በማስመሰል ለምግብነት ፍጆታ የሚውል ጨው (አዮዲን የሌለው) ለገበያ ለማቅረብ ጥረት ሲደረግ እየተያዘ እንደሆነ አቶ ሳምሶን አስረድተዋል፡፡ ‹‹ይህን ችግር ለመፍታት ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ ከንግድ ሚኒስቴርና ከሌሎች የዘርፉ መሥሪያ ቤቶች ጋር ሆነን የመቆጣጠር ሥራ እያከናወንን ነው፤›› ብለዋል፡፡ በቁጥጥር ሥር የዋሉት 40 ተሽከርካሪዎችም አስፈላጊው የምርመራ ሥራ ተካሂዶ ዕርምጃ እንደሚወሰድ ተናግረዋል፡፡ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ ባህላዊ የጨው አምራቾች ጨውን ከአዮዲን ጋር የሚያደባልቁበት መንገድ ነው፡፡ አምራቾቹ አዮዲኑን በጨው ላይ በነሲብ የሚረጩት በመሆኑ አዮዲኑ ከጨው ጋር በአግባቡ በሚፈለገው መጠን አይዳረስም፡፡‹‹በባህላዊ መንገድ የሚመረተው ጨው የማቀላቀል ሁኔታ ላይ ችግር ይከሰታል፡፡ የአዮዲን ይዘት የማነስና የመብዛት ሁኔታዎች እንዳሉ በቁጥጥር ሥራ ወቅት አይተናል፤›› ብለዋል አቶ ሳምሶን፡፡አዮዲን ለጤና አስፈላጊ የመሆኑን ያህል ከሚፈለገው (በደረጃ ከተቀመጠው) መጠን በላይ ሲገኝ ደግሞ ለሰውነት መርዛማ ሊሆን እንደሚችል ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ ዘመናዊ የገበታ ጨው ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች ሊበረታቱ እንደሚገባ ባለሙያዎቹ ይመክራሉ፡፡በባህላዊ አምራቾች በኩል የታየውን አዮዲን የመቀላቀል ድክመት ለማረም የኢትዮጵያ የምግብ፣ መድኃኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለሥልጣን ከሕፃናት መርጃ ድርጅትና ማይክሮ ኒዩትረንት ኢንሼቲቭ ተራድኦ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ባህላዊ የጨው አምራቾች ማኅበራት የአቅም ግንባታ ሥራዎች እየተሠራ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ጋር ሆነን ጥራት ያለው ምርት እንዲያመርቱ የተለያዩ የአቅም ግንባታ ሥራዎች እየሠራን ነው፡፡ ነገር ግን የአዮዲን መጠኑ ከፍና ዝቅ የማለት ሁኔታ አሁንም እያየን ነው፤›› ብለዋል፡፡በተቻለ መጠን አዮዲን የተቀላቀለበት ምርት እንዲያቀርብ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ እንደሆነ፣ ይህን ለማረጋገጥ በመግቢያና በመውጪያ ኬላዎች በመሣሪያዎች የታገዙ ጥብቅ ፍተሻ በማድረግ ላይ መሆኑን ባለሥልጣኑ ይገልጻል፡፡ የጨው ምርት ዋና ሥራ በሚካሄድበት አፍዴራ ባለሥልጣኑ ክትትል ያደርጋል ወይ የሚል ጥያቄ የቀረበላቸው አቶ ሳምሶን፣ በአፍዴራ የጨው ምርት ሒደት ላይና የማከማቸት ሒደት ላይ ቁጥጥር እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡‹‹የምርት ሒደት እናያለን፡፡ አዮዲን እንዴት እንደሚቀላቅሉ ከደኅንነት አኳያ እናያለን፡፡ ምርቱን እንዴት እንደሚያከማቹ እናያለን፡፡ ነገር ግን ቁጥጥራችን የተሟላ ነው ማለት አይቻልም፡፡ እኛ እያንዳንዱ ምርት ላይ በየጊዜው በየሰዓቱ እዚያው ቆይተን መመርመር አንችልም፡፡ ያን ማድረግ ከባድ ነው፡፡ ነገር ግን በተወሰነ ጊዜ የፍተሻ ሥራ እንሠራለን፤›› ብለዋል፡፡ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ማኅበራቱ ጥራት ያለው ምርት እንዲያመርቱ ከክልሉ መንግሥት ጋር የተለያዩ ውይይቶች እየተካሄዱ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ‹‹የእኛ ሚና አዮዲን የተቀላቀለበት ጨው አስመልክቶ በወጡ ደንቦች ላይ ማብራሪያ መስጠት፣ የተመጠነ የአዮዲን ይዘት የሌለው ጨው የሚፈጥረውን ጉዳቶች ማስረዳት፣ በምርት ሒደትና በአከመቻቸት ላይ የሚታዩ ክፍተቶች እንዲስተካከሉ ማድረግ፣ የአቅም ችግር ካለ ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር ድጋፍ መስጠት ነው፤›› ብለዋል፡፡ዘመናዊ የገበታ ጨው ማምረቻ ፋብሪካዎች መቋቋም እንደሚበረታታ የገለጹት አቶ ሳምሶን የጨው ጥራትን ከፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡ ከጥራት ባሻገር በጨው ምርትና ንግድ ዙሪያ ያለው ሥጋት ከገበያው ፍላጎት በላይ የማምረት ጉዳይ ነው፡፡ በአፍዴራ ሐይቅ ዙሪያ በርካታ የጨው አምራች ማኅበሮችንና ነጋዴዎች የሚገኙ ሲሆን፣ በሚደረገው የገበያ ሽሚያ ከአገሪቱ ዓመታዊ የጨው ፍጆታ በላይ ከሐይቁ እየተመረተ ጥቅም ላይ ሳይውል በሐይቁ አቅራቢያ ተከማችቶ እንደሚታይ ምንጮች ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡አላቂ የተፈጥሮ ሀብት በመሆኑ ጉዳዩ አሳሳቢ ነው፡፡ ፌዴራል መንግሥት ከክልሉ መንግሥት ጋር በመነጋገር ለጉዳዩ እልባት ሊያበጅለት ይገባዋል ብለዋል፡፡ በአማካይ 25 ሜትር ጥልቀት ያለው የአፍዴራ ሐይቅ በ116.8 ካሬ ኪሎ ሜትር ቦታ ላይ የተንጣለለ ነው፡፡ በሐይቁ ውስጥ የሚገኘው የጨው ክምችት 290 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ይገመታል፡፡ 
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.ethiopianreporter.com/content/%E1%8C%A5%E1%88%AB%E1%89%B1%E1%8A%95-%E1%8B%AB%E1%88%8D%E1%8C%A0%E1%89%A0%E1%89%80-%E1%8B%A8%E1%8C%A8%E1%8B%8D-%E1%88%9D%E1%88%AD%E1%89%B5-%E1%8C%88%E1%89%A0%E1%8B%AB%E1%8B%8D%E1%8A%95-%E1%88%9B%E1%8C%A5%E1%88%88%E1%89%85%E1%88%88%E1%89%81-%E1%8C%A5%E1%8B%AB%E1%89%84-%E1%8A%A0%E1%88%B5%E1%8A%90%E1%88%B5%E1%89%B7%E1%88%8D
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
98d54806b44e6029d3cadf45f04b45bf
7c06c6b4d137d5f72c4deb3e67769d30
የኢትዮ-ሩሲያ የጋራ ኮሚሽን የተሰሩ ሥራዎችን ገምግሟል፡፡
የኢትዮ-ሩሲያ የጋራ ኮሚሽን የተሰሩ ሥራዎችን ገምግሟል፡፡ባሕር ዳር፡ ታኅሣሥ 09/2013 ዓ.ም (አብመድ) የኢትዮጵያ እና የሩሲያ ኮሚሽን የኢኮኖሚ ፣ የሳይንስ ፣ የቴክኒክ እና የንግድ ትብብር ግምገማ በበይነ መረብ ተካሂዷል፡፡በጋራ የኮሚሽኑ ግምገማ ላይ በሩሲያ የኢትዮጵያ አምባሳደር አለማየሁ ተገኑ፣ የትምህርት ሚኒስትር ኢንጅነር ጌታሁን መኩሪያ(ዶ. ር) እና የሩሲያ ፌዴሬሽን የተፈጥሮ ሀብቶች እና የአካባቢ ጥበቃ ሚክትል ሚኒስትር እና የፌዴራል የማዕድን ሀብቶች ኤጀንሲ ኃላፊ ሚስተር ኤቭጂኒ ኪሴሌቭ ተሳትፈዋል፡፡በውይይቱ በኮሚሽኑ 7ኛ መደበኛ ስብሰባ ፕሮቶኮል ላይ የተላለፉ ውሳኔዎች አፈፃፀም ተገምግሟል ፡፡ግብርና፣ ኢነርጂ ፣ ጂኦሎጂ፣ ትምህርት፣ ስፔስ ሳይንስን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች የኢትዮጵያ ሩሲያ ትብብር ላይ ሀሳቦች ተለዋወጠዋል፡፡በኢትዮጵያ ንግድ ምክር ቤት እና በሩሲያ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ምክር ቤት መካከል ያለውን ትብብር ማጠናከር እንደሚገባ በውይይቱ ተመላክቷል፡፡
4ዓለም አቀፍ ዜና
https://www.amharaweb.com/%e1%8b%a8%e1%8a%a2%e1%89%b5%e1%8b%ae-%e1%88%a9%e1%88%b2%e1%8b%ab-%e1%8b%a8%e1%8c%8b%e1%88%ab-%e1%8a%ae%e1%88%9a%e1%88%bd%e1%8a%95-%e1%8b%a8%e1%89%b0%e1%88%b0%e1%88%a9-%e1%88%a5%e1%88%ab%e1%8b%8e/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
6be110a801fe912e9dae22d6ad7849d0
4e3193682e74bafd1b18b99b46cb8afd
አፍሪካዊቷ አገር ማዳጋስካር ባሳለፍነው ሚያዝያ ወር ላይ አገር በቀል የሆነ ተክልን በመጠቀም ለኮሮረናቫይረስ የሚሆን መድኃኒት ማግኘቷን ካስታወቀች በኋላ የዓለምን ትኩረት መሳብ ችላ ነበር።
ኮሮናቫይረስ፡ መድኃኒት ነው ስለሚባልለት ተክል ምን ያህል እናውቃለን?\nአርትሚዝያ የተባለውና ከአርቲ ጋር የሚመሳሰለው ተክልን በመጠቀም የተሰራው የሚጠጣ 'መድኃኒት' በአገሪቱ ፕሬዝዳንት አንድሬይ ራጆሊና ሲሞካሽ ነበር። የዓለም ጤና ድርጅት በበኩሉ በዋነኛነት የወባ በሽታን ለማከም ጥቅም ላይ ከሚውለው አርትሚዝያ ተክል የሚሰራው 'መድኃኒት' በትክክል ኮቪድ-19ኝን እንደሚያድን በሳይንሳዊ መንገድ እስካሁን አልተረጋገጠም ሲል ቆይቷል። ለመሆኑ ስለዚህ ተክል ባህሪዎችና አጠቃላይ ሁኔታ ምን ያክል እናውቃለን? አርትሚዝያ ከየት መጣ? አርትሚዝያ ዋናው መገኛው ከወደ እሲያ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ግን በመላው ዓለም በሚገኙኛ ፀሐያማና ሞቃታማ የአየር ጸባይ ባላቸው አገራት በብዛት ይታያል። በዋነኛነት ተክሉ ቻይና ውስጥ ላለፉት 2 ሺህ ዓመታት ለባህላዊ መድኃኒትነት ጥቅም ላይ ሲውል ቆይቷል። በዚህም እንደ ወባ፣ ትኩሳትና ሌሎች ህመሞችን ለማከም ያገለግል ነበር። ይህ ተክል በቻይናውያን ዘንድ 'ኪንጋኦ' ተብሎ የሚጠራ ሲሆን ከመድኃኒትነት በተጨማሪ አርትሚዝያ የአልኮል መጠጦችም ውስጥ ይጨመራል። የማዳጋስካሩ ፕሬዝዳንት ከአርቲ የተሰራውን ጭማቂ ይዘው አርትሚዝያ ኮቪድ-19ኝን ያክም ይሆን? የማዳጋስካሩ ፕሬዝዳንት አንድሬይ ራጆሊና ባሳለፍነው ሚያዝያ ወር ላይ ከአርትሚዝያ የተሰራው የሚጠጣ 'መድኃኒት' ላይ ሙከራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን በመግለጽ 'መድኃኒቱ' ኮቪድ-19ኝን ለማከም መዋል እንደሚችል ደርሰንበታል ብለዋል። በያዝነው የፈረንጆቹ መስከረም ወርም ቢሆን ይህንኑ አስተያየታቸውን ደግመውታል። ነገር ግን በይፋ ሊታይ የሚችል ማረጋገጫ እስካሁን ድረስ ማዳጋስካር ማቅረብ አልቻለችም። በተጨማሪም 'መድኃኒቱን' ለመስራት ምን አይነት ሂደት እንደተከተሉና ተክሉ ምን ያህል ጥቅም ላይ እንደዋለ የተገለጸ ነገር አለመኖሩ በርካቶች ጥርጣሬ ውስጥ እንዲገቡ አድርጓቸዋል። ማዳጋስካር ግን እነዚህን ሁሉ አስተያየቶች ወደጎን በማለት እንደውም ይህንኑ ተክል በመጠቀም ለኮቪድ-19 የሚሆን የሚዋጥ መድኃኒት ማምረት የጀመረች ሲሆን በመርፌ መልክ የሚሰጥ መድኃኒትም በማዘጋጀት ላይ ናት። ለእነዚህ 'መድኃኒቶች' ደግሞ ክሊኒካዊ ሙከራዋን አጠናክራ መቀጠሏን ማዳጋስካር አስታውቃለች። የጀርመን እና የዴንማርክ ተመራማሪዎች ደግሞ አርትሚዝያ ምን ያክል ውጤታማ ሊሆን ይችላል የሚለውን እና እውን ኮቪድ-19ኝን ማከም ይችላል የሚለውን ለማረጋገጥ ጥናት በማካሄድ ላይ ይገኛሉ። አዲስ በሰሩት ጥናትም ተክሉ ኮቪድ-19ኝን የማዳከም አቅም እንዳለው ላቦራቶሪ ውስጥ ማረጋገጥ እንደቻሉ ገልጸዋል። ምንም እንኳን የተመራማሪዎቹ ጥናት በገለልተኛ ባለሙያዎች ባይገመገምም ከተክሉ የተወሰደው ቅንጣት የቫይረሱን እንቅስቃሴ መግታትና ማቀዝቀዝና ኃይለኛቱን መቀነስ እንደሚችል ተገልጿል። ተመራማሪዎቹ በአሜሪካው ኬንተኪ ዩኒቨርሲቲ ስር ሆነው የሚሰሩ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ ክሊኒካዊ ሙከራ ለማድረግ በዝግጅት ላይ መሆናቸውም ተገልጿል። ቻይናም ብትሆን በዚሁ ተክል ላይ ምርምሮችን ማድረግ እንደጀመረች አስታውቃለች። በባህላዊ መንገድ ጥቅም ላይ ይውል የነበረውን ተክል በዘመናዊ ምርምርና እውቅት በመደገፍ የሚደረገው ለኮሮናቫይረስ ፍቱን መድኃኒት የማግኘት ሥራም ተጠናክሮ ቀጥሏል። በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ተመራማሪዎችም ቢሆኑ አርትሚዝያ ኮቪድ-19ኝን ምን ያክል ማከም ይችላል የሚለውን ማወቅ በማሰብ በላብራቶሪ ምርምር ማድረግ ከጀመረች ሰነባብታለች። የዓለም ጤና ድርጅት ግን አሁንም ቢሆን ከአርትሚዝያ ስለተሰራው 'መድኃኒት' ከማደዳስካር የተብራራ መረጃ አላገኘሁም እያለ ነው። የድርጅቱ የአፍሪካ አማካሪ ዢን ባፕቲስት ኒኬማ ለቢቢሲ እንደገለጹት ድርጅቱ በሚያገኘው መረጃ ላይ በመመስረት ክሊኒካል ሙከራዎች ላይ...
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
4941575f07ee7ff5e16cd705d9ca2ae2
20a763fc75ce0691eae3aaf5202902ea
ከቻይና የመጡ አራት ተማሪዎች ከኮሮና ቫይረስ ነፃ ስለመሆናቸው እየተጣራ ነው
በቻይና ኩቤት ግዛት ውሃን (Wuhan) ከተማ ውስጥ ከሚገኝ ዩኒቨርሲቲ ወደ ኢትዮጵያ የመጡ አራት ተማሪዎች በኖቭል ኮሮና ቫይረስ ተጠርጥረው፣ በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በሚገኘው ልየታ ማዕከል ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑ ታወቀ፡፡ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሊያ ታደሰ (ዶ/ር) እና የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኤባ አባተ (ዶ/ር) ማክሰኞ ጥር 19 ቀን 2012 ዓ.ም. በጋራ በሰጡት መግለጫ፣ ተጠርጣሪዎቹ በልየታ ማዕከል ክትትል እንዲደረግላቸው ያስፈለገው ከመካከላቸው አንደኛው ተጠርጣሪ ጉንፋን መሰል ምልክት ስለታየበት ነው፡፡ ይህም ሆኖ ግን በአሁኑ ጊዜ የአራቱም ተጠርጣሪዎቹ ጤንነት በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ፣ የላቦራቶሪ ምርመራ ተሠርቶላቸው ለጉንፋን መሰል በሽታ ኔጌቲቭ መሆናቸው እንደተረጋገጠ፣ ይህም ውጤት ለከፍተኛ ምርመራ ወደ ደቡብ አፍሪካ እንደተላከ አስረድተዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ከቻይና ጓንዡ ግዛት ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ሁለት ቻይናውያን መንገደኞች በአውሮፕላን ማረፊያ በሚገኘው የምርመራ ቦታ ለሁለት ሰዓታት ያህል አስፈላጊው ምርመራ ከተደረገላቸው በኋላ፣ ቫይረሱ ካሉበት አካባቢ ጋር ምንም ግንኙነት ስለሌላቸውና በሙቀት ልየታ መሣሪያውም የተገኘ ምልክት ስለሌለ፣ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ መደረጉ ተገልጾ፣ በመንገደኞቹ ላይ የማጣራት ሥራ የተከናወነው በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ በሰጠው ጥቆማ መሠረት መሆኑ ተመልክቷል፡፡ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከተገኘው መረጃ ለመረዳት እንደተቻለው፣ የቫይረሱ መነሻ በሆነው ውሃን ከተማ ከ300 በላይ ኢትዮጵያውያን ትምህርታቸውን ይከታተላሉ፡፡ በኮሮና ቫይረስ እንዳይጠቁ ለማድረግ በቻይና የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከፍተኛ ክትትልና ጥንቃቄ እያደረገ ነው ተብሏል፡፡እንደ ኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ኤባ (ዶ/ር) ማብራሪያ ከሆነ፣ በውሃን ከተማ የተከሰተውና ኖቭል ኮሮና ቫይረስ 2019 በሚል ስያሜ የሚጠራው ይህ በሽታ፣ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገባ አስፈላጊው የቅድመ ጥንቃቄ ሥራዎች በመካሄድ ላይ ናቸው፡፡ እስካሁንም በተካሄደው እንቅስቃሴ ስለበሽታው መረጃ መስጠትና በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ለሁሉም መንገደኞች የሰውነት ሙቀት ልየታ ሥራ መጀመር ይገኝበታል፡፡ የሙቀት ልየታ ሥራ የተጀመረው በዓለም ጤና ድርጅት ምክረ ሐሳብ መሠረት ሲሆን፣ በሙቀቱ መለየት ሥራ ላይ እስካሁን ያጋጠመ ችግር እንደሌለና መረጃ የመስጠቱም ተግባር የሚካሄደው በማንኛውም አየር መንገድ በኩል የሚጓዙ መንገደኞች ለቫይረሱ ተጋላጭ እንዳይሆኑ በማሰብ እንደሆነ፣ ከዚህም በተጨማሪ ኢንስቲትዩቱ ለክልሎችና ለባለድርሻ አካላት አስፈላጊውን የዝግጅት ሥራዎች እንዲያከናውኑ የቅድመ ዝግጅት መልዕክት እንዳሠራጩ ነው የተናገሩት፡፡ ኢትዮጵያ ከተለያዩ አገሮች ጋር የአየርና የየብስ ትራንስፖርት ትስስር የምታደርግ በመሆኑ፣ በሽታውን ሪፖርት ካደረጉት አገሮች ጋርም በአየር መንገዷ አማካይነት በርካታ በረራዎች አሏት፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቻይና ብቻ በአምስት መዳረሻዎች ማለትም ቤጂንግ፣ ሆንግ ኮንግ፣ ሻንግሃይ፣ ቸንዱና ጓንዡ በረራዎችን ያደርጋል፡፡ በዚህም የተነሳ ቫይረሱ የሚገባባቸው ዕድሎች ሰፊ እንደሆነ ነው የጠቆሙት፡፡ በሽታው ወይም ወረርሽኙ ያለባቸው ሰዎች ድንገት ቢገኙና ተጨማሪ ምርመራና መታየት የሚያስፈልጋቸው ከሆነ፣ በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ጊዜያዊ የማቆያ ማዕከል ተዘጋጅቷል፡፡ በዚህም ቦታ የሕክምና አገልግሎት የሚሰጡ ሐኪሞች እንደተመደቡ ተገልጿል፡፡ ለረዥም ጊዜ እየታዩ መታከም የሚያስፈልጋቸው በአዲስ አበባ ጥቁር አንበሳ ሪፈራል ሆስፒታልና በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ ተገቢውን አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን፣ ከኤባ (ዶ/ር) ማብራሪያ ለመረዳት ተችሏል፡፡ የኮሮና ቫይረስ ከቀላል እስከ ከባድ የመተንፈሻ አካል ሕመም የሚያስከትል የቫይረስ ዝርያ ሲሆን፣ በበሽታው የተያዙ ሰዎች ትኩሳት፣ ሳል፣ የትንፋሽ መቆራረጥና የመተንፈስ ችግር ምልክቶች ይታይባቸዋል፡፡ በሽታው በጠናባቸው ታማሚዎች ላይ ደግሞ እንደ ሳንባ ምች (ኒሞኒያ)፣ ከባድ የመተንፈሻ አካላት ሕመም የሚያሳይ ሲሆን፣ የኩላሊት ሥራን ማቆም ሊያስከትል የሚችል ነው፡፡ በሽታው ባልበሰሉ ምግቦች፣ በሳልና በማስነጠስ ወቅትና ከታማሚ ሰው ጋር በሚደረግ የቅርብ ንክኪ፣ ባልታጠበ እጅና በመሳሰሉት ይተላለፋል፡፡ በሽታውን ሪፖርት ወደ አደረጉ አገሮች የሚጓዙ መንገደኞት እጅን በሳሙናና በ መታጠብ አለባቸው፡፡ በተለይ ደግሞ ከታመሙ ሰዎች ወይም ከአካባቢያቸው ጋር ንክኪ አለመፍጠር፣ ያልበሰሉ የእንስሳት ተዋጽኦ የሆኑ ምግቦችን ከመመገብ መቆጠብ፣ በሕይወት ካሉም ሆነ ከሞቱ ከቤትና ከዱር እንስሳት ጋር ንክኪ አለማድረግ፣ ከኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት፣ ከጤና ሚኒስቴር፣ ከሕክምና ተቋማት፣ ከጉዞ ማኅበራት፣ ከአየር መንገድ፣ ከመዳረሻ ቦታዎች ወይም ከሌሎች የጤና መረጃ ምንጮች ስለበሽታው በቂ መረጃ ማግኘትና ራሳቸውን ከበሽታው መከላከል እንደሚጠበቅባቸውም ዋና ዳይሬክተሩ አሳስበዋል፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት የኖቭል ኮሮና ቫይረስ 2019 በሚል ስያሜ የሚጠራው በሽታ ከታኅሳስ 21 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ በቻይና ውሃን ከተማ መከሰቱን ማሳወቁ ይታወሳል፡፡ መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት ከሆነ በዚሁ በሽታ በቻይና 106 ሰዎች ለሕልፈተ ሕይወት ተዳርገዋል፡፡ ሌሎች 400 ያህል ሰዎች ደግሞ በበሽታው ተጠቅተው በከፋ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ፡፡ እንዲሁም ከ5,700 የሚበልጡ ሰዎች በቫይረሱ ተጠቅተዋል፡፡ በበሽታው ተይዘው የነበሩ 51 ሰዎች በተደረገላቸው ሕክምና አገግመው ተነስተዋል፡፡ የኮሮና ቫይረስ ከቻይና ውጪ ባሉ እንደ አሜሪካ፣ ታይላንድ፣ አውስትራሊያ፣ ሲንጋፖር፣ ደቡብ ኮሪያ ከቻይና በተነሱ መንገደኞች አማካይነት መሠራጨቱን ዘገባዎች ጠቁመው፣ በእነዚህም የሞተ ሰው ባይኖርም እንኳን 44 የሚደርሱ ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተጠቂ መሆናቸው ታውቋል፡፡
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.ethiopianreporter.com/article/17947
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
3c3b4c63d7096a1668060a9c5e978def
34ca8bb5724de3a60ca603a31a95d8c5
ከዛሬ 42 ዓመት በፊት የኢትዮጵያ ጦር የሶማሊያን ጦር አሽንፎ ካራማራ ላይ ስንደቅ አላማውን አውለበለበ
ከዛሬ 42 ዓመታት በፊት የካቲት 26 ቀን 1970 ዓ.ም የኢትዮጵያ ጦር ድንበር ጥሶ ወደ ኢትዮጵያ ሉዓላዊ ግዛት ገብቶ የነበረውን የሶማሊያን ሰራዊት ከኢትዮጵያ ግዛት በማስወጣት ካራማራ ተራራ ላይ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ማወለብለቡን ታሪክ ያስታውሳል፡፡ የካራማራ ድል ከደርግ ውድቀት በኋላ በመንግስት ደረጃ የማይከበር ድል ቢሆንም የቀድሞ ሰራዊት አባላትና ግለሰቦች በተነሳሽነት እያከበሩት ነው፤ በዓሉም ብሄራዊ በዓል ሆኖ በመንግስት እንዲከበር ይፈልጋሉ፡፡ ሶማሊያ በ1952 ዓ.ም ከጣሊያንና ከእንግሊዝ ቅኝ ገዢዎች ነፃነቷን ባገኘች ማግሥት የሀገሪቱ መሪዎች “ታላቋ ሶማሊያን እንገነባለን” የሚል ህልም ማለም ጀመሩ፡፡ በዚህም ምክንያት በ1953 ዓ.ም የድንበር ላይ ትንኮሳ ጀምረው በ1956 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር አብድረሺ አሊ ሸርማርኬ እንዲሁም በ1969፣ በ1972 እና በ1973 ዓ.ም ደግሞ ፕሬዝደንት ዚያድ ባሬ (ሜጀር ጀኔራል) የሶማሊያ ሰራዊት የኢትዮጵያን ድንበር ጥሶ እንዲገባና ወረራ እንዲፈፅም ሰራዊታቸውን አዘዙ፡፡ በተለያዩ ጊዜያት ደግሞ ሰርጎ ገቦችን አስታጥቆ ወደ ኢትዮጵያ ግዛት በማስገባት ፈንጅ በማፈንዳት፣ ድንገተኛና የደፈጣ ጥቃቶችን በመፈፀም እንዲሁም ባለስልጣናትንና ሰላማዊ ሰዎችን አፍኖ በመውሰድ ለኢትዮጵያ ሰላምና ልማት መሰናክል ሆነው መቆየታቸውንም በወቅቱ የነበሩ የኢትዮጵያ ወታደራዊ መሪዎች ይገልጻሉ፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ የሶማሊያ ወረራዎችና ጥቃቶች በኢትዮጵያ አሸናፊነት ቢመለሱም ዘላቂ ሰላም ሊሰፍን አለመቻሉ ይገለጻል፡፡ በተለይ የ1969 ዓ.ም የዚያድ ባሬ ወረራ የኢትዮጵያ ድንበር በምስራቅ በኩል እስከ 700 ኪሎ ሜትር እንዲሁም በደቡብ በኩል ደግሞ እስከ 300 ኪሎ ሜትር በሶማሊያ ሰራዊት እንዲደፈር፣ በርካታ ኢትዮጵያውያን እንዲሞቱና እንዲቆስሉ፣ አካል ጉዳተኛ እንዲሆኑ በአጠቃላይ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን በርካታ የሕይወትና የንብረት መስዋዕትነት እንዲከፍሉ ያደረገ ነበር፡፡ ኢትዮጵያ በወቅቱ በብዙ የውስጥ ችግሮች (የመሐል አገር የሥልጣን ሽኩቻ፣ የነጻነት ጠያቂዎች በሃገር ቤት፣ የተለመደው ድህነትና ረሀብ …) ተወጥራ ስለነበር የዚያድ ባሬ ወረራ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ሆኖባት ነበር ይላሉ የታሪክ ጸሐፊያን፡፡ ሶማሊያ ኢትዮጵያን ለመውረር ሰፊ የሰው ኃይል፣ የትጥቅ፣ የስንቅ፣ የሥነ ልቦና ዝግጅት ስታደርግ ቆይታለች፤ኢትዮጵያ ግን በውስጣዊ ችግሮች ከመወጠሯም ባሻገር በወቅቱ የነበራት የሰራዊት ቁጥርና ጥራትእንዲሁም የትጥቅ አቅርቦት እጅግ የተመናመነ እንደነበርም ነው የሚገለጸው፡፡300ሺ የሚሆን ሕዝባዊ ሰራዊት በአጭር ጊዜ ሰልጥኖ ለውጊያ የተሰለፈ ሲሆን ፤የኩባና የደቡብ የመን መንግሥታት ጦራቸውን ይዘው ከኢትዮጵያ ጎን መሰለፋቸውም ይታወሳል፡፡ ሶቭየት ኅብረት በጀኔራል ፔትሮቭ የሚመሩ ወታደራዊ አማካሪዎቿን ለኢትዮጵያ ረዳት አድርጋ ወደ ኢትዮጵያ መላኳንም መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ ከኢትዮጵያ በኩል ተሰልፈው ህይወታቸውን ላጡ ኩባውያ ወታደሮች በአዲስ አባበ መታሰቢያ ተሰርቶላቸዋል፡፡  የሶማሊያን ሰራዊት ከኢትዮጵያ ግዛት የማባረሩ ዘመቻ በሐምሌ ወር 1969 ዓ.ም ተጀመረ፡፡ ኢትዮጵያውያን በምድርና በአየር አስደናቂ ገድል ስለመፈጸማቸው የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዘዳንት ተናግረዋል፡፡ ዘመቻው እስከ የካቲት ወር 1970 ዓ.ም ቆይቶ የሶማሊያ ጦር በኢትዮጵያ ሰራዊት ተከቦ መፈናፈኛ ሲያጣ ለአሜሪካና ለሶቭየት ኅብረት የድረሱልኝ ጩኸቱን አሰማ፡፡ በወቅቱ የኢትዮጵያ ሰራዊት የሶማሊያን ጦር እያባረረ የሶማሊያን ድንበር ጥሶ ወደ ሃርጌሳ ሊገባ ይችላል የሚል ስጋት ስለነበር ከኢትዮጵያ ጎን ተሰልፈው የነበሩት የውጭ አገራት የኢትዮጵያ ጦር ወደ ሶማሊያ ግዛት እንዳይገባ ልመናና ተማፅኖ ጭምር ማቅረብ ጀመሩ፡፡ አሜሪካና ሶቭየት ኅብረትም ኢትዮጵያና ሶማሊያ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲያደርጉ፤የኢትዮጵያ ሰራዊት ወደ ሶማሊያ ድንበር ጥሶ እንዳይገባና የሶማሊያ ጦር ከኢትዮጵያ ድንበር በ24 ሰዓታት ውስጥ ጠቅልሎ እንዲወጣ ጥሪ አቀረቡ፡፡ የአሜሪካና የሶቭየት ኅብረት ጥሪ ተፈፃሚ ሆነ፡፡ የኢትዮጵያ ሰራዊትም የካቲት 26 ቀን 1970 ዓ.ም ካራማራ ተራራ ላይ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ አውለበለበ፡፡ በአሁኑ ወቅት ይህ የድል ዕለት ታዲያ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠው አይደለም የሚሉ ወቀሳዎች አሉ፡፡በተለይ ዕለቱን ሳይቀር ብዙዎች የማያስታውሱት እንደሆነና መንግስትም ሰፊ ትኩረት እየሰጠው እንዳልሆነ ይነገራል፡፡ በወቅቱ ከፍተኛ ሚና የነበራቸው የኢትዮጵያ ወታደራዊ መሪዎች ሳይቀሩ እየተዘከሩና እየታወሱ አለመሆኑም ይገለጻል፡፡ 42ኛው የካራማራ ድል በቀድሞው የሰራዊት መሪዎችና አባላት፣ የኢትዮ-ኩባ ወዳጅነት ማህበር እንዲሁም ግለሰቦች በግል ተነሳሽነት አክብረውታል፡፡
5ፖለቲካ
https://am.al-ain.com/article/42-years-ago-today-ethiopian-army-managed-to-defeat-aggressor-somalia
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
905833e5fd32ca7a29ae1087f3f8da28
fb5ab11908f55a78e6c94a5488d229f8
ግብፅ ሱዳንን ከኢትዮጵያ ለመነጠል ዲፕሎማሲያዊ ዘመቻ ጀመረች
አዲስ አበባ፤ ጥር 29/2006 (ዋኢማ) – የግብፅ መንግሥት በታላቁ የህዳሴ የኃይል ማመንጫ ግድብ በተመለከተ ሱዳን ለኢትዮጵያ የሰጠችውን ድጋፍ ለማጨናገፍ፣ ሱዳንን ከኢትዮጵያ ለመነጠል ዲፕሎማሲያዊ ዘመቻ መጀመርዋን ዘገባዎች አመለከቱ፡፡የተለያዩ የግብፅ መገናኛ ብዙኃን ሰሞኑን እንደዘገቡት፣ የግብፅ መንግሥት የተለያዩ የመንግሥት አመራሮችና ፖለቲከኞች ከሱዳን መንግሥት አቻዎቻቸው ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ጀምረዋል፡፡ለአብነት ከተጠቀሱት መካከል የግብፅ አል ዋፍድ ፓርቲ ሊቀመንበር ሳይድ አል ባዳዊ በካይሮ ከሱዳን አምባሳደር ከማል ሐሰን ዓሊ ጋር በሁለቱ አገሮች ድንበር የፀጥታ ጉዳዮች ላይ በዋነኝነት መክረዋል፡፡ በሁለቱ አገሮች ድንበር የጦር መሣሪያ ዝውውር ለማስቆም የተነጋገሩት ሁለቱ ባለሥልጣናት፣ ኢትዮጵያ እየገነባችው ባለው የታላቁ ህዳሴ የኃይል ማመንጫ ግድብና በሱዳን አቋም ላይ ተነጋግረዋል፡፡ከውይይታቸው በኋላ አል ባዳዊ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ሱዳን በታላቁ የህዳሴ ግድብ ላይ ያላት አቋም ከኢትዮጵያ ጋር ተመሳሳይ ነው መባሉ በእውነት ላይ ያልተመሠረተ ተባራሪ ወሬ ነው ብለዋል፡፡ በግድቡ ላይ ሦስቱ አገሮች ጥልቅ ውይይት አካሂደው የሁሉንም ወገን ጥያቄዎች በሚመለስ ደረጃ መግባባት ይኖርባቸዋል የሚሉት አል ባዳዊ፣ ሱዳን የግብፅን የውኃ ፍላጐት በሚነካና ብሔራዊ ደኅንነቷን በሚጐዳ ጉዳይ ላይ አሉታዊ አቋም አትይዝም ሲሉ አስታውቀዋል፡፡ የሱዳን የመገናኛ ብዙኃን ባለፈው ሰኞ ዘገባዎቻቸው የሱዳን የመከላከያ ሚኒስትር በዚህ ሳምንት ወደ ካይሮ በማቅናት ከግብፅ አቻቸው ከፊልድ ማርሻል አብዱልፋታህ አል ሲሲ ጋር በሁለቱ አገሮች የጋራ የደኅንነት ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል፡፡ በተመሳሳይ የሱዳን የመስኖ ሚኒስትር ወደ ግብፅ በዚህ ሳምንት እንደሚያመሩ የሱዳን ትሪቡን ዘገባ ያመለክታል፡፡ የግብፅ የመስኖ ሚኒስትር መሐመድ አብዱል ሙታሊብ ባለፈው ሰኞ በሰጡት መግለጫ ደግሞ ኢትዮጵያ የህዳሴውን ግድብ ግንባታ ማቆም እንደሚገባት ተናግረዋል፡፡ ‹‹ኢትዮጵያ በዓባይ ላይ የኃይል ማመንጫ ግድብ መገንባት ከፈለገች መጠኑ አነስተኛ መሆን ይገባዋል፤›› ብለዋል፡፡ እንደሳቸው አባባል የህዳሴው ግድብ ግንባታ ከታቀደው ስድስት ሺሕ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም ወደ 30 በመቶ ዝቅ ማለት አለበት፡፡ በዚህ ስሌት የታላቁ የህዳሴ ግድብ ኤሌክትሪክ የማመንጨት አቅም ወደ 1,800 ሜጋ ዋት መውረድ አለበት፡፡ይህ በእንዲህ እንዳለ 45 አባላትን የያዘ የግብፅ የዲፕሎማሲ ቡድን ከጥር 28 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ ለአምስት ቀናት በኢትዮጵያ ጉብኝት ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ግብፅ በኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ላይ ያላትን ተቃውሞ ለአፍሪካ ኅብረት እንደሚያሳውቅና የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናትንም እንደሚያነጋግር ለመረዳት ተችሏል፡፡ኢትዮጵያን የሚጐበኘው የልዑካን ቡድን በግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዲፕሎማሲ ኢንስቲትዩት ኃላፊ አምባሳደር ዓሊ ኣል ሃዲዴ የሚመራ መሆኑን በኢትዮጵያ የግብፅ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል፡፡ የልዑካን ቡድኑ ከአፍሪካ ኅብረት የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት ኃላፊና ከኅብረቱ የመሠረተ ልማትና ኢነርጂ ኮሚሽነር ጋር እንደሚመክር የተያዘው ፕሮግራም ያስረዳል፡፡ በተጨማሪም ከኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት፣ ከዓባይ ተፋሰስ ዳይሬክቶሬትና ከሕግ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ኃላፊዎች ጋር እንደሚነጋገር ታውቋል፡፡ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትሪያርክና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ጋር በመገናኘት በህዳሴው ግድብ ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡በቅርቡ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር የወሰንና ወሰን ተሻጋሪ ወንዞች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ፈቅአህመድ ነጋሽ፣ ሱዳን በህዳሴው ግድብ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር የወገነችው ለራሷ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንደሆነ አብራርተዋል፡፡ በአጋጣሚ ለድርድር በካርቱም በቆዩባቸው ጊዜያት በተለያዩ መስጊዶች ውስጥ ሳይቀር የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ሱዳንን እንዴት ሊጠቅም እንደሚችል ሲሰበክ በግርምት መታዘባቸውን በመግለጽ፣ ሱዳን ከኢትዮጵያ ጐን ለራሷ ጥቅም ስትል መቆሟን መረዳት ይቻላል ብለዋል፡፡የግብፅ ባለሥልጣናት ከኢትዮጵያ ጋር በሚደረገው ውይይትም ሆነ ድርድር ሱዳን የግብፅን ጥቅም የሚፃረር አቋም እንድትይዝ አለመፈለጋቸው ቢነገርም፣ ሱዳን እስካሁን የግድቡን ግንባታ እንደምትደግፍ ነው የሚታወቀው፡፡ ሱዳን ከኢትዮጵያ ጎን ለመሰለፍ የቻለችው በሦስቱ አገሮች ተወክሎ ሲሠራ የነበረውና ዓለም አቀፍ ባለሙያዎችን ያካተተው የኤክስፐርቶች ፓነል ሪፖርት ድምዳሜን አገናዝባ ነው፡፡ በሪፖርቱ ግድቡ በሱዳንም ሆነ በግብፅ ላይ ይህ ነው የሚባል ጉዳት እንደማያደርስ ማረጋገጡ ይታወሳል፡፡ ምንም እንኳ የግብፅ ባለሥልጣን የሱዳን አቋም ከኢትዮጵያ ጋር ወግኗል መባሉን ተባራሪ ወሬ ነው ቢሉም፣ የሱዳን ባለሥልጣናት በአደባባይ ድጋፋቸውን መግለጻቸው አይዘነጋም፡፡ (ሪፖርተር)
5ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/24864/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
84d1a64003381490b114fddb6e6e17f2
dab156d5330e184aed7b9e7c22d58b35
ሳውዲ አረብያ በሰሜን የሚያዋስኑዋት የትኞቹ ሀገራት ናቸው?
