Dataset Viewer
Auto-converted to Parquet
doc_no
int64
1
12.6k
doc_text
stringlengths
81
395k
relevant_topic_nos
sequencelengths
0
1
relevant_topic_titles
sequencelengths
0
1
relevant_topic_descriptions
sequencelengths
0
1
relevant_topic_narratives
sequencelengths
0
1
1
 16ኛ አለም አቀፍ የኤችአይቪኤድስና የአባላዘር በሽታዎች በአፍሪካ 2011አይካሳ ጉባኤ ተጀመረ, ህዳር 242004ዋኢማ 16ኛው አለም አቀፍ የኤችአይቪኤድስና የአባላዘር በሽታዎች በአፍሪካ 2011አይካሳ ጉባኤ በርካታ እንግዶች በተገኙበት በደመቀ ሁኔታ በሚሌኒየም አዳራሽ በይፋ ተከፈተ። በጉባኤው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኤድስ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ሚስተር ሚሼል ሲዲቤ በአፍሪካ ኤችአይቪኤድስን በመከላከልና በመቆጣጠር ረገድ ተጨባጭ የሆነ እንቅስቃሴ ሴደረግ እንደነበር ቀደም ሲል  የተሰሩ ስራዎችና ከውጤቶቻቸው ማየት ተችሏል ብለዋል። ቀደም ባሉት አመታት በአፍሪካ ኤችአይቪኤድስን መከላከልም ሆነ መቆጣጠር እንደማይቻል ይገለፅ እንደነበር ጠቁመው፤ አሁን እየታየ ያለው አበረታች ውጤት ቀደም ሲል ይታሰብ የነበረውን አመለካከት መለወጠቱን   ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ በኤችአይቪኤድስ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር በእጅጉ እየቀነሰ መመጣቱንና የጸረ ኤችአይቪኤድስ መድኃኒት ተጠቃሚዎችም ቁጥር ባስገራሚ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱ የስራው ውጤት ማሳያ መሆኑን ገልፀዋል። ቀደም ባሉት አመታት ኡጋንዳና ሴኔጋል የኤችአይቪኤድስ ስርጭትን በመቆጣጠር ረገድ ከአፍሪካ አህጉር ይጠቀሱ እንደነበር ጠቁመው፤ በአሁኑ ወቅት ግን ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ25 በላይ የሚሆኑ ሀገራት የኤችአይቪ ኤድስ ቫይረስ ስርጭትን ለመቆጣጠር ችለዋል መቻላቸውን ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡በተለይም ኤችአይቪ ከእናት ወደ ልጅ እንዳይተላለፍና ህፃናት ከቫይረሱ ነፃ ሆነው እንዲወለዱ በአፍሪካ እየተደረገ ያለው ጥረት አበረታች ውጤት እየታየበት መሆኑን ጠቁመው፤ በአህጉሪቱ አስገራሚ ለውጥ መገኘቱንም አመልክተዋል፡፡ኤችአይቪኤድስ በአፍሪካ የበርካታ ዜጎችን ህይወት መቅጠፉን ያስታወሱት ሲዲቤ፤ በተከናወኑት በርካታ ስራዎች የቫይረሱን ስርጭት ፍጥነትና በፀረ-ኤች አይ ቪ መድኃኒት እጦት ምክንያት የሚጠፋውን ህይወት መታደግ ተችሏል ብለዋል። የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ኤችአይቪኤድስ ስርጭትን በመከላከሉና በመቆጣጠር በኩል አመርቂ ውጤት አስመዝግባለች ብለዋል። ለውጤቱም በመላው ሀገሪቱ የተሰማሩት 34ሺ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች በህብረተሰቡ ውስጥ መሰማራታቸውና ውጤታማ ስራ መስራታቸው ለአብነት የሚጠቀስ ነው ብለዋል። ኤችአይቪኤድስ ስርጭትና መከላከሉና በመቆጣጠሩ ረገድ የተጀመረው ስራ ወደፊትም በተጠናከረ ሁኔታ   እንደሚቀጥልም ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ገልፀዋል። 16ኛ አለም አቀፍ የኤችአይቪኤድስና የአባላዘር በሽታዎች በአፍሪካ 2011አይካሳ ጉባኤ  « » በሚል መሪ ቃል ለአምስት ቀናት የሚካሄድ መሆኑን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል። ዋኢማአዓ ),
[ 1 ]
[ "የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምርመራ እና የምክር አገልግሎት" ]
[ "ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምክርና የምርመራ አገልግሎት አሰጣጥና የሚሰጥባቸው ቦታወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት." ]
[ "ሥለ ኤድስ በሽታ ምርመራ, የምክር አገልግሎት, ስለሚሰጡባቸው ቦታወች ወይም የህክምና ተቋማት( ሆስፒታሎች,የጤና ኬላወች ) ,ምርመራ ስለሚያደርጉ ሰወች የሚአትቱ ሰነዶች በሙሉ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሰለ ኤድስ በሽታ ባህሪና ስርጭት, መከላከያ, መቆጣጠሪያ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
2
በክልሉ 140 ሺህ ሰዎች ኤች አይ ቪ ኤድስ በደማቸው መኖሩ ተረጋገጠ፡፡ ባሕር ዳር፡ ሕዳር 22/2011ዓ.ም (አብመድ) በርካታ የወሲብ ጓደኞችን መያዝ እና በልጅነት ዕድሜ የግብረ ስጋ ግንኙነት ማድረግም በሽታው እንዲዛመት አድርገዋል፡፡ 30ኛውን የዓለም የኤድስ ቀን ምክንያት በማድረግ ‹‹ለኤች አይ ቪ ይበልጥ ተጋላጭ ነን፤ እንመርመር፤ ራሳችንን እንወቅ›› በሚል መሪ ሃሳብ በአማራ ክልል ጤና ቢሮ እና በባህር ዳር ጤና መምሪያ ትብብር የተዘጋጀ የፓናል ውይይት ተካሂዷል፡፡ ውይይቱ የተካሄደው ኤድስ በክልሉ እና በሀገሪቱ እያመጣ ያለውን ኪሳራ ለመቀነስ እና በሽታውን ለማጥፋት ነው፡፡ ኤች አይቪ ኤድስ ያለበትን ደረጃ የሚጠቁም እና ምን አይነት ጉዳት እያደረሰ እንዳለ የሚያመለክት ጥናት በአማራ ክልል ጤና ቢሮ ቀርቧል፡፡ በዓለም 36 ሚሊዮን ሰዎች በኤች አይቪ ኤድስ እንደተያዙ እና ከዚህ ቁጥር 70 በመቶ የሚሆነውን የአፍሪካ ሀገራት እደሚይዙ ተመላክቷል፡፡ አሁን ባለው መረጃ መሰረት በአማራ ክልል 140 ሺህ ሰዎች ኤች አይቪ ኤድስ በደማቸው ይገኛል፡፡ከፍተኛውን ቁጥር የሚይዙት ደግሞ ሀገር ተረካቢ ወጣቶች ናቸው፡፡ ከገጠር ወደ ከተማ የሚፈልሱ ሰዎች ቁጥር መብዛት፣ ሴተኛ አዳሪነት ቁጥር፣ ኤች አይ ቪ ኤድስ ጠፍቷል የሚል አስተሳሰብ መኖር እና ከዚህ ቀደም የነበረው የተቀናጀ ትኩረት መቀነሱ ኤች አይቪ ኤድስ በክልሉ እንዲስፋፋ ካደረጉት ምክንያቶች ተጠቃሽ እንደሆኑ ነው በቢሮው የተገለጸው፡፡ የአማራ ክልል ጤና ጥበቃ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አበባው ገበየሁ ችግሩ በረጅም ርቀት አሽከርካሪዎች፣በከፍተኛ ትምረት ተቋማት፣በድርጅት ስራዎች እና በቀን ሰራተኞች በስፋት እንደሚከሰት ነው የተናገሩት ነው፡፡ በርካታ የወሲብ ጓደኞችን መያዝ እና በልጅነት ዕድሜ የግብረ ስጋ ግንኙነት ማድረግም በሽታው እንዲዛመት አድርገዋል ነው ያሉት ዶክተር አበባው፡፡ የሃይማኖት አባቶች በየእምነት ተቋማቸው ስለ በሽታው አስከፊነት እንዲያስተምሩም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የክልሉ ጤና ጥበቃ ቢሮ ቫይረሱ በደማቸው ያለባቸውን ሰዎች በምርመራ በማሳወቅ፣መድሃኒት በማስጀመር፣በበሽታው የተያዙ ሰዎችን በመንከባከብ እና ብቁ በማድረግ በኩል 90 በመቶ በመስራት ኤች አይቪ ኤድስን ለመቀነስ እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡
[ 1 ]
[ "የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምርመራ እና የምክር አገልግሎት" ]
[ "ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምክርና የምርመራ አገልግሎት አሰጣጥና የሚሰጥባቸው ቦታወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት." ]
[ "ሥለ ኤድስ በሽታ ምርመራ, የምክር አገልግሎት, ስለሚሰጡባቸው ቦታወች ወይም የህክምና ተቋማት( ሆስፒታሎች,የጤና ኬላወች ) ,ምርመራ ስለሚያደርጉ ሰወች የሚአትቱ ሰነዶች በሙሉ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሰለ ኤድስ በሽታ ባህሪና ስርጭት, መከላከያ, መቆጣጠሪያ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
3
26ኛው የዓለም የኤች አይ ቪ ኤድስ ቀን በአገር ደረጃ በጋምቤላ ክልል ይከበራል, - ; .._2014. 0 261 197 ; 5; አዲስ አበባ፤ ህዳር162007 (ዋኢማ) - 26ኛው የዓለም የኤች አይቪኤድስ ቀን በአገር አቀፍ ደረጃ በጋምቤላ ክልል ይከበራል ። - ; የፌደራል  ኤች አይቪ  ኤድስ ጥምር  መከላከያና መቆጣጣሪያ  ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ እንደሻው ወልደሰንበት ለዋልታ እንደገለጹት   የዓለም የኤች አይቪ ኤድስ ቀን በአገር አቀፍ ደረጃ  በጋምቤላ  ክልል ዋና ከተማ  በሆነችው የጋምቤላ ከተማ ከህዳር  21  ጀምሮ ለአንድ ሳምንት በተለያዩ  ዝግጅቶች እንደሚከበር ገልጸዋል ። - ; በዓሉ  በሚከበርበት  አንድ ሳምንት  ጊዜ ውስጥ ከ2ሺ ሰዎች  በላይ በፈቃደኝነት  ላይ የተመሠረት  የኤች አይቪ ምርመራ እንደሚያድርጉ   የገለጹት አቶ  እንደሻው በተለይ  ከበዓሉ ጋር ተያይዞ  ነብስ  ጡር  ሴቶች የኤች አይቪ ምርመራን  በማካሄድ ላይ ትኩረት እንዲሠጡ   ትምህረት  ይሠጣል ብለዋል ። - ; እንደ አቶ እንደሻው ማብራሪያ  የጋምቤላ ክልል  የኤች አይቪ ኤድስን በአገር ደረጃ ለማክበር የተመረጠው በክልሉ የኤች አይቪ ኤድስ ሥርጭቱ ከፍተኛ በመሆኑ ሲሆን ኤች አይቪ ኤድስን በጋራ በመከላከል ረገድ  በክልሉ መነሳሳትና ንቅናቄ  ለመፍጠር ታቅዷል ብለዋል ። - ; የጋምቤላ ክልል ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ጽህፈት ቤት የዘርፉ ምላሽ ሰጪ ስራ ሂደት ባለቤት አቶ ደሳለኝ ብሩ በበኩላቸው በስምንት ሰዓታት ውስጥ 5ሺ ሰዎች በፍቃደኝነት የተመሠረተ  የኤች አይቪ  ምርመራ  ለማካሄድ ዝግጅታቸውን ማጠናቀቃቸውን አስታውቀዋል ። - ; በጋምቤላ ክልሉ የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭት 6ነጥብ 5 በመቶ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ደሳለኝ  በተለይም በማጃንግ ዞን የስርጭቱ መጠን 13ነጥብ6 በመቶ ላይ  የሚገኝ በመሆኑ  ተጨማሪ ሥራዎች  እንደሚያስፈልጉ አመልክተዋል ። - ; በኢትዮጵያ  700 ሺ የሚሆኑ ሰዎች  በኤች አይቪ ኤድስ ቫይረስ  በደማቸው ውስጥ እንደሚገኝና የቫይረሱ ሥርጭት  1ነጥብ 2  በመቶ ላይ  የተመዘገበ ሲሆን  በአገር ደረጃ  እየቀነሰ  የመጣውን የኤች አይቪ ኤድስ  ዳግም እንዳያንሰራራ  አሁንም ህብረተሰቡ  ጥንቃቄ አንዲያደርግ  አቶ ደሳለኝ ጥሪ አቅርበዋል ። ),
[ 1 ]
[ "የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምርመራ እና የምክር አገልግሎት" ]
[ "ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምክርና የምርመራ አገልግሎት አሰጣጥና የሚሰጥባቸው ቦታወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት." ]
[ "ሥለ ኤድስ በሽታ ምርመራ, የምክር አገልግሎት, ስለሚሰጡባቸው ቦታወች ወይም የህክምና ተቋማት( ሆስፒታሎች,የጤና ኬላወች ) ,ምርመራ ስለሚያደርጉ ሰወች የሚአትቱ ሰነዶች በሙሉ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሰለ ኤድስ በሽታ ባህሪና ስርጭት, መከላከያ, መቆጣጠሪያ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
4
የስራ ሃላፊዎች የደም ምርመራ በማድረግ አራያ ለሆኑ ይገባል ተባለ ። በኤች አይቪ ኤድስ ያለውን ዝምታ ለመስበር የክልሉ የስራ ሃላፊዎችና ታዋቂ ሰዎች የደም ምርመራ እንዲያደርጉ የጅጅጋ ከተማ ነዋሪዎቹ ጠየቁ ፤ በምስራቅ ሸዋ ዞን ከበሽታው ጋር የሚኖሩ 22 ሰዎች ህዝቡን ለማስተማር መዘጋጀታቸውን ገለጹ ። የጅጅጋ ከተማ አንዳንድ ነዋሪዎች የበሽታውን መዛመት በማስመልከት ሰሞኑን እንደገለጹት የመስተዳድር አካላት ፣ የቢሮ ሃላፊዎችና የቀበሌ አመራሮችና ታዋቂ ግለሰቦች ችምር አች አይቪ ኤድስ ምርመራ በማድረግ ለህዝቡ አራያ ሊሆኑ ይገባል ። የጅጅጋ ካራማራ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ሀረጉ ንጉሴ በበኩላቸው የነዋሪው ጥያቄ እውነትነት እንዳለውና በፈቃደኝነት የደም ምርመራ ለማድረግ ወደ ሆስፒታሉ ለሚመጡ ሰዎች ሆስፒታል ነጻ የኤች አይቪ ኤድስ ምርመራ ለማካሄድ መዘጋጀቱን አስታውቀዋል። የክልሉ የኤች አይቪ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ሴክሬታሪያት ሃላፊ ዶክተር ከድር መሀመድ በበኩላቸው ክልሉ ከፍተኛ የንግድና እንቅስቃሴ የሚታይበት በመሆኑ ባልስልጣናትና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ከምርመራው በተጓዳኝ በማስተማሩም በኩል ቢሳተፉ የተሻለ ግንዛቤን ለማስጨበጥ ይችላሉ ብለዋል ። ይህ በእንዲህ እንዳለ በምስራቅ ሸዋ ዞን ከበሽታው ጋር የሚኖሩ 22 ሰዎች ሀብረተሰቡን ለማስተማር በአዳማ ልዩ ወረዳ አች አይቪ አድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ጽህፈት ቤት በፈቃደኝነት ቀርበው መመዝገባቸውን የጽህፈት ቤቱ አስተባባሪ አቶ አሚር መሀመድ ገልጸዋል ። ካለፈው ነሀሴ እስከ ህዳር አጋማሽ የሃኪም ማስረጃ በመያዝ በፈቃደኝነት የተመዘገቡ እነዚሁ ሰዎች " ትውልድ ይዳን በእኛ ይብቃ" በሚል መርህ በዞኑ የተለያዩ ከተሞች በመዘዋወር ትምህርት ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ገጸዋል ። ጽህፈት ቤቱም ለህክምና በየወሩ ከ135- 200 ብር በመስጠት ለተነሱለት አላማ እገዛ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል ። አስተባባሪው አያይዘውም ከብሄራዊ ኤች አይቪ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ሴክሬታሪያት ቢሮ ለጽህፈትቤቱ 304 ሺ ብር በጀት በመመደቡ በወረዳው 69 ቀበሌ ገበሬ ማሀበራት አስር አባላት ያላቸው የቀበሌ ጸረ- ኤድስ ኮሚቴዎች በማቋቋም ትምህርት እየሰጠ እንዳለና ከቫይረሱ ጋር ለሚኖሩና ወላጅ ላጡ ህጻናት እንክብካቤ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል ። በተመሳሳይ በጅማ ዞን " መቅድም እትዮጵያ " የበተሰኘ የኤቻይቪ ኤድስ መከላከያ ማሀበር የተሰባሰቡና ከበሽታው ጋር የሚኖሩ አባላት ስለኤድስ በሽታ መከላከያ ዘዴ ህዝቡን ለማስተማር መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል ። ህጻናትን ያለአሳዳጊ ፣ አረጋውያንን ያለጧሪ በማሰቀረት ላይ ያለውን የዚሁን በሽታ ስርጭት ለመግታት አባላቱ በገ ጠሩ ዘልቆ በመግባት ህዝቡን ለማስተማር መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል ። ከ20 -30 አመት እድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ቫይረሱ በደማቸው የሚገኙባቸው እነዚሁ ወጣቶች መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ የመከላከል ዘመቻ እያደረገ ባለበት ወቅት እነሱ ሳያውቁ በቫይረሱ እንደተያዙ ሁሉ ሌላው ሀብረተሰብ ከእነሱ ትምህርት እንዲወስድ አስቀድሞ ለማስተማር ቃል ገብተዋል ። ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ እያለ በማሀበሩ ያልተደራጁ ሌሎች ወገኖችም ራሳቸውን ከመደበቅ ይልቅ በማሀበሩ በመደራጀት ወገናቸውን ከበሽታው እንዲያድኑ ጥሪ አቅርበዋል ።
[ 1 ]
[ "የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምርመራ እና የምክር አገልግሎት" ]
[ "ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምክርና የምርመራ አገልግሎት አሰጣጥና የሚሰጥባቸው ቦታወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት." ]
[ "ሥለ ኤድስ በሽታ ምርመራ, የምክር አገልግሎት, ስለሚሰጡባቸው ቦታወች ወይም የህክምና ተቋማት( ሆስፒታሎች,የጤና ኬላወች ) ,ምርመራ ስለሚያደርጉ ሰወች የሚአትቱ ሰነዶች በሙሉ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሰለ ኤድስ በሽታ ባህሪና ስርጭት, መከላከያ, መቆጣጠሪያ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
5
በስድስት ወራት ውስጥ 4 ሚሊየን ሰዎች የኤች አይ ቪ ኤድስ ምርመራ አደረጉ, - ; .._2015_16. 0 199 197 ; 5; አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 72007 (ዋኢማ) - በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ መንፈቅ ዓመት 4 ሚሊየን ሰዎች በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ የኤች አይ ቪ ኤድስ ምርመራ ማድረጋቸውን የፌደራል ኤች አይቪኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ። - ; የጽሕፈት ቤቱ የዕቅድ ፣ ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ተጠባባቂ ዳይሬክተር ዶክተር አቻምየለህ አለባቸው ለዋልታ እንደገለጹት በስድት ወራቱ ውስጥ ምርመራ ከተደረገላቸው ሰዎች ውስጥ ከ1 በመቶ በታች የሚሆኑት ቫይረሱ በደማቸው ተገኝቶባቸዋል። - ; ተጠባባቂ ዳይሬክተሩ አያይዘው እንደገለጹት በመላው አገሪቱ በተደረገው የተቀናጀ ጥረት የቫይረሱ ስርጭት በተለይም ባለፉት ሶስት ዓመታት ወደ 1 ነጥብ 2 በመቶ መውረዱን ገልጸዋል። - ; በተያዘው በጀት ዓመት ደግሞ ስርጭቱን ወደ 0 ነጥብ 9 በመቶ ለማውረድ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ጨምረው ተናግረዋል። - ; የቫይረሱ ስርጭት በአገር አቀፍ ደረጃ እየቀነሰ ቢመጣም የጋምቤላ ክልልን ጨምሮ  በአነስተኛ ከተሞችና በገጠር አካባቢዎች አሁንም ሥርጭቱ መኖሩን ዶክተር አቻምየለህ አመልከተዋል። - ; በጋምቤላ ክልል በተለይ በማጃንግ ዞን ባለው ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት ሳቢያ የበሽታው ስርጭት 13 ነጥብ 6 በመቶ መድረሱን የተናገሩት ዶክተር አቻምየለህ ስርጭቱን ለመግታት ህብረተሰቡና የመንግስት አመራሮች ጥረት እያደረጉ መሆኑን አስረድተዋል። - ; እስካሁን በተደረጉትም ጥረቶች ህብረተሰቡ በቫይረሱ ላይ ያለውን ግንዛቤ እየተሻሻለ መምጣቱን አስረድተዋል። - ; በመጨረሻም ህብረተሰቡ ከቫይረሱ እራሱን እንዲጠብቅና የመገናኛ ብዙሃንም በቫይረሱ ዙሪያ የህበረተሰቡን በተለይም የወጣቱን ግንዛቤ ሊያሳድጉት እንደሚገባ ተናግረዋል። ),