ሳዑዲ አረቢያ የሣውዲ አረቢያ ግዛት 28.7 ሚሊዬን የሚሆን ህዝብ ብዛት የያዘ ሲሆን 2ዐ ሚሊዬኑ የሣውዲ ዜጎች ሲሆኑ 8 ሚሊዬኑ የሌላ አገር ዜጎች ናቸው፡፡ ሳውዲ አረቢያ በምዕራብ ኤዥያ ከሚገኙ አገሮች በሙሉ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ ናት፡፡ የአገሪቱ መሬት ስፋት 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው፡፡ ጆርዳን እና ኢራቅ በሰሜን፣ ኩዌት ደግሞ በሰሜን ምስራቅ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት በምስራቅ ኦማን በደቡብ ምስራቅ እና በስተመጨረሻ የመን በደቡብ በኩል ሣውዲ አረቢያ ያዋስኗታል፡፡ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን የያዘ ብቸኛ አገር ሲሆን የሣውዲ መሬት ለመኖር በሚያስቸግር በረሃ የተከበበ ነው፡፡ አሁን ያለው የሣውዲ ግዛት በፊት ጊዜ አራት ቦታዎችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን የያዘነው፡፡ የሣውዲ አረቢያ ግዛት ተመሠረተው በ1932 እ.ኤ.አ. በኢብን ሣኡድ በተባለ ሰው ነው፡፡ ኢብን ሣኡድ ቀድሞ በ1894 ዓም (1902 እ.ኤ.አ.) ከብሪታንያ ግዛት ከኩወይት ዘምቶ ሪያድን ያዘ። ኢብን ሳኡድ አራት የነበሩትን የተለያዩ ግዛቶች አንድ በማድረግ ሣውዲ አረብያን ከተመሠረተ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ሀገሪቱ በዘውድ አገዛዝ እና በእስልምና ሃይማኖት መሠረት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡ እስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ ዋሀቢ እስላም የሣውዲ አረቢያ አንደኛ እምነት ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለእስልምና እምነት ትልቅ ቦታ የሚይዙት ቅዱስ ስፍራ ተብለው መካ እና መዲና በሣውዲ ስለሚገኙ ሣውዲ አረቢያ አብዛኛው ጊዜ የተቀደሱትን ሁለት መስጊዶች የያዘው መሬት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ትልቅ የነዳጅ አምራች ሀገራት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ካላቸው አገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በሀገሪቱ ባለው የተፈጥሮ ሀብት ከፍተኛ ክምችት ምክንያት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ እና የህዝብ ቁጥር እድገት ከያዙ ሀገራት ጋር ትመደባለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ G-2ዐ ተብለው ከሚታወቁት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸው የሀገራት ቡድን ውስጥ ብቸኛዋ የአረቡ ዓለም አገር ናት፡፡ ይህም ቢሆን የሣውዲ ኢኮኖሚ በአብዛኛው በአንድ ቡድን የተያዘ ነው፡፡ የሣውዲ አረብያን ፈላጭ ቆራጭ በሆነ የመንግስት ስርዓት በመመራት “ነጻነት የለም” በሚል “ነጻነት ቤት” በሚል በሚታወቀው ድርጅት ተሰይማለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ለጦር ሀይል ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ አገሮች ዝርዝር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2ዐ1ዐ-2ዐ14 በስኘሪ ተብሎ በሚታወቅ ድርጅት በተደረገው ጥናት ሣውዲ አረቢያ ዓለም ላይ ከሚገኙ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ደረጃ በማስገባት ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ሣውዲ አረቢያ በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በዓለም ላይ ከፍተኛ አስተዋጾኦ በማድረግ ላይ ያለች አገር ናት፡፡ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ አባል ናት፡፡
null
null
https://huggingface.co/datasets/israel/AmharicQA
771fffa685a9b3a9a5173b0c4ce0c141
979192fa269abf16c9550501401b48d3
ከሁለት ሳምንት በፊት በፖሊስ ቁጥጥር ሰር የዋሉት የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ፕሬዚደንት አቶ እስክንድር ነጋን በተመለከተ ፖሊስ ምርመራውን ለማጠናቀቅ የጠየቀው ተጨማሪ ቀን ፍርድ ቤት ተፈቅዶለታል።
ፍርድ ቤት ለፖሊስ በአቶ እስክንድር ላይ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ሰጠ\nዛሬ ፍርድ ቤት የቀረቡት አቶ እስክንድር ነጋ የብሔርና የሐይማኖት ግጭት እንዲፈጠር ወጣቶችን በማደራጀት ገንዘብና የተለያዩ ድጋፎችን አድርገዋል የሚል ክስ እንደቀረበባቸው ጠበቃቸው አቶ ሄኖክ አክሊሉ ለቢቢሲ ገልጸዋል። በዚህም ከፍተኛ መጠን ያለው ውድመት በንብረት ላይ እንዲሁም በሰዎች ህይወትና በአካል ላይ ጉዳት እንዲደርስ አድርገዋል የሚል ክስ በፖሊስ መቅረቡን ጠበቃው ጠቅሰዋል። ጉዳያቸው በፌደራል የመጀመሪያ አራዳ ምድብ ችሎት የሚታይ ቢሆንም ለደህንነት ሲባል ችሎቱ ልደታ በሚገኘው ፍርድ ቤት እንደተሰየመ የተናገሩት አቶ ሄኖክ፤ ፖሊስ ሃያ ምስክሮችን ማድመጡን እንዲሁም የኤሌክትሮኒክስ ማስረጃዎችን እየተመረመረ መሆኑን ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል ብለዋል። ይህንንም ተከትሎ ፖሊስ እስካሁን ያከናወናቸውን መረጃ የማሰባሰብና ምርመራ የማካሄድ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን አመልክቶ ቀሩኝ የሚላቸው ማስረጃዎችን ለማሰባሰብ ተጨማሪ ጊዜ እንዲሰጠው ፍርድ ቤቱን ጠይቋል። ከዚህ ሌላ አቶ እስክንድር ለፍርድ ቤቱ ተፈጽሞብኛል ያሉትን በደል ያቀረቡ ሲሆን፤ ይህም በቁጥጥር ሰር በዋሉበት ዕለት በፌደራል ፖሊስ አባላት ድብደባ እንደተፈጻመባቸው እራሳቸውና ጠበቃቸው ለችሎቱ አቤት ብለዋል። ፍርድ ቤቱም በቀረበው አቤቱታ መሰረት በአቶ አስክንድር ላይ ድብደባ የፈጸሙት የፌደራል ፖሊስ አባላት ላይ ምርመራ እንዲካሄድና እንዲጣራ ለፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ትዕዛዝ ሰጥቷል። ፖሊስ ምርመራውን ለማጠናቀቅ ያቀረበውን የተጨማሪ ጊዜ ጥያቄን በተመለከተ የአቶ አስክንድር ጠበቆች ፖሊስ ማስረጃ እንዳለው ለችሎቱ መግለጹንና ጠቅላይ አቃቤ ህግም ተከሳሹን ወንጀለኛ የሚያስብላቸው ማስረጃ ማግኘቱን ማመልከታቸው አስረድተዋል። ስለዚህም እነዚህ ማስረጃዎች ደግሞ በፖሊስ እጅ መኖራቸውን በመጥቀስ ተጨማሪ የጊዜ ገደብ መጠየቅ ተገቢ አይደለም ብለው ለፍርድ ቤቱ ተቃውሟቸውን አሰምተዋል። ፍርድ ቤቱ በቀረበው ተቃውሞ ላይ በሰጠው ምላሽ ምንም እንኳን ፖሊስ ማስረጃ አግኝቻለሁ ቢልም ምርመራው አልቋል ብሎ ስለማያምን ተጨማሪ 13 የምርመራ ቀናት መስጠቱ አስፈላጊ ነው በማለት ለሐምሌ 22 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። ጠበቆች ግን መረጃዎች በፖሊስ እጅ ያሉ በመሆናቸው ምርመራውን በራሱ ለማካሄድ የሚችል በመሆኑ ተጨማሪ ቀን መስጠት ተገቢ አይደለም ብለው ቢከራከሩም ፍርድ ቤቱ ፖሊስ የጠየቀው ተጨማሪ ጊዜ ፈቅዷል ሲሉ አቶ ሄኖክ ለቢቢሲ ተናግረዋል። የአቶ እስክንድር ነጋ ጠበቃ ጨምረው እንደተናገሩት ደንበኛቸው ቀደም ሲል ታስረውበት ከነበረው የማረፊያ ቦታ ከሁለት ቀናት በፊት ወደ ሌላ ቦታ መዘዋወራቸውንም ለቢቢሲ ገልጸዋል።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
82508192c80448ebe169b9f7bde789e2
3a2d62b61692c53e9a3c88c1fb906c3a
ስለአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ እስካሁን የምናውቀው
ስለአርቲስቱ ግድያ እና ከግድያው ጋር ተያይዘው ስለተከሰቱ ነገሮች የእስካሁን የሚታወቁ ጉዳዮች የሚከተሉት ናቸው። የሃጫሉ ሁንዴሳ በጥይት ተመቶ የመገደል ዜና በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ መዘዋወር የጀመረው ከምሽት 5፡30 አካባቢ ጀምሮ ነበር። በርካቶች የታዋቂውን ድምጻዊ ግድያን በማስመልከት ሃዘናቸውን በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ ሲገልጹ ነበር። ከዚያም ከእኩለ ለሊት በኋላ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው በብሔራዊው ቴሌቪዥን ላይ ቀርበው አርቲስት ሃጫሉ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ገላን ኮንዶሚኒየም ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ ከምሽቱ 3፡30 አከባቢ በጥይት ተመቶ መገደሉን አረጋገጡ። ኮሚሽነሩ ጨምረውም በግድያው ወንጀል የተጠረጠሩ የተወሰኑ ሰዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ገልጸዋል። ከእኩለ ለሊት በኋላ አዲስ አበባን ጨምሮ በበርካታ የኦሮሚያ ከተሞች ሰዎች ሃዘናቸውን ለመግለጽ ወደ መንገድ ወጡ። ሌሊቱን በፌስቡክ አማካኝነት ሲሰራጩ በነበሩ የቀጥታ ስርጭቶች፤ በርካቶች መንገድ ላይ በመውጣት ሲያለቅሱ ታይተዋል። በምሥራቅ እና ምዕራብ ኦሮሚያ ከተሞችም ንጋት ላይ መንገድ ዝግ የተደረገባቸው ከተሞች ነበሩ። የአስከሬን ሽኝት ከአዲስ አበባ የሃጫሉ ሁንዴሳ አስክሬን ወደ ትውልድ ከተማው አምቦ እንደተሸኘ የተነገረ ሲሆን። ቁጥሩ ከፍተኛ የሆነ ሕዝብ የአርቲስቱን አስከሬን ለመሸኘት ወጥቷል። አስከሬን ለመሸኘት የወጡ ሰዎች ሃዘናቸውን በተለያየ መልክ ሲገልጹ ነበር። በዚህ ጊዜ ፖሊስ አስለቃሽ ጪስ ሲተኩስ በስፍራው የነበሩ ሰዎች በፌስቡክ የቀጥታ ካሰራጩት ምስል ላይ ታይቷል። በተጨማሪም የድምጻዊውን አስክሬን ለመሸኘት ከወጡ ሰዎችም ቢቢሲ አረጋግጧል። የአስከሬን አቀባበል በአምቦ ዛሬ ንጋት ላይ የአርቲስት ሃጫሉ አስከሬን በበርካታ አድናቂዎቹ ታጅቦ ወደ አምቦ ሲያመራ የነበረ ቢሆንም ቀብሩ መፈፀም ያለበት አዲስ አበባ ነው የሚሉ ተቃውሞዎች መሰማታቸውን ተከትሎ አስክሬኑ ወደ አዲስ አበባ እንዲመለስ ተደርጎ ነበር። ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰም በኋላ አስክሬኑ ስታዲየም አቅራቢያ በሚገኘው የኦሮሞ ባህል ማዕከል እንዲያረፍ ተደርጎ ቆይቷል። ከዚያም አስክሬኑ ወደ አምቦ በሄሊኮፕተር ተጭኖ ወደ ከአምቦ ከተማ በቅርብ ርቀት ወደ ሚገኘው ሆሚቾ አሙኔሽን ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ መወሰዱ ተነግሯል። ማለዳ አምቦ ቁጥሩ እጅግ ከፍተኛ የሆነ ሕዝብ አስክሬኑን ለመቀበል በመጠባበቅ ላይ ነበር። “የከተማው ሕዝብ ወደ ዋና መንገድ ወጥቷል። ከገጠርም በጣም ብዙ ሰዎች በፈረስ እየመጡ ነው” ሲሉ አንድ የከተማው ነዋሪ ለቢቢሲ ተናግረዋል። የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎችም በነዳጅ ማደያ እና ባንክ ቤቶች በመሳሰሉት ተቋማት አካባቢ እንጂ በብዛት በከተማዋ ውስጥ እንደማይታዩ አኚሁ ነዋሪ ጨምረው ተናግረው ነበር። የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ የቀብር ስነስርዓት መቼ እንደሚፈፀም ከቤተሰቡም ሆነ ከመንግሥት አካል እስካሁን ምንም የተባለ ነገር የለም። ሃጫሉ ከዚህ ቀደም ምን ብሎ ነበር? ሃጫሉ ሁንዴሳ ከዚህ ቀደም ቢቢሲን ጨምሮ ከሌሎች መገናኛ ብዙሃን ጋር ባደረገው ቃለ መጠይቅ ተደጋጋሚ የግድያ ዛቻዎች ይደርሰው እንደነበረ ተናግሯል። ከሳምንት በፊት ሰኔ 15/2012 ዓ.ም በኦሮሚያ ሚዲያ ኔትዎርክ ላይ በተላለፈው ቃለ መጠይቁ፤ ሃጫሉ “እየታገልኩ እኮ ነው የምኖረው” በማለት ተደጋጋሚ የግድያ ዛቻ እንደሚደርስበት ተናግሯል። የሃጫሉን ግድያ ተከትሎ ማን ምን አለ? ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ በድምጻዊው ሞት የተሰማቸውን ሀዘን "ውድ ህይወት አጥተናል" በማለት "የዚህ ድንቅና አንፀባራቂ ወጣት አርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ህይወት መቀጠፍ ከተሰማ ጀምሮ በከባድ ሃዘን ውስጥ ለምንገኝ ሁሉ...
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
607d3620e4ec91a905c23dbefa26d01f
2ac0d6046042faf6d243e67b79673bb2
የኢትዮጵያ መርከቦች ለኢትዮጵያ ነዳጅ እየጫኑ አለመሆኑ ተገለጸ፡፡
ባሕር ዳር፡ መስከረም 10/2012 ዓ.ም (አብመድ) የኢትዮጵያ ባሕር ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ፤ ነገር ግን ለሜቴክ በዱቤ የሰጠው የ2 ቢሊዮን ብር ዱቤ አገልግሎት እንዳልተከፈለው ገልጿል፡፡የኢትዮጵያ ባሕር ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ባለፈው የበጀት ዓመት 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ትርፍ ማግኘቱን ገለጸ፡፡ የአገልግሎቱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሮባ መገርሳ እንዳስታወቁት ባለፈው ዓመት አማካይ የኮንቲነር የወደብ ቆይታ 6 ቀን ከ6 ሰዓት ነበር፡፡
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.amharaweb.com/%e1%8b%a8%e1%8a%a2%e1%89%b5%e1%8b%ae%e1%8c%b5%e1%8b%ab-%e1%88%98%e1%88%ad%e1%8a%a8%e1%89%a6%e1%89%bd-%e1%88%88%e1%8a%a2%e1%89%b5%e1%8b%ae%e1%8c%b5%e1%8b%ab-%e1%8a%90%e1%8b%b3%e1%8c%85-%e1%8a%a5/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
5687fc98d278c3b98a63b61af7c52665
5334dfc08ca4088747be23a3e55e9b91
ኦሮማይ
ኦሮማይ በጋዜጠኛና ደራሲ በዓሉ ግርማ በ1975 ዓ.ም ለኅትመት የበቃ ድርሰት ነው። የመጽሐፉ መቼት በጊዜው የኢትዮጲያ ኣካል በነበረው በኤርትራ በረሐዎች ይካሄድ በነበረውቀይ ኮከብ ዘመቻ ዙርያ የሚያጠነጥን ነው። ምስጋና በዓሉ ግርማ የኢትዮጵያ ሥነ-ጽሁፍ ደርግ
null
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
d2037e648dbb4a0e6e45c50f4231d54d
3a2d5a12613dfd09bfd1fb00db26eea8
በከፍተኛ ሊግ የመክፈቻ ጨዋታ ለገጣፎ እና ገላን አቻ ተለያይተዋል
የ2013 የውድድር ዘመን የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ዛሬ ባቱ ላይ 4:00 በተደረገ የምድብ ሀ ጨዋታ ሲጀመር ለገጣፎ ለገዳዲ ከ ገላን ከተማ ያለ ጎል ተለያይተዋል።የእግርኳስ ፌዴሬሽኑ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት የሆኑት አቶ ኢብራሂም መሐመድ እና ኢንጅነር ኤሌሮ አፒዮ በክብር እንግድነት በመገኘት ያስጀመሩት ጨዋታ ቀዝቀዝ ባለ ፉክክር፣ ጥቂት የግብ ዕድል እና ጥሩ ዳኝነት ታጅቦ ተከናውኗል።የመጀመርያው አርባ አምስት አጋማሽ ደቂቃ ድረስ ይህ ነው የሚባል የግብ ሙከራ ያላሳየው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ እንቅስቃሴ በሜዳው አጋማሽ ላይ ተገድቦ የቆየ ሲሆን በ26ኛው ደቂቃ ላይ ለገጣፎዎች በቅጣት ምት እና በ28ኛው ደቂቃ ዘካርያስ ከበደ አሻምቶት አንዋር አብዱልቃድር በሞከረው ኳስ ለግብ ቀርበው ነበር። በገላኖች በኩል በ30ኛው ደቂቃ ቢንያም ካሳሁን በግል ጥረቱ ከመስመር እየገፋ ሄዶ የሞከረው ሙከራ ተጠቃሽ ነበር።ጨዋታው ቀስ በቀስ እየተሟሟቀ ቀጥሎ የተሻለ ፉክክር አስተናግዷል። በ32ኛው ደቂቃ የገላን ተከላካዮች የሰሩትን የቅብብል ስህተት ተጠቅሞ ጥሩ ኳስ ያገኘው አንዋር አክርሮ መትቶ ግብ ለማስቆጠር ቢጥርም ኳስ እና መረብን ማገናኘት አልቻለም። አብዱለጢፍ ሙራድ እና ዝናቡ ባፋ በ43ኛው እና በ45ኛው ደቂቃ ከተመሳሳይ ቦታ ለማስቆጠር ሞክረው መክኖባቸዋል። የመጀመሪያው አጋማሽ ተጠናቆ በጭማሪው ሰዓት ገላኖች ጥሩ እድል አግኝተው አብዱልለጢፍ ሙራድ ከመስመር አፍትልኮ ወደ ጎል በሚያመራበት ወቅት የለገጣፎ ግብ ጠባቂ አብርሀም ከተማ በመውጣት በሰራው ጥፋት በእለቱ ዳኛ አሸናፊ በላይ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተወግዶል። ይህም የውድድሩ የመጀመርያ ቀይ ካርድ ሆኖ ተመዝግቧል።ከመጀመሪያው አጋማሽ በተቃራኒ መልኩ የጀመረው ሁለተኛው አጋማሽ ሙከራ ለማስተናገድ 3 ደቂቃዎች ብቻ ፈጅተውበታል። በ48ኛው ደቂቃ ተደራጅተው ወደ ገላኖች የግብ ክልል የደረሱት ጣፎዎች በፋሲል አስማማው አማካኝነት ግብ ቢስቆጥሩም ከጨዋታ ውጭ ተብሎባቸዋል። ለገጣፎዎች ምንም እንኳን ወደ ራሳቸው የግብ ክልል ተጠግተው ቢከላከሉም በአንድ አንድ አጋጣሚዎች ፍጥነት የታከለበት ሽግግር በማድረግ ግብ ለማስቆጠር ጥረዋል። በዚህም በ63ኛው ደቂቃ ገላኖች ትተውት የሄዱትን ክፍተት በመጠቀም በመልሶ ማጥቃት ጥሩ ሙከራ ሳዲቅ ተማም እና ፋሲል አስማማው አድርገው መክኖባቸዋል።በተሻለ ኳሱን ተቆጣጥረው ለመጫወት ጥረት ያደረጉት ገላኖች በበኩላቸው በ75፣ 81 እና 87ኛው ደቂቃ ከመስመር ባሻሟቸው ኳሶች ጥሩ ጥሩ እድል ቢፈጥሩም ግብ ሳያስቆጥሩ ቀርተዋል። የ2013 የመጀመሪያ ጨዋታም በዚህ መልኩ ያለ ግብ ተጠናቋል።
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/63013
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
232d5b6b67bcc30f7d2bf45eb6d38ddb
be740d830be0cc898f8a532872b30716
ኢራን የቀድሞ የመከላከያ ሚንስቴር ሠራተኛዋን ለአሜሪካ ምረጃ አቀብሏል በሚል ክስ በሞት መቅጣቷን አስታወቀች።
ኢራን ለሲአይኤ መረጃ አቀብሏል ያለችውን ግለሰብ በሞት ቀጣች\nኢራን በመካከለኛው ምሥራቅ ካሉ አገራት ግዙፍ የሚሳኤል ክምችት ያለባት አገር ናት። ሬዛ አስጋሪ የተባለው ግለሰብ የሞት ብይኑ የተፈጸመበት ባሳለፍነው ሳምንት መሆኑን የፍርድ ቤት ቃል አቀባይ ጎላምሁሴን ኢሰማኢሊ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል። ቃል አቀባዩ እንዳሉ የሞት ብይኑ የተፈጸመበት ሬዛ አስጋሪ የኢራንን የሚሳኤል ፕሮግራም ዝርዝር መረጃ ለአሜሪካ የስላል ተቋም (ሲአይኤ) እአአ 2016 ላይ አሳልፎ ሰጥቷል ተብሎ ነው። አስጋሪ መረጃውን ሰጠ የተባለው ከኢራን መከላከያ ሚንስቴር ሠራተኝነት በጡረታ ከተገለለ በኋላ ነው። ቃል አባዩ አስጋሪ መቼ በቁጥጥር ሥር እንደዋለ፣ የፍርድ ሂደቱ መቼ እንደተከናወነና ብይኑ ተግባራዊ የሆነው መቼ እንደሆነ ዝርዝሩን ከመናገር ተቆጥበዋል። ቃል አቀባዩ ጎላምሁሴን ኢሰማኢሊ የሞት ቅጣቱ ስለተፈጸመበት ግለሰብ የተናገሩት ስለ ሌላ ለውጪ ኃይሎች ሰልሏል ተብሎ ስለተከሰሰ ተጠርጣሪ በገለጹበት ወቅት ነበር። ቃል አቀባዩ እንደተናገሩት መሐሙድ ሙሳቪ-ማጃድ የተባለ ሌላኛው ግለሰብ ለሲአይኤ እና ለእስራኤል መንግሥት የስለላ ድርጅት ሞሳድ መረጃ አሳልፎ ሰጥቷል ተብሎ የሞት ፍርድ እንደተላለፈበት ተናግረዋል። መሐሙድ ሙሳቪ-ማጃድ ለሲአይኤ እና ሞሳድ አሳልፎ የሰጠው መረጃ በሶሪያ የኢራን ጦር እንቅስቃሴን በተመለከተ ነው ተብሏል። የአሜሪካ ባለስልጣን አስጋሪ በኢራን መንግሥት የሞት ፍርድ ተፈጻሚ እንዲሆንበት መደረጉን ተከትሎ ያሉት ምንም ነገር የለም። ከአንድ ዓመት በፊት የኢራን የደኅንነት ሚንስቴር የአገሪቱን የኒውክሌር እና ሌሎች ወታደራዊ ተቋማት ዝርዝር መረጃ ለሲአይኤ አሳልፈው ሰጥተዋል ያላቸውን 17 ሰዎች በቁጥጥር ሥር አውሎ እንደነበረ ማሳወቁ ይታወሳል። በወቅቱ ሚንሰቴር መስሪያ ቤቱ በቁጥጥር ሥር ከዋሉት መካከል በስም ያልጠቀሳቸው የሞት ፍርድ የተላለፈባቸው እንዳሉ አሳውቆ ነበር። በተመሳሳይ ከአንድ ወር በፊት የቀድሞ የኢራን መከላከያ ሚንስቴር መስሪያ ቤት ሠራተኛ የነበረው ጃላል ሃጂዛቫር ለሲአይኤ ሰልሏ ተብሎ በሞት ተቀጥቷል። በወቅቱ ሃጂዛቫር በክፍያ ለሲአይኤ ሲሰልል መቆየቱን አምኗል ተብሎ ነበር።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
266c943e9fe5a1f4ddf8fb54063dafb2
9f284d3603bb036470af5fbb22274991
እውን ክሬምሊን "ዳግም አሜሪካን ታላቅ ማድረግ" የሚለው የትራምፕ ሕልም ነው የሚስማማት? ለዚህም ተግታ ትሰራለች?
ሩሲያና ቻይና በአሜሪካ ምርጫ ማን እንዲያሸንፍ ነው የሚፈልጉት?\nእውን ቻይና ለባይደን ያላሰለሰ ድጋፍ እየሰጠች ነው? ትራምፕ አንገት ላይ ገመድ እያስገባች ነው? በመጪው የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ላይ ሦስት አገሮች ስለአሜሪካ ከአሜሪካኖች በላይ ሊጨነቁ ይችላሉ። ቻይና፣ ሩሲያና ኢራን። እነዚህ አገሮች የሚፈልጉት ሰው እንዲመረጥ በይፋም በህቡዕም፣ በቀጥታም በእጅ አዙርም የሚችሉትን ሀሉ ከማድረግ አይቆጠቡም። ምክንያቱም በአሜሪካ ወደ ዋይት ሐውስ የሚዘልቀው ሰው ጎሮሯቸውን ሊከፍተው ወይም ሊዘጋው ስለሚችል ነው ወራት ብቻ በቀሩት የአሜሪካ ምርጫ የትኛው አገር ማን እንዲመረጥ ይሻል? ለምን? የሚለውን በአጭሩ እንቃኝ። ለጊዜው ኢራንን እናቆያት። ሩሲያ ሩሲያ በባለፈው የ2016ቱ የአሜሪካ ምርጫ ዶልታለች፣ ፈትፍታለች የሚለው የአደባባይ ምስጢር ነው። ትራምፕና ወዳጆቻቸው ቢክዱትም። ፍርድ ቤት በቂ መረጃ አላገኘሁም ቢልም። የአሜሪካ ደኅንነት መሥሪያ ቤት እንደሚያምነው ሩሲያ ዶናልድ ትራምፕን የዛሬ 4 ዓመት ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት እጃቸውን ይዛ አስገብታቸዋለች። የትራምፕ ሰዎችና የሩስያ ሰዎች አብረው ሻይ ቡና ሳይሉ አይቀርም። የሳይበር ጥቃት በማድረግም ሒላሪን አሳጥተዋታል። ዲሞክራቶችን አሽመድምደዋል። የአገሬውን መራጭ ወደ ትራምፕ እንዲያጋድል በበይነ መረብ ጠልፈው ጥለውታል። አባብለውታል። ሩሲያ ይህን ለማድረግ በቂ አቅም ፈጥራለች። ባለፈው ወር ሪፐብሊካኖች የመሩት የሴኔት ጉባኤ ሩሲያ ትራምፕ እንዲመረጡ ስለመፈለጓ ተጨማሪ መረጃን ሰጥቶ ነበር። ሆኖም ይህ ወንጀል ሆኖ ትራምፕን በሕግ የመጠየቁን ነገር አልገፋበትም። በ2020 ሒላሪ በባይደን ተተክተዋል። ሩሲያም ሒላሪን እንዳበሻቀጠች ባይደንን ነክሳ ይዛለች። የአሜሪካ የብሔራዊ ደኅንነትና ስለላ ክፍል ኃላፊ ዊሊያም ኢናቪና እንደሚሉት ምክትር ፕሬዝዳንት ባይደንን ለማደናቀፍ ሩሲያ ሁሉን አቀፍ ዘመቻ ከፍታለች። በሰሞኑ መደማመጥ በራቀውና የሰፈር ጎረቤታሞች ብሽሽቅ ይመስል በነበረው የቀጥታ የቴሌቪዥን ክርክር ባይደን ዶናልድ ትራምፕን "የፑቲን አሻንጉሊት" ሲሉ የገለጽዋቸው ወደው አይደለም። ትራምፕ ለፑቲን በይፋም በጓዳም አድናቆት አላቸው። ምናልባትም ከፖለቲከኛ እንደ ፑቲን የሚያስቀናቸው ሰው የለ ይሆናል። የኤፍቢአይ ዳይሬክተር ክሮስቶፎር ሬይ እንደሚያምኑት ሩሲያ መቼም ቢሆን በአሜሪካ ምርጫ ውስጥ መፈትፈቷን ትታ አታውቅም። ከሁለት ዓመት በፊት በነበረው የሕዝብ ተወካዮች ምርጫ ሳይቀር ሩሲያ እጇን ማስገባቷን በመጥቀስ ክርስቶፎር ሬይ ክስተቱን "ለ2020 ተውኔት ቃለ ተውኔት ልምምድ ላይ ያለች ትመስል ነበር" ብለዋል። ሩሲያ በበኩሏ እኔ በውጭ አገር ምርጫ ምን ጥልቅ አደረገኝ ስትል ድርጊቱን እንደካደች ነው። በዚህ የፈረንጆች ዓመት መጀመርያ የክሬምሊን ቃለ አቀባይ አሜሪካኖች የሚያቀርቡትን ክስ "ደንብረው የሚዘላብዱት ነገር ነው" ሲሉ ተሳልቀውበታል። ሩሲያ ዶናልድ ትራምፕ ለ2ኛ ዙር ዋይት ሐውስ ቢቆዩላት ምርጫዋ ሲሆን ከዚህ በላይ የምትፈልገው ግን በአሜሪካ ፖለቲካ ውስጥ ትርምስን መፍጠር ነው ይላሉ የደኅንነት ጉዳይ አጥኚዎች። ለምሳሌ የአውሮፓ ኅብረት አንድ ሰነድ እንደሚያስረዳው ከሆነ ሩሲያ ከአብዛኛዎቹ ኮሮናቫይረስን ከሚመለከቱ ሐሳዊ ዜናዎች ጀርባ ያለች አገር ናት። ይህን የምታደርገውም ትርምሱ ፖለቲካዊ ትርፍ ስለሚያስገኝላት ነው። ጆ ባይደን ምን አሉ? ባይደን ሩሲያን ጠንከር ባለ ቃል አስጠንቅቀዋል። ሩሲያ በሉአላዊት ልዕለ ኃያል አሜሪካ ፖለቲካ ውስጥ እጇን አስገብታ መፈትፈቷን በቶሎ ካልገታች የምትከፍለው ዋጋ ይኖራል ብለዋል። የፑቲን አሻንጉሊት የሚሏቸው ዶናልድ ትራምፕም ከጠላት አገር ጋር መሞዳሞዳቸውን እንዲተዉ አሳስበዋል። ባይደን በሩሲያ ላይ ያላቸው አቋም ይህን...
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
8ee3083a2f191e3ba4ad4f5dfaa3bef7
cc708cf4b6b882adc4feca92ceeb7ea7
ሪፖርት | ሲዳማ ቡና ነጥቡን ከመሪው ጋር አስተካክሏል
2ኛ ሳምንት ላይ መካሄድ ሲገባው ሲዳማ ቡና ለፌዴሬሽኑ ባቀረበው ጥያቄ መሰረት በተስተካካይ ጨዋታ ዛሬ በአዲስ አበባ ስቴዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሲዳማ ቡና ወላይታ ድቻን 2-1 በመርታት በአሸናፊነት ጉዞው ቀጥሏል።በባዬ ገዛኸኝ የመጨረሻ ደቂቃ ጎል ከአዳማ ከተማ ጋር ነጥብ ተጋርቶ ከተመለሰው የመጀመርያ አሰላለፉ የሁለት ተጫዋቾች ለውጥ ያደረገው ወላይታ ድቻ በረከት ወልዴን (ጉዳት) በሐብታለም ታፈሰ፣ ዘላለም ኢያሱን ተቀይሮ ከገባ በኋላ ጎል በማስቆጠር እና ጥሩ መንቀሳቀስ የቻለው ባዬ ገዛኸኝን በመተካት ወደ ሜዳ ሲገባ  በአንፃሩ ሲዳማ ቡና ደደቢትን 3-0 ከረታበት ጨዋታ የሦስት ተጫዋቾች ለውጥ አድርጓል። ግብጠባቂው ፍቅሩ ወዴሳን መሳይ አያኖ፣ ግሩም አሰፋን በዮናታ ፍስሃ፣ ዳዊት ተፈራን በዳግም ንጉሴ በመተካት ወደ ሜዳ ገብቷል።በጥሩ ፉክክር ኳስን መሰረት ባደረገ አጨዋወት ተጋግሎ የጀመረው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ሲዳማ ቡና በመሐል ሜዳ ክፍል ብልጫ በመውሰደ ኳሱን በሚገባ ተቆጣጥረው ወደ ፊት የሚሄዱበት መንገድ መልካም የሚባል ቢሆንም ግልፅ የሆነ የግብ ዕድል መፍጠር አልቻሉም ። ወላይታ ድቻ በጥንቃቄ በመከላከል ከራሳቸው ሜዳ ክፍል ማለፍ ሳይችሉ ኳሱን አደራጅተው ከመሄድ ይልቅ ሲዳማዎች የሚሰሩትን ስህተት በመጠቀም የግብ ዕድል ለመፍጠር ሲንቀሳቀሱ ታይቷል።12ኛው ደቂቃ በኋላ ሙሉ ለሙሉ ብልጫ በመውሰድ የተጫኑት ሲዳማዎች የመጀመርያ ሙከራዎችን ማድረግ የቻሉት በ14ኛው ደቂቃ አዲስ ግደይ ከመሀል ሜዳ ኳሱን እየገፋ በመሄድ ከሳጥን ውጭ አክርሮ የመታውን የድቻው ግብጠባቂው መኮንን በጥሩ ሁኔታ ያዳነበት የሲዳማዎች የመጀመርያ ጠንካራ ሙከራ ነበር። በተደጋጋሚ ሀብታሙ ገዛኸኝ ከቀኝም መስመር ወደ ፊት የሚሄድባቸው መንገዶች እና የሚያሻግራቸው ኳሶች በሲዳማ ቡና አጥቂዎች በኩል የሚቀበል ጠፍቶ ኳሶቹ ሲባክኑ ተስተውሏል።20ኛው ደቂቃ ሐብታሙ ገዛኸኝ ከቀኝ መስመር ወደ ድቻ ሳጥን ውስጥ በመግባት የሚያሻግረው ኳስ ተቀባይ አግኝቶ ወንድሜነህ ዓይናለም አግኝቶ አገባው ሲባል ውብሸት በፍጥነት ደርሶ እንደምንም ተደርቦ ያወጣበት ሌላ ጎል መሆን የሚችል ግልፅ  አጋጣሚ ነበር። ወላይታ ድቻዎች ከቆሙ ኳሶች የግብ ዕድል ለመፍጠር ከሚደረጉ ጥረቶች ውጭ ወጥነት የሌላቸው የሚቆራረጡ ኳሶች የበዙበት እና አልፎ አልፎ  በመልሶ ማጥቃት በፍጥነት አደጋ ለመፍጠር ቢሞክሩም የሚጣሉት ኳሶች ያልተመጠኑ በመሆናቸው በቀላሉ ይባክኑ ነበር። በ28ኛው ደቂቃ ፈቱዲን ጀማል ኳሱን በመሸፈን በመልስምት ጨዋታውን ለማስጀመር ሲሞክር ቸርነት ጉጉሳ ከጀርባው ደርሶ የነጠቀውን ኳስ አምስት ከሃምሳ ውስጥ ነፃ አቋቋም ላይ ለሚገኘው አጥቂው ባዬ ገዛኸኝ ቢሰጠውም በማይታመን መልኩ የሲዳማው ግብጠባቂው መሰይ አያኖ ያደናበት በድቻ በኩል በመጀመርያው አጋማሽ ያገኙት ግልፅ የሚያስቆጭ የጎል አጋጣሚ ነበር።ሲዳማዎች በተደጋጋሚ ሲጠቀሙበት በነበረው በድቻ ቀኝ መስመር 35ኛው ደቂቃ ዮናታን ፍስሃ ወደፊት የተጣለለትን ኳስ ሰብሮ በመግባት ያሻገረውን አዲስ ግደይ በግንባሩ ኳሱን ከመሬት ጋር አጋጭቶ ቢመታውም ለጥቂት የግቡን ቋሚ ታኮ ወቶበታል። የግብ ሙከራ በማድረግ የተሻሉ የነበሩት ሲዳማዎች ቢሆኑም በመልሶ ማጥቃት በድቻዎች የሚወሰድባቸው ጥቃቶች የተከላካይ ክፍላቸውን ሲረብሸው ታይቷል።              ውጥረት የተሞላበት ጠንካራ ፉክክር በታየበት ሁለተኛ አጋማሽ ድቻዎች በተሻለ መንቀሳቀስ የቻሉ ሲሆን 53ኛው ደቂቃ ባዬ ገዛኸኝ ላይ መሳይ አያኖ ፍፁም ቅጣት ምት ክልል ውስጥ ጥፋት ቢሰራበትም የዕለቱ ዳኛ በዝምታ ማለፋቸው የድቻ ተጫዋቾች ተቃውሞ እንዲያነሱ አድርጓቸዋል። ከእረፍት መልስ ቀዝቃዛ አጀማመር ያደረጉ ቢመስሉም ሲዳማዎች በ57ኛው ደቂቃ በአንድ ሁለት ቅብብል አዲስ ግደይ ለመሐመድ ናስር ለማቀበል አስቦ በድቻ ተከላካዮች ተደርቦ ሲመለሰ ልማደኛው ወንድሜነህ ዓይናለም ከሳጥን ውጭ አክርሮ በመምታ ግሩም ጎል አስቆጥሮ ሲዳማዎችን መሪ ማድረግ ችሏል። ከጎሉ መቆጠር ሁለት ደቂቃ በኋላ የጨዋታውን መልክ የቀየረ ክስተት ተፈፅሟል። መሐመድ ናስር ከኃይማኖት ወርቁ ጋር በፈጠሩት ሰጣ ገባ በቀጥታ ቀይ ካርድ ከሜዳ ተወግዷል። የቁጥር ብልጫውን ተጠቅመው ድቻዎች ጫና ይፈጥራሉ ቢባልም እምብዛም ለሲዳማ ፈተና መሆን አልቻሉም። 64ኛው ደቂቃ ሐብታሙ ገዛኸኝ ከተከላካዩ ተክሉ የነጠቀውን ኳስ  የሚቀበለው አጥቶ ወደ ጎል ሞክሮ ግብጠባቂው መኳንንት በቀላሉ የያዘበትም በሲዳማ በኩል የሚጠቀስ ነበር። ድቻዎች በረጃም ኳሶች ወደ ጎል ለመድረስ የሚያደርጉት ጥረት ተሳክቶላቸው 75ኛው ደቂቃ ግብጠባቂው መሳይ አያኖ ፍፁም ቅጣት ምት ክልል ውስጥ የሰራውን ጥፋት ተከትሎ ባዬ ገዛኸኝ ወደ ጎልነት ቀይሮ ድቻዎችን አቻ ማድረግ ችሏል።ጨዋታው በአስገራሚ እና እልህ አስጨራሽ እንቅስቃሴ ቀጥሎ በ79ኛው ደቂቃ ከሳጥን ውጭ ራቅ ብሎ የተሰጠውን ቅጣት ምት ወንድሜነህ ዓይናለም የመታውን አዲስ ግደይ ከተከላካዮች መሐል በመውጣት በግንባሩ ጨርፎ ጎል በማስቆጠር ሲዳማዎችን በድጋሚ መሪ መድረግ ችሏል።በመጨረሻዎቹ 10 ደቂቃዎች ሲዳማዎች ተከላካይ በማስገባት እና አጥቂ በመቀነስ ውጤቱን ለማስጠበቅ ወደ ኋላ አፈግፍገው ሲካላከሉ ድቻዎች ተከላካይ በመቀነስ እና የአጥቂ ቁጥራቸውን በመጨመር ጫና ፈጥረው ተጫውተዋል። በተለይ 87ኛው ደቂቃ ከማዕዘን ምት የተሻማውን ቸርነት ጉግሳ መቶት ተከላካዮች ተረባርበው ያወጡት እና 89ኛው ደቂቃ ዘላለም ኢያሱ ግልፅ የማግባት አጋጣሚ አግኝቶ ኳሱን ሳያጠብቀው መትቶ መሳይ በቀላሉ የያዘበት እቻዎችን አቻ መድረግ የሚችሉ አጋጣሚዎች ነበሩ። ጨዋታውም ተጨማሪ ጎል ሳይቆጠርበት በሲዳማ ቡና 2-1 አሸናፊነት ሊጠናቀቅ ችሏል።
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/44491
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
111678fc0d4b4cb843f2e0ce526ffbdb
15118091cc53a7307f48f5bb5d8345f2
በቺካጎ ከተቃውሞ ጋር በተያያዘ ከዚህ በፊት ባልታየ ሁኔታ በርካታ ሰዎች ሞቱ
በዕለተ እሁድ ግንቦት 23 ከጆርጅ ፍሎይድ ሞት ጋር በተያያዘ በተደረገ የተቃውሞ ሰልፍ 18 ሰዎች ተገድለዋል። ግንቦት 22 እና 23 በተደረጉ ሰልፎች 85 ሰዎች በጥይት የተመቱ ሲሆን 24 ሰዎች ደግሞ መገደላቸውን ከዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቺካጎ የወንጀል ምርመራ ክፍል የተገኘው መረጃ ጠቁሟል። መረጃው እንደሚያሳያው አብዛኛዎቹ ተጎጂዎች ጥቁር አሜሪካውያን ናቸው። ቺካጎ ሰን-ታይም ጋዜጣ ይዞት የወጣው ዘገባ እንደጠቆመው ከተገደሉት እና ጉዳት ከደረሰባቸው 24 ሰዎች መካከል ተማሪዎች፣ ወላጆች እና ሠራተኞች ይገኙበታል። ከቺካጎ ዩኒቨርሲቲ የወንጀል ምርመራ ክፍል የተገኘው መረጃ ከ1961 (እአአ) ጀምሮ ያለውን ታሪክ የያዘ እንደሆነ በማስታወስ "እንዲህ አይነት ነገር በፍጹም ተመልክተን አናውቅም" ሲሉ ተመራማሪው ማክስ ካፑስቲን ለቺካኮ ሰን-ታይመስ ተናግረዋል። ከዚህ ቀደም በቺካጎ ከተማ ታሪክ በአንድ ቀን ውስጥ በርካታ ሰዎች የሞቱት 13 ሰዎች ሲሆኑ ዕለቱም ሐምሰሌ 23/1983 ዓ.ም. ነበር። የቺካጎ ከንቲባ ሎሪ ላይትፉት እንዳሉት 18 ሰዎች ተገድለዋል በተባለበት ቀን ለፖሊስ የተደረገው የድረሱልኝ ጥሪ ከ65 ሺህ በላይ ነበር። ይህም በአማካይ ለከተማው ፖሊስ ከሚደርሰው ጥሪ በ50 ሺህ የሚበልጥ ነው። የቺካጎ ከተማ ፖሊስ ለሰን-ታይምስ እንደተናገረው፤ ግንቦት 22 እና 23 ለፖሊስ በርካታ ጥሪዎች መደረጋቸውን በማስታወስ፤ በዜጎች ላይ የተፈጸሙ ጥቃቶችን እና መነሻዎችን እየመረመረ መሆኑን አስታውቋል። "በአመጹ ህይወታቸውን ላጡ እና ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች ፍትህ ለመስጠት እንሰራለን" ብሏል የከተማዋ ፖሊስ። ቺካጎ ከዚህ ቀደምም ቢሆን ይመዘግብባት የነበረው የግድያ ወንጀል ከፍ ያለ ነው። ቺካጎ ከሁለቱ የአሜሪካ ግዙፍ ከተሞች በላይ ብዙ የግድያ ወንጀሎች ተመዝግበውባታል። እአአ 2018 በቺካጎ 561 ሰዎች በሌላ ሰው የተገደሉ ሲሆን ይህም በተመሳሳይ ዓመት በኒው ዮርክ እና ሎስ አንጀለስ ከተሞች ከተመዘገበው የግድያ ወንጀል ድምር በላይ ነው።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
a1bfd475a19dd46cb208ecc848cd63de
61b18c41140d8d708b3603bdddfe2c94
የአፍሪካ ዋንጫ ዳሰሳ | ምድብ ስድስት
አራት የምዕራብ አፍሪካ ሃገራት የያዘው የመጨረሻው ምድብ ከሞት ምድብ ቀጥሎ አጓጊ ምድብ ነው። ቻምፒዮኗ ካሜሩን፣  ጋና፣ ቤኒን እና ጊኒ ቢሳዋን የሚያገናኘው ይህ ምድብ ጠንካራ እና እልህ አስጨራህ ፉክክር ይታይበታል ተብሎ ይጠበቃል።🇨🇲 ካሜሩን የተሳትፎ ብዛት – 19ምርጥ ውጤት – 5 ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ (1984, 1988, 2000, 2002, 2017)በቀድሞ የኤስሚላን ጀግና ክላረንስ ሲዶርፍ የሚመሩት የባለፈው ውድድር አሸናፊ ካሜሩን ይሄ ውድድር እንደባለፈው ፉክክር አልባ አፍሪካ ዋንጫ አልጋ በአልጋ እንደማይሆንላቸው የታወቀ ነው።በማጣርያው በምድብ ‘B’ ከሞሮኮ፣ ኮሞሮስና ማላዊ ተደልድለው በደካማው ምድብ ሳይፈተኑ ወደ ውድድር ያለፉት ካሜሩኖች የፓሪ ሰን ጀርመው አጥቂ ቾፓ ሞቲንግን ይዘው ወደ ግብፅ ሲያመሩ ቡድኑ ቻምፒዮን በሆነበት ዓመት በፍፃሜው ጨዋታ የቡድኑ የነብስ አዳኝ የነበረው ቪንሰንት አቡበከር እና ባለፈው የውድድር ዓመት ከሊቨርፑል ጋር ድንቅ ዓመት ያሳለፈውና የሃገሩን ጥሪ አልቀበልም በማለቱ በሃገሩ ልጆች እንደ ከሃዲ የታየው ቀውላላው ተከላካይ ዮኤል ማቲፕ በክላረንስ ሲዶርፍ ጥሪ አልደረሳቸውም።የቅድመ ዝግጅታቸው በስፔን እና ኳታር ያደረጉት ካሜሩኖች በአቋም መለኪያ ጨዋታ ዛምቢያ እና ኤዲ ኮርኮን የተባለ የስፔን ክለብ ሲያሸንፉ ከማሊ ጋር አቻ ተለያይተዋል።የማይበገሩት አናብስት ከአያክስ ጋር ድንቅ ዓመት ያሳለፈው ግብጠባቂው አንድሬ ኦናና እና በሃገሩ ማልያ ጥሩ የጎል ክብረወሰን ያለው ማክሰም ቾፓሞቲንግ ላይ ተስፋ ጥለዋል።🇬🇭 ጋና የተሳትፎ ብዛት – 22 ምርጥ ውጤት – 4 ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ (1963 ,1965 ,)ሃገራችን ኢትዮጵያ፣ ኬንያ እና ሴራሊዮን ከነበሩበት ምድብ ‘F’ ምድቡን በበላይነት በማጠናቀቅ በቀላሉ ወደ አፍሪካ ዋንጫው ያለፉት ጥቋቁር ከዋክብቶች በውድድሩ በተከታታይ አምስት ጊዜ ለፍፃሜ በመድረስ ባለ ታሪክ ናቸው። አንድሬ አየው አምበልነት ወደ ግብፅ የሚያቀኑት ጥቋቁር ከዋክብቶች በዱባይ በቆዩባቸው የዝግጅት ቀናት ሶስት የአቋም መለኪያ ጨዋታዎች አድርገው አንድ ድል ፣ አንድ አቻ እና አንድ ሽንፈት ቀምሰዋል።ሁሌም በውድድሩ ተጠባቂ ከሆኑት ሀገራት ተርታ ብትሰለፍም 37 ዓመት ያስቆጠረችው ሀገር ታሪኳን ለማደስ አስር ለውድድሩ እንግዳ የሆኑ ተጫዋቾችን ከማካተት ባሻገር እንደ አትሌቲኮ ማድሪዱ ቶማስ ፓርተይ፣ ባለልምዶቹ ክዋዱ አሳሙሃ፣ አንድሬ አዬው እና አሳሞሃ ጅያን ባሉ ተጫዋቾች ላይ ተስፋ ጥለዋል።ሳይጠበቅ አዳዲስ ፊቶች ይዞ ወደ ውድድሩ ለማቅናት የወሰነው ክዌሲ አፒያ እነ ባባ ኣህማን ፣ ጆናታን ሜንሳህ ፣ ጆሴፍ አይዶ እና ዓብዱልመጅድ ዋሪስ ወደ መጨረሻው ስብስቤ ሳያካትት ወደ ግብፅ ያመራል።🇧🇯 ቤኒን የተሳትፎ ብዛት – 3ምርጥ ውጤት – የምድብ ጨዋታዎችአልጀርያ ፣ ቶጎ እና ኮሞሮስ ከነበሩበት ምድብ ‘ D’ ከምድቡ መሪ አልጀርያ በአንድ ነጥብ ዝቅ ብላ በሁለተኛነት በማጠናቀቅ ከዘጠኝ ዓመት በኃላ ወደ አፍሪካ ዋንጫው የተመለሰችው ቤኒን የማጣርያ ጉዞዋን መሰረት በማድረግ ቀላል ተጋጣሚ እንደማትሆን መገመት አያዳግትም።በማጣርያው ጨዋታዎች ላይ አምስት ግቦች ብቻ ያስቆጠሩት ቤኒኖች እንደ አብዛኞቹ የአፍሪካ ሃገራት ግብ የማስቆጠር እና ንፁህ የግብ ዕድል በመፍጠር ረገድ ቀላል የማይባል ክፍተት አለባቸው።ለቅድመ ዝግጅት ሞሮኮ የቆዩት ቤኒኖች ሶስት ጨዋታዎች አድርገው ሶስቱም በድል ተወጥተዋል።በርከት ያሉ ተጫዋቾች ከፈረንሳይ የመረጡት ቤኒኖች በአንጋፋው ስቴፈን ሴሴኞ እና በሃደርስፊልዱ ስቲቭ ሞውኔ ላይ ተስፋ ጥለዋል።🇬🇼 ጊኒ ቢሳው የተሳትፎ ብዛት – 2ምርጥ ውጤት – የምድብ ጨዋታዎችዛምቢያ ፣ ናሚቢያ እና ሞዛምቢክ ከነበሩበት ምድብ ‘ k ‘ ሳትጠበቅ ምድቡን በበላይነት ያጠናቀቀችው ጊኒ ቢሳው ትላቋን ዛምቢያ ጨምሮ ሌሎቹን ሁለት ሃገራት ረምርማ ወደ ውድድሩ ታልፋለች ብሎ የገመታት አልነበረም። ከሞዛምቢክ ጋር በነበረው ድራማዊ ክስተት በተሞላበት ጨዋታ በአስደናቂ ብቃት አቻ ከተለያየች በኃላ የብዙዎች ትኩረት ስባ የነበረችው ጊኒ ቢሳው ሽንፈት ሳትቀምስ ነበር ወደ ውድድሩ ያለፈችው።በአሰልጣኝ ካንዴ እየተመራች ለሁለተኛ ጊዜ በውድድሩ የምትሳተፈው ጊኒ ቢሳው በማጣርያው ሶስት ግብ ያስቆጠረላት ፍሬድሪክ ሜንዲ ኮከብ ተጫዋቿ ነው።የምድቡ ተጠባቂ ጨዋታ፡ ካሜሩን ከ ጋናሁለቱ በውድድሩ ትልቅ ታሪክ ያላቸው የምንግዜም ተቃናቃኞች የሚያገናኘው ይህ ጨዋታ በታሪክም በወቅታዊ አቋም ረገድም ተጠባቂ ጨዋታ ነው።ተመሳሳይ አጨዋወት የሚከተሉት ሁለቱ ቡድኖች የሚያገናኘው ይህ መርሐ ግብር የምድቡ ሁለተኛ ጨዋታ ነው።ከምድቡ የሚጠበቅ ኮከብ ተጫዋች: ቶማስ ፓርቲይከምድብ ስድስት የሚጠበቀው ተጫዋች ጋናዊው የአትሌቲኮ ማድሪዱ ወሳኝ አማካይ ቶማስ ፓርተይ ነው። በምድቡ በርካታ የማጥቃት ባህሪ ያላቸው እና ከዚ በፊት በውድድሩ ልምድ ያላቸው እንደነ አሳሞሃ ጅያን የመሳሰሉ ተጫዋቾች ቢኖሩም እንደ የሃያ ስድስት ዓመቱ ውጤታማ አማካይ የሚያክል ግን አይጠበቁም። በአትሌቲኮ በበርካታ ሚናዎች ላይ የሚጫወተው አይደክሜው ተጫዋች በጋናም ተመሳሳዩ ሚና ከተሰጠው እንደሚያንፀባርቅ ይጠበቃል።የምድቡ ጨዋታዎችማክሰኞ ሰኔ 18 ቀን 2011ካሜሩን 2:00 ጊኒ ቢሳውጋና 5:00 ቤኒንቅዳሜ ሰኔ 22 ቀን 2011ካሜሩን 2:00 ጋናቤኒን 5:00 ኢኳቶርያል ጊኒማክሰኞ ሰኔ 25 ቀን 2011ቤኒን 1:00 ካሜሩንጊኒ ቢሳው 1:00 ጋና*ይፋዊ የተጫዋቾች ስብስብ እንደደረሰን እናካትታለን
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/49051
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
5fe45482726fb58c8b414ad12fe5cb34
523d906a2bdb5e1e628692b1d16680b4
ክራር አናጋሪው ሙዚቀኛና የአካባቢ ተቆርቋሪው ስለሺ ደምሴ (ጋሽ አበራ ሞላ) ለ17ኛው የኢትዮጵያ ባሕልና ስፖርት ፌስቲቫል ስዊዘርላንድ ዙሪክ በተገኘበት ሰሞን ክሎተን በተባለ ቀበሌ፣ አንድ የሕዝብ መናፈሻ ውስጥ አግኝተነው ዘለግ ያለ ቃለ ምልልስ አድርገናል። በአመዛኙ ያወጋነው ከሙዚቃ ይልቅ በወቅታዊ አገራዊ፣ ፖለቲካዊና ከተማዊ ጉዳዮች ላይ ነበር ማለት ይቻላል። ዙሪክ ብዙ ችግኝ ተተክሏል መሰለኝ.. ፣ እንደምታየው ዙሪያ ገባው ሁሉ አረንጓዴ ነው...(ሳቅ)
"የት ይቀርልሃል!? አፈር ድሜ ትበላለህ...!" ጋሽ አበራ ሞላ\n[እውነትህን ነው] አራት ቢሊየኑ እዚህ የተተከለ ነው'ኮ የሚመስለው (ሳቅ) •በአውሮፓ የኢትዮጵያዊያን ፌስቲቫል፡ ሙዚቃ፣ ኳስ፣ ፍቅርና ቡጢ.. ይሄን ይሄን አይተህ ቁጭት አንገብግቦህ ነበር እንዴ ያኔ ጠቅልለህ ወደ አገር ቤት ገብተህ አገሩን በዘመቻ ያመስከው? አዲስ አበባን ጄኔቭ የምታደርግ መስሎህ ነበር? (ሳቅ) እም...ይሄን አይቼ ሳይሆን በፊት ልጅ በነበርንበት ጊዜ፤ ከዚያ በፊት በአያት በቅድም አያቶቻችን ጊዜ ኢትዮጵያ 60 እና 65 እጅ ያህል ደን የነበረበት አገር ነበር [የነበረን]። ለም የሆነ አገር። ከዚያ በኋላ የተለያዩ ሥርዓቶች ያንን ሊያስጠብቁ አልቻሉም። የሕዝቡ ቁጥር እየጨመረ መጣ፤ ልቅ የሆነ ሥርዓት ተከተለ። ከሥርዓቱ የሚመጡ አስከፊ ሁኔታዎች ድርቅ አስከተሉ። የአየር ንብረቱ ተዛባ። ሕዝቡም ደኑን መጠቀሚያ አደረገው... ላቋርጥህ ጋሽ አበራ...ከኋላህ አንድ ወጣት ውሻው መንገድ ላይ ስለተጸዳዳ እሱን ጎንበስ ብሎ እያጸዳ ነው፤ እንደምታየው በእጁ የላስቲክ ጓንት አጥልቆ...ይህን አጋጣሚ አልለፈው ብዬ ነው። የት እንደሚጥለው እንመልከት...(ጋሽ አበራ ፊቱን አዙሮ መታዘብ ጀመረ)፣ እንዳየኽው በቅርብ ርቀት መጣያ አለ። በስተቀኝህ ደግሞ የሕዝብ መጸዳጃ አለ። እዚህ አጠገባችን እጅግ ያማረ ሌላ ቆሻሻ መጣያ ይታያል...። አንተ እነዚህን ነገሮች በአገር ቤት ለመሥራት በተወሰነ ደረጃ ሞክረህ ነበረ። የገነባኻቸው ሽንት ቤቶች ፈርሰዋል። መናፈሻዎችህ የቆሻሻ መጣያ ሆነዋል? ለመሆኑ ራስ መኮንን ድልድይ ስትሄድ ምንድነው የሚሰማህ? መሸነፍ? ተስፋ መቁረጥ? አይ ተስፋ አልቆርጥም ግን ለምን ይሆን ብዬ እጠይቃለሁ። የምታገኘው ምላሽ ምንድነው? መጀመርያ አካባቢ ለምን እንደዚህ ሆነ? ምንድነው ችግሩ እያልኩ እብሰለሰል ነበር። ግን መጨረሻ ላይ ያገኘሁት መልስ ምንድነው፣ አንደኛ ባህሪያችንን መለወጥ አልቻልንም፤ በዕውቀት ማደግን አላወቅንበትም። ለአንድ አገር ሥርዓት ወሳኝ ነው። መልካም ሥርዓት ለአንድ ከተማ ምን እንደሚያስፈልግ [ጠንቅቆ ይገነዘባል]። አሁን ተመልከት...መንገዱን ያየኸው እንደሆነ፣ መሻገሪያውን ያየኸው እንደሆነ፣ ምልክቶችን ያየኸው እንደሆነ [እያንዳንዷ ነገር ታስባ የተሠራች ናት]። • ተነግረው ያላበቁት የ'ጄል' ኦጋዴን የሰቆቃ ታሪኮች ተመልከት ይሄን ቆሻሻ መጣያ...ተመልከተው በደንብ... ሲጋራ መተርኮሻ ሁሉ አለው [በቅርብ ርቀት የተተከለ የቆሻሻ መጣያን እያመላከተ]። በዚህ ደረጃ ታስቦበት ነው የሚሠራው። ይሄን አግዳሚ የሕዝብ መቀመጫን ተመልከተው። ይሄን የእግረኛ መንገድ እይ፣ እዛ ጋ ተመልከት የሆነ በዓል አለ..ድንኳን ተክለዋል...ተመልከት ሕጻናት ሲቦርቁ ወዲያ ደ'ሞ...እያንዳንዱ ነገር ታስቦበት ነው። ሁሉ ነገር በሕግ፣ በደንብና በሥርዓት ነው ያለው። ለምን ይሄ ሆነ ብለህ ጠይቅ። የሥርዓቱ ችግር ነው እያልክ ነው? እንግዲህ ምንድነው፤ የሰለጠነ አስተሳሰብ ያስፈልጋል። አንድ ባለሥልጣን ስንል ኢትዮጵያ ውስጥ ሥልጣኑን ከያዘ በኋላ የእሱ ምቾትና ሥልጣኑን ማስቀጠል እንጂ [ሌላው አያሳስበውም።] ሥልጣን የሚለው ቃል ሥልጣኔ ማለት ነው። አንድ ባለሥልጣን እዚህ ቁጭ በል ሲባል ስለሠለጠንክ ሥልጣኔህን ተጠቅመህ ሕዝብ አስተዳድር እንደማለት ነው። እሱ ግን የሚመስለው በቃ ገዢ ሆኖ፣ የበላይ ሆኖ፣ አዛዥ ሆኖ፣ ቁጭ ብሎ፣ መኪና ነድቶ፣ ቁርጥ በልቶ፣ ውስኪ ጠጥቶ መኖር ነው። ሥልጣን ይዘው የተቀመጡ ሰዎች የሥልጣኔ ባህሪውም የላቸውም። ካልሠለጠነ አእምሮ ሥልጡን የሆነ ሥርዓትን እንዴት ትጠብቃለህ? የቅድሙን ጥያቄ መልሼ ላምጣው። ፒያሳ ራስ መኮንን ድልድይ ስትሄድ አበቦቹ ደርቀው፣ ችግኞቹ ከስመው፣ አረንጓዴ ያደረከው ቦታ የቆሻሻ ቁልል ሆኖ...
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
e1bf2b8dfc3c51edb42758b3be35b014
705de79f9dd8250a571b4882db101092
የትግራይ ዋንጫ | የጦና ንቦች የፍፃሜ ተፋላሚ መሆናቸውን አረጋግጠዋል
የትግራይ ዋንጫ ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ሲቀጥል ከምድብ አንድ ወላይታ ድቻ ወደ ፍፃሜው ማለፉን ያረጋገጠበትን ድል አስመዝግቧል።የወላይታ ድቻ ብልጫ እና ጥቂት የግብ ሙከራዎች በታዩበት የመጀመርያ አጋማሽ የጨዋታ እንቅስቃሴ ሙከራ ለማድረግ ቀዳሚ የነበሩት ወላይታ ድቻዎች ሲሆኑ ሙከራውም ከረጅም ርቀት የተደረገ ጥሩ የግብ ሙከራ ነበር። የጦና ንቦች ከመጀመርያው ሙከራ በኃላም በበርካታ አጋጠሚዎች ንፁህ የግብ ዕድሎች መፍጠር ችለው ነበር። በተለይም ደጉ ደበበ ከነጋሽ ታደሰ የተሻገረለት ኳስ ተጠቅሞ የሞከረው እጅግ ለግብ የቀረበ ሙከራ ቡድኑን ቀዳሚ ለማድረግ የተቃረበ ነበር።በአጋማሹ ጫና ፈጥረው የተጫወቱት ወላይታ ድቻዎች በሃያ ሰባተኛው ደቂቃ በቸርነት ጉግሳ ግብ ማስቆጠር ችለዋል። ግቡም ተስፋዬ አለባቸው ከረጅም ርቀት አክርሮ መቶት ግብ ጠባቂው ከተፋው በኃላ ነበር ቸርነት ጉግሳ ደርሶ በጥሩ መንገድ ያስቆጠረው።በአጋማሹ ብዙም የግብ ዕድል ያልፈጠሩት አክሱሞች በዮሐንስ ዓፈራ እና ዘካርያስ ፍቅሬ በኩል ሁለት ሙከራዎች አድርገዋል። በተለይም ዘካርያስ ፍቅሬ ከግብ ጠባቂው ጋር አንድ ለአንድ ተገናኝንቶ ያመከነው ኳስ አክሱሞች አቻ ለማድረግ የተቃረበ ነበር።ወላይታ ድቻዎች በትኩረት ማጣት እና በተጫዋቾች ውሳኔ አሰጣጥ ችግር በቁጥር እጅግ በርካታ የግብ ዕድሎች ያመከኑበት ሁለተኘሐው አጋማሽ አክሱም ከተማዎች የተጫዋች ለውጥ ካደረጉ በኃላ የተሻለ ተንቀሳቅሰዋል።ወላይታ ድቻዎች በዚህኛው አጋማሽም ግብ ለማስቆጠር ግዜ አልወሰደባቸውም፤ በአርባ ስምንተኛው ንጋሽ ታደሰ ከረጅም ርቀት ግሩም ግብ በማስቆጠር የቡድኑ ልዩነት ወደ ሁለት ከፍ ማድረግ ችሏል።ድቻዎች ከግቡ በኃላም በቢንያም እሸቱ እና በበረከት ወልዴ በርካታ ዕድሎች የፈጠሩ ሲሆን በተለይም ተቀይሮ የገባው ቢንያም እሸቱ ያመከናቸው የግብ ዕድሎች የግብ ልዩነቱ ማስፋት የሚችሉ ነበሩ።በሁለተኛው አጋማች በርካታ ተጫዋቾች ቀይረው ያስገቡት አክሱሞች በርካታ ሙከራዎች ማድረግ ችለው ነበር። ከነዚህም ዘካርያስ ፍቅሬ ከረጅም ርቀት ያደረገው ሙከራ እና ንስሃ ታፈሰ ከቅጣት ምት ያደረገው ጥሩ ሙከራ ይጠቀሳሉ።መደበኛ የጨዋታ ክፍለ ግዜ ተጠናቆ በተሰጠ ተጨማሪ ደቂቃም በሁለቱም ቡድኖች በኩል ሁለት ግቦች ተቆጥረዋል። በወላይታ ድቻዎች በኩል ቢንያም እሸቱ የተከላካይ ስህተት ተጠቅሞ ያስቆጠራት ግሩም ግብ ቡድኑ ሶስት ለባዶ እንዲመራ ያስቻለች ስትሆን በአክሱሞች በኩልም አዳነ ተካ ግብ አስቆጥሮ ቡድኑን በባዶ ከመሸነፍ አድኖታል።ጨዋታው በዚህ ውጤት መጠናቀቁን ተከትሎ በውድድሩ ፎርማት መሰረት ወላይታ ድቻ የፍፃሜ ተፋላሚ መሆኑ ሲያረጋግጥ አክሱም ከተማ ለደረጃ ይጫወታል።በውድድሩ ጥሩ ብቃቱ እያሳየ የሚገኘው በረከት ወልዴ የጨዋታው ኮከብ ሆኖ ተመርጧል።
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/51715
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
def6bb51faf46c722f5105b529969905
893a89af26e06977ff67a8f0e4139567
ጂን
ጂን (ቻይንኛ፦ 廑) በጥንታዊ ቻይና የሥያ ሥርወ መንግሥት ዘመን ንጉሥ ነበር። ሌላ ስሙ ዪንጅያ ነበር። የቀርከሃ ዜና መዋዕል በተባለው ጽሑፍ ዘንድ፣ ለዘመኑ የተዘገበው እንዲህ ነው፦ በመጀመርያው ዓመት በሆ ወንዝ ምዕራብ ኖረ። በ፬ኛው ዓመት «የምዕራብ ሙዚቃ» ቃነ፤ የኩንዉና ወይ ገዥ ጂ ታን ወደ ሹዦው ተዛወረ። በ፰ኛው ዓመት (1661 ዓክልበ.) በታምራዊ ትርዒት አሥር ፀሐዮች አብረው በሰማይ ታዩ፤ በዚያም አመት ጂን ዓረፈና የአጐቱ ቡ ጅያንግ ልጅ ኮንግ ጅያ ተከተለው። የሥያ ሥርወ መንግሥት
null
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
413c007dfafa157a6bfda6585d31c896
6d5e40d680cc44fe8ea086fefb2acbeb
የፌደራል መንግስት ተግባር ወንጀለኞችን ለህግ ማቅረብ፣ ህግና ስርዓት ማስከበርና መልሶ ማቋቋም ነው – ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት
የፌደራል መንግስት በትግራይ ክልል በአሁኑ ወቅት የሚያከናውናቸው ተግባራት ወንጀለኞችን ለህግ ማቅረብ ህግና ስርዓት ማስከበርና መልሶ ማቋቋም መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።ጽሕፈት ቤቱ በትግራይ ክልል የህግ ማስከበር እርምጃው ንጹሃን ዜጎች ሳይጎዱና ንብረቶች ሳይወድሙ የመቐለ ከተማን በመቆጣጠር እርምጃው መጠናቀቁን ገልጿል።በአሁኑ ወቅት የፌደራል መንግስት ተግባራት ወንጀለኞችን ለህግ ማቅረብ፣ በአካባቢው ሕግና ስርዓት እንዲኖር እንዲሁም መልሶ ማቋቋም መሆኑም ፅህፈት ቤቱ አስታውቋል።እንዲሁም ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ዜጎች የሰብዓዊ እርዳታ እንዲያገኙ፤ ከአካባቢያቸው ርቀው ድንበር አቋርጠው የተሰደዱ ዜጎችን መልሶ ማቋቋምና በወንጀለኛው ቡድን የፈረሱና አገልግሎት ያቋረጡ የትራንስፖርትና መገናኛ መሰረተ ልማቶችን መልሶ መገንባት እየተከናወኑ መሆኑንም ነው የገለጸው።የትግራይ ህዝብ የሚፈልገው ዕድገት፣ ሰላም፣ ነጻነትና ደህንነት ቢሆንም የህወሓት ጁንታ ቡድን በፍትሃዊና እኩልነት የተመሰረተች ኢትዮጵያን ለመመስረት አጋር መሆን የማይችል እንደሆነም አውስቷል፡፡ቡድኑ ከተጠያቂነት ለማምለጥ መንግስት የወሰደውን የህግ ማስከበር እርምጃ በተመለከተ የተሳሳቱ መረጃዎችን በማሰራጨት ዓለም አቀፍ ተቋማት ጣልቃ ገብተው ድርድር እንዲደረግ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱም ተመልክቷል።የጁንታው ህወሓት ቡድን በሚገባ የተሸነፈ እና የደፈጣ ውጊያ ለማድረግ ምንም አቅም የሌለው መሆኑ እየታወቀ ቡድኑ ግን ከእነሙሉ አቅሙ እንዳለና ስልታዊ ማፈግፈግ አድርጎ የደፈጣ ውጊያ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን የሚያትቱ የሐሰት ፕሮፖጋንዳ ሲነዛ መቆየቱንም ጽሕፈት ቤቱ አስታውሷል።ቡድኑ ዓለም የተለያዩ የሐሰት ውንጀላዎችን በማቅረብና የሕግ ማስከበር ዘመቻው ዓለም አቀፍ መልክ እንዲይዝና ከተጠያቂነት ለመምለጥ ጉዳዩ ወደ ድርድር እንዲወሰድ ፍላጎት አሳይቶ እንደነበርም አስታውቋል።የህወሓት ቡድን በሰሜን እዝ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ ጥቃት ከመፈጸሙም ባሻገር በማይካድራ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ጥቃት መፈጸሙ፣ እንዲሁም ወደ ባህርዳርና ጎንደር ጅምላ ጨራሽ የጦር መሳሪያ መላኩ ለሰላማዊ ዜጎች ምንም ግድ የሌለው ቡድን መሆኑን ግልጽ ያደርጋል ብሏል ጽሕፈት ቤቱ።የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በማብራሪያው መንግስት በማንኛውም ጊዜ ለዜጎች ደህንነት ቅድሚያ የሚሰጥ መሆኑንም አረጋግጧል።በትግራይ ክልል በተደረገው የሕግ ማስከበር ዘመቻ ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች እንዲሁም በክልሉ በስደተኞች ካምፕ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ላልሆኑ ስደተኞች ድጋፍ ለማድረግ የኢትዮጵያ መንግስት ከሰብአዊ ድጋፍ ሰጪ ተቋማትና ከመንግስታቱ ድርጅት ኤጀንሲዎች ጋር በትብብር እየሰራ ነውም ብሏል፡፡
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://waltainfo.com/am/%e1%8b%a8%e1%8d%8c%e1%8b%b0%e1%88%ab%e1%88%8d-%e1%88%98%e1%8a%95%e1%8c%8d%e1%88%b5%e1%89%b5-%e1%89%b0%e1%8c%8d%e1%89%a3%e1%88%ad-%e1%8b%88%e1%8a%95%e1%8c%80%e1%88%88%e1%8a%9e%e1%89%bd%e1%8a%95/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
74d16a9c6b6109d7618d6de79a732389
b26492cf96032184747fb4eebdb62da8
ቅድመ ዳሰሳ | ኢትዮጵያ ቡና ከ ሀዲያ ሆሳዕና
ነገ በስድስተኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ከሚደረጉ ጨዋታዎች መካከል አንዱ የሆነው የኢትዮጵያ ቡና እና የሀዲያ ሆሳዕና መርሐ ግብርን እንደሚከተለው ተመልክተነዋል።በእንቅስቃሴ ደረጃ ከጨዋታ ጨዋታ መሻሻሎችን እያሳየ የሚገኘው የካሳዬ አራጌ ቡድን ባሳለፍነው ሳምንት ወደ ምስራቁ የሃገሪቱ ክፍል ተጉዞ ነጥብ ከጣለበት ጨዋታ መልስ የነገውን መርሃ ግብር ይጠባበቃል። በተለይ ቡድኑ በአራተኛ ሳምንት በሜዳው ሃዋሳን 4-1 ካሸነፈበት ጨዋታ በመነሳት ለውጦች እንዳሉበት ሲነገር ቢቆይም የሊጉን ደካማ ቡድን ማሸነፍ ሳይችል ቀርቷል።በእንቅስቃሴ እና በውጤት ደረጃ እየተነቃቃ የመጣ የሚመስለው ቡድኑ በተለይ ተጋጣሚን የሚያደክሙ እና ክፍተት እንዲፈጥሩ የሚያስገድዱ የኳስ ቅብብሎችን በመፈፀም ጎሎችን ሲፈልግ ይታያል። ከእነዚህ አላማ ያላቸው የኳስ ቅብብሎች በተጨማሪ ቡድኑ ሳይታሰብ እያሳየ ያለው የፈጣን ሽግግሮች (ከመከላከል ወደ ማጥቃት) አጨዋወት ተጋጣሚን ሲያስደነግጥ ተስተውሏል። ከዚህ ውጪም ከወገብ በላይ ያሉት የቡድኑ ፈጣን እና ታታሪ ተጨዋቾች ጥረት ተጋባዦቹን ሊፈትን እንደሚችል አመላክቷል።ኳስን ከግብ ጠባቂ ጀምሮ ለመመስረት የሚጥሩት ኢትዮጵያ ቡናዎች ተጋጣሚ አስጨንቆ ኳስ ለመቀማት ሲሞክርባቸው እንደሚቸገሩ በተደጋጋሚ ታይቷል። በዚህም ረገድ ተጋጣሚያቸው ሃዲያ ሆሳዕና የኢትዮጵያ ቡና ግብ ጠባቂ እና ተከላካዮች የቅብብል ስህተቶችን እንዲሰሩ ካስጨነቁ ለቡድናቸው በጎ ነገር ሊያመጡ ይችላሉ።ኢትዮጵያ ቡናዎች በነገው ጨዋታ የታፈሰ ሰለሞን ግልጋሎት በጉዳት ምክንያት እንደማያገኙ ተረጋግጧል።ከሜዳቸው ውጪ ቀርቶ በሜዳቸውም አንድም ጨዋታ ማሸነፍ ያልቻሉት ሀዲያ ሆሳዕናዎች በነገው ጨዋታ ሦስት ነጥብን አላማ አድርገው ወደ ሜዳ እንደሚገቡ ይገመታል። እስከ አራተኛ ሳምንት የሊጉ መርሃ ግብር ሁለት ጎሎችን ብቻ ተጋጣሚ ላይ ማስቆጠር የቻለው ቡድኑ ባሳለፍነው ሳምንት ባህር ዳር ከተማ ላይ በአራት ጨዋታዎች ያስቆጠረውን የግብ መጠን (2) በማስቆጠር የጠፋበትን የግብ ማግባት መንገድ ያገኘ ይመስላል። ይህም ለቡድኑ የማጥቃት ባህሪ ላላቸው ተጫዋቾች የራስ መተማመን እንደሚያመጣ ይታሰባል።የኢትዮጵያ ቡና አጨዋወት ኳስን መሰረት ያደረገ መሆኑ ይህንን ለማጨናገፍ አሰልጣኝ ግርማ ታደሰ በርከት ያሉ የአማካይ መስመር ተጨዋቾችን እንደሚጠቀሙ ይገመታል። ይህ ውሳኔ ለኳስ ቁጥጥሩ ብቻ ሳይሆን አስተማኝ ላልሆነውን የቡድኑ የተከላካይ መስመር ሽፋን ለመስጠት ታስቦ እንደሚደረግ ይታሰባል። በተጨማሪም በፊት መስመር የሚገኙት ተጫዋቾች ከኳስ እና ያለ ኳስ እንቅስቃሴ ከግብ ክልሉ ኳስ መስርቶ የሚወጣው ቡናን የቅብብል ስህተቶች መጠቀም ላይ ያተኩራል ተብሎ ይጠበቃል። በአንፃራዊነት የቡድኑ ጠንካራ ጎን የሆነው የአየር ላይ ኳስ አጠቃቀምም በገነው ጨዋታ ከሚገኙ የቆሙ ኳሶች ውጤት ይዘው ሊወጡ እንደሚችሉ ይገመታል።የሊጉ አዲስ ክለብ ሀዲያ ከድሬዳዋ ከተማ በመቀጠል ብዙ ጎሎችን ያስተናገደ (9) ክለብ ነው። በነገውም ጨዋታ ቡድኑ ግብ ሊቆጠሩበት የሚችሉ ስህተቶችን ካልቀነሰ ችግሮችን ሊጋፈጥ ይችላል።ቡድኑ በጉዳት በረከት ወልደዮሐንስ፣ እርቅይሁን ተስፋዬ ፣ መሐመድ ናስር እንዲሁም ሙሳ ካማራን በነገው ጨዋታ አያሰልፍም።እርስ በእርስ ግንኙነትኢትዮጵያ ቡና እና ሃዲያ ሆሳዕና ከዚህ ቀደም ሁለት ጊዜ በሊጉ ተገናኝተው ሁለቱንም ኢትዮጵያ ቡና በተመሳሳይ 2-1 አሸንፏል።ግምታዊ አሰላለፍኢትዮጵያ ቡና (4-3-3)ተ/ማርያም ሻንቆአህመድ ረሺድ – ፈቱዲን ጀማል – ወንድሜነህ ደረጀ – አስራት ቱንጆፍ/የሱስ ተ/ብርሃን – ዓለምአንተ ካሣ – አማኑኤል ዮሐንስአቤል ከበደ – እንዳለ ደባልቄ – አቡበከር ናስርሀዲያ ሆሳዕና (4-3-3)አቤር ኦቮኖፍራኦል መንግስቱ – ደስታ ጊቻሞ – አዩብ በቃታ – ሄኖክ አርፊጮአፈወርቅ ኃይሉ – ይሁን እንደሻው – ዮሴፍ ደንገቱቢስማርክ አፒያ – ኢዮኤል ሳሙኤል – ቢስማርክ ኦፖንግ
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/53720
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
31c8d8235a2b17ad243bb330310da67f
bed5370669c291e49ecf460c832c40c1
በቀጣይ ስድስት ወራት አዲስ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ግንባታ እንደሚጀመር ተገለጸ
በተያዘው በጀት ዓመት ኹለተኛው አጋማሽ ላይ በትልቅነቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተፎካካሪ የሆነ አየር ማረፊያ ለማስገንባት ዝግጅት መጠናቀቁቀን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታወቀ። አየር መንገዱ በኦሮሚያ ክልል በቢሾፍቱ እና በዝቋላ መካከል በሚገኝ አካባቢ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ለማስገንባት ዕቅድ ይዞ ቦታ መረጣውም የተጠናቀቀ ሲሆን በቅርቡም የቦታ ርክክቡ እንደሚከናወን አስታውቋል።የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ ተወልደ ገብረማሪያምን ዋቢ አድርጎ ኢቢሲ እንደዘገበው የሚገነባው አዲሱ አየር ማረፊያ በፈረንሳይ  ዋና ከተማ ፓሪስ ከሚገኘው ቻርለስ ደጎል አየር ማረፊያ በትልቀቱ እንደሚልቅ ለማወቅ ተችሏል። ዋና ስራ አስፈጻሚው አያይዘውም በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ የሚታየውን መጨናነቅ በሰፊው ይቀርፋል የተባለለት ይኸው አየር ማረፊያ የግንባታ ሒደቱ ይህ ዓመት ሳይጠናቀቅ በበጀት ዓመቱ ኹለተኛው አጋማሽ ላይ እንደሚጀመር ለማወቅ ተችሏል።ከግንባታው ጋር ተያይዞም በሚነሱ የአካባቢው ማኅበረሰብ ለሚያገኙት ካሳም ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝ አየር መንገዱ አስታውቋል።
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://addismaleda.com/archives/9192
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
93256a8c9f895677d22be99ed070aebe
89c9a475f91c87c7d3fdf2259d2f0760
በኮቪድ 19 የተያዘ ሰው እንደተገኘባቸው ይፋ ያላደረጉ ሀገራት እነማን ናቸው?