[ 1 ]
[ "የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምርመራ እና የምክር አገልግሎት" ]
[ "ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምክርና የምርመራ አገልግሎት አሰጣጥና የሚሰጥባቸው ቦታወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት." ]
[ "ሥለ ኤድስ በሽታ ምርመራ, የምክር አገልግሎት, ስለሚሰጡባቸው ቦታወች ወይም የህክምና ተቋማት( ሆስፒታሎች,የጤና ኬላወች ) ,ምርመራ ስለሚያደርጉ ሰወች የሚአትቱ ሰነዶች በሙሉ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሰለ ኤድስ በሽታ ባህሪና ስርጭት, መከላከያ, መቆጣጠሪያ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
6
ሴክሬታሪያት ስህፈት ቤቱ የኤች አይ ቪ አድስ ምርመራ ለማሰጠት የሚያስችል የምርመራ ጣቢያ ሊያቋቁም ነው ። የአማራ ክልል አች አይ ቪ ኤድስ ሴክሬታሪያት ጽህፈት ቤት ከዩኒሴፍ ባገኘው 140 ሺ ብር የገንዘብ ድጋፍ በባህርዳር ከተማ ለበጎፈቃደኞች የኤድስ ምርመራ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል የምርመራ ታቢያ ለማቋቋም መዘጋጀቱን አስታወቀ ። የምርመራ ጣቢያውን በማቋቋም ስራ ለማስጀመር ጽህፈት ቤቱ እና በኢትዮጵያ ቤተሰብ መምሪያ ማሀበር የሰሜን ምእራብ ቅርንጫፍ ስህፈት ቤት ተቀናጅተው እየሰሩ መሆኑን የጽህፈት ቤቱ ሃላፊ ዶክተር አለማየሁ መኮንን ለዋልታ እንፎርሜሽን ማእከል አስታውቀዋል ። የምርመራ ጣቢያው መቋቋም በባህርዳር ከተማ እና አካባቢዋ የሚገኙ የሀብረተሰብ ክፍሎች የኤች አይ ቪ ኤድስ ምርመራ ለማድረግ ለሚፈልጉ በጎፈቃደኞች ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ሃላፊው ተናግረዋል ። እንደ ዶክተር አለማየሁ ገለጻ የበሽታውን ስርጭት ለመግታት ጽህፈት ቤቱ ከዞን እስከ ቀበሌ ያዋቀራቸው ኮሚቴዎች ከሃይማኖት ተቋማትና ከአገር ሽማግሌዎች ጋር በመቀናጀት ለሀብረተሰቡ ትምህርት እየሰጡ ይገኛሉ ። አንዳንድ የባህርዳር ነዋሪዎች በሰጡት አስተያየት በበሽታው ወላጆቻቸውን የሚያጡ ህጻናት ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ጠቅሰው ፤ ስለበሽታው ግልእ ውይይት ማድረግ እና ከቫይረሱ ነጻ መሆን እና አለመሆንን ለማረጋገጥ እንዲቻል የምክር አገልግሎት ተጠናክሮ መሰጠት እንዳለበት አሳስበዋል ። በአገሪቱ ከሚገኙት 2 ነጥብ 4 ሚሊየን የኤድስ ተጠቂዎች 700 ሺ ያህሉ በአማራ ክልል እንደሚገኙ ይታወቃል ።
[ 1 ]
[ "የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምርመራ እና የምክር አገልግሎት" ]
[ "ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምክርና የምርመራ አገልግሎት አሰጣጥና የሚሰጥባቸው ቦታወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት." ]
[ "ሥለ ኤድስ በሽታ ምርመራ, የምክር አገልግሎት, ስለሚሰጡባቸው ቦታወች ወይም የህክምና ተቋማት( ሆስፒታሎች,የጤና ኬላወች ) ,ምርመራ ስለሚያደርጉ ሰወች የሚአትቱ ሰነዶች በሙሉ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሰለ ኤድስ በሽታ ባህሪና ስርጭት, መከላከያ, መቆጣጠሪያ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
7
ኤድስ የሲዲፎር በመባል የሚታውቀውን በነጭ ደም ሴል ውስጥ የሚገኘውን የሴል ቁጥር (cd4 count) ከ200 በታች በማድረስ የቫይረሱ መጠን በደም ውስጥ እንዲጨምር በማድረግ ለሕይወት ኣደገኛ እና ምቹ ግዝ ተባቂ በመባል የሚታውቁትን በሸታዎች ኦፓርቸንሰቲክ እንፈክሽስ (Opportunistic infections) OIs. በመፍጠር የኤድስ ደረጃ ላይ እንዲደርስ ያደርጋል። አንድ ሰው አንድ ወይም ሁለት ኢንፌክሽኖች ሲኖሩበት እና በጣም ዝቅያለ የሲዲፎር ሴል ቁጥር 350 cells/mm3 ወይም በታች ሲሆን እና የቫይረሱ ብዛት (viral load) ከ 1,000 copies/mL በላይ ከሆነ የኤድስ ደረጃ ላይ ደረሰ ሊባል ይችላል። የበለጠ መረጃ ለማግኘት ዋና ግጽ ላይ ይመልከቱኤችአይቪ ኤችአይቪ ህዩመን ኢምዩኖደፊሸንሲ ቫይረስ Human Immunodeficiency Virus (HIV) በመባል የሚታውቅ ቫይረስ ነው። ኤችአይቪ ቫይረስ የሰውነትን የበሽታ መከላከያ በተለይ የነጭ ደም ሴሎችን በማጥቃት በቀላሉ ሰውነት ለበሽታ እንዲጋለጥ የሚያረግ ቫይረስ ነው። ኤችአይቪ ያለባቸው ሰዎች የበሽታው ምልክት ስይታይባቸው ለብዙ አመታት መኖር ይችላሉ። ቫይረሱ በሰውነታ ውስጥ እስከ አስር ዓመት በመቆየት ምንም ሳይታውቅ እና ምንም አይነት ይህመም ምልክት ሳይታይበት በመኖር እና አለማውቅ ከአንድ ሰው ወደሌላ ሰው ሊተላለፍ የሚችል አደገኛ ቫይረስ ነው። ለመጀመሪያ ግዜ በኢትዮጵያ ውስጥ የኤድስ ታማሚዎች መኖራችው የተረጋገጠው በ1978 ዓ/ም ነው። በአሁኑ ሰአት በኢትዮጵያ ውስጥ 1.3 ሚሊዮን በላይ የሚቆጠሩ ሰዎች ከኤችአይቪ ቫይርስ ጋር አብረው ይኖራሉ። ኤችአይቪ የሚያመለክት የደም ናሙና የተገኘው በሁለት የደም ናሙናዎችይ ላይ ብቻ ነበር። እነዚህም ከታህሳስ 1976 ዓ.ም እስከ 1977 ዓ.ም ባለው ጊዜ ከተሰበሰቡ የደም ናሙና የተገኘ በመሆኑ ኤችአይቪ ኢትዬጵያ ውስጥ የተገኘው 1976 ዓ.ም ነው። ከአካል የሚወጡ ፈሳሾች ላይ ሁሉ ኤችአይቪን ማግኝት የሚቻል ቢሆንም መደበኛ ኤችአይቪ ምርመራ በደም ናሙና ላይ የሚደረግ የኤችአይቪ-1/2 አንቲ ባዲ ምርመራ ነው። ኤላይዛ-ዌስተርን ብሎት ፈጣን የኤችአይቪ ምርመራ ማለት ለቫይረሱ የተዘጋጀ አንቲ ቦዲ በደም ውስጥ መኖሩንና አለመኖሩን የሚያመልክት የምርመራ አይነት ነው። በፈጣን የምርመራ ዘዴ ውጤቱን ከ10-60 ደቂቃዎች ውስጥ ማውቅ የሚያስችል የመመርመሪያ ዘዴ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ በአሁን ሰዓት የኤችእይቪ/ኤድስ ትምህርት በመስፋፋቱ ጥሩ የሆነ ለውጦች በማየት ላይ እንገኛለን። ከቫይረሱ ጋር ለሚኖሩም ሆነ ቫይረሱ እንደሌለባቸው የሚያቁም ሆን የማያቁም የቫይረሱ መስፋፋት ለመግታት የማያቋርጥ ትምህርት ያስፈልጋል። ሁለተኛ ሰዎችን ከመገለልም ሆነ ከማግለል የሚመጣውን ትልቅ ጥፋት ለመታገል ይረዳል። ከቫይረሱ የበለጠ ሕብረተሰባችን ጎድቶ የነበረ እና አሁንም በመጉዳት ላይ ያለው ይህ አግሎ ነው። እያንዳዱ ገለሰብ ስለኤችእይቪ/ኤድስ ያለው እውቀት ከፍተኛ ከሆነ ከመግላል እና ከመገለል የሚመጣውን መሽማቀቅ እና ጭንቀት መቆጣጠር ከቻልን ማለት ተልቅ ለውጥ እናመጣለን ማለት ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ይኸንን ዝምታ የሰበሩ ልንረሳቸው እና ሁሌ ልናስትውሳቸው የሚገቡ እራሳቸውን አውጥተው ከቫይረሱ ጋር እንድሚኖሩ ያስተማሩ እና የብዙ ወጣቶችን ሕይወት ያተረፍ የመጀመሪያው የተስፋ ጎህ ኢትዮጵያማህበር መስራቾች ናቸው። ኤድስ በሽታ እንደጀመረ በታማሚዎች ላይ ይታዩ የነበሩት የበሽታ ምልክቶችን በማየት የሰውነት የበሽታ መከላከያ አቅም ከመዳከም ጋር ተያያይዘው የሚመጡ ምልክቶች ሊሆኑ እንደሚችሉ ከመገመት በስተቀር ብዙም የሚታውቅ ነገር አልነበረ፤። ከምን እንደመጣና በምን እንደሚተላለፍ አይታወቅም ነበር። በኋላም በተለያዪ የምርምሮች ዘርፎች ተጠናክረው በመቀጠላቸው የኤድስ በሽታን የሚያመጣው ቫይረስ ለይቶ በማወቅ ተሕዋሱንም በላቦራቶሪ ለይቶ ማውጣት ተችሏል። ይህ የኤድስ በሽታ መንስዔ ተዋሕሳትም በኋላ ላይ ኤችአይቪ የሚለውን ስያሜ አግኝቶዋል ሪትሮ ቫይረስ ከሚባል ተሕዋስ ምድብ ወስጥ መሆኑ ተረጋግጥዋል። ኤድስ ወይም Acquired Immune Deficiency Syndrome (AIDS) በመባል የታወቀው በሽታ የሚመጣው ህዩመን ኢምዩኖደፊሸንሲ ቫይረስ Human Immunodeficiency Virus (ኤችአይቪ HIV) በሚባል ጀርም ነው። በሽታው የሰውነትን የበሽታ መከላከያ በተለይ ነጭ ሴሎችን በማጥፋት ለቀላል በሽታዎች ለሕይወት ኣስጊ የመሆን ዕድል በመስጠት የሚገድል ነው። የሚተላለፈው ቫይረሱ ያለበት ሰው የተጠቀመበትን ያልፀዳ መርፌ በመጠቀም ወይም ኣስፈላጊዎቹ ጥንቃቄዎች ሳይደረጉ በሚፈጸሙ የተለያዩ የግብረ ሥጋ ግንኙነቶች ነው። ኤድስን የሚያመጣው ሕይወት ያለው ጥገኛ ጠንቅ በኃይለኛ የማጉሊያ መሣሪያዎች ይታያል። ቫይረሱ ሰውነት ውስጥ እያለ እስከ ፰ ዓመታት የማይታመሙና በሽታውን የሚያስተላልፉ ጤነኛ ሰዎች ኣሉ። የኤድስ በሽታ ሲጀምር ሰውነት ወይም ኣካላችን በቀላሉ የሚከላከላቸው ጀርሞች እንደፈለጋቸው በመባዛት ለሕይወት ኣደገኛ ሆነው ይገኛሉ። ለምሳሌ ያህል ጤነኛ መድን በነበረን ጊዜ ከማይተናኮሉን ባክቴሪያዎች ኣንዱ ኒሞንያ ያስከትላል። የቆዳ ካንሰር (Kaposi's Sarcoma) እና የኣንጎል በሽታም ሊኖሩ ይችላሉ። AIDS-related complex (ARC) ወይም ኣርክ የሚባሉ ምልክቶችም ሊመጡ ይችላሉ። ከእነዚህም መካከል የንፍፊት ማበጥ፣ የማይለቁ ትኩሳቶች፣ ድካምና ተቅማጥ፣ ክብደት መቀንስ (ከ፲ በ፻ በላይ)፣ ደረቅ ሳልና ከባድ የእንቅልፍ ላብ ይገኙበታል። ትረሽ (Thrush) እና ሽንግልስ (Shingles) የሚባሉ በሽታዎችም ሊኖሩ ይችላሉ። ኤድስ ቀስ በቀስ እየተስፋፋ የመጣው ከ1970 ዓ.ም. ወዲህ ሲሆን እስከ 1985 እ.ኤ.አ. ድረስ የተበከለ ደም በመወጋትና በመሳሰሉት ብዙ ሰዎች ያለቅብጠታቸው በበሽታው ተይዘዋል። ከ1988 ወዲህ ግን ኤድስ ሲይዝ ነጭ ሴል የሚሠራውን ኣንቲቦዲ (Antibody) በመመርመር የኤድስ ቫይረስ እንዳጋጠመን የሚጣራበት ፈጣን የምርመራ ዘዴ ስለተሠራ በተለይ የደም ማነስን ለመከላከል ሆስፒታል ከሚሰጠን ደም በመተላለፍ ሊይዝ የሚችለው ኤድስ ወደ መጣፋቱ ደርሷል። ኤድስ በሚከተሉት ሁኔታዎች ሊተላለፍ ይችላል። ከኤድስ በሽታ ለመከላከል የሚከተሉትን እርምጃዎች መውሰድ ይጠቅማል። በተጨማሪም የሚከተሉት ታውቀዋል። AZT (ኤዚቲ) እና የመሳሰሉት መድኃኒቶች ቫይረሱ እንዳይባዛ በመከላከል በሽታው እንዳይገድል ጊዜ ለመግዛት ይጠቅማሉ ይባላል። በሽታው በመካከላችን ስላለ ባለማወቅና በጥንቃቄ ጉድለት በኤድስ ብንያዝ ጥፋቱና ፀፀቱ የራሳችን ይመስለኛል። እስከ (1991) በዩናይትድ እስቴትስ ውስጥ የኤድስ ቫይረስ ከተገኘባቸው ፪፻፸ሺህ ሰዎች መካከል ፩፻ሺህ (፩00, 000) በበሽታው ሞተዋል። በዓለም ላይም (፩፶፬ ኣገሮች) ኣንድ ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች በኤድስ በሽታ ተይዘዋል። (ሕዝቡም መጠንቀቅ ካልጀመረ በቫይረሱ የሚበከለው ሰው ቍጥር በየዓመቱ እጥፍ እየሆነ ሊቀጥል እንደሚችልና ለማስታመምም ብዙ ብሊዮን ዶላርስ እንደሚያስፈልግ ተገምቷል።) ግብረ ሰዶም የሚያዘወትሩና ድረግ የሚወጉ ሰዎች በሽታ ነው እየተባለ ቸል ሲባል ቆይቶ ኣሁን የሁላችንም ጠር መሆኑ ስለተደሰረበት የሚፈለግብንን ብናከናውንና (ከመንግሥታትም ጋር) ብንተባበር በሽታውን መቆጣጠር ይቻል ይሆናል። የፈንጣጣን በሽታ ከዓለም ለማጥፋት ከጠቀሙን መካከል ክትባትና የሕዝቡ ትብብር ዋናዎቹ ናቸው። ስለ ግብረ ሥጋ ግንኙነት ማውራት ለማንኛውም ሕብረተሰብ ኣሳፋሪ ቢሆንም ኤድስ ያመጣብን ዱብ-ዕዳ የሕይወት ጉዳይ ስለሆነ መወያየት መጀመር ኣለብን። ይህ ጽሑፍ የተጻፈው የሕክምና ዕርዳታ ለመስጠት ኣይደለም። በበለጠ ለመረዳት ሓኪሞቻችሁን ኣማክሩ። በ1988 እ.ኤ.አ. ለእያንዳንዱ የዩናይትድ እስቴትስ ቤተሰብ Understanding AIDS የተባለ ፰ ገጽ ጽሑፍ ከU.S. Department of Health and Human Services ሲላክ ወደ አማርኛ በነፃ በዶ/ር ኣበራ ሞላ ተተርጕሞና ተሰራጭቶ ነበር። የእዚህ የ፲፱፻፹፫ ዓ.ም. ጽሑፍ መነሻ ይኸው የHHS Publication No. (CDC) HHS 88-8404 ጽሑፍ ነው።
[ 1 ]
[ "የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምርመራ እና የምክር አገልግሎት" ]
[ "ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምክርና የምርመራ አገልግሎት አሰጣጥና የሚሰጥባቸው ቦታወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት." ]
[ "ሥለ ኤድስ በሽታ ምርመራ, የምክር አገልግሎት, ስለሚሰጡባቸው ቦታወች ወይም የህክምና ተቋማት( ሆስፒታሎች,የጤና ኬላወች ) ,ምርመራ ስለሚያደርጉ ሰወች የሚአትቱ ሰነዶች በሙሉ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሰለ ኤድስ በሽታ ባህሪና ስርጭት, መከላከያ, መቆጣጠሪያ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
8
 ሴክሬታሪያቱ ለተጓዳኝ በሽታዎችና ለኤድስ መመርመሪያ መሳሪያ ግዢ 340 ሺ ዶላር መደበ ። ብሄራዊ ኤች አይ ቪ ኤድስ ሴክሬታሪያት በ340 ሺ ዶላር የተጓዳኝ በሽታዎች መከላከያ መድሃኒት እና የኤች አይቪ ኤድስ ቫይረስ መመርመሪያ መሳሪያ ግዢ እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ ። የሴክሬታሪያቱ ሃላፊ ዶክተር ዳኛቸው ሃይለማርያም ዛሬ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማእከል እንደገለጹት ለመጀመሪያ ጊዜ በጽህፈት ቤቱ አማካኝነት የሚገዙት መድሃኒቶች ከቫይረሱ ጋር የሚኖሩ ግለሰቦች በተጓዳኝ በሽታዎች የሚደርስባቸውን ህመም ለማስታገስ ያገለግላሉ ። በሁሉም ክልሎች ተመጣጣኝ የተጓዳኝ በሽታዎች መከላከያ መድሃኒት በተፈለገው መጠን እንደሌለ ዶክተር ዳኛቸው ገልጸው ፤ የመጀመሪያው የመድሃኒት ግዢ አፈጻጸም ታይቶ ተከታታይ መድሃኒቶች ግዢ እንደሚከናወን ጠቁመዋል ። የቫይረሱ መመርመሪያ መሳሪያ ግዢም ሙሉ በሙሉ የመመርመሪያ መሳሪያ እጥረትን ባያቃልልም በተወሰነ ደረጃ እጥረቱን እንደሚያቃልል ተቁመው ፤ የመሳሪያ ግዢው ቀጣይነት እንደሚኖረው አስታውቀዋል ። በተመሳሳይም የእድሜ ማራዘሚያ መድሃኒት ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገባ በተፈቀደው መሰረት የአገዛዙን ፣ ስርጭቱንና የአጠቃቀም ስራቱ ረቂቅ መመሪያ መዘጋጀቱን ዶክተር ዳኛቸው ተቁመዋል ። በተለይም የአገዛዙ ሁኔታ የኢትዮጵያውያንን አቅም ያገናዘበ እንዲሆን እንዲሁም የስርጭቱ ሂደት በማንና ከየት ይጀምር በሚለውና በአጠቃቀሙ ዙሪያ ባለሙያዎችን በማወያየት ቁጥጥርና ስራት ባለው መልኩ መድሃኒቱ የሚደርስበትን ሁኔታ እየተመቻቸ መሆኑን ገልጸዋል ። በሌላ በኩል የሴክሬታሪያቱ ሉካን በአገሪቱ ተንቀሳቅሶ በጎበኘበት ወቅት አበረታች እንቅስቃሴዎችን በሁሉም ክልሎች እንደተመለከተ የጠቆሙት ዶክተር ዳኛቸው ፤ በጸረ-ኤድስ ክበባት ፣ በመስሪያ ቤቶች ፣ በሃይማኖት ተቋማት ፣ በልዩ ልዩ ድርጅቶች እና በጎሳ መሪዎች ኤች አይቪ ኤድስ የሀብረተሰቡ አደጋ መሆኑን ካለፉት አመታት የተሻለ ግንዛቤ ተገኝቷል ብለዋል ። ይሁን እንጂ ከቫይረሱ ጋር ለሚኖሩት ግለሰቦች የሚደረገው እንክብካቤና ፍቅር ጉድለት እንዳለው የጠቆሙት ሃላፊው ፤ ሀብረተሰቡ በግልእ ስለበሽታው እየተወያየ ከቫይረሱ ጋር የሚኖሩትንና ወላጅ አልባ ህጻነትን ድጋፍ ሊሰጣቸው እንደሚገባ አመልክተዋል ። ሴክሬታሪያት ጽህፈት ቤቱ ሁሉንም የአገሪቱን ክፍል ለማዳረስ የሚችል የገንዘብም ሆነ የሰው ሃይል አቅም እንደሌለው ዶክተር ዳኛቸው አመልክተው ፤ ቫይረሱን ለመከላከልና ለመቆጣጠር መፍትሄውና አቅሙ ያለው ከሀብረተሰቡ ጋር በመሆኑ ሀብረተሰቡ ተቀናጅቶ እንዲንቀሳቀስ ጥሪ አቅርበዋል ።
[ 1 ]
[ "የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምርመራ እና የምክር አገልግሎት" ]
[ "ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምክርና የምርመራ አገልግሎት አሰጣጥና የሚሰጥባቸው ቦታወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት." ]
[ "ሥለ ኤድስ በሽታ ምርመራ, የምክር አገልግሎት, ስለሚሰጡባቸው ቦታወች ወይም የህክምና ተቋማት( ሆስፒታሎች,የጤና ኬላወች ) ,ምርመራ ስለሚያደርጉ ሰወች የሚአትቱ ሰነዶች በሙሉ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሰለ ኤድስ በሽታ ባህሪና ስርጭት, መከላከያ, መቆጣጠሪያ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
9
በባሌ ዞን ጎሮና ጎለልቻ ወረዳዎች በፈቃደኝነት የኤች አይ ቪ ምርመራ ለማድረግ የሚፈልጉ ሰዎች በአቅራቢያቸው አገልግሎቱን ማግኘት እንዳልቻሉ ገለጹ፡፡ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አስተያየት የሰጡት ነዋሪዎች እንደገለጹት ራሳቸውን ለማወቅና ጋብቻ ለመፈጸም በፈቃደኝነት ለመመርመር ቢፈልጉም አገልግሎቱን ለማግኘት አልቻሉም፡፡ ምርመራ ለማድረግ ወደ ሮቤና ጊኒር ረጅም መንገድ ስለሚጓዙ ለወጪና ለእንግልት መዳረጋቸውን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል፡፡ የዞኑ ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ጽህፈት ቤት ባለሙያ አቶ ኡመር አናቶ ስለጉዳዩ ተጠይቀው ቀደም ሲል ችግሩ የተፈጠረው ባለሙያዎች ስራ በመልቀቃቸውና የቁሳቁስ ዕጥረት በማጋጠሙ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ግን ባለሙያ በመመደቡና መሳሪያዎች በመሟላታቸው አገልግሎቱ በቅርቡ እንደሚጀምር አቶ ኡመር ተናግረዋል፡፡
[ 1 ]
[ "የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምርመራ እና የምክር አገልግሎት" ]
[ "ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምክርና የምርመራ አገልግሎት አሰጣጥና የሚሰጥባቸው ቦታወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት." ]
[ "ሥለ ኤድስ በሽታ ምርመራ, የምክር አገልግሎት, ስለሚሰጡባቸው ቦታወች ወይም የህክምና ተቋማት( ሆስፒታሎች,የጤና ኬላወች ) ,ምርመራ ስለሚያደርጉ ሰወች የሚአትቱ ሰነዶች በሙሉ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሰለ ኤድስ በሽታ ባህሪና ስርጭት, መከላከያ, መቆጣጠሪያ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
10