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) መነሻውን ቻይና ያደረገው የኮሮና ቫይረስ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ በርካታ የዓለም ሀገራትን አዳርሷል።በርካታ ጉዳቶችን ያስከተለው ይህ ቫይረስም በዓለም ጤና ድርጅት ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ ሆኖ ታውጇል።188 የዓለም ሀገራትን ባዳረሰው በዚህ ቫይረስ ከ13 ሚሊየን በላይ ሰዎች ሲያዙ ለ578 ሺህ ሰዎች ህልፈት ምክንያት ሆኗል።ሆኖም እስከአሁን ድርስ በኮሮና ቫይረስ የተያዘ ሰው ይፋ ያላደረሁ ሀገራት በዓለም ላይ ይገኛሉ ።እነዚህም1. ኪሪባቲ2. ማርሻል አይስላንድስ3. ናኡሩ4. ሰሜን ኮሪያ5. ፓላኡ6. ሳሞኣ7. ሶሎሞን አይስላንድስ8. ቶንጋ9. ቱርክሜኒስታን10. ቱቫሉ11. ቫኑአቱ ናቸው።ቫይረሱ እንደተገኘባቸው ይፋ ካላዳረጉት ከእነዚህ ሀገራት መካከል በርካቶች በውቂያኖሶች የተከበቡ ደሴታማ ሀገራት ናቸው።
4ዓለም አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%89%a0%e1%8a%ae%e1%89%aa%e1%8b%b5-19-%e1%8b%a8%e1%89%b0%e1%8b%ab%e1%8b%98-%e1%88%b0%e1%8b%8d-%e1%8a%a5%e1%8a%95%e1%8b%b0%e1%89%b0%e1%8c%88%e1%8a%98%e1%89%a3%e1%89%b8%e1%8b%8d-%e1%8b%ad%e1%8d%8b/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
5977cc67bc2febc46319b16a66a7953c
22ca1db725b93e3ac3f5936e8482f81a
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ወደ ግብፅ አቀኑ
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ሥፍራው ያቀኑት የግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱልፋታህ አልሲሲ ባደረጉላቸው ግብዣ መሰረት ነው።በተያያዘ የኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብፅ መሪዎች ዛሬ በግብፅ የወደብ ከተማዋ ሻርም አል ሼክ ተገናኝተው እንደሚወያዩ ይጠበቃል፡፡የታላቁ ህዳሴ ግድብም የመሪዎቹ ዋነኛ የመነጋገሪያ ርዕስ እንደሚሆን ተነግሯል።የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ስብሰባው ከአፍሪካ ኢንቨስትመንት ጉባኤ ጎን ለጎን ነው የሚካሄደው።ለሁለት ቀናት የሚቆየው ጉባኤ በአፍሪካ የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ እና ኢንቨስትመንት ማሳደግ ላይ ያተኩራል፡፡በኢነርጂ፣ ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ፣ የፋይናንስ አገልግሎቶች፣ የአግሮ ቢዝነስ እና የጤናው ዘርፍ ላይ ያተኮሩ ጉዳዮች በሚዳሰሱበት በዚህ ጉባኤ ከአፍሪካ እና ከሌሎች አህጉራት ከ1 ሺ 500 በላይ ልኡካን ይሳተፉበታል፡፡ኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር ላይ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር የሚረዳ የጋራ ከፍተኛ ምክር ቤት ለማቋቋም በሻርም ኤል ሼክ ከስምምነት መድረሳቸው የሚታወስ ነው።(ኤፍ.ቢ.ሲ)
5ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/25654/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
e14c0b3a18edbe5ce79a7bf334538656
92b8b73cadd70ec5de8dd121eebe8f16
ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም በአገር ክህደት ተወነጀሉ
 “እኔ ውግንናዬ ከማንም ሳይሆን ከሰላም ነው” የአለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም፣ ከፌደራል መንግስት ጋር ጦርነት የገጠመውን የህወሃት ቡድን ደግፈው በመንግሰት ላይ ዲፕሎማሲያዊ ጫና ለማሳደር የማግባባትና የጦር መሳሪያ የማፈላለግ ተግባር ላይ ተጠምደው መሰንበታቸው የተገለፀ ሲሆን ይህ ድርጊታቸው በአገር ክህደት ወንጀል ሊያስጠይቃቸው ይችላል ተብሏል፡፡ዶ/ር ቴድሮስ በበኩላቸው፤ “ውግንናዬ ለህወሃት ቡድንም ሆነ ለፌደራል መንግስቱ አይደለም፤ የኔ ውግንና ከሰላም ነው” ብለዋል።  ከፌደራል መንግስት ጋር ጦርነት ገጥሞ የሚገኘው ህወሃት፤ የጦር መሳሪያ እንዲያገኝ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ከፍተኛ ጥረት ሲያደርጉ እንደነበር እንዲሁም  የአውሮፓ ህብረት የአፍሪካ ህብረት፣ የተባበሩት መንግስታትና የተለያዩ ሃገራት በፌደራል መንግስት ላይ ዲፕሎማሲያዊ ጫና እንዳያደርጉ ሲያግባቡ መሰንበታቸውን የመከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም  ጀነራል ብርሃኑ ጁላ አስታውቀዋል፡፡ዶ/ር ቴድሮስና ጎረቤት ሃገራት፣ የፌደራል መንግስትን ህግ የማስከበር እርምጃ እንዲያወግዙ ሲቀሰቅሱ ከመሰንበታቸው ጎን ለጎን፣ ህወሃቶች የጦር መሳሪያ የሚያገኙበትን መንገድ ሲያፈላልጉ መቆየታቸውም ተመልክቷል፡፡የዶ/ር ቴድሮስ ድርጊት ሀገሪቱን የካደ መሆኑን የሚገልፁት የህግ ፕሮፌሰሩ አለማየሁ ገ/ማርያም በበኩላቸው፤ በዚሁ ድርጊታቸው የተባበሩት መንግስታትንም ሆነ የዓለም ጤና ድርጅትን የስነ-ምግባር መርሆ መጣሳቸውን ያስረዳሉ፡፡መንግስት የአካባቢውን ሰላም የሚያደፈርስ ነገር ሲያጋጥመው ህግ የማስከበር ሃላፊነትም መብትም አለው ያሉት ፕ/ር አለማየሁ ገ/ማርያም፤ ጦርነትንም ማወጅ የሚችለው የክልል መንግስት ነኝ የሚል ሳይሆን የፌደራል መንግስት ነው ብለዋል።አንድ የክልሉ መንግስት ነኝ የሚል አካል ጦርነትን ለማወጅ መብት የለውም፤ ድርጊቱ የሚታየው  በአሸባሪነትና በአጥፊነት ደረጃ ነው  ብለዋል። አለማቀፍ የህግ ፕሮፌሰሩ።ከዚህ አንጻር የአለም ጤና ድርጅትን የሚመሩት ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የህወኃትን ድርጊት መደገፋቸውና የጦር  መሳሪያ ለማቅረብ ጥረት ማድረጋቸው አሸባሪነትን የመደገፍ ወንጀል ሆኖ ሊታይ ይችላል ያሉት ፕ/ር አለማየሁ፤ የዓለም ጤና ድርጅትም ሆነ የተባበሩት መንግስታት ያስቀመጧቸውን የባለሙያነት መርሆች የተቃረነ አካሄድ መከተላቸውንም አስረድተዋል። አንድ የአለም ጤና  ድርጅት መሪ በምንም መንገድ በአንድ ሃገር  የፖለቲካ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ መግባት አይችልም ያሉት ፕሮፌሰሩ ከአለም ጤና ድርጅት ጥቅም ውጪ የሌላ አካል ጥቅም ለማስጠበቅ በምንም መልኩ መንቀሳቀስ የድርጅቱ የስነ-ምግባር መርሆ እንደማይፈቅድም አብራርተዋል፡፡እነዚህን የስነ-ምግባር መርሆዎች  መጣሳቸውን ተከትሎም የህግ አንቀጾችንና  ድንጋጌዎችን በመጥቀስ፣ በዓለም ጤና ድርጅትና ዳሬክተር ዶ/ር  ቴድሮስ አድሃኖም ላይ ክስ  ለመመስረት መዘጋጀታቸውን ነው ፕ/ር አለማየሁ  ያስገነዘቡት።ከሃላፊነታቸው ውጪ በተንቀሳቀሱት ዶ/ር ቴድሮስ ላይ ክስ ለማቅረብ ሌሎች ኢትዮጵያውያንም ትብብር  እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርበዋል።ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የአለም ጤና ድርጅት አምስት መርሆችን ማለትም ህግ ማስከበር፣ ተጠያቂነት፣ ገለልተኝነት፣  አክብሮትንና የባለሙያነት መርሆችን መጣሳቸውን በማስረጃ ማረጋገጥ እንደሚቻል ነው ፕ/ር አለማየሁ ያስገነዘቡት። ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ የቅሬታ ደብዳቤ መፃፉን ጠቁመው፣ የኢትዮጵያ መንግስትም በዶ/ር ቴድሮስ ላይ በወንጀል ተጠርጣሪነት ክስ ከመሰረተባቸው ከዓለም ጤና ድርጅት ሃላፊነታቸውን የሚነሱበት ሁኔታም እንደሚፈጠር ገልጸዋል ፕ/ሩ አለማየሁ ገ/ማርያም፡፡
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.addisadmassnews.com/index.php?option=com_k2&view=item&id=26758:%E1%8B%B6-%E1%88%AD-%E1%89%B4%E1%8B%8E%E1%8B%B5%E1%88%AE%E1%88%B5-%E1%8A%A0%E1%8B%B5%E1%88%83%E1%8A%96%E1%88%9D-%E1%89%A0%E1%8A%A0%E1%8C%88%E1%88%AD-%E1%8A%AD%E1%88%85%E1%8B%B0%E1%89%B5-%E1%89%B0%E1%8B%88%E1%8A%90%E1%8C%80%E1%88%89&Itemid=180
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
87dc5a78fb2636350ee415071ecb7a2b
23b08767c5401091fa0ded1317f9b7b1
ዘንድሮ በዓለም ላይ የኩፍኝ ወረርሽኝ በሦስት እጥፍ ጨምሯል- የተባበሩት መንግሥታት
የዓለም አቀፉ የጤና ድርጅት መረጃዎች እንደሚያሳዩት "በአስደንጋጭ መልኩ እየተዛመተ" መሆኑን ነው ይህ የተባበሩት መንግሥታት አካል የሆነው ድርጅት እንዳስታወቀው ያሉት መረጃዎች መላው ዓለም የኩፍኝ ወረርሽኝ ሊያጋጥመው እንደሚችል የሚያሳዩ ናቸው። ወረርሽኙ በአፍሪካ በ700 በመቶ ጭማሪ ነው ያጋጠመው። • በኢትዮጵያ የኩፍኝ ክትባት ያልተከተቡ ህፃናት ቁጥር ከፍተኛ ነው • አለማችን የኩፍኝ ወረርሽኝ እንደሚያሰጋት አለም አቀፉ ጤና ድርጅት አስጠነቀቀ ድርጅቱ አክሎም ትክክለኛው የታማሚዎች ቁጥር ከዚህ ሊበልጥ ይችላል ሲል ስጋቱን አስቀምጧል፤ ለዚህም ምክንያት ብሎ ያቀረበው በዓለም ላይ ከ10 ታማሚዎች መካከል ሪፖርት የሚደረገው የአንዱ ብቻ መሆኑን ነው። ኩፍኝ ተላላፊ የሆነ በሽታ ሲሆን አንዳንድ ጊዜ ለከፋ የጤና ችግር ሊያጋልጥ ይችላል። በወረርሽኙ ክፉኛ ከተጠቁ ሃገራት መካከል ዩክሬን፣ ማዳጋስካር፣ እና ሕንድ ይገኙበታል። በማዳጋስካር ብቻ ከመስከረም ወር ጀምሮ 800 ሰዎች በኩፍኝ ምክንያት ሕይወታቸውን አጥተዋል። ወረርሽኙ ብራዚልን፣ ፓኪስታንና የመንንም "በርካታ ታዳጊ ሕፃናትን ለሞት በመዳረግ" አጥቅቷል። • እያነጋገረ ያለው የአማራ ክልል የቤተሰብ ዕቅድ ደብዳቤ በአሜሪካና በታይላንድ በከፍተኛ ቁጥር ክትባት የማዳረስ ሥራ እየተሠራ መሆኑ ተዘግቧል። የተባበሩት መንግሥታት በበኩሉ ኩፍኝ ተገቢውን ክትባት ከተሰጠ "ልንከላከለው የምንችለው" ወረርሽኝ ቢሆንም የክትባት መድኃኒት እጥረት አለ ብሏል። የዓለም ጤና ድርጅትን የሚያስተዳድሩት ቴዎድሮስ አድሃኖምና ባልደረባቸው ለሲኤን ኤን እንደተናገሩት ዓለም በኩፍኝ ወረርሽኝ ስጋት ውስጥ ናት፤ ለዚህም ስለ ክትባቱ እርስ በእርሳቸው የሚጋጩና የተሳሳቱ መረጃዎች የእራሳቸውን አስተዋፅዖ አድርገዋል ብለዋል።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
48b900a4b6b830a32af8d478f9c3ce44
6d802eaddc629bcbc1a803a5f405a998
ጥምቀትና ወጣቶቹ የክርስትና ምዕመናን
ከሃይማኖታዊ በዐልነቱ በተጨማሪ በቱሪስት መስህብነቱ የሚታወቀው የጥምቀት በዓል ዘንድሮም በድምቀት ተከብሯል፡፡በተለይ ባለፉት ዓመታት በጎ ፍቃደኛ የሆኑ በርካታ ወጣቶች የበዐሉን ሥነ-ሥርዓት ሲያስተባብረና ልዩ ልዩ አገልግሎቶችን ሲሰጡ ታይተዋል፡፡ታቦት በሚያልፍባቸው መንገዶች ሁሉ ለታቦት ቀይ ምንጣፍ እያነጠፉ ወደየጥምቀተ-ባሕሩ እየሸኙ ወደየደብራቸው መልሰዋል፡፡ለተጨማሪ የእስክንድር ፍሬውን ዘገባ ያዳምጡ፤ የድምፅ ፋይሉን ይክፈቱ
4ዓለም አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/ethiopian-epiphany-and-the-christian-youth-01-20-15/2606423.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
0893723f2956e517d7057ba4f1b93ec9
85e964eff7b54433dfff4a4507b08923
የሮናልድ ሬገን ቤተ መጻሕፍትን ከካሊፎርኒያ እሳት የታደጉት ፍየሎች
የተራቡ 500 ፍየሎች ባይታደጉት ኖሮ የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሮናልድ ሬገን ፕሬዘዳንታዊ ቤተ መጻሕፍትም ካሊፎርኒያን ካቃጠላት ሰደድ እሳት አይተርፍም ነበር። የቤተ መጻሕፍቱ ዙሪያ ተቀጣጣይ በሆኑ ደረቅነት ባህሪ ባላቸው ተክሎች የተከበበ በመሆኑ በሰደድ እሳቱ ለመበላት የተዘጋጀ ቦታ ስለነበር ባለፈው ግንቦት ላይ የተራቡ 500 ፍየሎች እነዚህን ተክሎች እንዲበሉ ቦታው ላይ ተሰማሩ። ፍየሎቹ ተቀጣጣይ አትክልቶቸን ለመብላት ሥራ የተሰማሩት ከአንድ ፍየል አርቢ ኩባንያ በቅጥር መልክ ነበር። ሰደድ እሳቱ ቤተ መጻሕፍቱ ላይ ደርሶ የነበረ ቢሆንም የተራቡት ፍየሎች ከስር ከስር ተቀጣጣይ አትክልቶቹን መብላታቸው ቦታው ላይ ለተሰማሩት የእሳት አደጋ መከላከል ሠራተኞች እሳቱን ለመቆጣጠር ጊዜ ሰጣቸው። የእሳት አደጋ ሠራተኞቹ ፍየሎች ሥራቸውን እጅግ እንዳቀለሉላቸው እንደተናገሩ የቤተ መጻሕፍቱ ሥራ አስኪያጅ ሜሊሳ ጊለር ለሮይተርስ ተናግረው ነበር። መጀመሪያ 13 ኤክር መሬት እየበሉ ለማፅዳት የተቀጠሩት 805 ፍየሎች ነበሩ። ፍየሎቹ የመጡበት ኩባንያ ባለቤት ስኮት ሞሪስ በአንድ ኤክር መሬት ለፍየሎቹ ስራ አንድ ሺህ ዶላር እንደሚከፈል ገልፀዋል። ካሊፎርኒያ በሰደድ እሳት መቃጠል ከቀጠለች የፍየሎቻቸውን ቁጥር መጨመር እንደሚኖርባቸውም ገልፀዋል። • ካሊፎርኒያ እየተቃጠለች ነው • ካሊፎርኒያ ከእንስሳት ፀጉር የሚሠሩ ምርቶችን አገደች • በካሊፎርንያ የመሬት መንሸራተት 13 ሰዎችን ገደለ
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
d364a4683f008d1d5f16c9353f885b1b
658195b23994296f50a1d540ab88814b
ጅማ አባ ቡና ከ ደደቢት | ቀጥታ የፅሁፍ ስርጭት
ተጠናቀቀ!!ጨዋታው ያለግብ በአቻ ውጤት ተጠናቋል፡፡ተጨማሪ ደቂቃ – 385′ ዳዊት ተፈራ የግብ ጠባቂውን መውጣት ተመልክቶ የመታውን ኳስ ክሌመንት አዳነበት፡፡ የሚያስቆጭ አጋጣሚ!የተጫዋች ለውጥ – ደደቢት 79′ አስራት መገርሳ ወጥቶ ሰለሞን ሐብቴ ገብቷል፡፡77′ በሁለቱም በኩል ትርጉም አልባ እኝቅስቃሴ እና የማሸነፍ ፍላጎት የማይታይበት ጨዋታ እየተመለከትን እንገኛለን፡፡የተጫዋች ለውጥ – ጅማ አባ ቡና 70′ በኃይሉ በለጠ በጉዳት ወጥቶ ሀይደረ ሸረፋ ገብቷል፡፡የተጫዋች ለውጥ – ደደቢት 61′ ሽመክት ጉግሳ ወጥቶ አቤል ያለው ገብቷል፡፡ቢጫ ካርድ 59′ ኃይለየሱስ ብርሃኑ በኤፍሬም አሻሞ ላይ በሰራው ጥፋት የማስጠንቀቂያ ካርድ ተመልክቷል፡፡የተጫዋች ለውጥ – ደደቢት 53′ ጌታነህ ከበደ ወጥቶ ኤፍሬም አሻሞ ገብቷልተጀመረ!! ሁለተኛው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በጅማ አባ ቡና አማካኝነት ተጀመረ፡፡እረፍት የመጀመርያው አጋማሽ ያለ ግብ ተጠናቋል፡፡36′ በሁለቱም በኩል ኢላማውን የጠበቀ ሙከራ እምብዛም ባይደረግም ወደ ግብ ለመቅረብ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ጨዋታው ተጋግሎ ቀጥሏል፡፡26′ መሀመድ ናስር የግብ ጠባቂው ክሌመንትን ከግብ ክልል መውጣት ተመልክቶ ከርቀት የመታውን ኳስ ክሌመንት እንደምንም አውጥቶታል፡፡24′ ጌታነህ ከበደ ከአስራት የፈጠረለትን ግልፅ የማግባት አጋጣሚ ሳይጠቀምበት ቀርቷል፡፡21′ ደደቢት ልምድ ባላቸው ተጫዋቾች ታግዞ የጅማ አባ ቡናን ጫና በመቋቋም ላይ ይገኛል፡፡7′ ጅማ አባ ቡና በደጋፊው ድባብ ታግዞ በፈጣን እንቅስቃሴ ተጭኖ እየተጫወተ ይገኛል፡፡ተጀመረ!! ጨዋታው በደደቢት አማካኝነት ተጀመረ፡፡ከ1977 እስከ 1981 ድረስ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለተጫወተው እና በዚህ ሳምንት ከዚህ ዓለም በሞት ለተለየው ዘላለም ተሾመ እንደ ትናንትናው ዛሬም የ1 ደቂቃ የህሊና ፀሎት ተደርጓል። የጅማ አባ ቡና አሰላለፍ22 ጀማል ጣሰው5 ጀሚል ያዕቆብ – 12 ቢያድግልኝ ኤልያስ – 21 በኃይሉ በለጠ – 18 ኃይለየሱስ ብርሃኑ11 ዳዊት ተፈራ – 27 ክርቶፈር ንታንቢ – 15 ቴዎድሮስ ገብረጻዲቅ – 7 በድሉ መርዕድ9 አሜ መሀመድ – 25 መሀመድ ናስር (አምበል)ተጠባባቂዎች1 ሙላቱ አለማየሁ4 ሀይደር ሸረፋ6 ታደለ ምህረቴ8 ሱራፌል አወል10 ቴዎድሮስ ታደሰ14 ሂድር ሙስጠፋ17 ቢንያም ኃይሌየደደቢት አሰላለፍ33 ክሌመንት አሼቲ7 ስዩም ተስፋዬ – 6 አይናለም ኃይለ – 14 አክሊሉ አየነው – 10 ብርሃኑ ቦጋለ (አምበል)24 ካድር ኩሊባሊ – 4 አስራት መገርሳ – 8 ሳምሶን ጥላሁን19 ሽመክት ጉግሳ – 9 ጌታነህ ከበደ – 17 ዳዊት ፍቃዱተጠባባቂዎች22 ታሪክ ጌትነት11 አቤል ያለው15 ደስታ ደሙ16 ሰለሞን ሐብቴ18 አቤል እንዳለ21 ኤፍሬም አሻሞ27 እያሱ እሸቴ
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/19435
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
585bc7c5648e9725874e1454cfc76add
1858a836c54991ccc7a5f12e1ee26c11
የ1999 ዓም የገና ዋዜማ ለካሚላት መህዲ እና ለቤተሰቦቿ መልካም ነገር ይዞ አልመጣም። በካሚላትና በእህቶቿ ላይ የደረሰው ብዙዎችን ያስደነገጠ፤ የኢትዮጵያውያንን ልብም በጋራ ቀጥ ያደረገ የካሚላትን ሕይወት ደግሞ የቀየረ ነበር።
"ሌሎች ሴቶች ላይ የአሲድ ጥቃት ሳይ ይረብሸኛል፤ ህመሜን ያስታውሰኛል" ካሚላት መህዲ\nካሚላት መህዲ በ1999 ዓ.ም የገና ዋዜማ ከእህቶቿ ጋር ከምትሰራበት ሱቅ አምሽታ ወደ ቤቷ ስትሄድ አንድ ሰው ወደ አጠገባቸው መጥቶ አሲድ ፊቷ ላይ ደፍቶ መሰወሩን በወቅቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበውታል። •አዲሷ የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ማን ናቸው? ካሚላት በወቅቱ በደረሰባት የፊት መቃጠል ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባት ሲሆን በተለያዩ ሆስፒታሎች ህክምና ቢደረግላትም ቃጠሎው ከፍተኛ ስለነበር ከሀገር ወጥታ መታከም እንዳለበት ተገለፀ። ጥቃቱን የፈፀመውም ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ዋለ። ከዚያ በኋላ ካሚላት በሼህ መሀመድ አሊ አላሙዲ ድጋፍ በፈረንሳይ ሀገር ሕክምና ለማግኘት ሄደች። ከዚህ የህክምና ጉዞ በኋላ አልፎ አልፎ በመገናኛ ብዙኃን ላይ ስለእርሷ ቢሰማም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ታይታ አታውቅም። •የሴቶች መብት ታጋይዋ ወይዘሮ መዓዛ አሸናፊ ማን ናቸው? በዚህ ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ወደ ፈረንሳይ ባመሩበት ወቅት በአየር መንገድ በመገኘት አቀባበል ካደረጉት የተለያዩ ሰዎች ምስል መካከል የካሚላትም አብሮ ታየ። ይሄኔ የካሚላት ጉዳይ ለማህበራዊ ሚዲያው መነጋገሪያ ሆነ። ካሚላት ፈረንሳይ ጠቅልላ መኖር ከጀመረች ስድስት ዓመት ሆኗታል። ባለትዳርና የአንድ ልጅ እናትም ሆናለች። ቢቢሲ አማርኛ፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ወደ ፈረንሳይ እንደሚመጡ ስትሰሚ ምን ተሰማሽ? ካሚላት፡ ደስ የሚል ስሜት ነው የተሰማኝ። እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ አንድ ቅን የሆነ መንግሥት ወዳለህበት ሊያይህ ሲመጣ የሚሰማህ ስሜት ነው የተሰማኝ። ቢቢሲ አማርኛ፡አየር መንገድ አቀባበል ከሚያደርጉት ሰዎች መካከል እንድትሆኚ እንዴት ተመረጥሽ? ካሚላት፡ እዚህ ለእርሳቸው አቀባበል የተቋቋመ ጊዜያዊ ኮሚቴ ነበር። ዲያስፖራው ከኤምባሲው ጋር በመሆን ማለት ነው። እዛ ላይ ነው የመረጡኝ። እና ተመርጠሻል ሲሉኝ በደስታ ተቀበልኩኝ። •ከኤለን ጆንሰን ሰርሊፍ እስከ ሣህለወርቅ ዘውዴ ቢቢሲ አማርኛ፡ለኤምባሲው ቅርብ ነሽ ማለት ነው። ካሚላት፡ ማለት ሁላችንም እዚህ ያለን ኢትዮጵያዊ ኤምባሲ የሚያስፈልገን ሲኖር እንሄዳለን፤ እንጠይቃለን። ከኤምባሲው በተሻለ እዚህ ካሉ ኢትዮጵያውያን ውስጥ ጥሩ ቦታ አለኝ። እኔም ለሰዉ ያለኝ አመለካከት ተመሳሳይ ነው። ቢቢሲ አማርኛ፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ አየር መንገድ ሲያገኙሽ ምን አሉ? ካሚላት፡ በጊዜው ሰላምታ ብቻ ነው የተለዋወጥነው። በጣም እንደተሰማቸው ያስታውቅ ነበር። እዛ ሰዓት ላይ ግን ምንም መነጋገር አትችልም ነበር። ይበርድ ነበር።ጊዜውም አጭር ነበር። ሰላምታ ብቻ ነው የተለዋወጥነው። ቢቢሲ አማርኛ፡ከዛ በኋላ የማውራት ጊዜ አላገኛችሁም። ካሚላት፡ አላገኘንም። ቢቢሲ አማርኛ፡ፈረንሳይ ኑሮሽን አድርገሻል። ሰዎች ሲያዩሽ ምን ሆነሽ ነው ብለው አይጠይቁም። ካሚላት፡ ይጠይቃሉ። መጀመሪያ ፊታቸው ላይ የምታየው ነገር ይኖራል። ከዛ በትህትና ይጠይቁሃል። እና እነግራቸዋለሁ። ቢቢሲ አማርኛ፡ሁሌ መጠየቅ አይረብሽሽም? ካሚላት፡ አይረብሸኝም አልልህም ይረብሻል። ቢቢሲ አማርኛ፡ አሁን አግብተሻል ወልደሻል ኑሮ እንዴት ነው? ካሚላት፡ ማግባት፣ መውለድ በጣም ደስ ይላል። ድርብ ኃላፊነት ነው። ኢትዮጵያ መጥቼ ካገባሁ በኋላ ልጄን እዚህ ፈረንሳይ ተመልሼ ነው የወለድኩት። ባለቤቴ ግን አሁንም ኢትዮጵያ ነው ያለው አልመጣም። እና ልጄን ብቻዬን ነው የማሳድገው። ቢቢሲ አማርኛ፡ልጅሽ ወንድ ነው ሴት ካሚላት- ወንድ ልጅ ነው፤ አራት ዓመት ሞልቶታል። ቢቢሲ አማርኛ፡ እና ፈረንሳይ ሕይወት እንዴት ነው? ካሚላት- ደስ ይላል ጥሩ ነው። በርግጥ እንደ ኢትዮጵያ አይደለም። ልጅ ስታሳድግ ብቻህን ነው። የምሄድበት ሁሉ ይዤው ነው የምዞረው። በተጨማሪም ባለቤቴ እዚህ...
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
9e1a316905ad668b2fe3d23746389163
f8cbbfda6d7e19071cee0d6c414fa862
የአገራት ኮመንዌልዝ
የአገራት ኮመንዌልዝ (እንግሊዝኛ፦ Commonwealth of Nations) የኢንተርናሽናል አገራት ስምምነት ማኅበር ነው። አሁን 53 አባላት አገራት አሉት። እነዚህ አገራት በተለይ በታሪክ የዩናይትድ ኪንግደም ግዛቶች ነበሩ። ብዙዎቹ ግን አሁን የራሳቸው መንግሥት አላቸው፤ አንዳንዶቹም እስካሁን የዳግማዊት ንግሥት ኤልሳበጥ ግዛቶች ሆነው ቀርተዋል። በ1942 ዓም የተመሠረተ የኢንተርናሽናል መንግሥታት ባህልና ምጣኔ ሀብት ስምምነት ወይም ጓደኝነት ነው። ፖለቲካ ድርጅቶች ዩናይትድ ኪንግደም
null
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
0a8de35fab52c42fbf552586963dedd3
191b46ee829219fa8f7e3bb7e9cb819f
ኢህአዴግ የግጭቶችን ምንጭ በዘላቂነት ለመፍታት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ
የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር /ኢህአዴግ/ ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት በሚያመጡ መፍትሄዎች ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገለጸ።አገር አቀፍ ተደራዳሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በአገሪቱ የሚታዩ ግጭቶችን በተመለከተ ባለፈው ሳምንት ለገዥው ፓርቲ  ያቀረቡትን ጥያቄ ተከትሎ ዛሬ ማብራሪያ ሰጥቷል።የኢህአዴግ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሽፈራው ሽጉጤ በአንዳንድ የአገሪቱ አካባቢዎች ለተከሰቱት ግጭቶች ምክንያት በሆኑ አራት ጉዳዮች ላይ ለፓርቲዎቹ ማብራርያ ተሰጥተዋል።የወሰን ማካለል፣ የማንነት ጥያቄዎች፣ የኪራይ ሰብሳቢነት ተግባር አመለካከትና የመልካም አስተዳደር ዕጦት ለግጭቶቹ መንስኤ መሆናቸውን ተናግረዋል።በኢህአዴግ የሚመራው መንግስት ችግሮቹን በመለየት በዘላቂነነት ለመፍታትና ሰላምና መረጋጋት ለማምጣት እየሰራ ነው ያሉት ኃላፊው በትግራይና አማራ ክልሎች የወሰን ማካለል ችግር እና በአማራ የቅማንት የማንነት ጥያቄ የተፈታበትን ሁኔታ በአስረጅነት ገልጸዋል።በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ በምስራቅ ኦሮሚያና ሱማሌ ክልሎች ያለውን የወሰን ጉዳይ በተመሳሳይ መንገድ ለመፍታት ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።በኪራይ ሰብሳቢዎችና በኮንትሮባንድ ንግድ የተሳተፉ ግለሰቦች ግጭቱን የፈጠሩበት ሁኔታ መኖሩንና ተጠያቂ የሚሆኑበት ስራ እየተሰራ ይገኛልም ብለዋል።በምዕራብ ኦሮሚያ አካባቢ ሰላማዊ ሰልፍ እናደርጋለን በሚል እንቅስቃሴ በሰው ህይወት፣ አካልና ንብረት ላይ ጉዳት ያደረሱ ግጭቶች መከሰታቸውንም ነው ያብራሩት፡፡ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች የተፈፀሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች በፌደራል ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ተጣርቶ ለፓርላማ ከቀረበ በኋላ ለህዝብ ይፋ እንደሚሆን ገልጸዋል።እንዲሁም ተመሳሳይ ወንጀል በተፈፀመባቸው አካባቢዎች በፌደራል ወንጀል ምርመራ ፅህፈት ቤት እየተጣራ መሆኑን ገልጸዋል።በግጭቱ የተፈናቀሉ ሰዎችን መልሶ የማቋቋም ስራ እየተሰራ መሆኑንም ለፓርቲዎቹ አብራርተዋል።የፌደራል እና የክልል መንግስታት በመከላከያ ሰራዊት እገዛ ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች የሰዎችን ህይወትና ንብረት ከጉዳት ከመታደግ አኳያ ፈጣን ምላሽ እየሰጡ መሆናቸውንም አብራርተዋል። (ኢዜአ) 
5ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/29445/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
168576e8fcf369a8bac26a7e17ec57ae
52ddeaf14f5ce8274bf1839d45b4d3d1
አዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ የሚጀመርበት ቀን ታውቋል
የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ የሚጀመርበት ጊዜ እና ተሳታፊ ክለቦች ታውቀዋል።በከተማ አስተዳደሩ የእግርኳስ ፌዴሬሽን አስተናጋጅነት የሚካሄደው ይህ ውድድር ከጥቅምት 22 ጀምሮ እስከ ህዳር 7 ሲካሄድ ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ኢትዮጵያ ቡና፣ መከላከያ፣ ኤሌክትሪክ ወልቂጤ እና ሰበታ ከተማ በውድድሩ መሳተፋቸው ተረጋግጧል። የኢኮስኮ እና የኢትዮጵያ መድን መሳተፍ ደግሞ አጠራጣሪ ሆኗል።በውድድሩ የመሳተፋቸው ነገር አጠራጣሪ በሆኑት ሁለቱ ክለቦች ምትክም ሲዳማ ቡና እና ያለፈው ዓመት የውድድሩ ክስተት ባህርዳር ከተማ ሊሳተፉ እንደሚችሉ ተሰምቷል።ከዓመት ዓመት በርካታ መሻሻሎች እያደረገ የሚገኘው ውድድሩ በዚህ ዓመት ውድድርም ከሽልማት ጀምሮ በርካታ ማሻሻያ አድርጎ እንደሚመለስ ታውቋል።
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/51025
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
0187dba2b6552ec37a050749466c4caf
cfea08fb8c1b0764b46df98fdb3a5ded
ከምናብ ወደ እውነት ማን ያስጠጋን?