 በአዲስ አበባ ኤድስ ምርመራ ለማካሄድ እውቅና የተሰጣቸው ክሊኒኮች 13 ብቻ ናቸው ። በአዲስ አበባ መስተዳድር ከሚገኙት የግል ክሊኒኮች መካከል የኤቻይቪ ኤድስ ደም ምርመራ ለማካሄድ አስፈላጊውን መመዘኛ ማሟላታቸው ተረጋገጦ እንዲሰሩ የተፈቀደላቸው ሶስት መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ጨምሮ 13 ክሊኒኮች ብቻ መሆናቸው ተገለጸ ። በመስተዳድሩ ጤና ቢሮ የጤና አገልግሎት ስልጠና መምሪያ ተጠባባቂ ሃላፊ አቶ ኪሮስ በላቸው ሰሞኑን እንዳሉት ፈቃድ አግኝተው ምርመራውን የሚካሂዱት ክሊኒኮች ቅድመና ድህረ የምክር አገልግሎት የሚሰጡ ሙያተኞችን ጭምር ማሟላታቸው ተረጋግጦ ፈቃድ የተሰጣቸው ናቸው ። ፈቃድ ተሰጥቷቸው የሚሰሩት 13 ክሊኒኮችም ከመመርመሪያ መሳሪያውና የላቦራቶሪ ምርመራውን ከሚያከናውነው ባለሙያ በተጨማሪ የምክር አገልግሎት የሚሰጥ ባለሙያ ያላቸው መሆኑ ተረጋግጦ እንደተሰጣቸው ገልጸዋል ። ከጤና ቢሮው ፈቃድ ሳያገኙ ምርመራ የሚያካሂዱትን ቢሮው የራሱን ክትትል እንደሚያደርግና ከከተማዋ ስፋት አንጻር በሁሉም አካባቢ በውስን ሰራተኞች ብቻ ውጤታማ የቁጥጥር ስራ ለማካሄድ እንደሚያስቸግር ጠቁመው ፤ ሀብረተሰብ ያለ ፈቃድ የሚሰሩ ክሊኒኮች ሲያጋጥሙት ለአቅራቢያው ጤና መምሪያ ወይም ጠና ቢሮ በመጠቆም የበኩሉን እገዛ እንዲያደርግ አሳስበዋል ። ያለ ፈቃድ ሲንቀሳቀሱ ተደርሶበት እርምጃ የተወሰደበት ክሊኒክ ስለመኖሩ ለቀረበላቸው ጥያቄ አቶ ኪሮስ ሲመልሱ ፤ ከአመት በፊት በዞን 5 በደረሰ ጥቆማ መሰረት አንድ ክሊኒክ መታሸጉንና ሃላፊውም በህግ አግባብ የተጠየቀ መሆኑን ዛሬ ለንባብ ለበቃው አዲስ ልሳን ጋዜጣ መናገራቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማእከል ዘግቧል ።
[ 1 ]
[ "የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምርመራ እና የምክር አገልግሎት" ]
[ "ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምክርና የምርመራ አገልግሎት አሰጣጥና የሚሰጥባቸው ቦታወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት." ]
[ "ሥለ ኤድስ በሽታ ምርመራ, የምክር አገልግሎት, ስለሚሰጡባቸው ቦታወች ወይም የህክምና ተቋማት( ሆስፒታሎች,የጤና ኬላወች ) ,ምርመራ ስለሚያደርጉ ሰወች የሚአትቱ ሰነዶች በሙሉ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሰለ ኤድስ በሽታ ባህሪና ስርጭት, መከላከያ, መቆጣጠሪያ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
11
ኤችአይቪ ኤችአይቪ (እንግሊዘኛ: Human Immunodeficiency Virus (HIV) "ህዩመን ኢምዩኖደፊሸንሲ ቫይረስ") በመባል የሚታውቅ ቫይረስ ነው። ኤችአይቪ ቫይረስ የሰውነትን የበሽታ መከላከያ በተለይ የነጭ ደም ሴሎችን (ህዋሳትን) በማጥቃት በቀላሉ ሰውነት ለበሽታ እንዲጋለጥ የሚያረግ ቫይረስ ነው። ኤችአይቪ ያለባቸው ሰዎች የበሽታው ምልክት ሳይታይባቸው ለብዙ አመታት መኖር ይችላሉ። ቫይረሱ በሰውነታ ውስጥ እስከ አስር ዓመት በመቆየት ምንም ሳይታውቅ እና ምንም አይነት የሚችል አደገኛ ቫይረስ ነው። ኤችአይቪ የሚያጠቃው የሰውነት የነጭ የደም ሴሎችን የሰውነት የበሽታ የመከላከያ ተቁዋማትን ነው። የሲዲፎር በመባል የሚታውቀውን የሰውነት የነጭ የደም ሴል ቁጥሩን (cd4 count) ከ 200 በታች በማድረግ የቫይረሱ መጠን በደም ውስጥ እንዲጨምር በማድረግ ለሕይወት ኣደገኛ እና ምቹ ግዝ ተባቂ በመባል የሚታውቁትን በሸታዎች (ኦፓርቸንሰቲክ እንፈክሽስ Opportunistic infections) OIs. በመፍጠር ኤድስ ደረጃ ላይ እንዲደርስ ያደርጋል። ኤችአይቪ ቀስ በቀስ እየተስፋፋ የመጣው ከ1978 (፲፱፻፸ ዓ.ም.) ወዲህ ነው። በአሁኑ ሰአት በኢትዮጵያ ውስጥ 1.3 ሚሊዮን በላይ የሚቆጠሩ ሰዎች ከኤችአይቪ ቫይርስ ጋር አብረው ይኖራሉ። በዓለም ላይም ከ 25 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ሰዎች በኤድስ በሚመጣ በሸታ ተይዘው ሞተዋል። ለመጀመሪያ ግዜ በኢትዬጵያ ውስጥ የኤድስ ታማሚዎች መኖራችው የተረጋገጠው በ1978 ዓ/ም ነው። በ2006ዓ/ም ወደ 2.9 ሚሊዮን የሚጠጉ ወንዶች፤ ሴቶች እና ሕጻናትም ሕይወታቸውን አተዋል። ኤችአይቪ ከተያዙት ውስጥ ከግማሸ በላይ የሚገምቱት ሲሞቱ 39.5 ሚሊዮን የሚሆኑ ከቫይርሱ ጋር በመኖር ይገኛሉ። በቅርቡ በUNAIDS/WHO እንደተዘገበው 4.3 ሚሊዮን የሚጠጉ አዲስ ሰዎች በኤችአይቪ እንደተያዙ ይገልጻል። መከላከያ እርምጃዎች 4ቱ " መ" ዎችይ. የውሽት ውጤት የሚባል (ዊንዶ ፔሬድ የሚባል) ነገር ስላለ ከ 3-6 ወር በሃላ እርግጠኛ ለመሆን ደግመው መመርመር ይገባል። ይህን ሲያረጉ ግን አሁንም ኮንዶም መጠቀሞን ኤችአይቪ ቀስ በቀስ እየተስፋፋ የመጣው ከ1978 (፲፱፻፸ ዓ.ም.) ወዲህ ሲሆን እስከ 1985 ድረስ የተበከለ ደም ናሙና በመወጋትና በመሳሰሉት ብዙ ሰዎች ይዚህ ሰለባ በመሆን ብዙ ሰዎች ተይዘዋል። ከ1988 ወዲህ ግን ኤችአይቪ ሲኖር ደም ውስጥ ነጭ ሴል የሚሠራውን ኣንቲቦዲ (Antibody) በመመርመር ኤችአይቪ ቫይረስ እንዳለ እና እንደሌለ የሚጣራበት ፈጣን የምርመራ ዘዴ ስለተሠራ በሆስፒታል ከሚሰጠን ደም መተላለፉ ቀርትዋል። ከአካል የሚወጡ ፈሳሾች ላይ ሁሉ ኤችአይቪን ማግኝት የሚቻል ቢሆንም መደበኛ የኤችአይቪ ምርመራ በደም ናሙና ላይ የሚደረግ የኤችአይቪ-1/2 አንቲ ባዲ ምርመራ ነው። ፈጣን ምርመራዎች የሚባሉት ተመርተው በገበያላይ የቀርቡ ወደ 60 የሚቆጠሩ መመርመሪያዎች ሲኖሩ በሶስት ዋና ዋና ቴክኒኮች ላይ የተመረኮዙ ናችው። አስተማማጝነታቸውም ከኤላይዛር ጋር የሚስተካከል ነው። ፈጣን የኤችአይቪ ምርመራ ማለት ለቫይረሱ የተዘጋጀ አንቲ ቦዲ በደም ውስጥ መኖሩንና አለመኖሩን የሚያመልክት የምርመራ አይነት ነው። በፈጣን የምርመራ ዘዴ ውጤቱን ከ10-60 ደቂቃዎች ውስጥ ማውቅ የሚያስችል የመመርመሪያ ዘዴ ነው።
[ 1 ]
[ "የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምርመራ እና የምክር አገልግሎት" ]
[ "ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምክርና የምርመራ አገልግሎት አሰጣጥና የሚሰጥባቸው ቦታወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት." ]
[ "ሥለ ኤድስ በሽታ ምርመራ, የምክር አገልግሎት, ስለሚሰጡባቸው ቦታወች ወይም የህክምና ተቋማት( ሆስፒታሎች,የጤና ኬላወች ) ,ምርመራ ስለሚያደርጉ ሰወች የሚአትቱ ሰነዶች በሙሉ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሰለ ኤድስ በሽታ ባህሪና ስርጭት, መከላከያ, መቆጣጠሪያ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
12
በዲላ ከተማ በቂ የኤች አይ ቪ ኤድስ የምርመራና የምክር አገልግሎት መስጫ ባለመኖሩ ነዋሪዎች በፈቃደኝነት ምርመራ ማድረግ እንዳልቻሉ አስታወቁ፡፡ ነዋሪዎቹ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት የኤች አይ ቪ ኤድስ ምርመራ በማድረግ ራሳቸውን ለማወቅና በጥንቃቄ ለመኖር ቢያቅዱም በዲላ ሆስፒታል ከሚሰጠው አገልግሎት በስተቀር በሌላ ቦታ ባለመኖሩ ተቸግረዋል፡፡ ከሆስፒታሉ አገልግሎት ለማግኘት ቢሞክሩም ረጅም ሰዓት ወረፋ ለመጠበቅና ለመጉላላት በመዳረጋቸው ችግሩን ለመፍታት እንዲታሰብበት አመልክተዋል፡፡ የሆስፒታሉ የኤች አይ ቪ ኤድስ የምክርና ምርመራ አገልግሎት ክፍል ሠራተኛ ሲስተር ሕይወት ዳመነ በበኩላቸው በፈቃደኝነት ለመመርመር የሚመጡ ሰዎች ብዛት ከአቅም በላይ እንደሚሆንና በቀን ለአሥር ተመርማሪዎች ብቻ አገልግሎት ስለሚሰጥ ብዙዎች እንደሚመለሱ ገልጸዋል፡፡ ይሁንና ችግሩን ለማቃለል በማዕከል ደረጃ የኤች አይ ቪ ኤድስ የምክርና ምርመራ መስጫ በሆስፒታሉ እየተገነባ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ የከተማው የኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ጽሕፈት ቤት ተወካይ አቶ ብሥራት በራሶ ተጠይቀው እንዳሉት በሆስፒታሉ ብቻ ተወስኖ የሚገኘውን የምርመራና የምክር አገልግሎት በዲላና በመካነየሱስ ጤና ጣቢያዎች ለማስጀመር ጥረት በመደረግ ላይ ነው፡፡
[ 1 ]
[ "የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምርመራ እና የምክር አገልግሎት" ]
[ "ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምክርና የምርመራ አገልግሎት አሰጣጥና የሚሰጥባቸው ቦታወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት." ]
[ "ሥለ ኤድስ በሽታ ምርመራ, የምክር አገልግሎት, ስለሚሰጡባቸው ቦታወች ወይም የህክምና ተቋማት( ሆስፒታሎች,የጤና ኬላወች ) ,ምርመራ ስለሚያደርጉ ሰወች የሚአትቱ ሰነዶች በሙሉ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሰለ ኤድስ በሽታ ባህሪና ስርጭት, መከላከያ, መቆጣጠሪያ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
13
የኢድ አል ፈጥር በአልን ምክንያት በማድረግ በሰሜን ሽዋ ዞን ደብረብርሃን ከተማ በአራት ቀናት ብቻ 294 ሰዎች የኤች አይ ቪ ምርመራ ማድረጋቸውን የከተማዋ ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ፅህፈት ቤት አስታወቀ፡፡ የፅህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ዮሃንስ ሰንደቆ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለፁት በአሉን ተከትሎ በነበሩት አራት ተከታታይ ቀናት ሶስት የምርመራ ማዕከላትን በማቋቋም የኤች አይ ቪ ኤድስ ምርመራ ካደረጉት ሰዎች መካከል 28ቱ ከቫይረሱ ጋር እንደሚኖሩ አውቀዋል፡፡ በነዚሁ ቀናት ኢድ ሙባረክ በሚል ርዕስ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት መሰጠቱን ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ የምክርና ደም ምርመራ አገልግሎቱን በነፃ የሰጡት በከተማዋ የሚገኙ ሁለት መንግስታዊና አንድ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት የጤና ተቋማት መሆናቸውም ታውቋል፡፡
[ 1 ]
[ "የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምርመራ እና የምክር አገልግሎት" ]
[ "ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምክርና የምርመራ አገልግሎት አሰጣጥና የሚሰጥባቸው ቦታወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት." ]
[ "ሥለ ኤድስ በሽታ ምርመራ, የምክር አገልግሎት, ስለሚሰጡባቸው ቦታወች ወይም የህክምና ተቋማት( ሆስፒታሎች,የጤና ኬላወች ) ,ምርመራ ስለሚያደርጉ ሰወች የሚአትቱ ሰነዶች በሙሉ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሰለ ኤድስ በሽታ ባህሪና ስርጭት, መከላከያ, መቆጣጠሪያ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
14
በደብረ ማርቆስ ከተማ በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ የደም ምርመራና የምክር አገልግሎት የሚያገኙ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን የደብረ ማርቆስ ሆስፒታልና የከተማዋ ጤና ጽህፈት ቤት አስታወቁ ፡፡ የደብረ ማርቆስ ሆስፒታል ሜዲካል ድሬክተር አቶ ጥላሁን ደምስና የከተማዋ ጤና ጽህፍት ቤት ኃላፊ ዮሐንስ አሞኘ እንደገለጹት በከተማዋ በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ የደም ምርመራ የሚያደርጉ ሰዎች ቁጥር ሊጨምር የቻለው የበሽታውን ስርጭት ለመከላከል የሚያስችል ትምህርት በተጠናከረ ሁኔታ በመሰጠቱ ነው፡፡ ባለሙያዎቹ በከተማዋ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን የተናገሩት ቤዛ ከኤች አይ ቪ/ኤድስ ቫይረስ ጋር የሚኖሩ ሰዎች ማህበር ሶስተኛ ዓመት የምስረታ ባህሉን ሰሞኑን በደብረ ማርቆስ ከተማ ሲያከብር ነው፡፡ በኢትዮጵያ ቤተሰብ መምሪያ ማህበር፣በደብረ ማርቆስ ክሊነክ፣ በደብረ ማርቆስ ጤና ጣቢያና ሆስፒታል ባለፈው ዓመት 4ሺህ 742 ሰዎች የደም ምርመራና የምክር አገልግሎት የተሰጣቸው ሲሆን፣ ይህም ከቀዳሚው ዓመት በ1 ሺህ 867 ሰዎች ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በከተማዋ ከቫይረሱ ጋር የሚኖሩ 450 ወገኖች የፀረ ኤች አይ ቪ/ኤድስ መደሐኒት በመውሰድ ላይ መሆናቸውንም አስታወቀዋል፡፡ በደብረ ማርቆስ ከተማ በነሐሴ ወር 1995 የተመሰረተው ቤዛ ከኤች አይ ቪ/ኤድስ ቫይረስ ጋር የሚኖሩ ወገኖች ማህበር በአሁኑ ወቅት ከ470 ለሚበልጡ ከቫይረሱ ጋር ለሚኖሩ ወገኖችና በኤድስ ወላጆቻቸውን ላጡ ሕጻናት ድጋፍና እንክብካቤ በማድረግ ላይ መሆኑን የማህበሩ የፕሮጄክት ኦፊሰር አቶ መንግስቱ እንዳለ ገልጸዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ማህበሩ መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶ ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ 125 የሚሆኑት አባላቱ በተለያዩ የገቢ ማስገኛ ስራዎች ተሰማርተው ራሳቸውን እንዲችሉ በማድረግ ላይ መሆኑን ኦፊሰሩ ገልጸው ፣ከ159 ሺህ ለሚበልጡ ሰዎችም የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት መስጠቱን ተናግረዋል፡፡ የምስራቅ ጎጃም ዞን ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁእ አቡነ ዘካሪያስ ለማህበሩ ድጋፍ ላደረጉ መንግስታዊና መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች የምስክር ወረቀት መስጠታቸውን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘግቧ፡፡
[ 1 ]
[ "የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምርመራ እና የምክር አገልግሎት" ]
[ "ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምክርና የምርመራ አገልግሎት አሰጣጥና የሚሰጥባቸው ቦታወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት." ]
[ "ሥለ ኤድስ በሽታ ምርመራ, የምክር አገልግሎት, ስለሚሰጡባቸው ቦታወች ወይም የህክምና ተቋማት( ሆስፒታሎች,የጤና ኬላወች ) ,ምርመራ ስለሚያደርጉ ሰወች የሚአትቱ ሰነዶች በሙሉ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሰለ ኤድስ በሽታ ባህሪና ስርጭት, መከላከያ, መቆጣጠሪያ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
15
በጌድኦ ዞን በሚገኙ ጤና ጣቢያዎች ኤች አይ ቪ ከእናት ወደ ልጅ እንዳይተላለፍ የሚያደርገውን ሕክምና ጨምሮ በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ የምክርና የደም ምርመራ አገልገሎት መስጠት መጀመሩን የዞኑ ጤና መምሪያ አስታወቀ፡፡ በመምሪያው የኤች አይ ቪ ኤድስ መቆጣጠሪያ ዴስክ ሃላፊ አቶ ሃይለሚካኤል ፈጦዮ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልገሎት እንደገለጹት በወናጎ፣በይርጋጨፌ ፣በጨለቅለቅቱና ቡሌ ወረዳዎች በሚገኙ ጤና ጣቢያዎች ኤች አይ ቪ ከእናት ወደ ልጅ እንዳይተላለፍ የሚያደርገው ሕክምና በቅርቡ መስጠት ተጀምሯል፡፡ በወረዳዎቹ የምክርና የደም ምርመራ አገልገሎት መስጠት በመጀመሩም የአገልገሎቱ ፈላጊዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን አመልከተው ባለፈው ዓመት ምረመራ ያደረጉ 2 ሺህ 927 ሰዎች ቁጥር ከቀዳሚው ዓመት በ800 ብልጫ እንዳለው ገልጠዋል፡፡ ኤች አይ ቪ ከእናት ወደ ልጅ እንዳይተላለፍ በሚያስችለው ሕክምና አገልገሎት ባለፈው ዓመት አንድ ሺህ 50 እናቶች ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጠዋል፡፡ በጤና ተቋማቱ በያዝነው ዓመት 30 ሺህ ለሚደርሱ ነዋሪዎች የምክርና ምርመራ አገልግሎት፣ለስምንት ሺህ እናቶች ደግሞ ኤች አይ ቪ ከእናት ወደ ልጅ እንዳይተላለፍ የሚያስችለው የሕክምና አገልገሎት ተጠቃሚ ለማድረግ መታቀዱን አስታውቀዋል፡፡
[ 1 ]
[ "የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምርመራ እና የምክር አገልግሎት" ]
[ "ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምክርና የምርመራ አገልግሎት አሰጣጥና የሚሰጥባቸው ቦታወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት." ]
[ "ሥለ ኤድስ በሽታ ምርመራ, የምክር አገልግሎት, ስለሚሰጡባቸው ቦታወች ወይም የህክምና ተቋማት( ሆስፒታሎች,የጤና ኬላወች ) ,ምርመራ ስለሚያደርጉ ሰወች የሚአትቱ ሰነዶች በሙሉ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሰለ ኤድስ በሽታ ባህሪና ስርጭት, መከላከያ, መቆጣጠሪያ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
16
በሀዲያ ዞን በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ የኤች አይ ቪ ኤድስ የደም ምርመራ የሚያደርጉ ሰዎች ቁጥር መጨመሩን የዞኑ ጤና መምሪያ ገለጸ፡፡ የመምሪያው የኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ዴስክ ኃላፊ አቶ ታምሬ ዱትሶ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በ1998 ዓ፡ም፡ በ15 የጤና ተቋማት በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ የደም ምርመራ ያደረጉ ሰዎች ቁጥር ከ3 ሺሀ 800 በላይ ደርሶአል፡፡ የተመርማሪዎቹ ቁጥር በ1997 ከነበረው በ1 ሺህ ብልጫ ያሳየ መሆኑን ሀላፊው ገልጸው ከተመርማሪዎቹ መካከል 1 ሺህ 870 ያህሉ ሴቶች መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ የምርመራና የምክር አገልግሎት መስጫዎችን በማስፋፋትና ሌሎች እገዛዎችንም በማድረግ መንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውንም ተናግረዋል፡፡ በፈቃደኝነት ከተመረመሩት መካከል 286ቱ ከቫይረሱ ከቫይረሱ ጋር እንደሚኖሩ መረጋገጡን ገልጸዋል፡፡ በዞኑ ከ270 ሺህ ሰዎች ጋር በኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ዙሪያ ውይይት በመደረጉ የተመርማሪዎች ቁጥር መጨመሩን አመልክተዋል፡፡
[ 1 ]
[ "የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምርመራ እና የምክር አገልግሎት" ]