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ከሐሳባዊነት ሳይላቀቅ የኖረበትን ዘመን እየጠቀሱ የሚያብራሩት ይነገር ጌታቸው፣ ሕዝብ እንዲሁም ፖለቲካ ፓርቲዎች ይመጣል እያሉ የሚጠብቁት ሁሉ በአንጻሩ ሲሆን የታየባቸው የታሪክ አጋጣሚዎች ያወሳሉ። ይህ በሆነበት ሁኔታ አሁን ላይ የሚታዩ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ‹ብልጽግና ይሸነፋል› የሚል እምነት መያዛቸው ካለፈው ሁኔታ አንጻር መገመት አለመቻል ነው ሲሉ ይሞግታሉ። የ2012 አገራዊ ምርጫንም ብልጽግና ያሸንፋል ሲሉ ከሐሳባዊነትና ምናብ ወጥቶ እውነታውን ወደማየት መሸጋገር ይገባል ብለዋል።ክርስትያን ታደለ ከመታሰሩ ከቀናት በፊት ስለ ፖለቲካችን በሰፊው ማውራታችንን አስታውሳለሁ። የውይይታችንን መነሻ ብዘነጋውም ሙግቱ ግን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፓርቲ በምርጫው ይሸነፋል አይሸነፍም የሚለው ነበር። ክሪስ ተስፈኛ፤ እኔ ፀለምተኛ ሆነን ያደረግነውን ክርክር ዛሬ ላይ ሳስበው በምናባዊነት እና እውናዊነት መካከል የተደረገ ይመስለኛል።የአብን ቃል አቀባይ በራሱና በፓርቲው ላይ የጣለውን ተስፋ ሰንቆ ገዥው ፓርቲ መሸነፉ እንደማይቀር ቅንጣት ታኽል ጥርጥር አልነበረውም። የእኔ መንገድ ግን ከዚህ ይለያል። በቀጣዩ አገራዊ ምርጫም ብልፅግናን አሸንፋለሁ ማለት የቁም ቅዠት ይመስለኛል።ለምን? የሚለውን ጥያቄ ከማንሳቴ በፊት ፖለቲካችን የምናብ እስረኛ ሆኖ መኖሩን ወደኋላ ተመልሼ ጥቂት ላስታውስ። ጄነራል መንግሥቱ ነዋይ የ1953 መፈንቅለ መንግሥት ከመካሄዱ ሰዓታት ቀደም ብለው በቢሯቸው ባካሄዱት ስብሰባ፣ ንጉሡን ለመጣል የተደረገው ቅደመ ዝግጅት ከበቂ በላይ መሆኑን እርግጠኛ ሆነው ተናግረው ነበር። ይሁን እንጂ ውጤቱ የተገላቢጦሽ ሆነ። ታሪካችን የምኞት ቁራኛ መሆኑ ግን እዚህ ላይ አላቆመም። ከአስራ ሦስት ዓመታት በኋላ የመጡት አብዮተኞች ሕዝባዊ መንግሥት ለመመስረት ከጫፍ ደረሱ። ትግሉ ነው ሕይወቴ ፍፁም ነው እምነቴ! የሚለውን መዝሙር እየዘመሩም ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ሕልው የመሆኗ ዋዜማ ላይ መድረሷን አበሰሩ። ምናብ የተጣባው ፖለቲካችን ግን ልፋታቸውን ሰማይ ላይ ባለ ማማ መሰለው። ተስፋ ቆርጠን አልቆምንም። ለምን ብለንም አልጠየቅንም። ይልቅ አንድ ቀን በሚል ተስፋ ወደፊት ነጎድን። ሌላ አስራ አራት ዓመት ጠብቀን 1981 መፈንቅለ መንግሥት አካሄድን። ፊልም የሚያስንቅ እውነትን አስታቀፎን ከመሄዱ ውጭ አዲስ ነገር አልተገኘም። ፖለቲካችን ሐሳባዊ እንደሆነ 1997 ባተ። ቅንጅቶች ታሪካችን የጎበጠው ምናባዊ ከመሆናችን ጋር ተዛምዶ እንደሆነ ጠርጥረዋል።በዚህ የተነሳም የቅደመ ምርጫ ዳሰሳ አድርግን እውነተኛ ውጤታችን ምን ሊሆን እንደሚችል መገመት ያስፈልጋል አሉ። ልደቱ አያሌውና ኃይሉ ሻወል (ኢንጅነር) ቅድመ ጥናት አድርገው የመነሻ ጽሑፍ እንዲያቀርቡ ተመረጡ። ለወራት የተካሄደው የዳሰሳ ውጤት ፍፁም ለየቅል የሚባል ነበር። ኃይሉ ሻወል በእኔ ጥናት ቅንጅት በሰፊ ልዩነት መንግሥት ለመመስረት እንደሚችል አረጋግጫለሁ አሉ።ቀጥሎ የልደቱ ተደመጠ። የምናገኘው ውጤት መንግሥት ለመመስረት አይደለም 200 ወንበሮች አያስገኝም አለ። ቤቱ ለኹለት ተከፈለ። ማን የነገ እጣ ፋንታችንን በቀረበ መንገድ ተንብዮት ይሆን ብሎ ተጨነቀ። ልዩነቱ የሚጠበቅ ቢሆንም በዚህ ደረጃ መስፋቱ ግን ተገቢ አይደለም ተባለ። አሁንም መሠረታዊውን እውነት መድፈቅ እንጂ መተርጎም የሚችል አልተገኘም። እንደውም በጊዜ ሂደት ብርሃኑ ነጋን (ፕሮፌሰር) የመሰሉ ፖለቲከኞች ልደቱ አያሌው አስቀድሞም ቢሆን ኢሕአዴግ የሰጠንን ኮታ ያውቅ ነበር የሚል ሽሙጥ ጀመሩ።ያስደንግጣል! ፖለቲካችንን ከሐሳባዊነት ሊያላቅቅ የሚችለው አጋጣሚ ጨነገፈ። ዛሬ ላይ ሳስበው የልደቱና የኃይሉ የናሙና ውጤት መለያየት መነሻው የትውልድ ዘመናቸው ይመስለኛል። የስላሳዎቹ ትውልድ ማናባዊ ነው። ከኢሕአፓ እስከ ኢጫት፣ ከመኢሶን እስከ ወዝሊግ ብናስስ የምንጨብጠው የረባ ነገር የለም። ግን በዛ መንደር ሰዎች ሽንፈት የሚታሰብ ነገር አልነበረም። እውነቱ ሌላ ቢሆንም በምናብ ፈረስ ከድል ማማ ላይ መውጣት ተለምዷል። እንዲህ ያለው ሀቅ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሰርክ ልማድ ሆኗል።ዛሬም የምንመለከተው የምናብ ምርኮ መሆንም ከዚህ ይቀዳል። የኦነግ አመራሮች ወደ ሀረር ሄደው ብልፅግናን እንደምናሸንፍ እርግጠኛ ነን ብለዋል። የኦፌኮ ሰዎች ወደ ባሌ አምረተው የራሳችሁ መንግሥት ሊኖራችሁ ወራት ቀሩ የሚል የድል ነጋሪት ጎስመዋል። ጎንደሮች ለብልፅግና ፓርቲ ቀይ ካርድ መዘዋል። የዚህ ድምር የገዥውን ፓርቲ ሽንፈት ይወልዳል የሚል ካለ ግን ወይ ታሪክን ዘንግቷል አልያም የምናብ ፖለቲካን ከዛሬ ዘመን ሊያደርስ አምሮታል። ስድስት ነጥቦችን በመጥቀስ ብልፅግና በቀጣዩ ምርጫ እንደማይሸነፍ ልሟገት።በኢትዮጵያ 1200 ወረዳዎችና መቶ ዞኖች ይገኛሉ። በእነዚህ የመንግሥት መዋቅሮች በእያንዳንዳቸው ቢያንስ 10 የቀድሞው ኢሕአዴግ የአሁኑ ብልፅግና አባላት ይኖራሉ ብለን እናስብ። ይህ አሃዝ የመንግሥት ካድሬዎች በብዛት የሚገኙባቸውን የቀበሌ መዋቅሮች ሳይጨምር አስራ ሦስት ሺሕ ያህል ዜጎች ሕልውናቸውን ከብልፅግና ጋር ማስተሳሰራቸውን ያረጋግጣል። ለእነዚህ ወገኖች በሥልጣን ላይ ያለው ፓርቲ መሸነፍ ሕልወናቸው ላይ የሚቃጣ ጥቃት ነው።ገዥው ፓርቲ በቀጣይ አገራዊ ምርጫ ሊሸነፍ አይችልም ስንል ገለልተኛ የሆነ ቢሮክራሲ በሌለበት አገር ዴሞክራሲ ቅንጦት ስለሚሆን ብቻ አይደለም። ይልቁኑ ብልፅግና ፓርቲ ዛሬም ገለልተኛ ሊሆን የሚገባውን የፀጥታን የደኅነንት መዋቅር በቁጥጥሩ ስር እንዳዋለው ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሥልጣን በያዙ ማግስት ከፖለቲካ ነፃ የሆነ የፀጥታና የደኅነንት መዋቅር እንደሚገነቡ ቃል ቢገቡም፣ ግብራቸው ግን የዚህ ተቃሪኒ ነው።የፖሊሲ ኮሚሽነሩ ከአማራ ብልፅግና ፓርቲ፣ የደኅንነት ቢሮ ኃላፊው ከኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ መሆናቸውም ለዚህ አብነት ይመስላል። ምርጫው የጠቅላይ ሚኒስትሩን ፓርቲ አያሰጋም ስንል ሌላም ማስረጃ ልንጠቅስ እንችላለን። የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ‹ገለልተኛ ነው አይደለም› የሚለው ብዙ ሊያወዛግብ ቢችልም ቢያንስ ግን በአንድ ነገር ላይ እርግጠኛ መሆን ይቻላል። እሱም ቦርዱ አገራዊ ምርጫው ሰርገኛ መጣ በርበሬ ቀንጥሱ ሆኖበታል። በዚህ የተነሳም ትናንት ነፃና ፍትሐዊ ምርጫ እንዳይካሄድ እንቅፋት የሆኑ ሰዎችን በድጋሚ በወረዳና በዞን መዋቅሮቹ ላይ በመቅጠር ላይ ይገኛል።የአገራችን ፓርቲዎች ከምናብ ባልወረደ ሐሳባዊ መስመር ዴሞክራሲን አምጠን ልንወልድ ነው የሚል እንጉርጉሮ እንዳስደመጡን ከዛሬ ደጃፍ ደርሰዋል። ይሁን እንጂ ቃላቸው ኑፋቄ ነው። ኹለት ነገሮችን እንጥቀስ፤ የመጀመሪያው ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር ይተሳሰራል።የአገራችን ተቃዋሚ ፓርቲዎች መንግሥትን ከመኮነን የዘለለ ግብ የላቸውም። በዚህ ምክንያትም ተፎካካሪ እንጂ ተወዳዳሪ ለመሆን ብዙ ይቀራቸዋል። በነገራችን ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚጠቀሙት ተፎካካሪ ፓርቲ የሚለው ቃል በፖለቲካ ውስጥ ቅይጥ ዴሞክራሲን በሚጠቀሙ ስርዓቶች ውስጥ የሚዘወተር ነው።ስቴፈን ሌቬቲስኪ ወቅት ጠብቀው ምርጫን ለይስሙላ በሚያካሄዱ መንግሥታት ውስጥ ያሉ ፓርቲዎች ተቃዋሚ ሳይሆን ተፎካካሪ (competitive party) ተብለው ይጠራሉ ይላል። እንዲህ ያለው ብያኔ ለአገራችን ፖለቲካ በልኩ የተሰፋ ነው። መንግሥት እውነተኛ ዴሞክራሲን ለማስፈን ከፈለገ ቢያንስ ከላይ የተጠቀሱትን ቀላል ቅድመ ሆኔታዎች ሊያሟላ ይገባዋል። የአገራችን ተቃዋሚ ፓርቲዎችም ከምናብ የዘለለ እውነታን ለመጋፈጥ ከፈለጉ የኢትዮጵያን ፖለቲካ ነባራዊ ስሪት ታሳቢ ማድረግ ይኖርባቸዋል። ማስታወሻ ፦ ለጽሑፉ ማጣቀሻ ‹Six causes of transitional trauma› የሚለውን የመሐመድ አሕመድ ጽሑፍ ተጠቅሜያለሁ ።ይነገር ጌታቸው ተለያዩ መገናኛ ብዙኀን በማገልገል ላይ የሚገኙ ባለሙያ ናቸው። በኢሜል አድራሻቸው [email protected] ሊገኘኙ ይችላሉ።ቅጽ 2 ቁጥር 66 ጥር 30 2012
5ፖለቲካ
https://addismaleda.com/archives/9573
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
39d43c83dda4868ae9a0d75218a643e2
b25d33f872621da4b498e23df635d78a
የአፍሪካ ኩባንያዎች የዓለም ንግድ ድርጅትን ኢፍትሐዊ ሲሉ ወቀሱ
ቅድመ ሁኔታዎችን ለማሟላት ዓመታት የወሰዱባት ኢትዮጵያ ለአባልነት እየተጣደፈች ነውከሰሞኑ 200 የአፍሪካ ኩባንያዎችን የሚመሩ ሥራ አስፈጻሚዎች ተሳትፈውበታል በተባለ የዳሰሳ ጥናት፣ አብዛኞቹ ኃላፊዎች የዓለም ንግድ ድርጅት አፍሪካን ኢፍትሐዊ በሆኑ ሕጎችና ቅድመ ሁኔታዎች አግልሎ ቆይቷል በማለት መውቀሳቸው ተገለጸ፡፡  ከሰሞኑ የፓን አፍሪካ የግሉ ዘርፍ የንግድና የኢንቨስትመንት ኮሚቴ የተሰኘው ተቋም በቪዲዮ ኮንፈረንስ ባካሄደው ስብሰባ፣ ስለዚሁ የዓለም ንግድ ድርጅት ጉዳይ ተነጋግሯል፡፡ ይኸው ተቋም ባስጠናው ጥናት፣ አሥር ዋና ዋና የንግድና የኢንቨስትመንት ዘርፎችን የሚወክሉ ከ25 አገሮች የተውጣጡ 200 የኩባንያ ሥራ አስፈጻሚዎች የተካተቱበት ቃለ መጠይቅ ተደርጓል፡፡ ከ65 በመቶ በላይ የኩባንያ ኃላፊዎች እንደሚያምኑት፣ በዓለም ንግድ ድርጅት የሚመራው የዓለም ንግድ ሥርዓት ለአፍሪካ ፍትሐዊ አይደለም፡፡ ከዚህ በተጨማሪም 37 በመቶዎቹ እንደገለጹት፣ የዓለም ንግድ ድርጅት ዓላማውን ለማስፈጸም የተሳነውና ውጤታማነት የጎደለው ተቋም ነው፡፡ የዓለም ንግድ ድርጅት ለአፍሪካ ሸቀጦች የማይመቹ የንግድና የኢንቨስትመንት ሕግጋትን የሚተገብር፣ በርካታ አገሮች ከውድድር ውጭ እንዲሆኑ የሚያስገድዱ አሠራሮችን በመከተል አፍሪካ ከዓለም ንግድ ሥርዓት ተጠቃሚነቷ ዳር ያወጣ ተቋም እንደሆነ በመኮነን፣ ለውጥ እንዲደረግበት መጠየቃቸውን ጥናቱን ያስጠናው ተቋም ያትታል፡፡ ምንም እንኳ የዓለምን የንግድ ሥርዓት በመምራት ረገድ የዓለም ንግድ ድርጅት እንዲጫወት የተሰጠው ሚና ሰፊ ቢሆንም፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ ይህንን ኃላፊነቱን መወጣት እንዳልቻለ፣ የአፍሪካ ደካማ አገሮች ካደጉት አገሮች እኩል በፍትሐዊነት ምርቶቻቸውንና ሸቀጦቻቸውን መገበያየት የሚችሉበትን መድረክ መፍጠር ያልቻለ፣ ይልቁንም አፍሪካን እንደ ጥሬ ዕቃ ምንጭነት እንጂ በአፍሪካ ለሚመረቱ ያለቀላቸው ምርቶች በዓለም ገበያ ቦታ እንዲያገኙ የሚያስችል የእኩል መወዳደሪያ ሥርዓት መፍጠር ያልቻለና መፍትሔ አልባ ተቋም ሆኖ እንዳገኙት የድርጅት መሪዎቹ ገልጸዋል፡፡ እንዲህ ያሉ ሐሳቦች ጎልተው መውጣት የጀመሩት የዓለም ንግድ ድርጅትን በዋና ዳይሬክተርነት ለመምራት ከሚፎካከሩ ስምንት ዕጩዎች መካከል ሦስቱ ከአፍሪካ በሆኑበት ወቅት መሆኑ፣ ተቋሙ ለአፍሪካ ቦታ እንዲሰጥ የሚያስገድድ ጊዜ ላይ እንደሚገኝ የሚጠቁሙ አሉ፡፡ ተቋሙን ለመምራት ፉክክር ላይ ከሚገኙት መካከል የቀድሞዋ የናይጄሪያ የገንዘብ ሚኒስትር ንጎዚ ኦኮንጆ አይዌላ (ዶ/ር)፣ የቀድሞዋ የኬንያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር አሚና ሞሐመድ፣ እንዲሁም ግብፃዊው የሕግ አዋቂና የዓለም ንግድ ድርጅት ባልደረባ አብደልሐሚድ ማሞድሐም ትልቅ ትኩረት የተሰጣቸው ተወዳዳሪዎች ናቸው፡፡ አምባሳደር አሚና ሞሐመድ የዓለም ንግድ ድርጅት ጠቅላይ ምክር ቤትን በሰብሳቢነት መምራታቸው ብቻም ሳይሆን፣ አፍሪካ እንደ አኅጉር ካላት የውክልና መጠን ጭምር ተቋሙን የመምራት ሚና እንደሚገባት የሚሞግቱ ድምፆች ተበራክተዋል፡፡ የቀድሞውን ጠቅላላ የንግድና ታሪፍ ስምምነት (GATT) የተባለውን ተቋም በመተካት እ.ኤ.አ. ከ1995 ጀምሮ በመንቀሳቀስ ላይ በሚገኘው የዓለም ንግድ ድርጅት ውስጥ አፍሪካ የ27 በመቶ ውክልና አላት፡፡ ለታዳጊ አገሮች በተሰጠው ኮታም የአፍሪካ ድርሻ 35 በመቶ ነው፡፡ ይህ ሆኖም አፍሪካውያን በተቋሙ አመራርነትም ሆነ በተቋሙ አባልነት፣ ተቋሙ በሚያወጣው ሕጎችና ደንቦች አግባብነት በዓለም የንግድ መድረክ ያላቸው ተሳትፎ እዚህ ግባ የሚባል እንዳልሆነ በሰፊው ሲነገር ቆይቷል፡፡ እስካሁን በዓለም የንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ ሲመዘገብ የቆየው የአፍሪካ ተሳትፎና ድርሻ እያሽቆለቆለ መጥቶ፣ በአሁኑ ወቅት 2.5 በመቶ ላይ ይገኛል፡፡ ይሁን እንጂ እ.ኤ.አ. በ1960 ከ5.5 በመቶ ያላነሰ እንደነበር መዛግብይት ያሳያሉ፡፡ በአንፃሩ ከአፍሪካ ወደ ተቀረው ዓለም የሚላኩ ጥሬ ዕቃዎች፣ በተለይም ማዕድናት፣ ቡና፣ ሻይ፣ ካካዋ፣ ጥጥና መሰል ምርቶች ከአፍሪካ በገፍ ቢላኩም በዓለም ገበያ ያላቸው ድርሻ በግብርናና በጥሬ ዕቃ ደረጃ የሚወከሉ፣ ዋጋቸውም ሲበዛ ዝቅተኛ እንዲሆን በመደረጉ ለአፍሪካ ውክልና ፍትሐዊነት የጎደለው ተቋም እንደሚያሰኘው በርካቶች እየገለጹ ይገኛሉ፡፡ ይህ ጥያቄ ሲብላላ በኖረበት ወቅት እ.ኤ.አ. ከ2013 ጀምሮ የዓለም ንግድ ድርጅትን ሲመሩ የቆዩት ብራዚላዊው ሮቤርቶ ዳ አዝቬዶን ለመተካት አፍሪካውያኑ ተወዳዳሪዎች የተሻለ ድምፅና ድጋፍ ያገኛሉ ተብለው እንዲጠበቁ፣ የዓለም ንግድ ድርጅትንም ይበልጥ ፍትሐዊ እንዲሆን ለማድረግ የሚያስችል ዕድል ያስገኛሉ የሚል ተስፋ ተበራክቷል፡፡   ምንም እንኳ የአፍሪካ አገሮች በዓለም የንግድ ሥርዓት ውስጥ ይህ ነው የሚባል ድርሻ ባይኖራቸውም፣ እርስ በርሳቸውም እንደ ልብ አለመገበያየታቸውም ጥያቄ እያስነሳ ይገኛል፡፡ ይህንን የሚቀይር ሁኔታ እንደሚፈጠር የሚታመንበት አኅጉራዊው የአፍሪካ ነፃ የንግድ ስምምነት በበርካታ አገሮች ፀድቆ ለትግበራ ሽር ጉድ እያለ ነው፡፡ ኢትዮጵያ በዚህ ሁለት ተቋማት ውስጥ በመሪነትም በተሳታፊነትም ያላት ሚና ይህ ነው የሚባል ባይሆንም፣ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን እየተጣደፈች ትገኛለች፡፡ ከሁለት ዓመታት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ሒደቱን አጠናቃ መደበኛ አባል ለመሆን ዝግጅት ላይ ስለመሆኗ መንግሥት አስታውቋል፡፡ የዓለም ንግድ ድርጅት ህልውናና እንደ ተቋም የመኖሩ አስፈላጊነት ጥያቄ ቢነሳበትም፣ አገሮች አባል ለመሆን የሚያስፈልጉ መሥፈርቶችን ለማለፍ በርካታ መሥፈርቶችንና ቅድመ ሁኔታዎችን ለማሟላት ይጣደፋሉ፡፡ በምርትና በአገልግሎት መስክ የሚጠየቁ የታሪፍ፣ የጥራትና የዋጋ ጥያቄዎች ላይ ለሚቀርቡላቸው የድርድር ጥያቄዎችና የሕግ ማሻሻዎች ክለሳ በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡ ኢትዮጵያም ይህንኑ ስታደርግ ሰንብታለች፡፡ ይህም ሆኖ የዓለም ንግድ ድርጅትን ፋይዳ ጥያቄ ውስጥ ከከተቱ ኹነቶች መካከል በአሜሪካና በቻይና መካከል የተካረረው የንግድ ጦርነት፣ ለአፍሪካ ምርቶችና ሸቀጦች የሚሰጠው የዋጋና የጥራት ቅድመ ሁኔታዎች ተቋሙን እግር ተወርች የሚያስሩ ችግሮች ሆነው የረባ ምላሽና መፍትሔ ያልሰጠባቸው ናቸው፡፡
3ቢዝነስ
https://www.ethiopianreporter.com/article/19859
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
b2b6a5bada5d926a74d14286eaf0a106
77b518122d9a33c991e435a789199ae9
የዑጋንዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ሰላማዊ ምርጫ እንደተካሄደ ለሕዝቡ ማረጋገጫ ሰጥተዋል
የዑጋንዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ሩሀካና ሩጉንዳ ነገ በሀገሪቱ የሚካሄደው ፕረዚዳንታዊና ምክር ቤታዊ ምርጫ ሰላማዊ እንደሚሆን ለሕዝቡ ማረጋገጫ ሰጥተዋል። ለመምረጥ የተመዘገቡት ዑጋንዳውያን በሙሉ ድምጽ ለመስጠት እንዲወጡ ጥሪ አድርገዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪውን ያቀረቡት በነገው ምርጫ ብጥብጥ ሊኖር ይችላል የሚለውን ስጋት መሰረት በማድረግ ነው። የሚያሰጋ ነገር የለም ሲሉም ሕዝቡን አረጋግተዋል።“እኔ በበኩሌና መንግሥት ሁሉም ለመምረጥ የተመዘገቡት ዜጎች በብዛት ወጥተው የፈለጓቸውን ተወዳዳሪዎችና ፓርቲዎች እንዲመርጡ እናበረታታለን” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።የዑጋንዳ ፖሊሶች ትላንት ዋናው ተቃዋሚ ተወዳዳሪ የዲሞክራስያዊ ለውጥ መድረክ የተባለው ፓርቲ መሪ ኪዛ ቤሲጄና ደጋፊዎቻቸው የመጨርሻ የምርጫ ዘመቻ ለማድረግ ሲሞክሩ በአንዳንድ የካምፓላ ክፍሎች ተደራሽነት እንዳያገኙ አግደዋቸዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ሩጋንዳ ታድያ ድርጊቱ ያሳዝናል ካሉ በኋላ ቤሲጄና ደጋፊዎቻቸውም ቢሆኑ በካምፓላ የቢዝነስ ወረዳ ዘመቻ ማካሄድ አልነበረባቸውም ሲሉ አስገንዝበዋል።
4ዓለም አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/uganda-prime-minister-assures-citizens-of-peaceful-election/3195399.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
b01f8ba704d66d6276f3706d242f9fa7
567b660625d39dc6c4110a6002b14edf
የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የኢትዮጵያን ምስል በአለም አቀፍ ደረጃ በበጎ የሚያመላክት መሆኑ ተገለፀ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅ የኢትዮጵያን ምስል በአለም አቀፍ ደረጃ በበጎ የሚያመላክት መሆኑን የታሪክ መምህርና ተመራማሪዉ ተባባሪ ፕሮፌሰር ከተቦ አብዲዮ ተናገሩ።አሁን ላይ ግንባታው 74 በቶ የደረሰው ታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ አሁንም ተጠናክሮ ቀጥሏል።በግድቡ የግንባታ ሂደት ዙሪያ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ክፍሌ ሆሮ፥ የዋናዉ ግድብ ኮንክሪት ሙሊት ስራ በጥሩ አፈጻጸም ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።ግድቡ በመጀመሪያውን ሃይል ማመንጨት የሚያስችለዉ እና ውሃ የሚተኛበትን ቦታ ለማመቻቸት የደን ምንጣሮ ዝግጅት እንደተጠናቀም ነው ኢንጅነር ክፍሌ ሆሮ ያነሱት።አሁን ላይ አጠቃላይ ግንባታው 74 በቶ የደረሰዉ ታላቁ የህዳሴ ግድብ፤ የብረታብረት ፣የኤሌክትሮ መካኒካል እና ሌሎች ስራዎች እየተከናወኑለት ይገኛል።ታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ሃገራዊ አንድነትን ከማረጋገጡ ባሻገር፣ አፍሪቃዉያንን የሚያስተሳስር አሻራ እንደሚሆን ይታመናል።በግድቡ ግንባታ ዙሪያ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት የታሪክ መምህርና ተመራማሪዉ ተባባሪ ፕሮፌሰር ከተቦ አብዲዮ፥ የግድቡ መጠናቀቅ የኢትዮጵያን ምስል በአለም አቀፍ ደረጃ በበጎ የሚያመላክት ነው ብለዋል።ግድቡ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ያሳተፈ መሆኑ የኔነት ስሜትን ፈጥሯል ያሉ ሲሆን፥ አባይ ከኢትዮጵያውያን ባሻገር አፍሪካውያንን የሚያገናኝ ቅርስ እንደሆነም ተባባሪ ፕሮፌሰር ከተቦ አብዲዮ ተናግረዋል።በአወል አበራ
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%8b%a8%e1%88%85%e1%8b%b3%e1%88%b4-%e1%8c%8d%e1%8b%b5%e1%89%a5-%e1%88%98%e1%8c%a0%e1%8a%93%e1%89%80%e1%89%85-%e1%8b%a8%e1%8a%a2%e1%89%b5%e1%8b%ae%e1%8c%b5%e1%8b%ab%e1%8a%95-%e1%88%9d%e1%88%b5/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
eaf40d118fc5947fb432f98cb6641701
57f6b6da8b752d66ff4850c19a43c549
‹‹የኢትዮጵያና አሜሪካ ግንኙነት የወዳጅነትና የመፈቃቀድ እንጂ የግዴታ አይደለም››- ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖበአአዩ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህርና የዓባይ ውሃ ጉዳይ ተመራማሪ
አዲስ አበባ፡- ‹‹ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ያላት ግንኙነት የወዳጅነትና የመፈቃቀድ ነው እንጂ የግዴታ አይደለም።›› ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህርና የዓባይ ውሃ ጉዳይ ተመራማሪው ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ ገለፁ።ፕሮፌሰር ያዕቆብ ሰሞነኛና ወቅታዊ አጀንዳ የሆነውን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በተመለከተ ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደተናገሩት፤ አሜሪካ ለኢትዮጵያ ልትጠቅም የምትችለውን ያህል ኢትዮጵያም ለአሜሪካ ልትጠቀም ትችላለች። በመሆኑም ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ያላት ግንኙነት የወዳጅነትና የመፈቃቀድ እንጂ የግዴታ አይደለም።‹‹ አሜሪካ የራሷን የኢኮኖሚ ጥቅም እንዲሁም ነፃነቷን ትወዳለች፤ የዚያኑ ያህል ኢትዮጵያም በተመሳሳይ ነፃነቷን የምትወድና ተከብራ የኖረችም አገር ጭምር መሆኗን አሜሪካ ማወቅ አለባት።›› ያሉት ፕሮፌሰሩ፣ በቅርቡ ኢትዮጵያ፣ ግብጽና ሱዳን በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ሲደራደሩ በታዛቢነት የተሰየመችው አሜሪካ ባሳለፈችው ለግብጽ የወገነ ውሳኔ የአሜሪካ ታዋቂ ግለሰቦችና ይህን ሐሳብ የማይደግፉ ወገኖች ጭምር አሜሪካንን በመተቸት ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።ፕሮፌሰሩ፣ አሜሪካ በታዛቢነት ጀምራ ወደ አደራዳሪነት ብሎም ሰነድ በማዘጋጀት ወደ አስፈራሚነት የመምጣቷ አካሄድ በኢትዮጵያ መንግሥት ተቀባይነት ማጣቱ ተገቢ እንደሆነ አመልክተዋል። በጉዳዩ ዙሪያ በአሁኑ ወቅት ያለው የአሜሪካ አስተዳደር የተሳሳተ እንደሚመስላቸውም ገልፀዋል። የአሜሪካ የፖለቲካ ተቋማት የሚደግፉት አይነት አሠራር ጭምር አለመሆኑን በምክንያትነት ጠቅሰዋል። ለወደፊት ስህተቱ ተስተካክሎ በሁለቱ አገራት መካከል የተሻለ ግንኙነት ይፈጠራል ብለው እንደሚያምኑም አስረድተዋል። እንደ ፕሮፌሰር ያዕቆብ ገለፃ፤ አሜሪካ በወሰደችው አቋም ምክንያት ኢትዮጵያ የያዘችው አቋም የዚያን ያህል የሁለቱን አገሮች ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ይጎዳዋል ተብሎ አይታሰብም። ይሁንና ጉዳት ሊኖረው ቢችል እንኳ ኢትዮጵያ ጥርሷን ነክሳ መቻል ይኖርባታል። ባስ የሚል ከሆነ ደግሞ የራሷን አማራጭ ትፈልጋለች እንጂ ለልጅ ልጆቿ የሚተርፍ ዕዳ ተሸክማ አትዘልቅም። ይህን ማንም ኢትዮጵያዊ አይፈቅድም።‹‹አሜሪካ አልፋ ጫና ማሳደሩን የምትገፋበት ከሆነ ግን ኢትዮጵያ እንዲህ አይነት ጣልቃ ገብነት በፍፁም የማትቀበል አገር ናት፤ ይህም በዓለም ዘንድ የታወቀ ነው። ምክንያቱም አንድን ጉዳይ አገራት በስምምነትና በመነጋገር እንዲሁም በወዳጅነት መንፈስ የመፈፀምን መንገድ የሚያበላሽ ነው። ስለዚህም ኢትዮጵያ የምትኖረው በአሜሪካ በጎ ፈቃድ ሳይሆን በራሷ ጥንካሬ ነው።›› ሲሉ ፕሮፌሰር ያዕቆብ አብራርተዋል።የኢትዮጵያ መንግሥትም ሆነ ህዝቡ የአገሪቱን ልማት፣ ዕድገትና ብልጽግና ወደፊት ለማስቀጠል ጠንክረው መሥራት እንደሚጠበቅባቸው ተናግረው፤ ኢትዮጵያ ከጎረቤት አገሮችም ሆነ በሩቅ ካሉ አገሮች ጋር በስምምነትና በወዳጅነት መንፈስ እንዲሁም በመተጋገዝና በመተባበር የመቀጠል ፍላጎት እንዳላት አስረድተዋል።ሰሞኑን የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በተመለከተ የአሜሪካ የገንዘብ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ኢትዮጵያ በሦስቱ አገሮች መካከል ስምምነት ሳይፈረም በፊት በታላቁ የህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሊትና መሰል ሥራዎች ማከናወን እንደሌለባት መግለፁ ይታወቃል። ይህ መግለጫ በኢትዮጵያ ዘንድ ተቀባይነት እንዳላገኘም ይታወሳል።አዲስ ዘመን መጋቢት 1/2012አስቴር ኤልያሰ
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=28805
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
b73f6d487fdf2a89f063fb930f52d9be
d7ec5624116fed6c0bc8326f364e3e14
ኢትዮጵያ የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ለመከላከል የሚያስችሉ የህክምና ቁሳቁሶች ድጋፍን ለጅቡቲ አደረገች
አዲስ አበባ ፣ሰኔ 18 ፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት የሚያስችሉ የህክምና ቁሳቁሶች ድጋፍን ለጅቡቲ አደረገች።ኢትዮጵያ የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ለመከላከልና በሽታው ከተከሰተ በኋላም ምላሽ ለመስጠት የሚያስችሉ ግምቱ ከ300 ሺህ የአሜሪካን ዶላር በላይ ዋጋ ያለው ልዩ ልዩ የህክምና መስጫ መድሀኒቶችንና ቁሳቁሶችን  ዛሬ ለጅቡቲ ዕርዳታ ሰጥታለች ፡፡እርዳታውን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ዛሬ ጅቡቲ በመገኘት አስረክበዋል፡፡አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን  በርክክብ ሥነ-ስርዓቱ ላይ ÷ሁለቱ አገራት ስትራቴጂያዊ አጋርነት በመልካም ጊዜ ብቻ ሳይሆን እንደ ኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በሚከሰትባቸው አስከፊ ወቅቶችም በጋራ የሚቆሙ መሆናቸውንና የዛሬው ድጋፍም የዚሁ ማሳያ መሆኑን  አንስተዋል፡፡ሁለቱ አገራት የጋራ ድንበር የሚጋሩ ከመሆናቸው አንጸር በሽታውን ለመከላከል በጋራ ተባብረው መስራት ይገባቸዋል ብለዋል።ከዚያም ባለፈ በቀጣይም በጤናና ሌሎች ዘርፎች የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ማጠናከር እንደሚገባቸው ገልጸዋል፡፡በተያያዘ ዜና አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከጅቡቲ የውጭ ጉዳይና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር መሀመድ የሱፍ ጋር በሁለትዮሽ ግንኙነት አካባቢያዊ እና ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡በወቅቱም አምባሳደር ሬድዋን ሁለቱ አገራት የጋራ ባህል፣ ቋንቋ እና ታሪካዊ ዳራ የሚጋሩና ስትራቴጂክ አጋር መሆናቸውን ጠቅሰው በሁሉም መስኮች ያሉትን የሁለቱን አገራት ግንኙነቶች አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ አንስተዋል፡፡አያይዘውም የሁለትዮሽ ግንኙነቱን የበለጠ ለማጠናከር በኢትዮጵያ በኩል ያለውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል፡፡የጅቡቲ የውጭ ጉዳይና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር ሙሀመድ የሱፍ በበኩላቸው ÷ኢትዮጵያ በዕርዳታ መልክ ላቀረበቻቸው የህክምና ግብዓቶች በጅቡቲ መንግስትና ህዝብ ስም የላቀ ምስጋናቸውን በማቅረብ ይህ ዓይነቱ ተግባር የሁለቱን አገራት ጥብቅ ወዳጅነት ማሳያ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡በተጨማሪም ጅበቲ እንደቀድሞ ሁሉ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም እንደምታከብርና በዓለም አቀፍ መድረኮች ላይም ከጎኗ እንደምትቆም አረጋግጠዋል፡፡በቀጣይም ሁለቱ አገራት በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት መስኮች ያሉትን ትብብሮች ይበልጥ ለማጠናከር ብሎም በቀጠናው ውስጥ ሰላምና ጸጥታን ለማስፈን ከመቼውም ጊዜ በላይ ተቀራርቦ ለመስራት ያላቸውን ቁርጠኝነት  ማረጋገጣቸውን ከውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%8a%a2%e1%89%b5%e1%8b%ae%e1%8c%b5%e1%8b%ab-%e1%8b%a8%e1%8a%ae%e1%89%aa%e1%8b%b5-19-%e1%8b%88%e1%88%a8%e1%88%ad%e1%88%bd%e1%8a%9d%e1%8a%95-%e1%88%88%e1%88%98%e1%8a%a8%e1%88%8b%e1%8a%a8/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
1aedb06c6a518ce24777b957745b4f93
39d5974c3517a8c9ca81764ab98801b4
ከመቶዎች እስከ መቶ ሺህ ብሮች የሚንቀሳቀስበት የቀብር ማስፈጸም አገልገሎት ልክ እንደተለያዩ ግብይቶች ሁሉ የቀብር ሥርዓትም የግለሰቦች አቅም የሚታይበት እየሆነ መጥቷል።
ከመቶዎች እስከ መቶ ሺህ ብሮች የሚንቀሳቀስበት የቀብር ማስፈጸም አገልግሎት\nእንደ አንዳንድ 'ቢዝነሶች' የቀብር አፈጻጸሙ ደረጃና አይነት አለው። እጅ ያጠረው የሟች ቤተሰብ 'እንደነገሩ' ቀብር ለማከናወን ቢያንስ 7 መቶ ብር ያስፈልገዋል። የለም 'ሞትና ሠርግ አንድ ነው' ቀብሩ ደመቅ ይበል መታሰቢያውም ይጉላ ያለ አቅም ያለው የሟች ቤተሰብ ደግሞ በመቶ ሺዎች የሚቆጠር ብር ከኪሱ ማውጣት ይጠበቅበታል። ታዲያ የሥርዓቱን ደረጃ የሚለዩት ቀብሩን ለማከናወንና ለቀስተኛን ለማስተናገድ ጥቅም ላይ የሚሉ ነገሮች ናቸው። የቀብር አፈጻጸም ደረጃና ዓይነቶች ነጋሽ ደገፉ ጠቅላላ የቀብር አስፈጻሚ ድርጅት በአዲስ አበባ ከሚገኙ የቀብር አስፈጻሚዎች አንዱ ነው። የድርጀቱ ሥራ አስኪያጅ ኃይሉ ነጋሽ አባታቸው የጀመሩት ይህ ሥራ አርባ ዓመታት ማስቆጠሩን ይገልጻሉ። አባታቸው በዚህ ሥራ ቀዳሚ ከሆኑት መካከል እንደሚመደቡም ይናገራሉ። እሳቸውም ቢሆኑ ቀብር ማስፈጸም 'ጥርሳቸውን የነቀሉበት' ነው - ከ25 ዓመታት ለሚልቅ ጊዜ በሥራው ላይ ቆይቷል። በአራት የተለያዩ ቦታዎች ሱቆች ከፍተው እየሰሩም ይገኛሉ። የቀብር ሥርዓትን በተሽከርካሪዎች እና በቅብር አስፈጻሚዎች 'ማጀብ' እየተለመደ ነው የሚሉት አቶ ኃይሉ ሥርዓቱ በተለያየ ደረጀና አይነት እንደሚፈጸም ያስረዳሉ። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለጻ የአገልገሎቱን ደረጃና ዋጋ ከሚወስኑት መካከል አንዱ የቀብር ሥርዓቱ የሚታጀብበት ተሽከርካሪ አይነትና ብዛት ነው። "አንድ ጥቁር የቀብር ቶዮታ ዶልፊን መኪና ሱፍ ለብሰው አስከሬን የሚያጅቡ ፕሮቶኮሎች ሳይኖሩ ቢፈለግ እንደቦታው ርቀት ነው፤ አንድ ሺህ ብር ወይም አንድ ሺህ ሁለት መቶ ብር ይሆናል" ሲሉ ያስረዳሉ። ተሸከርካሪው አይነት ሃይውንዳይ ወይም መሴዲስ ቢሆን ዋጋው እንዲሁ ከፍ ይላሉ። ይህ የሬሳ ሳጥንና ሌሎች ወጪዎችን አይጨምርም። ስለዚህ ተጠቃሚው "የሚወስደው የሳጥን ደረጃ፣ የሚጠቀመው የመኪና አይነት፣ የዲኮሬሽን [የማስጌጭያ] አበባ አይነትና መኪና ላይ የሚደረገው የሟች ፎቶ አጠቃቀም ላይ የሰው ፍላጎት ይለያያል" ሲሉ የሚያስረዱት አቶ ኃይሉ አገልገሎቱ በአማካይ ከ11 እስከ 20 ሺህ በር ሊያስወጣ እንደሚችል ገልጸዋል። ቀብር የማስፈጸም ሥራ የሬሳ ሳጥንን ከማቅረብ ድንኳንን ጨምሮ የድግስ ዕቃዎችን እስከ ማከራየት እንደሚዘልቅ የሚያስረዱት አቶ ኃይሉ፤ የተሟላ አገልገሎት ሰጥተው "በአንድ ሥራ ላይ እስከ ሦስት መቶ እና አራት መቶ ሺህ ብር" ተከፍሏቸው የሰሩባቸው ወቅቶች እንዳሉ ተናግረዋል። በዚህ ዋጋ የሚሰጠውን 'ሙሉ' አገልግሎት "ብዙ ጊዜ የሚውስዱት ውጭ አገር የሚኖሩና እድር የሌላቸው ሰዎች ናቸው" የሚሉት አቶ ኃይሉ ይህም የምግብ አገልግሎትን እንደሚጨምር ይጠቅሳሉ። የሬሳ ሳጥኖች ደረጃና ዋጋ የሬሳ ሳጥኖች በአገር ውስጥ እንደሚሰሩና ከውጭም እንደሚገቡ ያሉ ሲሆን ዋጋቸው እንደ ጥራት ደረጃቸው ይለያያል። ከዚህም ባሻገር የሳጥኖቹ 'ዲዛይን' ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለና እየተለወጠ ይገኛል። "ሳጥን ማለት እኮ ልክ እንደሶፋ ማለት ነው። የድሮና የአሁን የሶፋ ዲዛይን አንድ አይደለም። ሙያተኞቹም ከኢንተርኔት በማውረድና አንዱ ከአንዱ በመቀያየር ነገሩ እየሰፋ ሄዷል" ይላሉ አቶ ኃይሉ። ታዲያ ዝቅተኛ የጥራት ደረጃ ያለው የሬሳ ሳጥን ከ700 መቶ ብር እስከ 3 ሺህ ብር ሲሸጥ ከፍተኛ ጥራት ያለውና ከውጪ አገር የገባ ሳጥን ደግሞ እስከ 150 ሺህ ብር ያወጣል። "እኛ ማንኛውም ሰው እንደ አቅሙ የሚጠቀምበት አገልግሎት ይዘን ነው የምንንቀሳቀሰው" ሲሉም ያስረዳሉ። በከፍተኛ የጥራት ደረጃ የተቀመጠ ሳጥን በቀለሙ፣ በግዝፈቱና 'በዲዛይኑ' የሚለይ ሲሆን ከ80 ሺህ 150 ሺህ ባለው ዋጋም ይሸጣል። "ቀብር የማስፈጸም ሥራ እንደማንኛውም ቢዝነስ...