[ "ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምክርና የምርመራ አገልግሎት አሰጣጥና የሚሰጥባቸው ቦታወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት." ]
[ "ሥለ ኤድስ በሽታ ምርመራ, የምክር አገልግሎት, ስለሚሰጡባቸው ቦታወች ወይም የህክምና ተቋማት( ሆስፒታሎች,የጤና ኬላወች ) ,ምርመራ ስለሚያደርጉ ሰወች የሚአትቱ ሰነዶች በሙሉ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሰለ ኤድስ በሽታ ባህሪና ስርጭት, መከላከያ, መቆጣጠሪያ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
17
በወላይታ ዞን በዚህ ዓመት ለ71ሺህ ሰዎች በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ የኤች አይ ቪ ኤድስ የምክርና የምርመራ አገልግሎት እንደሚሰጥ የዞኑ ጤና መምሪያ አስታወቀ፡፡ በመምሪያው የኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ዴስክ ተወካይ አቶ ዋዱ እንዳለ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንዳስታወቁት በዞኑ 12 ወረዳዎች የምክርና የምርመራ ማዕከላትን ወደ 17 በማሳደግ ለህብረተሰቡ የተጠናከረ አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅት ተደርጓል፡፡ ዘንድሮ የምክርና የምርመራ አገልግሎት የሚያገኙ ሰዎች ቁጥር ከአምናው በ63 ሺህ ብልጫ እንደሚኖራቸው ተወካዩ አመልክተዋል፡፡ እንዲሁም በዞኑ ለ2ሺህ 500 ሰዎች የጸረ ኤች አይ ቪ መድሃኒት እንደሚሰጥ አስታዉቀዋል፡፡
[ 1 ]
[ "የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምርመራ እና የምክር አገልግሎት" ]
[ "ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምክርና የምርመራ አገልግሎት አሰጣጥና የሚሰጥባቸው ቦታወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት." ]
[ "ሥለ ኤድስ በሽታ ምርመራ, የምክር አገልግሎት, ስለሚሰጡባቸው ቦታወች ወይም የህክምና ተቋማት( ሆስፒታሎች,የጤና ኬላወች ) ,ምርመራ ስለሚያደርጉ ሰወች የሚአትቱ ሰነዶች በሙሉ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሰለ ኤድስ በሽታ ባህሪና ስርጭት, መከላከያ, መቆጣጠሪያ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
18
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በግሼ ወረዳ የኤች አይ ቪ/ኤድስ የደም ምርመራና የምክር አገልግሎት መስጫ ማዕከል አለመኖሩን የወረዳው ማስታወቂያ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡ የጽህፈት ቤቱ ተወካይ አቶ ደምሰው መንግስቱ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በወረዳው በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ የኤች አይ ቪ/ኤድስ የደም ምርመራና የምክር አገልግሎት መስጫ ማዕከል ባለመኖሩ ነዋሪዎች አገልግሎቱን ለማግኘት ከግሼ ራቤል ወደ መህል ሜዳ ለትራንስፖርት ከፍተኛ ገንዘብ አውጥተው ለመጓዝ ተገደዋል፡፡ የግሼ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት ተወካይ አቶ አድማሱ አስፋው ስለጉዳዩ ተጠይቀው በወረዳው የኤች አይ ቪ/ኤድስ የደም ምርመራና የምክር አገልግሎት መስጫ ማዕከል ለማቋቋም ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የዞኑ ጤና መምሪያ ተጠባባቂ ኃላፊ አቶ ዘሪሁን ኃይሌ በበኩላቸው ማዕከሉን ለማቋቋም መምሪያው ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ላይ ስለሆነ ችግሩ በቅርቡ ይወገዳል ብለዋል፡፡
[ 1 ]
[ "የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምርመራ እና የምክር አገልግሎት" ]
[ "ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምክርና የምርመራ አገልግሎት አሰጣጥና የሚሰጥባቸው ቦታወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት." ]
[ "ሥለ ኤድስ በሽታ ምርመራ, የምክር አገልግሎት, ስለሚሰጡባቸው ቦታወች ወይም የህክምና ተቋማት( ሆስፒታሎች,የጤና ኬላወች ) ,ምርመራ ስለሚያደርጉ ሰወች የሚአትቱ ሰነዶች በሙሉ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሰለ ኤድስ በሽታ ባህሪና ስርጭት, መከላከያ, መቆጣጠሪያ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
19
በደቡብ ክልል ባለፈው አመት 75 ሺህ ሰዎች በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ የኤች አይቪ ኤድስ ደም ምርመራ ማድረጋቸውን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡ በቢሮው የበሺታዎች መከላከልና መቆጣጠሪያ መምሪያ ሃላፊ አቶ መስቀሌ ሌራ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጡት በ1995 በክልሉ 36 ብቻ የነበሩትን የምክርና የምርመራ አገልግሎት መስጫ ማእከላት ቅጥር ወደ 200 ከፍ በማድረግ በአመቱ በአስር ወራት ውስጥ የተጠቀሰው ቁጥር ላላቸው ሰዎች አገልግሎቱን ለመስጠት ተችሏል፡፡ እንዲሁም አድሎና መገለልን ለማስቀረትና ሕብረተሰቡ ስለበሺታው ያለውን ግንዛቤ እንዲያሳድግ በ1 ሺህ 850 ቀበሌዎች የማህበረሰብ ውይይት መካሄዱን ተናግረዋል፡፡ የመንግስት መስሪያ ቤቶች በጀት መድበው በበሺታው ስርጭት መከላከል ዙሪያ የተጠናከረ እንቅስቃሴ እያደርጉ መሆኑንም አቶ መስቀሌ ጠቁመዋል፡፡ በክልሉ የሚገኙ 200 የጤና ተቋማት ኤች አይቪ ቫይረስ ላለባቸው ወገኖች በነጻ መድሃኒት በመስጠት ላይ መሆናቸውንም አሰረድትዋል፡፡
[ 1 ]
[ "የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምርመራ እና የምክር አገልግሎት" ]
[ "ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምክርና የምርመራ አገልግሎት አሰጣጥና የሚሰጥባቸው ቦታወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት." ]
[ "ሥለ ኤድስ በሽታ ምርመራ, የምክር አገልግሎት, ስለሚሰጡባቸው ቦታወች ወይም የህክምና ተቋማት( ሆስፒታሎች,የጤና ኬላወች ) ,ምርመራ ስለሚያደርጉ ሰወች የሚአትቱ ሰነዶች በሙሉ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሰለ ኤድስ በሽታ ባህሪና ስርጭት, መከላከያ, መቆጣጠሪያ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
20
 በአሶሳ ሆስፒታል የኤች አይ ቪ ኤድስ ምርመራ ተጠናክሯል ስምንት እጮኛሞችና አስር ባለትዳሮች ከኤች አይ ቪ ነጻ ሆኑ ። በአሶሳ ሆስፒታል የኤች አይ ቪ ኤድስ ምርመራ መጠናከሩን የክልሉ አደጋ መከላከል ፣ ሰራተኛና ማሀበራዊ ጉዳይ ቢሮ ከክልሉ አድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ስህፈት ቤት ጋ በመተባበር በተዘጋጀ አውደ ጥናት ላይ ተገለጸ ። በአውደ ጥናቱ ላይ የአሶሳ ሆስፒታል የምክር አገልግሎት ሰጪ ነርስ ለማ ብርሃኑ እንደገለጹት ባለፉት ስድስት ወራት በፈቃደኝነት ከጋብቻ በፊትና በኋላ የሚደረገው የኤች አይ ቪ ኤድስ ምርመራ እየጎለበተ መጥቷል ። በዚህ መሰረት በወራቱ 78 ፈቃደኛ የሆኑ ሰዎች ምርመራ ተደርጎላቸው 13ቱ አች አይ ቪ ኤድስ ቫይረስ እንደተገኘባቸው ተቅሰው ፤ አምስቱ ሴቶችና አንዷ የ8 አመት ታዳጊ መሆኗን አስረድተዋል ። እንዲሁም በ6 ወራት ውስጥ ምርመራ ያደረጉ ስምንት እጮኛሞችና አስር ባለትዳሮች ከበሽታው ነጻ ሆነው መገኘታቸውን አመልክተዋል ። በሌላ በኩል የቫይረሱ ተሸካሚ መሆኗን ያረጋገጠች አንዲት ሴት ራሷን ለሀብረተሰቡ ግልእ በማድረግ የበሽታው ስርጭትና መከላከል ላይ ትምህርት እየሰጠች እንደምትገኝ በአውደ ጥናቱ ላይ ተገልጿል ። የአውደ ጥናቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ማንኛውም ትዳር መመስረት የሚፈልግ ቴናማ ኑሮ ለመመስረት እስከፈለገ ድረስ ቅድሚያ ምርመራ ማድረግ እንደሚገባውና ግዴታም እንዲሆን የሚያስችል ደንብ እንዲወጣ ማድረግ ያስፈልጋል ሲሉ አስተያየት ሰጥተዋል ። በአውደ ጥናቱ ልዩ ልዩ ትምህርታዊ እሁፎች የቀረቡ ሲሆን ፤ 50 ያህል የሃይማኖት አባቶች ፣ የወረዳ አመራሮች ፣ የአሶሳ ተስፋና ወገን ለወገን ጸረ-ኤድስ ክበብ አባላት ተሳታፊ መሆናቸውን ዋልታ እንፎርሜሽን ማእከል ዘግቧል ።
[ 1 ]
[ "የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምርመራ እና የምክር አገልግሎት" ]
[ "ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምክርና የምርመራ አገልግሎት አሰጣጥና የሚሰጥባቸው ቦታወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት." ]
[ "ሥለ ኤድስ በሽታ ምርመራ, የምክር አገልግሎት, ስለሚሰጡባቸው ቦታወች ወይም የህክምና ተቋማት( ሆስፒታሎች,የጤና ኬላወች ) ,ምርመራ ስለሚያደርጉ ሰወች የሚአትቱ ሰነዶች በሙሉ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሰለ ኤድስ በሽታ ባህሪና ስርጭት, መከላከያ, መቆጣጠሪያ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
21
በከፋ ዞን ቢጣ ወረዳ በሁለት ወራት ውስጥ አርሶ አደሮችን ጨምሮ ከ740 በላይ ሰዎች የኤች አይ ቪ ኤድስ ምርመራ ማድረጋቸውንና በወባማ ቀበሌዎች 1 ሺህ 700 አጎበሮች መሰራጨታቸውን የወረዳው ጤና ፅህፈት አስታወቀ፡፡ የፅህፈት ቤቱ ኀላፊ አቶ ገረመው ታከለ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጡት ነዋሪዎቹ በፈቃደኝነት ተነሳስተው የደም ምርመራውን ያደረጉት በወረዳው በቅርቡ በተከፈተው የምርመራ ማዕከል ውስጥ ነው፡፡ በወረዳው በሚገኘው አንድ ጤና ጣቢያ በተቋቋመው በዚሁ ማዕከል ምርመራውን ያደረጉት ለጋብቻና ራሳቸውን ለማወቅ የፈለጉ ሰዎች መሆናቸውን የተናገሩት ኀላፊው ከመካከላቸው 90 በመቶ የሚሆኑት አርሶአደሮች መሆናቸውንም አስታውቀዋል፡፡ በሌላ በኩል የክረምቱን ዝናብ ተከትሎ የሚከሰተውን የወባ በሽታ ለመከላከል ወባማ በሆኑ ቀበሌዎች 1ሺህ 700 የአልጋ አጎበሮች መሰራጨታቸውንና ከ1 ሺህ በሚበልጡ ቤቶች ላይ የወባ ትንኝ መከላከያ ኬሚካል ርጭት መከናወኑን አቶ ገረመው ጨምረው ገልጠዋል፡፡
[ 1 ]
[ "የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምርመራ እና የምክር አገልግሎት" ]
[ "ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምክርና የምርመራ አገልግሎት አሰጣጥና የሚሰጥባቸው ቦታወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት." ]
[ "ሥለ ኤድስ በሽታ ምርመራ, የምክር አገልግሎት, ስለሚሰጡባቸው ቦታወች ወይም የህክምና ተቋማት( ሆስፒታሎች,የጤና ኬላወች ) ,ምርመራ ስለሚያደርጉ ሰወች የሚአትቱ ሰነዶች በሙሉ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሰለ ኤድስ በሽታ ባህሪና ስርጭት, መከላከያ, መቆጣጠሪያ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
22
የምክር ቤቱ አባላት በፈቃደኛነት የኤድስ ምርመራ እንዲያደርጉ ተጠየቀ ። የሀረሪ ክልል የኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ምክር ቤት አባላት በበጎ ፈቃደኝነት የደም ምርመራ በማድረግ ለሀብረተሰቡ አራያ እንዲሆኑ የተስፋህ ጎህ ኢትዮጵያ ማሀበር ጠየቀ ። ትናንት በሀረር ከተማ በተካሄደው የምክር ቤቱ ተቅላላ ጉበኤ ላይ በማሀበሩ የሀረር ቅርንጫፍ የተላለፈ መልእክት የኤድስን ስርጭት ለመግታትና የባህሪ ለውጥ ለማምጣት ለሚደረገው ሂደት ባለስልጣናትና የምክር ቤቱ አባላት በቅድሚያ ራሳቸው መመርመር ይኖርባቸዋል ብሏል ። በአካባቢው የጤና ባለሙያዎች ጭምር በፍቃደኝነት የደም ምርመራ የማድረግ ተነሳሽነቱ አይታይም ያለው መልእክቱ ፤ ይህ አካሄድ በኤድስ ላይ ያለውን ዝምታ የማይሰብር በመሆኑ የምክር ቤቱ አባላት ተመርምረው በአራያነት መንገዱን እንዲያሳዩ ጠይቋል ። በሃኪሞች ጥርጣሬ የደም ምርመራ የሚደረግላቸው ህሙማን ቫይረሱ ሲገኝባቸው ከመንገር ይልቅ በሚስጥር ስለሚያዙ ህሙማን ትንቃቄ ሳያደርጉ በሽታውን ለጤነኛው ሰው እያስተላለፉ መሆኑንም ገልጾ ፤ ከዚህ አኳያ ለህሙማኑ በቂ የስነ- ልቦናና የምክር አገልግሎት ተሰጥቷቸው በግልእ ቫይረሱ እንዳለባቸው ሊነገራቸው ይገባል ብሏል ። የምክር ቤቱ ሴክሬታሪያት ዶክተር መሃዲ ዘካሪያስ ባቀረቡት ሪፖርት በክልል 36 የገጠርና ከተማ ቀበሌዎች የኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ኮሚቴ እንዲሁም በሰባት ቢሮዎች ግብረ ሃይል ተቋቁሞ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን ገልጸዋል ። ከአለም ባንክና ከዩኒሴፍ በ1993/94 ለኤድስ መከላከያ ፕሮግራም ከተለቀቀው 1ነጥብ 1 ሚሊየን ብር ውስጥ 776 ሺ 600 ብር ለ16 የከተማ ቀበሌዎች ፣ ለሰባት ቢሮዎች ፣ ክበባት ፣ መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች ለክትትልና አቅምግንባታ ወጪ መደረጉን አስተባባሪው ተናግረዋል ። የክልሉ ርእሰ-መስተዳድር አቶ ፎአድ እብራሂም በበሽታውን ለመከላከል በክልሉ የቅንጅት ጉድለት መኖሩን ጠቁመው ፤ በቀጣይ የተጠናከረ ስራ እንደሚጠብቃቸው ለምክር ቤቱ አባላት ማሳሰባቸውን ዋልታ እንፎርሜሽን ማእከል ዘግቧል ።
[ 1 ]
[ "የኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምርመራ እና የምክር አገልግሎት" ]
[ "ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የምክርና የምርመራ አገልግሎት አሰጣጥና የሚሰጥባቸው ቦታወች የሚያትቱ ሰነዶችን መለየት." ]
[ "ሥለ ኤድስ በሽታ ምርመራ, የምክር አገልግሎት, ስለሚሰጡባቸው ቦታወች ወይም የህክምና ተቋማት( ሆስፒታሎች,የጤና ኬላወች ) ,ምርመራ ስለሚያደርጉ ሰወች የሚአትቱ ሰነዶች በሙሉ ጠቃሚ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ሰለ ኤድስ በሽታ ባህሪና ስርጭት, መከላከያ, መቆጣጠሪያ የሚያትቱ ሰነዶች አይጠቅሙም፡፡" ]
23
1  ንጉሥ ዳዊት አረጀ፤ ዕድሜውም እየገፋ ሄደ፤ ልብስ ቢደራርቡለትም እንኳ ሊሞቀው አልቻለም። 2  በመሆኑም አገልጋዮቹ “ለጌታዬ ለንጉሡ አንዲት ልጃገረድ ትፈለግለት፤ እሷም ንጉሡን እንደ ሞግዚት ሆና ትንከባከበው። ጌታዬ ንጉሡ እንዲሞቀው በእቅፉ ትተኛለች” አሉት። 3  ስለዚህ በመላው የእስራኤል ግዛት በመዘዋወር ቆንጆ ልጃገረድ ፈለጉ፤ ሹነማዊቷን አቢሻግንም አገኙ፤ ወደ ንጉሡም አመጧት። 4  እሷም እጅግ ውብ ነበረች፤ የንጉሡም ሞግዚት ሆነች፤ ትንከባከበውም ጀመር፤ ሆኖም ንጉሡ ከእሷ ጋር የፆታ ግንኙነት አልፈጸመም። 5  በዚህ ጊዜ የሃጊት ልጅ አዶንያስ “ንጉሥ እሆናለሁ!” በማለት ራሱን ከፍ ከፍ ያደርግ ጀመር። ለራሱም ሠረገላ ከነፈረሰኞቹ እንዲሁም ከፊት ከፊቱ የሚሮጡ 50 ሰዎች እንዲዘጋጁለት አደረገ። 6  አባቱ ግን አንድም ቀን “ይህን ያደረግከው ለምንድን ነው?” በማለት ተቃውሞት አያውቅም ነበር። በተጨማሪም አዶንያስ እጅግ መልከ መልካም ነበር፤ እናቱ እሱን የወለደችው ከአቢሴሎም በኋላ ነበር። 7  እሱም ከጽሩያ ልጅ ከኢዮዓብና ከካህኑ ከአብያታር ጋር ተመካከረ፤ እነሱም እርዳታና ድጋፍ አደረጉለት። 8  ሆኖም ካህኑ ሳዶቅ፣ የዮዳሄ ልጅ በናያህ፣ ነቢዩ ናታን፣ ሺምአይ፣ ረአይና የዳዊት ኃያላን ተዋጊዎች አዶንያስን አልደገፉትም። 9  በኋላም አዶንያስ በኤንሮጌል አቅራቢያ በሚገኘው በጾሃለት ድንጋይ አጠገብ በጎችን፣ ከብቶችንና የሰቡ እንስሳትን መሥዋዕት አድርጎ አቀረበ፤ የንጉሡ ልጆች የሆኑትን ወንድሞቹን በሙሉ እንዲሁም የንጉሡ አገልጋዮች የሆኑትን የይሁዳን ሰዎች ሁሉ ጠራ። 10  ይሁን እንጂ ነቢዩ ናታንን፣ በናያህን፣ የዳዊትን ኃያላን ተዋጊዎች ወይም ወንድሙን ሰለሞንን አልጠራም። 11  ከዚያም ናታን የሰለሞንን እናት ቤርሳቤህን እንዲህ አላት፦ “የሃጊት ልጅ አዶንያስ ንጉሥ እንደሆነና ጌታችን ዳዊት ደግሞ ስለ ጉዳዩ ምንም የሚያውቀው ነገር እንደሌለ አልሰማሽም? 12  ስለዚህ አሁን ነይ፣ የራስሽንም ሆነ የልጅሽን የሰለሞንን ሕይወት ማዳን እንድትችይ አንድ ነገር ልምከርሽ። 13  ወደ ንጉሥ ዳዊት ገብተሽ እንዲህ በዪው፦ ‘“ልጅሽ ሰለሞን ከእኔ በኋላ ንጉሥ ይሆናል፤ በዙፋኔም ላይ የሚቀመጠው እሱ ነው” በማለት ለአገልጋይህ የማልክላት አንተ ንጉሡ ጌታዬ አልነበርክም? ታዲያ አዶንያስ ንጉሥ የሆነው ለምንድን ነው?’ 14  አንቺም እዚያው ገና ከንጉሡ ጋር እየተነጋገርሽ ሳለ እኔ ተከትዬሽ እገባና ያልሽው ትክክል መሆኑን እናገራለሁ።” 15  በመሆኑም ቤርሳቤህ ንጉሡ ወዳለበት ወደ ውስጠኛው ክፍል ገባች። ንጉሡ በጣም አርጅቶ ነበር፤ ሹነማዊቷ አቢሻግም ንጉሡን እየተንከባከበች ነበር። 16  ከዚያም ቤርሳቤህ በንጉሡ ፊት ተደፍታ ሰገደች፤ ንጉሡም “ጥያቄሽ ምንድን ነው?” አላት። 17  እሷም እንዲህ ስትል መለሰች፦ “ጌታዬ ሆይ፣ ‘ልጅሽ ሰለሞን ከእኔ በኋላ ንጉሥ ይሆናል፤ በዙፋኔም ላይ የሚቀመጠው እሱ ነው’ በማለት ለአገልጋይህ በአምላክህ በይሖዋ የማልክላት አንተ ነበርክ። 18  ይኸው አሁን ግን አዶንያስ ንጉሥ ሆኗል፤ ጌታዬ ንጉሡም ስለዚህ ጉዳይ ምንም የሚያውቀው ነገር የለም። 19  እሱም በጣም ብዙ በሬዎችን፣ የሰቡ እንስሳትንና በጎችን መሥዋዕት አድርጓል፤ የንጉሡን ልጆች በሙሉ፣ ካህኑን አብያታርንና የሠራዊቱን አለቃ ኢዮዓብን ጠርቷል፤ አገልጋይህን ሰለሞንን ግን አልጠራውም። 20  አሁንም ጌታዬ ንጉሥ ሆይ፣ እስራኤላውያን በሙሉ ከጌታዬ ከንጉሡ በኋላ በዙፋኑ ላይ የሚቀመጠው ማን እንደሆነ እንድታሳውቃቸው ዓይኖቻቸው አንተ ላይ ናቸው። 21  አለዚያ ግን ጌታዬ ንጉሡ ከአባቶቹ ጋር በሚያንቀላፋበት ጊዜ እኔና ልጄ ሰለሞን እንደ ከዳተኞች ተደርገን እንቆጠራለን።” 22  እሷም ገና ከንጉሡ ጋር እየተነጋገረች ሳለ ነቢዩ ናታን ገባ። 23  ወዲያውም ለንጉሡ “ነቢዩ ናታን መጥቷል!” ብለው ነገሩት። ናታንም ንጉሡ ፊት ቀርቦ በግንባሩ መሬት ላይ በመደፋት ሰገደ። 