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
cffa3020280abedcdb0fd96a3eafc224
3ffb48e9d7b5972bf4d45121219e5bbb
ትራምፕ ምርጫውን እስከአሁን በምርጫ መሸነፋቸውን አላመኑም
የዶናልድ ትራምፕ በምርጫ መሸነፍ በዓለም ላይ ያለውን ሕዝብኝነትና አክራሪነትን ሊገታ እንደሚችል ተገለጸ፡፡ ትራምፕ ላለፉት ዓመታት ለቀኝ አክራሪ ሕዝበኞች እንደ መለኪያ አሊያም እንደ ማጣቀሻ እንደሚታዩ ሲኤንኤን በሰራው የትንታኔ ዘገባ ገልጿል፡፡ እንደ ዘገባው ከሆነ ንቅናቄው በትራምፕ ባይጀመርም እርሳቸው ግን ይህንን በፍጥነት እንዲዛመት አድርገውታል፡፡ትራምፕ ይህንን ያደረጉት የአሜሪካን ልዕለ ሃያልነት ተጠቅመው እንደሆነም በዘገባው ተጠቅሷል፡፡ በአሜሪካ በተካሄደው ምርጫ ትራምፕ መሸነፋቸው በዓለም ዙሪያ የእርሳቸውን ሀሳብ በመደገፍ ሕዝበኝነትን ሲያስፋፉና በአደባባይ ሲሰብኩ ለነበሩ መሪዎች ትልቅ ኪሳራ ነውም ተብሏል፡፡ትራምፕ ሲጠቀሟቸው የነበሩ ጸረ ስደተኛ፣ጸረ ጾታ፣ መጤ ጠልነት እና ሌሎችም መሪዎች አጉልተው ሲናገሯቸው እንደነበር ቢገለጽም እነዚህ ግን አብረው ይሸነፋሉ ተብሏል፡፡ ምንም እንኳን ከምርጫው ውጤት ጋር በተያያዘ እነዚህ የሕዝበኝነት ንግግሮች መገታት ቢችሉም ከስር መሰረታቸው ግን ላይጠፉ ይችላሉ ነው የተባለው፡፡ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ይህንን ሕዝበኝነትና ቀኝ አክራሪነት በተወሰነ መልኩም ቢሆን ቀንሶት እንደነበር ዘገባው ገልጿል፡፡ ይህ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ለአሜሪካ የዘንድሮ ምርጫ አይነተኛ ምክንያት መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡ ትራምፕ ወረርሽኙን ለመከላከል የወሰዱት እርምጃ ደካማ በመሆኑ በምርጫው ውጤት ላይ ተጽዕኖ ነበረው ተብሏል፡፡ በአጠቃላይ ዶናልድ ትራምፕ ከአራት ዓመት በፊት ኋይት ሀውስ ከገቡበት ጊዜ ጀምሮ ዘረኝነትና ሕዝበኝነትን ሲሰብኩ መቆየታቸው ቀኝ አክራሪዎች በውስጥ የነበረውን ፍላጎታቸውን ወደ አደባባይ እንዲያወጡት አድርጎ ነበር የሚሉ ተንታኞች አሉ፡፡ ይህ በመላው ዓለም አቆጥቁጦ የነበረው ሕዝበኝነት ታዲያ አሁን ላይ በአደባባይ ያቆጠቆጠውን ያህል ባይጠፋም እንደሚከስም ይጠበቃል፡፡ ትራምፕ ቅድሚያ ለአሜሪካ የሚለው ፖሊሲያቸው ከአክራሪዎች እና ሕዝበኞች አድናቆት ቢያስገኝላቸውም አሁን ግን ከኋይት ሀውስ ሊያስወጣቸው ነው፡፡ምንም እኳን እስካሁን በምርጫው መሸነፋቸውን በይፋ ባያምኑም፡፡
5ፖለቲካ
https://am.al-ain.com/article/trump-s-election-loss-will-negatively-impact-populism
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
419d6ab4bc3b38f0ee1c7ae97adae43e
82b824cabb8c5f0a7fb28cfa1b84a4f7
ቱልት
ቱልት ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ተክል ነው። የተክሉ ሳይንሳዊ ጸባይ አስተዳደግ የእርሻና የመናኸሪያ አረም ነው። በብዛት የሚገኝበት መልክዓ ምድር በእስያ ደግሞ በ1000-4300 ሜትር ከፍታ፣ በዳገት፣ እርጥብ ሸለቆ፣ በጉድጓድ ይገኛል። የተክሉ ጥቅም መርዝን የሚሽር እንዲሁም የሚያስቀምጥ መድሃኒት ነው። በባሕላዊ መድኃኒት፣ ሥሩ ለአሚባ ተቅማጥ ይኘካል። የሥሩም ጭማቂ ለቁርባ ወይም ለአንቃር ብግነት («እንጥል ሲወርድ») ይጠጣል። የኢትዮጵያ እጽዋት ተቅማጥ
null
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
1b2073b0fa8a945c5318a4b42674e83a
b5e91a8929b1de236b403d0fe09a95b8
ታንዛኒያ የሚገኙ ቡሩንዲያውያን ስደተኞች ሥጋት
ምዕራብ ታንዛንያ የሚገኘው ኢንዱታ ካምፕ የተጠለሉት ሪኖቫት እንዱዋዮ የሚባሉ ስደተኛ የታንዛንያ መንግሥት ከቡሩንዲ መንግሥት ጋር ተባባሮ በግድ ሊመልሰን እንደሆነ ግልጽ ነው ብለዋል።የታንዚንያ የሀገር ግዛት ሚኒስትርና የቡሩንዲ አቻቸው የፈረሙት ሥምምነት ዕሁድ ዕለት ይፋ ሆኗል። በሳምንት ሁለት ሺህ ስደተኞች ይመለሳሉ ነው የተባለው።የታንዛንያው የሀገር ግዛት ሚኒስትር ሉጎላ ሲናገሩ ሁለቱ መንግሥታት ተደራደረው ስምምነቱ ላይ የደረሱት የቡሩንዲ የፀጥታ ሁኔታ አርኪ ደረጃ ላይ መሆኑን ስላመኑ ነው ብለዋል። ስደተኛው ግን ፀጥታው አልተሻሽለም አብዛኞቻችን መመለስ እንፈልግም ብለዋል። ከዜና ዘገባዎች የምንሰማው ሰዎች እንደሚገደሉ የደረሱበት እንደሚጠፋ ከህግ ውጭ እንደሚታሰሩ ነው ሲሉ አስረድተዋል።ባለፈው ሰኔ ወር ሂዩማን ራይትስ ዋች ባወጣው ሪፖርት፣ የቡሩንዲ ባለሥልጣናት እና የገዢው ፓርቲ ወገን የሆኑ ወጣቶች፣ የተቃዋሚ ፖለቲካ ቡድን አባላትን ናቸው ተብለው የጠረጠሩዋቸውን በርካታ ሰዎች ደብደባዋል፣ ገድለዋል፣ በዘፈቀደ አስረዋል፣ ደብዛቸውን አጥፍተዋል ሲል ወንጅሉዋል። የታንዛኒያ መንግሥት አስገድዶ የሚመልሰን ከሆነ የተመድ የስደተኞች ኮሚሽነር ወደሌላ የምስራቅ አፍሪካ ሃገር እንዲያዛውረን እንጠይቃለን ብለዋል ስደተኛው።/ዩኤንኤችሲአር/ ስለሁለቱ ሃገሮች ስምምነት እስካሁን አስተያየት አልሰጠበትም። የቡሩንዲ የሰብዓዊ መብት ረገጣ ሰለባዎች ተሟጋች ጠበቆች ህብረት የተባለ ድርጅት የታንዛንያን መንግሥት በዓለምቀፍ ፍርድ ቤቶች እንከሰዋለን ሲል አስታውቋል።
4ዓለም አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/burundi-refugees-repatriate-8-28-2019/5060323.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
85b66955e5e28abf5d8f02c7bf77ae31
286f3c3cf80fa0a43919e89871f381ae
ዩናይትድ ስቴትስ ሶማሊያ ውስጥ ባደረሰችው የአየር ጥቃት የአልሸባብ አባላት ተገደሉ
ዩናይትድ ስቴትስ ትናንት ሶማሊያ ውስጥ ባደረሰችው የአየር ጥቃት አራት የፅንፈኛው አልሸባብ አባላት መግደሏን እና ዋና ከተማዋ ሞቃዲሾ አቅራቢያ ፈንጂ ጭኖ ይጓዝ የነበረ መኪና ማውደሟን የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ዕዝ ዛሬ አስታወቀ፡፡የአየር ጥቃቱ የተካሄደው ከሞቃዲሾ በስተምዕራብ ሃያ አምሥት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ አካባቢ ሲሆን መኪናው ላይ የተጫነው ፈንጂ፣ ሞቃዲሾ ውስጥ በሲቪሎች ላይ ሊደርስ የሚችል ጉዳት መከላከሉን ዕዙ አስታውቋል።የአፍሪካ ዕዙ ባወጣው መግለጫ ከሶማሊያ ፌዴራል መንግሥት ጋር በማስተባበር በተካሄደው የአየር ጥቃት አንድም ሲቪል ሰው እንዳልተገደለ አውቀናል ብለዋል፡፡ባለፈው ዓመት ውስጥ ዩናይትድ ስቴትስ በሽብርተኛው አልሸባብ እና ቁጥራቸው እየጨመረ በመጣው ከእስላማዊ መንግሥት ቡድን ጋር የተቆራኙ ተዋጊዎች ላይ ከሠላሣ በላይ መሰል የአየር ጥቃቶች አድርሳለች።ዕሁድ ዕለት ደቡባዊ ሶማሊያ ውስጥ በተካሄደ የአየር ጥቃት ኪስማዮ አቅራቢያ አሥራ ሦስት የአልሸባብ ተዋጊዎች መገደላቸው የዩናይትድ ስቴትስ የመከላከያ ሚኒስቴር ገልፀዋል።
4ዓለም አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/us-airstrike-kills-four-al-shabab-militants-destroys-bomb-near-mogadishu-12-28-2017/4182771.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
2edf3863e641f2cdac7458503af20ece
cffbebb1be5d01994067d058c93a0179
ሰነተር ክሩዝ ድጋፋቸውን ለሬፖብሊካኑ እጩ ባለመስጠታቸው ተቃውሞ ገጠማቸው
የሪፐብሊካን ፓርቲውን ፕሬዝደንታዊ ፉክክር እጩ የዶናልድ ትራምፕን መመረጥ መቀበላቸውንና ማጽደቃቸውን በይፋ ያሳውቃሉ ተብሎ ተጠብቀው የነበሩት የቴክሳሱ ሴናተር ቴድ ክሩዝ የተጠበቀባቸውን ባለማድረጋቸው ከትራምፕ ደጋፊዎች ጩኸት ተነስቶባቸዋል። የፓርቲው የምክትል ፕሬዝደንትነት እጩ ማይክ ፔይንስ ባደረጉት ንግግር ዶናልድ ትራምፕን ተዋጊና ድል አድራጊ ሲሉ ጠርተዋቸዋል። ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።
4ዓለም አቀፍ ዜና
https://amharic.voanews.com//a/republican-national-convention-and-donald-trump-nominee/3429323.html
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
22880256c7a7786598133ef83f158a26
8861efd99ea6d25e1e3263d56ef020a9
"መኖር የምፈልገው ልጆቼን ለማየት ብቻ ነው"
የአዲስ ዓለም ትንሿ ልጁ ወታደር ናት ከሁለት ዐሥርታት በላይ ተቋርጦ የነበረው የኢትዮጵያና ኤርትራ ግንኙነት ወደ ሰላም መመለሱና ጦርነቱንም ለማቆም የፈረሙት ስምምነት ተከትሎ የአዲስዓለም ተስፋ ታደሰ። ቤተሰቦቹን በዓይነ ሥጋ የማግኘት ተስፋው አንሰራራ። በሚቀጥለው ሳምንት እንደሚጀመር የሚጠበቀው የአየር በረራ ብዙ ቤተሰቦች እንዲናፍቁት የኾነውም ለዚሁ ነው። • የኢትዮጵያና ኤርትራን የአብሮነት እርምጃ ምን ይፈትነዋል? ለዓመታት ተቋርጦ የነበረው የስልክ ግንኙነት መመለሱ ጋር ተያይዞ ብዙዎች ናፍቆታቸውን በስልክ ለመወጣት ቢሞክሩም በድንበሩ ጦርነት ትዳሩ የፈረሰዉና ቤተሰቡ ለሁለት የተከፈለው አዲስዓለም ግን አሁንም በጉጉት እየጠበቀ ነዉ። በሁለቱ አገራት ጦርነት ምክንያት ከመቶ ሺዎች በላይ ሰዎች ሕይወት ጠፍቷል፤ ኢኮኖሚያዊ ኪሳራን አስከትሏል፤ ከዚህም በላይ በሕዝቦች መካከል መቃቃርን ፈጥሮ የጠላትነት ስሜት እንዲጎለብት አድርጓል። አዲስ ዓለም የደረሰበትን ሁኔታ በአንደበቱ እንዲህ ይተርከዋል። • ወደ አሥመራ ለመጓዝ ማወቅ የሚገባዎ 6 ነጥቦች ሁለት ወንድሞቼን በዚህ ጦርነት አጥቻለሁ። የጦርነቱ ጦስ ቤተሰቤንም አሳጥቶኛል። ከባለቤቴ ምፅላል ጋር የተጋባነው በ1972 ዓ.ም ነው። ሁለት ሴትና አንድ ወንድ ልጅም አፍርተናል። በ1994 ዓ.ም ወደ ኤርትራ ሁለት ሴት ልጆቼን ይዛ ከሄደች በኋላ ተያይተን አናውቅም። ኤርትራዊ በመሆንዋ ከምታስተምርበት ሥራ ስትባረር፤ ካገርም ሊያባርሯት ይችላሉ ብዬ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢትዮጵያዊ አግብታ እንደምትኖር ወረቀት አዘጋጅቼ ነበር። ከአንድ ዓመት በፊት ግን ኤርትራ ባካሄደችው ሕዝበ-ውሳኔ ላይ በኔ ተነሳሽነት ለነፃነት ድምፅ ሰጥታ ነበር። በወቅቱ እሷ ስጋት ቢኖርባትም ልጆቼ አባታቸው ከትግራይ መሆኑን እናታቸው ደግሞ ከኤርትራ መሆኗን እንዲያውቁ በማለት አደፋፍሬያት ድምፅ ሰጠች። ይህ ሕዝበ-ውሳኔም ሥራዋን እንድታጣና ኤርትራም እንድትሄድ ምክንያት ሆነ። ትዳራችንም አከተመ። የሞትኩ ያህል ነበር የመሰለኝ ትናንትና የተፈጠረ በሚመስል ሁኔታ የሆነውን በዝርዝር አስታውሰለሁ። ቀኑ ሮብ ነበር፤ ባለቤቴ አጎቷን ለመጠየቅ ሌላ ከተማ እንደምትሄድ ነገረችኝ። አጎቷም ቤት አልሄደች። ልጆቼን ይዛ ኤርትራ ገባች። ኤርትራ ለመሄድ አቅዳው የነበረ ቢሆንም ለኔ ግን ምንም ያለችኝ ነገር አልነበረም። ሰማይ የተደፋብኝ መሰለኝ፤ በሕይወት መኖሬ ትርጉሙ ጠፋኝ። ኤርትራ ውስጥ ይህ ነው የምትለው ቤተሰብ ባይኖራትም የስደተኞች መጠለያ ማዕከል ውስጥ ገባች። የሁለቱም ሀገራት ድንበር በመቋረጡ ተከትያትም መሄድ አልቻልኩም፤ የሞትኩ ያህል ነው የተሰማኝ። በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ከመቶ ሺዎች በላይ ህይወታቸውን አጥተዋል። ደብዳቤዬ ምላሽ አልነበረውም ባለቤቴ ሳትነግረኝ በድንገት መሄዷ ለቤተሰቦቼ አልተዋጠላቸውም። "አንድ ነገር ብታደርጋት ነው እንጂ እንዲህ ብን ብላ አትጠፋም ነበር" ይሉኝ ነበር። እኔ ግን ምንም እንዳልበደልኳት አውቃለሁ። በጣም የምንዋደድና የምንከባበር ባልና ሚስት ነበርን። ቤታችን ሳቅና ደስታ ተለይቶት አያውቅም ነበር። ስትሄድ ጎረቤቶቼ ጋር የተወችልኝ ደብዳቤ ሲሆን "መለያየት ከሞት በላይ እንደሚከብድ አውቃለሁ፤ ሆኖም ልጆቼን ይዤ ሄጃለሁ። ወንዱ ልጃችንን አንተ ጋር ትቼዋለሁ። አጋጣሚውን ካገኘሁ ደብዳቤ እጽፍልኸለሁ፤ ለማንኛውም እራስህን ጠብቅ" የሚል ነው። • የኢትዮጵያና ኤርትራ ግንኙነት ኢኮኖሚያዊ ትርፍ? ለሳምንት ያህል ሐዘን ተቀምጫለሁ፤ ጎረቤቶቼም ሊያፅናኑኝ ቢሞክሩም ለኔ ሕይወት ያከተመች መስሎ ነበር የተሰማኝ። እንዳበደ ሰው በቁሜ የሞትኩ ያህል ይሰማኝ ነበር። የባለፉትን ዓመታት በቃላት ልገልጻቸው አልችልም።...
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
1441fed5d253cb987b6c8e0cafce149f
779e8102d20c91fa73322782ca8edacc
አንጋፋዎቹ ከአንጋፋው ጋዜጣ ተምረዋል
የጋዜጠኝነት ስነምግባር የሚፈቅደውን ለመተግበር፤ ህዝብን ለማስተማርና በመረጃ ለማበልጸግ፤ መንግሥትና ህዝብን እንደ ድልድይ ሆኖ ለማገልገል ሲሞክሩ ‹‹አርፋችሁ ተቀመጡ›› የሚባሉበት አያሌ ጊዜያት እንደነበሩ አይዘነጉትም፡፡ አሻፈረኝ ብለው ለህዝቡ ዓይንና ጆሮ እሆናለሁ ካሉ ደግሞ አንድም በደመወዝ አሊያም ከሥራ እስከ መባረር ይቀጣሉ፡፡ እነዚህ አንጋፋ ጋዜጠኞች ብዙ ጫናዎችን ቢያልፉም ያገለገሉትን ተቋም ‹‹ትምህርት ቤት፣ መምህር፣ የታሪክ ጎተራ›› ይሉታል፡፡ ከእነዚህም መካከል አንጋፋው ጋዜጠኛ አበራ ለማ የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋዜጠኝነትን ያስተማራቸው ትምህርት ቤት መሆኑን ይናገራሉ፡፡ በአርትኦት፣ በዘገባ አጻጻፉ የጋዜጠኝነትን ምስጢር እየተማሩ ጥርሳቸውን የነቀሉበት መሆኑን ይገልጻሉ። ጋዜጣ በየዘመናቱ የነበሩትን መንግሥታት የልብ ትርታ ያስተላልፋል፡፡ ህዝብም መንግሥት ምን እንዳለ አውቆ ወደ ትግበራ ይገባ እንደነበር ይገልጻሉ፡፡ ህዝቡም ባህሉን ጠንቅቆ እንዲረዳ ዕድል ያገኝ እንደነበር ያስታውሳሉ፡፡ የኪነጥበቡ ጎን በስፋት እንዲታይ፤ ጋዜጠኞች ፣ ደራሲያንና ህዝብ ስሜቱን በመጠኑም ቢሆን እንዲተነፍስ አስችሏል ይላሉ። አንዳንዶቹ ፅሑፎች ተንኳሽ ነበሩ የሚሉት አንጋፋው ጋዜጠኛ፣ ተንኳሽነት ጥላቻ ለመዝራት ሳይሆን አገርን ለመጠበቅ፣ ህዝብን ለማስተማርና መንግሥትን ለማረም የሚደረግ እንደሆነ ይናገራሉ። ይህንን ሲያደርጉ የነበሩ ጋዜጠኞች ግን ቅድመ ምርመራን ጨምሮ ብዙ ፈተና ገጥሟቸው እንደነበር አይዘነጉም፡፡ እርሳቸውም የዚህ ሰለባ እንደነበሩ ይገልጻሉ፡፡ ‹‹አዲስ ዘመንን ስለቅ ከውስጤ አንድ ነገር ተቦጭቆ የተወሰደ ነበር የመሰለኝ›› የሚሉት አንጋፋው ጋዜጠኛ አበራ፤ ከዚያ ወዲህ ብዙ ነገር እንዳጎደለባቸው ይናገራሉ:: ዛሬም በዕድሜ ብቻ ሳይሆን በሥራም የቀድሞውን ተግባሩን እንዲያከናውን ሁለት ነገሮችን በዋናነት ማሻሻል ይገባል ይላሉ፡፡ አንደኛው ወግ ያለው የአማርኛ ቋንቋና በሳል ጽሑፍ ለአንባቢያን ማቅረብ ሲሆን፤ በመረጃ የደለበ ወቅታዊ ጉዳይን ከስርጭት ስፋት ጋር ይዞ መምጣት ሁለተኛው ጉዳይ መሆኑን ያነሳሉ፡፡ ‹‹አዲስ ዘመን ጋዜጣ የፕሬስ ብርሃን ባልነበረበት ዘመን ለህዝብ የመረጃ ብርሃን የሰጠ ነው። መንግሥት መልዕክት ለህዝብ የሚያስተላልፍበትም ድልድይ ሆኖ አገልግሏል፡፡ የአገሪቱን ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ ትስስር እያሳየ የመጣም ሰረገላ ነው፡፡›› ያሉት ደግሞ ሌላው አንጋፋ ጋዜጠኛ ጌታቸው ለማ ናቸው፡፡ እርሳቸው እንደሚናገሩት፤ አዲስ ዘመን በሙያው ያልሰለጠነ ጋዜጠኛና የቴክኖሎጂ ውጤት ባልነበረበት ጊዜ ጭምር ከፊደላት ጋር ትግል ገጥሞ ትናንትን በታሪክ ሰንዶ ማሳየት ችሏል፡፡ ህዝቡ ያንን ተከትሎ የዕለት ተዕለት ኑሮውን እንዲኖር ያደረገ ነው፡፡ ከበርካታ ፈተናዎች ውስጥ አንዱ በቴክኖሎጂ ምክንያት የቃላት ተቆርጦ መቅረት ሲሆን፤ ታላላቅ ባለስልጣናትን ሳይቀር የሚያዋርድ ጽሑፍ ይወጣ እንደነበር ይናገራሉ፡፡ አዲስ ዘመን በየወቅቱ የሚቀያየረውን ስርዓትን እያወደሰ የዘለቀ እንደነበር የሚያነሱት ጋዜጠኛ ጌታቸው፤ አሁን ብዙ ለውጦች እያሳየ ነው፡፡ ከቅርጹ ጀምሮ እስከ ይዘቱ ጭምር ለማንበብ ይጋብዛል ይላሉ፡፡ የማንበብ ሱስ ያለበት ሰው ዛሬ ለማንበብ የሚመርጠው ዓይነት መሆኑንም ያነሳሉ፡፡ በእኛ አገር እምነት የመንግሥትን ህጸጽ እንደ ዝሆን ማግዘፍ ይፈልጋልና ይህ ሁኔታ እየፈተነው መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ስርጭቱን በማስፋት፤ የምርምር ዘገባና ሌሎች ቀዳሚ መረጃ በመስጠት የበለጠ መሪነቱን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት መክረዋል። የጋዜጣው ምክትል ዋና አዘጋጅ የነበሩት ጋዜጠኛ መኮንን ብሩ ፤አዲስ ዘመን ጋዜጣ ‹‹ትምህርት ቤትና የታሪክ ማህደር ነው›› በማለት ይገልጹታል፡፡ እንደማንኛውም መረጃ ሰጪ መገናኛ ብዙኋን ስርዓቱን ጠብቆ መረጃን ለህዝብ፣ ለመንግሥትና ለጥናት ለሚሠራ ሁሉ ምንጭ እንደሆነ ይገልጻሉ። ከ1988 ዓ.ም በፊት የጋዜጠኝነት ትምህርት ቤት ስላልነበር ጋዜጠኞች የሙያ ፊደል እንዲቆጥሩና እነርሱም ሌሎችን እንዲያፈሩ ጉልህ ሚና ተጫውቷል፡፡ ‹‹የአገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ ከፋም ለማም ምን እንደሚመስል ለማወቅ ከአዲስ ዘመን ውጪ ገላጭ የለም›› የሚሉት ጋዜጠኛ መኮንን፤ ዘመናት እንዴት እንዳለፉ ፍንትው አድርጎ በመረጃ አስደግፎ ይነግረናል ይላሉ፡፡ አዲስ ዘመን ግንቦት 30/2012ጽጌረዳ ጫንያለው
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=33872
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
31b02a4763a23d326df12f823cd4619c
4edfe5cdb32bfcfbef1ded384316c60e
ኢትዮጵያ ቡና ሦስተኛ ተጫዋቹን አስፈርሟል
ሁለት ተጫዋቾችን ቀደም ብሎ ወደ ክለቡ የቀላቀለው ኢትዮጵያ ቡና ግብ ጠባቂው ተክለማርያም ሻንቆን ለማስፈረም ከስምምነት ደርሷል። የቀድሞው የሀላባ ከተማ እና አዲስ አበባ ከተማ ግብ ጠባቂው ተክለማርያም ሻንቆ ባለፉትን ሁለት የውድድር ዓመታት በሀዋሳ ከተማ ከቶጓዊው ግብ ጠባቂ ሶሆሆ ሜንሳህ ጋር እየተፈራረቀ የክለቡ ግብ የጠበቀ ሲሆን ዘንድሮም በተመሳሳይ በሀዋሳ ቆይታ ለማድረግ ተስማምቶ የነበረ ቢሆንም ስምምነቱን አፍርሶ ወደ ቡና ማምራቱ ታውቋል።ዓለምአንተ ካሳ የክለቡ ቀዳሚ ፈራሚ ነው። የቀድሞው የወልዋሎ የአማካይ ስፍራ ተጫዋች ወደ ደደቢት ከተመለሰ በኋላ ያለፉትን ሁለት የውድድር ዓመታት መጫወት ችሏል።ሁለተኛው አዲስ ፈራሚ የሆነው የአጥቂ ስፍራ ተጫዋቹ ሰይፈ ዛኪር ነው። በፌዴራል ፖሊስ በተጠናቀቀው ዓመት በተለይም በሁለተኛው ዙር ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ ያሳየው ይህ ወጣት አጥቂ ቡድኑ በከፍተኛ ሊጉ ከመውረድ እንዲተርፍ ያስቻሉ ወሳኝ ጎሎችን አስቆጥሯል።
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/50200
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
205785ebf45c453fe7ce37c3f00e755d
e4a471b7d3ecd0b4fb3ae76b677a3619
ላለፉት ጥቂት ቀናት ቡራዩ፣ ሰበታና ሱሉልታ ባሉ የአዲስ አበባ ዙሪያ የኦሮሚያ ከተሞች ህዝቡ ድምፁን ለማሰማት አደባባይ ወጥቷል። እንደ ወለጋና ነቀምት ያሉ የምዕራብ ኦሮሚያ ከተሞችም ተመሳሳይ ሰልፎችን ተስናግደዋል።
የኦሮሚያ ተቃውሞዎች ምን ይጠቁማሉ?\nምንም እንኳ እየተካሄዱ ያሉት ሰላማዊ ሰልፎች ናቸው ቢባልም የሰዎች ህይወት ጠፍቷል አካል ጉዳትም ደርሷል። ህዝቡን ገፍቶ አደባባይ ያወጣው ባለፈው ሳምንት በቤኒሻንጉልና ኦሮሚያ ክልል ድንበር አቅራቢያ ላይ የኦሮሚያ ፖሊሶች መገደል ነበር። ስለዚህም ግድያውን ማውገዝ የመጀመሪያው የሰልፉ አላማ ሲሆን የኦሮሞ ግድያና መፈናቀል ይቁም፤ የኦሮሞ ህዝብ ባለፉት ሶስትና አራት አመታት የታገለው የኦሮሞን ችግር ለመፍታት እንጂ ኦሮሞን ስልጣን ላይ ለማውጣት አይደለም የሚል ሃሳብም በሰልፎቹ ተንፀባርቋል። • ሶሪያውያን ስደተኞች በአዲስ አበባ ጎዳናዎች • ''የአንድ ቤተሰብ አባላት ግድያ'' በቤኒሻንጉል ክልሏ ያሶ ከተማ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ሙላቱ ገመቹ ህዝቡን አደባባይ ያወጣው መንግስት የቤት ስራውን አለመስራት ነው ይላሉ። መንግሥት የህዝብን ደህንነት ማስጠበቅ ባለመቻሉም ታጣቂዎች ሰላማዊ ሰዎችን ከመኖሪያ ቤታቸው እያፈናቀሉ እንደሆነ ይናገራሉ። እሳቸው እንደሚሉት መንግሥት የታጣቂዎችን ማንነት እያወቀ ምንም ባለማድረጉ፤ የዜጎቹን ሰላምና ደህንነት የማስጠበቅ ግዴታውን ባለመወጣቱ ህዝቡ እሮሮውን ለማሰማት አደባባይ ለመውጣት ተገዷል። መንግሥት ህዝቡን ማረጋጋት አለመቻሉ በአቅም ማነስ ነው ብለው አያምኑም። ይልቁንም ከመንግስት ቸልተኝነት ጀርባ ያለው ነገር ፖለቲካዊ ስሌት ሳይሆን እንደማይቀር ጥርጣሬ አላቸው። "የዜጎችን ደህንነት መጠበቅ ያቃተው መንግስት አለ ሊባል አይችልም" ይላሉ አቶ ሙላቱ። እሳቸው እንደሚሉት በአጠቃላይ የኦሮሚያ ህዝብም እያለ ያለው መንግስት ሊጠብቀኝ አልቻለም ነው። "ማንም ታጣቂና ጉልበተኛ ተነስቶ ሌላውን ከቤቱ ሲያፈናቅል፣ ንብረቱን ሲያቃጥልና ሲያወድም ይህን ማን እያደረገ እንደሆነ መንግሥት ያውቃል። መከላከል ይቻል የነበረ ቢሆንም መንግሥት ይህንንም እያደረገ አይደለም" ይላሉ። በተመሳሳይ 'አክቲቪስት' ለሚ ቤኛ የኦሮሚያ ተቃውሞ ሁለት ነገሮችን ማዕከል ያደረገ ነው ይላል። ሰላማዊ ሰልፎቹ በቤንሻንጉል ጉሙዝና በኦሮሚያ ክልሎች መካከል ባለፉት ጥቂት ወራት በግጭት በመቶ ሺ ለሚቆጠር ህዝብ በመፈናቀሉ፤ የ100 ሰዎች ህይወት በመቀጠፉና ከቀናት በፊትም የኦሮሚያ ፖሊሶች በመገደላቸው መንግሥት አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስድ የሚጠይቁ እንደሆኑ ይናገራል። ስለዚህ የሰልፈኞቹ ዋናኛ ጥያቄው መፈናቀልና ግድያ ይቁም የሚል እንደሆነ ያስረዳል። የኦሮሚያው ተቃውሞ ለውጡና የለውጡ መሪዎች ላይም ስጋት ይጋርጣል የሚል አስተያየት ያላቸው ቢኖሩም ለሚ ግን በዚህ አይስማም። ነገሩ ለውጡን መቃወም፤ የለውጡ መሪዎችን አለመቀበልም እንዳልሆነ ያስረዳል። ለውጡ ባለፉት ሶስትና አራት አመታት የኦሮሞ ወጣት ወይም ቄሮ ብዙ መስዋዕትነት የከፈለበት ከመሆኑ አንፃር ኦሮሞ ዘብ ቆሞ ከምንም በላይ የሚጠብቀው እንደሆነ ለሚ ያስረግጣል። ሀገሪቷ የሽግግር ጊዜ ላይ በመሆኗ ለነገሮች ጊዜ ሊሰጥ ይገባል የሚሉ የመኖራቸውን ያህል እየታዩ ያሉ ችግሮች ለውጡን ችግር ውስጥ ሊከቱት ብሎም ሊቀለብሱ የሚችሉ እንደሆኑ ስጋት ያላቸውም ጥቂት አይደሉም። መንግሥት ችግሩን እየፈጠሩ ያሉት ኢህአዴግ ውስጥ ለውጡን የማይደግፉ አካላት ናቸው የሚል ምክንያት ቢያቀርብም ሊተኮርበት የሚገባው ነገር አገር እየመራን ያለ አቅምና ስልጣን ያለው መንግሥት የህዝቡን ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ ያቃተው መሆኑ እንደሆነ አቶ ሙላቱ ተናግረዋል። የኢህአዴግ መንግሥት በህዝቡ ዘንድ በተለይም በኦሮሚያ ተቀባይነት አለመኖሩ ጋር ተያይዞ ኦሮሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መሆን የኦሮሚያን ጥያቄ የሚመልስ ነው ተብሎ መታየቱ ስህተት እንደሆነ ይናገራሉ። "የኦሮሞ ብሔር ያላቸው ግለሰቦች ጠቅላይ ሚኒስትርነትን ጨምሮ...