24  ከዚያም ናታን እንዲህ አለ፦ “ጌታዬ ንጉሥ ሆይ፣ ‘አዶንያስ ከእኔ በኋላ ንጉሥ ይሆናል፤ በዙፋኔ ላይ የሚቀመጠውም እሱ ነው’ ብለህ ተናግረሃል እንዴ? 25  ይኸው ዛሬ በጣም ብዙ በሬዎችን፣ የሰቡ እንስሳትንና በጎችን ለመሠዋት ወርዷል፤ እንዲሁም የንጉሡን ልጆች በሙሉ፣ የሠራዊቱን አለቆችና ካህኑን አብያታርን ጠርቷል። እነሱም በዚያ ከእሱ ጋር እየበሉና እየጠጡ ‘ንጉሥ አዶንያስ ለዘላለም ይኑር!’ እያሉ ነው። 26  ሆኖም እኔን አገልጋይህን ወይም ካህኑን ሳዶቅን አሊያም የዮዳሄን ልጅ በናያህን ወይም አገልጋይህን ሰለሞንን አልጠራም። 27  ጌታዬ ንጉሡ ከእሱ በኋላ በጌታዬ በንጉሡ ዙፋን ላይ የሚቀመጠው ማን እንደሆነ ለአገልጋዩ ሳይነግረው ይህ እንዲደረግ ፈቅዷል?” 28  በዚህ ጊዜ ንጉሥ ዳዊት “ቤርሳቤህን ጥሩልኝ” አለ። እሷም ገብታ ንጉሡ ፊት ቆመች። 29  ንጉሡም እንዲህ ሲል ማለ፦ “ከመከራ ሁሉ ባዳነኝ ሕያው በሆነው በይሖዋ እምላለሁ፣ 30  ‘ልጅሽ ሰለሞን ከእኔ በኋላ ንጉሥ ይሆናል፤ በእኔ ምትክ በዙፋኔ ላይ የሚቀመጠውም እሱ ነው!’ በማለት በእስራኤል አምላክ በይሖዋ በማልኩልሽ መሠረት ዛሬም ይህ እንዲፈጸም አደርጋለሁ።” 31  ከዚያም ቤርሳቤህ በግንባሯ መሬት ላይ ተደፍታ ለንጉሡ በመስገድ “ጌታዬ ንጉሥ ዳዊት ለዘላለም ይኑር!” አለች። 32  ንጉሥ ዳዊትም ወዲያውኑ “በሉ አሁን ካህኑን ሳዶቅን፣ ነቢዩን ናታንንና የዮዳሄን ልጅ በናያህን ጥሩልኝ” አለ። እነሱም ገብተው ንጉሡ ፊት ቀረቡ። 33  ንጉሡም እንዲህ አላቸው፦ “የጌታችሁን አገልጋዮች ውሰዱና ልጄን ሰለሞንን በበቅሎዬ ላይ አስቀምጣችሁ ወደ ግዮን ይዛችሁት ውረዱ። 34  በዚያም ካህኑ ሳዶቅና ነቢዩ ናታን በእስራኤል ላይ ንጉሥ አድርገው ይቀቡታል፤ ከዚያም ቀንደ መለከት እየነፋችሁ ‘ንጉሥ ሰለሞን ለዘላለም ይኑር!’ በሉ። 35  አጅባችሁትም ተመለሱ፤ እሱም መጥቶ በዙፋኔ ላይ ይቀመጣል፤ በእኔም ምትክ ንጉሥ ይሆናል፤ እኔም በእስራኤልና በይሁዳ ላይ መሪ አድርጌ እሾመዋለሁ።” 36  የዮዳሄ ልጅ በናያህም ወዲያውኑ ንጉሡን እንዲህ አለው፦ “አሜን! የጌታዬ የንጉሡ አምላክ ይሖዋ ይህን ያጽናው። 37  ይሖዋ ከጌታዬ ከንጉሡ ጋር እንደነበረ ሁሉ ከሰለሞንም ጋር ይሁን፤ ዙፋኑንም ከጌታዬ ከንጉሥ ዳዊት ዙፋን የበለጠ ያድርገው።” 38  ከዚያም ካህኑ ሳዶቅ፣ ነቢዩ ናታን፣ የዮዳሄ ልጅ በናያህ፣ ከሪታውያንና ጴሌታውያን ወርደው ሰለሞንን በንጉሥ ዳዊት በቅሎ ላይ አስቀመጡት፤ ወደ ግዮንም አመጡት። 39  ካህኑ ሳዶቅም ከድንኳኑ ውስጥ የዘይቱን ቀንድ ወስዶ ሰለሞንን ቀባው፤ እነሱም ቀንደ መለከት መንፋት ጀመሩ፤ ሕዝቡም ሁሉ “ንጉሥ ሰለሞን ለዘላለም ይኑር!” እያለ ይጮኽ ጀመር። 40  ከዚያም ሕዝቡ በሙሉ ዋሽንት እየነፋና በደስታ እየፈነደቀ ተከትሎት ወጣ፤ ከጩኸታቸውም የተነሳ ምድሪቱ ተሰነጠቀች። 41  አዶንያስና የጋበዛቸው ሰዎች ሁሉ በልተው ሲጨርሱ ይህን ድምፅ ሰሙ። ኢዮዓብ የቀንደ መለከቱን ድምፅ ሲሰማ “በከተማዋ ውስጥ የሚሰማው ይህ ሁሉ ሁካታ ምንድን ነው?” አለ። 42  እሱም ገና እየተናገረ ሳለ የካህኑ የአብያታር ልጅ ዮናታን መጣ። ከዚያም አዶንያስ “መቼም አንተ ጥሩ ሰው ስለሆንክ ምሥራች ሳትይዝ አትመጣምና ግባ” አለው። 43  ዮናታን ግን ለአዶንያስ እንዲህ ሲል መለሰለት፦ “ምሥራች ይዤስ አልመጣሁም! ጌታችን ንጉሥ ዳዊት ሰለሞንን አንግሦታል። 44  ንጉሡም ካህኑ ሳዶቅ፣ ነቢዩ ናታን፣ የዮዳሄ ልጅ በናያህ፣ ከሪታውያንና ጴሌታውያን አብረውት እንዲሄዱ አደረገ፤ እነሱም በንጉሡ በቅሎ ላይ አስቀመጡት። 45  ከዚያም ካህኑ ሳዶቅና ነቢዩ ናታን በግዮን ንጉሥ አድርገው ቀቡት። እነሱም ከዚያ እየተደሰቱ መጡ፤ ከተማዋ በጩኸት እየተናወጠች ነው። እናንተም የሰማችሁት ይህን ድምፅ ነው። 46  ከዚህም በላይ ሰለሞን በነገሥታቱ ዙፋን ላይ ተቀምጧል። 47  የንጉሡ አገልጋዮችም ‘አምላክህ የሰለሞንን ስም ከአንተ ስም በላይ ታላቅ ያድርገው፤ ዙፋኑንም ከአንተ ዙፋን የበለጠ ያድርገው’ በማለት ለጌታችን ለንጉሥ ዳዊት ደስታቸውን ለመግለጽ መጥተዋል። በዚህ ጊዜ ንጉሡ አልጋው ላይ ሰገደ። 48  ከዚያም ንጉሡ ‘ዛሬ በዙፋኔ ላይ የሚቀመጥ ሰው የሰጠኝና ዓይኖቼም ይህን እንዲያዩ ያደረገው የእስራኤል አምላክ ይሖዋ ይወደስ!’ አለ።” 49  አዶንያስ የጋበዛቸው ሰዎችም ሁሉ ተሸበሩ፤ እያንዳንዳቸውም ተነስተው በየፊናቸው ሄዱ። 50  አዶንያስም ሰለሞንን ስለፈራው ተነስቶ በመሄድ የመሠዊያውን ቀንዶች ያዘ። 51  በኋላም ሰለሞን “አዶንያስ ንጉሥ ሰለሞንን ፈርቶታል፤ ‘በመጀመሪያ ንጉሥ ሰለሞን አገልጋዩን በሰይፍ እንደማይገድል ይማልልኝ’ በማለት የመሠዊያውን ቀንዶች ይዟል” ተብሎ ተነገረው። 52  በዚህ ጊዜ ሰለሞን “ጸባዩን ካሳመረ ከራስ ፀጉሩ አንዲቷም እንኳ መሬት ላይ አትወድቅም፤ መጥፎ ነገር ከተገኘበት ግን ይሞታል” አለ። 53   በመሆኑም ንጉሥ ሰለሞን አዶንያስን ከመሠዊያው ላይ እንዲያወርዱት ሰዎች ላከ። ከዚያም አዶንያስ መጥቶ ለንጉሥ ሰለሞን ሰገደ፤ ሰለሞንም “ወደ ቤትህ ሂድ” አለው።
[]
[]
[]
[]
24
10  የሳባ ንግሥት ስለ ሰለሞን ዝና እንዲሁም ከይሖዋ ስም ጋር ስላለው ግንኙነት ሰማች፤ በመሆኑም አስቸጋሪ በሆኑ ጥያቄዎች ልትፈትነው መጣች። 2  እሷም እጅግ ታላቅ አጀብ አስከትላ እንዲሁም የበለሳን ዘይት፣ በጣም ብዙ ወርቅና የከበሩ ድንጋዮች በግመል አስጭና ኢየሩሳሌም ደረሰች። ወደ ሰለሞንም ገብታ በልቧ ያለውን ሁሉ ነገረችው። 3  ሰለሞንም ጥያቄዎቿን ሁሉ መለሰላት። ንጉሡ ሊያብራራላት ያልቻለው ምንም ነገር አልነበረም። 4  የሳባ ንግሥት የሰለሞንን ጥበብ ሁሉና የሠራውን ቤት ስትመለከት፣ 5  በገበታው ላይ የሚቀርበውን ምግብ፣ የአገልጋዮቹን አቀማመጥ፣ አስተናጋጆቹ በማዕድ ላይ የሚያስተናግዱበትን መንገድና አለባበሳቸውን፣ መጠጥ አሳላፊዎቹን እንዲሁም በይሖዋ ቤት ዘወትር የሚያቀርባቸውን የሚቃጠሉ መሥዋዕቶች ስታይ በመገረም ፈዛ ቀረች። 6  በመሆኑም ንጉሡን እንዲህ አለችው፦ “ስላከናወንካቸው ነገሮችና ስለ ጥበብህ በአገሬ ሳለሁ የሰማሁት ነገር እውነት ነው። 7  ይሁንና እኔ ራሴ መጥቼ በገዛ ዓይኔ እስከማይ ድረስ የተነገረኝን ነገር አላመንኩም ነበር። እንደዚያም ሆኖ ግማሹ እንኳ አልተነገረኝም! በጥበብም ሆነ በብልጽግና ከሰማሁት ሁሉ እጅግ የላቅክ ነህ። 8  አብረውህ ያሉ ሰዎች ደስተኞች ናቸው፤ ዘወትር በፊትህ ቆመው ጥበብህን የሚሰሙት አገልጋዮችህም እጅግ ደስተኞች ናቸው! 9  አንተን በእስራኤል ዙፋን ላይ በማስቀመጥ በአንተ ደስ የተሰኘው አምላክህ ይሖዋ ይወደስ። ይሖዋ ለእስራኤል ካለው ዘላለማዊ ፍቅር የተነሳ ፍትሕንና ጽድቅን እንድታሰፍን ንጉሥ አድርጎ ሾሞሃል።” 10  ከዚያም ለንጉሡ 120 ታላንት ወርቅ እንዲሁም እጅግ ብዙ የበለሳን ዘይትና የከበሩ ድንጋዮች ሰጠችው። የሳባ ንግሥት ለንጉሥ ሰለሞን የሰጠችውን የሚያህል መጠን ያለው የበለሳን ዘይት ከዚያ በኋላ መጥቶ አያውቅም። 11  ከኦፊር ወርቅ ጭነው የመጡት የኪራም መርከቦች ከኦፊር እጅግ ብዙ የሰንደል ዛፍ ሳንቃዎችንና የከበሩ ድንጋዮችንም አምጥተው ነበር። 12  ንጉሡም ከሰንደል ዛፍ ሳንቃዎቹ ለይሖዋ ቤትና ለንጉሡ ቤት ድጋፎችን እንዲሁም ለዘማሪዎቹ የሚሆኑ በገናዎችንና ሌሎች ባለ አውታር መሣሪያዎችን ሠራ። ይህን ያህል ብዛት ያለው የሰንደል ዛፍ ሳንቃ እስከ ዛሬ ድረስ መጥቶም ሆነ ታይቶ አያውቅም። 13  ንጉሥ ሰለሞንም ለሳባ ንግሥት በልግስና ተነሳስቶ ከሰጣት ሌላ የፈለገችውንና የጠየቀችውን ነገር ሁሉ ሰጣት። ከዚያም ተነስታ አገልጋዮቿን በማስከተል ወደ አገሯ ተመለሰች። 14  ሰለሞን በየዓመቱ 666 ታላንት ወርቅ ይመጣለት ነበር፤ 15  ይህም ከነጋዴዎች፣ ከሸቃጮች ከሚገኘው ትርፍ፣ ከዓረብ ነገሥታት ሁሉና ከአገረ ገዢዎች የሚሰበሰበውን ሳይጨምር ነው። 16  ንጉሥ ሰለሞን ከቅይጥ ወርቅ 200 ትላልቅ ጋሻዎችን ሠራ፤ (እያንዳንዱ ጋሻ በ600 ሰቅል ወርቅ ተለብጦ ነበር)፤ 17  እንዲሁም ከቅይጥ ወርቅ 300 ትናንሽ ጋሻዎችን ሠራ፤ (እያንዳንዱ ትንሽ ጋሻ በሦስት ምናን ወርቅ ተለብጦ ነበር)። ከዚያም ንጉሡ የሊባኖስ ደን በተባለው ቤት አስቀመጣቸው። 18  በተጨማሪም ንጉሡ ከዝሆን ጥርስ ትልቅ ዙፋን ሠርቶ በተጣራ ወርቅ ለበጠው። 19  ወደ ዙፋኑ የሚያስወጡ ስድስት ደረጃዎች ነበሩ፤ ዙፋኑም ከኋላው በኩል ክብ ከለላ ነበረው፤ መቀመጫውም በጎንና በጎኑ የእጅ መደገፊያዎች ያሉት ሲሆን ከእጅ መደገፊያዎቹም አጠገብ ሁለት አንበሶች ቆመው ነበር። 20  በስድስቱ ደረጃዎች ዳርና ዳር አንድ አንድ አንበሳ፣ በአጠቃላይ 12 አንበሶች ቆመው ነበር። እንዲህ ያለ ዙፋን የሠራ አንድም ሌላ መንግሥት አልነበረም። 21  የንጉሥ ሰለሞን የመጠጫ ዕቃዎች በሙሉ ከወርቅ የተሠሩ ነበሩ፤ የሊባኖስ ደን በተባለው ቤት የነበሩት ዕቃዎችም በሙሉ ከንጹሕ ወርቅ የተሠሩ ነበሩ። ከብር የተሠራ ምንም ነገር አልነበረም፤ በሰለሞን ዘመን ብር እንደ ተራ ነገር ይቆጠር ነበር። 22  ንጉሡ ከኪራም መርከቦች ጋር አብረው በባሕር ላይ የሚጓዙ የተርሴስ መርከቦች ነበሩት። እነዚህ የተርሴስ መርከቦች በሦስት ዓመት አንድ ጊዜ ወርቅ፣ ብር፣ የዝሆን ጥርስ፣ ጦጣና ጣዎስ ጭነው ይመጡ ነበር። 23  በመሆኑም ንጉሥ ሰለሞን በብልጽግናና በጥበብ ምድር ላይ ካሉ ሌሎች ነገሥታት ሁሉ ይበልጥ ነበር። 24  የምድር ሕዝቦችም ሁሉ አምላክ በሰለሞን ልብ ውስጥ ያኖረውን ጥበብ ይሰሙ ዘንድ ከእሱ ጋር ለመገናኘት ይጓጉ ነበር። 25  ወደ እሱ የሚመጡትም ሰዎች በየዓመቱ የብር ዕቃዎች፣ የወርቅ ዕቃዎች፣ ልብሶች፣ የጦር ትጥቆች፣ የበለሳን ዘይት፣ ፈረሶችና በቅሎዎች ስጦታ አድርገው ያመጡ ነበር። 26  ሰለሞንም ሠረገሎችንና ፈረሶችን መሰብሰቡን ቀጠለ፤ እሱም 1,400 ሠረገሎችና 12,000 ፈረሶች ነበሩት፤ እነሱንም በሠረገላ ከተሞችና በኢየሩሳሌም በንጉሡ አቅራቢያ አኖራቸው። 27  ንጉሡ በኢየሩሳሌም ያለውን ብር ከብዛቱ የተነሳ በየቦታው እንደሚገኝ ድንጋይ አደረገው፤ አርዘ ሊባኖሱንም ከብዛቱ የተነሳ በሸፌላ እንደሚገኘው የሾላ ዛፍ አደረገው። 28  የሰለሞን ፈረሶች ከግብፅ ያስመጣቸው ነበሩ፤ የንጉሡ ነጋዴዎችም የፈረሶቹን መንጋ አንዴ በተተመነው ዋጋ ይገዙ ነበር። 29  ከግብፅ የሚመጣው እያንዳንዱ ሠረገላ 600 የብር ሰቅል ያወጣ ነበር፤ አንድ ፈረስ ደግሞ 150 ሰቅል ያወጣል፤ እነሱ ደግሞ በተራቸው ለሂታውያን ነገሥታትና ለሶርያ ነገሥታት ሁሉ ሠረገሎችንና ፈረሶችን ይሸጡ ነበር።
[]
[]
[]
[]
25
11  ይሁንና ንጉሥ ሰለሞን ከፈርዖን ልጅ ሌላ ብዙ የባዕድ አገር ሴቶችን ማለትም ሞዓባውያን፣ አሞናውያን፣ ኤዶማውያን፣ ሲዶናውያንና ሂታውያን ሴቶችን አፈቀረ። 2  እነሱም ይሖዋ ለእስራኤላውያን “ከእነሱ ጋር አትቀላቀሉ፤ እነሱም ከእናንተ ጋር አይቀላቀሉ፤ አለዚያ ያለምንም ጥርጥር ልባችሁ አማልክታቸውን ወደ መከተል እንዲያዘነብል ያደርጉታል” ብሎ ከነገራቸው ብሔራት ወገን ነበሩ። ሆኖም ሰለሞን ከእነሱ ጋር ተጣበቀ፤ ደግሞም አፈቀራቸው። 3  እሱም ልዕልቶች የሆኑ 700 ሚስቶች እንዲሁም 300 ቁባቶች ነበሩት፤ ሚስቶቹም ቀስ በቀስ ልቡ ወደ ሌላ እንዲያዘነብል አደረጉት። 4  ሰለሞን በሸመገለ ጊዜ ሚስቶቹ ልቡ ሌሎች አማልክትን ወደ መከተል እንዲያዘነብል አደረጉት፤ ልቡ እንደ አባቱ እንደ ዳዊት ልብ በአምላኩ በይሖዋ ዘንድ ሙሉ አልነበረም። 5  ሰለሞን የሲዶናውያንን እንስት አምላክ አስታሮትንና አስጸያፊ የሆነውን የአሞናውያንን አምላክ ሚልኮምን ተከተለ። 6  ሰለሞንም በይሖዋ ፊት መጥፎ የሆነውን ነገር አደረገ፤ አባቱ ዳዊት እንዳደረገው ይሖዋን ሙሉ በሙሉ አልተከተለም። 7  ሰለሞን አስጸያፊ ለሆነው የሞዓብ አምላክ ለከሞሽና አስጸያፊ ለሆነው ለአሞናውያን አምላክ ለሞሎክ ኢየሩሳሌም ፊት ለፊት በሚገኘው ተራራ ላይ ከፍ ያለ የማምለኪያ ቦታ የሠራው በዚህ ጊዜ ነበር። 8  ለአማልክታቸው የሚጨስ መሥዋዕት ለሚያቀርቡትና ለሚሠዉት የባዕድ አገር ሚስቶቹ ሁሉ ልክ እንደዚሁ አደረገ። 9  ሰለሞን ሁለት ጊዜ ከተገለጠለት ከእስራኤል አምላክ ከይሖዋ ልቡ ስለሸፈተ ይሖዋ በሰለሞን ላይ ተቆጣ፤ 10  ደግሞም ሌሎች አማልክትን እንዳይከተል በማዘዝ ይህንኑ ጉዳይ አስመልክቶ አስጠንቅቆት ነበር። እሱ ግን ይሖዋ ያዘዘውን ነገር አልጠበቀም። 11  በዚህ ጊዜ ይሖዋ ሰለሞንን እንዲህ አለው፦ “ይህን ስላደረግክ እንዲሁም ባዘዝኩህ መሠረት ቃል ኪዳኔንና ደንቦቼን ስላልጠበቅክ መንግሥትህን ቀድጄ ከአንተ እወስደዋለሁ፤ ከአገልጋዮችህም መካከል ለአንዱ እሰጠዋለሁ። 12  ሆኖም ስለ አባትህ ስለ ዳዊት ስል በአንተ ዘመን ይህን አላደርግም። መንግሥትህን ከልጅህ እጅ ላይ እቀደዋለሁ፤ 13  ይሁንና መንግሥቱን በሙሉ ቀድጄ አልወስድም። ስለ አገልጋዬ ስለ ዳዊትና ስለመረጥኳት ስለ ኢየሩሳሌም ስል ለልጅህ አንድ ነገድ እሰጠዋለሁ።” 14  ከዚያም ይሖዋ ከኤዶም ንጉሣዊ ቤተሰብ የሆነውን ኤዶማዊውን ሃዳድን በሰለሞን ላይ ተቃዋሚ አድርጎ አስነሳው። 15  ዳዊት ኤዶምን ድል ባደረገበት ጊዜ የሠራዊቱ አለቃ የሆነው ኢዮዓብ የተገደሉትን ለመቅበር ወጥቶ የነበረ ሲሆን በኤዶም የሚገኘውን እያንዳንዱን ወንድ ለመግደል ሞክሮ ነበር። 16  (ምክንያቱም ኢዮዓብ በኤዶም የሚገኘውን እያንዳንዱን ወንድ ገድሎ እስኪጨርስ ድረስ ከመላው እስራኤል ጋር በዚያ ለስድስት ወር ተቀምጦ ነበር።) 17  ሆኖም ሃዳድ የአባቱ አገልጋዮች ከሆኑ የተወሰኑ ኤዶማውያን ጋር ሸሸ፤ እነሱም ወደ ግብፅ ሄዱ፤ በወቅቱ ሃዳድ ገና ትንሽ ልጅ ነበር። 18  እነሱም ከምድያም ተነስተው ወደ ፋራን ሄዱ። ከፋራንም ሰዎች ይዘው ወደ ግብፅ ይኸውም ወደ ግብፁ ንጉሥ ወደ ፈርዖን መጡ፤ ፈርዖንም ቤትና መሬት ሰጠው፤ ቀለብም እንዲሰፈርለት አደረገ። 19  ሃዳድም በፈርዖን ፊት ሞገስ ስላገኘ ፈርዖን የገዛ ሚስቱን እህት ማለትም የንግሥት ጣፍኔስን እህት ዳረለት። 20  ከጊዜ በኋላ የጣፍኔስ እህት፣ ጌኑባት የተባለ ልጅ ወለደችለት፤ ጣፍኔስም ልጁን በፈርዖን ቤት ውስጥ አሳደገችው፤ ጌኑባት በፈርዖን ቤት ከፈርዖን ልጆች ጋር ኖረ። 21  ሃዳድ በግብፅ ሳለ ዳዊት ከአባቶቹ ጋር እንዳንቀላፋ እንዲሁም የሠራዊቱ አለቃ ኢዮዓብ እንደሞተ ሰማ። በመሆኑም ሃዳድ ፈርዖንን “ወደ አገሬ እንድሄድ አሰናብተኝ” አለው። 22  ፈርዖን ግን “እዚህ እኔ ጋር እያለህ ምን ጎደለብህና ነው ወደ አገርህ መሄድ የፈለግከው?” አለው። እሱም “ምንም የጎደለብኝ ነገር የለም፤ ብቻ እንድሄድ አሰናብተኝ” አለው። 23  በተጨማሪም አምላክ ከጌታው ከጾባህ ንጉሥ ከሃዳድኤዜር የኮበለለውን የኤሊያዳን ልጅ ረዞንን በሰለሞን ላይ ተቃዋሚ አድርጎ አስነሳው። 24  እሱም ዳዊት የጾባህን ሰዎች ድል ባደረገበት ጊዜ ሰዎችን አሰባስቦ የአንድ ወራሪ ቡድን አለቃ ሆነ። በመሆኑም ወደ ደማስቆ ሄደው በዚያ ሰፈሩ፤ በደማስቆም መግዛት ጀመሩ። 25  ሃዳድ በእስራኤል ላይ ካስከተለው ጉዳት በተጨማሪ ረዞንም በሰለሞን ዘመን ሁሉ የእስራኤል ተቃዋሚ ሆነ፤ በሶርያ ላይ በነገሠበትም ዘመን ሁሉ ለእስራኤል ከፍተኛ ጥላቻ ነበረው። 26  እንዲሁም የሰለሞን አገልጋይ የሆነ ኢዮርብዓም የተባለ አንድ ኤፍሬማዊ ነበር፤ እሱም ከጸሬዳህ ወገን ሲሆን የናባጥ ልጅ ነበር፤ እናቱም ጽሩዓ የምትባል መበለት ነበረች። እሱም በንጉሡ ላይ ማመፅ ጀመረ። 27  በንጉሡ ላይ ያመፀውም በዚህ የተነሳ ነው፦ ሰለሞን ጉብታውን ሠርቶ እንዲሁም በአባቱ በዳዊት ከተማ ቅጥር ላይ የነበረውን ክፍተት ዘግቶ ነበር። 28  ኢዮርብዓም ከፍተኛ ችሎታ ያለው ሰው ነበር። ሰለሞንም ወጣቱ ጠንካራ ሠራተኛ መሆኑን ሲያይ በዮሴፍ ቤት በሚከናወነው የግዳጅ ሥራ ሁሉ ላይ የበላይ ተመልካች አደረገው። 29  በዚህ ጊዜ ኢዮርብዓም ከኢየሩሳሌም ወጣ፤ ሴሎናዊው ነቢዩ አኪያህም መንገድ ላይ አገኘው። አኪያህ አዲስ ልብስ ለብሶ ነበር፤ በሜዳውም ላይ ሁለቱ ብቻቸውን ነበሩ። 30  አኪያህም ለብሶት የነበረውን አዲስ ልብስ ይዞ 12 ቦታ ቀደደው። 31  ከዚያም ኢዮርብዓምን እንዲህ አለው፦ “አሥሩን ቁራጭ ለራስህ ውሰድ፤ ምክንያቱም የእስራኤል አምላክ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ ‘እንግዲህ መንግሥቱን ከሰለሞን እጅ እቀደዋለሁ፤ ለአንተም አሥር ነገዶችን እሰጥሃለሁ። 32  ሆኖም ስለ አገልጋዬ ስለ ዳዊትና ከእስራኤል ነገዶች ሁሉ መካከል ስለመረጥኳት ከተማ ስለ ኢየሩሳሌም ስል አንዱ ነገድ የእሱ እንደሆነ ይቀጥላል። 33  ይህን የማደርገው እኔን ትተው ለሲዶናውያን እንስት አምላክ ለአስታሮት፣ ለሞዓብ አምላክ ለከሞሽና ለአሞናውያን አምላክ ለሚልኮም ስለሰገዱ ነው፤ አባቱ ዳዊት እንዳደረገው በፊቴ ትክክል የሆነውን ነገር በማድረግ እንዲሁም ደንቦቼንና ድንጋጌዎቼን በመጠበቅ በመንገዴ አልሄዱም። 34  ሆኖም ትእዛዛቴንና ደንቦቼን ስለጠበቀው ስለመረጥኩት አገልጋዬ ስለ ዳዊት ስል መንግሥቱን በሙሉ ከእጁ አልወስድም፤ ደግሞም በሕይወት ዘመኑ ሁሉ አለቃ አደርገዋለሁ። 35  ይሁን እንጂ መንግሥቱን ይኸውም አሥሩን ነገድ ከልጁ እጅ ወስጄ ለአንተ እሰጥሃለሁ። 36  አገልጋዬ ዳዊት ስሜ እንዲኖርባት ለራሴ በመረጥኳት ከተማ በኢየሩሳሌም ዘወትር በፊቴ መብራት እንዲኖረው ለልጁ አንድ ነገድ እሰጠዋለሁ። 37  እኔም እወስድሃለሁ፤ አንተም በተመኘኸው ሁሉ ላይ ትገዛለህ፤ በእስራኤልም ላይ ንጉሥ ትሆናለህ። 38  አገልጋዬ ዳዊት እንዳደረገው ያዘዝኩህን ሁሉ ብትፈጽም እንዲሁም ደንቦቼንና ትእዛዛቴን በመጠበቅ በመንገዶቼ ብትሄድና በፊቴ ትክክል የሆነውን ነገር ብታደርግ እኔም ከአንተ ጋር እሆናለሁ። ለዳዊት እንዳደረግኩለት ሁሉ ለአንተም ጸንቶ የሚኖር ቤት እሠራልሃለሁ፤ እስራኤልንም እሰጥሃለሁ። 39  በዚህም የተነሳ የዳዊትን ዘር አዋርዳለሁ፤ ይህን የማደርገው ግን ለሁልጊዜ አይደለም።’” 40  በመሆኑም ሰለሞን ኢዮርብዓምን ሊገድለው ሞከረ፤ ሆኖም ኢዮርብዓም ተነስቶ ወደ ግብፅ፣ ወደ ንጉሥ ሺሻቅ ሸሸ፤ ሰለሞን እስኪሞትም ድረስ በግብፅ ተቀመጠ። 41  የቀረው የሰለሞን ታሪክ፣ ያደረጋቸው ነገሮች ሁሉና ጥበቡ በሰለሞን የታሪክ መጽሐፍ ውስጥ ተጽፈው ይገኙ የለም? 42  ሰለሞን በኢየሩሳሌም ሆኖ በመላው እስራኤል ላይ የገዛበት የጊዜ ርዝመት 40 ዓመት ነበር። 43  ከዚያም ሰለሞን ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ በአባቱ በዳዊት ከተማ ተቀበረ፤ በእሱም ምትክ ልጁ ሮብዓም ነገሠ።
[]
[]
[]
[]
26
12  ሮብዓም እስራኤላውያን በሙሉ ሊያነግሡት ወደ ሴኬም መጥተው ስለነበር እሱም ወደ ሴኬም ሄደ። 2  የናባጥ ልጅ ኢዮርብዓም ይህን እንደሰማ (ምክንያቱም ኢዮርብዓም ከንጉሥ ሰለሞን ሸሽቶ በግብፅ ይኖር ስለነበር በወቅቱ በዚያ ይገኝ ነበር)፣ 3  ልከው አስጠሩት። ከዚያም ኢዮርብዓምና መላው የእስራኤል ጉባኤ መጥተው ሮብዓምን እንዲህ አሉት፦ 4  “አባትህ ቀንበራችንን አክብዶብን ነበር። አንተ ግን አባትህ የሰጠንን አስቸጋሪ ሥራና በላያችን የጫነብንን ከባድ ቀንበር የምታቀልልን ከሆነ እናገለግልሃለን።” 5  በዚህ ጊዜ “እንግዲያው ሂዱና ከሦስት ቀን በኋላ ተመልሳችሁ ኑ” አላቸው። በመሆኑም ሕዝቡ ሄደ። 6  ከዚያም ንጉሥ ሮብዓም አባቱ ሰለሞን በሕይወት በነበረበት ጊዜ ሲያገለግሉት የነበሩትን ሽማግሌዎች “ለዚህ ሕዝብ ምን ምላሽ እንድሰጥ ትመክሩኛላችሁ?” በማለት ምክር ጠየቀ። 7  እነሱም “ዛሬ አንተ የዚህ ሕዝብ አገልጋይ ብትሆንና የጠየቁህን ብትፈጽምላቸው እንዲሁም መልካም ምላሽ ብትሰጣቸው ምንጊዜም አገልጋዮችህ ይሆናሉ” በማለት መለሱለት። 8  ሆኖም ሮብዓም ሽማግሌዎቹ የሰጡትን ምክር ትቶ አብሮ አደጎቹ ከነበሩትና አሁን የእሱ አገልጋዮች ከሆኑት ወጣቶች ጋር ተማከረ። 9  እሱም እንዲህ ሲል ጠየቃቸው፦ “‘አባትህ የጫነብንን ቀንበር አቅልልልን’ ለሚለኝ ለዚህ ሕዝብ ምን ምላሽ እንድንሰጥ ትመክሩኛላችሁ?” 10  አብሮ አደጎቹ የሆኑት ወጣቶችም እንዲህ አሉት፦ “‘አባትህ ቀንበራችንን አክብዶብን ነበር፤ አንተ ግን ቀንበራችንን አቅልልልን’ ለሚልህ ለዚህ ሕዝብ እንዲህ በለው፦ ‘ትንሿ ጣቴ ከአባቴ ወገብ ትወፍራለች። 11  አባቴ ከባድ ቀንበር ጭኖባችሁ ነበር፤ እኔ ግን ቀንበራችሁን የባሰ አከብደዋለሁ። አባቴ በአለንጋ ገርፏችሁ ነበር፤ እኔ ግን በእሾህ አለንጋ እገርፋችኋለሁ።’” 12  ኢዮርብዓምና መላው ሕዝብ ንጉሡ “በሦስተኛው ቀን ተመልሳችሁ ኑ” ባላቸው መሠረት በሦስተኛው ቀን ወደ ሮብዓም መጡ። 13  ንጉሡ ግን ሽማግሌዎቹ የሰጡትን ምክር ትቶ ለሕዝቡ መጥፎ ምላሽ ሰጠ። 14  ወጣቶቹም በሰጡት ምክር መሠረት “አባቴ ቀንበራችሁን አክብዶባችሁ ነበር፤ እኔ ግን ቀንበራችሁን የባሰ አከብደዋለሁ። አባቴ በአለንጋ ገርፏችሁ ነበር፤ እኔ ግን በእሾህ አለንጋ እገርፋችኋለሁ” አላቸው። 15  በመሆኑም ንጉሡ ሕዝቡን ሳይሰማ ቀረ፤ ይህም የሆነው ይሖዋ በሴሎናዊው በአኪያህ አማካኝነት ለናባጥ ልጅ ለኢዮርብዓም የተናገረው ቃል ይፈጸም ዘንድ ይሖዋ እነዚህ ነገሮች በዚህ መንገድ እንዲከናወኑ ስላደረገ ነው። 16  እስራኤላውያን ሁሉ ንጉሡ ሊሰማቸው ፈቃደኛ አለመሆኑን ሲያዩ ንጉሡን እንዲህ አሉት፦ “ከዳዊት ምን ድርሻ አለን? ከእሴይ ልጅ ምንም ርስት የለንም። እስራኤል ሆይ፣ ወደ አማልክትህ ተመለስ። ዳዊት ሆይ፣ እንግዲህ የገዛ ቤትህን ጠብቅ!” ከዚያም እስራኤላውያን ወደየቤታቸው ተመለሱ። 17  ይሁንና ሮብዓም በይሁዳ ከተሞች በሚኖሩት እስራኤላውያን ላይ መግዛቱን ቀጠለ። 18  ከዚያም ንጉሥ ሮብዓም የግዳጅ ሥራ እንዲሠሩ የተመለመሉት ሰዎች አለቃ የነበረውን አዶራምን ላከው፤ ሆኖም እስራኤላውያን በሙሉ በድንጋይ ወግረው ገደሉት። ንጉሥ ሮብዓም ግን እንደ ምንም ብሎ ሠረገላው ላይ በመውጣት ወደ ኢየሩሳሌም ሸሸ። 19  እስራኤላውያንም እስከዚህ ቀን ድረስ በዳዊት ቤት ላይ እንዳመፁ ናቸው። 20  እስራኤላውያን በሙሉ ኢዮርብዓም መመለሱን እንደሰሙ ወደ ማኅበረሰቡ ካስጠሩት በኋላ በመላው እስራኤል ላይ አነገሡት። ከይሁዳ ነገድ በስተቀር ከሕዝቡ መሃል የዳዊትን ቤት የተከተለ ማንም አልነበረም። 21  ሮብዓም ኢየሩሳሌም በደረሰ ጊዜ ከእስራኤል ቤት ጋር ተዋግተው ንግሥናውን ለሰለሞን ልጅ ለሮብዓም እንዲያስመልሱ ከመላው የይሁዳ ቤትና ከቢንያም ነገድ የተውጣጡ 180,000 የሠለጠኑ ተዋጊዎች ወዲያውኑ ሰበሰበ። 22  ከዚያም የእውነተኛው አምላክ ቃል የእውነተኛው አምላክ ሰው ወደሆነው ወደ ሸማያህ እንዲህ ሲል መጣ፦ 23  “ለይሁዳ ንጉሥ ለሰለሞን ልጅ ለሮብዓም፣ ለይሁዳ ቤት ሁሉ፣ ለቢንያምና ለቀረው ሕዝብ እንዲህ ብለህ ተናገር፦ 24  ‘ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ “ከወንድሞቻችሁ ከእስራኤላውያን ጋር ለመዋጋት አትውጡ። ይህ እንዲሆን ያደረግኩት እኔ ስለሆንኩ እያንዳንዳችሁ ወደ ቤታችሁ ተመለሱ።”’” ስለዚህ የይሖዋን ቃል ሰሙ፤ ይሖዋ እንደነገራቸውም ወደየቤታቸው ተመለሱ። 25  ከዚያም ኢዮርብዓም በኤፍሬም ተራራማ አካባቢ ሴኬምን ገንብቶ በዚያ መኖር ጀመረ። ከዚያ ወጥቶ በመሄድ ጰኑኤልን ገነባ። 26  ኢዮርብዓም በልቡ እንዲህ ሲል አሰበ፦ “እንግዲህ አሁን መንግሥቱ ወደ ዳዊት ቤት ይመለሳል። 27  ይህ ሕዝብ በኢየሩሳሌም በሚገኘው የይሖዋ ቤት መሥዋዕት ለማቅረብ ወደዚያ መውጣቱን ከቀጠለ የዚህ ሕዝብ ልብ ጌታው ወደሆነው ወደ ይሁዳ ንጉሥ ወደ ሮብዓም ይመለሳል። እኔንም ይገድለኛል፤ ወደ ይሁዳ ንጉሥ ወደ ሮብዓምም ይመለሳል።” 28  በመሆኑም ንጉሡ ከተማከረ በኋላ ሁለት የወርቅ ጥጃዎችን ሠርቶ ሕዝቡን “ወደ ኢየሩሳሌም መውጣት መንገላታት ይሆንባችኋል። እስራኤል ሆይ፣ ከግብፅ ምድር ያወጣህ አምላክህ ይኸውልህ” አለ። 29  ከዚያም አንደኛውን በቤቴል ሌላኛውን ደግሞ በዳን አቆመው። 30  ይህም ለኃጢአት ዳረጋቸው፤ ሕዝቡም በዳን የሚገኘውን ጥጃ ለማምለክ እስከዚያ ድረስ ይሄድ ነበር። 31  እሱም በኮረብቶቹ ላይ የአምልኮ ቤቶችን ሠራ፤ ከሕዝቡም መካከል ሌዋውያን ያልሆኑ ሰዎችን ካህናት አድርጎ ሾመ። 32  በተጨማሪም ኢዮርብዓም በስምንተኛው ወር ከወሩም በ15ኛው ቀን በይሁዳ ይከበር የነበረው ዓይነት በዓል እንዲቋቋም አደረገ። ለሠራቸውም ጥጆች በቤቴል በሠራው መሠዊያ ላይ መሥዋዕት አቀረበ፤ በቤቴል ለሠራቸው ከፍ ያሉ የማምለኪያ ቦታዎችም ካህናት መደበ። 33  በቤቴል በሠራው መሠዊያም ላይ ራሱ በመረጠው ወር ይኸውም በስምንተኛው ወር በ15ኛው ቀን መባዎችን ማቅረብ ጀመረ፤ ለእስራኤል ሰዎችም በዓል አቋቋመ፤ እንዲሁም መባዎችንና የሚጨሱ መሥዋዕቶችን ለማቅረብ ወደ መሠዊያው ወጣ።
[]
[]
[]
[]
27
13  ኢዮርብዓም በመሠዊያው አጠገብ የሚጨስ መሥዋዕት ለማቅረብ ቆሞ ሳለ አንድ የአምላክ ሰው በይሖዋ ቃል በታዘዘው መሠረት ከይሁዳ ወደ ቤቴል መጣ። 2  ከዚያም በይሖዋ ቃል በታዘዘው መሠረት መሠዊያውን በመቃወም እንዲህ ሲል ተጣራ፦ “መሠዊያ ሆይ! መሠዊያ ሆይ! ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ ‘እነሆ፣ ኢዮስያስ የተባለ ልጅ ለዳዊት ቤት ይወለዳል! እሱም በአንተ ላይ የሚጨስ መሥዋዕት እያቀረቡ ያሉትን ከፍ ያሉ የማምለኪያ ቦታዎች ካህናት በላይህ ይሠዋቸዋል፤ በአንተም ላይ የሰዎችን አጥንት ያቃጥላል።’” 3  እሱም በዚያ ቀን እንዲህ በማለት ምልክት ሰጠ፦ “ይሖዋ የሰጠው ምልክት ይህ ነው፦ እነሆ፣ መሠዊያው ይሰነጠቃል፤ በላዩም ላይ ያለው አመድ ይፈስሳል።” 4  ንጉሡ ኢዮርብዓምም የእውነተኛው አምላክ ሰው በቤቴል የሚገኘውን መሠዊያ በመቃወም የተናገረውን ቃል ሲሰማ እጁን ከመሠዊያው ላይ አንስቶ በመዘርጋት “ያዙት!” አላቸው። ወዲያውኑም ወደ እሱ የዘረጋው እጁ ደረቀ፤ እጁንም ሊያጥፈው አልቻለም። 5  ከዚያም የእውነተኛው አምላክ ሰው በይሖዋ ቃል ታዞ በሰጠው ምልክት መሠረት መሠዊያው ተሰነጠቀ፤ አመዱም ከመሠዊያው ላይ ፈሰሰ። 6  በዚህ ጊዜ ንጉሡ የእውነተኛውን አምላክ ሰው “እባክህ፣ የአምላክህን የይሖዋን ሞገስ እንዳገኝ ለምንልኝ፤ እጄም ወደ ቦታው እንዲመለስ ጸልይልኝ” አለው። በዚህ ጊዜ የእውነተኛው አምላክ ሰው የይሖዋን ሞገስ እንዲያገኝ ለመነለት፤ የንጉሡም እጅ ተመልሶ እንደቀድሞው ሆነ። 7  ከዚያም ንጉሡ የእውነተኛውን አምላክ ሰው “አብረኸኝ ወደ ቤት ሂድና ምግብ ብላ፤ ስጦታም ልስጥህ” አለው። 8  ሆኖም የእውነተኛው አምላክ ሰው ንጉሡን እንዲህ አለው፦ “የቤትህን ግማሽ ብትሰጠኝ እንኳ ከአንተ ጋር አልሄድም፤ በዚህም ቦታ ምግብ አልበላም፤ ውኃም አልጠጣም። 9  ምክንያቱም የይሖዋ ቃል ‘ምግብ እንዳትበላ፤ ውኃም እንዳትጠጣ፤ በሄድክበትም መንገድ እንዳትመለስ’ ሲል አዞኛል።” 10  በመሆኑም በሌላ መንገድ ሄደ፤ ወደ ቤቴል በመጣበትም መንገድ አልተመለሰም። 11  በዚህ ጊዜ በቤቴል የሚኖር አንድ አረጋዊ ነቢይ ነበር፤ ልጆቹም ወደ ቤት መጥተው የእውነተኛው አምላክ ሰው በዚያ ቀን በቤቴል ያደረገውን ነገር ሁሉና ለንጉሡ የተናገረውን ቃል ነገሩት። ይህን ለአባታቸው ከተረኩለት በኋላ 12  አባታቸው “ለመሆኑ የሄደው በየት በኩል ነው?” ሲል ጠየቃቸው። ልጆቹም ከይሁዳ የመጣው የእውነተኛው አምላክ ሰው የሄደበትን መንገድ አሳዩት። 13  እሱም ልጆቹን “በሉ አህያውን ጫኑልኝ” አላቸው። እነሱም አህያውን ጫኑለት፤ እሱም አህያው ላይ ተቀመጠ። 14  ከዚያም የእውነተኛውን አምላክ ሰው ተከተለው፤ በአንድ ትልቅ ዛፍ ሥር ተቀምጦም አገኘው። እሱም “ከይሁዳ የመጣኸው የእውነተኛው አምላክ ሰው አንተ ነህ?” አለው፤ እሱም “አዎ፣ እኔ ነኝ” ሲል መለሰለት። 15  ከዚያም “አብረን ወደ ቤት እንሂድና ምግብ ብላ” አለው። 16  እሱ ግን እንዲህ አለው፦ “ከአንተ ጋር ተመልሼ ልሄድ ወይም ያቀረብክልኝን ግብዣ ልቀበል አልችልም፤ ደግሞም በዚህ ቦታ ከአንተ ጋር ምግብም ሆነ ውኃ አልቀምስም። 17  ምክንያቱም የይሖዋ ቃል ‘እዚያ ምግብ እንዳትበላ፤ ውኃም እንዳትጠጣ። በመጣህበትም መንገድ እንዳትመለስ’ በማለት አዞኛል።” 18  በዚህ ጊዜ አረጋዊው ሰው “እኔም እኮ እንደ አንተው ነቢይ ነኝ፤ አንድ መልአክ ‘ምግብ እንዲበላና ውኃ እንዲጠጣ መልሰህ ወደ ቤትህ አምጣው’ በማለት የይሖዋን ቃል ነግሮኛል” አለው። (እሱም አታለለው።) 19  በመሆኑም እሱ ቤት ምግብ ለመብላትና ውኃ ለመጠጣት አብሮት ተመለሰ። 20  እነሱም በማዕድ ተቀምጠው ሳሉ የይሖዋ ቃል የእውነተኛውን አምላክ ሰው መልሶ ወዳመጣው ነቢይ መጣ፤ 21  ከዚያም ከይሁዳ የመጣውን የእውነተኛውን አምላክ ሰው ጠርቶ እንዲህ አለው፦ “ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ ‘በይሖዋ መመሪያ ላይ ስላመፅክና አምላክህ ይሖዋ የሰጠህን ትእዛዝ ስላልጠበቅክ፣ 22  ከዚህ ይልቅ ምግብ ለመብላትና ውኃ ለመጠጣት ስትል “ምግብ እንዳትበላ፤ ውኃም እንዳትጠጣ” ወደተባልክበት ቦታ ስለተመለስክ ሬሳህ በአባቶችህ የመቃብር ቦታ አይቀበርም።’” 23  የእውነተኛው አምላክ ሰውም ከበላና ከጠጣ በኋላ አረጋዊው ነቢይ ከመንገድ መልሶ ላመጣው ለዚያ ነቢይ አህያውን ጫነለት። 24  ከዚያም መንገዱን ቀጠለ፤ ሆኖም አንድ አንበሳ መንገድ ላይ አግኝቶ ገደለው። ሬሳውም መንገዱ ላይ ተጋድሞ፣ አህያው ደግሞ አጠገቡ ቆሞ ነበር፤ አንበሳውም ሬሳው አጠገብ ቆሞ ነበር። 25  በዚያ የሚያልፉ ሰዎችም ሬሳው መንገድ ላይ ተጋድሞ፣ አንበሳው ደግሞ አጠገቡ ቆሞ አዩ። ከዚያም መጥተው ይህን ነገር አረጋዊው ነቢይ በሚኖርበት ከተማ አወሩ። 26  ከመንገድ መልሶ ያመጣውም ነቢይ ይህን ሲሰማ ወዲያውኑ “ይህ ሰው በይሖዋ መመሪያ ላይ ያመፀው የእውነተኛው አምላክ ሰው ነው፤ ይሖዋ በነገረው ቃል መሠረት እንዲቦጫጭቀውና እንዲገድለው ይሖዋ ለአንበሳ አሳልፎ ሰጥቶታል” አለ። 27  እሱም ልጆቹን “በሉ አህያውን ጫኑልኝ” አላቸው። እነሱም ጫኑለት። 28  ከዚያም ሄደ፤ ሬሳው መንገድ ላይ ተጋድሞ፣ አህያውና አንበሳውም አጠገቡ ቆመው አገኛቸው። አንበሳው ሬሳውን አልበላውም፤ አህያውንም ቢሆን አልቦጫጨቀውም። 29  ነቢዩም የእውነተኛውን አምላክ ሰው ሬሳ አንስቶ አህያው ላይ ከጫነ በኋላ አልቅሶ ሊቀብረው ስላሰበ ወደሚኖርበት ከተማ ይዞት ተመለሰ። 30  ከዚያም ሬሳውን በራሱ የመቃብር ቦታ ቀበረው፤ እነሱም “ወይኔ ወንድሜን!” እያሉ አለቀሱለት። 31  እሱንም ከቀበረው በኋላ ልጆቹን እንዲህ አላቸው፦ “እኔም ስሞት የእውነተኛው አምላክ ሰው በተቀበረበት የመቃብር ቦታ ቅበሩኝ። አጥንቶቼንም ከአጥንቶቹ አጠገብ ቅበሯቸው። 32  በይሖዋ ቃል በታዘዘው መሠረት በቤቴል በሚገኘው መሠዊያና በሰማርያ ከተሞች በሚገኙት ኮረብቶች ላይ ባሉት የአምልኮ ቤቶች ሁሉ ላይ የተናገረው ቃል ያለጥርጥር ይፈጸማል።” 33  ይህ ሁሉ ከሆነም በኋላ ቢሆን ኢዮርብዓም ከመጥፎ መንገዱ አልተመለሰም፤ ከዚህ ይልቅ ከፍ ላሉት የማምለኪያ ቦታዎች ከሕዝቡ መካከል ካህናት መሾሙን ቀጠለ። እንዲሁም ካህን ለመሆን የሚፈልግን ማንኛውንም ሰው “ከፍ ላሉት የማምለኪያ ቦታዎች ካህን ይሁን” በማለት ይሾመው ነበር። 34  ይህም ኃጢአት የኢዮርብዓም ቤት ከምድር ገጽ እንዲጠፋና እንዲደመሰስ ምክንያት ሆነ።
[]
[]
[]
[]
28
14  በዚህ ጊዜ የኢዮርብዓም ልጅ አቢያህ ታመመ። 2  በመሆኑም ኢዮርብዓም ሚስቱን እንዲህ አላት፦ “እባክሽ፣ ተነሺና የኢዮርብዓም ሚስት መሆንሽን እንዳያውቁ ራስሽን ለውጠሽ ወደ ሴሎ ሂጂ። ነቢዩ አኪያህ ያለው እዚያ ነው። እኔ በዚህ ሕዝብ ላይ ንጉሥ እንደምሆን የተናገረው እሱ ነው። 3  አሥር ዳቦና የተቀቡ ቂጣዎች እንዲሁም አንድ ገንቦ ማር ይዘሽ ወደ እሱ ሂጂ። እሱም በልጁ ላይ የሚደርሰውን ነገር ይነግርሻል።” 4  የኢዮርብዓምም ሚስት እንዳላት አደረገች። ተነስታ ወደ ሴሎ በመሄድ ወደ አኪያህ ቤት መጣች። አኪያህ ከማርጀቱ የተነሳ ማየት ተስኖት የነበረ ቢሆንም ዓይኖቹ ፊት ለፊት ትኩር ብለው ይመለከቱ ነበር። 5  ይሖዋ ግን አኪያህን እንዲህ አለው፦ “የኢዮርብዓም ሚስት ልጇ ስለታመመ ስለ እሱ ልትጠይቅህ እየመጣች ነው። እኔም ምን እንደምትላት እነግርሃለሁ። እሷም እዚህ ስትደርስ ማንነቷ እንዳይታወቅ ራሷን ትለውጣለች።” 6  አኪያህም በሩ ጋ ስትደርስ የእግሯን ኮቴ ሰምቶ እንዲህ አላት፦ “የኢዮርብዓም ሚስት ግቢ። ማንነትሽ እንዳይታወቅ ራስሽን የለወጥሽው ለምንድን ነው? መጥፎ ዜና እንድነግርሽ ታዝዣለሁ። 7  ሂጂና ኢዮርብዓምን እንዲህ በዪው፦ ‘የእስራኤል አምላክ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ “በሕዝቤ በእስራኤል ላይ መሪ እንድትሆን ከሕዝብህ መካከል አስነሳሁህ። 8  ከዚያም መንግሥቱን ከዳዊት ቤት ላይ ቀድጄ ለአንተ ሰጠሁህ። አንተ ግን በፊቴ ትክክል የሆነውን ነገር ብቻ በማድረግ ትእዛዛቴን እንደጠበቀውና በሙሉ ልቡ እንደተከተለኝ እንደ አገልጋዬ እንደ ዳዊት አልሆንክም። 9  ከዚህ ይልቅ ከአንተ በፊት ከነበሩት ሁሉ የከፋ ድርጊት ፈጸምክ፤ እኔንም ለማስቆጣት ለራስህ ሌላ አምላክና ከብረት የተሠሩ ምስሎችን ሠራህ፤ ጀርባህንም ሰጠኸኝ። 10  በዚህም የተነሳ በኢዮርብዓም ቤት ላይ ጥፋት አመጣለሁ፤ በእስራኤል ውስጥ የሚገኘውን ምስኪኑንና ደካማውን ጨምሮ የኢዮርብዓም የሆነውን ወንድ ሁሉ ጠራርጌ አጠፋለሁ፤ አንድ ሰው ፋንድያን ሙልጭ አድርጎ በመጥረግ እንደሚያስወግድ ሁሉ እኔም የኢዮርብዓምን ቤት ሙልጭ አድርጌ እጠርጋለሁ! 11  ከኢዮርብዓም ወገን የሆነውን በከተማ ውስጥ የሚሞተውን ሁሉ ውሾች ይበሉታል፤ በሜዳ ላይ የሚሞተውን ደግሞ የሰማይ አሞሮች ይበሉታል፤ ይሖዋ ይህን ተናግሯልና።”’ 12  “እንግዲህ አሁን ተነስተሽ ወደ ቤትሽ ሂጂ። እግርሽ ከተማዋን እንደረገጠ ልጁ ይሞታል። 13  ከኢዮርብዓም ቤተሰብ መካከል በመቃብር ቦታ የሚቀበረው እሱ ብቻ ስለሆነ እስራኤል ሁሉ አልቅሰው ይቀብሩታል፤ ምክንያቱም የእስራኤል አምላክ ይሖዋ ከኢዮርብዓም ቤት ሁሉ አንድ መልካም ነገር ያገኘበት እሱን ብቻ ነው። 14  ይሖዋም ከዚያን ቀን ጀምሮ እንዲያውም አሁኑኑ፣ የኢዮርብዓምን ቤት የሚያስወግድ በእስራኤል ላይ የሚነግሥ ንጉሥ ለራሱ ያስነሳል። 15  ይሖዋ በውኃ ውስጥ እንደሚወዛወዝ ሸምበቆ እስራኤልን ይመታል፤ እንዲሁም እስራኤላውያንን ለአባቶቻቸው ከሰጣቸው ከዚህ መልካም ምድር ላይ ይነቅላቸዋል፤ ከወንዙም ማዶ ይበትናቸዋል፤ ምክንያቱም የማምለኪያ ግንዶችን ለራሳቸው በማቆም ይሖዋን አስቆጥተውታል። 16  እሱም ኢዮርብዓም በሠራው ኃጢአትና እስራኤላውያን እንዲሠሩ ባደረገው ኃጢአት የተነሳ እስራኤልን ይተዋል።” 17  በዚህ ጊዜ የኢዮርብዓም ሚስት ተነስታ በመሄድ ወደ ቲርጻ መጣች። ቤቱ ደጃፍ ላይ ስትደርስም ልጁ ሞተ። 18  ይሖዋ በአገልጋዩ በነቢዩ አኪያህ አማካኝነት በተናገረውም መሠረት ቀበሩት፤ እስራኤልም ሁሉ አለቀሰለት። 19  ኢዮርብዓም ስላደረገው ውጊያና ስለ አገዛዙ የሚናገረው የቀረው ታሪኩ በእስራኤል ነገሥታት ዘመን ስለተፈጸሙት ነገሮች በሚተርከው የታሪክ መጽሐፍ ውስጥ ተጽፏል። 20  ኢዮርብዓም የገዛበት የጊዜ ርዝመት 22 ዓመት ነበር፤ ከዚያም ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ በእሱም ምትክ ልጁ ናዳብ ነገሠ። 21  ይህ በእንዲህ እንዳለ የሰለሞን ልጅ ሮብዓም በይሁዳ ላይ ነግሦ ነበር። ሮብዓም በነገሠ ጊዜ ዕድሜው 41 ዓመት ነበር፤ እሱም ይሖዋ ስሙ እንዲኖርባት ከእስራኤል ነገዶች ሁሉ መካከል በመረጣት ከተማ በኢየሩሳሌም ሆኖ ለ17 ዓመት ገዛ። እናቱም ናዕማ የተባለች አሞናዊት ነበረች። 22  ይሁዳም በይሖዋ ፊት መጥፎ የሆነውን ነገር አደረገ፤ እነሱም በፈጸሙት ኃጢአት የተነሳ ከአባቶቻቸው ይበልጥ አስቆጡት። 23  እነሱም ቢሆኑ በእያንዳንዱ ኮረብታ ላይና በእያንዳንዱ የለመለመ ዛፍ ሥር ከፍ ያሉ የማምለኪያ ቦታዎችን፣ የማምለኪያ ዓምዶችንና የማምለኪያ ግንዶችን ለራሳቸው ሠሩ። 24  ሌላው ቀርቶ በምድሪቱ ላይ የቤተ መቅደስ ቀላጮች ነበሩ። ይሖዋ ከእስራኤላውያን ፊት አባሮ ያስወጣቸው ብሔራት ይፈጽሟቸው የነበሩትን አስጸያፊ ነገሮች በሙሉ አደረጉ። 25  ንጉሥ ሮብዓም በነገሠ በአምስተኛው ዓመት የግብፁ ንጉሥ ሺሻቅ ኢየሩሳሌምን ለመውጋት መጣ። 26  እሱም በይሖዋ ቤት የነበሩትን ውድ ንብረቶችና በንጉሡ ቤት የነበሩትን ውድ ንብረቶች ወሰደ። ሰለሞን የሠራቸውን የወርቅ ጋሻዎች ጨምሮ ሁሉንም ነገር ወሰደ። 27  በመሆኑም ንጉሥ ሮብዓም በእነሱ ምትክ የመዳብ ጋሻዎችን ሠርቶ የንጉሡን ቤት በር ለሚጠብቁት የዘብ አለቆች ሰጣቸው። 28  ዘቦቹም ንጉሡ ወደ ይሖዋ ቤት በመጣ ቁጥር ጋሻዎቹን ያነግቡ ነበር፤ ከዚያም ወደ ዘቦቹ ክፍል ይመልሷቸው ነበር። 29  የቀረው የሮብዓም ታሪክና ያደረጋቸው ነገሮች በሙሉ በይሁዳ ነገሥታት ዘመን ስለተፈጸሙት ነገሮች በሚተርከው የታሪክ መጽሐፍ ውስጥ ተጽፈው ይገኙ የለም? 30  በሮብዓምና በኢዮርብዓም መካከል የማያቋርጥ ጦርነት ነበር። 31  በመጨረሻም ሮብዓም ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ በዳዊት ከተማም ከአባቶቹ ጋር ተቀበረ። እናቱ ናዕማ የተባለች አሞናዊት ነበረች። በእሱም ምትክ ልጁ አብያም ነገሠ።
[]
[]
[]
[]
29