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
2e94ce12fb5987ec8a652a20f68d4759
9e601c41a2271ba7801056f7f2881aaf
ከፍተኛ ሊግ ሀ| ሰበታ ከተማ ወደ ፕሪምየር ሊግ ማደጉን ሲያረጋግጥ አውስኮድ ወደ አንደኛ ሊግ ወርዷል
በከፍተኛ ሊጉ ምድብ ሀ 21ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በሙሉ እሁድ ተከናውነው ሰበታ ከተማ ወደ ፕሪምየር ሊግ ያደገበትን፣ አውስኮድ ወደ አንደኛ ሊግ የወረደበትን ውጤት አስመዝግበዋል።ለገጣፎ ላይ የሳምንቱ ተጠባቂ ጨዋታ በለገጣፎ ለገዳዲ እና ሰበታ ከተማ መካከል ተከናውኖ 1-1 ተጠናቋል። ሰበታ ከተማም አንድ ጨዋታ እየቀረው ወደ ፕሪምየር ሊጉ ማደጉን አረጋግጧል። የሁለቱም ከተማ ከንቲባዎች እንዲሁም የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝደንት አቶ ኢሳይያስ ጂራ እና በርከት ያሉ የለገጣፎ እና የሰበታ ደጋፊዎች በታደመበት በዚህ ጨዋታ በፈጣን እንቅስቃሴ ተጭነው የተጫወቱት ለገጣፎዎች በ2ኛው ደቂቃ ሐብታሙ ፍቃደ ከርቀት አክርሮ በመምታት ባደረገው የመጀመርያ የጎል ሙከራ ነበር የሰበታን የግብ ክልል መፈተሽ የጀመሩት። ብዙም ሳይቆይ ሐብታሙ ከመስመር ያሻገረውን የሰበታ ተከላካዮች በግንባር ገጭተው ኳሱን ለማራቅ ቢያስቡም ተቆርጦ እዛው የቀረውን ኳስ አጥቂው ሳዲቅ ተማም በአግባቡ በመጠቀም ለገጣፎን ቀዳሚ ማድረግ ችሏል።ወደ ፕሪምየር ሊግ ማደጋቸውን ለማረጋገጥ ጎል ወደ ማስቆጠር ግዴታ ውስጥ የገቡት ሰበታዎች ጫላ ድሪባ ከርቀት የሞከረውና በዕለቱ ለሰበታ መልካም እንቅስቃሴ ሲያደርግ የዋለው ኢብራሂም ከድር ከማዕዘን ምት ተደርቦ ሲመለስ ያገኘውን ኳስ ወደ ጎል ሲመታው የለገጣፎው ግብጠባቂ አንተነህ ሀብቴ ያዳነበት ጎል መሆን የሚችሉ አጋጣሚዎች ፈጥረዋል።ከጨዋታው እንቅስቃሴ ይልቅ በኳስ አቀባዮቹ በሚፈጥሩት የኳስ መዘገይት የተነሳ የጨዋታውን መንፈስ ሲቆራረጥ ለማስተዋል የቻልን ሲሆን ኳሱን ተቆጣጥረው በመጫወት ብልጫ የነበራቸው ሰበታዎች ወደ ፊት ሄደው በጎል ሙከራ ያልታጀበ እንቅስቃሴ በመሆኑ ሲቸገሩ ይልቁንም በሚነጠቁት ኳሶች ለገጣፎዎች በመልሶ ማጥቃት አደጋ ለመፍጠር ተንቀሳቅሰዋል። በጥሩ ቅብብሎች ወደፊት በመግባት የቀድሞው የሀዋሳ ከተማ ተጫዋች ፍርድአወቅ ሲሳይ 30ኛው ደቂቃ ሳጥን ውስጥ ኳሱን ይዞ በመግባት በግራ እግሩ ወደ ጎል ቢመታውም በድጋሚ የለገጣፎ ግብ ጠባቂ አንተነህ በጥሩ ብቃት ወደ ውጭ ያወጣበትም ሌላው የሰበታ ተጠቃሸ ሙከራ ነበር።ከዕረፍት መልስ የአቻነት ጎል ፍለጋ ጥረታቸውን የቀጠሉት ሰበታዎች የፕሪምየር ሊጉን ትኬት የቆረጡበትን ጎል በ53ኛው ደቂቃ አግኝተዋል። ኢብራሂም ከድር ከግራ ወደ ቀኝ ሰብሮ በመግባት ከርቀት ግሩም የሆነ ጎል አስቆጥሮ የሰበታ ደጋፊዎችን በደስታ አስጨፍሯል።በእያንዳንዱ እንቅስቃሴ ግርግር ያላጣው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ከጎሉ መቆጠር በኃላ መጠነኛ ግርግር ተፈጥሮ የነበረ ቢሆንም እንቅስቃሴው ቀጥሎ ለገጣፎዎች በተደጋጋሚ የሰበታን የግብ ክልል ሲፈትሹ ውለዋል። 65ኛ ደቂቃ የሰበታ ግብ ጠባቂ ሰለሞን ደምሴ ከለገጣፎ አጥቂዎች ከርቀት ቅጣት የተመታውን እና ከማዕዘን ምት የተሻገረውን በግንባር የተገጩ ሙከራዎች አድኗል። የጨዋታው ደቂቃ ወደ መጠናቀቂያው ሲቃረብ ሙሉ ለሙሉ ወደ መከላከል ያመዘኑት ሰበታዎች በለገጣፎዎች በኩል የሚደረገውን ጎል ፍለጋን በመከላከል ቆይተዋል። በተለይ ለገጣፎዎችን አሸናፊ የምታደርግ የግብ ዕድል 86ኛው ደቂቃ ከመስመር የተሻገረውን ዳዊት ቀለመወርቅ በግንባሩ በመግጨት ወደ ጎል የመታውን ኳስ የሰበታው ግብጠባቂ ሰለሞን ያዳናት ለለገጣፎዎች የሚያስቆጭ ነበር። በመጨረሻም የዕለቱ ዳኛ የጨዋታው ጭማሪ ሦስት ደቂቃ መስጠታቸውን ተከትሎ ተገቢ አይደልም በማለት ለገጣፎዎች ቅሬታ ያሰሙ ሲሆን ጨዋታውም አንድ አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል። በ2003 ከፕሪምየር ሊጉ የወረደው ሰበታ ከተማም ከ8 የውድድር ዘመናት በኋላ በምድብ ሀ አንድም ጨዋታ ሳይሸነፍ ወደ ሊጉ ተመልሷል።ወደ አክሱም ያመራው አውስኮድ 1-0 ተሸንፎ ከምድቡ የመጀመርያው ወራጅ ቡድን መሆኑን አረጋግጧል። የአክሱምን ብቸኛ የድል ጎል ያስቆጠረው ሙሉጌታ ረጋሳ ነው።ቡራዩ ከተማ በሜዳው ገላን ከተማን ገጥሞ በክንዳለም ፍቃዱ ብቸኛ ጎል 1-0 አሸንፏል። ከመውረድ ለመትረፍ ያለውን ጭላንጭል ተስፋም ወደ ቀጣዩ ሳምንት አስቀጥሏል።አቃቂ ቃሊቲ ከሜዳው ውጪ ወሳኝ ነጥብ ይዞ ተመልሷል። ደሴ ከተማን በዮናስ ባቢና ጎል 1-0 ያሸነፈው አቃቂ ቃሊቲ በድሉ በመታገዝ ከመውረድ ለመትረፍ ከቀጣይ ጨዋታ አንድ ነጥብ ማግኘት በቂው ሆኖለታል።ወልዲያ ላይ ወልዲያ ኢትዮ ኤሌክትሪክን 1-0 ያሸነፈበት እና ወሎ ኮምቦልቻ ከፌዴራል ፖሊስ 0-0 የተለያዩበት ጨዋታዎች ሌሎች የዚህ ሳምንት መርሐ ግብር አካል ናቸው።
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/48963
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
152b2ede131a69ac2f1a8edf76f1e80e
965e21370cbb92b20f76bacba222da23
ለፓርኪንሰን ህሙማን የሚሰጠው የህክምና አገልግሎት ውስን ነው ተባለ
አዲስ አበባ፡- ለፓርኪንሰን ሁሙማን የሚሰጠው የህክምና አገልግሎት ውስን መሆኑን  የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡በጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ቡድን መሪ አቶ አበባው አየለ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለፁት ፤የፓርኪንሰን ህሙማን ህክምና  የሚያገኙት በሆስፒታሎች ውስጥ ቢሆንም፣ አገልግሎት አሰጣጡ ግን ውስን ሆኗል፡፡የፓርኪንሰን ህመም ህክምና በባህሪው አስቸጋሪ መሆኑን አቶ አበባው ጠቅሰው፣ የበሽታውን ምልክቶች በማየት ካልሆነ በስተቀር በህክምና መሳሪያዎች ብቻ በመመርመርና ውጤቱን በማወቅ ህክምና መስጠት እንደማይቻል ተናግረዋል፡፡ ይህም የህክምና አገልግሎት አሰጣጡን ውስን እንዳደረገው ጠቁመዋል፡፡በዘርፉ የሰለጠኑ ባለሙያዎች ቁጥር አነስተኛ መሆንና በተለይም የነርቭ ህክምና ባለሙያዎች ቁጥር በዝቅተኛ ደረጃ ላይ መገኘት በሆስፒታል ደረጃ ህክምናውን በተሟላ መልኩ ለመስጠት ችግር መፍጠሩን ቡድን መሪው  ገልፀው፤ ህክምናው በሚሰጥባቸው ሆስፒታሎች ውስጥ ለሚገኙ ሃኪሞች በህመሙ ዙሪያ አጫጭር ስልጠናዎች አለማግኘታቸውና  የግብአት አቅርቦት እጥረት መኖር አገልግሎት አሰጣጡን እንደገደበው አስታውቀዋል፡፡ቡድን መሪው ህመሙ በጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም፣ በትምህርት ቤት ጤናና ስርአተ ምግብ ፕሮግራምና በአእምሮ ጤና ስትራቴጂ እቅድ ውስጥ ተካቶ እየተሰራበት እንደሆነ ጠቅሰው፣አገልግሎቱን ለማስፋት መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሁለንተናዊ እገዛ ሊያደርጉ እንደሚገባ አሳስባዋል፡፡ ከህክምና አገልግሎቱ ባሻገር ታማሚዎች በማህበረሰቡ የሚደርስባቸውን አድሎና መገለል ብሎም  ኢኮኖሚያዊ ችግር ለመፍታትም በአጋርነት መስራት  እንደሚጠበቅ ገልፀዋል፡፡ከህሙማን ማህበሩ ጋር በመተባበር አጫጭር ስልጠናዎችን ለሃኪሞች በመስጠት የህክምና አገልግሎቱን ለህሙማን የበለጠ ተደራሽ ማድረግ እንደሚቻልም ቡድን መሪው ተናግረው፣  በሃገር አቀፍ ደረጃ ያሉ ጤና ነክ  ዩኒቨርሲቲዎች ህመሙን በስርአተ ትምህርታቸው ውስጥ በማካተት የሚያስተምሩበት ከሆነ በዘርፉ የሚታየውን የባለሙያዎች እጥረት መፍታት እንደሚቻል ጠቁመዋል፡፡ፓርኪንሰን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየባሰ የሚሄድ እንቅስቃሴን የሚያውክና በአእምሮ ህመም ስር የሚካተት  የስነ ነርቭ ህመም መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይጠቁማሉ፡፡ በጥናት የተረጋገጠ መረጃ ባይኖርም በኢትዮጵያ የፓርኪንሰን ህሙማን ቁጥር ከ200 እስከ 300 ሺ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል፡፡አዲስ ዘመን ታህሳስ 30/2011በአስናቀ ፀጋዬ
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=2643
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
59a1e31ce94cbc6c4ecb8caad106ff14
d7fa31718d932854f0fc42b501f1af7f
ባለፈው ሳምንት ማብቂያ በነበሩ ቀናት በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በደረሰው የጎርፍ አደጋ የስድስት ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገለጸ።
በኢትዮጵያ ከባድ ዝናብ ለስድስት ሰዎች ሞት ምክንያት ሆነ\nአርብ ዕለት በምሥራቅ ኢትዮጵያ በምትገኘው የድሬዳዋ ከተማ ላይ የጣለው ከባድ ዝናብ ያስከተለው ጎርፍ ለአራት ሰዎች ሞት ምክንያት ሲሆን ሌሎች ሁለት ሰዎች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳትን አስከትሏል። ከዚህ በተጨማሪም በጎርፉ ምክንያት ከ30 በላይ ቤቶች የመፍረስ አደጋ የገጠማቸው ሲሆን በሌሎች ንብረቶች ላይም መጠኑ ያልተገጸ ውድመት አጋጥሟል። በተመሳሳይ በደቡብ ክልል ውስጥ በጋሞ ዞን ገረሴ እና ጋጮ ባባ ወረዳዎቾ ለቀናት በተከታታይ የጣለ ዝናብን ተከትሎ ባጋጠመ የመሬት መንሸራተት የሁለት ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ ሌሎች በሁለት ሰዎች ላይ ደግሞ ጉዳት መድረሱን የዞኑ መስተዳደር ገልጿል። በተጨማሪም በዚህ አደጋ 33 የቤት እንሳት የሞቱ ሲሆን 10 ቆርቆሮና 42 የሳር ቤቶች ከነሙሉ ንብረታቸው በመውደማቸው 2757 ሰዎች የመፈናቀል ችግር ላይ ወድቀዋል። እዚያው ደቡብ ክልል ውስጥ በጂንካ ከተማ የጣለ ከባድ ዝናብ ደግሞ በከተማዋ የሚገኝ ወንዝን እንዲሞላ በማድረግ በአካባቢው መሰረተ ልማቶችና ንብረት ላይ ውድመትን አድርሷል። በደቡብ ኦሞ ዞን ባለስልጣንት እንዳስታወቁት ከተማውን ከሌሎች አካባቢዎች ጋር የሚያገናኙ ሁለት ድልድዮች በጎርፍ ተወስደዋል። በተጨማሪም መኖሪያ ቤቶችን ጨምሮ በጎርፍ አደጋው በሰብልና በቤት እንስሳት ላይ ጉዳት ደርሷል። የአየር ትንበያ ባለሙያዎች ቀደም ብለው እንዳስጠነቀቁት በኢትዮጵያና በአካባቢው አገራት ውስጥ ጉዳትን ሊያስከትል የሚችል ከባድ ዝናብ እንደሚጥል ገልጸዋል። ዝናቡ በተከታታይ ሳምንታት ውስጥ የሚቀጥል በመሆኑ ነዋሪዎች አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉም መክረዋል።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
894468a06a16091eb4df4fcbb7b76437
246addf55fa218285a98fefc8a6a79b7
አለም አቀፍ የቱሪዝም ቀንን በድምቀት ለማክበር ዝግጅት እየተደረገ ነው
አዲስ አበባ:- የዘንድሮውን አለም አቀፍ የቱሪዝም በአል በድምቀት ለማክበር እንዲቻል ሁኔታዎችን የማመቻቸት ተግባራት በመከናወን ላይ መሆናቸው ተገለፀ። “ቱሪዝም ለስራ እድል ፈጠራና ለተሻለ ህይወት” በሚል መሪ ቃል የሚከበረው የዘንድሮው የአለም ቱሪዝም ቀን በአገራችን በድሬዳዋ ከተማ የሚከበር ሲሆን በክብረ በአሉ ላይም የተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚቀርቡ ተገልጿል። በባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የአገር ውስጥ ቱሪዝም ማስፋፊያ ጊዜያዊ አስተባባሪ አቶ ቴዎድሮስ ሀብታሙ ለአዲስ ዘመን እንደገለፁት፤ የዘንድሮው አለም አቀፍ የቱሪዝም ቀን በአለም አቀፍ ደረጃ ለ40ኛ፣ በሀገራችን ደግሞ ለ32ኛ ጊዜ መስከረም 17 የሚከበር ሲሆን፤ በበአሉ ላይም ባህላዊ እሴቶችን የሚያሳዩ በርካታ ሁነቶች እንደሚቀርቡ ታውቋል። ባህላዊ ሁነቶቹ የአገራችንን ባህላዊ እሴቶች በሚያስተዋውቅና በሚያበለፅግ መልኩ ለእይታ ይቀርባሉ የሚሉት አቶ ቴዎድሮስ፤ ባህላዊ ሲምፖዚየም፣ ኤግዚቢሽን፣ ፋሽን ትርኢት፣ የጥናትና ምርምር ስራዎች፣ ውይይቶች፣ የድሬዳዋን ልዩ ባህሪ፣ አብሮ መኖርና መቻቻልን የሚያስተጋቡ ሁነቶች፣ ምስራቅ ኢትዮጵያን የሚገልፁ ማሳያዎች፤ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች፣ የግመል ውድድር፣ ባህላዊ ምግቦች አሰራርና አመጋገብ እና ሌሎች ፓኬጆችም ይቀርባሉ። የድሬዳዋ አጎራባች ክልሎችም ባህላዊ እሴቶችና ሌሎች ተግባራትም በበአሉ ላይ ሰፊ ቦታን ይይዛሉ ሲሉም ተናግረዋል። በአሉ “በአጠቃላይ የምስራቅ ኮኮቦች የሚታዩበት፤ የአገራችን ቱሪዝም በስፋት የሚተዋወቅበት፤ ዘርፉን ለማበልፀግ ሰፊ ስራ የሚሰራበት፣ በዘርፉ ለመሰማራት የሚፈልጉ ባለሀብቶች የሚበረታቱበት፤ የቱሪስት ፍሰትን ለመጨመር ቃል የሚገባበት፣ የአገራችን ህዝቦች ከተለያዩ የአገራችን ባህላዊ እሴቶች ልምድ የሚካፈሉበት” እንደሚሆንም ጊዜያዊ አስተባባሪው አቶ ቴዎድሮስ ተናግረዋል። “የበአሉ አከባበር በ2012 የስራ እድል ፈጠራ የሚለው ጎልቶ የሚወጣበት ነው” የሚሉት አቶ ቴዎድሮስ በቱሪዝሙ ዘርፍ ከፍተኛ የስራ እድል ለወጣቱ የሚፈጠርበትና ዜጎች፤ በተለይም ወጣቱ ተጠቃሚ የሚሆንበት የስራ ዘመን እንደሚሆንም ተናግረዋል። ይህ ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ በቅርቡ ያስተላለፉትን መልእክትና ያስቀመጡትን አቅጣጫ ተከትሎ የተያዘ እቅድ መሆኑንም አቶ ቴዎድሮስ ተናግረዋል። በአሉ የቱሪዝምን ምንነት ከማስገንዘብ ባሻገር አገራችን በዘርፉ ያላትን አቅም የምንለይበት በመሆኑ የጎብኚዎችን ቁጥር፤ በተለይም ያገር ውስጥ ጎብኚዎችን ለማበረታታትና ቁጥራቸውን ለማሳደግ ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው አቶ ቴዎድሮስ ጠቁመዋል፡፡ 110 ሚሊዮን ህዝብ ባላት አገራችን ያገር ውስጥ ቱሪስት ቁጥር ገና ከ23 ሚሊዮን አልዘለለም ያሉት አቶ ቴዎድሮስ ይህንን ችግር ለመቅረፍ በዓሉ ከፍተኛ እድል እንደሚፈጥርም ይገልፃሉ። በአብዛኛው ክልሎች ትልቁን ኃላፊነትና ድርሻ የሚይዙበትና የሚሳተፉበት ይህ በአል ሁሉም ክልል እራሱን የሚያስተዋውቅበት፣ ያለውን የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ ሀብቱን ለይቶ የሚያውቅበት፣ አውቆም ለሌላው የሚያሳውቅበት፣ የአገሪቱን የቱሪዝም ዘርፍ ከማሳደግ አኳያ ሁሉም የየድርሻውን እንዲወጣ የሚያደርግበት፣ በየአካባቢው የአገር ውስጥ ቱሪስት ቁጥርን ለማሳደግ እድል የሚሰጥበት፣ በዘርፉ ለመሰማራት የሚፈልጉ ባለሀብቶችን ለመሳብ አመቺ ሁኔታ የሚፈጠርበት መሆኑንም ኃላፊው ጠቁመዋል።አዲስ ዘመን መስከረም 5/2012ግርማ መንግሥቴ
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=18077
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
02976a723e7cd13a8b9c9ec214f43999
94274a1507ee6ca0653a6b2bfaaf396e
እስራኤል 2,000 ቤተ እስራኤላውያን ወደ አገሯ እንዲገቡ ፈቀደች። ይህም ለዓሠርታት ለዘለቀው ጥያቄያቸው ምላሽ የሰጠ ውሳኔ ነው።
እስራኤል 2,000 ቤተ እስራኤላውያንን ለመቀበል ፈቀደች\nኢትዮጵያውያኑ ወደ እስራኤል ለመጓዝ ለዓመታት ሲጠባበቁ ከነበሩ ወደ 8,000 የሚጠጉ የአይሁድ እምነት ተከታዮች መካከል ናቸው። ቤተ እስራኤላውያኑ፤ እስራኤል የመኖር መብት ጥያቄያቸው ለዓመታት ሲነሳ የነበረ ነው። ለአብዛኞቹ አይሁዳውያን የእስራኤል ዜግነት የማግኘት መብት የሚሰጠው ሂደት ለነሱ አይሠራም። እንደ ጎርጎሮሳውያኑ በ1980ዎቹ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በሚሥጥራዊ ተልዕኮ ወደ እስራኤል ተወስደዋል። አብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን የአይሁድ እምነት ተከታዮች ያኔ ከሄዱት ቤተ እስራኤላውያን ጋር የደም ትስስር አላቸው። ሆኖም ግን ከዛ በኋላ ወደ እስራኤል መሄድ የተፈቀደላቸው ጥቂቶቹ ብቻ ሲሆኑ፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን አይሁዶች በጎንደር እና አዲስ አበባ በሚገኙ ማቆያዎች ይገኛሉ። ማኅበረሰቡ ከቤተ እስራኤላውያን የዘር ግንድ የሚመዘዝ ሲሆን፤ በ1880ዎቹ አውሮፓውያን ሚሽነሪዎች ክርስቲያን አድርገዋቸው ነበር። . ቲፋኒ ሃዲሽ፡ ጥቁርነትና ይሁዳዊነት . ከኢትዮጵያ የሄደችው ቤተ እስራኤላዊት በሚኒስትርነት ተሾመች . 119 ቤተ እስራኤላውያን ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል አቀኑ . በኢትዮጵያ የሚገኙ ቤተ እስራኤላውያን ወደ ፅዮን ውሰዱን ተማፅኖ ከዛ ግን ወደ አይሁድ እምነት ተመልሰዋል። ሆኖም የእስራኤል የአገር ውስጥ ሚንስትር እንደ ሙሉ የአይሁድ እምነት ተከታይ እውቅና አልሰጣቸውም። እስራኤል እንዲሄዱ መፈቀድ አለበት ወይስ የለበትም? የሚለው እስራኤል በሚኖሩ ቤተ እስራኤላውያን ሳይቀር መከፋፈል ፈጥሯል። አንዳንድ ቤተ እስራኤላውያን፤ ኢትዮጵያውያን የእምነቱ ተከታዮች እስራኤል የመኖር መብት አላቸው ሲሉ፤ ሌሎች ደግሞ አይሁዳዊ ያልሆኑ ኢትዮጵያውያን ናቸው በማለት ሐሳቡን አይቀበሉትም። . "ወደ እናት ሃገራችን እስራኤል ውሰዱን" . መባረር ወይም እስር የሚጠብቃቸው ስደተኞች በእስራኤል በቅርቡ በስደተኞች ጉዳይ ሚንስትርነት የተሾሙት ትውልደ ኢትዮጵያዊት ኒና ታማኖ-ሻታ በበኩላቸው፤ 2,000 ቤተ እስራኤላውያን ወደ እስራኤል እንዲገቡ በመፈቀዱ ደስታቸውን ገልጸዋል። በትዊተር ገጻቸው "በጣም ደስ ብሎኛል" ሲሉም ጽፈዋል። ሚንስትሯ እስከ ቀጣዩ ዓመት ማገባደጃ ድረስ ቤተ እስራኤላውያንን ወደ እስራኤል ለመውሰድ ቃል ገብተው ነበር። ቤተ እስራኤላውያን መጀመሪያ ላይ ወደ እስራኤል የተወሰዱት ከሱዳን የስደተኞች ማቆያዎች ነበር። በ1980ዎቹ መባቻ ላይ የእስራኤሉ የስለላ ተቋም ሞሳድ ጉዟቸውን እንዳመቻቸም ይታወሳል። ውሳኔውን ያስተላለፉት የያኔው ጠቅላይ ሚንስትር ነበሩ። በቀጣይም በ1991 በርካታ ኢትዮጵያውያን ወደ እስራኤል ተወስደዋል። ቤተ እስራኤላውያኑ ከእስራኤል ማኅበረሰብ ጋር ተዋህደው ለመኖር ያሚያደርጉት ጥረት ቀላል አይደለም። ብዙዎቹ ሥራ አጥ ሲሆኑ፤ መድልዎም ይደርስባቸዋል።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
376a34013f35a133421b077508d9458b
2b2425e3edf02ca952105a53e2e275e5
የአሜሪካ ልማት ተርአዶ ድርጅት የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ መሳሪያዎችን ለኢትዮጵያ አበረከተ
አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 28፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ዓለም አቀፉ የአሜሪካ ልማት ተርአዶ ድርጅት (ዩ.ኤስ.ኤይድ) የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ መሳሪያዎችን ለኢትዮጵያ አበረከተ።ዩ.ኤስ.ኤይድ ኢትዮጵያ በትዊተር ገፁ እንዳስታወቀው፥ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር እያሻቀበ ባለበት በዚህ ወቅት ከጤና ሚኒስቴር እና ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት ጋር በመተባበር የመመርመር አቅመን ለማሳደግ እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቋል።በዚህም መሰረት ድርጅቱ የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ ቁሳቁሶችን ለኢትዮጵያ ማበርከቱን የገለፀ ሲሆን፥ ድጋፉም የኢትዮጵያን የምርመራ አቅምን ያሳድጋል ብሏል።የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ ቁሳቁሶቹ አዲስ አበበን ጨምሮ የኮሮና ቫይረስ በከፍተኛ ሁኔታ በተዛመተባቸው አካባቢዎች እንደሚውልም አስታውቋል።የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%8b%a8%e1%8a%a0%e1%88%9c%e1%88%aa%e1%8a%ab-%e1%88%8d%e1%88%9b%e1%89%b5-%e1%89%b0%e1%88%ad%e1%8a%a0%e1%8b%b6-%e1%8b%b5%e1%88%ad%e1%8c%85%e1%89%b5-%e1%8b%a8%e1%8a%ae%e1%88%ae%e1%8a%93-%e1%89%ab/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
2e028a80721b5c1f672b70f638c34940
513302aae53b2a5945c4c52ae561a974
ሩዋንዳ 55 ከመቶ ካቢኔዋን ሴቶች አደረገች::
በሀገሪቱ ሴቶች ለከፍተኛ ኃላፊነት ራሳቸውን እያበቁ እንዲቀጥሉም ተነግሯል፡፡ሩዋንዳ ባለፈው ረቡዕ ካቢኔዋን እንደገና ስታዋቅርና አዳዲስ ባለስልጣናትን ስትሾም የሴቶችን ቁጥር ከ52 በመቶ ወደ 55 በመቶ አሳድጋለች፤ የካቢኔ አባላቱን ቁጥርም ከ27 ወደ 29 ከፍ ማድረጓ ተሰምቷል፡፡ ከ29 የካቢኔ አባላት 16 ሴቶች መሆናቸውም ታውቋል፡፡ የሩዋንዳ ሕገ መንግሥት በማናቸውም የውሳኔ መስጫ እርከኖች ሴቶች ቢያንስ በ30 በመቶ እንዲወከሉ ይደነግጋል፡፡ ከሰሞኑ አዲስ ከተሾሙ አራት ሚኒስትሮችም የትምህርት፣ የሥርዓት ፆታና ቤተሰብ እንዲሁም የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትሮች ሆነው የተሾሙት ሦስት ሴቶች ናቸው፡፡ በሴቶች መብት ዙሪያ የሚሠሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የሩዋንዳን ተግባር አድንቀዋል፤ በቀጣይም ተተኪ ወጣት ሴቶችን ማብቃትና ወደ መሪነት ማምጣት ላይ አተኩሮ መሥራት እንደሚገባ መክረዋል፡፡ የሴቶች ብቁ ሆኖ መገኘት ለከፍተኛ ኃላፊነት እንዳበቃቸው የገለጹት የመብት አቀንቃኞቹ ወደፊትም ሴቶች በትምህርታቸውና በመሪነት ብቃታቸው ተሽለው በመገኘት የሚመጥናቸውን የኃላፊነት ቦታ ለማግኘት ዝግጁ እንዲሆኑ አሳስበዋል፡፡ ምንጭ፡- ኒው ታይምስ በአብርሃም በዕውቀት
4ዓለም አቀፍ ዜና
https://www.amharaweb.com/%e1%88%a9%e1%8b%8b%e1%8a%95%e1%8b%b3-55-%e1%8a%a8%e1%88%98%e1%89%b6-%e1%8a%ab%e1%89%a2%e1%8a%94%e1%8b%8b%e1%8a%95-%e1%88%b4%e1%89%b6%e1%89%bd-%e1%8a%a0%e1%8b%b0%e1%88%a8%e1%8c%88%e1%89%bd/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
cd33325a6d8dfd6525f7ab1962b1b628
5a714a6d2038a0f972df06caf787fbd8
ሱዳን ለሦስት ዓመታት ለሚቆየው የሽግግር መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር ሾመች
ሱዳን ለሦስት ዓመታት ለሚቆየው የሽግግር መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር ሾመች።አዲስ የተሾሙት ጠቅላይ ሚንስትር አብደላ ሃምዶክ የሽግግር መንግሥቱ መሪ በመሆን ቃለ መሃላ የፈፀሙ ሲሆን፣ በቃለ መሃላቸው በአገሪቱ ያለውን ሰላም ማረጋገጥ እና ለምጣኔ ሐብታዊ ቀውሶች እልባት መስጠት ቅድሚያ የሚሰጡት ጉዳይ እንደሆነ ገልፀዋል።ሌተናንት ጄነራል አብደል ፈታህ አብደልራህማን ቡርሃን ለሉዓላዊ ምክርቤቱ መሪ ሆነው መምራት ከጀመሩ በኋላ የተሾሙት ጠቅላይ ሚንስትሩ እስከ ቀጣዩ የአገሪቷ ምርጫ ድረስ እንደሚያስተዳድሩ ተገልጿል።የሉዓላዊ ምክር ቤቱና ሃምዶክ በቃለ መሃላ ሥነስርዓቱ ላይ ሱዳን ኦማር አል በሽር ሥልጣን በኋላ ከወታደራዊ አገዛዝ ሥርዓት የተላቀቀችበት የመጀመሪያው ጊዜ ብለውታል።ተቃዋሚ ፓርቲዎችም በበኩላቸው አሁን የተመሰረተው መንግሥት በአገሪቷ የነበረውን የወታደራዊ አገዛዝ ሥርዓት እንዲያከትም ያደርገዋል በማለት ተስፋ ሰንቀዋል።ጠቅላይ ሚንስትር ሃምዶክ ከአውሮፓዊያኑ 2011 ጀምሮ በተባበሩት መንግሥታት ከፍተኛ የምጣኔ ሐብት ባለሙያ ሆነው አገልግለዋል።መንግሥት ቅድሚያ ሰጥቶ ከሚሰራቸው ተግባራት መካከል፤ ጦርነትን ማስቆም፣ ዘላቂነት ያለው ሰላም መገንባት፣ የምጣኔ ሐብት ቀውስን መፍታት እና ሚዛናዊነቱን የጠበቀ የውጭ ፖሊሲ መገንባት እንደሆኑ ሃምዶክ ለሮይተርስ ዜና ወኪል አስታውቀዋል።ባለፈው ዓመት ሃምዶክ የአገሪቷ የገንዘብ ሚኒስቴር እንዲሆኑ ከሥልጣን በተወገዱት ፕሬዚዳንት ኦማር አልበሽር የታጩ ሲሆን ጥያቄው ሳይቀበሉት መቅረታቸውን ኤ ኤፍ ፒ የዜና ወኪል ዘግቧል።በሱዳን የተፈጠረው ቀውስ የጀመረው ባለፈው ዓመት መጨረሻ አካባቢ ሲሆን አገሪቷን ለ30 ዓመታት ያስተዳደሩት ኦማር አል በሽር ከሥልጣን እንዲወርዱ በመጠየቅ ነበር።የሲቪል መንግሥት እንሻለን የሚሉ የአገሪቷ ዜጎች ለወራት ተቃውሟቸውን ያሰሙ ሲሆን በእነዚህ ጊዜያትም የበርካቶች ሕይወት ማለፉ ይታወሳል ሲል የዘገበው ቢቢሲ ነው።
5ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/33327/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
21b2c882c8b3c733772bdd5feca6837e
0e49a64c81fc18b27bb32eeb81fe19ac
የግርማ ታደሰ ውዝግብ – አሰልጣኙ የደቡብ ፖሊስ ወይስ የሀዲያ ሆሳዕና ?