15  የናባጥ ልጅ ንጉሥ ኢዮርብዓም በነገሠ በ18ኛው ዓመት አብያም በይሁዳ ላይ ነገሠ። 2  እሱም በኢየሩሳሌም ለሦስት ዓመት ገዛ። የእናቱ ስም ማአካ ሲሆን እሷም የአቢሴሎም የልጅ ልጅ ነበረች። 3  እሱም አባቱ ከእሱ በፊት በሠራው ኃጢአት ሁሉ መመላለሱን ቀጠለ፤ ልቡ እንደቀድሞ አባቱ እንደ ዳዊት ልብ በአምላኩ በይሖዋ ዘንድ ሙሉ አልነበረም። 4  ሆኖም በዳዊት የተነሳ አምላኩ ይሖዋ ከእሱ በኋላ ልጁን በማስነሳትና ኢየሩሳሌም ጸንታ እንድትኖር በማድረግ በኢየሩሳሌም መብራት ሰጠው። 5  ምክንያቱም ዳዊት በይሖዋ ፊት ትክክል የሆነውን ነገር አድርጓል፤ እንዲሁም ከሂታዊው ከኦርዮ ጋር በተያያዘ ከፈጸመው ነገር በስተቀር በሕይወት ዘመኑ ሁሉ እሱ ከሰጠው ከየትኛውም ትእዛዝ ፈቀቅ አላለም። 6  በሕይወት ዘመኑ ሁሉ በሮብዓምና በኢዮርብዓም መካከል ጦርነት ነበር። 7  የቀረው የአብያም ታሪክ፣ ያደረጋቸው ነገሮች በሙሉ በይሁዳ ነገሥታት ዘመን ስለተፈጸሙት ነገሮች በሚተርከው የታሪክ መጽሐፍ ውስጥ ተጽፈው ይገኙ የለም? በአብያምና በኢዮርብዓም መካከልም ጦርነት ነበር። 8  በመጨረሻም አብያም ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ በዳዊት ከተማም ቀበሩት፤ በእሱም ምትክ ልጁ አሳ ነገሠ። 9  የእስራኤል ንጉሥ ኢዮርብዓም በነገሠ በ20ኛው ዓመት አሳ በይሁዳ ላይ መግዛት ጀመረ። 10  እሱም በኢየሩሳሌም ለ41 ዓመት ገዛ። የአያቱም ስም ማአካ ሲሆን እሷም የአቢሴሎም የልጅ ልጅ ነበረች። 11  አሳ እንደ አባቱ እንደ ዳዊት በይሖዋ ፊት ትክክል የሆነውን ነገር አደረገ። 12  እሱም የቤተ መቅደስ ቀላጮችን ከምድሪቱ አባረረ፤ እንዲሁም አባቶቹ የሠሯቸውን አስጸያፊ ጣዖቶች በሙሉ አስወገደ። 13  ሌላው ቀርቶ አያቱ ማአካ ለማምለኪያ ግንዱ አምልኮ ጸያፍ ጣዖት ሠርታ ስለነበር ከእመቤትነቷ ሻራት። አሳ፣ አያቱ የሠራችውን ጸያፍ ጣዖት ቆርጦ በቄድሮን ሸለቆ አቃጠለው። 14  ከፍ ያሉት የማምለኪያ ቦታዎች ግን አልተወገዱም ነበር። ያም ሆኖ አሳ በሕይወት ዘመኑ ሁሉ ልቡ በይሖዋ ዘንድ ሙሉ ነበር። 15  እሱና አባቱ የቀደሷቸውን ነገሮች ይኸውም ብሩን፣ ወርቁንና ልዩ ልዩ ዕቃዎችን ወደ ይሖዋ ቤት አስገባ። 16  በአሳና የእስራኤል ንጉሥ በሆነው በባኦስ መካከል የማያቋርጥ ጦርነት ነበር። 17  በመሆኑም የእስራኤል ንጉሥ ባኦስ በይሁዳ ላይ ዘመተ፤ እሱም ማንም ወደ ይሁዳ ንጉሥ ወደ አሳ እንዳይገባና እንዳይወጣ ለማድረግ ራማን መገንባት ጀመረ። 18  በዚህ ጊዜ አሳ በይሖዋ ቤት ግምጃ ቤትና በንጉሡ ቤት ግምጃ ቤት የቀረውን ብርና ወርቅ ሁሉ አውጥቶ ለአገልጋዮቹ ሰጣቸው። ከዚያም ንጉሥ አሳ እነዚህን አገልጋዮቹን በደማስቆ ወደሚገኘው የሶርያ ንጉሥ ማለትም የሄዝዮን ልጅ፣ የታብሪሞን ልጅ ወደሆነው ወደ ቤንሃዳድ እንዲህ ሲል ላካቸው፦ 19  “በእኔና በአንተ እንዲሁም በአባቴና በአባትህ መካከል ውል አለ። እኔ የብርና የወርቅ ስጦታ ልኬልሃለሁ። ስለዚህ ና፣ የእስራኤል ንጉሥ ባኦስ ከእኔ እንዲርቅ ከእሱ ጋር የገባኸውን ውል አፍርስ።” 20  ቤንሃዳድ የንጉሥ አሳን ሐሳብ ተቀብሎ የጦር ሠራዊቱን አለቆች በእስራኤል ከተሞች ላይ አዘመተ፤ እነሱም ኢዮንን፣ ዳንን፣ አቤልቤትማዓካን እንዲሁም ኪኔሬትን ሁሉና መላውን የንፍታሌም ምድር መቱ። 21  ባኦስም ይህን ሲሰማ ወዲያውኑ ራማን መገንባቱን አቁሞ በቲርጻ መኖሩን ቀጠለ። 22  ከዚያም ንጉሥ አሳ ማንንም ሳያስቀር የይሁዳን ሰዎች ሁሉ ሰበሰበ፤ እነሱም ባኦስ እየገነባባቸው የነበሩትን የራማን ድንጋዮችና ሳንቃዎች አጋዙ፤ ንጉሥ አሳም በድንጋዮቹና በሳንቃዎቹ በቢንያም የምትገኘውን ጌባንና ምጽጳን ገነባ። 23  የቀረው የአሳ ታሪክ ሁሉ፣ ኃያልነቱ ሁሉ፣ ያደረጋቸው ነገሮች በሙሉና የገነባቸው ከተሞች በይሁዳ ነገሥታት ዘመን ስለተፈጸሙት ነገሮች በሚተርከው የታሪክ መጽሐፍ ውስጥ ተጽፈው ይገኙ የለም? ሆኖም አሳ ባረጀ ጊዜ በእግር ሕመም ይሠቃይ ነበር። 24  በመጨረሻም አሳ ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ በአባቱ በዳዊት ከተማም ከእነሱ ጋር ተቀበረ፤ በእሱም ምትክ ልጁ ኢዮሳፍጥ ነገሠ። 25  የይሁዳ ንጉሥ አሳ በነገሠ በሁለተኛው ዓመት የኢዮርብዓም ልጅ ናዳብ የእስራኤል ንጉሥ ሆነ፤ እሱም በእስራኤል ላይ ለሁለት ዓመት ገዛ። 26  በይሖዋም ፊት መጥፎ የሆነውን ነገር ማድረጉን ገፋበት፤ የአባቱንም መንገድ ተከተለ፤ እንዲሁም አባቱ እስራኤላውያን እንዲፈጽሙ ባደረገው ኃጢአት ተመላለሰ። 27  ከይሳኮር ቤት የሆነው የአኪያህ ልጅ ባኦስ በእሱ ላይ አሴረ፤ ናዳብና እስራኤል ሁሉ የፍልስጤማውያን ከተማ የሆነችውን ጊበቶንን ከበው ሳሉ ባኦስ ጊበቶን ላይ ናዳብን ገደለው። 28  በመሆኑም ባኦስ የይሁዳ ንጉሥ አሳ በነገሠ በሦስተኛው ዓመት ናዳብን ገድሎ በምትኩ ነገሠ። 29  እሱም እንደነገሠ ወዲያውኑ የኢዮርብዓምን ቤት ሁሉ ፈጀ። ከኢዮርብዓም ቤት እስትንፋስ ያለውን አንድም ሰው አላስቀረም፤ ይሖዋ በአገልጋዩ በሴሎናዊው በአኪያህ በኩል በተናገረው መሠረት ሁሉንም ደመሰሳቸው። 30  ይህም የሆነው ኢዮርብዓም በፈጸመው ኃጢአትና እስራኤላውያን እንዲፈጽሙ ባደረገው ኃጢአት የእስራኤልን አምላክ ይሖዋን ክፉኛ ስላስቆጣው ነው። 31  የቀረው የናዳብ ታሪክና ያደረጋቸው ነገሮች በሙሉ በእስራኤል ነገሥታት ዘመን ስለተፈጸሙት ነገሮች በሚተርከው የታሪክ መጽሐፍ ውስጥ ተጽፈው ይገኙ የለም? 32  በአሳና የእስራኤል ንጉሥ በሆነው በባኦስ መካከል የማያቋርጥ ጦርነት ነበር። 33  የይሁዳ ንጉሥ አሳ በነገሠ በሦስተኛው ዓመት የአኪያህ ልጅ ባኦስ በቲርጻ ሆኖ በመላው እስራኤል ላይ ለ24 ዓመት ገዛ። 34  ሆኖም በይሖዋ ፊት መጥፎ የሆነውን ነገር ማድረጉን ገፋበት፤ የኢዮርብዓምን መንገድ ተከተለ፤ እንዲሁም ኢዮርብዓም እስራኤላውያን እንዲፈጽሙ ባደረገው ኃጢአት ተመላለሰ።
[]
[]
[]
[]
30
16  ከዚያም በባኦስ ላይ የተነገረው የይሖዋ ቃል የሃናኒ ልጅ ወደሆነው ወደ ኢዩ እንዲህ ሲል መጣ፦ 2  “ከአቧራ ላይ አንስቼ በሕዝቤ በእስራኤል ላይ መሪ አደረግኩህ፤ አንተ ግን የኢዮርብዓምን መንገድ ተከተልክ፤ ሕዝቤ እስራኤልም ኃጢአት እንዲሠራ አደረግክ፤ እነሱም በኃጢአታቸው አስቆጡኝ። 3  ስለሆነም ባኦስንና ቤቱን ሙልጭ አድርጌ እጠርጋለሁ፤ ቤቱንም እንደ ናባጥ ልጅ እንደ ኢዮርብዓም ቤት አደርገዋለሁ። 4  ከባኦስ ወገን የሆነውን በከተማ ውስጥ የሚሞተውን ሁሉ ውሾች ይበሉታል፤ ከእሱ ወገን የሆነውን በሜዳ ላይ የሚሞተውን ሁሉ ደግሞ የሰማይ አሞሮች ይበሉታል።” 5  የቀረው የባኦስ ታሪክ፣ ያደረጋቸው ነገሮችና ኃያልነቱ በእስራኤል ነገሥታት ዘመን ስለተፈጸሙት ነገሮች በሚተርከው የታሪክ መጽሐፍ ውስጥ ተጽፈው ይገኙ የለም? 6  በመጨረሻም ባኦስ ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ በቲርጻም ተቀበረ፤ በእሱም ምትክ ልጁ ኤላህ ነገሠ። 7  በተጨማሪም ባኦስ ልክ እንደ ኢዮርብዓም ቤት በእጁ በሠራቸው ነገሮች ይሖዋን በማስቆጣት በፊቱ መጥፎ የሆነውን ነገር ሁሉ ስለፈጸመ እንዲሁም እሱን ስለገደለ የይሖዋ ቃል የሃናኒ ልጅ በሆነው በነቢዩ ኢዩ አማካኝነት በባኦስና በቤቱ ላይ መጣ። 8  የይሁዳ ንጉሥ አሳ በነገሠ በ26ኛው ዓመት የባኦስ ልጅ ኤላህ በቲርጻ ሆኖ በእስራኤል ላይ ነገሠ፤ ለሁለት ዓመትም ገዛ። 9  የግማሹ የሠረገላ ሠራዊት አለቃ የሆነው አገልጋዩ ዚምሪ በእሱ ላይ አሴረ፤ በዚህ ጊዜ ኤላህ በቲርጻ የሚገኘው የንጉሡ ቤት ኃላፊ በነበረው በአርጻ ቤት ጠጥቶ ሰክሮ ነበር። 10  የይሁዳ ንጉሥ አሳ በነገሠ በ27ኛው ዓመት ዚምሪ ገብቶ ኤላህን መትቶ ገደለው፤ በእሱም ምትክ ነገሠ። 11  እሱም ነግሦ ገና በዙፋኑ ላይ እንደተቀመጠ የባኦስን ቤት ሁሉ መታ። ከዘመዶቹም ሆነ ከወዳጆቹ መካከል አንድም ወንድ አላስተረፈም። 12  በዚህ መንገድ ይሖዋ በነቢዩ ኢዩ አማካኝነት በባኦስ ላይ በተናገረው ቃል መሠረት ዚምሪ መላውን የባኦስን ቤት አጠፋ። 13  ይህም የሆነው ባኦስ እና ልጁ ኤላህ በፈጸሙት ኃጢአት እንዲሁም ከንቱ በሆኑት ጣዖቶቻቸው አማካኝነት የእስራኤልን አምላክ ይሖዋን በማስቆጣት እስራኤላውያን እንዲፈጽሙ ባደረጉት ኃጢአት የተነሳ ነው። 14  የቀረው የኤላህ ታሪክ፣ ያደረጋቸው ነገሮች ሁሉ በእስራኤል ነገሥታት ዘመን ስለተፈጸሙት ነገሮች በሚተርከው የታሪክ መጽሐፍ ውስጥ ተጽፈው ይገኙ የለም? 15  የይሁዳ ንጉሥ አሳ በነገሠ በ27ኛው ዓመት፣ ሠራዊቱ የፍልስጤማውያን የሆነችውን ጊበቶንን ከቦ በነበረበት ወቅት ዚምሪ በቲርጻ ለሰባት ቀን ነገሠ። 16  በኋላም ከተማዋን ከቦ የነበረው ሠራዊት “ዚምሪ ሴራ በመጠንሰስ ንጉሡን ገድሎታል” የሚል ወሬ ሰማ። በመሆኑም መላው እስራኤል የሠራዊቱ አለቃ የሆነውን ኦምሪን በዚያን ቀን በሰፈሩ ውስጥ በእስራኤል ላይ አነገሡት። 17  ኦምሪና ከእሱ ጋር የነበሩት እስራኤላውያን በሙሉ ከጊበቶን ወጥተው ቲርጻን ከበቡ። 18  ዚምሪም ከተማዋ መያዟን ሲያይ በንጉሡ ቤት ወዳለው የማይደፈር ማማ ገብቶ በውስጡ እንዳለ ቤቱን በእሳት አቃጠለው፤ በዚህም የተነሳ ሞተ። 19  ይህም የሆነው የኢዮርብዓምን መንገድ በመከተል በይሖዋ ፊት መጥፎ የሆነውን ነገር በመፈጸም በሠራው በገዛ ኃጢአቱና እስራኤላውያን እንዲሠሩ ባደረገው ኃጢአት የተነሳ ነው። 20  የቀረው የዚምሪ ታሪክና የጠነሰሰው ሴራ በእስራኤል ነገሥታት ዘመን ስለተፈጸሙት ነገሮች በሚተርከው የታሪክ መጽሐፍ ውስጥ ተጽፎ ይገኝ የለም? 21  የእስራኤል ሕዝብ በሁለት አንጃ የተከፈለው በዚህ ጊዜ ነበር። አንደኛው ወገን የጊናትን ልጅ ቲብኒን ለማንገሥ ስለፈለገ የእሱ ተከታይ ሆነ፤ ሌላኛው ወገን ደግሞ ኦምሪን ተከተለ። 22  ሆኖም ኦምሪን የተከተለው ሕዝብ የጊናትን ልጅ ቲብኒን በተከተለው ሕዝብ ላይ አየለ። በመሆኑም ቲብኒ ሞተ፤ ኦምሪም ነገሠ። 23  የይሁዳ ንጉሥ አሳ በነገሠ በ31ኛው ዓመት ኦምሪ በእስራኤል ላይ ነገሠ፤ ለ12 ዓመትም ገዛ። በቲርጻም ሆኖ ለስድስት ዓመት ገዛ። 24  እሱም የሰማርያን ተራራ ከሼሜር ላይ በሁለት ታላንት ብር ገዛ፤ በተራራውም ላይ ከተማ ገነባ። የገነባትንም ከተማ የተራራው ጌታ በሆነው በሼሜር ስም ሰማርያ ብሎ ሰየማት። 25  ኦምሪም በይሖዋ ፊት መጥፎ የሆነውን ነገር ማድረጉን ቀጠለ፤ ከእሱ በፊት ከነበሩት ሁሉ የከፋ ድርጊት ፈጸመ። 26  የናባጥ ልጅ ኢዮርብዓም በሄደበት መንገድ ሁሉ ሄደ፤ እንዲሁም ኢዮርብዓም እስራኤላውያን በከንቱ ጣዖቶቻቸው አማካኝነት የእስራኤልን አምላክ ይሖዋን እንዲያስቆጡት በማድረግ በተከተለው የኃጢአት ጎዳና ተመላለሰ። 27  የቀረው የኦምሪ ታሪክ፣ ያደረጋቸው ነገሮችና በኃያልነቱ የፈጸማቸው ጀብዱዎች በእስራኤል ነገሥታት ዘመን ስለተፈጸሙት ነገሮች በሚተርከው የታሪክ መጽሐፍ ውስጥ ተጽፈው ይገኙ የለም? 28  በመጨረሻም ኦምሪ ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ በሰማርያም ተቀበረ፤ በእሱም ምትክ ልጁ አክዓብ ነገሠ። 29  የይሁዳ ንጉሥ አሳ በነገሠ በ38ኛው ዓመት የኦምሪ ልጅ አክዓብ በእስራኤል ላይ ነገሠ፤ የኦምሪ ልጅ አክዓብ በሰማርያ ሆኖ በእስራኤል ላይ ለ22 ዓመት ገዛ። 30  የኦምሪ ልጅ አክዓብ ከእሱ በፊት የነበሩት ሁሉ ከፈጸሙት የከፋ ድርጊት በይሖዋ ፊት ፈጸመ። 31  አክዓብ የናባጥ ልጅ ኢዮርብዓም በተከተለው የኃጢአት ጎዳና መመላለሱ ሳያንሰው የሲዶናውያን ንጉሥ የኤትባዓል ልጅ የሆነችውን ኤልዛቤልን አገባ፤ እንዲሁም ባአልን ማገልገልና ለእሱ መስገድ ጀመረ። 32  እንዲሁም በሰማርያ ለባአል በሠራው ቤት ውስጥ ለባአል መሠዊያ አቆመ። 33  በተጨማሪም አክዓብ የማምለኪያ ግንድ ሠራ። እንዲሁም ከእሱ በፊት ከነበሩት የእስራኤል ነገሥታት ሁሉ ይበልጥ የእስራኤልን አምላክ ይሖዋን የሚያስቆጣ ድርጊት ፈጸመ። 34  በአክዓብ ዘመን የቤቴል ሰው የሆነው ሂኤል ኢያሪኮን መልሶ ገነባ። ይሖዋ በነዌ ልጅ በኢያሱ አማካኝነት በተናገረው ቃል መሠረት የከተማዋን መሠረት ሲጥል የበኩር ልጁ አቤሮን ሞተ፤ በሮቿን ሲያቆም ደግሞ የመጨረሻ ልጁ ሰጉብ ሞተ።
[]
[]
[]
[]
31
17  በዚህ ጊዜ ከጊልያድ ነዋሪዎች አንዱ የሆነው ቲሽባዊው ኤልያስ አክዓብን “በማገለግለውና ሕያው በሆነው በእስራኤል አምላክ በይሖዋ እምላለሁ፣ በእኔ ትእዛዝ ካልሆነ በቀር በእነዚህ ዓመታት ጠል ወይም ዝናብ አይኖርም!” አለው። 2  የይሖዋም ቃል እንዲህ ሲል ወደ እሱ መጣ፦ 3  “ከዚህ ተነስተህ ወደ ምሥራቅ አቅጣጫ ሂድ፤ ከዮርዳኖስ በስተ ምሥራቅ በሚገኘው በከሪት ሸለቆም ተደበቅ። 4  ከጅረቱ ትጠጣለህ፤ ቁራዎችም እዚያ ምግብ እንዲያመጡልህ አዛለሁ።” 5  እሱም ወዲያውኑ ሄዶ ይሖዋ እንዳዘዘው አደረገ፤ ሄዶም ከዮርዳኖስ በስተ ምሥራቅ በሚገኘው በከሪት ሸለቆ ተቀመጠ። 6  ቁራዎቹም ጠዋትና ማታ ምግብና ሥጋ ያመጡለት ነበር፤ እሱም ከጅረቱ ይጠጣ ነበር። 7  ሆኖም በምድሪቱ ላይ ዝናብ ስላልዘነበ ከተወሰኑ ቀናት በኋላ ጅረቱ ደረቀ። 8  ከዚያም የይሖዋ ቃል እንዲህ ሲል ወደ እሱ መጣ፦ 9  “ተነስተህ በሲዶና ወደምትገኘው ወደ ሰራፕታ ሂድ፤ እዚያም ተቀመጥ። እኔም በዚያ አንዲት መበለት እንድትመግብህ አዛለሁ።” 10  ኤልያስም ተነስቶ ወደ ሰራፕታ ሄደ። ወደ ከተማዋ መግቢያ በደረሰም ጊዜ አንዲት መበለት ጭራሮ ስትለቅም አገኘ። መበለቲቱንም ጠርቶ “እባክሽ የምጠጣው ትንሽ ውኃ በዕቃ ስጪኝ” አላት። 11  ልታመጣለት ስትሄድም ጠራትና “እባክሽ ቁራሽ ዳቦም ይዘሽልኝ ነይ” አላት። 12  በዚህ ጊዜ እንዲህ አለችው፦ “ሕያው በሆነው አምላክህ በይሖዋ እምላለሁ፣ በማድጋው ውስጥ ካለው አንድ እፍኝ ዱቄትና በማሰሮው ውስጥ ካለው ጥቂት ዘይት በስተቀር ምንም ዳቦ የለኝም። ለእኔና ለልጄ የሆነች ነገር ለማዘጋጀት ጭራሮ እየለቀምኩ ነው። እኛም እሷን ቀምሰን እንሞታለን።” 13  ከዚያም ኤልያስ እንዲህ አላት፦ “አይዞሽ ስጋት አይግባሽ። ወደ ቤት ገብተሽ እንዳልሽው አድርጊ። ብቻ በመጀመሪያ ከዚያችው ካለችሽ ላይ ትንሽ ቂጣ ጋግረሽ አምጪልኝ። ከዚያ በኋላ ለአንቺና ለልጅሽ የሆነ ነገር ማዘጋጀት ትችያለሽ። 14  ምክንያቱም የእስራኤል አምላክ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ ‘ይሖዋ በምድሪቱ ላይ ዝናብ እስከሚያዘንብበት ዕለት ድረስ ከማድጋው ዱቄት አይጠፋም፤ ከማሰሮውም ዘይት አያልቅም።’” 15  ስለሆነም ሄዳ ኤልያስ እንዳላት አደረገች፤ እሷም ሆነች እሱ እንዲሁም ቤተሰቧ ለብዙ ቀናት ሲመገቡ ቆዩ። 16  ይሖዋ በኤልያስ አማካኝነት በተናገረው ቃል መሠረት ከማድጋው ዱቄት አልጠፋም፤ ከማሰሮውም ዘይት አላለቀም። 17  ይህ ሁሉ ከሆነ በኋላ የቤቱ ባለቤት፣ ልጇ ታመመ፤ ሕመሙም እጅግ ስለጠናበት እስትንፋሱ ቀጥ አለ። 18  በዚህ ጊዜ ሴትየዋ ኤልያስን “የእውነተኛው አምላክ ሰው ሆይ፣ ምን አደረግኩህ? የመጣኸው በደሌን ልታስታውሰኝና ልጄን ልትገድል ነው?” አለችው። 19  እሱ ግን “ልጅሽን ስጪኝ” አላት። ከዚያም ልጁን ከእቅፏ ወስዶ እሱ ወዳረፈበት በሰገነቱ ላይ ወዳለው ክፍል ይዞት ወጣ፤ ልጁንም በራሱ አልጋ ላይ አስተኛው። 20  እሱም “አምላኬ ይሖዋ ሆይ፣ እኔን ያሳረፈችኝ የዚህች መበለት ልጅ እንዲሞት በማድረግ በእሷም ላይ መከራ ታመጣባታለህ?” በማለት ወደ ይሖዋ ጮኸ። 21  ከዚያም ልጁ ላይ ሦስት ጊዜ ከተዘረጋበት በኋላ “አምላኬ ይሖዋ ሆይ፣ እባክህ የዚህ ልጅ ሕይወት ይመለስለት” ብሎ ወደ ይሖዋ ጮኸ። 22  ይሖዋም የኤልያስን ልመና ሰማ፤ የልጁም ሕይወት ተመለሰለት፤ እሱም ሕያው ሆነ። 23  ከዚያም ኤልያስ ልጁን ይዞት ሰገነት ላይ ካለው ክፍል ወደ ቤት ከወረደ በኋላ ለእናቱ ሰጣት፤ ኤልያስም “ይኸው፣ ልጅሽ ሕያው ሆኗል” አላት። 24  በዚህ ጊዜ ሴትየዋ ኤልያስን “አንተ በእርግጥ የአምላክ ሰው እንደሆንክ በአንደበትህም ያለው የይሖዋ ቃል እውነት እንደሆነ አሁን አወቅኩ” አለችው።
[]
[]
[]
[]
32
18  ከተወሰነ ጊዜ በኋላም በሦስተኛው ዓመት የይሖዋ ቃል “ሂድና አክዓብ ፊት ቅረብ፤ እኔም በምድሩ ላይ ዝናብ አዘንባለሁ” ሲል ወደ ኤልያስ መጣ። 2  ስለሆነም ኤልያስ አክዓብ ፊት ለመቅረብ ሄደ፤ በዚህ ወቅት ረሃቡ በሰማርያ ክፉኛ ጸንቶ ነበር። 3  በዚህ ጊዜ አክዓብ በቤቱ ላይ አዛዥ የነበረውን አብድዩን ጠራው። (አብድዩ ይሖዋን በጣም ይፈራ ነበር፤ 4  ኤልዛቤል የይሖዋን ነቢያት እያጠፋች በነበረበት ጊዜም አብድዩ 100 ነቢያትን ወስዶ 50ውን በአንድ ዋሻ 50ውን ደግሞ በሌላ ዋሻ ውስጥ ከደበቃቸው በኋላ ምግብና ውኃ ይሰጣቸው ነበር።) 5  ከዚያም አክዓብ አብድዩን እንዲህ አለው፦ “በምድሪቱ ላይ ወደሚገኙት የውኃ ምንጮች ሁሉና ሸለቆዎች ሁሉ ሂድ። እንስሶቻችን በሙሉ እንዳያልቁ፣ ፈረሶቹንና በቅሎዎቹን በሕይወት ማቆየት የሚያስችል በቂ ሣር እናገኝ ይሆናል።” 6  በመሆኑም አቋርጠውት የሚሄዱትን ምድር ተከፋፈሉ። አክዓብ ለብቻው በአንድ በኩል፣ አብድዩም ለብቻው በሌላ በኩል ሄደ። 7  አብድዩ እየተጓዘ ሳለ ኤልያስን መንገዱ ላይ አገኘው። እሱም ወዲያውኑ ስላወቀው በግንባሩ ተደፋ፤ ከዚያም “ጌታዬ ኤልያስ ሆይ፣ በእርግጥ አንተ ነህ?” አለው። 8  ኤልያስም “አዎ፣ እኔ ነኝ። ሄደህ ለጌታህ ‘ኤልያስ እዚህ አለ’ ብለህ ንገረው” አለው። 9  እሱ ግን እንዲህ አለው፦ “እኔ አገልጋይህ እንድሞት ለአክዓብ አሳልፈህ የምትሰጠኝ ምን ኃጢአት ሠርቼ ነው? 10  ሕያው በሆነው አምላክህ በይሖዋ እምላለሁ፣ ጌታዬ አንተን ፍለጋ ሰው ያልላከበት አንድም ብሔር ሆነ መንግሥት የለም። እነሱም ‘እዚህ የለም’ ባሉት ጊዜ ያ መንግሥትም ሆነ ብሔር አንተን አለማግኘቱን በመሐላ እንዲያረጋግጥለት ያደርግ ነበር። 11  አንተ ደግሞ አሁን ‘ሄደህ ለጌታህ “ኤልያስ እዚህ አለ” ብለህ ንገረው’ ትለኛለህ። 12  ከአንተ ተለይቼ ስሄድ የይሖዋ መንፈስ ወደማላውቀው ቦታ ይወስድሃል፤ ለአክዓብ ብነግረውና ሳያገኝህ ቢቀር እንደሚገድለኝ የታወቀ ነው። ነገር ግን እኔ አገልጋይህ ከወጣትነቴ ጀምሮ ይሖዋን ስፈራ ኖሬአለሁ። 13  ኤልዛቤል የይሖዋን ነቢያት በገደለች ጊዜ ከይሖዋ ነቢያት መካከል 100ዎቹን ወስጄ ሃምሳ ሃምሳ በማድረግ ዋሻ ውስጥ እንደደበቅኳቸው እንዲሁም ምግብና ውኃ እሰጣቸው እንደነበር ጌታዬ አልሰማም? 14  አሁን ግን አንተ ‘ሄደህ ለጌታህ “ኤልያስ እዚህ አለ” ብለህ ንገረው’ ትለኛለህ። እሱም በእርግጠኝነት ይገድለኛል።” 15  ሆኖም ኤልያስ “በማገለግለው ሕያው በሆነው በሠራዊት ጌታ በይሖዋ እምላለሁ፣ ዛሬ እሱ ፊት እቀርባለሁ” አለ። 16  ስለዚህ አብድዩ ወደ አክዓብ ሄዶ ነገረው፤ አክዓብም ኤልያስን ለማግኘት ሄደ። 17  አክዓብም ልክ ኤልያስን ሲያየው “በእስራኤል ላይ ከፍተኛ ችግር የምትፈጥረው አንተ ነህ?” አለው። 18  በዚህ ጊዜ ኤልያስ እንዲህ አለው፦ “የይሖዋን ትእዛዛት በመተውና ባአልን በመከተል በእስራኤል ላይ ችግር የምትፈጥሩት አንተና የአባትህ ቤት እንጂ እኔ አይደለሁም። 19  ይልቅስ አሁን እስራኤላውያንን በሙሉ፣ ከኤልዛቤል ማዕድ ከሚበሉት 450 የባአል ነቢያትና 400 የማምለኪያ ግንድ ነቢያት ጋር በቀርሜሎስ ተራራ ላይ ሰብስብልኝ።” 20  በመሆኑም አክዓብ ወደ እስራኤል ሰዎች ሁሉ መልእክት ላከ፤ ነቢያቱንም በቀርሜሎስ ተራራ ላይ ሰበሰበ። 21  ከዚያም ኤልያስ ወደ ሕዝቡ ሁሉ ቀርቦ “በሁለት ሐሳብ የምታነክሱት እስከ መቼ ነው? እውነተኛው አምላክ፣ ይሖዋ ከሆነ እሱን ተከተሉ፤ ባአል ከሆነ ደግሞ እሱን ተከተሉ!” አላቸው። ሕዝቡ ግን አንዲት ቃል አልመለሰለትም። 22  ከዚያም ኤልያስ እንዲህ አላቸው፦ “ከይሖዋ ነቢያት መካከል የቀረሁት እኔ ብቻ ነኝ፤ የባአል ነቢያት ግን 450 ናቸው። 23  እንግዲህ አሁን ሁለት ወይፈኖች ይስጡን፤ እነሱም አንድ ወይፈን መርጠው በየብልቱ እየቆራረጡ በእንጨቱ ላይ ያድርጉት፤ ሆኖም እሳት አያንድዱበት። እኔ ደግሞ ሌላኛውን ወይፈን አዘጋጅቼ በእንጨቱ ላይ አደርገዋለሁ፤ ሆኖም እሳት አላነድበትም። 24  ከዚያም እናንተ የአምላካችሁን ስም ትጠራላችሁ፤ እኔም የይሖዋን ስም እጠራለሁ። እሳት በመላክ መልስ የሚሰጠው አምላክ እሱ እውነተኛው አምላክ እንደሆነ ያሳያል።” በዚህ ጊዜ ሕዝቡ ሁሉ “ያልከው ነገር ጥሩ ነው” አሉ። 25  ኤልያስም የባአል ነቢያትን “እናንተ ብዙ ስለሆናችሁ በቅድሚያ አንድ ወይፈን መርጣችሁ አዘጋጁ። ከዚያም የአምላካችሁን ስም ጥሩ፤ ሆኖም እሳት አታንድዱበት” አላቸው። 