ደቡብ ፖሊስን ከስምንት ዓመታት በኋላ ዳግም ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የመለሱት አሰልጣኝ ግርማ ታደሰ ባሳለፍነው ሳምንት ከክለቡ ጋር ለመቀጠል መስማማታቸው የተነገረ ቢሆንም ሀዲያ ሆሳዕና ለክለባቸው እንደፈረሙ አረጋግጧል። አሰልጣኙ ደግሞ ከሁለቱም ወገን ጋር ስምምነት እንደሌላቸው ተናግረዋል። አሰልጣኙ ባለፉት ጥቂት ቀናት በደቡብ ፖሊስ የማይገኙ ሲሆን በጉዳዩ ዙርያ ያላቸውን ሀሳብ ለሶከር ኢትዮጵያ ገልጸዋል። ደቡብ ፖሊስ እና ሀዲያ ሆሳዕናም ምላሻቸውን ሰጥተውናል።  አሰልጣኝ ግርማ ከክለቡ ጋር የማይቀጥሉበትን ምክንያት ለሶከር ኢትዮጵያ እንዲህ አብራርተዋል። “አዎ ከደቡብ ፖሊስ ጋር ለመቀጠል ተስማምተን ነበር። ነገር ግን ሰሞኑን እናቴ ስለታመመች እና ከፍተኛ ክትትል ስለምትሻ ከጎኗ ሆኜ ማገዝ እንዳለብኝ በማመኔ ከፖሊሶች ጋር የነበረኝን ስምምነት ለማንሳት ተገድጃለው። አሁን ባለሁበት ሁኔታ እኔ ሙሉ ጉልበቴን እና እውቀቴን በትኩረት ለክለቡ መስጠት አልችልም እነሱ ደግሞ ይህንን መረዳት አለባቸው። ጊዜው በጣም እየሄደ ስለሆነ እና የቤተሰቤ ነገር ጊዜ ስለሚወስድ ክለቡን ለመልቀቅ ተገድጃለው። እንደ አሰልጣኝ ደግሞ በከፍተኛ ሊጉ የሰራሁትን ጥሩ ነገር በማይሆን ነገር መናድ እና ማፍረስ አልፈልግም። ስለዚህ ይህንን ውሳኔ ወስኛለው።” ብለዋል።ለጥያቄዎች ምላሽ መስጠታቸውን የቀጠሉት አሰልጣኝ ግርማ ከደቡብ ፖሊሶች ጋር ለመለያየት መወሰናቸውን ለክለቡ አመራሮች ስለማሳወቃቸው እና ስለ ውላቸው ይህንን ምላሽ ሰተዋል። “ለክለቡ አመራሮች ውሳኔዬን በአጭር የፅሁፍ መልዕክት (SMS) ጨምሮ በስልክ በመደወል አሳውቄያቸዋለው። ትላንት እና ከትላንት በስትያ ስልኬ ስለተበላሸ ነው እንጂ በተደጋጋሚ ከአመራሮቹም ጋር ከምክትሎቼም ጋር መልዕክቶችን ስንለዋወጥ ነበር። እውነት ለመናገር ክለቡ ከፍተኛ ችግር ያለበት ክለብ ነው፤ ዘንድሮ ብዙ ችግሮች ነበሩብን። እኔ እና ልጆቼ ብዙ ታግለን ነው ለፕሪምየር ሊጉ የበቃነው። የነበሩብን ችግሮች ሳይስተካከሉ ቀጣይ ነገር ማቀድ በጣም ከባድ ነው። እንደ አጋጣሚ የማይቀየር የቤተሰብ ችግር ሆነብኝ እንጂ እሱም ባይሆን እንኳ ከክለቡ ጋር መቆየት ከባድ ነው። ውሉን በተመለከተ ከስምምነት በቀር ከክለቡ ጋር ምንም ይፋዊ ውል የለንም፤ ስለዚህ ውል አለው የሚባለው ነገር ውሸት ነው። ክለቡ ከዚህ በኋላ ስለ እኔ ማሰብ አቁሞ ቀጣይ የክለቡን አሰልጣኝ የመሾም ጉዳይ ላይ ትኩረቱን ማድረግ አለበት።”በመጨረሻም ስለቀጣይ ማረፊያቸው የተናገሩት አሰልጣኙ “አሁን ማሰብ የምፈልገው ስለቤተሰቤ ብቻ ነው። ሃዲያ ሆሳዕናዎች ሃዋሳ ድረስ በመምጣት አናግረውኝ ነበር። ነገር ግን አሁን ያለሁበት ወቅታዊ ሁኔታ ምንም ነገር እንዳስብ አያደርገኝም። ስለዚህ ከማንም ክለብ ጋር አልተፈራረምኩም።” ብለዋል።የክለቡ ፕሬዝዳንት ኮማንደር ዳንኤል ገዛኸኝ በበኩላቸው አሰልጣኙ ከክለባቸው ጋር እንደሚቀጥል ብቻ እንደሚያውቁ ገልፀዋል። “በከፍተኛ ሊጉ ውድድር ማብቂያ ሰሞን ስለ ቀጣዩ ዓመት ሰፊ ውይይት አድርገን በተጫዋች መረጣ እና ምልመላ ላይም አብረን ስንሰራ ነው የቆየነው። እኔ እስካለኝ መረጃ አሰልጣኙ ከክለቡ ጋር ውል እንዳለው እና እንደሚቀጥል ነው የማውቀው። ከዛ ውጪ በተለያዩ የሚድያ አውታሮች የሚወሩት እና የሚጠይቁኝ ነገሮችም እኔ የማውቃቸው አይደሉም። እንደ ህግ ስንሄድ ደግሞ ፌዴሬሽኑ ባስቀመጠው ደንብ መሰረት የውል ግዴታዎቻችንን እንደምንፈፅም ነው የምንረዳው። ስላለመቀጠሉ ከማንኛውም ኃላፊ ጋር ንግግር አድርጎ አያውቅም። ወላጅ እናቱ ታመው በዛ ምክንያት ከክለቡ እንደራቀ ነው መረጃው ያለኝ። ከሱ ጋር አንቀጥልም የምንልበት ጉዳይ የለም። የማይቀጥልበት አስገዳጅ ሁኔታ ቢኖር እንኳን ሊያሳውቀን ይገባል። አሰልጣኞች የራሳቸው ፍላጎት ሊኖር ይችላል። እንደ ክለብ ደግሞ በህግ እና ደንብ ነው ልንመራ የምንችለው። ስለዚህ ጉዳያችን በስምምነት ብቻ ነው ሊቋጭ የሚችለው። ለዚህ ደግሞ ኦፊሻል ሆኖ የቀረበ ነገር በሌለበት ሁኔታ አሰልጣኙ ከኛ ጋር ያለውን ነገር አቋርጧል ብለን መናገር አንችልም። ” ብለዋል።አሰልጣኝ ግርማ በክለቡ አካባቢ ባይኖሩም ደቡብ ፖሊስ ተጫዋቾችን በማዘዋወር ላይ ይገኛል። ያለ አሰልጣኙ ተሳትፎ ዝውውሮች መከናወናቸውን በተመለከተም ስራ አስኪያጁ የሚከተለውን ብለዋል። ” የተጫዋቾች መረጣ ጉዳይ ከዚህ ቀደም ከአሰልጣኙ ጋር የተካሄደ ነው። የሚቀጥሉት እና አዳዲስ የሚመጡት ቀድሞ ተወስኗል። ስለዚህ ስራችን እነሱን አግባብቶ ማስፈረም ነው የሚሆነው። እሱ ከለቀቀ የሚሆነውን ወደ ፊት አብረን እናያለን፤ አሁን ግን በእቅዳችን መሰረት ነው እየተጓዝን ያለነው። ” ብለዋል። አሰልጣኙ ከሌላ ክለብ ጋር ከተስማሙም በህግ አግባብ ጉዳዩን እንደሚመለከቱት በመግለፅ ሀሳባቸውን አጠቃለዋል።የሀዲያ ሆሳዕና ስራ አስኪያጅ አቶ መላኩ አሰልጣኝ ግርማ ታደሰ ለክለባቸው እንደፈረመ ለሶከር ኢትዮጽያ ገልፀዋል። ” ግርማ ታደሰ ለኛ ፊርማውን አኑሯል። ከአሰልጣኝ ክፍሌ ቦልተና ጋር በስምምነት ለመለያየት ከወሰንን በኋላ ግርማን ወደ ክለባችን ለማምጣት ተስማምተን በዕለተ ማክሰኞ ፊርማውን አኑሮልናል። ለኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽንም ስምምነታችንን አስገብተናል። ስለዚህ ግርማ በ2011 ከሀዲያ ሆሳዕና ጋር እንደሚቆይ ነው የማውቀው።” ብለዋል። ሶከር ኢትዮጽያ ከፌዴሬሽኑ ባደረገው ማጣራት ሀዲያ ሆሳዕና ከግርማ ጋር ያደረገው ስምምነት የገባ ቢሆንም ለማፅደቅ ግን ከክፍሌ ቦልተና ጋር በስምምነት መለያየታቸውን የሚገልፅ ደብዳቤ ይዘው መምጣት ስለሚጠበቅባቸው እስካሁን አልፀደቀም።አሰልጣኝ ግርማ ለሀዲያ ሆሳዕና መፈረማቸውን ተከትሎ በቀጣይ የደቡብ ፖሊስ እርምጃ ምን ይሆናል? ክለቡ እንደሚለው አሰልጣኙ ውል አላቸው? ወይስ አሰልጣኝ ግርማ እንደሚሉት ይፋዊ ውል የላቸውም? የሚለው የሚጠበቅ ጉዳይ ነው።
2ስፖርት
https://soccerethiopia.net/football/39740
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
252dab72d0e041d186fd7cc300b724e7
2026e30f61755d875380281814de6ade
አሜሪካ፣ ካሊፎርንያ ውስጥ በኮሮናቫይረስ ተይዞ ሆስፒታል የነበረ ግለሰብ ሌላ ቫይረሱ ያለበትን ታማሚ ገደለ።
የኮሮናቫይረስ ታማሚው ሆስፒታል ውስጥ ሌላ ታማሚን ገደለ\nየ37 ዓመቱ ግለሰብ ባለፈው ሳምንት ታማሚውን የገደለው በኦክስጅን መያዣ ታንክ ደብድቦት ነው። ግለሰቡ በግድያ እና በጥላቻ ወንጀል ተከሷል። ጀሲ ማርቲኔዝ የተባለው ግለሰብ የ82 ዓመት አዛውንት በኮሮናቫይረስ ተይዘው እሱ የሚገኝበት የሆስፒታል ክፍል ውስጥ ከገቡ በኋላ ነው ግድያውን የፈጸመው። ለሎስ አንጀለስ ፖሊስ በሰጠው ቃል መሠረት አዛውንቱ የሆስፒታሉ ክፍል ውስጥ እየጸለዩ ስለነበረ ተበሳጭቶባቸዋል። አዛውንቱ በኦክስጅን ታንክ ከተመቱ በኋላ በቀጣዩ ቀን ሕይወታቸው አልፏል። ፓሊስ እንዳለው፤ ሁለቱ ግለሰቦች በተመሳሳይ የሆስፒታል ክፍል ውስጥ ሕክምና ሲደረግላቸው ነበር። ከዚያ በፊትም አይተዋወቁም። አንቲሎፕ ቫሊ በተባለውና በደቡብ ካሊፎርንያ በሚገኝ ሆስፒታል ሕክምና ሲደረግለት የነበረው ጀሲ "አዛውንቱ ሲጸልዩ ተበሳጨና በኦክስጅን ታንክ ገደላቸው" ሲል ፖሊስ መግለጫ አውጥቷል። ከግድያ በተጨማሪ የጥላቻ ወንጀል እና አረጋውያንን የማሰቃየት ክስም ተመስርቶበታል። ካሊፎርንያ ውስጥ በስድስት ሳምንት ብቻ አንድ ሚሊዮን ሰዎች ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል። ሆስፒታሎች ህሙማንን ለማስተናገድ እየተጣጣሩም ነው። ወረርሽኙ ከጀመረ ወዲህ በግዛቲቱ ከሁለት ሚሊዮን በላይ ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል። ሆስፒታሎች የጤና ባለሙያዎች እጥረት ስለገጠማቸው ከአውስትራሊያ እና ታይዋን 3000 ባለሙያዎች ለመውሰድ አቅደዋል። የካሊፎርንያ የጤና ቢሮ ጸሐፊ ዶ/ር ማርክ ጋሊ በዚህ ወር መጨረሻ ለህሙማን አልጋ ላይኖር እንደሚችል ተናግረዋል። አገረ ገዢው ጋቪን ኒውሰም ዜጎች ከቤት እንዳይወጡ አዘዋል። እጅግ አስፈላጊ ከሆኑ አገልግሎቶች ውጪ ያሉ ተቋሞችም ተዘግተዋል።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
375719529daa50b89b4f3ef268fa26b1
40c83eb0a95946b25c92c61ed50b5875
1ሺ 500 ዓመት ዕድሜ ያለው ዝነኛው የአያ ሶፊያ ቅርስ መስጊድ እንዲሆን መወሰኑ ይታወሳል።
አወዛጋቢው አያ ሶፊያ ቅርስ ዛሬ ለጁምአ ጸሎት ክፍት ይሆናል\nድሮ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የነበረው አያ ሶፊያ አሁን መስጊድ ሆኗል፡፡ ቱርክም ሆነች መላው ዓለም የሚደመምበት የአያ ሶፊያ ሕንጻ በከፊል መስጊድ ሆኖ እንዲያገለግል የወሰነው ፍርድ ቤት ነው፡፡ በቱርክ ኢስታንቡል የሚገኘው አያ ሶፊያ ከዓለም ቅርሶች ልዩ ቦታ የሚሰጠው ነው፡፡ ሙስሊሞች በዜናው ተደስተዋል፤ ጁምዓ ሁሉም ሰው እዚያ ለመገኘት ይፈልጋል ብለዋል የኢስታንቡል ከንቲባ የርሊካያ አሊ፡፡ አንድ ሺ አምስት መቶ ዓመት ያስቆጠረው ይህ በዩኔስኮ ልዩ ቦታ የሚሰጠው ታሪካዊ ሕንጻ ወደ ሙዚየምነት የተቀየረው በፈረንጆቹ በ1934 ነበር፡፡ ከዚያ ቀደም ባሉ ረዥም ዓመታት ግን መስጊድ ነበር፡፡ ይህንን ቅርስ ወደ መስጊድነት እንዲመለስ መወሰኑ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ቅሬታን ፈጥሯል፡፡ ይህም የሆነው ቅርሱ በቢዛንታይን ጊዜ ሲገነባ የዓለም ትልቁ ቤተ ክርስቲያን የነበረ በመሆኑ ነው፡፡ ከዛሬ አርብ ጀምሮ በአንድ ጊዜ አንድ ሺ ሰዎች በአያ ሶፊያ ተገኝተው ሊሰግዱበት ይችላሉ ተብሏል፡፡ የቱርኩ መሪ ጣይብ ኤርዶጋን ዛሬ ለጁምአ ከሚገኙት ምዕመናን መካከል አንዱ እንደሚሆኑ ይጠበቃል፡፡ ይህ ቅርስ መስጊድ ይሁን ወይስ ቅርስ ሆኖ ይቀጥል የሚለው ጉዳይ ላይ ለዓመታት የቱርክ ማኅበረሰብን ሲያነታረክ ነበር፡፡ ኤርዶጋን ይህ ቅርስ መስጊድ እንዲሆን መወሰኑን ሲያሳውቁ በርካቶች የተደሰቱትን ያህል ከፍተኛ ቅሬታዎችም ተስተናግደዋል፡፡ ለምሳሌ የካቶሊኩ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ ‹‹ለኢስታንቡል እጸልያለሁ፤ ሳንታ ሶፊያን ባሰብኩ ቁጥር ሐዘኔ ይበረታል›› ብለዋል ውሳኔውን ተከትሎ፡፡ የምሥራቅ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናትም በውሳኔው ሐዘናቸውን ገልጸዋል፡፡ ፓትሪያርክ ባርቶሎሜ እንደተናገሩት ይህ ቅርስ መስጊድ መሆኑ የብዙ ኦርቶዶክሶችን ልብ የሚሰብር ነው፡፡ 350 ቤተክስትያኖችን ያቀፈው የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ በበኩሉ ውሳኔው እንዲቀለበስ ጠይቋል፡፡ ይህ ውሳኔ አንድነትን ሳይሆን ክፍፍልን የሚፈጥር ነው ሲሉ አስጠንቅቋል፡፡ ‹‹ኤርዶጋን ግን ሉአላዊ አገር ነን፡፡ ውሳኔያችንም ሉአላዊነታችንን የሚያረጋግጥ ነው›› ብለዋል፡፡ በሕንጻው ውስጥ የሚገኙ የቅድስት ማርያምና ሌሎች ክርስቲያናዊ ምሥሎችና ምልክቶችም ተጠብቀው እንደሚቆዩ አረጋግጠዋል፡፡ ‹‹አያ ሶፊያ ከ86 ዓመታት በኋላ ወደ መስጊድነት ተቀይሯል፡፡ የኢስታንቡል ወራሪ የነበረው የሕንጻው ባለቤት በኑዛዜው ቤቴ መስጊድ እንዲሆን ባለው መሰረት ኑዛዜው እነሆ ተከብሮለታል›› ብለዋል ኤርዶጋን፡፡ ሆኖም ኤርዶጋን ሕንጻው ለክርስቲያኖችም ክፍት መሆኑን አስምረውበታል፡፡ ከክርስቲያች በተጨማሪም ለጎብኚዎች ዓመቱን ሙሉ ክፍት ይደረጋል፡፡ አያ ሶፊያ የማን ነው? አያ ሶፊያ በ537 በቢዛንታይን ኢምፐረር ጀስቲኒያን የተገነባ ልዩና ብርቅዬ ቤተክርስቲያን ነበር፡፡ ንጉሡ ይህ ስፍራ ትልቁ የዓለም ቤተ ክርስቲያን እንዲሆን አስቦ እንዳስገነባው ይነገራል፡፡ ሆኖም እንደ አውሮጳዊያኑ በ1453 ኦቶማን ሱልጣን አሕመድ ዳግማዊ ቀድሞ ኮንስታንቲኖፕል ትባል የነበረችውን ኢስታንቡልን በመውረር ተቆጣጠረ፡፡ ወረራውን ተከትሎም የኦርቶዶክስ ክርስቲያን ካቴድራል የነበረችው አያ ሶፊያ ወደ መስጊድነት ተቀየረች፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱን ወደ መስጊድነት በመቀየሩ ረገድ በዚያ ዘመን አራት ሚናሬቶችም እላዩ ላይ እንዲገነቡ ተደርጓል፡፡ አያ ሶፊያ ለብዙ መቶ ዓመታት መስጊድ ሆኖ ካገለገለ በኋላ ይህ ስፍራ በከማል አታቱርክ ግፊት ወደ ሙዝየምነት ተቀየረ፡። አያ ሶፊያን በዓመት ወደ 4 ሚሊዮን የሚጠጉ ቱሪስቶች ይጎበኙታል፡፡
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
e026c506fdd4d021c694b6ad0584485a
03bd565b1acd8cd6814cc8c8a8d2b9da
ቻይና የአሜሪካን ከዓለም ጤና ድርጅት መሸሽ ኮነነች፤ ድጋፏን እንደምታጠናክርም ገለጸች፡፡
ባሕር ዳር፡ ሚያዝያ 07/2012 ዓ.ም (አብመድ) ቻይና የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለዓለም ጤና ድርጅት የሚያደርጉትን ድጋፍ በጊዜያዊነት ማቋረጣቸውን ነቀፈች፤ እርሷ ግን ድጋፏን የበለጠ እንደምታጠናክር አስታውቃለች፡፡ ዶናልድ ትራምፕ ትናንት በሰጡት መግለጫ ‘‘የዓለም ጤና ድርጅት ለቻይና በመወገን ስለኮሮና በቂ መረጃ አልሰጠንም’’ በሚል አሜሪካ ድጋፏን ማቋረጧን አስታውቀው ነበር፡፡ የቻይና የውጭ ጉዳይ ቃል አቀባይ ዦ ሊጂያ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ደግሞ ‘‘አሜሪካ ኃላፊነቷን መወጣት ይኖርባታል፤ ቻይናም ጉዳዩን በቅርበት የምታየው ይሆናል’’ ብለዋል፡፡‘‘የአሜሪካ ውሳኔ የዓለም ጤና ድርጅትን አቅም የሚያዳክም ነው፤ ዓለማቀፍ ትብብርንም የሚጎዳ ነው፡፡ የአሜሪካ በዚህ ዓለማቀፍ የጤና ቀውስ ወቅት ከዓለም ጤና ድርጅት መሸሽ ከፍተኛ ወቀሳን እያስከተለባትና ኃላፊነት የማይሰማት ሀገር እያስባላት ነው፡፡ የጤና ባለሙያዎችና ቢሊየነሮች (ቢልጌትን ጨምሮ) የትራምፕ ውሳኔ ልክ አለመሆኑን እየተናገሩ ነው፡፡ ብሉምበርግ እንደሚለው ግን ትራምፕና ደጋፊዎቻቸው አሁንም ከዓለም ጤና ድርጅት ትክሻ አልወረዱም፤ ‘‘አስቀድሞ በሚገባ አላስጠነቀቀንም’’ እያሉ ነው፡፡በአብርሃም በዕውቀት
4ዓለም አቀፍ ዜና
https://www.amharaweb.com/%e1%89%bb%e1%8b%ad%e1%8a%93-%e1%8b%a8%e1%8a%a0%e1%88%9c%e1%88%aa%e1%8a%ab%e1%8a%95-%e1%8a%a8%e1%8b%93%e1%88%88%e1%88%9d-%e1%8c%a4%e1%8a%93-%e1%8b%b5%e1%88%ad%e1%8c%85%e1%89%b5-%e1%88%98%e1%88%b8/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
361c84c4fffd2626bf109b1b1a9d22fe
0359c5b6052d6f3f86f3305066bce5a8
በፌዴራሊስት ኃይሎች ጥምረት አባላት መታሰር የትግራይ ክልል ተቃውሞ አሰማ
ሰኞ ግንቦት 10 ቀን 2012 ዓ.ም. በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ በሚደረገው የኢትዮጵያ የፌዴራሊስት ኃይሎች ጥምረት መድረክ ላይ ለመሳተፍ በመሄድ ላይ የነበሩ የጥምረቱ አምስት አባላት፣ ከቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ተወስደው መታሰራቸው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድንጋጌዎችንና ሕገ መንግሥቱን የጣሰ መሆኑን የትግራይ ክልል መንግሥት አስታወቀ፡፡ የትግራይ ክልል ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ የጥምረቱ አባላት ማንነታቸው ባልታወቀ የፀጥታ ኃይሎች ግንቦት 7 ቀን 2012 ዓ.ም. ከሰዓት በኋላ 8፡45 ሰዓት ላይ በቁጥጥር ሥር ውለው የታሰሩት የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ንቅናቄ (አነን) ሊቀመንበር አቶ መሳፍንት ሽፈራው፣ የኢዲዩኅ አባል አቶ ገብሩ በርሄ፣ የነፃነት ለአንድነት አባል አቶ ተሻገር አረጋ፣ የኢሴዴፓ አባል መዲና ይማምና የኢዜአን ሊቀመንበር አቶ ጉዑሽ ገብረ ሥላሴ ናቸው፡፡ የኮሮና ቫይረስ ምርመራ እንደሚደረግላቸው ተነግሯቸው ከቦሌ ኤርፖርት የተወሰዱት የጥምረቱ አባላት የት እንደታሰሩ እንደማያውቅ የገለጸው ቢሮው፣ ይህ የሰብዓዊ መብት ጥሰት በመሆኑ አባላቱ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ ጠይቋል፡፡ አባላቱ በሕገ መንግሥቱ የተፈቀደላቸውን የመደራጀት መብት ተጠቅመው በፈለጉት የፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ የመሳተፍና የመደራጀት መብት ያላቸው ቢሆንም መብታቸውን መነፈጋቸውን ጠቁሟል፡፡ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ (17) የተጎናፀፉት ነፃ የመሆን መብታቸው፣ እንዲሁም በአንቀጽ 18 ተደንግጎ የሚገኘውና ለማንኛውም ኢትዮጵያዊ ሊከበርለት የሚገባው ሰብዓዊ መብት  ጥሰት እንደ ተፈጸመባቸውም ቢሮው ገልጿል፡፡ የፌዴራል መንግሥት ተገቢውን  የዕርምት ዕርምጃ በመውሰድ የታሰሩትን የጥምረቱ አባላት እንዲፈታቸው አሳስቧል፡፡ ዜጎች በነፃነት እንዳይንቀሳቀሱ የሚደረገው ክልከላና አፈናም እንዲቆም ጠይቋል፡፡ የትግራይ ክልል መንግሥት ያቀረበውን ተቃውሞና ታስረዋል ያላቸው የፌዴራሊስት ኃይሎች አባላት ለምን እንደ ታሰሩና የት እንደ ታሰሩ መረጃ ለማግኘት ሪፖርተር ያነጋገራቸው የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል እንደሻው ጣሰው፣ ከሌላ ጥምር ኃይል ጋር እየተሠራ በመሆኑ ሰሞኑን እንደሚያሳውቁ ከመናገር ውጪ ያሉት ነገር የለም፡፡ ግለሰቦቹ ከግንቦት 7 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ልደታ በሚገኘው የሕንፃ ኮሌጅ አካባቢ ለየብቻቸው መታሰራቸውንና ቤተሰብም ሆነ ሌላ አካል እየጠየቃቸው እንዳልሆነ ተጠቁሟል፡፡ ቤተሰቦቻቸው ለስብሰባ መቐለ እንደሄዱ እንጂ መታሰራቸውን ስለማያውቁ፣ መንግሥት የተጠረጠሩበት የወንጀል ድርጊት ካለም እውነታውን ነግሮ ቢያንስ እንዲጠይቋቸው ጠይቀዋል፡፡ እንዲሁም ከእስር እንዲለቀቁ ጠይቀው፣ መታሰራቸውን ከማኅበራዊ የትስስር ገጾች ማንበባቸውን የተወሰኑት የታሳሪዎች ቤተሰቦች ተናግረዋል፡፡
5ፖለቲካ
https://www.ethiopianreporter.com/article/18895
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
acc4c35b3723bba360abdd2e998762af
a56dc595794729104ed8540fe4b117bf
‹‹በአገሪቱ እየተከሰተ ያለውን ችግር ለመቅረፍ እያንዳንዱ የኃይማኖት ተቋም የበኩሉን ኃላፊነት ሊወጣ ይገባል›› ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ
፡- በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ እየተከሰተ ያለውን ችግር ለመቅረፍ እያንዳንዱ የሃይማኖት ተቋም የበኩሉን ሃላፊነት ሊወጣ እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ አሳስቡ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ከጣሊያን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ውይይት አካሂደዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትናንትናው ዕለት 400 ከሚሆኑ የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት መሪዎች ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይት መድረኩ ሃይማኖቶች በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት ላይ ከፍተኛ ሚና መጫወታቸውን የገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሃይማኖት ተቋማት አገሪቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ርዕስ በርዕስ በመናበብ በጋራ ሊሠሩ እንደሚገባና በተለይ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ እየታዩ ያሉትን ችግሮች ለመቅረፍ የሃይማኖት ተቋማት ሚና ከፍተኛ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ውይይቱ በተለያዩ የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት መሪዎች መካከል ያለውን አንድነት ለማጠናከር ያለመ መሆኑን፤ ይህም በአሁኑ ወቅት በአብያተ ክርስቲያናቱ መካከል እየታየ ያለውን የመከፋፈል አዝማሚያ ለማስቀረት ጠቅላይ ሚንስትሩ ዶክተር አብይ ተናግረዋል። ከዚህ ባለፈ የሃይማኖት ተቋማት ያሏቸውን ልዩነቶች በማክበር የሚመሳሰሉባቸውን ጉዳዮች ለማጉላት በቅንጅት መሥራት እንደሚገባቸው ጠቁመዋል፡፡ የሃይማኖት ተቋማት መሪዎችም ለተከታዮቻቸው አርአያ ሊሆን የሚችሉ ተግባራትን ማከናወን እንደሚገባቸው ገልፀዋል፡፡ የውይይቱ ተሳታፊዎች የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ፈቃድ በሚያወጡበት እና በሚያሳድሱበት ጊዜ ያሉ ችግሮችን፣ አንዳንድ የመንግሥት ተቋማት በአብያተ ክርስቲያናት የውስጥ ጉዳይ ላይ ጣልቃ የመግባት ሁኔታንና ሌሎች ጉዳዮችን አንስተዋል። በአብያተ ክርስቲያናቱ እና ምእመኑ አንድነትና ሕብረት እንዲሁም ውስጣዊ ችግሮች ላይ ጥናት አድርጎ የመፍትሄ ሀሳብ የሚያቀርብ 15 አባላት ያሉት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሯል። በተያያዘ ዜና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከጣሊያን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በአክሱም ሐውልት ጥገናና በሌሎች ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል፡፡ ከውይይቱ በኋላ ማብራሪያ የሰጡት የጣሊያን ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስት ኢማኑኤል ሲ ዴል ሪ እንዳሉት፤ የልዑካን ቡድኑ የአክሱም ሐውልት ያለበትን ሁኔታ እንደጎበኙና ቅርሱ ያለበትን ሁኔታ በመመልከት የጣሊያን ቴክኒካል ቡድን ሐውልቱ ዳግም ማደስ የሚቻልበትን መንገድ አጥንቷል፡፡ ‹‹ የቅርስ ቦታዎችን መልሶ ማቋቋም ላይ ልምድ አለን፡፡›› ያሉት ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፤ ልምዳቸውን በመጠቀም አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ አሳውቀዋል፡፡ በቻይና በተካሄደው ቤልት ኤን ሮድ ፎረም ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ከጣሊያኑ አቻቸው ጉሴፔ ኮንቴ ጋር የአክሱም ሐውል መልሶ የሚጠገንበት መንገድ ላይ ውይይት ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡ እ.ኤ.አ 2019 ሰኔ 10 ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአክሱም ከተማ በመገኘት ሐውልቱ ያለበትን ሁኔታ መጎብኘታቸው ይታወሳል፡፡አዲስ ዘመን ሰኔ 14/2011በጋዜጣው ሪፖርተሮች
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.press.et/Ama/?p=12889
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
5f8abb091e81c04d799ac3efc74ecae7
9b024fee3794734c5e1c1a100aaac5ed
1 ቱትሞስ
፩ ቱትሞስ ዓኸፐርካሬ (ግብጽኛ፦ /ጀሁቲመስ/) በጥንታዊ ግብጽ የግብጽ አዲስ መንግሥትና የ18ኛው ሥርወ መንግሥት ፈርዖን ሲሆን ምናልባት 1513-1501 ዓክልበ. የገዛ ነበረ። ቱትሞስ የቀዳሚው የ1 አመንሆተፕ አልጋ ወራሽ ተደርጎ ነበር፣ ዝምድናው ግን በእርግጡ አይታወቅም። የቱትሞስ እናት ስም ሰንሰነብ እንደ ነበር ይታወቃል። በቀዳሚው በአመንሆተፕ ዘመን ፱ኛው አመት የሥነ ፈለክ ሊቃውንት የውሻ ኮከብ (ሲሪዩስ) የተነሣበት ቀን ስለ ዘገቡ፣ የቱትሞስ ዘመን በ1513 ዓክልበ. ያህል እንደ ጀመረ ሊታወቅ ይቻላል። የጦር አለቆቹ አሕሞስ ወልደ አባና እና አሕሞስ ፐን-ነኽበት ሁለቱ በመቃብር ጽሑፎቻቸው ውስጥ በኩሽ መንግሥትና በ «ናሓሪን» (ምሥራቅ ሶርያ) ላይ በዓኸፐርካሬ ዘመን እንደ ዘመቱ ዘግበዋል። በናሓሪን አገር ግብጻውያን ሠረገሎች፣ ፈረሶችና ባርዮችን ማረኩ። የመርከብ ኃይል አለቃ አሕሞስ ወልደ አባና እንደ ገለጸው፣ ፈርዖኑ መጀመርያ በረጨኑ (ምዕራቡ ሶርያ) ደርሶ ከዚያ በናሓሪን ዘመተ። ወደ ደቡብ በከነዓን/እስራኤል የሚቃወሙት ሕዝብ ባይጠቀሱም፣ ግብጻውያን በመርከብ በሶርያ እንደ ደረሱ ይቻላል። በኋላም የ3 ቱትሞስ ጽላት እንዳለ፣ በኤፍራጥስ ወንዝ ላይ በ1 ቱትሞስ ድሮ ጽላት አጠገብ ሌላ ጽላት አቆመ። «ናሓሪን» ማለት ከኤፍራጥስ ማዶ ወይም አራም-ናሓራይን ሲሆን ከትንሽ በኋላ ይህ የአዲሱ ሚታኒ መንግሥት መጠሪያ ሆነ፤ ኗሪዎቹም ያንጊዜ ሑራውያን ተባሉ። እንዲሁም የውሃ ሰዓት ፈልሳፊውና የከዋክብት መርማሪው አመነምኸት በጻፈው መግለጫ የ«መተኒ» (ሚታኒ) ዘመቻ ሲጠቅስ፣ ማለቱ ይኸኛው የ1 ቱትሞስ እንደ ነበር ይታመናል። የሶርያ ዘመቻ በ፪ኛው ዓመት (1512 ዓክልበ. ገደማ)፣ የኩሽ ዘመቻ በ፩ኛውና ፫ኛው ዓመቶቹ (1513 እና 1511 ዓክልበ.) እንደ ተከሠቱ ይታመናል። በኩሽ ኖቢያ ጠረፉን ከ፪ኛው የአባይ ሙላት (ቡሄን አምባ) ወደ ደቡብ ከ፬ አባይ ሙላት ደቡብ እስካለው ድረስ አስፋፋው። የዘመኑም ፰ኛውና ፱ኛው ዓመቶች የሚጠቀሱ ቅርሶች ስለ ተገኙ፣ የማኔቶን መረጃ 12 ዓመት 9 ወር እንደ ቆየ ሆኖ ይህ እንደ ትክክል ያህል ተቀብሏል። ተከታዩ 2 ቱትሞስ ልጁ በንግሥቱ ሙትኖፍረት ነበር። በሌላ ንግሥቱ ንግሥት አሕሞስ ደግሞ ሴት ልጁን ሃትሸፕሱት ወለደ፤ እርሷም የ2 ቱትሞስ ንግሥትና ወደፊትም በራሷ መብት የግብጽ ንግሥት ሆነች። የአዲስ መንግሥት ፈርዖኖች
null
null
https://huggingface.co/datasets/yosefw/amharic-wikipedia
e177ed7af9d76277c129d071b503b80f
553446b0de3cb72a40f968d2590ff6a6
በሜክሲኮ በኮሮና ቫይረስ ሳቢያ ለህልፈት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር ከ46 ሺህ አልፏል
አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 25 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በሜክሲኮ በኮሮና ቫይረስ ሳቢያ ለህልፈት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር ከ46 ሺህ አልፏል፡፡አሁን ላይ በሃገሪቱ 424 ሺህ 637 ሰዎች ቫይረሱ ሲገኝባቸው 46 ሺህ 688 ሰዎች ደግሞ ለህልፈት ተዳርገዋል ተብሏል፡፡ይህን ተከትሎም በቫይረሱ ለህልፈት በተዳረጉ ሰዎች ቁጥር ከአሜሪካ እና ብራዚል ቀጥላ ሶስተኛዋ ሃገር ሆናለች፡፡የሃገሪቱ የተለያዩ ግዛት አስተዳዳሪዎች ደግሞ ቫይረሱ ያለባቸው ሰዎች ቁጥር ሪፖርት ከተደረገው በላይ መሆኑን ይናገራሉ፡፡መንግስት የቫይረሱን ስርጭት ለመቆጣጠር ያደረገው ጥረትም አነስተኛ ነው በሚል በሃገሪቱ ጤና ሚኒስቴር ላይ ትችት ሰንዝረዋል፡፡ምንጭ፣ ቢቢሲ
4ዓለም አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%89%a0%e1%88%9c%e1%8a%ad%e1%88%b2%e1%8a%ae-%e1%89%a0%e1%8a%ae%e1%88%ae%e1%8a%93-%e1%89%ab%e1%8b%ad%e1%88%a8%e1%88%b5-%e1%88%b3%e1%89%a2%e1%8b%ab-%e1%88%88%e1%88%85%e1%88%8d%e1%8d%88%e1%89%b5/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
412c1aff128ffc964a3a42aa8effae74
df512a08628995f67f14f664bd3212f8
የደቡብ ሱዳን አማጺ ቡድን ጦር መሪ ፖል ማሎንግ በሀገሪቱ የተኩስ አቁም ስምምነት ዘላቂ እንዲሆን እንደሚሰሩ ገለጹ
የቀድሞ የደቡብ ሱዳን የጦር አዛዥና የአማጺ ቡድኑ ጦር መሪ ፖል ማሎንግ በሀገሪቱ የተደረገው የተኩስ አቁም ስምምነት ዘላቂ እንዲሆን እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡ደቡብ ሱዳን ለአመታት በእርስ በእርስ ግጭት ስትታመስ መቆየቷ ይታወቃል፡፡ ሃገሪቱ በተለያዩ የሃገሪቱ አማፂያን ቡድኖች ከጦርነት አለመላቀቋን ተከትሎ የምስራቅ አፍሪካ በይነ መንግስታት በሀገሪቷ ሰላም ለማስፈን የተለያዩ የሰላም ድርድሮች ሲካሄዱ ቆይቷል፡፡የቀድሞ የሃገሪቱ የጦር አዛዥ ማሎንግ የምስራቅ አፍሪካ በይነ መንግስታት መልዕክተኞችን ተቀብለዉ ያነጋገሯቸዉ ሲሆን በዚህም የደቡብ ሱዳን ጦርነት እንዲያበቃ በሰላማዊ መንገድ መደራደር እንደሚፈልጉ ገልፀዋል፡፡ማሎንግ ቀደም ሲል ኢጋድ ባካሄደዉ የመደራደሪያ ሂደት መካፈል ፈልገዉ እንደነበር ፍላጎት የነበራቸዉ ቢሆንም በወቅቱ አደራዳሪዎቹ አለምአቀፍ ማዕቀብ ተጥሎባችኋል በማለት ጥያቄአቸዉን ውድቅ በማድረጋቸዉ በድርድሩ ላይ ሳይካፈሉ መቅረታቸዉን ተናግረዋል፡፡በኢጋድ የደቡብ ሱዳን ልዩ መልዕክተኛ እስማኢል ዋኢስ ዩናይትድ ፍሮንት ከተሰኘዉ የደቡብ ሱዳን የቀድሞ አማፂ ቡድን በናይሮቢ ኬኒያ ኢጋድ ባዘጋጀዉ ስብሰባ ተገኝተዉ በደቡብ ሱዳን የተኩስ አቁም ስምምነትና በምን አይነት መንገድ ሰላም ማስፈን እንሚቻል ተወያይተዋል፡፡ደቡብ ሱዳን እ.አ.አ ታህሳስ 21 2017 የሃገሪቱን ሰላም መመለስ፣ ንፁሃን ዜጎችን ደህንነት ማረጋገጥና ሰብአዊ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸዉ ዜጎች እርዳታ እንዲያገኙ ማስቻል በሚሉት ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ ደርሰዉ እንደነበርም የጦር አዛዡ አስታዉሰዋል፡፡ከዚህም በተጨማሪ አማፂ ቡድኑ በደቡብ ሱዳን የማይጣስ የተኩስ አቁም ስምምነት ለማምጣት ስምምነት ላይ እንደደረሱና በቡድኑ በኩል ሙሉ ተነሳሽነትና ፍላጎት እንዳላቸዉ አስታዉቀዋል፡፡ቀደም ሲል እኤአ  በ2017 ላይ በተደረገዉ የኢጋድ መደበኛ ጉባኤ አማፂ ቡድኑ በአሜሪካ፣ 2018 ላይ ደግሞ በኢጋድ በርካታ ማእቀቦች ተጥሎባቸዉ እንደነበር ገልፀዉ አሁን በኢጋድ መልዕክተኞች የቀረበዉ የሰላም መልእክትን ግን ከዚህ በኋላም በደቡብ ሱዳን ሰላም ለማምጣት ጥረታችንን አጠናክረን እንድንቀጥል ያስችለናል ብለዋል፡፡ሰላምን ለማረጋገጥ በሚደረግ ማንኛዉም ድርድር ምንም አይነት ተቃዉሞ እንደሌላቸዉ የገለፁት ማሎንግ የምንታገለዉም ደቡብ ሱዳናዉያንን ከጦርነት ለማዉጣት ሰላምና መረጋጋት የሰፈነባት ለዜጎቿ ምቹ የሆነች ሃገር ለመመስረት ነዉ ሲሉ አክለዋል፡፡አማፂ ቡድኑ የሰላም ድርድሩንና የተኩስ አቁም ስምምነቱን በምን አይነት መንገድ እንደሚያስኬደዉ እንዲሁም ከሃገሪቱ መንግስት ጋር ድርድሩን እንደሚያስቀጥለዉ በመረጃዉ አልታወቀም፡፡ (ምንጭ፡- ሱዳን ትሪቡን)
5ፖለቲካ
https://waltainfo.com/am/33228/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification
88579304625b8c97e598768d9e5335eb
212b667d3e925dd0b7445ad700c57ec5
አሜሪካ ፈንጂ አነፍናፊ ውሾችን ወደ ዮርዳኖስና ግብጽ ላለመላክ ወሰነች። እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰችው በቸልተንነት የተነሳ በርካታ ውሾች ከሞቱ በኋላ ነው ተብሏል።
አሜሪካ አነፍናፊ ውሾዎቼ 'ነጡ፤ ገረጡብኝ' በሚል ወደ ግብጽና ዮርዳኖስ ላለመላክ ወሰነች\nአነፍናፊ ውሾች የጸረ ሽብር ተግባሩን ለማገዝ በተለያዩ ሀገራት ተሰማርተው ይገኛሉ "በተልዕኮ ላይ ያለ የየትኛውም ውሻ ሞት ልብ ይሰብራል" ያሉት የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ቃል አቀባይ ናቸው። በመስከረም ወር የወጣ አንድ ሪፖርት ይፋ እንዳደረገው በዮርዳኖስ፣ ግብጽና ሌሎች ስምንት አገራት ለግዳጅ ከተላኩ ከ100 በላይ አነፍናፊ ውሾች በቸልኝነትና እንክብካቤ ጉድለት የተነሳ መጎሳቆላቸወን አሳይቷል። • ለማነፍነፍ የሰነፈችው ጥሩ ውሻ • ሟች አሳዳጊውን የሚጠባበቀው ውሻ የአሜሪካ አነፍናፊ ውሾች የጸረ ሽብር ፕሮግራሙን ለመደገፍ የተሰማሩ ናቸው። ዮርዳኖስም ሆነች ግብጽ በጉዳዩ ላይ እስካሁን ድረስ አስተያየታቸውን አልሰጡም። አሜሪካ ጊዜያዊ እገዳዋን ይፋ ያደረገችው ሰኞ እለት ሲሆን የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት እንዳስታወቀው እርምጃው የተወሰደው ተጨማሪ ሞትን ለመከላከል ነው። ውሾቹ "ከሌሎች አገራት ጋር በመሆን የምናደርገውን የጸረ ሽብር ተግባር በመደገፍና የአሜሪካዊያንን ሕይወት በመታደግ ረገድ ቁልፍ ሚና አላቸው" ብለዋል ባለስልጣኑ። ባለስልጣኑ አክለውም በዮርዳኖስና ግብጽ ያሉት ውሾች ለጊዜው በዚያው ይቆያሉ ብለዋል። በከፍተኛ ሁኔታ ክብደታቸው የቀነሰ ሁለት አነፍናፊ ውሾች በጆርዳን የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ያወጣው ሪፖርት እንደሚያሳየው እ.ኤ.አ. በ2017 አንድ ውሻ በዮርዳኖስ በከፍተኛ ሙቀት ምክንያት ህይወቱ አልፏል። ሌሎች ሁለት ውሾች ደግሞ "ክፉኛ ታመው ወደ አሜሪካ ተመልሰዋል" ይላል ሰነዱ። • 'ሕዝቤ ሆይ! እባክህ ውሻ አትብላ'፡ ቪየትናም • "በዓይን የሚታይ የእምቦጭ አረም ወደ ሚቀጥለው ዓመት እንዳይተላለፍ እናደርጋለን" የአሜሪካ ባለሰልጣናት እንዳሉት ከሆነ ውሾቹ ተጎሳቁለውና ክብደታቸው ቀንሶ ስለነበር ጤንነታቸው እስኪመለስና እስኪያገግሙ ድረስ እንክብካቤ እየተደረገላቸው ነው። በቅርቡ የወጣ ሌላ ሪፖርት እንደሚያሳየው ደግሞ ወደ ዮርዳኖስ ከተላኩ ውሾች ሁለቱ "ተፈጥሮአዊ ባልሆነ ምክንያት" ሞተዋል። የፈረንሳዩ የዜና ወኪል እንደዘገበው ከሆነ አንዱ ውሻ በከፍተኛ ሙቀት ሌላኛው ደግሞ የፖሊስ አባል በረጨው የተባይ ማጥፋያ ምክንያት ሞተዋል። በርካታ አነፍናፊ ውሾች ከአሜሪካ ወደ ዮርዳኖስ የሚሄዱ ሲሆን 100 ያህሉ ደግሞ በመከከለኛው ምሥራቅ አገራት ተሰማርተው ይገኛሉ። የአሜሪካ ሪፖርት እንደሚያሳየው ወደ ግብጽ ለግዳጅ ከተላኩ ውሾች አስር ያህሉ በሳንባ ካንሰር፣ በከፍተኛ ሙቀት እንዲሁም በሽንት ፊኛ መቀደድ ምክንያት ተልዕኳቸውን መፈፀም አቅቷቸዋል።
null
null
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/xlsum_amharic_summarization
cdb405622e6acc998f129990c38d3ddf
6fc4bd7ada086b3ba843360336a1d54f
በአርሲ ዞን የመጀመሪያው የግብርና ባዛርና የገበያ ትስስር ኤግዚቢሽን እየተካሄደ ነው
አዲስ አበባ፣ ህዳር 30፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)በአርሲ ዞን የመጀመሪያው የግብርና ባዛርና የገበያ ትስስር ኤግዚቪሽን እየተካሄደ ይገኛል።በመርሃ ግብሩ የግብርና ውጤቶች፣ ቴክኖሎጂዎች፣ ግብአቶች ከአምራቹ ወደ ገዢው በቀጥታ የሚቀርቡበት ነውም ተብሏል።አምራቾች ቀጥታ ለሸማቾች ምርቶቻቸውን ማቅረባቸውም የሽያጭ ሰንሰለቱን በማሳጠር የዋጋ ውድነትን የሚቀንስ እንዲሁም ለአርሶ አደሩ የገበያ ትስስርን የሚፈጥር መሆኑን የአርሲ ዞን ግብርናና ተፈጥሮ ሀብት ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አባቡ ዋቆ ተናግረዋል።በተጨማሪም ሃላፊው መርሃ ግብሩ በዞኑ ለመጀመሪያ ጊዜ መዘጋጀቱን ገልፀው፤ ከዚህ በፊት ይነሱ የነበሩ የገበያ ትስስር ችግሮችን ይፈታል ብለዋል።በግብርና ባዛርና ኤግዚቢሽኑ የግብርና ቴክኖሎጂ አምራቾች፣ የፀረ አረምና ፀረተባይ አምራች ኩባንያዎች፣ ማህበራት እና አርሶ አደሮች ምርቶቻቸውን ያቀረቡ ሲሆን በዞኑ የሚገኙ ወረዳዎችም ተሳታፊ ሆነዋል።መርሃ ግብሩ ለ3 ቀናት ይቀጥላልም ነው የተባለው።በአፈወርቅ እያዩ
0ሀገር አቀፍ ዜና
https://www.fanabc.com/%e1%89%a0%e1%8a%a0%e1%88%ad%e1%88%b2-%e1%8b%9e%e1%8a%95-%e1%8b%a8%e1%88%98%e1%8c%80%e1%88%98%e1%88%aa%e1%8b%ab%e1%8b%8d-%e1%8b%a8%e1%8c%8d%e1%89%a5%e1%88%ad%e1%8a%93-%e1%89%a3%e1%8b%9b%e1%88%ad/
https://huggingface.co/datasets/rasyosef/amharic-news-category-classification