26  በመሆኑም የተሰጣቸውን ወይፈን ወስደው አዘጋጁ፤ ከጠዋት አንስቶ እስከ እኩለ ቀን ድረስም “ባአል ሆይ፣ መልስልን!” እያሉ የባአልን ስም ጠሩ። ሆኖም ድምፅ የለም፤ የሚመልስም አልነበረም። በሠሩትም መሠዊያ ዙሪያ እያነከሱ ዞሩ። 27  እኩለ ቀን ገደማም ኤልያስ እንዲህ በማለት ያፌዝባቸው ጀመር፦ “ድምፃችሁን ከፍ አድርጋችሁ ጩኹ እንጂ! አምላክ እኮ ነው! ምናልባት በሐሳብ ተውጦ ይሆናል፤ ወይም ሊጸዳዳ ሄዶ ይሆናል። አሊያም ደግሞ ተኝቶ ሊሆን ስለሚችል የሚቀሰቅሰው ያስፈልገው ይሆናል!” 28  እነሱም ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ይጮኹ እንደ ልማዳቸውም ደም በደም እስኪሆኑ ድረስ ሰውነታቸውን በጩቤና በጦር ይተለትሉ ነበር። 29  እኩለ ቀን አልፎ የእህል መባ እስከሚቀርብበትም ጊዜ ድረስ እንደ እብድ ሲያደርጋቸው ቆየ፤ ሆኖም ምንም ድምፅ የለም፤ የሚመልስም የለም፤ ትኩረት የሰጠም አልነበረም። 30  በኋላም ኤልያስ ሕዝቡን ሁሉ “ወደ እኔ ቅረቡ” አላቸው። ሕዝቡም ሁሉ ወደ እሱ ቀረቡ። ከዚያም ፈርሶ የነበረውን የይሖዋን መሠዊያ ጠገነ። 31  በመቀጠልም ኤልያስ “ስምህ እስራኤል ይባላል” የሚል የይሖዋ ቃል በመጣለት በያዕቆብ ወንዶች ልጆች ነገዶች ቁጥር ልክ 12 ድንጋዮችን ወሰደ። 32  በድንጋዮቹም በይሖዋ ስም መሠዊያ ሠራ። በመሠዊያውም ዙሪያ ሁለት የሲህ መስፈሪያ ዘር ሊያዘራ የሚችል ስፋት ያለው ቦይ ቆፈረ። 33  ከዚያም እንጨቶቹን ረበረበ፤ ወይፈኑንም በየብልቱ ቆራርጦ በእንጨቶቹ ላይ አደረገ። ቀጥሎም “በአራት ጋኖች ውኃ ሞልታችሁ በሚቃጠለው መባና በእንጨቱ ላይ አፍስሱ” አለ። 34  ከዚያም “አሁንም ድገሙ” አለ። እነሱም ደገሙ። “ለሦስተኛ ጊዜ ድገሙ” አላቸው። እነሱም ለሦስተኛ ጊዜ ደገሙ። 35  ውኃውም መሠዊያውን ዙሪያውን አጥለቀለቀው፤ ቦዩንም በውኃ ሞላው። 36  ነቢዩ ኤልያስም የምሽቱ የእህል መባ በሚቀርብበት ጊዜ ገደማ ወደ ፊት ቀረብ ብሎ እንዲህ አለ፦ “የአብርሃም፣ የይስሐቅና የእስራኤል አምላክ ይሖዋ ሆይ፣ አንተ በእስራኤል ውስጥ አምላክ እንደሆንክ፣ እኔም አገልጋይህ እንደሆንኩና እነዚህን ሁሉ ነገሮች ያደረግኩት በአንተ ቃል እንደሆነ ዛሬ ይታወቅ። 37  ይሖዋ ሆይ፣ መልስልኝ! እነዚህ ሰዎች አንተ ይሖዋ እውነተኛው አምላክ እንደሆንክና ልባቸውን ወደ አንተ እየመለስክ መሆንህን እንዲያውቁ መልስልኝ።” 38  በዚህ ጊዜ የይሖዋ እሳት ወርዶ የሚቃጠለውን መባ፣ እንጨቱን፣ ድንጋዮቹንና አፈሩን በላ፤ በቦዩ ውስጥ የነበረውንም ውኃ ላሰ። 39  ሕዝቡ ሁሉ ይህን ሲያዩ ወዲያውኑ በግንባራቸው ተደፉ፤ ከዚያም “እውነተኛው አምላክ ይሖዋ ነው! እውነተኛው አምላክ ይሖዋ ነው!” አሉ። 40  በዚህ ጊዜ ኤልያስ “የባአልን ነቢያት ያዟቸው! አንዳቸውም እንዳያመልጡ!” አላቸው። እነሱም ወዲያውኑ ያዟቸው፤ ኤልያስም ወደ ቂሾን ጅረት ይዟቸው በመውረድ በዚያ አረዳቸው። 41  ኤልያስም አክዓብን “የከባድ ዝናብ ድምፅ እያጉረመረመ ስለሆነ ሂድ ብላ፤ ጠጣም” አለው። 42  በመሆኑም አክዓብ ሊበላና ሊጠጣ ሲወጣ ኤልያስ ደግሞ ወደ ቀርሜሎስ አናት ወጣ፤ ፊቱንም በጉልበቶቹ መካከል አድርጎ ወደ መሬት አቀረቀረ። 43  ከዚያም አገልጋዩን “እባክህ ውጣና ወደ ባሕሩ አቅጣጫ ተመልከት” አለው። እሱም ወጥቶ ተመለከተና “ኧረ ምንም የለም” አለ። ኤልያስም ሰባት ጊዜ “ተመልሰህ ሂድ” አለው። 44  በሰባተኛውም ጊዜ አገልጋዩ “እነሆ! የሰው እጅ የምታክል ትንሽ ደመና ከባሕሩ እየወጣች ነው” አለ። ኤልያስም “ሄደህ አክዓብን ‘ሠረገላህን አዘጋጅ! ዝናቡ እንዳያግድህ ወደዚያ ውረድ!’ በለው” አለው። 45  በዚህ ጊዜ ሰማዩ በደመና ጠቆረ፤ ነፋስም ነፈሰ፤ ከባድ ዝናብም ይጥል ጀመር፤ አክዓብም እየጋለበ ወደ ኢይዝራኤል ሄደ። 46  ሆኖም የይሖዋ እጅ በኤልያስ ላይ መጣ፤ እሱም ልብሱን ጠቅልሎ መቀነቱ ውስጥ በመሸጎጥ ከአክዓብ ፊት ፊት እየሮጠ እስከ ኢይዝራኤል ድረስ ሄደ።
[]
[]
[]
[]
33
19  ከዚያም አክዓብ ኤልያስ ያደረገውን ሁሉና ነቢያቱን በሙሉ እንዴት በሰይፍ እንደገደለ ለኤልዛቤል ነገራት። 2  በዚህ ጊዜ ኤልዛቤል “ነገ በዚህ ሰዓት ከእነሱ እንደ አንዱ ሳላደርግህ ብቀር አማልክት እንዲህ ያድርጉብኝ፤ ከዚህ የባሰም ያምጡብኝ!” ብሎ ለኤልያስ እንዲነግረው መልእክተኛ ላከችበት። 3  በዚህ ጊዜ ኤልያስ ፈራ፤ በመሆኑም ሕይወቱን ለማትረፍ ሸሸ። በይሁዳ ወደምትገኘው ወደ ቤርሳቤህም መጣ፤ አገልጋዩንም እዚያ ተወው። 4  ከዚያም በምድረ በዳው የአንድ ቀን መንገድ ከተጓዘ በኋላ ወደ አንድ የክትክታ ዛፍ ሲደርስ ሥሩ ተቀመጠ፤ እንዲሞትም መለመን ጀመረ። እንዲህም አለ፦ “አሁንስ በቅቶኛል! ይሖዋ ሆይ፣ እኔ ከአባቶቼ አልበልጥምና ሕይወቴን ውሰዳት።” 5  ከዚያም በክትክታው ዛፍ ሥር ጋደም አለ፤ እንቅልፍም ወሰደው። ሆኖም ድንገት አንድ መልአክ ነካ አደረገውና “ተነስና ብላ” አለው። 6  እሱም ቀና ብሎ ሲመለከት ራስጌው አጠገብ በጋሉ ድንጋዮች ላይ የተቀመጠ ዳቦ እንዲሁም በውኃ መያዣ ዕቃ ውስጥ ያለ ውኃ አየ። እሱም ከበላና ከጠጣ በኋላ ተመልሶ ተኛ። 7  በኋላም የይሖዋ መልአክ ለሁለተኛ ጊዜ መጥቶ ነካ አደረገውና “ሩቅ መንገድ ስለምትጓዝ ተነስና ብላ” አለው። 8  ስለሆነም ተነስቶ በላ፤ ጠጣም፤ ከምግቡም ባገኘው ብርታት እስከ እውነተኛው አምላክ ተራራ እስከ ኮሬብ ድረስ ለ40 ቀንና ለ40 ሌሊት ተጓዘ። 9  እዚያም ሲደርስ ወደ አንድ ዋሻ ገብቶ አደረ፤ በዚህ ጊዜ የይሖዋ ቃል ወደ እሱ መጥቶ “ኤልያስ እዚህ ምን ታደርጋለህ?” አለው። 10  እሱም እንዲህ አለ፦ “እኔ ለሠራዊት ጌታ ለይሖዋ እጅግ ቀንቻለሁ፤ ምክንያቱም የእስራኤል ሰዎች ቃል ኪዳንህን ትተዋል፤ መሠዊያዎችህንም አፈራርሰዋል፤ ነቢያትህን በሰይፍ ገድለዋል፤ እንግዲህ የቀረሁት እኔ ብቻ ነኝ። ይኸው አሁን ደግሞ የእኔንም ሕይወት ለማጥፋት እየፈለጉ ነው።” 11  እሱ ግን “ውጣና ተራራው ላይ ይሖዋ ፊት ቁም” አለው። በዚህ ጊዜ ይሖዋ እያለፈ ነበር፤ ታላቅና ኃይለኛ ነፋስም በይሖዋ ፊት ተራሮቹን ሰነጣጠቀ፤ ዓለቶቹንም ፈረካከሰ፤ ይሖዋ ግን በነፋሱ ውስጥ አልነበረም። ከነፋሱ ቀጥሎ ደግሞ የምድር መናወጥ ተከሰተ፤ ይሖዋ ግን በምድር መናወጡ ውስጥ አልነበረም። 12  ከምድር መናወጡ በኋላም እሳት መጣ፤ ይሖዋ ግን በእሳቱ ውስጥ አልነበረም። ከእሳቱ በኋላ ደግሞ ዝግ ያለና ለስለስ ያለ ድምፅ ተሰማ። 13  ኤልያስ ይህን ድምፅ ሲሰማ ወዲያውኑ በለበሰው የነቢይ ልብስ ፊቱን ሸፈነ፤ ወጥቶም ዋሻው ደጃፍ ላይ ቆመ። ከዚያም አንድ ድምፅ “ኤልያስ እዚህ ምን ታደርጋለህ?” ሲል ጠየቀው። 14  እሱም እንዲህ አለ፦ “እኔ ለሠራዊት ጌታ ለይሖዋ እጅግ ቀንቻለሁ፤ ምክንያቱም የእስራኤል ሰዎች ቃል ኪዳንህን ትተዋል፤ መሠዊያዎችህንም አፈራርሰዋል፤ ነቢያትህን በሰይፍ ገድለዋል፤ እንግዲህ የቀረሁት እኔ ብቻ ነኝ። ይኸው አሁን ደግሞ የእኔንም ሕይወት ለማጥፋት እየፈለጉ ነው።” 15  ይሖዋም እንዲህ አለው፦ “ወደ ደማስቆ ምድረ በዳ ተመልሰህ ሂድ። እዚያም ስትደርስ ሃዛኤልን በሶርያ ላይ ንጉሥ አድርገህ ቀባው። 16  እንዲሁም የኒምሺን የልጅ ልጅ ኢዩን በእስራኤል ላይ ንጉሥ አድርገህ ቀባው፤ የአቤልምሆላ ሰው የሆነውን የሻፋጥን ልጅ ኤልሳዕን ደግሞ በአንተ ምትክ ነቢይ አድርገህ ቀባው። 17  ከሃዛኤል ሰይፍ ያመለጠውን ኢዩ ይገድለዋል፤ ከኢዩ ሰይፍ ያመለጠውን ደግሞ ኤልሳዕ ይገድለዋል። 18  እኔም ለባአል ያልተንበረከኩና እሱን ያልሳሙ በእስራኤል ውስጥ የቀሩ 7,000 ሰዎች አሉኝ።” 19  ኤልያስም ከዚያ ወጥቶ ሄደ፤ የሻፋጥንም ልጅ ኤልሳዕን ከፊቱ 12 ጥማድ በሬዎች እያረሱ፣ እሱም በ12ኛው ጥማድ በሬ እያረሰ አገኘው። ኤልያስም ወደ እሱ በመሄድ የራሱን የነቢይ ልብስ አውልቆ ላዩ ላይ ጣል አደረገበት። 20  በዚህ ጊዜ ኤልሳዕ በሬዎቹን እዚያው በመተው ኤልያስን ተከትሎ እየሮጠ “እባክህ፣ አባቴንና እናቴን ስሜ እንድመጣ ፍቀድልኝ። ከዚያ በኋላ እከተልሃለሁ” አለው። እሱም “ሂድ ተመለስ፤ እኔ መቼ ከለከልኩህ?” አለው። 21  በመሆኑም ተመለሰ፤ ከዚያም አንድ ጥማድ በሬ ወስዶ መሥዋዕት አደረገ፤ በእርሻ መሣሪያዎቹም የበሬዎቹን ሥጋ በመቀቀል ለሕዝቡ ሰጠ፤ እነሱም በሉ። ይህን ካደረገ በኋላም ተነስቶ ኤልያስን ተከተለው፤ እሱንም ያገለግለው ጀመር።
[]
[]
[]
[]
34
2  ዳዊት የሚሞትበት ቀን ሲቃረብ ልጁን ሰለሞንን እንዲህ ሲል አዘዘው፦ 2  “እንግዲህ እኔ የምሞትበት ጊዜ ቀርቧል። ስለሆነም በርታ፤ ወንድ ሁን። 3  በሙሴ ሕግ ላይ በተጻፈው መሠረት በመንገዶቹ በመሄድ እንዲሁም ደንቦቹን፣ ትእዛዛቱን፣ ፍርዶቹንና ማሳሰቢያዎቹን በመጠበቅ ለአምላክህ ለይሖዋ ያለብህን ግዴታ ፈጽም፤ ይህን ካደረግክ የምታከናውነው ሁሉ ይሳካልሃል፤ በምትሄድበትም ሁሉ ይቃናልሃል። 4  ይሖዋም እንዲህ በማለት የገባልኝን ቃል ይፈጽማል፦ ‘ልጆችህ፣ በሙሉ ልባቸውና በሙሉ ነፍሳቸው በፊቴ በታማኝነት በመመላለስ መንገዳቸውን ከጠበቁ ከዘር ሐረግህ በእስራኤል ዙፋን ላይ የሚቀመጥ ሰው አይታጣም።’ 5  “የጽሩያ ልጅ ኢዮዓብ በእኔ ላይ ያደረገውን ነገር ይኸውም በሁለቱ የእስራኤል ሠራዊት አለቆች ማለትም በኔር ልጅ በአበኔርና በየቴር ልጅ በአሜሳይ ላይ ያደረገውን በሚገባ ታውቃለህ። ይህ ሰው እነዚህን ሰዎች በመግደል ጦርነት ሳይኖር በሰላሙ ጊዜ ደም አፍስሷል፤ እንዲሁም በወገቡ ላይ የታጠቀው ቀበቶና በእግሩ ላይ ያደረገው ጫማ በጦርነት ጊዜ በሚፈሰው ደም እንዲበከል አድርጓል። 6  እንግዲህ እንደ ጥበብህ አድርግ፤ ሽበቱ በሰላም ወደ መቃብር እንዲወርድ አታድርግ። 7  “ሆኖም ለቤርዜሊ ልጆች ታማኝ ፍቅር አሳያቸው፤ እነሱም ከማዕድህ ከሚበሉ ሰዎች መካከል ይሁኑ፤ ምክንያቱም ከወንድምህ ከአቢሴሎም ፊት በሸሸሁ ጊዜ እነሱም ከጎኔ ቆመው ነበር። 8  “በተጨማሪም ከባሁሪም የመጣው ቢንያማዊው የጌራ ልጅ ሺምአይ አብሮህ አለ። ወደ ማሃናይም በሄድኩበት ዕለት ከባድ እርግማን የረገመኝ እሱ ነው፤ ሆኖም እኔን ለማግኘት ወደ ዮርዳኖስ በወረደ ጊዜ ‘በሰይፍ አልገድልህም’ ብዬ በይሖዋ ማልኩለት። 9  አንተ ጥበበኛ ስለሆንክና በእሱ ላይ ምን ማድረግ እንዳለብህ ስለምታውቅ ሳትቀጣ አትተወው፤ ሽበቱ በደም ወደ መቃብር እንዲወርድ አድርግ።” 10  ከዚያም ዳዊት ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ በዳዊት ከተማም ተቀበረ። 11  ዳዊት በእስራኤል ላይ ንጉሥ ሆኖ የገዛው ለ40 ዓመት ነበር። በኬብሮን ለ7 ዓመት፣ በኢየሩሳሌም ደግሞ ለ33 ዓመት ነገሠ። 12  ከዚያም ሰለሞን በአባቱ በዳዊት ዙፋን ላይ ተቀመጠ፤ ቀስ በቀስም ንግሥናው እየጸና ሄደ። 13  ከጊዜ በኋላም የሃጊት ልጅ አዶንያስ ወደ ሰለሞን እናት ወደ ቤርሳቤህ መጣ። እሷም “የመጣኸው በሰላም ነው?” አለችው፤ እሱም “አዎ፣ በሰላም ነው” አላት። 14  ከዚያም “አንድ የምነግርሽ ጉዳይ አለኝ” አላት። እሷም “እሺ፣ ንገረኝ” አለችው። 15  እሱም እንዲህ አላት፦ “ንግሥናው የእኔ ሊሆን እንደነበረና እስራኤልም ሁሉ ይነግሣል ብለው ይጠብቁ እንደነበር በሚገባ ታውቂያለሽ፤ ይሁንና ንግሥናው የእኔ መሆኑ ቀርቶ የወንድሜ ሆነ፤ ምክንያቱም ይሖዋ ንግሥናው የእሱ እንዲሆን ወስኖ ነበር። 16  ሆኖም አሁን አንድ የምጠይቅሽ ነገር አለ። መቼም አታሳፍሪኝም።” እሷም “እሺ ንገረኝ” አለችው። 17  እሱም “እባክሽ፣ ንጉሥ ሰለሞን የጠየቅሽውን እንቢ ስለማይልሽ ሹነማዊቷን አቢሻግን እንዲድርልኝ ጠይቂው” አላት። 18  በዚህ ጊዜ ቤርሳቤህ “መልካም! ንጉሡን አነጋግርልሃለሁ” አለችው። 19  በመሆኑም ቤርሳቤህ የአዶንያስን ጉዳይ ልትነግረው ወደ ንጉሥ ሰለሞን ገባች። ንጉሡም ወዲያውኑ ሊቀበላት ተነሳ፤ ሰገደላትም። ከዚያም ዙፋኑ ላይ ተቀመጠ፤ የንጉሡም እናት በቀኙ እንድትቀመጥ ዙፋን አስመጣላት። 20  እሷም “አንዲት ትንሽ ነገር ልጠይቅህ አስቤ ነበር። መቼም እንቢ አትለኝም” አለችው። ንጉሡም “እናቴ ሆይ፣ ንገሪኝ፤ የጠየቅሽኝን እንቢ አልልሽም” አላት። 21  እሷም “ሹነማዊቷ አቢሻግ ለወንድምህ ለአዶንያስ ትዳርለት” አለችው። 22  በዚህ ጊዜ ንጉሥ ሰለሞን ለእናቱ እንዲህ ሲል መለሰላት፦ “ለአዶንያስ ሹነማዊቷን አቢሻግን ብቻ ለምን ትጠይቂለታለሽ? ታላቅ ወንድሜ ስለሆነ ንግሥናም ጠይቂለት እንጂ፤ ካህኑ አብያታርና የጽሩያ ልጅ ኢዮዓብም እየደገፉት ነው።” 23  ከዚያም ንጉሥ ሰለሞን እንዲህ ሲል በይሖዋ ማለ፦ “አዶንያስ ይህን በመጠየቁ ሕይወቱን ሳያጣ ቢቀር አምላክ ይህን ያድርግብኝ፤ ከዚህ የከፋም ነገር ያምጣብኝ። 24  አሁንም በሚገባ ባጸናኝ፣ በአባቴ በዳዊት ዙፋን ላይ ባስቀመጠኝና በገባው ቃል መሠረት ቤት በሠራልኝ ሕያው በሆነው በይሖዋ እምላለሁ፣ አዶንያስ በዛሬዋ ዕለት ይገደላል።” 25  ንጉሥ ሰለሞንም ወዲያውኑ የዮዳሄን ልጅ በናያህን ላከው፤ እሱም ወጥቶ አዶንያስን መታው፤ እሱም ሞተ። 26  ንጉሡም ካህኑን አብያታርን እንዲህ አለው፦ “በአናቶት ወደሚገኘው እርሻህ ሂድ! አንተ ሞት የሚገባህ ሰው ነህ፤ ሆኖም በአባቴ በዳዊት ፊት የሉዓላዊውን ጌታ የይሖዋን ታቦት ስለተሸከምክና በአባቴ ላይ የደረሰውን መከራ ሁሉ ስለተጋራህ ዛሬ አልገድልህም።” 27  በመሆኑም ይሖዋ በሴሎ፣ በኤሊ ቤት ላይ እንደሚደርስ የተናገረው ነገር ይፈጸም ዘንድ ሰለሞን አብያታርን የይሖዋ ካህን ሆኖ እንዳያገለግል አባረረው። 28  ኢዮዓብ ቀደም ሲል ከአቢሴሎምጋር ወግኖ ያልነበረ ቢሆንም አዶንያስን ደግፎ ስለነበር ይህን ወሬ ሲሰማ ወደ ይሖዋ ድንኳን በመሸሽ የመሠዊያውን ቀንዶች ያዘ። 29  ከዚያም ንጉሥ ሰለሞን “ኢዮዓብ ወደ ይሖዋ ድንኳን ሸሽቶ እዚያ በመሠዊያው አጠገብ ይገኛል” ተብሎ ተነገረው። በመሆኑም ሰለሞን የዮዳሄን ልጅ በናያህን “ሂድና ግደለው!” ብሎ ላከው። 30  ስለዚህ በናያህ ወደ ይሖዋ ድንኳን ሄዶ ኢዮዓብን “ንጉሡ ‘ና ውጣ!’ ብሎሃል” አለው። እሱ ግን “እዚሁ እሞታታለሁ እንጂ በፍጹም አልወጣም!” አለ። በዚህ ጊዜ በናያህ “ኢዮዓብ እንዲህ እንዲህ ብሏል፤ እንዲህም ሲል መልሶልኛል” በማለት ለንጉሡ ተናገረ። 31  ከዚያም ንጉሡ እንዲህ አለው፦ “በል ልክ እንዳለው አድርግ፤ ግደለውና ቅበረው፤ ኢዮዓብ አላግባብ ካፈሰሰውም ደም እኔንና የአባቴን ቤት አንጻ። 32  ኢዮዓብ አባቴ ዳዊት ሳያውቅ ከእሱ ይልቅ ጻድቅና የተሻሉ የነበሩትን ሁለት ሰዎች ማለትም የእስራኤል ሠራዊት አለቃ የነበረውን የኔርን ልጅ አበኔርንና የይሁዳ ሠራዊት አለቃ የነበረውን የየቴርን ልጅ አሜሳይን በሰይፍ መትቶ በመግደሉ ይሖዋ ደሙን በራሱ ላይ ይመልስበታል። 33  ደማቸውም ለዘላለም በኢዮዓብ ራስና በዘሮቹ ራስ ላይ ይሆናል፤ በዳዊት፣ በዘሮቹ፣ በቤቱና በዙፋኑ ላይ ግን የይሖዋ ሰላም ለዘላለም ይሁን።” 34  ከዚያም የዮዳሄ ልጅ በናያህ ወጥቶ ኢዮዓብን መትቶ ገደለው፤ እሱም በምድረ በዳ በሚገኘው በራሱ ቤት ተቀበረ። 35  ከዚያም ንጉሡ በኢዮዓብ ምትክ የዮዳሄን ልጅ በናያህን በሠራዊቱ ላይ ሾመው፤ በአብያታር ቦታ ደግሞ ካህኑን ሳዶቅን ሾመው። 36  ንጉሡም ሺምአይን አስጠርቶ እንዲህ አለው፦ “ኢየሩሳሌም ውስጥ ቤት ሠርተህ በዚያ ኑር፤ ከዚያም ወጥተህ ወደ ሌላ ቦታ አትሂድ። 37  ከዚያ ወጥተህ የቄድሮንን ሸለቆ የተሻገርክ ቀን ግን እንደምትሞት እወቅ። ደምህ በራስህ ላይ ይሆናል።” 38  ሺምአይም ንጉሡን “ጥሩ ሐሳብ ነው። አገልጋይህ፣ ጌታዬ ንጉሡ እንዳለው ያደርጋል” አለው። ስለሆነም ሺምአይ በኢየሩሳሌም ለብዙ ጊዜ ተቀመጠ። 39  ሆኖም ከሦስት ዓመት በኋላ ከሺምአይ ባሪያዎች መካከል ሁለቱ የጌት ንጉሥ ወደሆነው ወደ ማአካ ልጅ ወደ አንኩስ ኮበለሉ። ሺምአይም “ባሪያዎችህ ያሉት ጌት ነው” ተብሎ ሲነገረው 40  ወዲያውኑ አህያውን ጭኖ ባሪያዎቹን ለመፈለግ በጌት ወዳለው ወደ አንኩስ አቀና። ሺምአይ ባሪያዎቹን ይዞ ከጌት ሲመለስ 41  ለሰለሞን “ሺምአይ ከኢየሩሳሌም ወጥቶ ወደ ጌት ሄዶ ነበር፤ አሁን ግን ተመልሷል” ተብሎ ተነገረው። 42  በዚህ ጊዜ ንጉሡ ሺምአይን አስጠርቶ እንዲህ አለው፦ “‘ከዚህ ወጥተህ ወደ ሌላ ቦታ በሄድክ ቀን እንደምትሞት እወቅ’ ብዬ በይሖዋ አስምዬህና አስጠንቅቄህ አልነበረም? አንተስ ብትሆን ‘ጥሩ ሐሳብ ነው፤ እንዳልከኝ አደርጋለሁ’ ብለኸኝ አልነበረም? 43  ታዲያ በይሖዋ ፊት የገባኸውን መሐላና የሰጠሁህን ትእዛዝ ያልጠበቅከው ለምንድን ነው?” 44  ከዚያም ንጉሡ፣ ሺምአይን እንዲህ አለው፦ “በአባቴ በዳዊት ላይ ያደረግከውን ክፉ ነገር ሁሉ ልብህ ያውቀዋል፤ ይሖዋም ያደረግከውን ክፉ ነገር በራስህ ላይ ይመልስብሃል። 45  ንጉሥ ሰለሞን ግን ይባረካል፤ የዳዊትም ዙፋን በይሖዋ ፊት ለዘላለም ይጸናል።” 46  ከዚያም ንጉሡ የዮዳሄን ልጅ በናያህን አዘዘው፤ እሱም ወጥቶ ሺምአይን መትቶ ገደለው። በዚህ መንገድ መንግሥቱ በሰለሞን እጅ ጸና።
[]
[]
[]
[]
End of preview. Expand in Data Studio

Original Dataset and Paper

Original dataset: https://www.irit.fr/AmharicResources/airtc-the-amharic-adhoc-information-retrieval-test-collection/

Evaluation is highly important for designing, developing, and maintaining information retrieval (IR) systems. The IR community has developed shared tasks where evaluation framework, evaluation measures and test collections have been developed for different languages. Although Amharic is the official language of Ethiopia currently having an estimated population of over 110 million, it is one of the under-resourced languages and there is no Amharic adhoc IR test collection to date. In this paper, we promote the monolingual Amharic IR test collection that we build for the IR community. Following the framework of Cranfield project and TREC, the collection that we named 2AIRTC consists of 12,583 documents, 240 topics and the corresponding relevance judgments.

@inproceedings{yeshambel20202airtc,
  title={2AIRTC: The Amharic Adhoc Information Retrieval Test Collection},
  author={Yeshambel, Tilahun and Mothe, Josiane and Assabie, Yaregal},
  booktitle={International Conference of the Cross-Language Evaluation Forum for European Languages},
  pages={55--66},
  year={2020},
  organization={Springer}
}
Downloads last month
6